You are on page 1of 56

[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር

በ ዘይነብ ሐሰን

1 | ገገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

“የፍልስጤማዊያን የውጊያ መሣርያ… ”

የተቀደሰው የፍልስጤም
ምድር

(የፍልስጤም ሕዝብ ፍትሐዊ ጦርነት


አጭር መግለጫ)

-በ ዘይነብ ሐሰን

2 | ገገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ማውጫ
መግቢያ ገጽ
ምዕራፍ አንድ
አራዲል ሙቀደሣ

የፍልስጤማውያን አመጣጥ 1
አልቁድስ ሙስሊማዊት ከተማ 2
የቁድስ ሐረምነት በቁርአንና በሐዲስ 4
በይተል-መቅዲስ የእስላም ምሽግ 9

ምዕራፍ ሁለት
አልቁድስ/ኢየሩሣሌም

መዲነቱል ቁድስ 11
አል-ሐራም አሸ-ሸሪፍ 12
መስጂደል አቅሷ 12
የመስጂደል አቅሷ ደረጃ በኢስላም 13
የተባረከው የፍልስጤም ምድር 14
የቁድስ ሙስሊማዊት አገር መሆን 17
ዑመራዊ ቃል-ኪዳን 18
የአይሁድ የኃይል እርምጃ 18
በመስጂዱ ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶች 19
የሠላም ቃል-ኪዳን 21
ድሉ የሙስሊሞች ነው 21

3 | ገገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ሻአላሁ ተአላ 22
ምዕራፍ -ሦስት
ዝክረ- ታሪክ

ቅድመ-ኑብዋ 23
ድህረ-ኑብዋ 24
ኢንቲሳር(የፍልስጤሟ ሙሽራ) 29
ፍልስጤም 33

እስከ መቼ ድረስ
ፒስ ፕሮሰስ
ይሉናል ፒስ ፕሮሰስ
ከበስተጀርባው ረሳስ
ሕዝቡን ለመጨረስና መሬቱን ለመውረስ

4 | ገገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

መግቢያ
የተቀደሠው የፍልስጤም ምድር መቼም ቢሆን የአይሁድ ይዞታ ሆኖ አያውቅም፡፡
ለዚሁ አንድ ማስረጃ “ለአይሁድ የተለየ አገር ቤት /separate homeland” የመፍጠሩ ሀሳብ
ሲንሸራሸር በነበረበት ወቅት ከፍልስጤም ውጭ ሌላም ቦታ ታስቦ የነበረ መሆኑ ነው፡፡ ዛሬ
ምዕራባውያን የተቀረውን ዓለም ለማደናገር እንደሚሞክሩት የፍልስጤም ምድር ከድሮም
የአይሁድ የነበረ ቢሆን ኖሮ፤ ለነሱ አገር ቤት በመፍጠሩ ሀሣብ ውስጥ እንደ አርጀንቲናና
ዑጋንዳ የመሳሰሉትን ሀገራት ማካተቱ ባላስፈለገም ነበር፡፡
ይሁንና ለ‘አይሁድ የብቻ አገር ቤት’ የመፍጠሩ ሀሣብ የአውሮፓውያንን ይሁንታ
አግኝቶ በዋናነት ፍልስጤም ተመረጠች፡፡ ዓላማውን እውን የማድረጉ እንቅስቃሴም ተጀመረ፡
፡ ጊዜው በ 8ተኛው መቶ ሂጅሪያ1 ማብቂያ ላይ ነበር፡፡ የምዕራብ ኃይላት የዑስማንያ ቱርክ
ኢስላማዊ መንግሥትን ለመጣል የተጠናከረ ርብርቦሽ እያደረጉበት የነበረ ወቅት ነው፤ ይህንኑ
አጋጣሚ በመጠቀምና ገጸ በረከትም በመያዝ አንድ ከማኅበረ-አይሁድ የተውጣጣ የልዑካን
ቡድን በአውሮፓውያን ድጋፍ ሰጪነት ወደ ወቅቱ የዑስማንያ ኻሊፋት ሡልጣን ዐብዱል
ሐሚድ አመራ፡፡ አይሁዳውያን ፍልስጤም ውስጥ መሥፈር እንዲችሉና የመግቢያ ፈቃድም
እንዲሰጣቸው ተማጽኖ አቀረበ፡፡
ሡልጣን አብዱል ሐሚድ ግን በጊዜው መንግሥታቸው ላይ እየተደረገ በነበረው
አፍራሽ ግፊት ሳይበገሩ፤ በቀረበላቸው የከበረ ሥጦታም ሳይደለሉ የአይሁዶችን ጥያቄ ውድቅ
አደረጉት፡፡ የሁዶች አንዴ እንደምንም ብለው ፍልስጤም ውስጥ እግር መትከል ከቻሉ አገሪቱን
ከተቀረው ኢስላማዊ ዓለም በቀላሉ መነጠል ይችላሉ የሚል ስጋት ነበራቸው፡፡ ከዚህም
በመነሳት ይመስላል፤ በ1900 እና 1901 መካከል በነበረው ጊዜ ተጨማሪ ደንቦችን በማውጣት
ማንኛውም የአይሁድ ተጓዥ ከሦስት ወር በበለጠ ፍልስጤም ግዛት ውስጥ ውሎ ማደር
እንደሌለበት ይደነግጋሉ፡፡ ከዚህም ሌላ ምንም ዓይነት የመሬት ሽያጭ ለአይሁድ እንዳይደረግ
ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላለፉ፡፡
የአይሁድ ጥረት ግን በዚህ አልተገታም፡፡ ሰላሣ አምስት ሚሊዮን የወርቅ ዲናሮችን
በመቋጠር እንደገና በ1920 ወደ ሡልጣኑ ቤተ-መንግሥት አቀኑ፡፡ በጊዜው የዑስማንያ
ኢስላማዊ መንግሥት ካዝና በብዙ ወጪዎች ተራቁቶ እንደነበረም ያውቃሉ፡፡ እንደዛም ሆኖ
ግን የኢስላማዊውን መንግሥት ይሁንታ በወርቅ ሣንቲሞች ለመግዛት ያደረጉት ጥረት
በሡልጣኑ ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም፡፡ የጉዳዩ ዋና አስተባባሪ ለነበረው ለቴዎዶር ሄርዞል
በላኩት ማስታወሻ ግልጽ እንዳደረጉት፡- “… ከፍልስጤም መሬት ላይ ስንዝር መስጠት
አልችልም፡፡ ምክንያቱም የግል ንብረቴ አይደለምና፡፡ ይልቅ ባለመብቱ ሕዝቡ ነው፡፡ ሕዝቦቼ

1
. ሂጅሪያ ማለት የዐረብኛ ቃል ሲሆን የአማርኛ ትርጉሙም ‹‹ስደት›› ማለት ነው፤ ስደቱም የሚያመለክተው የነብዩ
ሙሐመድ(ሶ.ዐ.ወ) ከመካ ወደ መዲና ያደረጉትን ታሪካዊ ክስተት መሆኑ ልብይለዋል፡፡ (ይህ የግርጌ ማስታወሻ
ከታተመው ዋና መጽሐፍ የሌለ ሲሆን ለአንባቢ በማሰብ በመልሶ ተያቢ የተጨመረ መሆኑ ማስታወስ
እንወዳለን፡፡)

5 | ገገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ለዚህ መሬት ሲሉ የሕይወት መስዋትነት ከፍለውበታል፡፡ ደማቸውን አፍሰውበታል፡፡ ስለዚህ


አይሁዶች የወርቅ ዲናሮቻቸውን ለራሳቸው ያድርጉት፡፡ ምናልባት መንግሥቴ ቢፈርስ ያን ጊዜ
ፍልስጤም በቀላሉ ነጥሎ መያዝ ይቻላቸው ይሆናል፡፡ በሕይወት እያለው ግን ከሰውነቴ ላይ
በስለት ተቆርጦ ቢወሰድ ይቀለኛል -ፍልስጤም ከኢስላማዊ መንግሥት ተነጥላ ስትሄድ ከማይ፡
፡ ይህ ደሞ በጭራሽ ሊሆን የማይችል ነገር ነው፡፡” በማለት ያላቸውን ቁርጠኝነት ግልጽ
አደረጉ፡፡
እንደሚታወቀው ቴዎዶር ሄርዞል ‘የአይሁድ አገር ቤት’ ምሥረታ ቀንደኛ አቀንቃኝ
የነበረ ሲሆን፤ ሠፈራን መሠረት ያደረገ ቅኝ አገዛዝ እንዴት ሊቋቋም እንደሚችል ቀደም ሲል
ጀምሮ ከሮዲዚያና ከመሰል ሀገራት ልምድ በመውሰድ የአይሁድ አገር ቤት ምሥረታም
በተመሳሳይ መንገድ ሊከናወን እንደሚችል የጸና እምነት የነበረው ሰው ነው፡፡
ከዚህ በኋላ የሁዶችም በቀጥታ ወደ ፍልስጤም ለመግባት ያደረጉት ሙከራ
እንዳልተሳካ እየገባቸው ሲመጣ አሳቻ መንገዶችን መጠቀም ይጀምራሉ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜም
ተሳክቶላቸው ‘union & progress spciety’ በተሰኘና አባላቱ ቱርካዊ ስያሜ በመያዝ
ሙስሊም ነን በሚሉ አንድ የአይሁድ ጐሳ ድርጅት በኩል ወደ ፍልስጤም መግባት ቻሉ፡፡
ይህን ያህል መግቢያ ቀዳዳ ካገኙም በኋላ ወደ ፍልስጤም የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በድርጅቱ
አባላት በኩል የበለጠ በማጠናከር እስከ 1924 የካሊፌቱ ይፋ ውድቀት ድረስ ሲንቀሳቀሱ
ቆይተዋል፡፡
ከ1917 ጀምሮ ኢየሩሳሌም የገባውና ቁጥጥሩን የዘረጋው የእንግሊዝ ጦር
በሚሰጣቸው ከለላ አንድ አንድ እያሉ በፍልስጤም ምድር መሥፈር የቀጠሉት የሁዶችም ቀስ
በቀስ ድንበር እየገፉ አጥር ማጠራቸውን ተያያዙት፡፡ ድርጊቱ ነዋሪዎችን ዐረቦች እያስቆጣ
ሲመጣ የእንግሊዝ ጦር ከሠፋሪዎቹ በስተጀርባ በመሆን ይተኩሱባቸው ጀመር፡፡ በዚህ ዓይነት
መንገድ የአይሁድ በፍልስጤም ምድር ላይ መስፋፋት ከእንግሊዞች በኩል ያልተቆጠበ ድጋፍ
እየተደረገለትና የብረት ሽፋንም እየተሰጠው ሲቀጥል እናያለን፡፡
በምዕራባውያን በኩል ፍልስጤምን ቀኝ የማድረጉ ፍላጐትና የአይሁድ የአገር ቤት
ምሥረታ ጥያቄ አንድ ላይ የመገጣጠሙ ነገርም የራሱ ድርሻ ነበረው፡፡ ምዕራባውያን
የዑስማንያ ኢስላማዊ መንግሥትን ካሸነፉ በኋላ በሥሩ የነበረውን ሰፊ ኢስላማዊ ግዛት
ከፋፍለው ለመግዛት ከነበራቸው ፍላጐት አንፃር ፍልስጤም አንዷ ዒላማቸው ነበረች፡፡ በዚህ
ላይ ፍልስጤም በመልከዐ ምድራዊ አቀማመጧ በአፍሪካዊት ዐረባዊት ግብጽና በእስያ ዐረቦች
መሃል እንደ አገናኝ ድልድይ ናት፡፡ የእስያና የአፍሪካ ሕዝቦችም ብቸኛ የየብስ መገናኛ ናት፡፡
ስለሆነም በዚህ ጊዜና ከዚህም በኋላ ሊኖር በሚችለው የሙስሊሞች ዓለም አቀፋዊ ትብብር
ላይ ሣንካ ለመፍጠር ከመሃል ፍልስጤምን ነጥሎ የመያዙ ነገር በምዕራባውያን ዘንድ
የታሰበበት ጉዳይ ነበር፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በጊዜው የግብጽ ገዢ የነበረው ሙሐመድ ባሻ
ወደ ሻም/ቢላዱ-ሻም) ንቅናቄ ያደርጋል፡፡ የሱ ጉዞ ግብጽና ሱርያን ሊያስተባብር ይችላል የሚል
አንድምታ ነበረው፡፡ በዚህም እንግሊዞች ሀሳብ አደረባቸው፡፡

6 | ገገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ቀደም ሲል ጀምሮ ታሣቢ በነበረው መሠረት ግብጽና አገረ-ሻም በሚገናኙበት


ማዕከላዊ ግዛት ላይ የአይሁድን የሠፈራ ፕሮግራም መቀበልና ማጠናከር እንዳለባቸው በማመን
ተንቀሳቀሱ፡፡ ይህ ደሞ በሌላ ወገን ለአውሮፓ ራስ ምታት ከሆኑት የሁዶች መገላገያ ዘዴም
ነበር፡፡ እናም ፍልስጤም በእንግሊዞች እጅ ለአይሁድ ተበረከተች፡፡
መርዛሙን እሾህ ፍልስጤም ምድር ላይ በመትከልና ተንከባክቦም በማሣደግ ረገድ
አውሮፓ በተለይም እንግሊዝ በኩል ተጠያቂ ናቸው የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡ በ1907 በወቅቱ
የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚንሥቴር በሐነሪ ካምቤል የተቋቋመ ኮሚቴ ባቀረበው ሪፖርት መሠረት
ከዐረቦች በኩል የሚመጣውን አደጋ ለመከላከል በመሃከላቸው የኖረውን ታሪካዊ፤ መንፈሣዊና
ዝምድናዊ ትስስር መነሻ እያደረገ የሚፈጠረውን አንድነት መስበርና ሕብረታቸውን ማዳከም
አስፈላጊ መሆኑን ያሠምርበታል፡፡ ይህ ደሞ በተሳካ መልኩ ሊከናወን የሚችለው የክልሉን
አፍሪካዊና እስያዊ ክፍል ለሁለት በመክፈልና መሃል ላይ ለምዕራቡ ወዳጅ ለዐረቡ ጠላት የሆነ
ሰብዐዊ ጋሬጣ ማቆም ሲቻል ብቻ መሆኑን በግልጽ ያስቀምጣል፡፡ የአፍሪካና የእስያ ማዕከላዊ
ክልል ደሞ ፍልስጤም መሆኗ ግልጽ ነገር ነው፡፡ የእስያና የአፍሪካ ሙስሊሞች ታላላቅ
ጦርነቶችን እጅና ጓንት እየሆኑ ሲዋጉ የኖሩበት ምድር ቢኖር ፍልስጤም ቀዳሚዋ ተጠቃሽ
ናት፡፡ ይኸውም ፍልስጤም በእስልምና ውስጥ ካላት የላቀ ደረጃና የተከበረች ሥፍራ ከመሆኗ
የመጣ ነው፡፡ ሌላው ከሙስሊሙ ዓለም የምዕራብ በር ላይ የምትገኝ መሆኗ ነው፡፡
እናም ይህን ሥፍራ መያዙንና ከአካባቢው ሕዝብ ጋር የጐሪጥ በሚተያይ ባዕድ ኃይል
ማስጠበቁ ከሙስሊሙ ዓለም በኩል የሚመጣውን አደጋ በመከላከል ረገድ መተማመኛ
መፍጠር መሆኑን ነው የሔነሪ ካምፕቤል ኮሚቴ ዘገባ የሚያትተው፡፡ በኖቬምበር 2 1917
ይፋ የሆነው የባልፎር ሠነድ መሠረታዊ ይዘትም ይኸው ነው በፍልስጤም ምድር ላይ
የአይሁድ አገር ቤት መመሥረት-
በተለያዩ ሪፖርቶች፣ ጥናቶች፣ መግለጫዎችና አቋሞች እየተጠናከረ የመጣው
የአይሁድ አገር ቤት ምሥረታ ከተሠነደና ግልጽ ከተደረገ በኋላ ዲሴምበር 11/1917 የብሪትሽ
ጦር ሠራዊት በጄኔራል አለንቢ እየተመራ ኢየሩሳሌም ገባ፡፡ በወቅቱ ጠቅላይ ሚንሥቴር
አርተር ባልፎር የተሰየመውና Balfour decleration የተሰኘውን ፍርደ ገምድል ሠነድ በመሬት
ላይ የማዋሉ ሥራም አንድ ተባለ፡፡ ይህንኑ ተከትሎ በነዋሪው ዐረብ ኅብረተሰብና በመጪዎቹ
ሠፋሪ የሁዶች መሃል ውጥረት ነገሠ፡፡
ጽዬናውያን ዕለቱን እንደ ድል ቀን ሊያከብሩት ሲሞክሩ ከዐረቦች በኩል ደሞ
የአይሁዶችን ሤራ የሚቃወሙ ኮሚቴዎችን በማቋቋምና የአቋም መግለጫዎችን በማውጣት
የሠላማዊ ሠልፍ ጥሪ ተላለፈ፡፡ ገና ከውጥኑ የሴራው አባሪ ተባባሪ የነበሩት እንግሊዞች ከዐረብ
ፍልስጤሞች በኩል እየተቀሰቀሰ የመጣውን አመፅ ባጭሩ ለመቅጨት ሲሉ በሠላማዊ ሠልፉ
የሚገኝ እያንዳንዱ ዐረብ ተይዞ እንደሚታሰር በብሪትሽ ከፍተኛ ኮሚሽነር ሐርበርት ሰሜል
በኩል ማስጠንቀቂያ እንዲተላለፍ አደረጉ፡፡

7 | ገገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

በሜይ 1920 የእንግሊዝ መንግሥት በፍልስጤም ላይ ሙሉ ማንዴት ተሰጠው፡፡


ከማንዴቱ መታወጅ ሦስት ቀናት በኋላ የእንግሊዞች ልዩ ተልዕኮ የአይሁድ አገር ቤት ምሥረታ
መሆኑንም እራሳቸው እንግሊዞች ይፋ አወጡት፡፡ በእንግሊዝ ዘቦችና በዐረቦች መሃል
ለመጀመሪያ ጊዜ የለየለት ግጭት ተካሄደ፡፡ በኢሪያኮ ከተማ ሊካሄድ የነበረው የፍልስጤሞች
ሁለተኛ ጉባኤም በዚሁ ሰበብ ታገደ፡፡
እንግዲህ የእንግሊዝና የአይሁድ ጽዩናውያን ሴራ ከ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ
ጀምሮ ሲካሄድ እንደነበረ ግልጽ ነው፡፡ በመሠረቱ የፍልስጤም ሥቃይና መከራ የተጠነሰሰው
መላውን የሙስሊም ዓለም በስሩ ሲያስተዳድር የነበረው የቱርክ ዑስማንያ ኢስላማዊ
መንግሥት በምዕራባውያን እጅ ሲሸነፍና ጨርሶም በ1924 ሲያበቃለት ነው፡፡ የውድቀቱ
ቀጥተኛ ውጤት ሆነናም ባንድ መንግሥት ተማክሎ ይኖር የነበረው ሙስሊም ዓለም
በምዕራባውያን እቅድና ፍላጎት ለየብቻው ተከፋፈለ፡፡
ምዕራባውያን ኢስላማዊውን መንግሥት ለመከፋፈል የተጠቀሙበት ዘዴ የቱርክና
የዐረብ ብሔርተኛ ስሜት በመጫር ነበር፡፡ በኢስላም ዓርማ ሥር ወንድማማች ሆኖ ባንድ
ዓላማና ግብ ተሳስሮ የኖረውን ሕዝብ ገዢና ተገዢ አድርገው በመሳል አቃቃሩት፡፡ ቱርኮችን
እንደገዢ፤ ዐረቦቹን እንደተገዢ፡፡ በዚህም ዐረቦች ከቱርክ ነጻ መውጣት አለባችሁ ተብለው
በተነገራቸው መሠረት እነሱም በየፊናቸው ዐረብ ብሄርተኝነትን ማራገብ ይዘዋል፡፡ ስለሆነም
የታሪካቸውና የሃይማኖታቸው ሞገስ የሆነቸው ፍልስጤም ክብሯን ስትገፈፍና በባዕዳን
ስትመዘበር እነሱ የእንግሊዝ መንግሥት በሰጣቸው የቤት ሥራ ተጠምደዋል፡፡ የነብያቱ አገር
ቤት፣ የኢስራእ-ወል-ሚዕራጅ አገር፣ የአቅሷና የኸሊል ምድር፣ የስንቶች ሙጃሂዲን ደም
የፈሰሰባት ቅድሥት ሀገር በከሐዲያን ስትረክስ ዐረቦች እዚያው ግድም ሁነው አይሰሙም
አይለሙም፡፡ ከኢስላማዊ አንድነት ይልቅ ብሔራዊ ልዩነት ይሻለናል በሚል የዘቀጠ እምነት
ጐራ ለይተዋል፡፡ ወደ ፍልስጤም ዞር ብለው ለማየትና የተቃውሞ ድምፅ ለማሰማት ጊዜ
አልነበራቸውም፡፡
ፍልስጤሞች የዐረብ ወገኖቻቸውን ድጋፍ በመፈለግም ጭምር አገራቸው ፍልስጤም
የታላቁ ሱርያ/ቢላዱ-ሻም አንድ አካል መሆኗን አበክረው ለማስረዳት ቢሞክሩም ለነሱ
የተደገሰላቸው ሌላ ነገር ስለነበረ ሰሚ አላገኙም፡፡ እንደሌሎቹ ሁሉ ለነሱም አገራዊ ነጻነት
እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም አልተፈቀደላቸውም፡፡ ሌሎች ዐረብ አገራት በላያቸው ላይ የአይሁድ
ሠፋሪ ሳይኖርባቸው ነው የብሔራዊ ነጻነታቸውን ጉዳይ እያስተካከሉ ያሉት፡፡ ፍልስጤም ግን
ባዕድ ሠፋሪም ተለቆባት ብሔራዊ ተብዬውን ነጻነትም ተነፍጋ ለሕልውናዋ በመታገል ላይ
ነበረች -እስካሁንም አለች፡፡

የመከላከሉ ጦርነት
ፍልስጤሞች ከ20ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በሕልውናቸው ላይ የመጣባቸውን ባዕድ
ኃይል በከፍተኛ የሕይወት መሥዋዕትነት በመከላከል ላይ እንዳሉ ናቸው፡፡

8 | ገገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

በ1918 አንድ የአርበኞች ኮሚቴ የፍልስጤም ፖሊስ አባላትንም በማካተት በሕቡዕ


ተቋቋመ፡፡ ይህ ኮሚቴ ለዐረብ አብዮት መሠረት በመጣልና በምሥራቅ ኦርዶን በሚኖሩት
በረኸኛ አዕራቦች ዘንድ የሲዮንያን ሤራ በማጋለጥ የላቀ ሚና ተጫውቷል፡፡ ኮሚቴው
በመሪዎቹና አስተባባሪዎቹ ላይ በደረሰው እስራትና ማሳደድ ሊዳከም ቢችልም፣ ብሶት
የወለደው የፍልስጤሞች መነሳሳት ግን እየቀጠለ በመምጣት በ1920 ከኤፕሪል 4 እስከ 10
የዘለቀ አመፅ ተካሂዷል፡፡ ቀጥሎም በ1921 የጃፋ አብዩት ተካሂዷል፡፡ እንደገናም የቡራቅ
አብዩት በ1929 ቀጥሏል፡፡ እነዚህ አመፆች ምንም እንኳን ባደረጃጀት ያልተሟሉና ግብታዊ
የነበሩ ቢሆንም ትግሉን በማጋጋልና የሲዩንያን መሠሪ እቅድ በማጓተት የጎላ ሚና ነበራቸው፡፡
የፍልስጤም ታጋዬች ተጨማሪ ኃይል ማደራጀታቸውን ቀጠሉ፡፡ ከነዚህ መሃል
በኢዘዲን አል-ቋሳም የተደራጀው በዋናነት ይጠቀሳል፡፡ ኢዘዲን አል-ቋሳም ከሱሪያ ወደ
ፍልስጤም በመምጣት እንደአስተማሪ በመሆን የራሱን የትግል እንቅስቃሴ የጀመረ ሰው ነበር፡
፡ በ1926 አንድ የንቅናቄ ኮሚቴ ውስጥ በአባልነት ይገባል፡፡ በ1928 የንቅናቄውን የሓይፋ
ቅርንጫፍ ይመሠርታል፡፡ ቀጥሎም የዚሁ ቅርንጫፍ መሪ ሆነ፡፡ በ1930 ያስተዳደር ኮሚቴው
አባል በመሆን እንደገና የመሪነቱን ቦታ ያዘ፡፡
ከዚህ በኋላ አል-ቋሷም የመንግሥት ሠራተኛ በመምሰል በብዙ የፍልስጤም ክልሎች
እየተዘዋወረ በአምስት በአምስት አባላት የተደራጁ ኩትላዎች/ሕዋሳት በስፋት አዋቀረ
ኢስላማዊ ደምቦችን መመሪያው በማድረግ ብቸኛው የነፃነት መንገድ ጂሃድ መሆኑንም አፅንዖት
አደረገበት፡፡
ይህ በኢዘዲን አል-ቋሷም የተደራጀ የሕቡዕ ንቅናቄ ባይነቱ ለየት ያለና በዐረብ
ፍልስጤሞች የትግል ታሪክ ውስጥ ትልቁ የፊዳይን ንቅናቄ እንደሆነም ይታመናል፡፡ ማዘዣ
ቢሮዎቹ ድሃው ሕዝብ በሚበዛበት የኢያሪኮ ከተማ ነበር፡፡ ባካባቢው ሰፊ ተቀባይነት እያገኘም
ሲመጣ አደረጃጀቱን በማስፋት የደዕዋና የአሕዝቦት፣ የወታደራዊ ስልጠና፣ ያቅርቦት፤
የኤሌክትሮኒክስና የውጭ ግንኙነት አካላትን በመፍጠር አቋሙን ይበልጥ አጠናከረ፡፡
በ1935 ኢዘዲን አል-ቋሷም የአብዮቱን መጀመር ይፋ አደረገ፡፡ ይህም የሆነው
ሠላማዊ መፍትሔ የማፈላለጉ ጥረት ለተደጋጋሚ ጊዜ ተሞክሮ ያለውጤት መቅረቱ እውን
ከሆነ በኋላ ነው፡፡ የአብዮቱን መጀመር ተከትሎ በቋሳም ታጣቂዎች/ ሙስሊሒን እና
በእንግሊዝ ጦር መካከል ተከታታይ ግጭቶች ተካሂደው ብዙ ፍልሚያዎች ከተደረጉ በኃላ
አል-ቋሷም ማፈግፈግ ግድ ይሆንበታል፡፡ ከተወሰኑ የጦር ተባባሪዎቹ ጋር እንዳለ በእንግሊዝ
ጦር ይከበብና እጁን እንዲሰጥ ይጠየቃል፡፡ ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ በዚህ መሃል አቅጣጫው
በውል ያልተለየ ጥይት ያገኘውና ሕይወቱ ታልፋለች፡፡ በተቀሩት ጓደኞቹና በእንግሊዝ ጦር
መካከል የከረረ ውጊያ ተካሂዶ የሞቱት ሞተው የተቀሩት ተያዙ፡፡
አል-ቋሷም የመሠዋቱ ዜና ሲሰማ መላው ፍልስጤም ተነቃነቀ፡፡ የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ
ለፍልስጤም ሌላ የትግል ቃልኪዳን ቀን ሆኖ ዋለ፡፡ የቋሳም ንቅናቄ በዓላማውና በተነሳሽነቱ

9 | ገገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ረገድ ባይነቱ የመጀመሪያው ነበር፡፡ በአይሁዶችና እንግሊዞች ላይ በቀጥታ ያነጣጠረ ወታደራዊ


ንቅናቄ ነበር፡፡
ኢዘዲን አልቋሳም ለፍልስጤም ነጻነት መዋጋትን ኒይያው አድርጐ ከሱርያ ወደ
ፍልስጤም በመምጣት ኑሮውን እዚያው ያደረገ አላህን ፈሪ ሰው መሆኑን ይታወቃል፡፡ እሱ
ባቀጣጠለው አብዮትና በከፈለው መሥዋዕትነት በፍልስጤሞች ዘንድ የላቀ የተነሳሽነት ስሜት
ተቀሰቀሰ ፡፡ በርግጥም እሱ ያመላከተው ኢስላማዊ የትግል አቅጣጫ፣ የውጊያ ስልትና
የተጋፋጭነት አቋም ትምህርት ሰጪ ነበር፡፡ የአይሁድ እንግሊዝ መሠሪ እቅድ ጂሃድን መርሁ
ባደረገ ስልት መዋጋት እንደሚያስፈልግ በሁሉም ፍልስጤማዊ ዘንድ እየታመነበት መጣ፡፡
በቋሳም መሞት የፍልስጤም አብዮት አልተቀለበሰም፡፡ ነገሮች ቤንዚን
እንደተርከፈከፈበት እሣት እየተቀጣጠሉ በመምጣት የ1936ቱን የተራዘመ አብዬት አስከተሉ፡
፡ የሥራ ማቆም አድማዎች፣ ሰላማዊ ሰልፎች፣ ለቅኝ አገዛዛዊ ሕጐች እምቢ ማለት፣ የዚህ
አብዮት ዓይነተኛ መለያዎች ነበሩ፡፡ ሕዝባዊ አመፁ የብረት ድጋፍም ሳይለየው በ1930ዎቹ እና
በ1940ዎቹ ውስጥ ቀጥሏል፡፡
ሁኔታው በፍልስጤሞች ወገን ባጭሩ ከላይ የተወሳውን ሲመስል፣ በአይሁዶች በኩል
የተጀመረው አፍራሽ ድርጊትም በእንግሊዝ ጦር ሽፋን ሰጪነት እንደቀጠለ ነበር፡፡ በ1930ዎቹና
በ1940ዎቹ ውስጥ ይበልጥ እየተጠናከረና ዓይን እያወጣ የመጣው የሲዮንያ እንቅስቃሴ ወደ
ከፋ ደረጃ በመድረስ የ1948ቱ የአይሁድ መንግሥት ምስረታ እውን ሊሆን ችላል፡፡
ፍልስጤሞች ይህን ዓይን ያወጣና ገደብ የጣሰ ድርጊት በይሁንታ አላለፉትም፡፡
በቁጥርና በትጥቅ ከፍ ብሎ ተጠናክሮ ከተጋረደባቸው የእንግሊዝ ጦርና የአይሁድ ሠፋሪ
ታጣቂ ኃይል ጋር እጃቸው ላይ ባለ ነገር ሁሉ ተፋልመዋል፡፡ የተቀሰቀሰው የሕዝብ ፍልስጤም
ቁጣ በዋዛ እንደማይበገር የተረዱት እንግሊዝና አይሁድ ሠፋሪዎች የተነሡበትን ግዛት
የማስፋት እቅድ ይበልጥ ለማሳካት ሲሉ እስከዛሬ ድረስ ጦሱ ያልሻረውንና በሙስሊሙ ዓለም
በተለይም ዐረብ ፍልስጤሞች ዘንድ መሪር ትውስታ ያስከተለውን የሜይ 15/1948 አስከፊ
ድርጊት በፍልስጤም ሰላማዊ ሕዝብ ላይ ፈፀሙ፡፡
አል-ነቐባ
ሜይ 15/1948
የአይሁድ ሠፋሪ ታጣቂዎች (ይህን ጊዜ ከመንግሥታት ምሥረታው ጋር በተያያዘ ወደ
መደበኛ ሠራዊትነት ተለውጠዋል) ዳር-ያሲን የምትባለውንና ከኢየሩሣሌም ባቅራቢያ
የምትገኘውን ፀጥተኛ መንደር ዙሪያዋን ክብብ ያደርጋሉ፡፡ ከዚያም ሴት ወንድ ሳይሉ፣ ህፃን
ከአዋቂ ሳይለዩ፣ አዕሩግ ሳይሉ - ብቻ ፊለፊት ያገኙትን ሁሉ በጥይት ቆሉት፡፡ በስለትና
በመጥረቢያ ጨፈጨፉት ፡፡ ተርፎ ለማምለጥ የሚሞክረውን መግቢያ መውጫውን በመዝጋት
እየጠበቁ ደፉት፡፡ በመጨረሻም 256 ነዋሪዎችን ጭፍጭፍ አድርገው ማንም እንዳልተረፋቸው
እርግጠኛ ሲሆኑ ቤት ንብረቱ ላይ (የፍየልና የግመል ማደሪያ፣ የእህል ማከማቺያ ሳይቀር)

10 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

እሣት ለቀቁበት፡፡ ይህ የሆነው በሜይ 15 ቀን 1948 ላይ ነው፡፡ ፍልስጤማውያን ይህን ቀን


አል-ነቐባ’ በማለት በምሬት ያስታውሱታል፡፡ የሃዘንና የእልቂት ቀን ማለት ነው፡፡
አይሁድ በዚህ አልበቃቸውም፡፡ ታንቱራ በተባለችው መንደር ላይም ተመሳሳይ
ጥቃት በማድረስ 200 ነዋሪዎችን ፈጅተዋል፡፡
ፍልስጤማውያን ወገኖቻቸው ላይ በደረሰው ጅምላ ፍጀት ክፉኛ ተረበሹ፡፡ በገዛ ቤት
ንብረታቸው ላይ ውለው ለማደር ደህንነት አልሰማቸው አለ፡፡ ባፋጣኝ ቀያቸውን እየለቀቁ
በቀንና በሌሊት ተሰደዱ፡፡ ምንም አልያዙ፡፡ አልቋጠሩም ፣ አልሰነቁም ፡ ብቻ ነፍሳቸውን
ይዘው እግር ወደመራቸው አቅጣጫ ጐረፉ፡፡ ሰላም እናገኛለን ወዳሉበት ግድም ርቀው ሄዱ፡

ድርጊቱ ዓለም አቀፋዊ ውግዘት አስከትሎ ተኩስ አቁም ሲደረግ 800.000
ፍልስጤማውያን ቤተሰቦች ቀያቸውን ለቀው ተሰደዋል፡፡ ገሚሱ የዬርዳኖስን ወንዝ ተሻግረው
ኦርዶን ገቡ፡፡ ገሚሱ በረሃ አቋርጠው ወደሉብናን ዘለቁ፡፡ ገሚሱ እስከዚህ ጊዜ ድረስ የዐረቦቹ
ጠንካራ ይዞታ ወደነበረው የምዕራብ ዳርቻና የገዛ ሠርጥ ሄደው ሜዳ ላይ ፈሰሱ፡፡ የተቀሩት
ወደ ማዕከላዊ ፍልስጤም ተራራማ ቀበሌዎች በመሄድ ተገን ያዙ፡፡ 160.000 የሚሆኑ የገሊላ
አካባቢ ነዋሪ ዐረቦች ብቻ እዚያው ሙጥኝ ብለው ሲቀሩ ሌላው ተበተነ፡፡
ተኩስ አቁም ተደርጓል ተብሎ አገር አማን ሲመስል ተሰዳጆቹ ፍልስጤማውያን ሌላ
ያልጠበቁት ነገር ገጠማቸው፡፡ ወደነበሩበት ቀያቸው እንዳይመለሱ ተከለከሉ፡፡ የኢስራኤል
ጦር መንገዱን ሁሉ በከባድ መሣሪያና ፀረ-ሰው ፈንጂ አጥሮ አላስገባ አላቸው፣ አሳደዳቸው፣
ተኮሰባቸው፡፡ ይህን ጊዜ የተባበሩት መንግስታት ልዩ ኮሚሽን ተቋቁሞ ፍልስጤማውያን
ተሰደው ባሉበት አካባቢ ወደ 50 የሚሆኑ ጊዜያዊ የመጠለያ ካምፖችን በማቋቋም ተፈናቃዩን
ሕዝብ ማስተናገድ ጀመረ፡፡
በአይሁዶች ላይ ጫና አሳድሮ ተፈናቃዩን ሕዝብ ወደ ነበረበት መንደሮቹ የማስመለሱ
ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ከዐረብ መንግሥታት በኩል ግፊት እየተደረገበት ለረጂም ጊዜ ቢቀጥልም
ውጤት አላመጣም፡፡ የፍልስጤማውያን ከዛሬ ነገ ወደ ቤታችን እንመለሳለን የማለት ተስፋም
የሩቅ ሃሣብ ብቻ ሆነ፡፡ ይህ በንዲህ እንዳለ በኢስራኤል ቁጥጥር ሥር ባሉት ከተሞች የሚገኙ
ፍልስጤም ዐረቦች ሌላ አመፅ በማስነሣት የ1953ቱን የግድያ ርምጃ ወሰዱ፡፡ ከአይሁዶችም
በኩል ተመሳሳይ ጥቃት በዐረቦች ላይ ሲፈፀም ነገሩ ተቀጣጠለ፡፡ በግጭቱ የሞቱት
በሚቀበሩበት ወቅት በዐረቦችና በይሁዶች መካከል ረብሻ ተቀሰቀሰ፡፡ አመፁ እየተባባሰ
ማዕበሉ ሌሎችንም ከተሞች አናወጠ፡፡ የብሪትሽ ባለስልጣኖች በጃፋና ቴላቢብ ከተሞች ላይ
የሰዓት እላፊ ገደብ እስከመጣል ደረሱ፡፡ በናብሉስ ከተማም አስተባባሪ ኮሚቴ ተቋቁሞ
አጠቃላይ የሕዝብ አድማ ተጠራ፡፡
ሁኔታውን ተከትሎ የብሪትሽ ጦር ወደ 20.000 ወታደሮች ከፍ ካለ በኃላ
በፍልስጤም የፊዳይን ንቅናቄ አባላትና በብሪትሽ አይሁድ ጣምራ ኃይላት መካከል ኖቨምበር
1953 ላይ ደም አፋሳሽ ውጊያ ተካሄደ፡፡ የነዚህ ተከታታይ አመፆችና ግጭቶች ድምር ውጤት
11 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ብዙ እንግሊዞችና ሠፋሪዎች የተገደሉበትና የአካል ጉዳት ያገኙበት ሲሆን ከዐረቦችም በኩል


145ሰዎች ሸሂድ የሆኑበትና በመቶዎቹ የሚቆጠሩ የተጐዱበት ነበር፡፡
የፍልስጤሞች መነሳሳት እንደገናም በመቀጠል የእንግሊዝ መንግሥት እስከዚህ ጊዜ
ድረስ ይዞት በነበረው አይሁድ- ዘመም አቋሙ ላይ እንዲያወላውል የተገደደበት ርምጃ ወሰዱ፡
፡ የጀሊል ከተማን እንግሊዛዊ አስተዳዳሪ ገደሉት፡፡ በዚህም የተነሳ እንግሊዞች ካንዳንድ
አቋሞቻቸው በማፈግፈግ አገሪቱን በየሁዶችና ፍልስጤሞች መሃል ለማካፈል አስበው ነበር፡፡
ባንድ በኩል ምንም ውጤት ያለመገኘቱ ነገር እንዳለ ሆኖ ውስጥ ውስጡን ደሞ
የኢስራኤል መንግሥት ድንበር እየገፋ ሠፈራውን የማስፋፋቱ ሁኔታ የተጐራባች ዐረብ
መንግሥታትን ቁጣ በማስነሣት መቆራቆስና ወታደራዊ ግጭቶች ተካሂደዋል፡፡ በዚህ በኩል
በ1956 ሲናይ ምድር ላይ ከግብጽ ጋር የተደረገው ውጊያ ተጠቃሽ ነው፡፡ አይሁዶች በሲናይ
አቅጣጫ ከግብጽ በኩል እየተደረገባቸው ከነበረው ወታደራዊ ጫና ፋታ ለማግኘትና
ለወዲያኛውም ከግብጽ ተከታታይ ጥቃት ለመጠበቅ ሲሉ ከፈረንሳይና እንግሊዝ ጐን በመሆን
ግብጽን ወግተዋል፡፡ የሲናይን ምድር ለመቆጣጠር የነበራቸውን ሃሳብ ግን አልተሳካም፡፡
ሊሳካላቸው የቻለው ኋላ ላይ በ1967 የስድስቱ ቀን ጦርነት ጊዜ ነው፡፡ በዚህ ጦርነት ከግብጽ
የሲናይን ምድር፣ ከሱርያ የጎላንን ኮረብታዎች፣ የደቡብ ሊባኖስን ከፍታማ ቦታዎች፣ መያዝ
ችለዋል፡፡ በዐረቦች ይዞታ ሥር በነበሩበት የምዕራብ ዳርቻና የጋዛ ሠርጥ ላይ ቁጥጥር
አጥብቀዋል፡፡ ይህንንም አዲስ ጥቃትና ወረራ ተከትሎ ተጨማሪ ፍልስጤሞች ለስደት ተዳረጉ፡
፡ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኛ ኮሚሽንም ተጨማሪ 10 ካምፖችን በማቋቋም
የመጠለያውን ቁጥር ወደ 60 ከፍ አደረገው፡፡
ፍልስጤማውያን ከመሬታቸው ላይ በግፍ ከተፈናቀሉበት ጊዜ ጀምሮ በምዕራብ
ዳርቻ ፣ በጋዛ ሰርጥና በጐረቤት ዐረብ አገሮች በስደተኛ ካምፖች ውስጥ እየኖሩ ናቸው፡፡
በጐረቤት አገራት የምጣኔ ሀብትና የማህበራዊ ህይወት መዋቅር ውስጥ መቅለጥና
ማንነታቸውን እንዲረሳ አልፈለጉም፡፡ ይህ ደሞ ወደ አገር ቤታቸው ለመመለስ ያላቸውን
ቁርጠኝነት ያሣያል፡፡ በመሰረቱ ይህ የፍልስጤማውያን ወደ አገር ቤት የመመለስ ቁርጠኛ
አቋምም ነው የሁዶችን እረፍት እየነሣ ያለው፡፡
የፍልስጤሞች ኃይልን በኃይል የመቋቋም ቀጣይ ርምጃ
ከዓለም አቀፉ ኮሚኒቲ ሆነ ከዐረቡ ዓለም በኩል የፍልስጤሞችን ወደ አገር ቤት
የመመለስ ተስፋ የሚያለመልም ነገር እየጠፋ በመምጣቱ ፍልስጤማውያን ሁሉን ነገር ትተው
በራሳቸው ትግል ወሳኝነት ብቻ በመተማመን ለበለጠ ፍልሚያ ተነሳሱ፡፡ በ1958 ሐረከት-
ተሕሪር ፈሊስጢኒያህ/ በምህፃረ ቃል ‹አልፈታህ› ተመሰረተ፡፡ ስደተኛውን ሕዝብ መሰረት
በማድረግ ኢስራኤል ላይ ጥቃት መመንዘሩን ቀጠለ፡፡ በሕዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ተነሳሽነት
እንዲኖር በማድረግ ተቀባይነቱ እየጨመረ መጣ፡፡ በ1960ዎቹ ጠላትን በሽምቅ ውጊያ
በማርበድበድ ምዕራባውያንን አንገት ያስደፋ ድሎችን አስመዘገበ፡፡ ስኬታማ ኦፕሬሽኖችን
በማካሄድ እስራኤል ፍልስጤምን ይዛ በሰላም ውላ ማደር እንደማትችል ለተቀረው ዓለም

12 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ጭምር ትምህርት ሰጪ ርምጃዎችን ወሰደ፡፡ ተከታታይና ቀጣይ የሆኑ ፈጣን ጥቃቶችን


በመሰንዘር የእስራኤልን ጦርና አይሁድ ሰፋሪዎችን ፋታ ነሳ፡፡ በፍርሃት እንዲሸማቀቁ አደረገ፡
፡መብረቃዊ ጥቃት ማድረስ የፍልስጤም ፊዳይን መለያ እየሆነ መጣ፡፡
በዚህ ጊዜ የፋታህ ንቅናቄ የጦር ቤዝ ኦርዶን ነበረች፡፡ ተዋጊዎቹ ከዚህ በመነቃነቅ
ነበር የአይሁድን ጦር የሚወጉት፡፡ በኋላም የፍልስጤማውያን የነጻነት ድርጅት /P.L.O’
ተመሥርቶ ባደረጃጀት ስፋትና ባጠቃቅ ስልት ለውጥ ተደረገ፡፡ በአገሯ ተሰደው ከሚኖሩት
ከሁለት ሚሊዬን በላይ ፍልስጤሞች በተጨማሪ የP.L.O’ በዋና ከተማይቱ አማን እየተጠናከረ
መምጣት ለሐሺማዊት ኦርዶን አልተዋጠላትም፡፡ በ1970 ላይ ከነፃነቱ ድርጅት ጋር ይዞታውን
ለማስለቀቅ በብረት ተፋለመች፡፡ P.L.O’ም ቀሪ ኃይሉን ይዞ ወደሉብናን መዛወር ግድ ሆነበት፡
፡የሉብናን መንግሥትም ያገሪቱን ክርስትያን-ሙስሊም ሕብረተሰብ ሚዛን ሊያዛቡብኝ ይችላሉ
በሚል ስጋት ገና ከጅምሩ የፍልስጤማውያን ስደተኞች ቆይታ ላጭር ጊዜ ብቻ መሆን አለበት
ሲል የነበረ በመሆኑ የP.L.Oን እዚያ መገኘት አልወደደውም፡፡ ይባስ ብሎም በ1972
ከፍልስጤማውያኑ ጋር ደሞ አፋሳሽ ውጊያ አካሄደ፡፡ ይሁንና ግን ፒ.ኤል.ኦ ድርጅታዊ ብቃቱን
በመጠበቅ ኢስራኤል ላይ የሚያደርሰውን ጥቃት እስከ 1982 የኢስራኤል የበይሩት ወረራ ድረስ
መቀጠል ችሏል፡፡
የኢስራኤል ጦር የፍልስጤሞችን ድንበር አቋራጭ ጥቃት ለማምከን በሚል 1969
ላይም ሉብናንን መወረሩ ይታወቃል፡፡በ1982 ደሞ መጠነ ሰፊ ዘመቻ በማድረግ በይሩት ድረስ
ዘልቆ ገባ፡፡ ነገር ግን የፒ.ኤል.ኦን አመራርና ተዋጊ ኃይል ቀለበት ውስጥ አስገብቶ ለመደምሰስ
ያደረገው ሙከራ ፍልስጤማውያኑ ባደረጉት አስደናቂ ከላከል ሊሳካለት አልቻለም፡፡
በመጨረሻም የነፃነት ድርጅቱ ዕዝ መስጫና ተዋጊው በይሩትን ለቀው እንዲወጡ ተወሰነ፡፡
ሆኖም ግን ለኢስራኤል ተጐራባች የሆኑት የዐረብ መንግሥታት የፍልስጤምን ነፃ አውጪ
ድርጅት ከነትጥቅም ሆነ አለትጥቅ ለመቀበል ፈሩ፡፡ ጦሱ ይተርፈናል በሚል ፍራቻ ዋና
መምሪያው ወደ ቱኒሲያ እንዲዛወር ሲደረግ ዘጠኝ ሺ የሚሆኑት ተዋጊዎች ደሞ ራቅ ወዳሉት
የዐረብ አገራት በመርከብ ተጓጓዙ፡፡
አዲሱ የትግል ምዕራፍ
የተዋጊው ከአካባቢው መራቅ ፍልስጤሞችን ለኢስራኤል ጥቃት እንደልብ
አጋለጣቸው፡፡ የኢስራኤል ጦርም ክፍተቱን በመጠቀም የሰላማዊ ስደታኛ ሠፈሮችን ከአየርና
ከመሬት ማጋየቱን ቀጠለ፡፡ በተያዙት ግዛቶችም ውስጥ የሚገኙትን ማዋከብና ማስጨነቁን
ተያያዘው፡፡ በርቀት ያለው ፍልስጤማዊ አመራር የሕዝቡን ትግል ለመደገፍ ሲሞክር
የኢስራኤል የጦር አይሮፕላኖች ቱንሲ ገብተው የቢሮው ሕንጻ በ1985 ደበደቡ፡፡
ፍልስጤም የትግል ደሃ ሁና አታውቅም፡፡
ትጥቃዊ ከለላ የሌለውና ያልተደራጀ በመሆኑ ከንግዲህ የፍልስጤም ሕዝብ
በኢስራኤል እጅ ያለ እስረኛ እንጂ ሌላ ሊሆን አይችልም በተባለበት ተስፋ አስቆራጭ ወቅት
የብልሃት ምንጩ የማይደርቅበት ጀግናው የፍልስጤም ሕዝብ መላውን ዓለም ያስደመመ አዲስ
13 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

የትግል ስልት ቀይሶ እፍልሚያው መድረክ ላይ እንደገና አንድ ጊዜ ብቅ አለ፡፡ ኢንቲፋዳ


የተሰኘው ሕዝባዊ መነሳሳት ድንጋይ በሚወረውሩ ወጣቶች ተጀመረ፡፡ በየጎዳናው በየአውራ
መንገዱ የኢስራኤል ወታደር በድንጋይ እያሳደዱ ውሻ አደረጉት፡፡ መቆም መቀመጥ ከለከሉት፡
፡ ኢንቲፋዳውን እንዳስጀመረ የሚነገርለትን ፍልስጤማዊ ታጋይ ኸሊል አልወዚርን በቱኒሲያ
የሜድትራንያን የባሕር ዳርቻ በአየር ድብደባ በመግደሏ ኢስራኤል እየወረደባት ከነበረው
የድንጋይ ውርጅብኝ ፋታ ያገኘች መስሏት ነበር፡፡ ነገር ግን ኢንቲፋዳው እስከ 1980ዎቹ
ማብቂያ ድረስ ተባብሶ ቀጠለ፡፡ ወንጭፍና ባላ የፍልስጤም ወጣቶች ትጥቅ ሆነ፡፡ የኢስራኤልን
ጦር ባገኙበት ቦታ ሁሉ እንደእባብ እራስ እራሱን እየወቀሩ እራሱን እንዲጠላ አደረጉት፡፡ በዚህ
ጊዜ ነበር 500 የኢስራኤል የጦር መኮንኖች የሥነ ልቡና ጭንቀት አድሮባቸው ከሥራ ውጭ
የሆኑት፡፡ በዚህ ወቅትም ነበር ለመጀመሪያ ጊዜ (ከፍልስጤም ነፃ አውጭ ድርጅት ውጭ)
ሕዝቡን መሰረት ያደረገ ንቅናቄ የተከሰተው ፡፡ የሐማስ ኢስላማዊ ንቅናቄ፡፡ የውጊያው አንደኛ
መሥመር ተሰላፊ በመሆን የሕዝቡን አመኔታ ያተረፈ ድርጅት ሐማስ፡፡
በ1991 ኢራቅ የአምሪካን የባሕር ማዶ የነዳጅ ክፍለ ሀገራት አንዷ የሆነችውን
ኸወይትን ወረረች፡፡ በጊዜው የአምሪካን አመራር ኸወይትን ለማስመለስ በሚያደርገው ጦርነት
የዐረቦችን ድጋፍ ለማግኘት ሲል - ከኹወይት መለቀቅ በኃላ ለፍልስጤም-ኢስራኤል ግጭትም
ላንዴና ለመጨረሻ መፍትሄ እንደሚያሥገኝ ቃል ገባ፡፡ ኹወይት ተለቀቀች፡፡ ድርድሮችም
በፒ.ኤል.ኦ እና በኢስራኤል መሃል በሶስተኛ ወገን አገናኝነት ተጀመሩ፡፡ ኢንቲፋዳው ጋብ
እንደማለት አለ፡፡
በሴብቴምበር 13/1993 በፍልስጤም ነፃ አውጪና በኢስራኤል መንግስት መሃል
ዋሽንግተን ላይ በተፈረመው ውል መሠረት ለፍልስጤማውያን የራስ ጋዝ መርሃ-ግብር
ሊተገበር ነው ቢባልም ለሕገ ወጧ ኢስራኢል እውቅና ከማሰጠትና የፒ.ኤል.ኦ የትግል
ፕሮግራም ውስጥ የኢስራኤልን መኖር የማይቀበለውን አንቀጽ ከማሰረዝ ሌላ ለፍልስጤም
አንዳች ሲፈይድ አልታየም፡፡
በ1967 የስድስቱ ቀን ጦርነት ኢስራኤል ቀንቷት ተጨማሪ ቦታዎችን ከዐረቦች
ነጥቃለች፡፡ ይሁንና ግን አሁን ካንዳንዱ ቦታ ለቃለች፡፡ ከግብጽ የሲናይ ምድር፤ ከሱርያ ጎላንን፡
፡ ደቡብ ሊባኖስን፣ እዚያው ፍልስጤም ውስጥ ደሞ ምሥራቅ እየሩሳሌም መያዟ ይታወሳል-
ግብጽ ምስራቃዊ በሯን ከወታደራዊ ክምችት ምንግዜም ነፃ እንድታደርግ የቀረበላትን ቅድመ
ሁኔታ ተስማምታበት መሬቷን መልሳ አግኝታለች፡፡ ኢስራኤል ከደቡብ ሊባኖስም በሕዝቡሏህ
ጦር በደረሰበት ተከታታይ ጥቃት ከ18 ዓመታት በኃላ እንደውሻ ጭራዋን ሸጉጣ ለመውጣት
ተገዳለች፡፡ ከሱርያ በያዘችው የጎላን ኮረብታ ላይ ሰሞኑን አዳዲስ መንደሮች እንደምትገነባ
እያስታወቀች ነው፡፡ በፍልስጤም ላይ ጭበጣዋን ማላላት አልፈለገችም፡፡ ለይስሙላ
ከሚንከላወሰው የፍልስጤም አመራር አፍንጫ ስር ያዳዲስ መንደሮች ግንባታውን ቀጥላለች፡
፡ ቤት ማፍረሱ፣ ማፈናቀሉ፣ የፍልስጤማውያን ደም በየጎዳናው ማዝራቱ አልተገታም፡፡ይህ
በንዲህ እንዳለ የኢንቲፋዳው ሁለተኛ ምዕራፍ ተገለጠ፡፡

14 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ኢንቲፋዳ ጀዲዳ
ሴብቴምበር 2000
በ2000 ሴብቴምበር ወር ውስጥ አሪል ሻሮን የተቀደሠውን የሐረም አሸ-ሽሪፍ ስፍራ
የመጐብኘቱ ድፍረት ታላቅ ቁጣ ቀሰቀሰ፡፡ ፍልስጤማውያን ወጣቶች ያስቀመጡትን ድንጋዮች
እንደገና አነሱ፡፡ ኢንቲፋዳው ቀጠለ፡፡ የአል-አቅሷ ኢንቲፋዳ፡፡ እንደገናም በኢስራኤል
ወታደሮች ጆሮ ግንድ ስር ድንጋይ ማፋጨቱን ቀጠለ፡፡
ኢንቲፋዳ ማለት በመሠረቱ በገዛ ቤት ንብረት ላይ የሚደረግ የሞት ሽረት መከላከል
ነው፡፡ በህልውና ላይ የመጣውን ጠላት የመመከት ርምጃ፡፡ ከምድር ተነስቶ የራሱን እኩይ
ዓላማ ለማሣካት ሲል ብቻ የሌላውን መኖር በሚክድ፣ ቤት በሚንድ፣ ዛፍ በሚነቅል፣ ሕጻናትን
በሚፈጅ፣ ሴትን ልጅ በሚያሰቃይ፣ አዕሩግ በሚያቀል እርጉም ኃይል ላይ ፍልስጤሞች
የጀመሩትን አመጽ “ኢንቲፋዳ” ይሉታል-ሕዝባዊ መነሳሳት ነው፡፡ ታዲያ ሐቁ ይሄ ሆኖ ሳለ
የኢስራኤል መንግሥት ለዚህ ያልታጠቀ ሕዝባዊ ተቃውሞ ምላሽ እየሰጠ ያለው ጨርሶ
ባልተመጣጠነ ኃይል (በአምሪካን ሠራሽ አፓቼ ሄሊኮፕተሮች፣ ከሰማይ ወደ መሬት
ተወንጫፊ ሳሩኾች፣ ታንኮችና ኤፍ 16 ተዋጊ ጀቶች) የመሆኑ ነገር የፍልስጤምን ሕዝቦች
ፈጅቶ መሬታቸውን ለመውረስ ያለውን ቁርጠኛ ዓላማ አመላካች ነው፡፡
ሁለተኛው ኢንቲፋዳ ከተጀመረበት (ከሴብቴምበር 2000) ይህ ፅሑፍ
እስከተጠናቀረበት 2003 ማብቂያ ድረስ 35 ወሮች ተቆጥረዋል፡፡ ሰላሳ አምስት የሰቆቃ ወሮች፡
፡ የከዚህ በፊቱን ትተን በነዚህ 35 አስከፊ ወሮች ብቻ በተቀደሰው የፍልስጤም ምድር ላይ
በኢስራኤል ጦር እጅ ምን እንደተፈጸመ ስናይ በርግጥም የአይሁዶች ዓላማ ፍልስጤሞችን
ፈጅቶ የፍልስጤምን ምድር የራሳቸው ማድረግ እንደሆነ ይበልጥ ሳንረዳ አንቀርም፡፡
የተሰውና የቆሰሉ
እነሆ በጦር ኃይል ድንገት ሰብሮ በመግባት ግድያ መፈጸም፣ ከተሞችን መክበብ፣
መንገዶችን መዝጋት፣ መኖሪያ መንደሮችን (ከአየር ወይ ከመሬት) በከባድ መሳሪያ መደብደብ፣
ቤቶችን ማፍረስ፣ ፍሬያማ ዛፎችን መንቀል፣ ሰብሎችን በታንክ እግር መረመም፣ ሰዎችን
ማዋከብና ማሰር፣ እንቅስቃሴዎችን በማቀብ ሕዝቡ ለረጂም ቀናት እንዳይገናኝ፣ እንዳይሰራ፣
እንዳይሸምት፣ እንዳይታከም በማድረግ ጅምላውን መቅጣት ዓይነተኛው የአይሁድ ጥቃት
ስልት ነው፡፡ በዚህም የተነሳ በተጠቀሰው የ 35 ወር ጊዜ ውስጥ ብቻ 2875 ፍልስጤሞች
ሙት፣ 41‚322 ቁስለኛ ሁነዋል፡፡ 403 ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ልጆችም ሆን ተብሎ
በተነጣጠረ ተኩስ ተገድለዋል፡፡
አለፍርድ ሂደት የተገደሉ
Palestinian center for human rights / PCHR” የተሰኘ የፍልስጤማውያን
የሰብዐዊ መብት ማዕከል ባቀረበው ዝርዝር በሦስት ዓመት የአል-አቅሳ ኢንቲፋዳ ወቅት 309

15 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ፍልስጤማውያን ከፍርድ ሂደት ውጭ በተካሄደ 157 ርሸና ተገድለዋል፡፡ ከነዚህ 195ቱ


የተመረጡ ዒላማዎች ሲሆኑ፣ 114ቱ እግረ-መንገዳቸውን በዚያ ሲያልፉ ሰለባ የሆኑ ናቸው፡፡
በተመረጠ ዒላማነት ተነጣጥሮባቸው ከተገደሉት መሃል ሦስቱ 18 ዓመት ያልሞላቸው
እንደነበሩም ተዘግቧል፡፡ የግድያው ርምጃ ቀጥተኛ ዒላማ ሳይሆኑ ከተገደሉት 114
ፍልስጤማውያን መሃል 18 ዓመት ያልሞላቸው 38 ልጆች ፣ 14 ሴቶች ፣ 16 በዕድሜ የገፉና
አንድ የሁለት ወር ሕጻን ይገኙበታል፡፡
ከፍርድ ሂደት ውጭ የተካሄደው 157 የግድያ ርምጃ በማዕከላዊ አሃዝ ሲሰላ ቢያንስ
በሣምንት አንድ የግድያ ርምጃ በፍልስጤማውያን ላይ ይወሰዳል ማለት ነው፡፡ በነዚህ ድንገተኛ
ርምጃዎች 627 ፍልስጤማውያን ዜጎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ ከነዚህ መሃል 34 ብቻ
“የተመረጡ ዒላማዎች” ሲሆኑ የተቀሩት 593 አደጋው ሲደርስ በአካባቢው የነበሩና የተጐዱ
ናቸው፡፡ እነዚህ ከፍርድ ሂደት ውጭ በዘፈቀደ የተካሄዱ ርሸናዎች ይበልጡኑ የተካሄዱት
በምዕራብ ዳርቻ በሚገኙ ከተሞችና በጋዛ ሠርጥ መሆኑንም ሪፖርቱ ሳይጠቅስ አላለፈም፡፡
አለፍርድ ሂደት የሚካሄደው ግድያ ከዓመት ወደ ዓመት እየጨመረም የመጣ ክስተት
ነው፡፡ በመጀመሪያ ዓመት 41 የግድያ ርምጃዎች ተወስደው 54 ፍልስጤማውያን ተገድለዋል፡
፡ 35ቱ “የተመረጡ ዒላማዎች”ሲሆኑ የተቀሩት ባጋጣሚው የተጎዱ ናቸው፡፡ ለአካል ጉዳት
የተዳረጉ 65 ሲሆኑ ከነዚህ መሃል 13ቱ “የተመረጡ ዒላማዎች” ነበሩ፡፡ በሁለተኛው ዓመት
50 የግድያ ርምጃዎች ተወስደው 114 ሲገደሉ ከነዚህ መሃል 70ው “የተመረጡ ዒላማዎች
ነበሩ፡፡ ለአካል ጉዳት የተዳረጉ 188 ሲሆኑ 8ቱ “የተመረጡ ዒላማዎች” ነበሩ፡፡ በሦስተኛው
ዓመት 66 የግድያ እርምጃዎች ተወስደው 141 ፍልስጤም ዜጐች ሲገደሉ 90ው “የተመረጡ
ዒላማዎች” ነበሩ፡፡ ከነዚህ በተጨማሪ 18 ዓመት ያልሞላቸው 16 ልጆች ሲገደሉ 3ቱ የተመረጡ
ዒላማዎች ነበሩ፡፡ የቆሰሉና ለአካል ጉዳት የተዳረጉት 374 ሲሆኑ 15ቱ የተመረጡ ዒላማዎች
ናቸው፡፡
ከቀረበው ዝርዝር መረዳት እንሚቻለው የኢስራኤል ጦር “የተመረጡ ዒላማዎችን
ለማጥቃት” በሚል ሰበብ የሚወሰደው የግድያ ርምጃ ዕድሜና ፆታ የማይለይ፣ የፈለገው አንድ
ላይ ቢሞት ደንታ የሌለው ፍጹም አረመኒያዊ ድርጊት መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ እርግጥ ነው
የኢስራኤል ጦር ሰራዊት በፍልስጤሞች ላይ ግድያ መፈጸምን ዋነኛ ስትራቴጂው አድርጎ
ይዞታል፡፡ እነዚህ የተነጣጠሩ ግድያዎች ብዙውን ጊዜ የሚካሄዱት ከአፓቼ ሄሊኮፕተሮች ላይ
ወደ መሬት በሚተኩሱ ሚሳኤሎች ወይም በተጠመዱ ቁንቡላዎችና መሠል ጥቃቶች
እንደሆነም ይታወቃል፡፡
ቀደም ሲል ከተጠቀሰው የሙት ፍልስጤማውያን አሃዝ (2875)ውስጥ አብዛኛው
በጄትና በከባድ መሣሪያ ድብደባ የተፈፀመ ሲሆን የተቀሩት “ማሰስና መደምሰስ” በተሰኘው
የኢስራኤል ወታደሮች የቤት ለቤት ወረራ የተገደሉ ናቸው፡፡ ማቾቹም ሠላማዊ ነዋሪዎች ሲሆኑ
553 የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ 220 ወንድና ሴት ስፖርተኞች፣ 25 የሕክምና ቡድን አባላትና
የአምቡላንስ ሹፌሮች ይገኙበታል፡፡ 41 ፍልስጤማውያን በአይሁድ ሠፋሪ ታጣቂዎች
ተገድለዋል፡፡

16 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

የቁጥጥር ኬላዎችና መሰናክሎች


ሌላው የኢስራኤል ጦር እንደ “ውጊያ ታክቲክ” የሚጠቀምበት አረመኒያዊ ድርጊት
በማንኛውም ጊዜ እየተነሳ በፍልስጤም ከተሞች፣ መንደሮችና የስደትኛ መጠለያዎች ላይ ከበባ
ማድረግና መቆጣጠሪያ ኬላዎችን ማቆም ነው፡፡ እንዳስፈላጊነቱ ከሚዘጉት አውራ መንገዶች
በተጨማሪ 1617 የቁጥጥር ኬላዎች በመላው ፍልስጤም ተዘርግተዋል፡፡ ይህ ማለት
በእያንዳንዱ የፍልስጤም ከተማ፣ መንደርና የስደተኛ መጠለያ ዙርያ የእስራኢል የአፈና ጣቢያ
መኖሩ ግልጽ ነው፡፡ ከዚህም ሌላ የአይሁድ ጦር በፈለገው ጊዜ በፍልስጤማውያን ይዞታ ላይ
ይሠፍርና የፈለገውን ያደርጋል፡፡
የቁጥጥር ኬላዎች ድንገት በኢስራኤል ወታደሮች ዝግ ሲሆኑ ወዲህም ወዲያም ማለት
አይቻልም፡፡ ላልተወሰነ ቀን ዝግ ሁነው ብቻ ይቆያሉ፡፡ መቼ ተመልሰው ይከፈታሉ
ፍልስጤማውያን የሚያውቁት ነገር የለም፡፡ አንዳንዴ ጊዜው ይራዘማል፡፡ አብሮት የሰዓት እላፊ
ገደብም ይጣላል፡፡ አምቡላንሶች ሳይቀሩ ለሕሙማን አገልግሎት ሲሰጡ ከተገኙ ተገደው
እንዲቆሙ ይደረጋሉ፡፡ ለሆስፒታሎች መድኃኒትና ኦክስጂን የሚያደርሱ መኪኖችም ጭምር
ዝውውር አይፈቀድላቸውም፡፡ በዚህ አይነቱ አስከፊ ድርጊት 83 ሕሙማን ወደ ሕክምና
መስጫ ጣቢያ እንዳይደርሱ ተደርገውረ አምቡላንስ ውስጥ ሕይወታቸው አልፋለች፡፡ 12ቱ ገና
አምስት ዓመት እንኳን ያልሞላቸው ሕጻናት ነበሩ፡፡ 48 በምጥ የተያዙ ሴቶችም እንደዚሁ ወደ
ሐኪም ቤት ለማለፍ ሲሞክሩ ኬላዎች ዝግ እየሆኑባቸው እዚያው ለመገላገል ሲገደዱ 27
ጽንሶች መጉላላት እየደረሰባቸው ተጨንገዋል፡፡ 226‚000 ተማሪዎች መንገድ ዝግ
እየሆኑባቸው ከትምህርት ገበታ ተስተጓግለዋል፡፡ በወይራ ምርት መሰብሰቢያ ወቅት ከሆነ ደሞ
ማንም ከከተማ ወደ ገጠር ሄዶ ምርቱን መሰብሰብ አይፈቀድለትም፡፡
እስረኞችና ታጋዮች
ዓለም አቀፍ የሰብዐዊ መብት ተሟጋቾች እና ኦፊሴላዊ ማዕከላት ባደረጉት ጥናት -
ኢስራኢል በምትቆጣጠራቸው ግዛቶች ውስጥ በሚገኙ 22 አደገኛ ወህኒ ቤቶች ውስጥ 11‚112
እስራኞች አላግባብ ታስረው አሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ 300ው በጽኑ ሕመም እየተሰቃዩ ያሉ
ናቸው፡፡ 90 የሚሆኑት እንደውም የቅርብ የሕክምና ክትትል /intensive medical care
የሚያስፈልጋቸው ነበሩ፡፡ የኢስራኢል መንግስት የአፈና ፖሊሲ ሆነና የታሳሪ ቤተሰቦች ታሳሪ
ዘመዶቻቸውን መጠየቅ አይፈቀድላቸውም፡፡ እስረኞቹ ብሶታቸውን የሚያሰሙበት ሕጋዊ
አካል (ፍርድ ቤት፣ ጠበቃ….) ማግኘት አይችሉም፡፡ ከሁሉም ደሞ በሴት እስረኞች ላይ
የሚደርሰው በደል አንድና ሁለት የለውም፡፡ ፍልስጤማውያን ሴት ታሳሪዎች መሠረታዊ የጤና
አገልግሎት እንኳን ስለተነፈጉ ከዕለት ወደ ዕለት የጤና ማጣት ችግር እየገጠማቸው እንደሆነ
ይናገራሉ፡፡ መታሰሪያ ክፍሎቹም ሆን ተብሎ ምቾት እንዳይኖራቸው የተደረጉ ቆሻሻ ክፍሎች
ናቸው፡፡ በዚህ ላይ የሴቶቹን ሞራል ለመስበር ሲባል በየቀኑ የተለያየ ደምብ እየወጣ ውሃ
ቀጠነ ይባላሉ፡፡ ብዙ ዓይነት ማስጨነቅም ይደርስባቸዋል፡፡ማስፈራራት፣ ማስራብ …

17 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

የኢስራኢል እርጉም ባለስልጣናት ከ18 ዓመት በታች የሆኑ 1300 ታዳጊዎችንም


አስረው በማንገላታት ላይ ናቸው፡፡ ከአካላዊ እንግልቱ በተጨማሪ ከልክ ያለፈ ማስፈራራትና
ማስጨነቅ የልጅ አእምሮአቸው ሊሸከመው ከሚችለው በላይ እየደረሰባቸው መሆኑን ጥናቶች
ይጠቁማሉ፡፡ በሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን በኢስራኢል ወህኒ ቤቶች ውስጥ እየተሰቃዩ
ስለመሆናቸው የበለጠ ግንዛቤ ለማግኘት ከዚህ ቀጥሎ በፍልስጤማውያን የእስረኞች ጉዳይ
ሚኒስቴር መስሪያ ቤት የቀረበውን አንድ የእንግሊዝኛ ቅጂ ሪፖርት ይመልከቷል፡፡

Thousands of Palestinian prisoners Humiliated by Israel

Palestinian ministry of prisoners affairs, reported that palesetinian prisoners


held in Israeli prisons are being exposed to harsh Israeli practices including
physical torture, solitary confinement, beating and tear gas inhalation, It is said
that along with the said practices, Israeli prison administratons have recently
installed glass walls in prison rooms, preventing warm famiy visits, followed
recently by Israeli complete denial of visits made regularly by prisoners’ families
to their beloved ones.
It pointed out there are 8,000 palestinian prisoners including 361 minors and
80 women, 6,200 of whom have been jailed over the past three Years of the
Intifadas, and are being held in various Israeli prisons and detention camps like
Ofer, Al-Ramala, Asqalan, desert prison of Negev, Shatta, Narha….etc
“Due to Israeli maltreatment of minor prisoners, 16 of whom have recently
attempted to commit suicide, rejecting the Israeli wardens humiliation,
including forced labor under harsh treatment,” the ministry confirmed.
As for sick prisoners, there are 800 patients including 22 with chronic diseases,
being hospitalized in the clinic of Al-Ramala prison.
It also highlighted that 2,500 prisoners have been already sentenced while 3,000
others are awaiting trial under continued interrogation. About 1,000
administrative detainees are being detained in the Israeli detention camp of
Ketse’out in the Negev desert, south of Israel. Administrative detention without
trial or charges is prohibited under international law.
Those prisoners, some of whom are held in Ofer detention camp, have had their
detention period frequently extended six-months by the so-called “Sarafand”
Israeli military governor” and without trial.

18 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

The ministry mad clear, concerning the secret Israeli detention camps for
Palestinians,that since 1967 up to date,Israel army camps as special interrogation
wings in certain Palestinian cases. “safarand” Israeli military camp,for example
was used by Israeli after 1967 for detaining several Palestinian ‘fidayeens’
(freedom fighters), asserting that lawyers and red cross staff were denied access
into such camps.
As for the palesetinian political figures and leaders in detention, the ministry
declared that they’re constantly being held in solitary confinement since the day
they were arrested, as in the case in Fateh’s Secretary General in the west bank
and Palestinian Legislative Council member marwan Al Barghouti.
The ministry pointed out to the struggle and steadfastness of the Palestinian
prisoners behind bars, as they sent a letter of support and solidarity from within
their prison cells to the president Yasser Arafat, denouncing the Israeli decision
of expelling or killing him, and considering it as a true evidence to the Israeli
“Transfer” policy, adopted by the Israeli government since the beginning of its
occupation.
የፈረሱ ሕንጻዎች ተቋማትና
መኖሪያ ቤቶች
የኢስራኢል መንግሥት በፍልስጤማውያን ላይ ከሚያራምደው የጥፋት ፖሊሲ
አንዱ ቤቶችንና መኖሪያ አካባቢዎችን ተቀባይነት በሌለው ምክንያት (ያላግባብ የተገነቡ ናቸው
በሚል) እየተነሳ ማውደሙ ይጠቀሳል፡፡ ባይነቱ የተለየ የጦር ወንጀል ቢኖር ይኸው
የኢስራኢል ጦር በቤቶችና መኖሪያ አካባቢዎች ላይ በማንአለብኝነት ቀጥሎት ያለው
የመክበብና ቡልዶዝ የማድረጉ ተግባር ነው፡፡ ጦሩ ከተሞችን ሰብሮ ሲገባ ከታንኮቹ በስተጀርባ
ቡልደዘሮች ይከተላሉ፡፡ በከባድ መሣሪያ (በጄት፣ በሚሳኢል…) የተደበደበውን ቤት ከሥር
ቡልደዘሮቹ መሠረቱን በመናድ ያስተኙታል፡፡ ቤቶችን አላንዳች ቅድመ ማስጠንቀቂያ ማፍረሱ
ሳያንስ፣ ባለቤቶቹን የትም ድረሱ ብሎ ማባረሩ፣ ይባስ ብሎም አንዳንዱጋ ባለቤቶቹ እውስጡ
እያሉ ሠብሮ በመግባት ቤቱን ለወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያነት በኃይል የመገልገሉ ነገር በደሉን
ያባብሰዋል፡፡ እነሆ በዚህ ዓይነት 282 ት/ቤቶች 15 የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ 553
የአስተዳደርና የሕዝብ ህንፃዎች ወድመዋል፡፡ 53‚656 መኖሪያ ቤቶች ተደብድበው 3‚877
ሙሉ ለሙሉ እንዳልነበረ ሁነዋል፡፡
የጥበብን ችቦ የማጨለም እርምጃ
የኢስራኢል መንግስትና ጦሩ ፍልስጤምን እንዳገር ለማጥፋት
ከሚጠቀሙበት ዘዴ መሃል አንዱ ፍልስጤማውያንን የመሬት ብቻ ሳይሆን የዕውቀት ድሃ

19 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ማድረግ ነው፡፡ ለዚህ ደሞ የአይሁድ ጦር ፍልስጤማውያን ተማሪዎችና መምህራን ላይ


በትምህርት ተቋማትና በመማር ማስተማሩ ሂደት ላይ እየፈጠረ ካለው ችግር የተሻለ ማስረጃ
የለም፡፡ 205 ትምህርት ቤቶች በጦር ጄት፣ በሞርታርና በአፓቼ ሄሊኮፕተሮች ተደብድበዋል፡
፡ ዘጠኝ ዩንቨርሲቲዎችና ኮሌጆች ፣ 7 ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ ከነአካቴው ተዘግተዋል፡፡
በ850 ት/ቤቶች የመማር ማስተማሩ ሂደት ተስተጓግላል፡፡ 60 ት/ቤቶች ወረራ ተካሂዶባቸው
ተመዝብረዋል፡፡ 25 ት/ቤቶች ተማሪው ተባሮ ለኢስራኢል ጦር የዕዝ መስጫ ጣቢያ
ተደርገዋል፡፡ የኢስራኢል ጦር ከተሞች ላይ ከበባ ሲያደርግና መንገዶችን ሲዘጋ ሆን ብሎ እነሱ
ላይ በማነጣጠር 227 ተማሪዎችን በጠራራ ጸሃይ ረሽኗል፡፡ 2‚690 አቁስሏል፡፡ 166 አስሯል፡

የወደሙ ኢንዱስትሪዎችና የንግድ ተቋማት
ሆነ ተብሎ በተሰነዘረ የከባድ መሳሪያ ጥቃት 7‚129 የኢንዱስትሪና የንግድ ተቋማት
ፈራርሰዋል፡፡ የፍልስጤማውያኑን ምጣኔ ሀብት ለመጉዳት በታለመ አንድ ኦፕሬሽን ብቻ 62
ሱቆችና የመገበያያ ማዕከላት በምዕራብ ዳርቻ አንድ ከተማ ውስጥ እንዲወድሙ ተደርጓል፡፡
በእርሻና በእርሻ ውጤቶች ላይ
የደረሰ ጥፋት
ኦገስት 5/2003 የቀረበው የፍልስጤም የእርሻ ሚኒስቴር ሪፖርት ይፋ እንዳደረገው
-(ከሴብቴምበር 2000 - እስከ ጁላይ 2003) ወራሪው የኢስራኢል ጦር በፍልስጤም የእርሻ
ይዞታዎች ላይ በፈጸመው ጥፋት የ$235.867.256 ኪሣራ ተመዝግቧል፡፡ ይህ ኪሣራ ሊደርስ
የቻለው በፍልስጤማውያኑ ገበሬዎች የልማት ሥራ ላይ ከዓመት ዓመት እየተባባሰ የቀጠለ
ውድመት በመድረሱ እንደሆነ ይታመናል፡፡ የተምር ፣ የወይራ ዘይት፣ የሩማን ፣ የቱፋህ (የልዩ
ልዩ ዓይነት ኮምጣጤ ዛፎችን ጨምሮ) 934.446 ዛፎች በግፈኛው የኢስራኢል ወታደር እጅ
ተነቅለው ተጥለዋል፡፡ ማሳዎቹን መልሶ ለማልማት የሚደረገውን ጥረት ለማዳከም ሲባልም
235 ቢዕሮች ተደፍነዋል፡፡ 841 የውኃ ማቆሪያ ገንዳዎች አገልግሎት እንዳይሰጡ ተደርገዋል፡፡
መጠነ ሰፊ የአትክትልትና ፍራፍሬ ማብቀያ መደቦች፣ 7‚900 የንብ ቀፎዎች፣ የአዝመራ ወቅት
ሰብሎች ከቀረቡት ዝርዝሮች ውስጥ ናቸው፡፡ በገዛ የወደብ ከተማ 3 የዓሳ ማስገሪያና ማሸጊያ
ጣቢያዎችን ጨምሮ አንድ ትልቅ የአትክልት ማስቀመጫና ማቀዝቀዣ ቤት ተደምስሰዋል፡፡
የርሻ መሳሪያ መጋዘኖች፣ ክምችት ቤቶች፣ ብቻ የግፍ ዱላ ያላረፈበት የለም፡፡ 156 የዶሮ እርባታ
ጣቢያዎች 89 የከብት / ፍየል ፣ በግ፣ ግመል/ ማደለቢያዎች ወድመዋል፡፡
በአካባቢው የተፈጥሮ ሚዛን ላይ
እየደረሰ ያለ መዛባት
በድምሩ 60.467.000 ስኩዌር ሜትር መሬት ቡልዶዝ ተደርጓል፡፡ በግሬደር
ተቆፋፍሯል፡፡ በታንክ እግር ታርሶ ለአገልግሎት እንደማይመች ሆኗል፡፡ የኢስራኢል ጦር

20 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

በፍልስጤማውያን ላይ ከሚጠቀመው ክልክል የጦር መሣሪያ በሚወጡ ጭሶችና መርዛማ


ጋዞች በተጨማሪ ሠፋሪ የሁዶች ሆን ብለው ወደ ፍልስጤማውያን መኖሪያ የበሚለቁት ጥራጊ
የአካባቢውን አየርና ውሃ ስለተበከለ በሚሊዩን የሚቆጠሩ ወፎች ርቀው ተሰደዋል፡፡ የአይሁድ
ሠፋሪዎች በዓመት 224‚000 ቶን ቆሻሻ ፍልስጤም ላይ እንደሚደፋ በአንድ ሌላ ጥናት(john
Reese) ተመልክቷል፡፡ የኢስራኢል ወታደር እየነቀለ ከሚጥለው በተጨማሪ እነዚህ ሠፋሪ
የሁዶች በየወንዙና በየእርሻ መሬት ላይ የሚደፉት ጥራጊ ባስከተለው የተፈጥሮ መበከል
250‚000 የወይራና የሌላም ዓይነት ፍሬ አብቃይ ዛፎች ባለፉት ሁለት ዓመታት(2001 እና
2002) ውስጥ ተበላሽተው ቀርተዋል፡፡
ለአካባቢ ተፈጥሮ መበከል አስተዋጽኦ ያደረገ ሌላም ነገር ይጠቀሳል፡፡ የኢስራኢል
ጦር ከተሞችን ሲቆጣጠርና ኬላዎችን ዝግ ሲያደርግ የማዘጋጃ ቤት የጽዳት መኪኖች ከከተማ
ውጭ ወዳለው የቆሻሻ መድፊያ ሄደው መድፋት አይፈቀድላቸውም፡፡ ከዛሬ ነገ ኬላቸው
ይከፍታሉ እየተባለ ውሎ ሲያድር ቆሻሻው ተጠራቅሞ ከተማው ለተላላፊ በሽታ መቀስቀስ
አስጊ መሆን ሲጀምር የተጠራቀመውን ቆሻሻ አግባብ በሌለው መንገድ (ማቃጠል፤ ወደ ወንዝ
መጣል…) እዚያው ከተማ ውስጥ ማጣራቱ የግድ ይሆናል፡፡ ውጤቱ የወንዞች፣ የምንጮች፣
የአየርና የአፈር ብክለት ነው፡፡ ይህም በተራው በመሬቱ ምርታማነት ላይ ችግር
እንደሚያስከትል ግልጽ ነው፡፡
ሌላው ነገር የኢስራኢል ጦር ንቅናቄ በሚያደርግበት ጊዜ ሆን ብሎ የሚያደርሰው
ጥፋት ነው፡፡ ገበሬዎች ለዓመታት ተንከባክበው የያዙትን መሬት ማበላሸትና ለመጪው ዓመት
ሠርተን እናገኝበታለን የሚል ተስፋ እንዳይኖራቸው ለማድረግ በሚወስደው አጥፊ ርምጃ
221.000 የገበሬው አጥሮች ፈርሰዋል፡፡ የድንጋይ ካቦች ተንደዋል፡፡ መስኖዎቹ ተቆፋፍረው
አለውል ጠፍተዋል፡፡ መሬቱ ከዓመት ወደ ዓመት የአፈር ጥበቃና እንክብካቤ እየጐደለው
ሲሄድ ምርታማነቱ እንደሚቀንስ አያጠያይቅም፡፡አሁን አሁን ደሞ የኢስራኢል መንግስት
የተጀመረው የኢፖርታይድ አጥር ግንባታ 26.000 ፍልስጤማዊ ዜጎችን ያለመሬት የሚያስቀር
ተግባር ነው፡፡በግንባታው ቅያስ መሠረት ምንጮችና ለም መሬቶች ወደ ሠፋሪው አቅጣጫ
እየተደረጉ ፍልስጤማውያን መሬት ላይ እየታጠረባቸው ነው፡፡
ቀጣዩ የኑሮ ጫና
በኢንዱስትሪና ንግድ ተቋማት ላይ እየደረሰ ያለው ውድመት በሥራና በቤተሰብ
ሕይወት ላይ ጫናውን እያሣረፈ መጥቷል፡፡ የፍልስጤማውያን ኑሮ መልኩን እየቀየረ ነው፡፡
የሥራ አጡ ቁጥር ወደ 43.7% አሻቅቧል፡፡ ስልሳ ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ኑሮው ከድህንነት
መሥመር በታች በፍጥነት እያሽቆለቆለ መጥቷል፡፡
እንግዲህ ከሞላ ጎደል እውነታውን ለማሳየት በተደረገው ሙከራ አንድ ነገር ግልጽ
መሆን አለበት፡፡ የኢስራኢል ወራሪ ጦር በፍልስጤምና ሕዝቧ ላይ እያደረሰ ባለው የማን
አለብኝነት ጥቃት የሰው ሕይወት፣ ቤትና ንብረት፣ ትምህርትና የትምህርት ሂደት፣ መሬትና

21 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

መሬቱ ያበቀለው ሁሉ ዒላማዎች ናቸው፡፡ ኑሮና ኑሮን ለማሸነፍ የሚደረግ እንቅስቃሴም


የጥቃቱ ዒላማ ነው፡፡
ይህ እኩይ ኃይል ፍልስጤማውያንን ጥግ እያስያዘና ኑሮ እያጠበባቸው ሲገኝ በሌላ
በኩል ደሞ በኃይል እያስለቀቀ በሚያሰፋው የፍልስጤም መሬት አይሁዶችን እያሰፈረ ይገኛል፡
፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብቻ 242 አዲስ የሠፈራ መንደሮች መቆርቆራቸው ተዘግቧል፡፡
ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመሩ የሚሄዱ የአይሁድ የሠፈራ መንደሮች፣ ከአንድ ሺ በላይ
ወታደራዊ ኬላዎችና ይዞታዎች፣ በአዲሱ የአፓርታይድ ግንብ ቅያስ መሠረት
ከፍልስጤማውያን ላይ እየተነጠቁ ወደ ኢስራኢል ይዞታነት እየተጨመሩ ያሉ ሰፋፊና ለም
መሬቶች፣……
ፍልስጤሞች የቀራቸው ነገር ቢኖር በምዕራብ ዳርቻና ጋዛ ሠርጥ አካባቢ ባጭር
ርቀት የታጠረባቸው ከተሞች፣ መንደሮችና የስደተኛ መጠለያ ካምፖች….
ወራሪው የኢስራኢል ጦር በኃይል በያዘው የፍልስጤም መሬት ላይ እየፈጸመ ያለው
ድርጊት በዓለም አቀፉ ሕግ አኳያም ቢሆን ከእውነት የማይገጥም ነው፡፡ እንደሚታወቀው
በጦርነት ያሸነፉ አገሮች ተሸናፊውን አገር ለተወሰነ ጊዜ ተቆጣጥረው መቆየት እንደሚችሉ
ይታመናል፡፡ ነገር ግን ከተያዘው አገር ላይ ስንዝር መሬት ወደራሳቸው መቁረስ፣ የራሳቸውን
ሲቪል ሕብረተሰብ እዚያ አምጥቶ ማስፈር በጭራሽ አይችሉም፡፡ የተቆጣጠሩትን አገር ሕዝብ
የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ማክበርም ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይሁንና ኢስራኢል
የፍልስጤምን ምድር በኃይል መያዝዋ እየታወቀ መሬት ትገምሳለች፡፡ የራሷን ሕዝብ አምጥታ
በፈለገችው ጊዜ የፈለገችው ቦታ ላይ ታሰፍራለች፡፡ ለፍልስጤማውያን የራስን ዕድል በራስ
የመወሰን መብትም አፍና እንደያዘች አለች-
ዳር-ያሲን ሰብራና ቨቲላ
ከዚያም ወዲህ ከዚያም በኃላ
እስከዛሬም የጊዜ ጥላ
የደም ጐርፍ ነው የደም አበላ
ቀጥሎ ያለው ሣያባራ -

ማቆሚያም የለው እንዴ


ሕፃን እሚቀጠፍበት ሳይል ዳዴ?

22 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

እያየም-- እንዳላየ
እየሰማም - እንዳልሰማ
እንዲሆን ተደርጐ ነውማ
ይህ ዓለም ቀልቡን የተቀማ
ኢስራኢሎች (በተለይም በአምሪካን አይዞህ ባይነትና ያልተቆጠበ ድጋፍ) በፍልስጤምና
በሕዝቧ ላይ ይህን ሁሉ ግፍ ሲፈፅሙና የማይረሳ በደል ሲያደርሱ ዓላማው ግልጽ ነው፡፡
1. ነዋሪውን ዐረብ ፍልስጤም የፈጁትን ፈጅተው፣ ያፈናቀሉትን አፈናቅለው፣
የተቀረውን በአፓርታይድ ግንብ(አሁን እንደጀመሩት) አጥረው -አገሪቱን የራሳቸው
ማድረግ፤
2. ሦስተኛውን የኢስላም ሐረም በመቆጣጠር ሙስሊሞች በዚያ ላይ ያላቸውን
የባለቤትነት መብት መንፈግ፤
3. ዐረቡ ዓለም መሃል እንደ አጥንት ተሸንቁረው ሲያደሙት መኖር
4. የአካባቢውን ገጽታ ለሙስሊሞች ሕብረት እንማይመች አድርጐ መቀየር…..
ይህ ነው ዓላማው፡፡ ከዚህ ውጪ ከታሪክ፣ ከሃይማኖት፣ ከሕግና ከሕሊና ፍርድም
አንጻር በቦታው ላይ አንድ ሐቅ ኖሮአቸው አይደለም -ኢስራኢሎች ይህን የሚያደርጉት
በአንፃሩ ዐረብ ፍልስጤማውያን ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ መከራ እያዩና እየተዋደቁ
ያሉት ከታሪክ፣ ከሃይማኖት፣ ከህግና ከኅሊና ፍርድም አኳያ ከተቀረው ሙስሊም ዓለም ጋር
የሚጋሩት ሐቅ በቦታው ላይ ስላላቸው ነው፡፡ እነሆ በቀጣይ የሚቀርበው የዚህ መፃፍ
ጭብጥም ይህንኑ አመላካች ይሆናል፡፡

23 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ምዕራፍ አንድ አራዲል ሙቀደሣ


የፍልስጤማውያን አመጣጥ
አል-ቁድስ፣ ሙስሊማዊት ከተማ
የአል-ቁድስ ሐረምነት ፣ በቁርአንና በሐዲስ
በይት አል-መቅዲስ ፣ የኢስላም ምሽግ

የፍልስጤማውያን አመጣጥ
ከዒሣ ኢብን መርየም ዐለይሂ ሰላም መምጣት ምናልባትም 25 ክፍለ ዘመናት ቀደም
ብሎ በቦታው ላይ አራምዩች ነበሩ፡፡ ቀጥሎ ከነዓኒዩች ወደ ስፍራው ፈለሱ፡፡በመቀጠልም
ከወደ ትንሹ አስያ ወይም ከሙተወስጥ የባሕር ደሴቶች ግድም ፍልስጤማውያን መጡ፡፡
የመስርን ጠረፋማ ከባቢዎች በመውረር ወደ ሰሜን አቅንተው በጁዲያ ተረተርና በባሕሩ መሀል
በሚገኘው ትልቁ ሸለቆ ላይ ሠፈሩ፡፡ ከዛ ጊዜ ጀምሮ በቦታው ላይ የነበሩና ዛሬም ያሉ ናቸው፡

ቬስፖሲየን፣ ቲትስ፣ ትራጃን እና ሐድሪያን እንዲሁም የተለያዩ ክርስትያን ነጋሢዎች
በየተራ ባደረሱባቸው አውዳሚ ጦርነት የተነሳ አይሁዶች ከነሥርዐተ-ወጋቸው ተንኮታኩተው
ስብርባሪያቸው በአራቱ የሰማይ መስኮቶች ተበትኗል፡፡
“….ለሰላምሽ የሚሆነውን በዚህ ቀን አንቺስ ስንኳ ብታውቂ፣ አሁን ግን
ከዓይንሽ ተሰውሮአል፡፡ ወራት ይመጣብሻልና፣ ጠላቶችሽም ቅጥር ይቀጥሩብሻል
ይከቡሻልም፣ በየበኩሉም ያስጨንቁሻል፣ አንቺንም በአንቺም ውስጥ የሚኖሩትን

24 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ልጆችሽንም ወደታች ይጥላሉ፣ በአንቺ ውስጥም ድንጋይ በድንጋይ ላይ አይተውም፣


የመጐብኘትሽን ዘመን አላወቅሽምና”-(የሉቃስ ወንጌል ምዕ 19፡41-44)
“ግና አጼ ሐድሪያን (ኢሊዩስ ይባልም የነበረው) እየሩሳሌምን እንደገና ገነባት፡፡
የጌታንም መቅደስ እንደገና አሳነፀው፡፡ የከተማይቱን ጠረፍም እስከ ዳዊት ግንብ አሰፋው፡፡
በቀድሞ ዘመን የዳዊት ግንብ ከከተማይቱ ዐውደ ክልል ማለፊያ ርቀት ነበረው፡፡ (ማንም ሰው
ከማውንት ኦሊቨ ላይ ሁኖ ማስተዋል እንደሚችለው የከተማይቱን ምዕራባዊ ጠረፍ የትጋ ድረስ
እንደነበረና ከዛ ወዲህ የቱን ያህል እንደጨመረ መረዳት ይችላል)፡፡ አፄ ሐድርያን ከተማይቱን
አስገንብቶ ሲያበቃ በራሱ ሥም “ኢሊያ” ብሎ ጠራት ትርጉሙም የአምላክ ቤት ማለት ነው፡፡
"wright, the travels of sawult, Ad 1102 and 1103, travels in Palestine, p.37::
በ17 ዓ.ሂ/ 638 ክዘ ሙስሊሞች አል-ቁድስንና የፍልስጤምን መሬት ከክርስትያናዊው
የቢዛንታይን ኢምፓየር በማስለቀቅ ነጻ አወጡ፡፡ የቢዛንታይን አገዛዝ በኖረበት ዘመን ሁሉ
(ከ132-638 ክዘ)፣ ለ500 ዓመታት ማለት ነው የሁድ የተባሉ ዘሮች ወደ ቁድስ እንዳይገቡ
ጥብቅ እገዳ ተደርጐባቸው ወደዛ ድርሽ አይሉም ነበር፡፡ ነገር ግን በሙስሊሞች አገዛዝ ስር
ወደተቀደሰችው የአል-ቁድስ ከተማ መመለስና በሰላም መኖር ቻሉ፡፡
እንደገና ከ600 ዓመታት በኋላ ሙስሊሞች አል-ቁድስን ከሳሊቢዩን (የመስቀል
ጦረኞች) ነፃ አወጡ፡፡ ሳሊቢዩን ጅምላውን ማህበረ አይሁድ ካፈናቀሉ በኃላ የተቀሩትን
የሁዶች ወደ ቅድስቲቱ ከተማ እንዳይደርሱ እገዳ አድርገውባቸው ነበር፡፡እንደገናም
ሙስሊሞች እገዳውን በማንሳት ወደ ቅድስቲቱ ከተማ መመለስ እንዲችሉ ፈቀዱላቸው፡፡
አሁን በቦታው ላይ የሚገኙትን የሁዶች የቅርብ ጊዜ መጤ ከመሆናቸውም ሌላ
የአካባቢው ነጻነት በሩቅ ዘመን ሃይላት በተደፈረ ቁጥር አደጋውን መክቶ በመመለስ ረገድ
አንድም ጊዜ ይህ ነው የሚባል ሚና ኖሮአቸው አያውቁም፡፡
የሚገርመው ግን እንደገና ከሌላ 600 ዓመት በኃላ መሆኑ ነው የአውሮፓ ጽዮናውያን
እራሳቸውን በማሰባሰብና በምዕራቡ የክርስትያን ቅኝ አገዛዝ ሃይሎች በተለይም በእንግሊዝና
በተባበረው አሜሪካ ልዩ ድጋፍ ሙስሊሞችን ከፍልስጤም ምድር ገፍቶ ለማስወጣት፣ በ3ኛው
የኢስላም ሐረም በሆነው በመስጂጅ አል-አቅሳ እንዳይሰግዱ ለማድረግና በሐረም አል-
ኢብራሂም (በኸሊል ውስጥ) የሙስሊሙን ደም ለማፍሰስ በሙሉ ሃይል ተጠናክረው
የመምጣታቸው ነገር ነው፡፡

አል-ቁድስ ሙስሊማዊት ከተማ


አል-ቁድስ ሙስሊማዊት ከተማ ናት፡፡ ሙስሊማዊት ከተማ የመሆኗ እውነታ
ከአስተውሎት የራቀ አይደለም፡፡ ግልጽ ነው፡፡
“Three branches of monotheism have flourished in Jerusalem first the
jewish, then the Christian, and finally the muslim, All three still flourish

25 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

there, but it is well to remember that the historic city of Jerusalem has
been a muslim city, as it stiil predominantly is, for much longer than it
ever was either a jewish or a Christian city “stewart perowne: Jerusalem
& bethelehem, new York,1965.p2
“በኢየሩሳሌም ሦስት የአሃዳዊ እምነት ቅርንጫፎች አብበዋል፡፡ መጀመሪያ
የአይሁዶች ከዚያም የክርስትና፡፡ በመጨረሻም የሙስሊም፡፡ አስካሁንም እንዚህ ሶስቱ በዚያ
እንዳበቡ ይገኛሉ፡፡ነገር ግን ታሪካዊት ኢየሩሳሌም ልክ በዛሬው ግዜም በአመዛኙ ሆና
እንደምትገኘው፣ የአይሁድ ወይም የክርስትያን ከተማ ከነበረችው ይበልጥ ለረጂም ጊዜ
ሙስሊማዊት ከተማ እንደነበረች ማስታወስ ተገቢ ነው፡፡ “ ስቲዎርት ፔሩኒ እየሩሳሌም እና
በይትለሐም - ኒውዩርክ 1965 ገጽ 2፡፡
እነሆ አል-ቁድስ ሙስሊማዊት ከተማ ስለመሆኗ፣ በይት አል-መቅዲስና ዙርያው
የሻም መሬት ወይም “ትልቁ ሱርያ” በመባል የሚታወቀው አካባቢ “አርደል ሙቀደሣ (የተባረኩ
መሬቶች) ስለመሆናቸው ከበቂ በላይ አረባዊና ኢስላማዊ ማገናዘቢያዎች አሉ፡፡ በፊሊስጢን
ነዋሪ የሆኑት አረቦች ሥረ-መሠረታቸው ከራሱ ከክልሉ ቅድመ ታሪክ በፊት ነው፡፡ ከታሪክ
ንጋት ጀምሮ የከንዓን ምድር በመባል በሚታወቀው አገር የነሱ መኖር ከአስር ሺህ ዓመታት
በፊት የጀመረ ነገር ነበር፡፡ መላው ታሪክና የቁፋሮ ሠነዶች (እራሱን ብሉይ ኪዳንን ጨምሮ)
ይህንኑ እውነታ ያረጋግጣሉ፡፡
ከመቶ ዓመት በፊት ያውም ሣይንሳዊ የምርምር ባሕል ገና ዳዴ በሚልበት ዘመን ላይ
ጥናቱን ያካሄደውና “Palestine illustrated” በሚል ርዕስ የጥናት ውጤቱን ያቀረበው ሰር
ረቻርድ ቴምፕል በፍልስጤም ማዕከላዊ ተረተር ስለሚኖሩ ሕዝቦች እንዲህ ይላል “… they
are veritable descendants of the Canaanites described in the bible of the
jebusites and amorites”
“…እነሱ በመጽሃፍ ቅዱስ ከተጠቀሱት ዩቡሲዩች / ኢያቡሳውያንና አራምዩች / አሞራውያን
የከነዓን ወገኖች የመጡ ( መምጣታቸው የታወቁ) ናቸው፡፡”
በዚህ ጉዳይ ዙርያ ሰር ጄምስ ፍራዘር ‘folk-lore in the old testament’ በተሰኘው
መድብሉ ቅጽ 1 ገጽ 417 ላይ የሚከተለውን ብሏል፡፡ የጹሑፍ ጥንቅር የመጀመሪያው ታሪካዊ
ግኝት በ “ገዘር” ከተደረገ በኃላ ነበር፡፡ ከተናገራቸው ነገሮች ሁሉ “ It is the opinion of
competent judges that the modern fellahin of Arabic speaking peasants of
Palestine are descendants of the tribes which dwelt there before the Israelite
invasion and have clung to the soil ever since. Being submerged but never
destroyed by each successive wave of conquest which has swept over the land”
“ይህ የብቁ ሊቃውንት አስተያየት ነው፡፡ እነዚህ አረብኛ ተናጋሪ የሆኑ የፍልስጤም ገበሬዎች
(ዘመነኞቹ ፈላሒን) በቦታው ላይ የኢስራኢል ወረራ ከመካሄዱ በፊት ነዋሪ ከነበሩ ነገዶች
የመጡ ናቸው፡፡ ከዛ ጊዜ ጀምሮ ዝንተ አለማቸውን አፈሩን የሙጥኝ ብለው፤ አካባቢው

26 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

በተከታታይ ወራሪዎችና ቅኝ አድራጊ ሃይሎች ማዕበል ሲመታ ውስጡን ተቀብረው ነገር ግን


ተነቅለው ሳይጠፉ ያሉ ናቸው“
በኢየሩሳሌም ይኖር የነበረውና በተሟላ ማቴሪያል በመደገፍ ጥናቱን ያቀረበው
አሜሪካዊ ቄስ canon c.t. bridgeman በበኩሉ የሚከተለውን አስተያየት እንዳሰፈረ እናያለን
- “…when, therefore, the Jews now return to the holy land, they should remeber
that the native population represents a stay at-home brother, who, though he
has married foreign wives, has by his faithfulness in maintaining the family
estate established no mean claim to enjoy it,”(bible lands,jan, 1939)
“…እና እንግዲህ አሁን የሁዶች ወደተቀደሰው ምድር ሲመለሱ፣ ያገሬው ሕዝብ ’ባገር ቤት የቆየ
ወንድም’ ተምሣሌት እንደሚወክል መረዳት አለባቸው፡፡ ምንም እንኳን ’ይሄ ባገር ቤት የቆየው
ወንድም’ ባዕድ ሚስቶች ቢያገባም በታማኝነት የቤተሰቡን ርስት ጠብቆ በማቆየቱ (በርስቱ ላይ
ለኔ ብቻ የማለት) ሰገብጋባ አቋም አልያዘም” – edwardes pp.9-10
ግና! ይሄ ወደተቀደሠው ምድር የተመለሰ የሁዲ በቁጣና በጥላቻ ተሞልቶ የመመለሱ
ብዛት ያላንዳች ይሉኝታ ’ባገር ቤት የቆየውን ወንድም’ ጨርሶ ለማውደም ያላደረገው ጥረትና
አሁንም እያላደረገ ያለው ነገር የለም፡፡
በመሆኑም እነዚህ በቁጣና በምሬት ተሞልተው የተመለሱ ጽዮናውያን በተገኙበት
ሁሉ ሊነገራቸው ይገባል
1ኛ. በ7ኛው ክ/ዘመን አል-ቁድስንና የፍልስጤምን መሬት ከቢዛንታይን የአገዛዝ
ቀንበር ሥር ነፃ ለማውጣት፣ እነሱንም የሁዶችን ወደቁድስ እንዳይገቡ በማገድ ነፃነታቸውን
ረግጦ የኖረውን የግፍ ሃይል ለማስወገድ በተካሄደው ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ አረብ
ሙስሊሞች ሸሂድ ሆነዋል፡፡
2ኛ እንደገናም በ12ኛው ክ/ዘመን ከነዚያ ከመስቀል ጦረኞች፣ (የሁዶችን
በመጨፍጨፍና ወደቁድስ ድርሽ እንዳይሉ እገዳ ጥለውባቸው ከኖሩት) ነፃ ወራሪ ሃይሎች
የግፍ አገዛዝ ኢየሩሳሌምና ፍልስጤምን ነጻ ለማውጣት በተደረገው ሌላ ጦርነት በሺዎች
የሚቆጠሩ ሙስሊሞች በሂደት ተሰውተዋል፡፡ በመስጂደል አቅሳ ውስጥ ብቻ ከ 70 ሺህ በላይ
የሚሆኑ ሙስሊሞች በሳሊቢዩን የግፍ ርምጃ መጨፍጨፋቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ኢብነል
ጀውሲይ “አል-ሙንተዚም” ቅጽ 17 ገጽ 47፡፡
እና ይሄ ሁሉ ሲሆን ዛሬ በፍልስጤም መሬት ላይ የባለቤትነት ጥያቄ ያነሱትና
ከቀደምቱ የሁዶች የመጣን ነን ባዮች፣ ያን ጊዜ ያ ሁሉ ሲሆን የነሱ ቅድመ አያት የሚሆኑት
የሁዶች የት ነበሩ? ያሰኛል፡፡ የሚገርመው ደሞ ለይገባኛል ጥያቄያቸው መሠረት ያደረጉት
ብሉይ ኪዳን“ የሚሰኝ ከአፈታሪክ እምብዛም ያልተሻለ መጽሐፍ ነው፡፡ እዚህ ላይ አንድ
መነሳት ያለበት ነጥብ አለ፡፡ ዛሬ በዚህ ዘመን በየትኛውም የምድር ማዕዘን አንድ ሰው ቢነሳና
“ብሉይ ኪዳንን” እነደመረጃ ይዞ በሆነ ንብረት ላይ የይገባኛል ጥያቄ በማንሳት ወደ ፍርድ ቤት

27 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ቢሄድ፣ እውን ፍርድ ቤቱ እንደበቂ ሕጋዊ ሠነድ ቆጥሮለት የጠየቀውን ንብረት ሊፈቅድለት
ይችላል ወይ?... ፍርዱን ለአዕምሮ ባለቤቶች፡፡

የአል-ቁድስ ሐረምነት ፣ በቁርአንና በሐዲስ


ከጥንት ጀምሮ በዚህ ዓለም ላይ የተወሰኑ ሥፍራዎች ለአምልኮ ሥርዓት የተከለሉ
ናቸው፡፡ የአል-ሐረም አሸ-ሸሪይፍ ተራራ ከነዚህ አንዱ ነው፡፡ በብዙ መቶ ዓመታት ከሱለይማን
(ዐለይሂ ሰላም) ዕድሜ ዘመን ይረዝማልም፡፡

በቁርአን
ከኢብራሂም ዐለይሂ ሰላም በፊትም ቢሆን ሥፍራው መስዕዋት ማቅረቢያ ነበር፡፡
“እነሆ ያ አባት ወደዚህ ከፍታ በመውጣት በልጁ በኢስሐቅ ምትክ የበግ መስዕዋት አቀረበ” -
(the sacrificed son of Abraham is ismael and not isacc) የተሰዋው የአብራሃም ልጅ
ኢስማኢል እንጂ ኢስሐቅ አይደለም.stoddard, p.141)
በኢስላም የቁድስ ሐረምነት ከሁሉ አስቀድሞ ከቁርአን የመጣ ነው፡፡ በይት አል-
መቅድስን እና መስጂደል አቅሳን በተመለከተ አላህ ሱብሃን ወተዓላ እንዲህ ይላል

“ያ ባሪያውን (ሙሐመድን) ከተከበረው መስጊድ ወደዚያ ዙሪያውን ወደ ባረክነው


ወደ ሩቁ መስጊድ (በቁድስ ውስጥ ወዳለው ሩቅ መስጊድ) በሌሊት ውስጥ ያስኬደው (ጌታ)
ጥራት ይገባው…” (አል-ኢስራእ 17፡1)
እውቁ ሙፈሢር ሙሐመድ ኢብን ጀሪይር አ-ጠበሪይ የቁድስን ቅድሥና በተመለከተ
ብዙ ቁርአናዊ አያዎች መኖራቸውን ይናገራሉ፡፡ ቢያንስ አስር አያዎች አሉ፡፡
የሙስሊሞች የቁድስ ግንኙነትም ቢሆን ረጂም ዕድሜ ያስቆጠረ ክስተት ነው፡፡ የነቢዩ
ሙሐመድ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም የነብይነት ተልዕኮ ሲጀምር አብሮ የጀመረ ነገር ነው፡፡ ነብዩ
ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም በተልዕኳቸው ንጋት እሳቸውና ቀደምቱ ሙስሊሞች መካ ውስጥ
በነበሩበት ጊዜ ለ13 ዓመት ወደ ቁድስ ተቅጣጭተው ይሠግዱ ነበር፡፡ በመዲናም ቂብላው
በአላህ ፈቃድ ወደ መካ እስከተቀየረበት ጊዜ ድረስ፤ ለ16 ወራት ወደ ቁድስ ዞረው ሲሰግዱ
ቆይተዋል፡፡

28 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

“የፊትህን ወደ ሰማይ መገላበጥ በእርግጥ እናያለን፤ ወደምትወዳትም ቂብላ እናዞርሃለን፤


ስለዚህ ፊትህን ወደ ተከበረው መስጊድ (ወደካዕባ) አቅጣጫ አዙር፤ የትም ስፍራ ብትሆኑም
(ሙስሊሞች) ስትሰግዱ ፊቶቻችሁን ወደርሱ አቅጣጫ አዙሩ፤….”(አልበቀራህ 2፡144)
ታላቁ አሊምና የነብዩ(ሰዐወ) ሰሃባ የነበሩት አብደላህ ኢብን አባስ(ረዐ) ሲናገሩ፣
“ነብዩ(ሰዐወ) መካ በነበሩበት ጊዜ ካዕባ ከስተፊታቸው ሆኖ ወደ በይት አል-መቅዲስ
ዞረው ይሰግዱ ነበር፡፡ ወደ መዲና ከተሰደዱም በኃላ ለ16 ወራት ወደ በይት አል-መቅዲስ
ዞረው ሲሰግዱ ከቆዩ በኃላ ወደ ካዕባ ተዞሩ” ይላሉ ፡፡ (ኢማም ሱዩጢ ጃሚዕ አሓዲስ)
ኢሥራዕ ወልሚዕራጅ - ከመካ ወደ በይት አል-መቅዲስ የተደረገው የነብዩ (ሰዐወ)
የለይል ጉዞ፣ ከዚያም ወደ ሠማይ የተደረገው እርገትና ደርሶ መልሱ ለበይት አል-መቅዲስ
በኢስላም ውስጥ ቋሚ ሁኖ እስከቂያማ ሚዘልቅ የሐረምነት ደረጃ ሲያጎናጽፋት ችሏል፡፡
አንዳንድ ኦሪየንታሊስት በአብዛኛው የሁዶች ይህ መስጂደል አቅሷ በኢየሩሣሌም
ሣይሆን ዓለም ውስጥ ሌላ የሆነ ቦታ ያለ ነው ይላሉ፡፡ መሐመድ እንደነሱ አባባል “ቁድስን
የተጠቀመው እራሱን ከየሁዶች ለማገናኘትና እውቅና ለማግኘት ሲል ነው፡፡”
ነገር ግን ሙሐመድ(ሰዐወ) ለማግኘት እንደፈለጉ የሚነገርላቸው እውቅና ከማን
ይሆን ?-እውቅና ማግኘት ከማን? ከአረቦች? ከክርስትያኖች? ከየሁዶች?
ከአረቦች ?- አረቦች በዚያን ጊዜ ስለየሁዶችና ስለዲናቸው ቅንጣት ደንታ
አልነበራቸውም፡፡ስለዚህ ሙሐመድ(ሰለ አላሁ አለይሂ ወሰለም) የዐረቦችን እውቅና ለማግኘት
በምንም መልኩ እራሳቸውን ከአይሁድና ከሃይማኖታቸው ማገናኘት አላስፈለጋቸውም፡፡
ከክርስትያኖች?- ክርስትያኖች ያን ጊዜ በየሁዶች ላይ ጦርነት ካወጁ ቆይተዋል፡፡
ኢየሱስን ዐለይሂ ሰላም “ሰቅለዋል” በሚል ውንጀላ በጠላትነት ፈርጀው ወደ ኢየሩሳሌም ድርሽ
እንዳይሉም እገዳ እንደጣሉባቸው የሚታወቅ ነው፡፡ በዚህና በዚያ ከምድር ገጽ ሊያጠፏቸው
ተቃርበውም ነበር፡፡ስለሆነም ነብዩ (ሰለ አላሁ ወሰለም) ለምን ብለው ከአይሁድ ነኝ ይላሉ?
ከአይሁድ ነኝ በማለት ከክርስትያኑ ጐራ እውቅና ማግኘት ቢኖርባቸው እራሳቸው ክርስትያኖቹ
ለአይሁድ ከበሬታና ፍቅር ቢኖራቸው ነበር፡፡ሃቁ ግን ይህ አልነበረም፡፡
ከራሳቸው ከየሁዶች?- ከአይሁድ እውቅና ማግኘት ፈልገው ነው እንዳይባል ደሞ
በጊዜው የሁዶች (በ7ኛው ክፍለ ዘመን)እዚህ ግቡ የሚባሉ አልነበሩም፡፡አንቱ ሚያሰኝ ተፅዕኖ
ማሣደርም ሆነ ጦርነት ለማወጅና ለየትኛውም ወገን ድጋፍ ለመስጠት የሚያስችላቸውን አቅም
አልነበራቸውም፡፡ አይደለም ለሌላው ተገን መሆን ለራሳቸውም እንኳን የሚደርስባቸውን በደል
ለመገፍተር የሚችሉ አልነበሩም፡፡ እየተነሣ አዛ የሚያደርጋቸውን ሁሉ ተሸንፈውለትና
ተናንሰው ይኖሩ የነበሩ ናቸው፡፡

29 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ይበልጥ ደሞ ኢስራዕና ሚዕራጅ በሆነበት ወቅት በቁድስ ውስጥ አንድም የቋጥኝ


ፍላጭ “እኔ የሁድ ነኝ” የሚል አልነበረም፡፡
በዚያ ጊዜ ንጉስ ሐድርያን አይሁድ የተባለ ሁሉ አይደለም በቁድስ መኖር ሲሳለም እንኳን እዚያ
ድርሽ እንዳይል አዋጅ አስነግሯል፡፡
የቢዛንታይን ገዢ ቀይስር ሂረቅል በ630 ክ/ዘ ወደ ኢየሩሳሌም በመጣ ጊዜ
ሐድራዊውን ድንጋጌ እንደገና ከማጽደቁም በላይ ተጨማሪ ማሻሻያ በማድረግ ከከተማይቱ
እምብርት የ3 ማይሎች ርቀት አንስቶ ለአይሁድ የተከለከለ ቀጠና እንዲሆን ወስኗል፡፡ በ634
ክ/ዘ ሌላም ሃሳብ ወጥኖ ነበር፡፡ በግዛቱ ደቡባዊ ጠረፍ ላይ ሙስሊሞች በከፈቱት ዘመቻ
ፍፃሜ ሳያገኝ ቀረ እንጂ የሁዶች ሁሉ ተገደው በክርስትና እንዲጠመቁ የማድረግ ሰፊ እቅድ
ነበረው፡፡
ከ630 ክ/ዘ ግድም ጀምሮ ሙስሊም ሙጃሂዲን በቤዛንታይን ኢምፓየር ጠረፋማ
ቀበሌዎች መታየት ሲጀምሩ፣ ንቁ ደጋፊዎቻቸው የሁዶች ነበሩ፡፡ ምክንያቱም የሁዶች
መለኮታዊውን ተልዕኮ በመውጣት ላይ የነበሩትን አረብ ሙስሊሞች እንደ አዳኞቻቸው ነበር
ያዩዋቸው፡፡
ሌላም በዋቢነት የሚጠቀስ ደሊል አለ፡፡ ካዕብ አል-አሕባር በየመን ራቢ የነበረና
በኸሊፋ ዑመር (ረዐ) ዘመን የሰለመ የሁዲ ነበር፡፡ ሙስሊም ሙጃሂዲን ቁድስን ነፃ ሲያወጡም
በቦታው ላይ ተገኝቷል፡፡ የመስጂዱን ቦታ በተመለከተ ከአሚረል ሙዕሚኒን ዑመር ኻጣብ
(ረዐ) ጋር የተካረረ ምልልስ ያደርጋል፡፡ በመጨረሻም ዑመር ረድየሏሁ ዐንሁ ይህን ያልተገራ
አይሁዳዊ ጸባዩን ወዲያ እንዲተው ከገጸሱት በኃላ እሳቸውና ወታደሮቻቸው በመስጂዱ ቦታ
ላይ ሮማውያን የቆለሉትን ቆሻሻ ማጽዳት ይጀምራሉ፡፡ይህን ጊዜ ካዕብ አንድ ነገር ትውስ
አለውና ተናገረ
“አሁን አንቱ ሚሰሩትን ስራ አንድ ነብይ ከ500 ዓመት በፊት ተናግሮት
(ተንብዬት)ነበር“ አላቸው፡፡
ዑመር(ረዐ) እኮ እንዴት? አሉት
ካዕብ ፣ “ሮማውያን በኢስራኢል ልጆች ላይ ተነሡ፣ አሸነፋዋቸው፡፡
ቦታውን የፍግ መጣያ አድርገውት ቀበሩት፡፡ ከዚያም በኒ ኢስራኢል በሮማውያን
ላይ ድል አገኙ፡፡ ነገር ግን ጊዜ አግኝተው ሳያፀዱት በፊት ፋርሳውያን መጡባቸው፡
፡ ወጉና አሸነፋቸው፡፡ በኒ ኢስራኢል በነሱ እጅ ለጭቆና ተዳረጉ፡፡ ከዚያም
ሮማውያን መልሰው ፋርሶችን በማሸነፍ እስከናንተ መምጣት ድረስ ቆዩ፡፡ አላህ
በፍጉ ተራራ ላይ ነብይ ላከና ተናገረ -“አርሻሊም ሆይ! ደስ ይበልሽ! ፋሩቁ
ከጉድፍሽ ያፀዳሻልና“ …(ታሪኽ አጥ-ጠበሪይ ቅጽ 3፡ ገጽ 611-612)

30 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ከዚህ አኳያ የሙሐመድንና የተከታዩቻቸውን እውቅና ማግኘት ቢፈልጉ የሁዶች


እንደነበሩ መረዳት እንችላለን፡፡ ተገዶ ከመጠመቅና ከምድረ ገጽ ከመጥፋት ለመዳን
የሙስሊሞችን እውቅና ማግኘት ነበረባቸው፡፡ በርግጥም ሙስሊሞች ደርሰው የሁዶችን
ከጥፋት ታደጉዋቸው፡፡ ዲናቸውን እንዲጠብቁም ረዱዋቸው፡፡ ከዚህ ውጭ ሙሐመድ
(ሰዐወ) ያልነበረ ሐረግ መዝዘው ከኢብራሂምና ከኢስማኢል ዘር ሊቆጥሩ ሞክረው ቢሆን ኖሮ
ባጠቃላይ አረቦች በተለይም ቁረይሽ (በእርግጠኝነት የዘር ሐረጋቸውን እስከ አደም ዐለይሂ
ሰላም ድረስ ያውቁት ስለነበር በጣም ይስቁባቸውና ይሳለቁባቸው ነበር፡፡ ስለዚህ ሙሐመድ
(ሰዐወ) የአይሁዶችን ቅበላና እውቅና ፈልገው ነበር ማለት መሠረተ ቢስ ነው፡፡

አል-ቁድሥ፣ በሐዲስ
የቁድስን ሐረምነት የሚያመለክቱ በርካታ ነብያዊ ሐዲሶች አሉ፡፡ በአቡበከር አል-
ኻቲብ በተዘጋጀውና The virtue of Al-Quds በሚለው ጥንቅር ውስጥ ብቻ 165 ሃዲሶች
ተጠቅሰዋል፡፡ የትኛውንም የሐዲስ መድበል ያገላበጠ ደሞ የቁድስንና የመስጂደል አቅሷን
ቅድስና የሚያወሱ ሃዲሶች ብዙ እንደሚገኝ ነው፡፡ ከመሠል ብዙ ብዙ ሐዲሶች በሲሐነቱ
የሚታወቀውና ነብዩ (ሰዐወ) በይት አል-መቅዲስንና የአቅሷ መስጂድ ያደነቁበት ሃዲስ ተጠቃሽ
ነው፡፡ ነብዩ (ሰዐወ) በዚህ ሃዲስ አማካይነት ወደ አቅሷ የሚደረገውን የተቀደሰ ጉዞ በድንጋጌ
እንዳፀኑት እናያለን፡፡

ወደነዚህ ሦስቱ መሣጂዶች ቢሆን እንጂ ወደሌላ መንፈሣዊ ጉዞ አይደረግም፣


“እዚህ በኔው መስጅድ፣ መካ መስጂደል ሐራም እና መስጅደል አቅሷ” (ቡኻሪ
ሙስሊም)
ይህም ብቻ ሳይሆን ነብዩ (ሰዐወ) በሁለቱ ቅዱሣን መስጂዶች (በካዕባ እና በመስጂደል
አቅሷ) መሃል የነበረውን የምሥረታ ጊዜም ነግረውናል፡፡
አባዘር(ረዐ)፣ የአላህን መልዕክተኛ ጠየኳቸው አሉ “የትኛው መስጂድ በምድር ላይ ቀድሞ
እንደተሰራ?”
 “የተቀደሠው መስጂድ /ካዕባ” አሉኝ
 “ከዚያስ(የትኛው መስጂድ)?” አልኳቸው
 ∙“አል-መስጂድ አል-አቅሷ” አሉኝ∙
 “በመሃከላቸው ስንት ዓመት አለ?“ አልኳቸው

31 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

 “አርባ ዓመት ካሉኝ በኃላ በማያያዝም የሰላት ወቅት በደረሰበት ቦታ የትም ቢሆን
ስገዱ፣ ምክንያቱም መላው ምድር መስገጃ ነውና አሉኝ - (ሙስሊም)
ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህም ብለዋል
“ከመሬቶች ሁሉ የአላህ ምርጫ ኢየሩሳሌም ናት፡፡ በኢየሩሣሌም የወረደ ጤዛ
ለማንኛውም ህመም ፈውስ ነው፡፡ ምክንያቱም ከገነት የነጠበ ነውና” (ኢብኑል ጀውሲይ ታሪኽ
በይተል መቅዲስ)፡፡
አልቁድስ በኢስላም ልዩ ቦታ ናት፡፡ ሐረምነቷ /ቅድሥናዋ እስከቂያማ ቀን እንደተጠበቀ
ይቀጥላል፡፡ ሠዎች ሁሉ በምድር ሕይወት የሠሩትን ዋጋ ያገኙ ዘንድ በፍርዱ ቀን በሷ
ይሰበሰባሉ፡፡ ስለዚህ ሙስሊሞች ሊጎበኟትና በመስጂዳም ሊሰግዱ ተገባቸው፡፡ በዚህ ላይ
የነብዩ አቋም ግልጽ ነው-
መይሙናህ የምትባል ሴት ወደነብዩ (ሰዐወ) በመቅረብ “ስለቁድስ ይንገሩን”
አለቻቸው፡፡
“በፍርዱ ቀን የሰው ሁሉ መሰብሰብያ ስፍራ ናት ልትጐበኛትና በመስጂዷ (መስጂድ አል-
አቅሷ) ተገኝተሸ ልትሰግጂ ተገባሽ ፡፡ ምክንያቱም በመስጂደል አቅሷ ውስጥ የተሰገደ ሠላት
በሌሎች መስጂዶች ከሚሰገዱ 500 ሠላቶች ጋር በደረጃ እኩል ነው” አሉዋት፡፡ በመቀጠልም
መይሙናህ- “ወደዛ መሄድ ባልችልስ - ምን ላድርግ?” አለች፡፡ ነብዩ (ሰዐወ) “በፋኖሶቿ ውስጥ
የሚቀጣጠ”ል የዘይት ስጦታ ላኪ፡፡ ማንም ቢሆን እንደዛ ቢያደርግ፣ ልክ(በቦታው ላይ ተገኝቶ)
እንደጐበኛት ይቆጠራል” (ኢብን ማጃህ)

በይት አል-መቅዲሥ፤የኢስላም ምሽግ


በይት አል-መቅዲሥ የኢስላም ምሽግ ናት፡፡ነብዩ(ሰዐወ) ለአቡ ዑበይዳህ ቢን ጀርህ
እንዲህ አሉት፣ “መከራና ፈተና ሲሆን በበይት አል-መቅዲስ ተጠለል”
አቡ ዑበይዳ ፣ “ያረሱሉሏህ! ወደበይት አልመቅዲስ መድረስ ባልችልስ? ነብዩ(ሰዐወ)፣
“ገንዘብህን መጽውትና ኢማንህን ያዝ (አጥብቅ)”-
በሙስሊሞች ላይ መከራና ሥቃይ ሲሆን ደግ መጠለያ ሚሆናቸው በይተል መቅዲስ
ነው፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩ በኋላ ተከታዬቻቸው የሻምን መሬት ፣
ፍልስጥኤምንና በይተል መቅዲስን ነፃ ለማውጣት ባደረጉት ወሣኝ ጦርነት አቡ ዑበይዳህ ቢን
ጀረህ(ረ.ዐ) የጦር አዛዥ በመሆን መርቷል፡፡ በዚህ ሃላፊነት ላይ እያለም ሞቶ በተቀደሰው
የፍልስጤም ምድር ተቀበረ፡፡
የበይተል መቅዲሥ ሠዎች የኢስላምና የሙስሊም ተከላካይ ሃይል ናቸው፡፡ የሻም
መሬት፣ በይት አል-መቅዲሥ ፣ እና መስጂደል አቅሷ እነዚህ በአላህና በረሱል(ሰዐወ) የተባረኩ

32 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ቅዱሣን ሥፍራዎች ናቸው፡፡ ነዋሪዎቹም የኢስላምና የሙስሊሙ ኡማህ የፊት መሥመር


ተሠላፊዎች በመሆን ሁሌም በአላህ መንገድ ይዋጋሉ፡፡ በገቡበት ፍልሚያ እስከፍርዱ ቀን
ሁልጊዜ አሸናፊ ናቸው፡፡እስካሁን የታዩት ያካባቢው ታሪኮች ይህንኑ በተደጋጋሚ ያረጋግጣሉ፡

የሻምና የበይተል መቅዲሥ ጀግና ሕዝቦች ከሌላው ሙስሊም መሬት በተለይም
ከግብጽና ከኢራቅ በተገኙ ሙስሊም ወንድሞቻቸው ፅኑ ትብብር የመስቀል ጦረኞችን፣
ሞንጎሎችን፣ እንግሊዝን፣ ፈረንሣይን በየተራ እየገጠሙ ድባቅ መምታታቸው በታሪክ
ተመዝግቦ ያለ ነው፡፡ እነሆ ዛሬም እነዚሁ ሕዝቦች ከጽዩናውያንና ከአባሪ ተባባሪዎቻቸው
የምዕራብ ሃይሎች ጋር በፊትለፊት ውጊያ እየተፋለሙ ይገኛሉ፡፡ ካለፈው ተሞክሮና
ከተገባላቸው ቃል በመነሣት ይህንንም ጦርነት በድል እንደሚወጡት እርግጠኞች ነን፡፡
ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ ማለታቸውን አቡ ኡማማህ (ረዐ) ይናገራሉ፣ “ከኔ ኡመት የሆኑ
ጭፍሮች የእውነት ሐዋሪያት በመሆን ይፀናሉ፡፡ ደርሶ በነካቸው ላይ ባለድል ናቸው፡፡
በጠላትነት የሚነሣባቸው ሁሉ አይጐዳቸውም፡፡ የፍርዱ ቀን እስከሚሆንም እንደዚሁ
ይቀጥላሉ” ብለው ሲሉ “ያ ረሱሉሏህ! እነዚህ እነሱ ወዴት ያሉ ናቸው? የሚል ጥያቄ
ቀረበላቸው፡፡ “እነሱ በበይተል መቅዲስ ያሉ ናቸው” በማለት መለሱ፡፡(ኢማም ሱዩጢ ጃሚዕ
አሐዲስ)
በሌላ ሪዋያ ነብዩ(ሰዐወ) የኢስላምን ጠላቶች በመዋጋት የዲመሽቅን ሕዝቦች
ጨምረዋል፡፡ በመሠረቱ ረሱል(ሰዐወ) ኡማው በጠላቱ ፊት አንድነት እንደሚያስፈልገው
መግለፃቸውም ነበር፡፡ ታሪካዊ ሁነቶች የዚያን አንድነት ጠቀሜታ በመስቀል ጦርነት፣
ሞንጎሎችን በመመለስ እንዲሁም ከሌሎች ፀረ-ኢስላም ሃይሎች ጋር በተደረጉ ፍልሚያዎች
ያንድነቱ ውጤት ተስተውሏል፡፡ ዛሬም ቢሆን ኡማው በተለይም የሱርያ፣ የሉብናን፣ የኡርዶን፣
የኢራቅና የፊሊስጢን ሙስሊም ሕዝቦች የነብዩን ትንቢት ከግንዛቤ በማስገባት በሲዩኒያ
ሃይሎች ላይ መተባበር አለባቸው፡፡
ነብዩ(ሰዐወ)፣ “ከኡመቴ መሃል የሆኑ ጭፍሮች በደማስቆ በሮችና በዙርያው፣
እንዲሁም በበይተል መቅዲሥ በሮችና በዙርያው ለእውነት በመቆም እስከፍርዱ ቀን
መዋደቃቸውን ይቀጥላሉ፡፡ የፈለገ ቢከዳቸው የሚያመጣባቸው ጉዳት የለም ብለዋል”፡፡
(ሱዩጢ፤ጃሚዕ አሐዲስ)
ሙስሊሞች እስከ ዕለተ ቂያማ ጂሃድን እንደሚቀጥሉ የሚያወሱ ሃዲሶች በጣም ብዙ
ናቸው፡፡ ከበይተል መቅዲሥ እና ከደማስቆ ውጭ ሌሎች ከተሞችንም ይጨምራሉ፡፡ አሁን
ሙስሊሙ ካለበት አጠቃላይ እውነታ በመነሣት እነዚህ ሃዲሶች ትክክለኛ መሆናቸውን እያየን
ነው፡፡ እናም አንድ ነገር ግልጽ ነው፡፡ የሙስሊሞች ትግል ፍትሕ የበላይነቱን እስከሚቀዳጅ
ይቀጥላል፡፡ የአላህ ዲን የበላይ እስከሚሆን የሚቆም አይደለም፡፡

33 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

በታሪክ እንደተረጋገጠው ደሞ የአላህን ቁርአንና የነብዩ ሙሐመድን ሱንና በፅናት


የተከተሉትና ለሕግጋቱ ታምነው የተገበሩት ሙእሚኖች ብቻ ናቸው ፍትሕን ሊያስገኙ
የሚችሉት፡፡ ሙናፊቆችማ በማስመሰል ምህዋር ላይ ሲሽከረከሩ ውለው ቢያድሩ እንጂ ይህን
ዓላማ ጋት ፈቅ የሚያደርጉት አይደሉም፡፡ ሡብሃነሏህ፡፡ አላህ ጥራት ተገባው፡፡ እቅዱን
በታማኝ ባሮቹ አማካይነት ከዳር ያደርሣል፡፡ አላህ ከነዚህ ያድርገን፡፡ ለእቅዱ ማስፈጸሚያ
ከሚመርጣቸው ባሮቹ ያድርገን፡፡ እሷ ትልቅ ዕድል፣ በደረጃም በላጫ ናትና ኒይያው ይኑረን፡

ምዕራፍ ሁለት
አል-ቁድስ/ኢየሩሳሌም
አል-ቁድሥ ምንግዜም በሙስሊሙ ሃሣብ ውስጥ አለች፡፡ በአዕምሮአቸው ጓዳ
ትነዝራለች፡፡ በኡማው የዕድሜ ዘመን ሁሉ በያንዳንዱ ሙስሊም ትውልድ ህሊና ውስጥ
ኖራለች፡፡ ዛሬም ቢሆን የታሪካችንና የህልውናችን ሕያው አካል በመሆን እንደቀጠለች ናት፡፡
ምክንያቱም
1. ከአላህ የተላኩት ነብያት በሙሉ የኢስላም ነብያት በመሆናቸው፣
2. መላው ሙሥሊም በሁሉም ነብያት (ከኢብራሂም እስከ ሙሳ፣ ዒሣ እስከ
ነብያቱ መደምደሚያ እስከ ሙሐመድ ዐለይሂሙ ሰላም ድረስ በተላኩት)
ስለሚያምን፣
3. የሁሉም ነቢያት ደዕዋ በተልዕኳቸው ዘመን ባንድ ወይም በሌላ መልኩ
ከቁድስ የተገናኘ በመሆኑ ነው፡፡
በመሆኑም ሙስሊሞች ከቁድስ ጋር ያለን መንፈሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነልቡናዊ ትስስር
እንዲበጠስ ወይም እንዲላላ በጭራሽ አንፈልግም፡፡
አልቁድስ የታወቁት አሃዳዊ እምነቶች መገናኛ እንደመሆኗ መጠን በሙስሊሞች ዘንድ
የተውሂድ ማዕከል ናት፡፡ ኢማን ዒባዳና ግንዛቤ ባንድ ተገናኝተውና ነጥረው ብርሃን
እንደሚሰጡበት የአዕምሮ ልዩ ጓዳ ትታያለች፡፡
ይበልጥ ደሞ አል-ቁድሥ ለሙስሊሞች የጂሃድ ዓርማ ናት፡፡ ቀደምት ታሪኮቿና
የወቅቱም እውነታ ይህንኑ ያረጋግጣሉ፡፡ በተለይም አሁን በፍልስጤም ሙስሊሞች እየተካሄደ
ያለው ኢንቲፋዳ በሙስሊሙ ኡማህ ዘንድ የቀሰቀሰው መንፈሳዊና ስሜታዊ ማዕበል በውነትም
ቁድስ በሙስሊሙ ዓለም እስከልብ ሥር የዘለቀ ቦታ እንዳላት የሚያመለክት ነው፡፡ ይህ ሃቅ

34 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ሙስሊሙን ዓለም ለመስዋዕትነት ያዘጋጀዋል፡፡ ልዩነቱን አቻችሎ በጠላቱ ፊት ትከሻ


እንዲገጥም ያደርገዋል፡፡ አል-ቁድስ ሙስሊሙ ዓለም ህብረቱን ሚገልጽበት ያንድነቱ ዓርማ
ናት የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡
መዲነቱል ቁድስ /የቁድስ ከተማ
አል-ቁድስ ወይም ኢየሩሣሌም ጥንታዊት ዐረባዊት ከተማ ናት፡፡ በፍልሥጤም
ምድር ቀደምት ሠፋሪ በነበሩት የዐረብ ከነዓንዮች ተቆረቆረች፡፡ በተለምዶ እንደሚታወቀው
ኢየሩሣሌም የሚለው ቃል እብራይስጥ አይደለም፡፡ ኢየሩሣሌም አረባዊ ሥም ነው፡፡
ሥያሜውን የሰጣት የከነዓን ንጉስ የነበረው ንጉስ ሣሌም አል-የቡሲይ ነው፡፡ ንጉስ ሣሌም
በእምነቱ መዋሒድ ነበር፡፡
ከተማይቱ “ዩር-ሣሌም“ ተባለች፡፡ ‘ዩር’ ማለት ሥፍራ/ መካን ማለት ነው፡፡ እናም ዩር እና
ሣሌም ተገናኝተው የሩሣሌም ሆነች፡፡ ከንጉሥ ሣሌም ወይም ደሞ ‹ሠላም› ከሚለው
የደህንነት ቃል ጋር ለማገናኘት ይመስላል፡፡ ትርጉሙ፣ የንጉሥ ሣሌም ከተማ ወይም የሠላም
ከተማ ማለት ነው፡፡ ቀስ በቀስ ወደ ኢየሩሣሌም ወይም በንግሊዝኛው “Jerusalem”
ወደሚለው ተወሰደ፡፡
ኢየሩሣሌም ብዙ ሥሞች ተሰጥታለች፡፡ በይቱል መቅዲሥ፡፡ አል-ቁድስ፡፡ የተቀደሰ
ሥፍራ ለማለት ነው፡፡ ከኢስላም በፊት ደሞ ኢሊያ ትባል ነበር፡፡
አል-ሐራም አሽ-ሸሪፍ
የቁድስ ከተማና የተባረከው የፍልስጤም ምድር በሙስሊሞች ዘንድ ትልቅ ከበሬታ
ሊኖራቸው የቻለው አል-ሐራም አሽ-ሸሪፍ እዚያ ስለሚገኝ ነው፡፡ አል-ሐራም አሽ-ሸሪፍ
በተባረከው የፍልስጤም ምድር በቁድስ ከተማ ይገኛል፡፡ አል-ሐራም አሽ-ሸሪፍ በጥቅሉ
የተከበረ፣ የተቀደሠ ሥፍራ እና ቁበተል ኸድራ ነው፡፡
አል-ሐራም አሽ-ሸሪፍ መስጂደል አቅሳን አመልካች ሲሆን መስጂደል አቅሳ ደሞ
የሙስሊሞች የመጀመሪያ ቂብላህ፣በአረቢያ ሰርጥ ከመካና ከመዲና ቀጥሎ ሶስተኛው ቅዱስ
ስፍራ ነው፡፡ ያን ጊዜ ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በኢስራእ ለይል ወደሰማይ ከማረጋቸው
በፊት የአላህን ሩሡሎችና አንቢዩች ዐለይሂሙ ሰላም በሶላት የመሩበትም እዚህ ስፍራ ላይ
ነው፡፡
አል-መስጂድ አል-አቅሷ፣ የቁድስ ከተማ እና የፍልስጤም መሬት አንድ ላይ በቁርአን “አርደል
ሙቀደሳ” (ማኢዳህ 5፡21) የተባረከው ምድር ይባላሉ፡፡ እነዚህ ሥፍራዎች በሙስሊሙ ዘንድ
የላቀ ከበሬታ፣ ደረጃና ዋጋ አላቸው፡፡ ይኸውም በብዙ ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ጭብጦች
የተረጋገጠ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
አል-መስጂድ አል-አቅሷ

35 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

አላሁ ተዓላ እንዲህ ይላል፣

“ያ ባሪያውን (ሙሐመድን) ከተከበረው መስጊድ ወደዚያ ዙርያውን ወደ ባረክነው


ወደ ሩቁ መስጊድ በሌሊት ውስጥ ያስኬደው ጌታ ጥራት ይገባው፤ ከታምራቶቻችን ልናሳየው
አስኬድነው፤ እነሆ እርሱ አላህ ሰሚው ተመልካቺው ነው፡፡” (17፡1)
አልመስጂድ አል-አቅሷ ወይም በሩቅ ያለው መስጂድ ማለት ከመካ መስጂደል ሐራም
በርቀት ሥፍራ የሚገኘው መስጂድ ለማለት ነው፡፡ የኢስራእ ወል ሚዕራጅ ክንዋኔም ቁርአንና
እንደተገለጸው አላህ ሱብሃነ ወተዓላ ለባሪያው ለሙሐመድ ከተአምራቱ ሊያሳያቸው በሌሊት
እንዳስኬዳቸው ሁሉ በፍልስጤም የሚገኘውን የአቅሷ መስጅድ ከመካው መስጅደል ሐራም
ጋር ለማገናኘት እንደተጠቀመበት ዑለሞች ይናገራሉ፡፡ አላህ ይህን በማድረጉ ለሙስሊሞች
የሚሰጠውን ቀጥተኛ እንድምታ የሁለቱም ቅዱሣን ሥፍራዎች ሕጋዊ ኻዲሞች/ ጠባቂዎች
እነሱ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ እናም አላህ በመለኰታዊ ጥበቡ አንድ አድርጐ ያገናኘውን
ማንም ተነስቶ ሊያለያይ አይችልም፡፡ መብቱም የለው፡፡

የመስጂደል አቅሷ ደረጃ በኢስላም


1. አል መስጂደል አቅሷ ለሙስሊሞች የመጀመሪያ ቂብላህ ነበር
ሙስሊሞች ከመካ ወደ መዲና በተሰደዱበት ሰሞን (በሂጅራው የመጀመሪያው ወራት
ማለት ነው) ወደ መስጂደል አቅሳ እየዞሩ ሲሰግዱ ቆይተዋል፡፡ ይኸውም
ከመደምደሚያው ነብይ ከሙሐመድ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በፊት ጀምሮ ከአላህ
የተላኩትን ነብያት ለመቀበላቸው ማረጋገጫ ነው፡፡ ኢማም ቡኻሪ እንዳወጉት የአላህ
መልዕክተኛ በቂብላው ጉዳይ የአላህን መመሪያ በመፈለግና ወደካዕባ መካ ዞረው
እንዲሰግዱ ከልብ በመሻት በተደጋጋሚ ፊታቸውን ወደሠማይ ያነሱ ነበር፡፡ አላህ የነብዩን
ዱኣ ተቀበለ፡፡ እንደልባቸው መሻት እንዲሆንላቸው ፈቀደ፡፡ ቂብላውን ወደ መካ
ቀየረው፡፡

”የፊትህን ወደ ሠማይ መገላበጥ በእርግጥ እናያለን፤ ወደምትወዳትም ቂብላ


እናዞርሃለን፤ ስለዚህ ፊትህን ወደ ተከበረው መስጊድ (ወደካዕባ) አቅጣጫ አዙር፤ የትም
ስፍራ ብትኾኑም ስትሰግዱ ፊቶቻችሁን ወደርሱ አቅጣጫ አዙሩ፤….“ 2.144

ታዲያ ግን የቂብላው ከበይተል መቅዲሥ ወደ ካዕባ መቀየር በቁርአንና በሱንና


ዘላለማዊ ክብር የተቸረውን የመስጅደል አቅሷን ደረጃ የሚቀንስ አይደለም፡፡ ይልቅ

36 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

እንደውም የመጀመሪያው ቂብላህ መሆኑና ከመጨረሻው ቂብካ ከካዕባ መገናኘቱ


በሌሎች መስጅዶች ላይ የሚያልቀው እና በኢስላም ውሰጥ ልዩ ቦታ ሚያሰጠው ነው፡፡

2. አል መስጅድ አል-አቅሳ የኢስራእ ወል ሚእራጅ መሬት ነው፡፡


(ሰኽረተል ሙሸረፈህ)
የመስጂደል አቅሷን ደረጃ ከሚያጐሉት ተጨማሪ ነጥቦች አንዱ ሥፍራው የኢስራእ
ወል ሚእራጅ ተአምር የተከናወነበት መሆኑ ነው፡፡ በሱራህ አል-ኢስራእ (17፡1)
እንደተገለጸው የነብዩ ሙሐመድ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከመካ ወደቁድስ መስጅደል
አቅሷ የተደረገ የለይል ጉዞ፣ ከዚያም ወደ ሰማይ ሠማያቱ የመጨረሻ ጠርዝ (የትኛውም
የአላህ ፍጡር ሊደርስ ወደማይችልበት ጫፍ) የተደረገ እርገት መነሻ መሆኑ የቦታውን
ክብረት ያልቀዋል፡፡ ይህ በአላህ ጥበብና ችሎታ የተመራ ሂደት በቁድስ፣ በመስጂደል
አቅሷ እና በመላው ሙስሊም ትውልድ እነዲሁም በጠቅላላው የሠው ዘር ታሪክ ውስጥ
ያዲስ ምዕራፍ መክፈቻ ሊሆን ችሏል፡፡ እንዴት ቢባል፣ በየዘመኑ የኖረው ሙስሊም
ትውልድ ልብና አዕምሮ ከመካ /ካዕባ ጋር የተገናኘውን ያህል የኢስራእ ወል ሚዕራጅ
ተአምርም ተከታታይ ሙስሊም ትውልዶች ከአቅሷ መስጂድና ከተባረከ ዙርያው ጋር
ለእስከወዲያኛውም ያስተሣሠረ መንፈሣዊ ተፍፃም በመሆኑ ነው፡፡ በመሆኑም ተአምሩ
የሚያጅበንን ያህል ለተከናወነበት ሥፍራም አክብሮትና ሃላፊነተ ይሰማናል፡፡

3. አል-መስጅድ አል-አቅሳ የኢስላም 3ኛው ሐረም ነው፡፡


ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ይህን የተቀደሠ ሥፍራ ሙስሊሞች መጐብኘት እንዳለብን
ሲያሳስቡ እንዲህ በማለት ነው፡፡

ወደነዚህ ሶስቱ መሣጂዶች ቢሆን እንጂ ወደሌላ ጉዞ አታደርጉም


“መስጅደል ሐራም፣ መስጂደል አቅሷና መስጅደ ነቢ (መዲና)
(ቡኻሪ ሙስሊም)
በመስጅደል አቅሷ የተሠገደ ሰላት አጅሩ 500 እጥፍ ነው፡፡
ነብዩ (ሰዐወ) ከተናገሩት፣
“በመካ መስጅደል ሐረም የተሠገደ አንድ ሰላት ከሌላው ቦታ 100‚000 ሰላት ጋር እኩል
ነው፡፡ በኔ መስጅድ(መዲና) የተሰገደ አንድ ሰላት ከሌላው ቦታ 1000 ሰላት ጋር እኩል
ነው፡፡ (እንደዛውም ሁሉ) በበይቱል መቅዲሥ የተሠገደ አንድ ሰላት ከሌላው ቦታ 500
ሰላት ጋር እኩል ነው፡፡” (ሐሰን ሃዲስ፡በይሐቂ)
መስጂድ አቅሳ ፀረ-ክርስቶሱ ደጃል ከሚያመጣው አበሳና መከራ ለሙስሊሞች
መጠለያ ምሽግም ነው፡፡ አድ-ደጃል ወደ መስጂደል አቅሷ እንዲገባ አይፈቀድለትም፡፡
አላሁ ሱብሃነሁ ወተዓላ መካንና መዲናን እንደሚጠብቅ ሁሉ ይህንንም ስፍራ
ይጠብቀዋል፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ “እሱ (ደጃል) በምድር ላይ ለዐርባ ቀናት

37 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ይቆያል፡፡ የማይገባበት ቦታ የለም፡፡ እነዚህ ብቻ ሲቀሩ፤“ ካዕባ፣ መስጂድ ነቢ፣ መስጂድ


አቅሷ እና ጡሩ ሲና” (አህመድ)

የተባረከው የፍልስጤም ምድር


መስጂደል አቅሷ እና ዙርያው የፍልስጤም ምድር የተባረኩ ናቸው፡፡ ክብርና ቅድስና
አላቸው፡፡ ብዙ ቁርአናዊ አያዎች፣ ብዙም ሐዲሶች ይህንኑ ያረጋግጣሉ፡፡ ከእውቅ
ሙፈሲሮችም እንደ ኢብኑ ከሲር፣ ኢብኑል ጀውሲይ፣ ቁርጡቢ እና ሌሎችም በሱራህ አል-
ኢስራእ(17) አንቀጽ (1) ላይ “አለዚይ ባረክና ሐውለሁ” የሚለውን ሐረግ የሻም ምድር እንደሆነ
በመግለጽ ነው የፈሠሩት፡፡ የሻም ምድር ሲባልም በመልክዐ ምድራዊ አገላለጽ ፍልስጤምን
ጨምሮ ታላቁ ሱርያ በመባል የሚታወቀው ክልል ነው፡፡ ይህ ክልል በሁሉም ዓይነት
መንፈሳዊና ቁሣዊ ፀጋ ተባርኳል፡፡ በረከቱ ለፍልሰጤሞችና ለአረቦች ወይም ለሙስሊሞች ብቻ
አይደለም፡፡ አላሁ ተዓላ “አርዲ ለቲ ባረክና ፊሃ ሊልዓለሚን” በማለት በቁርአን እንደገለጸው
በረከቱ ለመላው የሰው ዘር ነው (አንቢያ 21-71)

ከበረከቱ በጥቂቱም እነሆ

1/ የቦታው በዓለም ማዕከላዊ ስፍራ ላይ መገኘት


በምዕራብ ኢስያና አፍሪካ፣ በሰሜኑ የዓለም ክፍልና በደቡቡ መሃል እንደመተላለፊያ
በር ነው፡፡ በለምነቱ በሚታወቀውና fertile crescenet በሚሰኘው ክልል መሃል እምብርት
ላይ መገኘቱ ቦታውን ስትራቴጂያዊ ያደርጉታል፡፡ fertile crescent የሚባለው ክልል ከዓባይ
ተፋሰስ እስከ ኤፍራጥስ/ፉራት የሚዘረጋ ሲሆን በተፈጥሮ ሃብትም የደለበ ነው፡፡
በመሆኑም የተለያየ እምነት ተከታይ ሕዝቦችና ነገዶች ከጥንት ጊዜ ጀምሮ ወደዚያ
በመጉረፍ ሲሠፍሩበትና ሕብረ ባህላዊ ማህበረሰብ ሲፈጥሩበት ኖረዋል፡፡ ክልሉ የአላህ
መልዕክት የሚነገርበት የነብያት አገር እንዲሆን የተመረጠውም ለዚህ ነው፡፡ ማዕከላዊነቱና
የብዙ ሕብረባሕል ሕዝቦች መናኸሪያ መሆኑ፡፡ እናም ይህ የተባረከ ምድር ከመልከዐ ምድራዊ
ማዕከላዊነቱ፣ አቀማመጡና ብልፁግነቱ በተጨማሪ የአላህ መልዕክት የሚነገርበት የነቢያት
አገር ቤት በመሆን ለመላው የሠው ዘር የእውቀት ፋና ሚንቦገቦግበት የሂዳያ መቅረዝ ሊሆን
ችሏል፡፡

2/ አርዱል መንዚል መላኢካ


ነብዩ (ሰዐወ) “መልካም ዜና (የምስራች) ለሻም!” አሉ በዙርያቸው የነበሩት፣
ምንድነው እሱ- ያ ረሱሉሏህ? አሉዋቸው “የአላህ መላኢካዎች በሻም ላይ አክናፋቸውን
እየዘረጉ ነው” በማለት መለሱላቸው (ቲርሚዚይ)

3/ የነብያት አገር
አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ይህ አካባቢ የአንቢዩቹን የሩሡሎቹ አገር ቤት እንዲሆን
መረጠው፡፡ የሱን ትዕዛዝና መልዕክት ተቀብለው በማስተላለፍ ለየወገናቸው ያስተማሩበት

38 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ምድር ሊሆን ቻለ፡፡ ሙሐመድ (ሰዐወ) ጎብኝተውታል፡፡ በውስጡም ወደአላህ ሠግደዋል፡፡


ኢብራሂም እና ሉጥ ዐለይሂሙ ሠላም በውስጧ ተሰደዋል፡፡ ሌሎችም ብዙ ነብያት በሷ
ተወልደውጧ፣ አድገው ሞተው እንደተቀበሩባት የሚታወቅ ነው፡፡ ኢስሐቅ፣ ያዕቆብ፣ ዩሱፍ፣
ዳውድ፣ ሱለይማን በውስጡ ያስተማሩበት ቢሆን እንጂ በቁድስ አንድም ቦታ የለም፡፡
-በብዙ ነብያዊ ሃዲሶች እንደተነገረው የነቢዩላህ ዒሳ ዐለይሂ ሠላም መመለስም
የሚሆነው በመስጂደል አቅሷ ነው፡፡

4/ የተባረከው ምድር ለሙስሊሞች ወቅፍ ነው


በፍልስጤም መሬት ላይ የሙስሊሞች ባለቤትነት በነብዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) አፅንኦት
የተደረገበት ጉዳይ ነው፡፡ የሔብሮንን አገረ-ከተማ ለተሚም ቢን አውስ አድ-ዳሪና ለወንድሞቹ
ከዚያም ለነሱ የዘር ዘሮች እስከ ዕለተ ቂያማ ወቅፍ እንዲሆን ሰጥተዋል፡፡ ተሚም ቢን አውስ
አድ-ዳሪይ የነብዩ(ሰዐወ) ሰሃባና የመጀመሪያው ፍልስጤማዊ ሙስሊም ነበር፡፡ በየዘመኑ የኖሩ
ሙስሊም ገዢዎችም ነብያዊውን ፈለግ በመከተል በአገረ-ፍልስጤም ብዙ ወቅፍ አድርገዋል፡
፡ በዑስማንያህ ያገዛዝ ዘመንም የወቅፍ ይዞታው በሰነድ ሰፍሮ/ዶክሜንትድ ሁኖ በኢስታንቡል
ተቀምጦ ነበር፡፡ ሙስሊሞች በተባረከው የፍልስጤም መሬት ላይ ያላቸውን የባለቤትነት
መብት የሚያጠናክር ተጨማሪ ነጥብ መጥቀስ ቢያስፈልግ ባንድ ወቅት በሥፍራው ላይ
የነበረው የንግሊዝ ማንዴት ይህንኑ ተቀብሎ ለሙስሊሞች የባለቤትነት መብት እውቅና ሠጥቶ
እንደነበር የሚታወቅ ነው፡፡

5/ እስከ ዕለተ ቂያማ የጂሃድና የሪባጥ መሬት


የተባረከውን አገር ነዋሪዎች በማስመልከት ነብዩ(ሰዐወ) ሲናገሩ- ”እነሱ ፣
ሚስቶቻቸው፣ ልጆቻቸው፣ አገልጋዩቻቸው (ወንዱም ሴቱም) በአላህ መንገድ ሪባጥ ላይ
ናቸው“ ብለዋል፡፡(ጦበራኒ)

“ሪባጥ” ማለት ለሙስሊሙ መሬት የሚደረግ ጥበቃ ነው፡፡ በኢስላም በጣም


ከሚወደዱ ስራዎች ይመደባል፡፡ በሪባጥ ላይ የሚሞት ከአዛበል ቀብር ይጠበቃል፡፡ ደግ
ሥራው አይቋረጥም እስከ ዕለተ ቂያማ እየጨመረ ቢሄድ እንጂ፡፡ (አቡ ዳውድ/ቲርሚዚይ
የዘገቡት)

ነብዩ (ሰዐወ)፣ “ከኡመቴ የሆኑ ጭፍሮች የእውነት ሐዋሪያ በመሆን/ ለሃቁ በመሟገት
ይቀጥላሉ፡፡ ሰዐቲቱ /ቂያማ እስከምትቆምም ድረስ በጠላቶቻቸው ላይ እነሱ ሁሌም
ባለድል ናቸው፡፡"- ብለው ሲሉ፣ ከታዳሚዎች አንዱ "ያ ረሱሉሏህ! እነሱን የት
ልናገኛቸው እንችላለን? ሲል ጠየቃቸው
”እነሱ በበይተል መቅዲስ እና በዙርያው ይገኛሉ” አሉት፡፡ (አህመድ)

39 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ለዚህም ነው ብዙ የኢስላም ዑለሞች (ይህን ነብያዊ ቃልና የተገባላቸውን ሽልማት


ከግንዛቤ በማስገባት) የፍልስጤም ሕዝቦች የሪባጥና የጂሃድ ኒያ እንዲኖራቸው የሚመክሩት፡

6/ የሐሽርና የመሐሸር መሬት( ) የውመል መሕሸር


አርዱል ሐሽር፣ የሐሸር መሬት፡፡ በሻም ውስጥ ያለና የዓለም ፍጻሜ ሚሆንበት
መሬት ነው፡፡ ከሰዓቲቱ/ቂያማ መቃረብ ምልክቶች አንዱ ሕዝቡን ሁሉ ወደሐሸር የሚሰበስብ
ሃይለኛ እሳት ከወደ የመን/ኤደን ይነሳል፡፡ መላእኩ ኢስራፊልም በተባረከው መሬት ላይ ሆኖ
የቀጣዩን ዓለም ንጋት በማስመልከት (ቀጣዩ ዓለም መጀመሩን በማስታወቅ) በቀንዱ ይነፋል፡

መይሙና ቢንት ሰዒድ፣ "ያ ረሱሉሏህ! ስለበይቱል መቅዲስ ይንገሩን እስኪ ብላ ስትል-
”እሷ የሐሽር እና የመሕሸር (የትንሳኤ) መሬት ናት” በማለት መለሱላት (ጦበራኒ)

7/ የሸሂዶች መሬት
የዚህ ብሩክ መሬት አፈሩ በብዙ ሸሂዶች ደም የረጠበና የተቀመመ ነው፡፡በጣም ብዙ
የሆኑ ወሳኝ ጦርነቶች በፍልስጤም ምድር ተካሂደዋል፡፡ የሐቲን፣ ዓይን ጃሉት፣ የአካህ፣
የቁድስና ያካባቢው ጦርነቶች ይጠቀሳሉ፡፡ በነዚህ ታላላቅ ጦርነቶች በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ
ሙስሊሞች ተሰውተዋል፡፡ ባለፈው 50 ዓመት ብቻ (ዛሬ ዓለም የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት
በሚል ሥም ሰጥቶ የሙስሊሙን እይታ ባጭበረበረበት) በዚሁ “የመካከለኛው ምሥራቅ”
ተብዬ ጦርነት በአረቦችና የሁዶች መሃል በተካሄደውና እየተካሄደም ባለው ፍልሚያ በሺዎች
የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ሸሂድ ሆነዋል፡፡ እስከዚህም ደቂቃም መሥዕዋትነትን እየከፈሉ ናቸው፡
፡ 2ኛው ኢንቲፋዳ (ኢንቲፋዳ ጀዲዳ) በ1421ሂ የሻዕባን ወር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶም በየቀኑ
ብዙዎች በሸሂድነት መውደቃቸውን እንደቀጠሉ ነው፡፡ እነሆ ጂሃድና ሸሂድነት የተባረከው
የፍልስጤም ምድር ልዩ እንደቀጠሉ ነው፡፡ እነሆ ጂሃድና ሸሂድነት የተባረከው የፍልስጤም
ምድር ልዩ መለያ እንደሆነ ይቀጥላል፡፡

የቁድስ ሙስሊማዊት አገር መሆን


በ16ሂ አል-ቁድስ የሙስሊሙ አገር ቤት አካል ሆነች፡፡ ከአራት ወራት አስጨናቂ
ከበባ በኋላ በጊዜው ስለ “መደምደሚያው ነብይ” ኢልሙ የነበራቸው የከተማይቱ ከፍተኛ
ቀሣውስት አንድ አቋም ወሰዱ፡፡ ሙሐመድ እውነተኛ ነቢይ መሆናቸውንና ተከታዩቻቸውም
ባሸናፊነት እንሚወጡ በመረዳት ከሙስሊሙ ሠራዊት ጋር ሠላም ለመፍጠር ተስማሙ፡፡
እንደዛም ሆኖ ግን በነሱ መፃሕፍት ትንቢቱ ለተነገረለት ግለሠብ ቢሆን እንጂ ለሌላ ሰው
የከተማይቱን ቆልፎች ማስረከብ እንደማይችሉ ተናገሩ፡፡ ቃለ ትንቢቱም ለሙስሊሞች
በተነበበላቸው ጊዜ የተባለው ግለሠብ ዑመር ኢብኑል ኻጣብ እንደሆኑ ገባቸው፡፡ ዑመር(ረ.ዐ)
በጊዜው የኢስላማዊ መንግስት ኻሊፍ እና አሚረል ሙዕሚኒን ነበሩ፡፡ ወደ ቁድስ ተጉዘው
በመምጣት የከተማይቱን ቁልፎች ከሊቀ ካህናቱ እጅ ተረከቡ፡፡ የሰላት ወቅት በገባም ጊዜ
ከከኒሳው (ከቤተ-ክርስትያኑ) ውጭ አሁን የቁበተል ኸድራ መስጅድ ያለበትጋ ሰገዱ፡፡

40 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ዑመራዊ ቃል ኪዳን
በመቀጠልም ዑመር(ረዐ) ከሊቀ ካህናቱ ጋር የስምምነት ውል አፀደቁ፡፡ በስምምነቱ
መሠረት ለቁድስ ነዋሪዎች የሕይወት፣ ያምልኮ ነጻነት፣ የንብረትና የማምለኪያ ስፍራ ጥበቃ
ዋስትና ገቡላቸው፡፡ ሙስሊም ካልሆኑ የከተማይቱ ነዋሪዎች ጋር ስለሚኖረው ግንኙነትም
ውል ተበጀለት፡፡ ዛሬ ሁሉም የታሪክ ሊቃውንት እንደሚቀበሉት ዑመራዊ ቃልኪዳን ፍትሐዊና
ባካባቢው ታሪክ ወደር ያልነበረው ነው፡፡ ከኢስላማዊ አገዛዝ በፊት በቦታው ላይ የነበሩትና
በጂሃድ ጦርነት የተወገዱት ክርስትያን ቢዛንታይኖች የሁዶችን ሲያሳድዱ ነበር፡፡ ወደቁድስ
ድርሽ እንዳይሉም ማዕቀብ ጥለውባቸው ነበር፡፡ ሙስሊሞች መጡና ማዕቀቡን አነሱላቸው፡፡
የሁዶች ወደ ቁድስ መግባት ቻሉ፡፡ ወደቁድስ መግባት ብቻ ሳይሆን የኢስላማዊ ወቅፍ ይዞታ
ወደሆነው ”የኢየሩሳሌም ማርገጃ ግንብ“ ሄደው እንዲፀልዩም ተፈቀደላቸው፡፡

የሁዶችና መስሂዩች ኢስላማዊውን አመራር በመቀበል ባዲሱ የመቻቻል ሕይወት


ሠላምና መረጋጋት አገኙ፡፡ የራሳቸውን ሃይማኖትና ማሕበራዊ ወግ ለመተግበር የሚያስችል
ነጻነት ተሰጣቸው፡፡ በሂደት ብዙው የፍልስጤም ነዋሪ ኢስላምን ተቀበለ፡፡ በ1ኛው መቶ ሂጅራ
ማብቂያ ግድም ብዙኃኑ የፍልስጤም ነዋሪ ኢስላምን በመቀበሉ የሁድ ወይም ክርስትያን
እንደሆኑ የቀሩት ጥቂቶች ብቻ ነበሩ፡፡

የአይሁድ የሃይል ርምጃ


በዓለም አቀፍ ህግ መሠረት የኢየሩሳሌም ምሥራቃዊና ምዕራባዊ ክፍሎች በሃይል
የተያዙ ግዛቶች (occuipied territories) ናቸው፡፡ ኢስራኢል በነሱ ላይ ምንም ዓይነት ሕጋዊ
መብት የላትም እንደዛም ሆኖ የኢስራኢል መንግሥት ኢየሩሳሌምን የሁዳዊት ከተማ ለማድረግ
የሚያራምደው ፖሊሲ አልተገታም ”ኢየሩሳሌም የማትከፋፈል፣ ዘላለማዊት የኢስራኢል ዋና
ከተማ “the united & E ternal capital of Israel“ በሚል ከፍ አድርጐ እያስደመጠ ነው፡፡
ትልቅ ድፍረት! የኢስራኢል ማን አለብኝነት ብዙ ተጉዛል፡፡ ብዙ የአረብ መሬቶችንና ታሪካዊ
ንብረቶች በሃይል ይዛለች፡፡ በከተማይቱ ዙርያ አዳዲስ የአይሁድ የሰፈራ መንደሮችን
መስርታለች፡፡ አዲስ መጤ የሁዶችን ለማስፈር በሚል መንደሮቹን ወደ ጐን እንደፈለጋት
ታሰፋለች፡፡ አረብ ነዋሪዎች ምርር ብሏቸው ከርስታቸው እንዲነቀሉ በዘዴ ታዋክባለች፡፡
ስትፈልግ ተነስታ መሬታቸውን ትይዛለች፡፡ ቤታቸውን በቡልዶዘር ታፈርሣለች፡፡ አሁን
አሁንማ ፍልስጤማዊ ቤተሰቦች ያደሩበትን ቤት ይውሉበት እንደሆነ አያውቁም፡፡ ጠዋት
የወጡበት ቤት ተመልሰው ያደሩበት እንደሆነ መጠራጠር ላይ ደርሰዋል፡፡ ለምን ቢባል
የኢስራኢል ቡልደዞሮች በማንኛውም ጊዜ በታንክና በሄሊኮፕተር እየታገዙ መጥተው ሊንዱት
ይችላሉ፡፡ ለአሮጌ ቤቶች እድሣት ወይም አዲስ ህንጻ ለማቆም ፍልስጤማውያን ፈቃድ
አያገኙም፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሁዶችን በሚጠቅም መንገድ የከተማይቱን የሕዝብ አሰፋፈር/
ዲሞግራፊ ለመለወጥ ሲባል በከተማው አቅራቢያ የነበሩ የአይሁድ ቀበሌዎች ወደ ከተማይቱ
ክልል ተጨምረዋል፡፡
የኢስራኢል መንግስት የኢየሩሣሌምን አረባዊና ኢስላማዊ ገጽታ ለመቀየር ባወጣው
ንድፍ መሠረት ብዙ ህንፃዎችን ገንብቷል፡፡ የመዋቅር ለውጥ አድርጓል፡፡ ከ1987 ጀምሮ የቁድስ

41 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ታሪካዊ በሮች መጠሪያ ወደ እብራይስጥ እየተለወጡ ናቸው፡፡ ይበልጡኑ ደሞ የከተማይቱን


ኢስላማዊ መልክ ለማጥፋት ኢስላማዊ የሆኑ ታሪካዊ ሥፍራዎችን ፣ ነባር መስጂዶችን፣
ኢስላማዊ ጥበብ/አርት ያረፈባቸውን ጥንታዊ ሕንጻዎችን፣ የመቃብር አፀዶችን የመሳሰሉትን
በማውደም ላይ ይገኛሉ፡፡ ከዚህ በመነሣት ዛሬ ብዙ የአረብ-ኢስራኢል ግጭት ኤክስፐርቶች
እንደሚያምኑበት የጽዩናውያን የመጨረሻ ግብ መስጂደል አቅሷን /ቁበተል ኸድራ/ ማውደም
እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ሙስሊሙ ሕብረተሰብ ለዚህ እውነታ ዓይኑን መግለጥ አለበት፡፡ አንድ
ነገር መደረግ ካለበት የመጀመሪያው የሁዳዊ መዶሻ መስጂዱ ግንብ ላይ ሣያርፍ በፊት መሆን
አለበት፡፡ አንዲት ብሎኬት ከተሰበረች በኋላ ጠቅላላው መዋቅር ደህንነት ሊሰማው አይችልም፡

በመስጂዱ ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶች


መስጂደል አቅሷ በአዕምሮአችን ጓዳ እንዳለ ሥፍራ ነው፡፡ የሚገርመው ግን
በአዕምሮአችን ጓዳ ላይ ጥቃቱ ሲያርፍና ሲያቆስለን ብዙም ሊሰማን አለመቻሉ ነው፡፡ የኡማው
ቁጣ በድንገተኛ ማዕበል እንደተመታ የባህር አንጀት ላንዳፍታ ተነዋውጦ ፀጥ ከማለት ያለፈ
አይደለም፡፡ ሆኖም ከንውጥውጥታው ስር አዲስ ማዕበል እየተጠነሰሰ ለመሆኑ ጥርጥር
የለውም፡፡ ይህ በንዲህ እንዳለ እስከዛሬ በመስጂዱ ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶች እንዴት እንደነበሩ
እንይ

ከ1967 ጀምሮ መስጂዱን ለማጥቃት በግልና በቡድን ደረጃ በርካት ሙከራዎች


ተደርገዋል፡፡ መስጂዱን ለማውደም፡፡ አሊያም የሃይል ሚዛኑን በማዛባት status quo ላይ
አንድ የሆነ ለውጥ ማምጣት ይህ ነበር ዓላማው፡፡

ኦገስት 21‚1969 ሚሼል ሮሐን የተባለና እራሱን የ”church of god” አባል የሚል
አውስትራሊያዊ መስጂዱን ለማቃጠል ሙከራ አደረገ፡፡ እሱ በለኮሰው እሣት አንድ ሺህ ዓመት
ያስቆጠረ ሚንበር ወደመ፡፡ በገንዘብ የማይተመን፣ ከምርጥ እንጨትና ከዝሆን ጥርስ የተሰራ
ውድ ዕቃ ነበር፡፡ ሚንበሩ ከሀሊብ/ሱሪያ በሰለሃዲን አል አዩቢ ነበር የመጣውና ለመስጂዱ
የተበረከተው፡፡

ኦክቶበር 1982 የ“kach” ንቅናቄ አባል የሆነ ግለሠብ መስጂዱ ላይ ሊሸጥር አቅዶ
በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ ዩኤል ለርነር “ቁበተል ኸድራን” ሊያጋይ በማቀድ ወንጀል ተከሶ የሁለት
ዓመት እስራት ተፈረደበት፡፡

አፕሪል 1982 አንድ ኢስራኢላዊ ወታደር ሆን ብሎ ወደ መስጂደል አቅሷ በመምጣት


ተኩስ ከፈተ፡፡ ብዙ ሙስሊሞችን ሙትና ቁስለኛ አደረገ፡፡ በሱ በኩል “የተቀደሰውን ስፍራ ነፃ
ማውጣቱ” ነበር፡፡ ኋላ ላይ “ዕድሜ ይፍታህ ተበየነበት” ይባላል፡፡

42 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ማርች 10-1983 ባብዛኛው የሽብርተኛው የ“ሜይር -ካሐን” ደጋፊ የሆኑ የሁዶች


መስጂዱ ላይ ዓይን ያወጣ ወረራ ሊፈጽሙ ሲሉ ተደረሰባቸው፡፡ ቀንደኛ የተባሉት 45ቱ
በመያዛቸው የታሰበው ሳይሆን ቀረ፡፡
እንደገናም በ1983 የበጋ ወራት ላይ የምዕራቡ ግንብ ራቢ እንደሆነ የሚነገርለትና
የሁዳ ጌታስ የተባለ ሰው የጥንቱን ቤተመቅደስ የማግኘት ህልሙን እውን ለማድረግ ሲል
በአሮጌው ከተማ ስር ውስጥ ለውስጥ የሚሄድ መንገድ (ቱኔል) ለመሥራት ነው በሚል ሽፋን
በምዕራቡ ግንብ ስር መቆፈር ጀመረ፡፡ ድርጊቱ በኢስላማዊ የወቅፍ ድርጅት በኩል
ቢደረስበትም ለማስቆም አልተቻለም፡፡ ይህ በ1996 ለሕዝብ የተከፈተው የመሬት ውስጥ
ለውስጥ መንገድ የመስጂዱን ደህንነት በብዙ መልኩ ጉዳት ላይ ጥሎታል፡፡ ድርጊቱ የኡማውን
አጥር እንደመነቅነቅ ያህል ድፍረት የተሞላበት ቢሆንም፣ በዝምታ መታለፉ ደሞ በውስጣችን
ያደረውን ድክመት የሚያጋልጥና ጠላት ሰብሮ እንዲገባ የልብ ልብ የሚሰጥ ነው፡፡

ዳር-ዳርታውና እውነታው በሐራም አሸ-ሸሪፍ ቦታ ላይ እነሱ 3ኛው


ቤተመቅደስ(ሐይከል ሱለይማን) ብለው የሚሉትን ለመገንባት ነው፡፡ ለዚህ ማስረጃው ከላይ
በመጠኑ የተገለፁት መሰል ጥቃቶች ካመት ዓመት እየተባባሱ መምጣታቸው ነው፡፡ እናም አል-
ሐራም አሸ-ሸሪፍ አንድ ቀን የመፍረስ አደጋ ሊያጋጥመው ይችላል የሚለው ስጋት ባዶ
አይደለም፡፡ እውነትነት አለው፡፡ የጥበቃውን ሃላፊነት የያዘው የወቅፍ ድርጅት የመስጂዱን
ደህንነት የማረጋገጡ ነገር ካቅሙ በላይ እየሆነበት መጥቷል፡፡ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ
በሙስሊሞች ላይ እየከፋ በመጣው የኢስራኢል መንግሥት ጥቃት አኳያ ነገሮች ወዴት
እያመሩ እንደሆነ መገመት አያዳግትም፡፡ ባለፉት አስርቶች የሆነውን ብናይ የሁዶችን የመታደግ
ወይም ቤተመቅደሱን እንደገና የማነጽ ተልዕኮ አለን በሚሉና እራሳቸውን አንድ ጊዜ እንደ
“መሲህ” ሌላ ጊዜ እንደ "ሙሴ“ ወይም እንደ አንድ መንፈሣዊ መሪ በሚቆጥሩ ግለሠቦች
አነሳሽነት ብዙ አደጋዎች ተከስተዋል፡፡ የኢየሩሳሌም ጣጣ አላልቅ ከማለቱና ከመደጋገሙ
የተነሳ “Jerusalem syndrome” ተብሏል-በንግሊዝኛው፡፡

እውን ግን የአቅሷ መስጂድ ሊፈርስ ይችል ይሆን? ይህ የብዙዎቻችን ጥያቄ ቢሆንም


በዚያው ልክ ብዙ ሙስሊሞች የአቅሷን መስጂድ "ከመፍረስ አደጋ የተጠበቀ ነው" የሚል
እምነት አላቸው፡፡ ነገር ግን በዲናችን ውስጥ በሠነድ የሠፈረ አረጋጋጭ ደሊል የለም፡፡ ከዚህ
ቀደምም ቢሆን መስጂዱ ለተደጋጋሚ አደጋዎች ተጋልጦ ብዙ ጉዳት አግኝቶት ያውቃል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደሞ ልክ እያጣ በመጣው የኢስራኢል የማን አለብኝነት ርምጃና የሙስሊም
መንግሥታት አስፈሪ ዝምታ አንፃር አደጋው ሊደርስ እንደሚችል ነው፡፡ አላህ አቅሷንና
መላውን የሙስሊም መሬት ይጠብቅ፡፡

ሙስሊሞች የመካውን መስጂደል ሐራም የመጠበቅና ከአደጋ የመከላከል ሃላፊነት


እንዳለባቸው ሁሉ መስጂደል አቅሷንም የመጠበቅና ከአደጋ የመከላከል ትልቅ ሃላፊነት
አለባቸው፡፡ ይህ መታወቅ አለበት! የአቅሷ መስጂድን ችላ ማለት መስጂደል ሐራምን ችላ
ከማለት ያነሰ አይሆንም፡፡

43 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

የሠላም ቃል ኪዳን
ኢሥላም መቼም ፀረ-ሰላም ሆኖ አያውቅም፡፡ ኢስላም የሠላም ሃይማኖት ነው፡፡
አልቁድስ/ኢየሩሣሌም የሠላም ከተማ ናት፡፡ ጠላት ከልቡ ሠላም ከፈለገ ሙስሊሞችንም
ይህንኑ መቀበል አለባቸው፡፡ ነገር ግን ሠላሙ የይስሙላ ሣይሆን እውነተኛና ቀጥተኛ እንዲሆን
እንፈልጋን፡፡ ሙስሊሙ ኡማህ መልሶ ለሽንፈት፣ ለውርደትና የራሱን ሃቅ አሳልፎ እንዲሰጥ
ለሚገደድበት ሠላም ማደር የለብንም፡፡ ብቃት ያለው ሙስሊማዊ አመራር ጨርሶ በሌለበት
ሁኔታ የኢስራኢል መንግሥት በምዕራብ ሃያላን ድጋፍ ሰጪነት በሙስሊሞች ላይ ለመጫን
የሚሞክረው ሠላም በመሠረቱ ሠላም አይደለም፡፡ ፍትሃዊ፣ የሚሰራም አይደለም፡፡
የፍልሥጤም ባለስልጣናት እንዲቀበሉት ቢገደዱ እንኳን ባካባቢው ላይ ሠላምና መረጋጋት
ሊሰፍን አይችልም፡፡ የሰብዐዊ መብት ረገጣውና ብጥብጡ እንዳለ ይቀጥላል፡፡ ችግሩን
ከማባባስና የሕዝቡን ስቃይ ከማራዘም በስተቀር የሚፈይዱት የለም፡፡ የችግሩ መባባስና
የሕዝቡን ሥቃይ መራዘም ደሞ ቀጣዩን አመፅ የበለጠ ያደርገዋል፡፡ “ጠያራትና ደባባት“
አሁንም አልገቱት፣ ወደፊትም አያቆሙት-

ድሉ የሙስሊሞች ነው
ሙስሊሞች የተባረከውን መሬት ለማስመለስና የዳዕዋ ግዳጃቸውን ለመወጣት
በሚያደርጉት ትግል አሸናፊዎች እንደሚሆኑ በቁርአንና በሱና ብስራቱ ተነግሯል፡፡ በቅርብም
ይሁን በመጪው ጊዜ ድሉ የሙስሊሞች እንደሚሆን ጥርጥር የለውም፡፡ ካሁኑ አመልካች
ሁኔታዎች እየታዩ ነው፡፡

ለውጥና እንቅስቃሴ ሁለት የማይቋረጡ የተፈጥሮ ሕግጋት ናቸው፡፡ አላህ ይህን


ዓለምና የውስጡን ሂደት በለውጥ ሕግ ላይ መሠረተው፡፡ እርግጥ ነው ኢስላሙ ዓለም አሁን
ባለበት ድክመት አኳያ ስቃይ ውስጥ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ በንዲህ እንዳለ አይቀጥልም፡፡ ለውጥ
የዩኒቨርስ/ከውንያ ሕግ ነውና ነገሮች ይለዋወጣሉ፡፡

“ይህችንም ቀናት በሰዎች መካከል እናዘዋውራታለን፣ እንዲገሰጹና አላህም እነዚያን


ያመኑትን እንዲያውቅ(እንዲለይ)፤ ከናንተም ሰማዕታትን(በሰማዕታትነት የሚገደሉን)እንዲይዝ
ነው“
(አል-ዒምራን 3፤40)
ደካማው ይበረታል፣ የበረታውም ይደክማል፡፡ እንደነበረና እንዳለ የሚቀጥል ነገር
የለም፡፡ በ2ኛው የመስቀል ጦርነት ጊዜ (1099) ሙስሊሞች የተባረከውን መሬትና የአቅሷን
መስጂድ ለ92 ተከታታይ ዓመታት ተነጥቀው መቆየት ግድ ሆኖባቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ላንዲት
ጀምበር እንኳን ግንባራቸው ሣይታጠፍ ፀንተው በመታገላቸው መጨረሻ ላይ ለድል በቁ፡፡
አሸነፉ፡፡ ዛሬም ቢሆን “ጊዜና ሁኔታው አይፈቅድም“ በሚል ሰበብ ብዙዎች ሊያሳምኑን
እንደሚሞክሩት ተስፋ መቁረጥና ለጠላት መበለጥ የለብንም፡፡ ወይም ለኢስራኢል እውቅና

44 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

በሚያስገኝ የሠላም ማዕቀፍ ውስጥ ገብተን መውተፍተፍ አንፈልግም፡፡ የዚህ ዓይነቱ አቋም
በሙስሊሞችና በየሁዶች መካከል እየተካሄደ ያለውን ትግል በምንም ዓይነት እንደማይወክል
ለወዳጅም ለጠላትም ግልጽ ይሁን፡፡

ኢንሻአሏሁ ተዓላ-
በቅርቡ ሌላውን ሰለሃዲን እናያለን፡፡ እሱ በ1187 (የደም ጎርፍ ሳይኖር) በተዋጣለት
ወታደራዊ ክህሎት የተባረከውን መሬት መልሶ በመቆጣጠር ሠላምና መረጋጋት እንዳሰፈነበት
ሁሉ እኛም ተጠናክረን፣ ደመናችን ሃይል አካብቶ በቦታው ላይ ሠላሙን የምናሰፍንበት ጊዜ
ሩቅ አይሆንም፡፡ እርግጥ ነው ሙስሊሞች አሁን ያሉበትን አስከፊ ገጽታ ለመቀየር በጣም ብዙ
መሥራት ይጠበቅባቸዋል፡፡ አለስራ ውጤት የለም፡፡

አልሐምዱሊላህ ኡማችን አበረታች የለውጥ አየር እያየም ነው፡፡ ላለፉት ሦስት


አስርታት ሙስሊሙ ዓለም ያላወሳው ኢስላማዊ መነሣሣት/ ተበኒህ አሁን አሁን የምሥራች
መስጠት ጀምራል፡፡ ፍሬው እየታየ ነው፡፡ የዚህ ፍሬ የላቀ ምልክት በሙስሊም ወጣቶች
እየተካሄደ ያለውና እጅግ ፈታኝ በሆነው መከራና ስቃይ ፊት አልበገር ብሎ የቆመው
የኢንቲፋዳህ ንቅናቄ ነው፡፡

ስለመጪው ጊዜም ቢሆን ከአላህ በኩል የተስፋ ቃል እንደተገባልን እናውቃለን፡፡


የሌላው ቃል ሁሉ ባጢል ነው የአላህ ብቻ ሲቀር፡፡ ስለእውነተኛውና ውሸተኛው የተስፋ ቃል
እንዲሁም ስለተባረከው ምድር የገባንበትን ትግል፣ ሱራህ አል-ኢስራእ ምን እንደሚል እናንብ፡
፡ እናስተንትን፡፡

ደሞም ነብዩላህ ዒሣ ዐለይሂ ሰላም እንደሚመለሱና በአላህ ዘንድ ተቀባይነት ያለው


ሃይማኖት “ኢስላም“ ብቻ መሆኑን እንደሚያረጋግጡ እናስታውስ፡፡ የዒሣ ዐለይሂ ሰላም
መመለስ በሙስሊሞች፣ መስህዩችና የሁዶች መካከል ያለማቋረጥ እየተካሄደ ያለው ትግል
ቀጣይ አካል ነው፡፡ እናም ዒሣ ኢብን መርየም በርግጥ ይመለሳሉ፡፡ ከዚያም ስለሳቸው፣
ስለአቅሷ እና ስለተባረከው መሬት እውነቷ ትወጣለች፡፡

ምዕራፍ ሶስት
የታሪክ ማስታወሻ
 በቅድመ ኑቡዋ (ነብዩ ከመላካቸው በፊት) ነብዩ አደም አለይሂ(ዐሰ) በመካ ካዕባን
ካቆሙ ካቆሙ ከ40 ዓመት በኃላ መስጂደል አቅሷን ሰሩ፡፡ እነዚህ ሁለት መስጂዶች
መጀመሪያ በመላዕክት እንደተሠሩም ይነገራል፡፡ ይህ ደሞ የሁዶች እንደሚሉት
መስጂደል አቅሷ ለነሱ የተለየ ያምልኮ ስፍራ አለመሆኑን ያሣያል፡፡ ምክንያቱም
መስጂዱ ህልውና ያገኘው ከኢብራሂም(ዐሰ)በፊት ነውና፡፡
 ነብዩ ኢብራሂም (ዐሰ) እና ልጃቸው ኢስማኢል(ዐሰ) ካዕባን እንደገና ካነጹ ከ40
ዓመት በኃላ እሳቸውና ሌላው ልጃቸው ኢስሐቅ(ዐሰ) መስጂደል አቅሷን እንደገና
ገነቡት፡፡
45 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

 ነብዩ ያዕቆብ የነብዩ ኢስሐቅ ልጅ ለመስጂደል አቅሷ እድሳት በማድረግ ጠቅላላውን


ወደ ውስጥ ባካተተ መልኩ አሻሻሉት፡፡ በአላህ ለሚያምኑት ሁሉ (እብራዊ ለሆኑትም
ላልሆኑትም ጭምር) ክፍት አደረጉት፡፡
 ነብዩላህ ያዕቆብና ልጆቻቸውም ከዩሱፍ(ዐሰ) ጋር ለመሆን ወደ ግብጽ ከተጎዳኙ በኃላ
እብራዊ ያልሆኑ የኢብራሂም ተከታዩች የመስጂዱን ክድሚያ በመረከብ በውስጡ
ዒባዳ ማድረጋቸውን ቀለጡ፡፡
 የሁዶች ወደፍልስጤም ከተመለሱ በኃላ ነብዩ ኢያሱ(ዐሰ) በሰላት ወደዛ
ለመቅጣጨት የሙሴን ድንኳን “በድንጋዩ” ላይ አቆመው፡፡
 ነብዩ ዳውድ(ዐሰ) የኢስራኢልን ስርወ መንግሥት መሠረተ፡፡ መስጂዱንም እንደገና
ለማነጽ ቦታና ዕቃ አዘጋጅቶ እንዳበቃ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ ከዚያም ልጁ ነብዩ
ሱለይማን(ዐሰ) በፊሊስጢን ተወላጆች እገዛ ስራው እንዲጠናቀቅ አደረገ፡፡ አዲሱ
ዴሉክስ ሕንጻ ዓለም ከዛ በፊት በማያውቀው ዓይነት የሕንጻ ጥበብ አርፎበታል፡፡
ተውቧል፡፡ ተጊጣል፡፡ የሁዶች “ሐይከል ሱለይማን /የሰሎሞን መቅደስ” የሚሉት
ይህንን እንደገና ማሻሻያ ተደርጎለት የተሰራውን የመስጂደል አቅሷ ውብ ሕንጻ ነው፡
፡ ሱለይማን(ዐሰ) ሕንጻውን ለማሰራት የመጀመሪያው ሰው እንዳልሆነ እየታወቀ
እንዲህ መባሉ ተራ ፈጣጣነት እንጂ ሌላ ሊሆን አይችልም፡፡
 በ586 ከክርስቶስ የባቢሎናውያን መሪ የነበረው ናቡኸዘነሱር ፍልስጤምን ወረረ፡፡
መስጂዱንም አወደመው፡፡ የሁዶችም በእስረኝነት ወደ ባቢሎን ተወሰዱ ተጋዙ፡፡
 የሁዶች (ከ150 ዓመት በኃላ) ወደ ፍልስጤም እንዲመለሱ ተፈቀደላቸው፡፡ ኢዝራ
ብዙ የመልሶ ግንባታ ሥራዎችን በማከናወን መስጂዱንም እንደገና ገንብቶ ሠራው፡፡
 የሁዶች ነብዩ የሕያን እና ነብዩ ዘከሪያን ገደሉ፡፡ ዒሣንም ለመግደል ሙከራ አድርገው
አልቻሉም፡፡ መስጂዱን ግን አወደሙት፡፡ ሕዝብ ክርስትያኑንም ከፍልስጤም
ጠራርገው አባረሩት፡፡

ድህረ ኑቡዋ (ከነብዩ መላክ በኃላ)


 ዑመር ኢብኑል ኸጣብ ኢየሩሳሌምን በተረከቡበት ጊዜ በመስጂዱ ቦታ ላይ አንድም
ቤተመቅደስ ወይም በተሰኪያን አልነበረም፡፡ እንደው ባዶውን ቀርቶ የከተማው
ነዋሪዎች የቆሻሻ መጣያ አድርገውት ነበር፡፡
 በድህረ ኑቡዋ መስጂደል አቅሳን እንደገና ለማነጽ ዑመር የመጀመሪያው ኻሊፍ ነበሩ፡
፡ ከሐራም አሸ-ሽሪፍ በስተደቡብ “ከቁበተል ኸድራ” ትይዩ አንድ ትንሽ መሰጂድ
በማቆም ጀመሩት፡፡
 የዑመር ኻሊፍ የነበረው አብዱል ማሊክ ቢን መርዋን የቁበተል
ኸድራን(በ68ሂ)እጅግ የተዋበ መስጅድ ከወርቃማ ቁባው ጋር አነጸው፡፡ በጣም
አድርጎም አስዋበው፡፡
 ሌሎች ኹለፎችና ዋሊወችም በሁለቱ መስጂዶች ላይ ማሻሻያ በማድረግና በማስዋብ
ሕንጻዎቻቸውን አስፋፉት፡፡ መድረሳዎችንና መርከዞችን፣ ሆስፒታሎችንና የቲም

46 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ሴንተሮችን፣ የእንግዳ ማረፊያና አገልግሎት መስጫዎችን ወደግቢው በመጨመር


ባንድ አዋቅረው አደራጁት፡፡
 ሳሊቢዩን የመስቀል ጦረኞች የአቅሷን መስጂድ በ1099 ተቆጣጠሩት፡፡ 70‚000
መደኒይን/ሲቪሎች (በአብዛኛው መስጂድ ውስጥ በተጠለሉበት)ተጨፈጨፉ፡፡
በሺዎች የሚቆጠሩ የሁዶች በቤተክርስያን ቅጽር ግቢ ተሰብስበው ተቃጠሉ፡፡
 በ1187 በሰለሃዲን አል-አዩቢ የጦር አመራር ቁድስ ነጻ ወጣች፡፡ መስጂዱ የመልሶ
ግንባታ ተደርጎለት እንደገና ታነጸ፡፡ ሰለሃዲን የሁዶች ከስደት ወደ ፍልስጤም
እንዲመለሱ ፈቀደላቸው፡፡ ወደ ቁድስ መግባት እንዲችሉም ዕድል ሰጣቸው፡፡
 ቀጣይ ሙስሊም መሪዎችም ለቁድስ፣ ለመስጂደል አቅሷ እና ለቁበተል ኸድራ
ከፍተኛ ትኩረት መስጠታቸውን በመቀጠል ለእድሳቱ፣ ለጥበቃውና ላገልግሎቱ ብዙ
ወጪ ሲደረግበት ቆይቷል፡፡
 በ1947 የተመድ የፍልስጤምን መከፋፈል አፀደቀ፡፡ አልቁድስ/ኢየሩሳሌም ዓለም
አቀፍ ግዛት ተባለች፡፡
 በ1947 የኢስራኢል መንግሥት ከመታወጁ ቀደም ብሎ የአይሁድ ወታደሮች
የተመድን የፖርቲሽን ውሳኔ በመጣስ ከቁድስ በስተምዕራብ ያለውን መሬት በሃይል
ያዙት፡፡
 በ 1948 ጽዩናውያን የኢስራኢል መንግሥት አወጁ፡፡ የምዕራብ ገማገም በኦርዶን
መንግሥት ሥር እንዲሆን ሲወስን የገዛ ሰርጥ ደም በግብጽ ስር እንዲሆን ተወሰነ፡፡
ኢየሩሳሌም ዓለም አቀፍ ስታተስ ተሰጥቷት በኦርዶን/ጆርዳን ተወላጆች ትስተዳደር
ጀመር፡፡
 በ 1967 ጽዩናዊት ኢስራኢል በአረቦች ላይ አዲስ ጦርነት በመክፈት ከሱርያው የጉለን
ከፍታ እና ከግብጹ የሲናይ ግዛት በተጨማሪ ምስራቅ ኢየሩሳሌም ምዕራብ
ገማገምንና የገዛን ሰርጥ ያዘች፡፡
የኢስላም ጠላቶች በሙስሊሙ ይዞታ ላይ ይህን ያህልና ከዚህም በላይ ጥቃት እያደረሱ
ናቸው፡፡ የቀራቸው ነገር የለም፡፡ድርጊታቸው የበደል በደል ነው፡፡

“የአላህንም መስጊዶች በውስጣቸው ስሙ እንዳይወሳ ከከለከለና እርሷንም በማበላሸት ከሮጠ


ሰው ይበልጥ በዳይ ማነው? እነዚያ ፈሪዎች ኾነው እንጂ ለነርሱ ሊገቡዋት የላቸውም፤ለነርሱ
በቅርቢቱ ዓለም ውርደት አላቸው፣ ለነርሱም በመጨረሻይቱ አገር ታላቅ ቅጣት አላቸው፡፡
”(2፡114)

ይህ በንዲህ እንዳለ ግን የኡማው ትግል በቀጥታ ከመቀላቀል ይልቅ በአጉል


ሚዛናዊነት ሥም ከኢስላም ማዕቀፍ ውጭ በሆነው የሠላም ሂደት መሳተፉን የመረጡ ሁሉ
በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ ፍልስጤምን ለይየሁዳ ለመሸጥ እያስማሙ እንደሆነ
መታወቅ አለበት፡፡

47 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

“ሚዛናዊነትን” ማለታቸው ከሆነ ከአላህ የበለጠ ሚዛናዊ የለም-

“ከነዚያ በሃይማኖት ካልተጋደሏችሁ፣ ካገሮቻችሁም ካላስወጡዋችሁ (ከሐዲዎች)


መልካም ብትውሉላቸውና ወደነርሱ ብታስተካክሉ አላህ አይከለክላችሁም፡፡ አላህ
ትክክለኞችን ይወዳልና የሚከለክላችሁ ከነዚያ በሃይማኖት ከተጋደሉዋችሁ፣ ከቤቶቻችሁም
ካወጣችሁ እናንተንም በማውጣት ላይ ከረዱት (ከሐዲዎች) እንዳትወዳጁዋቸው ብቻ ነው፡፡
ወዳጅ የሚያደርጋጓቸው ሰዎች እነዚያ እነርሱ በዳዩች ናቸው” (60፡8-9)

እነዚህን ሙጅሪሞች (በአላህ አንድነት የካዱ፣በአንድነቱም ላይ ያጋሩ፣ጣኦታውያን፣


አማልክት አምላኪዮች አረመኒዎችን መወዳጀት ክልክል ነው፡፡

“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ጠላቶቼንና ጠላቶቻችሁን ወዳጆች አድርጋችሁ አትያዙ፡፡”


(60፡1)

ከነሱ የሚወዳጅና የዓላማቸው መገልገያ የሚሆን ሁሉ

“….እርሱ ከነርሱ ነው፤” (5፡51)

የተፍሲር ኢማሞች፣ “ፈኢነሁም ሚንሁም” የሚለውን ቃል ከነሱ ካምፕ(ከየሁዳና


ከነሳራ) የሆነ ማለት እንደሆን ይገልፃሉ፡፡ ዕጣ ፈንታው እንደነሱ ነው፡፡

እንግዲህ በቁርአኑ ጥቅሶች ግልጽ ሁኖ እንደተቀመጠው ከየሁዳ እና ከአጋሮቻቸው


ጋር ሆን ብሎ መወገን፣ የዓላማቸው መገልገያ መሆን ምን ሊያስከትል እንደሚችለ ግልጽ ነው፡
፡ ይህን እያወቁ የጭቆናው መሣሪያ በሚሆኑት ላይ

1. በሞቱ ጊዜ ሰላተል ጀናዒዝ ሊሰገድባቸው አይፈቀድም


2. በሙስሊሞች መካነ መቃብር ሊቀበሩ አይችሉም
3. ከነርሱ ጋር ግንኙነትን መቁረጥ፤እነሱን አለመውደድና አለመወዳጀት ቢጢዎቻቸውን
ሁሉ መጥላት ግዴታ ነው፡፡

ይህ አቋም የራስ ወገን (አባት፤ልጅ፤ ባለቤትና ሌላም ቢሆን)በሆነው ላይ ሁሉ ይሠራል፡፡

48 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

“እናንተ ያመናችሁ ሆይ!አባቶቻችሁና ወንድሞቻችሁ ክህደትን ከእምነት አብልጠው ቢወዱ፣


ወዳጆች አድርጋችሁ አትያዙዋቸው፤ ከናንተ ውስጥ ወዳጅ የሚያደርጋቸው፣ እነዚያ እነሱ
በዳዩች ናቸው” (9፡23)

ከአላህ ከመልዕክተኛውና ከሙዕእሚኖች መንገድ እያወቁ በመውጣት የአላህንና


የሙስሊሙን ጠላት የተወዳጁትን መልሶ መወዳጀትም በራሱ የአላህን ቁጣ በራስ ላይ
መቀስቀስ ነው-

“…አባቶቻችሁንና ወንዶች ልጆቻችሁ፣ ወንድሞቻችሁም፣ የሰበሰባችሁት ሃብትም፣ መክሰሩዋን


የምትፈሩለት ንግድም፣ የምትወዷቸው መኖሪያዎችም፣ እናንተ ዘንድ ከአላህና
ከመልዕክተኛው፤ በርሱ መንገድም ከመታገል የበለጠ የተወደዱ እንደሆኑ አላህ ትእዛዙን
እስኪያመጣ ድረስ ተጠባበቁ በላቸው፡፡ አላህ አመጠኞች ሕዝቦችን አይመራም፤”(9፡24)
በመጨረሻም ሃቁ ይህ መሆኑ እየታወቀ በነዚህ ሰዎች ሥራ ውስጡን መደሰት፣እኩይ
ድርጊታቸውን እያዩ እንዳላዩ ማለፍ የአላህን የውስጥ ምርመራ እንደመካድ ነው፡፡

“ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህንና መልዕክተኛው ሕያው ወደሚያደርጋችሁ እምነት


በጠሯችሁ ጊዜ ለአላህና ለመልዕክተኛው ታዘዙ፣ አላህ በሰውየውና በልቡ መካከል የሚጋርድ
መሆኑን፣ወደርሱም የምትሰበሰኑ መኾናችሁን ዕወቁ፡፡ ከናንተም ውስጥ እነዚያን የበደሉትን
ብቻ ለይታ የማትነካን ፈተና ተጠንቀቁ፤አላህም ቅጣቱ ብርቱ መኾኑን ዕወቁ፡፡” (8፡24-25)

49 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ኢንቲሳር/- የፍልስጤሟ ሙሽራ


እረጭ ባለው ረሞጭ ምድረ-በዳ
በስደተኞች መንደር ወረዳ
ለሙሽሮች ደስታ ሲበተን ጽጌሬዳ
ከላይ ወረደ የሣት ናዳ
በአይሁድ እጅ የተሰናዳ
የግፍ ስጦታ
የማይለይ ዕድሜና ጾታ …
ገጸ በረከት መሆኑ ነው በድንኳን ለተደገሰ ጋብቻ
ከማሳው ተነቅሎ ስንዴው እንዳረም -እንዳራሙቻ
ጥግ በያዘበት የመሬት ኮትቻ
ዋ! ብቻ…
ሰውም ግመሉም ፍየሉም በየፊናው
ብትን ሲል ደመነፍስ እየነዳው
ድብልቅልቅ አርጐት የሳት ናዳው
ከጠራ ሰማይ የወረደው…
በዚህ መሃል ሁለቱ
ሙሽራውና ሙሽሪቱ
በ“ግር - አውጭኝ” የትም ሊደርሱ
ተያይዘው ሲወድቁ ሲነሱ
50 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

በመሃል አልቻለም እሱ
አቃተው መላወሱ፡፡

ዛለ ደከመ ጉልበቱ
ኢንቲሳር ተጨነቀች በብርቱ፡፡
የሰው ስጋ የቀመሰ
አሞራውም በሰማይ ተመላለሰ
ይህንን ማየቱ ዘገነናት
ሙሽራው ባሏ (ገና ሳይፈፀም) ውሃ ውሃ እያላት
የገዛ ደሙን አትግተው ጨነቃት
ጭንቅ ጥብብ አላት
ደሙን አስቁማ…
ሥቃዩን አስታማ ሕይወቱን ለማትረፍ
እርግፍግፍ አለች እንስፍስፍ…
…ተጨነቀች ተጠበበች
ዕንባዋ ሳይቀር ባፉ አነጠበች
የሚቻላትን ሆነች
ከሚቻላትም በላይ ሞከረች
ዕንጥሉን ቢያርስለት ብላ ከንፈሮቹም ላይ አለቀሰች

የሚቻላትን ሆነች
ከሚቻላትም በላይ ሞከረች
51 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

አመልካች ጣቱን ሲቀስር አብራው መሰከረች


የኢማን ውሉን ከቋጠረ- በቃ ተከተተ እያለች፡፡

በድኑን ታቅፋ በቁጭት እያየች


የሆነውን ሁሉ እያመላለሰች
ወደ አላህ ተከዘች
“ኢና ሊላሂ ወዒና ዒለይሂ ራጂዑን እያለች፡፡

በረደችናም- እንደመስከን ብላ
ደሞ ደፈረሰች እራሷን ነቅንቃ
የፊሊስጢኗ ምንጭ ያልተቀዳች ቡርቃ
ታትማ ያደገች በኢማን ተጠብቃ፡፡

ዕንባ ባንገቷ እየተለካ


ውስጥ አንጀቷን ሲነካ
በከፋው ሆድ ላይ የዕንባ ራጨቱ፤
እሣት ይፈጥራል ለካ!
ልቧ በቀል ጫረ
ነደሽ አንድጂ እያለ
ተቃጥለሽ አሳርሪ እያለ
የበቀል ግፊቱ ናረ
ሙት አካሉን ከጭኗ ላይ ወደ መሬት አለችው
52 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

የሰማይ አንበሶች እንዳይበሉትም በስስት እያየችው፡፡


ቋንቋ በኖራቸው ለሷ ሲሉ
እንዴት በተማፀነቻቸው ስጋውን እንዳይበሉ፡፡
እነሱም እንዳዘነ በነገሩ
ሁሉም ዋይ! ብለው በረሩ

እሷም ይሄኔ
ቁርጥን ማወቅ በለገሳት ወኔ
የሂጃባን ቅዳጅ እራፊ
ደም ያረጠበውን የጨርቅ ትራፊ

እፊቱ ላይ ጥላ
/ሥፍራው እንዳይጠፋት በበረሃው ማምሻ
ምልክጽ ብጤም አድርጋ

እንደመሄድ አለች ጨክና


ወደኃላም እየተገላመጠች አዝና

ህቅ እንቅ እያደረጋት ዕንባ


በቁጣ ያዝ አርጋው ወደ ውስጥ አምቃ

ከተማ ስትደርስ እጅግ ብዙ ሮጣ


የዋጠችው ብሽቀት ፈነቃቀሏት ወጣ

እያንገፈገፋት አደባባይ ቆማ

53 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ያገኛትን ጉድ ስትናገር ጩኻ

የዕልህ ዕንባ ካይኗ ፈሰሰ


በፊቷ ትኩሳት ከተማው ጨሰ

የጋለ አየር ካፍንጫዋ ነፈሰ


የሰውም እራስ እንደዛፍ ተላወሰ
ተርመሰመሰ - ተቀሰቀሰ….

“ያ ቢላዲ/ያ ቢላዲ/” ተባባለ


አላሁ አክበር! አላሁ አክበር! አለ
ኢንቲፋዳው ቀጠለ፤…

ፍልስጤም
ገዛ ረፋእ ኢየሩሣሌም
የግፍ ዱላ ቅጥቃጤ ጥቁር ደም
በድርድር እማይታገም
የግፍ ዱላ ቅጥቃጤ እብጠቱ
በገዛ መሬት ላይ ነፃነት የማጣቱ
አስቆጥቶ አስጨንቆ ወኒ ሲያግት
በኢማን ሙላት ሲነሽጥ
በሠይፍ ስለት ነው ‘ሚወጣለት’

54 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

በጂሃድ ብቻ ነው ‘ሚለይለት’

የምን ድርድር ምን ሊፈይድ


ቀለሙ ሣይደርቅ ለሚጣስ ሰነድ

ፍልስጤም
በይት ጃላ በይት ለሐም
የሙስሊሙ የዓመታት ሕመም
የቁጣው ንዝረት ትርታ
ከቁበተል ኸድራ ሚመታ
እያለ ኢላ- መታ

እስከ መቼ ድረስ
ፒስ- ፕሮሰስ
ይሉናል ፒስ-ፒርሰስ
ከበስተጀርባው ረሣስ
ሕዝቡን ለመጨረስና መሬቱን ለመውረስ
ፍልስጤም
ጦርነት ባንቺ ግድም
ድል የሚታፈስበት ነው ከጥንትም
እየወቃሽ ነው ዘንድሮም

55 | ገ ገ
[የተቀደሰው የፍልስጤም ምድር] በ ዘይነብ ሐሰን

ይብላኝለት እንጂ ለሌላው


ባንቺ ላይ እየሞተ ሸሂድ መሆን ሲገባው
ዝን ብሎ ላለው
ይብላኝለት ለንደዛው

አንቺማ ምን አለብሽ
እውስጥሽ እየተቀጣጠሉ እንደጥይት አረር ልጆችሽ
የጋለ ጠመንጃ አፈሙዝ ነው አይያዝም መሬትሽ
አይጨበጥም ግዛትሽ
ያቃጥላል ዛትሽ

56 | ገ ገ

You might also like