ADSWE New 4th Round Collective Agreement
ADSWE New 4th Round Collective Agreement
መግቢያ ............................................................................................................................................. 1
አንቀጽ አራት (4) በህብረት ስምምነቱና አግባብ ባላቸው ህጎች መሀል ያለው ግንኙነት ....................... 5
አንቀጽ ዘጠኝ (9) ቅጥር፣ ምደባ፣ የደረጃ ዕድገት፣ ዝውውር፣ ትምህርትና ስልጠና .............................. 15
ክፍል አራት..................................................................................................................................... 44
ii
መግቢያ
አማራ የዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ድርጅት በአማራ ብሄራዊ ክልል የመንግስት ልማት
ድርጅቶች አመሰራረት፣ አደረጃጀት፣ አመራርና ድጋፍ አሰጣጥን ለማቋቋም በወጣ አዋጅ ቁጥር
236/2008 ዓ.ም አንቀጽ 46 ንዑስ አንቀጽ 1 (ሀ) መሰረት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት
መስተዳድር ምክር ቤት መጋቢት 22 ቀን 2010 ዓ.ም ባወጣው ደንብ ቁጥር 161/2010 ዓ.ም
እንደገና የተቋቋመ መንግስታዊ የልማት ድርጅት ነው፡፡
በመሆኑም በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 "አሰሪ" እየተባለ በሚጠራው
በአማራ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ድርጅት እና "የሠራተኛ ማኀበር" ወይም “ማህበር” ተብሎ
በሚጠራው የአማራ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ድርጅት መሰረታዊ የሠራተኛ ማኀበር
መካከል ይህ አራተኛ (4ኛ) ዙር የኀብረት ስምምነት ዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2013 ዓ.ም ተፈረመ፡፡
1
አንቀጽ ሁለት (2) አጭር ርዕስ
የቃሉ አግባብ ሌላ ትርጉም ካልተሰጠው በስተቀር ይህ የህብረት ስምምነት ‹‹አራተኛው
(4ተኛው) የአማራ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ድርጅትና የአማራ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች
ድርጅት መሰረታዊ ሰራተኛ ማህበር የህብረት ስምምነት›› ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
2
ታይቶ በልዩ ሁኔታ በሚወሰነው መሰረት በእየለቱ ለቁርስ፣ ለምሣ፣ ለእራትና ለመኝታ
እንደቆይታው የሚከፈለው ክፍያ ነው፡፡
3.9 “ቤተሰብ” ማለት የሠራተኛው/ዋ ሕጋዊ ሚስት/ ባል፣ ልጆች፣ እናት፣ አባት፣ ወንድምና
እህት፣ አክስት፣ አጎት የሆነ የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመድ ማለት ነው፡፡
3.10 “ማስጠንቀቂያ” ማለት ለአንድ ሠራተኛ የቅርብ ሀላፊው ወይም የበላይ ሀላፊው የጥፋቱን
ዓይነትና አድራጎት እንዲሁም የደንቡን አንቀጾች ጠቅሶ ጥፋቱ እንዳይደገም በቃል
ወይም በጽሑፍ የሚሰጥ ተግሳጽ ነው፡፡ በቃል የሚሰጠው ማስጠንቀቂያ በፁሑፍ
የሚገለፀ ይሆናል፡፡
3.11 “የሕክምና ፈቃድ” ማለት በመንግስት ህጋዊ ዕውቅና ከተሰጣቸው ከግልም ሆነ
ከመንግስት የሕክምና ተቋማት የሚገኝ በፁሁፍ የተረጋገጠ የህመም ፈቃድ ነው።
3.12 “የደመወዝ እርከን ጭማሪ” ማለት በድርጅቱ ውስጥ ቢያንስ ለአስራ ሁለት ተከታታይ
ወራት ላገለገሉ ላልተወሰነ ጊዜ (ቋሚ) እና ለተወሰነ ጊዜ/ ስራ (ኮንትራት) ሰራተኞች
በየበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ሀምሌ ወር ጀምሮ የደረጃ ለውጥ ሳይኖር በያዙት የደመወዝ
ደረጃ ከፍታ የድርጅቱን ትርፋማነት መሰረት አድርጎ በሚወሰነው መሰረት ወደ ጎን
እርከን ከደመወዛቸው ላይ የሚጨመር የደመወዝ እርከን ጭማሪ ነው፡፡
3.13 “የትርፍ ስዓት ስራ” ማለት በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጁና በዚህ የህብረት ስምምነት
ከተወሰነው የቀኑ መደበኛ የሰራ ስዓት በላይ የሚሰራ ስራ የትርፍ ስዓት ስራ ነው፡፡
3.14 “የሥራ” ወይም “የደንብ ልብስ” ማለት አንድ ሰራተኛ ስራውን በሚያከናውንበት ጊዜ
እንደ ሰራው ፀባይ ለስራው ማከናወኛ ወይም ለሰራተኛው ደህነነትና ንፅህና
እንዲያገለግል የሚሰጥ ልብስ፣ ጫማ ወይም ሌላ ለስራ ሲባል የሚሰጥ የስራ መገልገያ
መሳሪያ ነው፡፡
3.15 “የአደጋ መከላኪያ መሳሪያ” ማለት የድርጅቱን ንብረትና ሰራተኛውን ከአደጋ ለመከላከል
የሚሰጥ ወይም የሚተከል ወይም የሚቀመጥ የመከላከያ መሳሪያ ነው፡፡
3.16 “ቅሬታ” ማለት በዚህ ስምምነት ወይም በህግ ትርጉም ወይም አፈፃፀም ችግር ምክንያት
በድርጅቱና በሰራተኛው ወይም በድርጅቱና በማህበሩ መካከል በሚፈጠረው
አለመግባባት ጉዳይ ለሚመለከተው አካል የሚቀርብ አቤቱታ ማለት ነው፡፡
3.17 “የሰራተኛ ተጠሪ” ማለት የማህበሩ የስራ አሰፈፃሚ ኮሚቴና በቅሬታ አቀራረብ ስነ
ስርዓት ውስጥ ለተጠቀሰው በማንኛውም ደረጃ ሰራተኛውን በመወከል ጉዳዩን
ለመከታተል ወይም ከሰራተኛው ጋር ለመመካከር እንዲችሉ ኮሚቴው የሚወክላቸው
ሰራተኞች ወይም ሌሎች ህጋዊ ውክልና ያላቸው ናቸው፡፡
3
3.18 “የደረጃ ዕድገት” ማለት አንድን ሰራተኛ ከነበረበት የስራ ደረጃና ደመወዝ ወደ ተሻለ
የስራ ደረጃና ደመወዝ ከፍ አድርጎ ማሳደግ ወይም መመደብ ማለት ነው፡፡
3.19 “የስራ መደብ” ማለት በድርጅቱ አደረጃጀት የተካተተና በአዋጅ ቀጥር 1156/2011
አንቀፅ 9 እና 10 በተገለፀው መሰረት በተደረገ የስራ ውል ሰራተኛ የተቀጠረበት ወይም
የተመደበበት ወይም የሚቀጠረበት የስራ መደብ ነው፡፡
3.20 “ተዋዋዩች” ማለት በዚህ የህብረት ስምምነት ላይ የተደራደሩና ስምምነታቸውን
በፊርማቸው ያረጋገጡ የድርጅቱና የማህበሩ ተወካዮች ማለት ነው፡፡
3.21 “የአስተዳደር ኮሚቴዎች” ማለት ለደረጃ ዕድገት፣ ለቅጥር፣ ለትምህርት፣ ለዲስኘሊንና
የመሳሰሉ መታየት ያለባቸውን አስተዳደር ነክ ጉዳዩችን ተመልክተው የውሳኔ ሀሳብ
ለማቅረብ ከድርጅቱና ከሰራተኛው ወገን ተመርጠው የሚሰሩ የተለያዩ ኮሚቴዎች
ናቸው፡፡
3.22 “ዝውውር” ማለት ከአንድ የስራ መደብ ወደ ሌላ ይሰሩበታል ተብሎ በሚታመንበት የስራ
መደብ ወይም ከአንድ የስራ ቦታ ወደ ሌላ የስራ ቦታ ተመሳሳይ መነሻ ደመወዝና ደረጃ
(ደመወዝ ደረጃ ከፍታ) ባላቸው እንዲሁም ተመሳሳይ የትምህርት ዝግጅትና የስራ ልምድ
በሚጠይቁ የሰራ መደቦች ላይ የሚፈፀም ጊዜያዊ ወይም ቋሚ ዝውውር ነው፡፡
3.23 “ትምህርት” ማለት ለድርጅቱ የስራ ዕድገት በማሰብ ሰራተኛው ችሎታውንና ዕውቀቱን
በማሻሻል የተሟላና የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እንዲችል ሲባል በሀገር ውስጥም ሆነ
ከሀገር ውጭ የሚሰጥ ነው፡፡
3.24 “ቦነስ” ማለት ድርጅቱ በአንድ በጀት ዓመት ካገኘው ትርፍ አንጻር እየታየ እያንዳንዱ
የድርጅቱ ሰራተኛ ባስገኘው የስራ አፈጻጸም ውጤትና የስራ ላይ ቆይታ ጊዜ አንጻር
እየተመዘነ፣ ወደፊት ለድርጅቱ የላቀ ትጋት አገልግሎት እንዲሰጥ ታስቦ ለሰራተኛው
ሊከፈል የሚችል ጉርሻ /bonus/ ነው፡፡
3.25 "ደመወዝ" ማለት በአዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 53 ንዑስ አንቀጽ 1 የተመለከተው
ትርጉም ይኖረዋል፡፡
3.26 "የአየር ፀባይ አበል" ማለት አንድ ሠራተኛ በተመደበበት የሥራ ቦታ ያለው የአየር
ፀባይ ለመኖር አስቸጋሪ በመሆኑ ምክንያት በመንግሥት በረሀ/ ቆላ ተብለው ተለይተው
በሚታወቁ ቦታዎች ተመድቦ ለሚሰራ ሰራተኛ ከሚከፈለው የወር ደመወዝ ወይም የቀን
ውሎ አበል ተመን ላይ በተጨማሪ የሚከፈል የማካካሻ ክፍያ ነው፡፡
4
3.27 ’’ተጠባባቂ’’ ማለት በአንድ በተለያዩ ምክንያቶች ክፍት የሆነ የሥራ መደብ ሲፈጠር
በቦታው ላይ በቋሚነት ሰው እስኪመደብ ድረስ የግድ ስራው መሰራት ስላለበት
በጊዜያዊነት ቦታውን ሸፍኖ የሚሰራ ሰራተኛ ነው፡፡
3.28 ’’ተወካይ’’ ማለት አንድ ሰራተኛ/ የስራ መሪ በተለያዩ ምክንያቶች ለተወሰነ ጊዜ ከስራው
ሲለይ በምትኩ የስራ መደቡን በመወከል ከያዘው ስራ ጋር ደርቦ እንዲሰራ አግባብ ባለው
አካል የሚመደብ ሰራተኛ ነው፡፡
3.29 በዚህ ኅብረት ስምምነት አደጋ የሚለው ቃል ድርጅቱ በገባው የኢንሹራንስ ፖሊሲ
መሠረት በአንድ ሰው ላይ ሳይፈቅደውና ሳይፈልገው የሚደርስበት ድንገተኛ የአካል
ጉዳት ወይም ሞት ነው፡፡
3.30 ማንኛውም በወንድ ጾታ የተገለፀው የሴትንም ጾታ ይጨምራል፡፡
5
አንቀጽ ስድስት (6) የድርጅቱ መብትና ግዴታዎች
6.1. የድርጅቱ መብቶች
ድርጅቱ ይህንን የህብረት ስምምነትና አሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ላይ
የተደነገጉትን ሳይቃረን የሚከተሉት መብቶች ይኖሩታል፡፡
6.1.1. በስራ ውል መሰረት የሰራተኛውን የስራ እንቅስቃሴና ክንውን የመምራት የማስተዳደርና
የመቆጣጠር፣
6.1.2. የድርጅቱን የስራ ፕሮግራም በማዘጋጀት የአሰራር ስልቶችን፣ መመሪዎችንና ደንቦችን
የማውጣት፣ የመፈፀም፣ የማስፈፀም፣
6.1.3. ሰራተኛን የመቅጠር፣ በስራ ደረጃ የማሳደግ፣ ጥፋት ሲኖር ከስራ ደረጃ ዝቅ ማድረግ፣
የማዛወር፣ የዲስፕሊን እርምጃ የመውሰድ፣ የማገድ፣ የማሰናበት፣
6.1.4. የስራ ደረጃዎችን ማውጣት፣ ማሻሻል፣ መለወጥ፣ መሰረዝ፣ የስራ ውክልና መሰጠት
እንዲሁም የደመወዝ ተመን ወይም ሌላ ክፍያ መወሰን፣
6.1.5. ለድርጅቱ ጥቅም ሲባል ያሉትን ሠራተኞች የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅን እንዲሁም
ሌሎች አግባብ ያላቸውን ህጎችና ይህን የህብረት ስምምነት በማይቃረን ሁኔታ እየሰሩ
ካሉበት ሥራ በሌላ ሥራ ላይ ለማሠራት ወይም ካሉበት የስራ ቦታ ወደ ሌላ የስራ ቦታ
አዛውሮ ማሰራት አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ አዛውሮ ማሠራት ይችላል። የተዛወረው
ሠራተኛም ቀደም ሲል የተመደበበትን የሥራ ደረጃና ደመወዝ እንዲሁም በተዛወረበት
የስራ መደብ የሚገኝ ጥቅም ካለ ያገኛል። ይሁን እንጂ ከሙያው ጋር ባልተዛመደ
ሁኔታ ሠራተኛን አያሰራም።
6.1.6. በኦዲት የተረጋገጠ የጥሬ ገንዘብ ወይም የንብረት ጉድለት ወይም ማናቸውም
ከሰራተኛው የሚጠየቅ የድርጅቱ ገንዘብ ካለ ሌሎች እርምጃዎችና የድርጅቱ ፋይናንስ
አሰራር እንደተጠበቁ ሆነው ከሰራተኛው ደመወዝ ከ1/3ኛ ያልበለጠውን በቀጥታ
በመቀነስ ለድርጅቱ ገቢ ማድረግ ይችላል፡፡
6.1.7. ያለአግባብ የደመወዝ፣ አበልና ጥቅማጥቅም ብልጫ ጭማሪ የተሰጠው ሠራተኛ
ሲያጋጥም የተሰጠውን ብልጫ ጭማሪ በየወሩ ከደመወዙ 1/3 እየቀነሰ ገቢ የማስደረግ
መብት አለው ፡፡
6.1.8. በሀኪም ቦርድ የቦታ ለውጥ የታዘዘለት ሠራተኛ ሊሰራ ወደሚችልበት ሌላ ቦታ ወስዶ
በዝቅተኛም ሆነ በተመሳሳይ የስራ መደብ አሰማርቶ የማሰራት መብት አለው፡፡
የሚመደብበት ቦታ ከጠፋ አስተያየት ጠይቆ ዘላቂ መፍትሄ መስጠት ይችላል፡፡
በሰራተኛው ላይ የተከሰተው የጤና ሁኔታ ታይቶ ከአንድ ዓመት በኋላ ምርመራ
6
እንዲያካሂድ ተደርጎ የጤናውን ሁኔታ ያገናዘበ ማስረጃ ሲቀርብ እንደገና የሚታይና
ምደባ የሚሰጠው ይሆናል፡፡
6.1.9. ድርጅቱ የሰራተኛውን የሙያ ፈቃድ ለመጠቀም ሲፈልገው የመጠቀም መብት አለው፤፤
7
6.2.7. ሠራተኛው የሰራበትን የሥራ መደብ፣ ደመወዝና የአገልግሎት ጊዜ የሚገልጽ ማስረጃ
እንዲሰጠው በጽሁፍ ከጠየቀ መስጠት፡፡
6.2.8. ሠራተኛው በዓመት ሁለት ጊዜ የግል ማህደሩን ለማየት በጽሁፍ ሲጠይቅ ለሰው ሀብት
አስተዳደርና ቡድን መሪ ወይም እርሱ የሚወክለው ባለሙያ ባለበት እንዲያይ ድርጅቱ
ይፈቅዳል፡፡
6.2.9. ማንኛውም ሠራተኛ በሥራ ላይ እንዳለ የምስክር ወረቀት ወይም የድጋፍ ደብዳቤ
እንዲሰጠው ምክንያቱን ገልፆ በጽሁፍ ሲጠይቅ ጥያቄው ተገቢ መሆኑ ከማህደሩ
ተመሳክሮ የጠየቀው እንዲሰጠው ይደረጋል።
6.2.10. በድርጅቱ ውስጥ የሚገኙት የሥራ መደቦች ተጠንተው ዝርዝራቸው ተዘጋጅቶ ከፀደቀ
በኋላ ለእያንዳንዱ ሠራተኛ ኃላፊነቱንና ተግባሩን የሚገልጽ የሥራ መዘርዝር (Job
Description) እንዲደርሰው ያደርጋል። በፕሮጀክቶች ላይ ሠራተኞች ሲመደቡ
ድርጅቱ ደብዳቤና የሥራ መመሪያ ይሰጣል።
6.2.11. ድርጅቱ ለድርጅቱ መሰረታዊ ሰራተኛ ማህበር ቋሚ ጽ/ቤት ያሟላል፡፡
6.2.12. ከሰራተኛ ማህበሩ ጋር በመተባበር ሰራተኞች የህብረት ስምምነቱን አንቀፆች ትርጉምና
አፈፃፀም በሚገባ እንዲረዱ አሰፈላጊውን ሁሉ ያደርጋሉ፡፡
6.2.13. የሰራተኛውን ጤንነት፣ ደህንነትና ሞራሉን ለመጠበቅ የስራ አካባቢውን ተገቢውን
ጥንቃቄ ያደርጋል፤ ከማህበሩ ጋርም በመመካከር አሰፈላጊ የሆኑ የመፍትሄ እርምጃዎች
ይወስዳል፡፡
6.2.14. ድርጅቱ የድርጅቱ ሰራተኞችን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የትምህርት ተቋማት
የድርጅቱ የወደፊት ዕቅድና ስልጠና ፍላጎት እና የስልጠና መመሪያ መሰረት
በማድረግ እንዲሰለጥኑ ያደርጋል፡፡
6.2.15. በዚህ የህብረት ስምምነትና በድርጅቱ መመሪያ መሰረት የሰራተኛውን የደረጃ ዕድገት፣
ደመወዝ ጭማሪ በየጊዜው እየተከታተለ ይፈጽማል፡፡
6.2.16. ለእያንዳንዱ ሰራተኛ የውጤት ተኮር ዕቅድና የስራ አፈፃፀም ምዘና ውጤት በዚህ
ስምምነት በአንቀፅ 29.1 እንዲሁም 29.2 መሰረት መሰጠቱን ያረጋግጣል፡፡
6.2.17. ድርጅቱ ለሰራተኞች በጠዋት በመግቢያና በማታ በመውጫ ሰዓት የትራንስፖርት
አገልግሎት ያቀርባል፡፡ የሰርቪስ መኪናው ሰራተኞችን የሚያሳፍርበት ቦታ
በድርጅቱና በማህበሩ በጋራ ይወሰናል፡፡ ነገር ግን በተለያዩ ከአቅም በላይ በሆኑ እንደ
መኪና ብልሽት፣ በሀገራዊ ወይም ክልላዊ ግዳጆች ድርጅቱ የትራንስፖርት አገልግሎት
ማቅረብ ካልቻለ ሰራተኛው በራሱ ትራንስፖርት ሥራ መግባት ይኖርበታል፡፡
8
ድርጅቱም ሰርቪስ መኪና ሳይኖር ሲቀር የድርጅቱ ሰራተኞች እንዲያውቁት በውስጥ
ሰሌዳ ማስታወቂያ ይለጥፋል፡፡
6.2.18. ድርጅቱ የበጀት አመቱ ሂሳብ በመዝጋት በውጭ ኢዲተር አስመርምሮ የውጤቱን ኮፒ
ለማህበሩ የሚያሳውቀው ከሀምሌ 1 ቀን ጀምሮ ባሉት 90 ቀናት ውስጥ ነው፡፡ ይህም
ተግባራዊ የሚሆነው ለቦርድ ቀርቦ ከፀደቀ በኋላ ነው፡፡
6.2.19. ሰራተኛ ሲቀጠር፣ ሲመደብ፣ የደረጃ እድገት ሲያገኝ፣ የዲሲፕሊን እርምጃ ሲወሰድበት፣
የስራ ምስጋና የተሳትፎ ደብዳቤ ሲሰጠው፣ ለትምህርት ሲሄድ፣ ሲዛወር፣ ሲሰናበትና
ሲሞት ድርጅቱ ለማህበሩ ያሳውቃል፡፡
6.2.20. በድርጅቱ ውስጥ አስተዳደር እንዳይዛባ፣ የምርት ጊዜ በክርክር እንዳይባክን፣
የአስተዳደር ፍትሕ እንዲሰፍን፣ ሠራተኛው መላ ኃይሉን፣ ችሎታውን እና ሙያውን
በሥራ ላይ እንዲያውል በበኩሉ የሚችለውን ሁሉ ያደርጋል፣
6.2.21. በማንኛውም ምክንያት የሥራ ውሉ ለተቋረጠበት ሠራተኛ የርክክብ ማስረጃ ሲያቀርብ
ድርጅቱ ሥራውን፣ ሙያውን፣ የሠራበት ዘመን፣ ደመወዙን ገልፆ እንደአስፈላጊነቱ
ፎቶግራፍ ያለበት የምስክር ወረቀት ይሰጣል፡፡
6.2.22. የዓመቱን የሥራ አፈፃፀም ሪፖርትና የሥራ መግለጫዎች እንዲሁም የሚቀጥለውን
የበጀት ዘመን የሥራ ዕቅድ ለማኀበሩ እንዲደርሰው ያደርጋል፣ ድርጅቱም ለማኀበሩ
ሥራ አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶችን ማኀበሩ ሲጠይቅ ይሰጣል፤
6.2.23. ይህን የህብረት ስምምነት ለማሻሻል ወይም ማህበሩ ሊሳተፍባቸው በሚገባቸው
በአዳዲስ የስራ ሁኔታዎች (የአሰራር ስርዓቶችና ማሻሻያዎች) ላይ ማህበሩን ለውይይት
ማሳተፍ፡፡
9
7.1.3 የሰራተኛ ማህበሩ ለድርጅቱ ስራ መሻሻል እና ሁለንተናዊ ዕድገት በድርጅቱ ዕቅድ፣
የስራ አፈፃፀም ክትትል እና ግምገማ ላይ እንዲሁም ትምህርትና ስልጠና፣ በዝውውር‹
በደረጃ እድገት፣ በቅጥር፣ በዲሲፕሊን፣ ኮሚቴዎች ላይ ይሳተፋል፡፡
7.1.4 አሰፈላጊ በሆነ ጊዜ ከደርጅቱ ጋር በመመካከር ማህበሩ በህጋዊ መንገድ ጠቅላላ ጉባኤ
የመጥራት ወይም የመሰብሰብ መብት አለው፡፡ ስብሰባም ሲጠራ በቅድሚያ ለድርጅቱ
ከ3 ቀናት በፊት አሳውቆ ሁለቱም በጋራ በሚስማሙበት ቀን ይሆናል፡፡
7.1.5 ለማህበሩ ስራ በድርጅቱ የተዘጋጀውን ማስታወቂያ ሰሌዳ የመጠቀም መብት አለው፡፡
7.1.6 ማንኛውም የስራ ሁኔታዎች በተመለከተ የድርጅቱ ሰራተኞች በመወከል የህብረት
ስምምነት መደራደር፡፡
7.1.7 ማሀበሩ ለሰራተኛው አገልግሎት መስጠት የሚችሉ መዝናኛዎችን ጨምሮ ሌሎች የገቢ
ማስገኛ ፕሮጀክት በድርጅቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ከድርጅቱ ጋር በመመካከር በሰራተኛውና
በድርጅቱ ስራ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የማያሳድሩ መሆኑን በማረጋገጥ የማቋቋም መብት
አለው ድርጅቱም አዋጭነቱን ሲያምንበት አስፈለጊውን ድጋፍ ያደርጋል፡፡
7.1.8 ለሰራተኛው ደህንነት ሲባል ካምፕ ባላቸው ፕሮጀክቶች ከድርጅቱ ጋር ሆኖ የካምፕ
አስተዳደር መመሪያ ያወጣል፡፡
11
8.2 የሠራተኛ ግዴታዎች
ሰራተኛው በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 13 ከንዑስ አንቀጽ 1-7
እና አንቀጽ 93 ከንዑስ አንቀጽ 1-5 እንዲሁም አግባብነት ባላቸው ህጉች ከተጠቀሱት
ግዴታዎች በተጨማሪ የሚከተሉት ግዴታዎች ይኖሩበታል፡፡
8.2.1. በተመደበበት ሥራ ሙሉ ችሎታውንና ዕውቀቱን በመጠቀም ለድርጅቱ ምርታማነት
ማደግ እንዲሁም ለሥራ አፈፃፀም ጥራት አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋል።
8.2.2. በዚህ ደንብ መሠረት የተዘረዘሩትን የዲሲፒሊን ሁኔታና የቅሬታ አቀራረብ ሥነ-
ሥርዓት ደንቦችን ያከብራል።
8.2.3. ድርጅቱ በየጊዜው የሚያዘጋጃቸውን ክትባቶችና የጤና ምርመራዎች ከኤች አይ ቪ
ኤድስ (HIV/ AIDS) በስተቀር ይፈጽማል።
8.2.4. ሠራተኛው የሥራ ሰዓትን በሚገባ ያከብራል፣ ከአቅም በላይ ካልሆነ በስተቀር አስቀድሞ
ፈቃድ ሳያገኝ ከመደበኛ ሥራው አይለይም።
8.2.5. ድርጅቱ ለመዝናኛና ለመመገቢያ ስፍራዎች የሚያወጣውን የሥነ-ሥርዓት
መመሪያዎችና ደንቦች ያከብራል።
8.2.6. ድርጅቱ ለሚይዘው የሠራተኛ ማህደር አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን የመስጠትና
በሰጣቸው መረጃዎች ላይም ለውጥ ባደረገ ቁጥር ይህንኑ በጽሁፍ ለድርጅቱ ያሳውቃል።
8.2.7. አንድ ሠራተኛ በልዩ ልዩ ምክንያት ከሥራው ሲለይና በቦታው ተተክቶ የሚሠራ
ሠራተኛ ሲያስፈልግ ሠራተኛውን ተክቶ ይሠራል።
8.2.8. ካምፕ በሚሠራባቸው አካባቢዎች ድርጅቱና የሰራተኛ ማህበሩ የሚያወጣቸውን የካምፕ
አስተዳደር ደንቦችና ሥነ-ሥርዓቶች ያከበራል።
8.2.9. ሠራተኛው ሥራውን በትጋት ያከናውናል፣ በድርጅቱ የሥራ ሰዓት የግል ሥራ
ማከናወን አይችልም።
8.2.10. በድርጅቱ ውስጥ ሠራተኛው በተለያዩ ኮሚቴዎች ሲመደብ ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ
ይሰራል። በዚህ መልክ የሚሠሩ ሠራተኞች ለኮሚቴው አገልግሎት የሚያውሉት ጊዜ
በኮሚቴው ሰብሳቢ በኩል ለሥራ ኃላፊው እንዲቀርብ ይደረጋል።
8.2.11. የድርጅቱ ሰራተኛ ሆኖ እያለ ድርጅቱን ሳይለቅ በሌላ መ/ቤት በመደበኛ የስራ ሰዓት
ሰራተኛ ሆኖ ማገልገል አይችልም፡፡ ይህ ሆኖ ከተገኘ ድርጅቱ ከስራ ያሰናብታል፡፡
8.2.12. ማንኛውም የድርጅቱ ሠራተኛ ከሥራ መልቀቅ ቢፈልግ ከአንድ ወር በፊት ለድርጅቱ
በጽሁፍ የማሣወቅ ግዴታ አለበት፡፡ በዚህ የተገለፀውን ያላሟላ ሰራተኛ ከመልቀቁ
በፊት የወር ደመወዙን ለድርጅቱ ይከፍላል፡፡ ሆኖም ከ15 ቀናት በላይ የማስጠንቀቂያ
12
ጊዜ ሰጦ የቆየ ሰራተኛ ከሆነ ማስጠንቀቂያ የሰጠበት ጊዜ ተቀንሶለት የቀሪውን ቀናት
ደመወዝ ለድርጅቱ እንዲከፍል ይደረጋል፡፡ 15 (አስራ አምስት) ቀናትና ከዚያ በታች
ከሆነ ግን ሙሉ የ30 (ሰላሳ ቀናት) መክፈል ይኖርበታል፡፡
8.2.13. በማናቸውም ጊዜ ቢሆን የድርጅቱንና የእርሱን ክብር እንዲሁም ሚስጥር ይጠብቃል፡፡
8.2.14. ሰራተኛ ህገወጥ ሰነዶችን አያሰራጭም፣ አይልክም በድርጅቱና በሰራተኛ ማህበሩ
መካከል አለመግባባትን የሚፈጥር፤ ወይም የድርጅቱን መልካም የስራ ሁኔታ የሚጎዳ፤
ወይም ከድርጅቱ ስራ ጋር በተገናኘ የድርጅቱንም ሆነ የማንኛውንም የስራ ሃላፊ/
ሰራተኛ ስም የሚያጎድፍ በማስረጃ ያልተረጋገጠ የሃሰት ወሬ፣ ሃሜት፣ ስም የማጥፋት
ተግባር ከመፈጸም መቆጠብ አለበት፡፡ ይህ አይነት ድርጊት በማንኛውም የመገናኛ
መንገድ መፈጸሙን ያወቀ ሰራተኛ ችግሩን ለድርጅቱና ለማህበሩ ማሳወቅ አለበት
8.2.15. ሰራተኛው ከቅርብ ሀላፊው የሚሰጡትን ማንኛውም የስራ የጽሁፍ ሰነዶች ይቀበላል
መልስ ያቀርባል፡፡ እንዲሁም ከቅርብ ሀላፊው የሚሰጠውን በስራ ውሉና በስራ ደንቡ
መሰረት ህጋዊ ትዕዛዞች አክብሮ ይሰራል፡፡
8.2.16. ሠራተኛው ከድርጅቱ በኃላፊነት የተረከባቸውን ወይም በስራ አጋጣሚ በእጁ የገቡ
ሰነዶች፣ ዕቃዎችና መሣሪያዎችን ወይም ሌሎች ንብረቶችን በጥንቃቄ ይይዛል፣
ይንከባከባል፣ ይጠብቃል፣ ሥራው ሲፈፀም መመለስ የሚገባውን መልሶ ለድርጅቱ
ያስረክባል፣ የድርጅቱን ንብረት ሆነ ብሎ ካበላሸ፣ ካጠፋ ወይም በድርጅቱ ንብረት
ወይም ጥቅም ላይ ማናቸውንም ሆነ ብሎ ጉዳት ካደረሰ ተጠያቂ ይሆናል፤
8.2.17. በሠራተኛው ላይ የተለዬ ፍርሃት፣ ጭንቀትና የመንፈስ መረበሽን የሚያሣድሩ፣ የሥራ
መንፈስና ምርታማነትን የሚፃረሩ ድርጊቶችን፣ ነውጥን፣ አድመኝነትን፣ በሠራተኛው
ውስጥ ከማስፋፋት መቆጠብ፤ ሌላው ሲያደርግ ቢያገኝ ወይም ቢሰማ የመታገል እና
ለድርጅቱ በወቅቱ ሪፖርት ማድረግ አለበት፡፡
8.2.18. በሥራው ምክንያት የማይገባውን ጥቅም ለማግኘት አይሞክርም፣ ማማለጃ ወይም ጉቦ
አይሰጥም ወይም አይቀበልም፡፡
8.2.19. ከድርጅቱ በሰነድ የወሰደውን ገንዘብ በሕጋዊ መንገድ የተጠቀመበትን በሕጋዊ የወጪ
ማስረጃዎች በወቅቱ የማወራረድ፣ በሥራው ያልተጠቀመበትንም ገንዘብ በድርጅቱ
የፋይናንስ ደንብ መሠረት ተመላሽ ማድረግ አለበት፡፡
8.2.20. የሥራ ውሉ ተቋርጦ ከድርጅቱ ሲሰናበት በእጁ የሚገኘውን የድርጅቱን ንብረት ወይም
ገንዘብ በሙሉ ያስረክባል ወይም ገቢ ያደርጋል እንዲሁም ዕዳ ካለበት ድርጅቱ
ለሰራተኛው የሚከፍለው ገንዘብ ካለ ዕዳውን ሙሉ ለሙሉ ቀንሶ ማስቀረት ይችላል፡፡
13
8.2.21. ሠራተኛው በኦዲት የተረጋገጠበት ዕዳ ሲኖርበት ድርጊቱ ከስራ የማያሰናብት ከሆነ
ድርጅቱ በየወሩ ከሰራተኛው ደመወዙ ላይ 1/3 እየቆረጠ ያስቀራል፡፡ ሠራተኛውም
የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡ ሆኖም ይህ ከአስተዳደራዊም ሆነ ከወንጀል ተጠያቂነት
አያድነውም፡፡
8.2.22. ድርጅቱ የሰራተኛውን የሙያ ፈቃድ ሲፈልገው ሰራተኛው የመስጠት ግዴታ አለበት፤፤
14
ክፍል ሁለት
አንቀጽ ዘጠኝ (9) ቅጥር፣ ምደባ፣ የደረጃ ዕድገት፣ ዝውውር፣
ትምህርትና ስልጠና
9.1 ቅጥር
9.1.1 በድርጅቱ ውስጥ የሰራተኛ ቅጥር የሚፈፀመው በአዋጅ ቁጥር 1156/2011፣ በዚህ ህብረት
ስምምነትና ይህን ህብረት ስምምነት መሰረት በማድረግ በወጣው በድርጅቱ የሰው ሀብት
ሥራ አመራር መመሪያ መሰረት ይሆናል፡፡ መመሪያው ለሰራተኛ ማህበሩ በቅጅ
እንዲደርሰው ይደረጋል፡፡
9.1.2 ከስራ መሪና ከዋና ስራ አስፈፃሚ አማካሪ ውጭ በቀላሉ ገበያ ላይ በማይገኙ፣ ለከፍተኛ
ፕሮጀክቶች ለሚያስፈልጉና በተመሳሳይ ደረጃ ባሉ የፕሮፌሽናልና የቴክኒክ ሙያ የስራ
መደቦች ላይ ለድርጅት ጥቅም ሲባል በድርጅቱ ማኔጅመንት ውሳኔ ያለውድድር በፈታና
ወይም ያለፈተና ቀጥታ ቅጥር ይፈፀማል፡፡
9.1.3 ከላይ በ9.1.2 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ አንድን ከተሿሚ፣ ከሥራ መሪና ከአማካሪ
ውጭ ያለ ክፍት የሥራ መደብ ከድርጅቱ ስራተኞች ውስጥ በዝውውር እና በደረጃ
እድገት መሙላት ሳይቻል ሲቀር የውጭ ተወዳዳሪዎች ለቅጥር በማስታወቂያ ሊጋበዙ
ይችላል፡፡
9.1.4 የሰራተኛ ቅጥር የሚፈፀመው በግልፅ ውድድር ሲሆን ለተጠየቀው ቦታ ተፈላጊውን
መስፈርት እና በቅጥርና የደረጃ ዕድገት ኮሚቴ የሚሰጠውን መመዘኛ አሟልቶ ሲገኝ
ቅጥሩ ይከናወናል፡፡ ለቅጥር በሚሰጥ የተግባርም ሆነ የጽሁፍ ፈተና ተወዳዳሪዎች
ቢያንስ 60 (ስልሳ) ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይኖርባቸዋል፡፡
9.1.5 በማጭበርበር፣ በስርቆትና በሌሎች የሙስና ጉዳዩች በዲስኘሊን የተባረረ ሰራተኛ
በድጋሚ በድርጅቱ መቀጠር አይችልም፡፡ ሆኖም በሌሎች የዲስኘሉን ጉዳዩች የሥራ
ውላቸው የተቋረጠ ሠራተኞች እስከ 2 (ሁለት) አመት ድረስ በድርጅቱ መቀጠር
አይችሉም፡፡
9.1.6 ላልተወሰነ ጊዜ (በቋሚ) በሚወጣ ክፍት የሥራ መደብ ላይ በድርጅቱ ለተወሰነ ጊዜ/
ሥራ (በኮንትራት) የተቀጠረ ሰራተኛ ስራ ላይ እያለ ላልተወሰነ ጊዜ (በቋሚ) ቅጥር
ማስታወቂያ ቢወጣ መስፈርቱን እስካሟላ ድረስ እንደማንኛውም ተወዳዳሪ ተመዝግቦ
መወዳደር ይችላል፡፡ ካለፉ የተወሰነ ጊዜ ቅጥሩ በስምምነት ተቋርጦ ባለፉበት ቋሚ የስራ
መደብ ላይ በአዲስ መልክ ሊቀጠሩ ይችላል፡፡
15
9.1.7 በድርጅቱ ለተወሰነ ጊዜ/ ሥራ (በኮንትራት) የተቀጠረ ሰራተኛ ሆኖ በድርጅቱ ቢያንስ
አንድ ዓመት ያገለገለ ስራ ላይ እያለ ሌላ ካለበት ደረጃ የተሻለ የተወሰነ ጊዜ/ ስራ
(ኮንትራት) ቅጥር ማስታወቂያ ቢወጣ መስፈርቱን እስካሟላ ድረስ እንደማንኛውም
ተወዳዳሪ ተመዝግቦ መወዳደር ይችላል፡፡ ካለፈ የተወሰነ ጊዜ/ ስራ ቅጥር ውሉ
በስምምነት ተቋርጦ ባለፈበት የተወሰነ ጊዜ/ስራ የስራ መደብ ላይ በአዲስ መልክ
ሊቀጠር ይችላል፡፡
9.1.8 በድርጅቱ ላልተወሰነ ጊዜ (ቋሚ) የተቀጠረ ሰራተኛ ሆኖ በድርጅቱ ቢያንስ አንድ
ዓመት ያገለገለ ስራ ላይ እያለ ሌላ ካለበት ደረጃ የተሻለ የተወሰነ ጊዜ/ ስራ (ኮንትራት)
ቅጥር ማስታወቂያ ቢወጣ መስፈርቱን እስካሟላ ድረስ እንደማንኛውም ተወዳዳሪ
ተመዝግቦ መወዳደር ይችላል፡፡ ካለፈ ላልተወሰነ ጊዜ (ቋሚ) ቅጥር ውሉ በስምምነት
ተቋርጦ ባለፈበት የተወሰነ ጊዜ/ ስራ የስራ መደብ ላይ በአዲስ መልክ ሊቀጠር
ይችላል፡፡ የተወሰነ ጊዜ ቅጥሩ ሲጠናቀቅ በውሉ መሰረት የሚቋረጥ ይሆናል፡፡ የቋሚ
ጥያቄ ቢያነሳ ተቀባይነት የለውም፡፡
9.1.9 በአንድ የስራ መደብ ላይ በቅጥር ተወዳድሮ ከማለፊያ ነጥብ በታች ያመጣ (የወደቀ)
ተወዳዳሪ በዚሁ የስራ መደብ ላይ በድጋሚ መወዳደር የሚችለው ውጤቱ ከታወቀ ከ3
ወር በኋላ ነው፡፡
16
9.3.2 በተለያየ ምክንያት በስራ መደቡ ላይ የነበረ ሠራተኛ/ የስራ መሪ በማይኖርበት ጊዜ
በሰራተኛው የቅርብ ሀላፊ ወይም በራሱ በስራ መሪው ውክልና የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ተጠባባቂነት ግን በዋና ሥራ አስፈፃሚ/ በጽ/ቤት ሀላፊ ውሳኔ ተፈፃሚ ይሆናል።
9.3.3 ማንኛውም ውክልና ከዝቅተኛ የኃላፊነት ደረጃ ወደ ከፍተኛ ወይም ተመሳሳይ ወይም
ትይዩ የስራ ደረጃ ይሆናል፡፡ ይህም ከስራ ጋር የተያያዘ መሆን ይኖርበታል፡፡
9.3.4 በማንኛውም ክፍት በሆኑ የሥራ መደቦች ላይ በተጠባባቂነት ሰራተኛው ከሰራ
በተጠባባቂነት ከተመደበበት ጊዜ ጀምሮ ለስራ መደቡ የተፈቀደ የሀላፊነት አበል ካለ
ይከፈለዋል፡፡
9.3.5 በፈቃድ፣ በህመምና በሌሎች በማንኛውም ምክንያት ለጊዜው ቀሪ የሆነ የሥራ መሪን
ወክሎ ከ30 ቀን በላይ ለሰራ ሰራተኛ ለስራ መደቡ የተፈቀደ የሀላፊነት አበል ብቻ ካለ
ይከፈለዋል፡፡ ክፍያው የሚፈጽመው ሠራተኛ በቦታው ተወክሎ እስካገለገለ ድረስ ብቻ
ነው፡፡
9.3.6 የተጠባባቂ ምደባ ከስድስት ወራት አይበልጥም። ሆኖም ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ
ሲያጋጥም ለተጨማሪ ስድስት ወራት ሊራዘም ይችላል።
9.3.7 በአንቀጽ 9.3.6 በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ ድርጅቱ ቋሚ ምደባ ካላደረገ
ሠራተኛው ይህንኑ በጽሁፍ በመግለጽ የተጠባባቂነት ኃላፊነትን ሥራ የመተው መብት
ይኖረዋል፡፡
17
9.4.3 ከላይ 9.4.1 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ክፍት የሥራ መደቦች ሲፈጠሩ/ ሲኖሩ
ላልተወሰነ ጊዜ (ቋሚ) ሠራተኞች ለመመዝገብ እንዲችሉ ድርጅቱ ማስታወቂያ
ይለጥፋል። በተጨማሪም በወቅቱ መስክ ላይ ላሉ ላልተወሰነ ጊዜ (ቋሚ) ሠራተኞች
የመገናኛ ችግር እስካላጋጠመ ድረስ እንዲያውቁት ይደረጋል። በማስታወቂያውም
የመመዝገቢያ ቀን፣ ሰዓትና ቦታ እንዲሁም መመዘኛዎችና ምዝገባው የሚጠናቀቅበት
ቀንና ሰዓት ይገለፃል። ሆኖም የመገናኛ ችግር ካለና ደረጃ እድገቱ የሚመለከተው
ሰራተኛ ሆኖ ከተገኜ በቅርብ ሃላፊው በኩል እንዲመዘገብ ይደረጋል፡፡
9.4.4 በውስጥ ማስታወቂያ ለደረጃ ዕድገት የሚወጣ ክፍት የሥራ መደብ ለ5 (አምስት)
ተከታታይ የሥራ ቀናት መቆየት ይኖርበታል። በእነዚህ ቀናት ውስጥ እጩ ተወዳዳሪ
ካልቀረበ በስራ መደቡ ላይ እስከ 1 (አንድ) ወር ጊዜ ውስጥ የውጭ ቅጥር ማስታወቂያ
እንዲወጣ ይደረጋል። ከአንድ ወር በላይ ከዘገየ ግን ድጋሚ የደረጃ ዕድገት ሊወጣ
ይገባል፡፡
9.4.5 የደረጃ እድገት ማስታወቂያዎች ወጥተው ለሥራው ተፈላጊ ሰው ከተመዘገበ በኋላና
የምዝገባው ጊዜ ካለቀበት ቀን ጀምሮ ኮሚቴው ከ10 ቀናት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የውሳኔ
ሀሳቡን ያቀርባል።
9.4.6 የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይም ውክልና የተሰጠው አካል በቅጥር፣ እድገትና
ዝውውር ኮሚቴ የቀረበለትን የደረጃ ቅደም ተከተል እና የውድድር አካሄዶችን አጥንቶ
በ5 (አምስት) የሥራ ቀናት ውስጥ ውሳኔውን ይሰጣል።
9.4.7 የደረጃ እድገት ኮሚቴው የውሳኔ ሃሳብ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይም ውክልና በተሰጠው
አካል ከፀደቀ በኋላ የሁሉም ውጤት በማስታወቂያ ሰሌዳ ይለጠፋል።
9.4.8 ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይም ውክልና የተሰጠው አካል ከደረጃ እድገት ኮሚቴ የቀረበው
የውሳኔ ሀሳብ ውሳኔ ለመስጠት የማያስችል ሆኖ ሲያገኘው ወይም ኮሚቴው
ያላገናዘባቸው ነጥቦች ሲኖሩ ወይም ምዘናውና የኮሚቴው አሰራር ግልጽ ሆኖ ሳይቀመጥ
ሲቀር ይህንኑ በመጥቀስ እድገቱ እንደገና እንዲጠና ለኮሚቴው ይመራል። ዋና ሥራ
አስፈጻሚ ወይም ውክልና የተሰጠው አካል ከኮሚቴው በድጋሚ የቀረበለትን አስተያየት
በመመርመር የመጨረሻ ውሳኔ በ5 (አምስት) ቀናት ውስጥ ይሰጣል።
9.4.9 የቅጥር፣ የደረጃ እድገትና ዝውውር ኮሚቴ በሚከተለው ሁኔታ ይመሰረታል።
የሰው ሀብት አስተዳደር ቡድን መሪ----------------------------------------------------- ሰብሳቢ
የሰው ሀብት ኦፊሰር/ ባለሞያ---------------------------------------------------------------- አባል
የሰራተኛ ማህበር 2 (ሁለት) ተወካይ------------------------------------------------------- አባል
18
ክፍት የሥራ መደቡ በቅጥር/ በደረጃ እድገት እንዲሟላለት የጠየቀው የስራ ዘርፍ/
ክፍል ኃላፊ ወይም ተወካይ------------------------------------------------------------------ አባል
9.4.10 ለአንድ ክፍት የስራ መደብ (ቦታ) መስፈርቱን አሟልቶ የተገኘ አንድ ወይም ብቸኛ
ተወዳዳሪ ቢሆን ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች አሟልቶ ከተገኘና በተሰጠው ፈተና
እና በአጠቃላይ የማወዳደሪያ መስፈርት ዝቅተኛ የማለፊያ ነጥብ ካስመዘገበ እድገቱን
ማግኘት ይችላል፡፡ ለደረጃ ዕድገት በሚሰጥ የተግባርም ይሁን የጹሁፍ ፈተና
ተወዳዳሪው/ዎች ወደ ሚቀጥለው ውድድር ለማለፍ ቢያንስ 50 (ሀምሳ) በመቶ
ማስመዝገብ ይኖርባቸዋል፡፡
9.4.11 የደረጃ እድገት የተፈቀደለት ሠራተኛ የደረጃ እድገቱ ከፀደቀበት ቀን ጀምሮ ለሥራ
መደቡ የተወሰነውን መብትና ጥቅም ያገኛል።
9.4.12 የደረጃ እድገት የሚያገኝ ሠራተኛ የሚያገኘው የደመወዝ ጭማሪ በድርጅቱ የሰው
ሀብት ሥራ አመራር ወይም የምልመላና መረጣ መመሪያ መሠረት ይሆናል።
9.4.13 ለደረጃ እድገት የሚወዳደር ሰራተኛ የቅርብ ጊዜ ተከታታይ የ2 ጊዜ የስራ አፈፃፀም
ምዘና ውጤት እያንዳንዱ ከ60% በታች መሆን የለበትም፡፡ የ2 ጊዜ ከሌለ የአንድ ጊዜ
ከበቂ ምክንያት ጋር ሊያዝ ይችላል፡፡
9.4.14 አንድ ስራተኛ የደረጃ ዕድገት ካገኘ አንድ ዓመትና ከዚያ በላይ ከሆነው በሌላ የደረጃ
ዕድገት ሊወዳደር ይችላል፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት ግን ሊወዳደር አይችልም፡፡
9.4.15 አዲሰ ሰራተኛ ተቀጥሮ በድርጅቱ ውስጥ አንድ ዓመት ከሰራ እና መስፈርቱን ካሟላ
የደረጃ ዕድገት ሊወዳደር ይችላል፡፡
9.4.16 በአንድ የስራ መደብ ላይ በደረጃ እድገት የተመደበ ሰራተኛ ከ3 ወር በፊት ቢለቅ
የደረጃ ዕድገት ማስታወቂያ ማውጣት ሳያስፈልግ ቀደም ሲል በዚህ የስራ መደቡ ላይ
ተወዳድረው ከነበሩት ሰራተኞች መካከል የማለፊያ ነጥብና በላይ ካመጡት ውስጥ
በውጤታቸው ቅደም ተከተል መሰረት የደረጃ ዕድገቱ ይሰጣል፡፡
9.4.17 በአንድ የስራ መደብ ላይ ተወዳድሮ ከማለፊያ ነጥብ በታች ያመጣ (የወደቀ) ተወዳዳሪ
በዚሁ የስራ መደብ ላይ በድጋሚ መወዳደር የሚችለው ውጤቱ ከታወቀ ከ3 ወር በኋላ
ነው፡፡
9.4.18 በማንኛውም በድርጅቱ ውስጥ በሚሰጠው የደረጃ እድገት ቅሬታ ያለው ህጋዊ በሆነ
መንገድ ቅሬታውን በወቅቱ በ3 (ሶስት) የስራ ቀናት ውስጥ ማቅረብ አለበት፡፡
9.4.19 በዚህ የህብረት ሥምምነት ስለቅጥርና ደረጃ እድገት የተገለፁትን በማያፈርስና
በማይቃወም ሁኔታ ሌሎች ያልተጠቀሱ ዝርዝር የዝውውር፣ የደረጃ እድገት እና
19
የቅጥር አፈፃፀሞች በድርጅቱ የሰው ሀብት አስተዳደር ወይም የምልመላና መረጣ
መመሪያ መሠረት የሚፈፀሙ ይሆናል፡፡
20
9.5.6 በኤች አይቪ /ኤድስ/ በደሙ ውስጥ ለመኖሩ ማስረጃ ያቀረበ ሰራተኛ ወደ ሚስማማው
ወይም ቤተሰብ ወዳለበት ቦታ ዝውውር ሲጠይቅ ቦታ እስካለ ድረስ ቅድሚያ ተሰጥቶት
እንዲዛወር ይደረጋል፡፡
22
አንቀፅ አስራ አንድ (11) የሥራ ውል የሚቋረጥበት ሁኔታ
11.1 የማንኛውም ሠራተኛ የሥራ ውል የሚቋረጠው በአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር
1156/2011 እና በዚህ የህብረት ስምምነት መሰረት ይሆናል፡፡
11.2 ሠራተኛው ከድርጅቱ ከሚፈለግበት ንብረት ወይም ገንዘብ ነፃ ስለመሆኑ ድርጅቱ
ባዘጋጀው የማረካከቢያ ወይም ክሊራንስ ቅጽ የሚመለከታቸው ክፍሎችን አስፈርሞ
እንዳመጣ የአገልግሎት የምስክር ወረቀትና ሌሎች ለሠራተኛው የሚገቡት ክፍያና
ጥቅሞች በሰባት (7) ቀናት ጊዜ ውስጥ ተሟልተው ይሰጡታል፡፡
11.3 የሥራ ውሉ የተቋረጠ ሠራተኛ ከማንኛውም ዕዳ ነፃ መሆኑ ሲረጋገጥና የሥራ ምስክር
ወረቀት እንዲሰጠው በጽሁፍ ሲጠይቅ የሚሰጠው የሥራ የምስክር ወረቀት በአማርኛና
በሰራተኛው ፍላጎት በእንግሊዝኛ ጭምር የሠራተኛውን ሙሉ ሥም ከነአያቱ፣ በድርጅቱ
የሰራባቸውን የሥራ አይነቶችና የሠራባቸውን ቦታዎች፣ የመጨረሻ ወር ደመወዙን፣
ሠራተኛው በድርጅቱ ውስጥ በሰራባቸው ጊዜያት የሥራ ግብርና ሌሎች መዋጮዎችን
መክፈሉን፣ የቅጥሩን ሁኔታና እንደአስፈላጊነቱ ሰራተኛው የሥራ ውሉ የተቋረጠበትን
ሁኔታ በመጥቀስ ይፃፍለታል፤ የድርጅቱ ማህተምም ይታተምበታል፡፡ ሰራተኛው በተለያየ
መ/ቤት የሰራበት ወይም በተለያየ የስራ መደብ ተቀጥሮ ወይም ተወክሎ ወይም ደርቦ
የሰራ እና ስለመስራቱ ከማህደሩ መኖሩ ሲረጋገጥ ይኸው ተገልፆ የስራ ልምዱ
ይሰጠዋል፡፡ ሆኖም ሠራተኛውን የሚጐዳ አስተያየት በስራ ልምድ ማስረጃ ላይ
አይገለጽም፡፡
23
ክፍል ሦስት
አንቀጽ አሥራ ሁለት (12) ስለ መደበኛ የሥራ ሰዓት
12.1 የማንኛውም ሠራተኛ መደበኛ የሥራ ሰዓት በቀን ከ8 ሰዓት በሣምንት ከ48 ሰዓት
መብለጥ የለበትም፤
12.2 የስራ መግቢያና መውጫ ሰዓት ከሰኞ እሰከ ሀሙስ
ከሰኞ እሰከ ሀሙስ ጧት ከ2:30-6:30
ከሰዓት ከ7:30-11:30 ይሆናል፡፡
አርብ ጧት ከ2:30-5:30
ከሰዓት ከ7:30-11:30
ቅዳሜ ጧት ከ2:30-6:30 ይሆናል፡፡
ከሰዓት ከ7:30-11:30 ብቻ ይሆናል፡፡
12.3 ከላይ በተ.ቁ 12.2 የተጠቀሰው ቢኖርም ከመስክ ስራና ከፕሮጀክት በስተቀር የድርጅቱ
ዋናው መ/ቤት እና የምዕራብ አማራ ቅ/ጽ/ቤት በሚገኝበት ባህርዳር ከተማ እንዲሁም
የምስራቅ አማራ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሚገኝበት ደሴ ከተማ ቅዳሜ ቀን መደበኛ የቢሮ
መግቢያና መውጫ ሰዓት ጧት ከ2:30-5:30 ይሆናል፡፡ ሆኖም ቅዳሜ ከሰዓት ከ7:30-
11:30 ሥራ ኖሮ ማንኛውንም የድርጅቱን ሠራተኛ ሥራ እንዲገባ ሲጠየቅ የመግባት
ግዴታ አለበት፡፡ በዚህም መሠረት የሰራተኛ የቅርብ ሀላፊ ሠራተኞችን በግል፣ በከፊልና
ሙሉ በሙሉ ሥራ ካለው እንዲገቡ ማድረግ ይችላል፡፡ የሚገቡ ሠራተኞችንም የቅርብ
ኃላፊው አስቀድሞ መንገር ይገባዋል፡፡
12.4 ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ በምንም ሁኔታ የትርፍ ሰዓት ክፍያ የማይጠየቅበት ነው፡፡
12.5 ለድርጅቱ ሥራ ሲባል በሳምንት የሚሰራበትን ጠቅላላ የሥራ ሰዓት መጠን ሳይጨምር
የመግቢያና የመውጫ ሰዓት ሊለወጥ ይችላል፡፡
12.6 በመስክ የሚሠሩ ወይም/ እና የፕሮጀክት ሠራተኞች የሥራ ቀናት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ
ሆኖ ከ48 ሰዓት ሳይበልጥ ቅዳሜ ሙሉ ቀን እንደመደበኛ የሥራ ሰዓት ተቆጥሮ እንዲሰሩ
ይደረጋል፡፡ የመግቢያና የመውጫ ሰዓት እንደስራው ባህሪና እንደ አካባቢው የአየር
ጠባይ ድርጅቱና ማህበሩ ተስማምተው በሚያወጡት የሥራ መግቢያና መውጫ መሠረት
ይሆናል፡፡
12.7 የጥበቃ ሠራተኞች የሚሰሩበት የሥራ ሰዓት በአማካይ በቀን 8፡00 ሰዓት በሳምንት
48፡00 ሰዓት የማይበልጥ ይሆናል፡፡
24
12.8 ድርጅቱ ለሰራተኞች የሻይ ዕረፍት የሚሆን ከመደበኛ የስራ ሰዓት የሚቆጠር በቀን 30
ደቂቃ ዕረፍት ይሰጣል፡፡ ይኸውም ጧት 4.15 እስከ 4.30 አስራ አምስት ደቂቃ ከስዓት
9.30-9.45 አስራ አምስት ደቂቃ ይሆናል፡፡
12.9 የተለየ የስራ ባህሪ ካላቸው የስራ መደቦች ላይ ተመድበው ከሚሰሩ ሰራተኞች በስተቀር
የድርጅቱ ሰራተኞች የሳምንት ዕረፍት ቀን እሁድ ይሆናል፡፡ የሣምንት የዕረፍት ጊዜ
ለድርጅቱ ሠራተኞች በሙሉ በአንድ ላይና በአንድ ጊዜ ይሰጣል፤ ይሁን እንጅ በሥራ
ፀባያቸው ምክንያት በፈረቃ ወይም በሽፍት የሚሠሩ ሠራተኞች የሥራ ሰዓት በአዋጅ
ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 64 መሠረት መደበኛ የሥራ ሰዓቶችን አማካይ በማድረግ
የሚደለደል ሲሆን የዕረፍት ጊዜያቸውም በሚወጣው የሥራ ፕሮግራም ድልድል መሠረት
ይሆናል፡፡
12.10 ወላድ ሴት ሰራተኞች የወለዱት ህፃን አንድ ዓመት እስኪሞላው ድረስ ጡት አጥብተው
ስራ ለመግባት እንዲችሉ የምሳ መውጫ ሰዓታቸው 6፡00 እና መግቢያ ሰዓታቸው 8፡00
ይሆናል፡፡ ይህ የሚሆነው ድርጅቱ የራሱን የህፃናት ማቆያ አገልግሎት እስኪያቋቁም
ድረስ ነው፡፡
25
15.1.3 ሰራተኛው የስራ ልምድ በሚጠይቅ የስራ መደብ ላይ ሲቀጠር በቅጥር ወቅት/ ጊዜ
ያስያዘው በሌላ መ/ቤት የሰጠው አገልግሎት ወይም የስራ ልምድ ካለ እስከ 10 (አስር)
ዓመት ድረስ ብቻ ለእያንዳንዱ ሁለት የአገልግሎት ዓመታት አንድ የስራ ቀን
እየተጨመረ ይያዝለታል፡፡ ሆኖም የስራ ልምድ በማይጠይቅ (ዜሮ ዓመት) የስራ
መደብ ላይ የተቀጠረ ከሆነ የስራ ልምዱ ለዓመት ፈቃድ አሰላል ጥቅም ላይ
አይውልም፡፡
15.1.4 በደርጅቱ ከአንድ ዓመት በላይ ላገለገለ ሠራተኛ በተራ ቁጥር 15.1.1 እና 15.1.3
የተመለከተው እንዳለ ሆኖ በድርጅቱ ለሰራበት ለእያንዳንዱ ሁለት የአገልግሎት
ዓመታት አንድ የስራ ቀን እየተጨመረ ያገኛል፡፡ የ2011 እና የ2012 በጀት ዓመት
ፈቃድ በነበረው አግባብ የሚሰላ ሆኖ የ2013 በጀት ዓመት በዚህ ህብረት ስምምነት
መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
15.1.5 ሰራተኛው ከሌላ መ/ቤት ያልተጠቀመበት የአመት ፈቃድ ቢኖርው ደርጀቱ
ስላልተጠቀመበት ፈቃድ አይመለከተውም፡፡
15.1.6 በእረፍት ላይ ያለ ሠራተኛ ከዕረፍቱ ላይ ለሥራ ሲጠራ በሠራተኛው ምርጫ በገንዘብ
ሊተካለት ወይም ሊተላለፍለት ይችላል፡፡ ይህም ሲሆን የነበረበት ሥፍራ ከመደበኛ
የሥራ ቦታው ውጭ ከሆነ ወደ መደበኛ የሥራ ቦታው ሲመለስ እንዲሁም እረፍቱን
እንደገና እንዲቀጥል ሲደረግ በድርጅቱ መመሪያ መሠረት የትራንስፖርት ወጪና የጉዞ
ቀናት የውሎ አበል ይከፈለዋል፡፡ ይሁን እንጂ የተቋረጠ እረፍቱ ለመቀጠል ካልፈለገ
እረፍቱ ለሌላ ጊዜ ሊተላለፍ ይችላል፡
15.1.7 የድርጅቱንና የሠራተኛውን ጥቅሞች በማስማማት የዓመት እረፍት ከዓመቱ ውስጥ
በድርጅቱ ፈቃድ በአንድ ላይ ወይም በሁለት ጊዜ ከፋፍሎ ምቹ በሆነ ወራት
ይወሰዳል፡፡ ድርጅቱ ከሠራተኛው ጋር በመመካከር የዓመት ፈቃዳቸውን መቼ
እንደሚወስዱ የሚያሳይ ሠንጠረዥ ያዘጋጃል፡፡ ሆኖም የድርጅቱና የሠራተኛው የጥቅም
ግጭት ከተፈጠረ የድርጅቱ ጥቅም ቅድሚያ ይኖረዋል፡፡ ሰራተኛው ባለመጠየቁ
ምክንያት በእቅዱ መሰረት እረፍት ካልወሰደ ድርጅቱ በፈለገው ጊዜ ሰራተኛው
እረፍቱን እንዲወስድ ያደርጋል፡፡
15.1.8 አንድን ሰራተኛ በሥራው ባህሪ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የሚሰራው ስራ ከሌለው
ድርጅቱ አስቀድሞ የ5 (አምስት) ቀናት ማስጠንቀቂያ በመስጠት የዓመት ፈቃድ
መስጠት ይችላል፡፡
26
15.1.9 የዓመት ፈቃድ አቆጣጠር የሕዝብ በዓላትን እና የሳምንት የእረፍት ቀንን ማለትም
ቅዳሜ ከሰዓት በኋላና እሁድን አይጨምርም፡፡
15.1.10 የዓመት ፈቃድ የተሰጠው ሠራተኛ በደመወዝ ክፍያ ወቅት የአመት ፈቃድ ላይ
በመሆኑ የቅድሚያ ደመወዝ ክፍያ የሚጠይቅ ከሆነ ደመወዙንም ጭምር ከፈቃዱ ጋር
መውሰድ ይችላል፡፡
15.1.11 ሰራተኛው ከድርጅቱ ምንም ዓይነት ሀላፊነት/ ተጠያቂነት ሳይኖርበት በህጋዊ መንገድ
ስራ ሲለቅ ወይም ሲሰናበት ያልተጠቀመበት ህጋዊ ቀሪ የዓመት ዕረፍት ቀናት ካለው
በህጉ መሰረት በገንዘብ ተቀይሮ ይሰጠዋል፡፡
15.1.12 በመደበኛ /በቀን/ በክረምት ፕሮግራም ስራ ትተው እንዲማሩ የተፈቀደላቸው
ሰራተኞች በትምህርት ቆይታ ላይ እያሉ ወይም ለትምህርት ቆይታ ጊዜው የዓመት
ዕርፍት ፈቃድ አይታሰብላቸውም፡፡
15.1.13 በየበጀት ዓመቱ በድርጅቱ የሥራ ባህሪ ምክንያት በክረምት/ በአየር ፀባይ ችግር
ምክንያት ፕሮጀክት ሲዘጋ የፕሮጀክት ሰራተኞች (የተሽከርካሪ ኦፕሬተሮችን ጨምሮ)
በዋናው መ/ቤት ወይም ሌላ በክረምት ወቅት ባልተዘጋ ፕሮጀክት ላይ ለሥራ
እስካልተፈለጉ ድረስ ያልተጠቀሙበትን የዓመት ፈቃድ ቀናት እንዲወስዱ
ይደረጋል፡፡
28
15.3 የአስታማሚ ፈቃድ
በድርጅቱ የምትሰራ ወይም የሚሰራ ሰራተኛ ህጋዊ ባል፣ ሚስት፣ ልጅ፣ እናት እና አባት
ለሆኑት በህጋዊ ህክምና ተቋም ተኝተው ለሚታከሙና ይህንን የሚገልጽ ማስረጃ ካቀረቡ 2
(ሁለት) ቀን የአስታማሚ ፈቃድ ይሰጣል፡፡ በተጨማሪም ተኝቶ የሚታከመው የሴት ሰራተኛዋ
ከአንድ ዓመት በታች የሆነ ህፃን ከሆነ ለሰራተኛዋ በምታቀርበው ህጋዊ የሀኪም ማስረጃ
መሰረት የ5 (አምስት) ተከታታይ ቀናት ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
30
15.6 የትምህርት ፈቃድ
15.6.1 ሠራተኛው በትርፍ ጊዜው በሚከታተለው ትምህርት ፈተና የሚሰጠው በሥራ ሰዓት
ከሆነ ሠራተኛው በሚያቀርበው ማስረጃ መሠረት ድርጅቱ ከደመወዝ ጋር ፈቃድ
ይሰጠዋል፤
15.6.2 ድርጅቱ ፕሮግራም ይዞ ከሚያሰተምረው ውጭ እየተማረ ያለ ሰራተኛ ከተገኘ
የድርጅቱን የስራ ስዓት በድሎ ከሆነ ለዲስፕሊን ቀርቦ እንዲወሰንበት ይደረጋል፡፡
15.6.3 በድርጅቱ ተፈቅዶ በማታው ክፍለ ጊዜ የዲግሪ ትምህርቱን የሚከታተል ሰራተኛ
ኮርሱን ለማጠናቀቅ በሚቀረው የ1 (አንድ) ዓመት የመጨረሻ ትምህርት ኮርሱ
የሚሰጠው በቀን መሆኑ በተቋሙ ሲረጋገጥ ኮርሱ ለሚፈጀው ጊዜ ሙሉ ቀን ፈቃድ
ከሙሉ ደመወዝ ጋር ይሰጠዋል፡፡
15.9 ልዩ ፈቃድ
ማንኛውም የዓመት ፈቃዱን የጨረሰ ሠራተኛ ልዩና አሳሳቢ ሁኔታ ሲያጋጥመውና ለዚህም
ማስረጃ ማቅረብ ከቻለ ደመወዝ የሚከፈልበት በተከታታይ ከሁለት ቀን ያልበለጠ በዓመት
ውስጥ በአጠቃላይ ከሦስት ቀናት ያልበለጠ ልዩ ፈቃድ ድርጅቱ ሲያምንበት ይሰጠዋል፡፡
31
አንቀጽ አስራ ስድስት (16) ደመወዝና የደመወዝ ብድር
16.1 የደመወዝ ክፍያ ቀን በኢትዮጵያ የቀን አቆጣጠር በወሩ መጨረሻ ከ25ኛው አስከ 28ኛው
ቀን ይከፈላል፡፡ ሆኖም የሕዝብ በዓላት ሲኖሩ ድርጅቱ በዓሉ የሚውልበትን ቀን መሰረት
አድርጎ በቅድሚያ ሊከፍል ይችላል፡፡
16.2 የድርጅቱ አቅም አስከፈቀደ ድረስ በድርጅቱ ውስጥ ከተቀጠረ ጀምሮ አንድ ዓመት
ያገለገለ ሰራተኛ ያልተጣራ የ3 ወር ደመወዙን በሁለት ዓመት ተከፍሎ የሚያልቅ
ከወለድ ነፃ በሆነ መንገድ ሊበደር ይችላል፡፡ ለዚህም በቂ ዋስ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡
16.3 ሠራተኛው የወሰደውን የደመወዝ ብድሩን ለድርጅቱ በየወሩ ከደመወዙ ላይ 1/3
እየተቆረጠ ገቢ ይደረጋል፡፡ የሠራተኛው የሥራ ውል የተቋረጠ ከሆነ ያለበትን ቀሪ ዕዳ
ከሚከፈለው ማንኛውም ገንዘብ ላይ ሙሉ ለሙሉ ቆርጦ ያስቀራል፡፡
16.4 በድርጅቱ በሚሰጡ የብድር አገልግሎቶች በሚቋቋም ኮሚቴ ውስጥ የሰራተኛ ማህበር
ተወካይ በኮሚቴ አባልነት እንዲኖር ይደረጋል፡፡
32
አንቀጽ አስራ ስምንት (18) የደመወዝ እርከን ጭማሪ እና የቦነስ
አሰጣጥ
18.1. የደመወዝ እርከን ጭማሪ እና የቦነስ አሰጣጥ
18.2.1 ድርጅቱ በአንድ የበጀት ዓመት ጊዜ ውስጥ ከስራ ጋር በተያያዘ ከሚያገኘው
ያልተጣራ ትርፍ ላይ የትርፍ ገቢ ግብር ተቀንሶ ከሚገኘው የተጣራ ትርፍ ላይ ሕጋዊ
መጠባበቂያ 5% በመቀነስ ለሠራተኞች የደመወዝ እርከን ጭማሪ ወይም የደመወዝ
እርከን ጭማሪ እና ቦነሰ ይሰጣል፡፡ አፈፃፀሙም ከታች ከአንቀጽ 18.2.2-18.2.17
በተጠቀሰው መሰረት ይሆናል፡፡
18.2.2 በአንቀጽ 18.2.1 መሠረት የሚሰጠው የደመወዝ ጭማሪ ወይም ቦነስ ወይም የደመወዝ
ጭማሪና ቦነስ አፈፃፀም እንደሚከተለው ይሆናል፡፡
18.2.3 ለሰራተኛው የሚሰጠው ቦነስም የስራ አፈፃፀም ምዘና ውጤትን መሠረት አድርጎ
እንደሚከተለው ይሆናል፡፡
ከ86ና በላይ A 100%
ከ81-85 B+ 95%
ከ75-80 B 90%
ከ65-74 C+ 85%
ከ50-64 C 80%
18.2.4 ሙሉ የበጀት ዓመቱን ለድርጅቱ ትርፋማነት አስተዋጽኦ ያበረከቱ ሰራተኞች በስራ
አፈጻጸማቸው ቀመር መሰረት ቦነስ ያገኛሉ፡፡ በተጨማሪም የሙከራ ጊዜያቸውን
የጨረሱ ሆነው ለበጀት ዓመቱ ለተመዘገበው ትርፍ አስተዋፅኦ ያበረከቱ ሰራተኞች
በአገልግሎት ጊዜ ልክ እየተሰላ ቦነስ ይከፈላቸዋል፡፡
33
18.2.5 በበጀት ዓመቱ 9 (ዘጠኝ) ወር እና ከዚያ በላይ ያገለገለ ሰራተኛ የደመወዝ እርከን
ጭማሪ ያገኛል፡፡ የደመወዝ እርከን ጭማሪ ተግባራዊ የሚሆነው ትርፍ በተገኘበት
በጀት ዓመት መጨረሻ ወር ቀጥሎ ባለው በአዲሱ በጀት ዓመት የመጀመሪያ ወር
ሀምሌ 1 ቀን ጀምሮ ይሆናል፡፡
18.2.6 በሞት ወይም በጡረታ ምክንያት የስራ ውሉ የተቋረጠ ሠራተኛ የበጀት አመቱ ሙሉ
ቦነስ እና ስራ ላይ ለቆየበት ጊዜ የደመወዝ እርከን ጭማሪ ይከፈለዋል፡፡
18.2.7 በበጀት አመቱ ለረጅም ጊዜ በሕመም ፈቃድ ላይ ያሳለፋ ካሉ ጉዳዩ ከአቅም በላይ
በሆነ ምክንያት የተፈጠረ መሆኑን በማየት የስራ ውላቸው ለተቋረጠ ቦነስና የስራ
ውላቸው እስከተቋረጠበት ጊዜ ድረስ ብቻ የደመወዝ ዕርከን ጭማሪ እንዲሁም በሥራ
ላይ ያሉ ካሉ ደግሞ የተፈቀደውን ቦነስም ሆነ የደመወዝ ዕርከን ጭማሪ ያገኛሉ፡፡
18.2.8 በራሳቸው ጥያቄ/ ፈቃድ ከድርጅቱ የተሰናበቱ ወይም የስራ ውላቸው የተቋረጠ
ሠራተኞች ስድስት ወርና ከዚያ በላይ ያገለገሉ ከሆነ ለሰሩበት ጊዜ ተሰልቶ ቦነስ
ይከፈላቸዋል፡፡ ነገር ግን የእርከን ጭማሪ አያገኙም፡፡ ሆኖም በዲስፕሊን ጉድለት
የተሰናበቱ ሠራተኞች አይከፈላቸውም፡፡ ይህ ተፈጻሚ የሚሆነው ክፍያው እንዲከፈል
በተወሰነ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ጥያቄው ከቀረበ ብቻ ነው፡፡
18.2.9 እርከን በተገኘበት በጀት ዓመት በደረጃ ዕድገትም ይሁን በምደባ የ1 (አንድ)
ደመወዝ ደረጃ ከፍታ ወይም የ3 (ሶስት) እርከን እና በላይ ዕድገት ወይም የደመወዝ
ጭማሪ ያገኙና በበጀት ዓመቱ ቢያንስ 6 (ስድስት) ወር ያላገለገሉ ሰራተኞች
የደመወዝ እርከን ጭማሪ አይከፈላቸውም/ አያገኙም፡፡
18.2.10 ቦነሱ የሚመሰረተው ሰራተኛው በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ሰኔ ወር ላይ በተከፈለው
ደመወዝ ላይ ይሆናል፡፡
18.2.11 የድርጅቱ ትርፍና ኪሳራ የሚመሰረተው የድርጅቱ የበጀት ዓመት ሂሳብ በውጪ
ኦዲተሮች ተመርምሮ መግለጫ ከተሰጠበት በኋላ ነው፡፡
18.2.12 ድርጅቱ የበጀት ዓመቱን ሂሳብ ዘግቶ በውጪ ኦዲተሮች አስመርምሮ ትርፍና
ኪሳራውን ማወቅ ያለበት ከሐምሌ አንድ ቀን ጀምሮ ባለው ሶስት (3) ወር ጊዜ
ውስጥ ይሆናል፡፡
18.2.13 ትርፍ በተመዘገበበት ወይም ቦነስ በሚከፈልበት በጀት ዓመት በመደበኛ ትምህርት
ላይ ላለ ሰራተኛ ቦነስም ሆነ የደመወዝ እርክን ጭማሪ አይከፈለውም፡፡
34
18.2.14 ትርፍ በተመዘገበበት ወይም ቦነስ በሚከፈልበት በጀት አመቱ ከ1-5 ቀናት ደመወዝ
የተቀጡ ሰራተኞች የተፈቀደውን ቦነስ መጠን 75% እና የተፈቀደውን የደመወዝ
ዕርከን ጭማሪ ያገኛሉ፡፡
18.2.15 ትርፍ በተመዘገበበት ወይም ቦነስ በሚከፈልበት በጀት አመቱ ከ6-30 ቀናት ደመወዝ
የተቀጡ ሰራተኞች የተፈቀደውን ቦነስ መጠን 50% እና የተፈቀደውን የደመወዝ
ዕርከን ጭማሪ ያገኛሉ፡፡
18.2.16 ትርፍ በተመዘገበበት ወይም ቦነስ በሚከፈልበት በጀት አመቱ ከ30 ቀናት በላይ
ደመወዝ የተቀጡና ከዚያ በላይ የዲስፕሊን እርምጃ የተወሰደባቸው ግን የተፈቀደውን
ቦነስም ሆነ የደመወዝ ዕርከን ጭማሪ ሙሉ ለሙሉ አያገኙም፡፡
18.2.17 ከላይ በተጠቀሰው አግባብ የእርከን ጭማሪም ሆነ ቦነስ የሚሰጠው የድርጅቱ የተጣራ
ትርፍ ቢያንስ ዓመታዊ የእርከንና የቦነስ ጭማሪ ወጭውን ሊሸፍን ከቻለ ብቻ ነው፡፡
18.2.18 መንግስት የኑሮውን ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ለመንግስት ሠራተኞች የደሞዝ ጭማሪ
ካደረገ መስሪያ ቤቱ ይህንኑ የኑሮ ሁኔታ በማየት አቅም ባገናዘበ ሁኔታ የደሞዝ
ጭማሪ ያደርጋል፡፡ ሆኖም ጥያቄው ለቦርድ ቀርቦ ሲፀድቅ ተግባራዊ ይደረጋል፡፡
35
ካልተመለሰ የምሳ አበል ይከፈለዋል፡፡ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት በኋላ ወደ ተመደበበት
ከተማ ክልል ከተመለሰ የእራት አበል ይከፈለዋል፡፡
ለ/ ማንኛውም ሠራተኛ ከተመደበበት ከተማ ክልል ውጭ የአየር ጠባይ አበል ወደ
ሚከፈልበት ቦታ ለሥራ ከተላከ በክልሉ ለሚኖረው ቆይታ ለቦታው የተመደበው
የአየር ጠባይ አበል በመደበኛ የውሎ አበል ላይ ተደምሮ ይከፈለዋል፡፡
36
19.5 የካዝና መጠበቂያ
ለገንዘብ ያዥዎች የሚከፈል የገንዘብ መጠባበቂያ አበል (Cash Indemnity Allowance) ገንዘብ
ያዦች በምንዛሪና በአሰጣጥ ስህተት ገንዘብ ሊጎልባቸው ስለሚችል በዚሁ ምክንያት ለገንዘብ
መጠባበቂያ ይረዳን ዘንድ ድርጅቱ በየወሩ የሚከፍለው ሲሆን የክፍያ አፈፃፀሙም ከዚህ በታች
በተመለከተው መሠረት ይሆናል፡፡
19.5.1 ድርጅቱ በዋና መስሪያ ቤትና በጽ/ቤቶች ለሚገኙ ዋና ገንዘብ ያዦች በየወሩ ብር 250
(ሁለት መቶ ብር) እንዲሁም ለረዳት ገንዘብ ያዦችና ለዕለት ገንዘብ ተቀባዮች በየወሩ
ብር 150 (አንድ መቶ ሀምሳ ብር) ወርሃዊ የገንዘብ መጠባበቂያ አበል ለአሥራ ሁለት
ወራት በሠራተኛው ስም በመጠባበቂያ ገንዘብ (Fund) መልክ ያጠራቀማል፡፡ ከዚህ
በኋላ ግን የመጠባበቂያ ገንዘብ ክፍያው በየወሩ ለገንዘብ ያዥ ይከፈላል፡፡
19.5.2 ገንዘብ ያዥ የተረጋገጠ የገንዘብ ጉድለት ሲገኝበት ድርጅቱ በስሙ ከተያዘው
ከተጠራቀመው መጠባበቂያ ገንዘብ ተቀናሽ በማድረግ ጉድለቱን ወዲያውኑ አሟልቶ
ከመጠባበቂያ ገንዘብ ላይ የተቀነሰውን ሂሣብ ከገንዘብ ያዥ ወርሃዊ መጠባበቂያ ክፍያ
ተቀናሽ በማድረግ ይሞላል፡፡ ይሁን እንጂ ያጎደለው ገንዘብ ከማካካሻ ገንዘብ በላይ
ከሆነ የጉድለቱን ልዩነት በሚሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሠራተኛው አሟልቶ እንዲከፍል
ይደረጋል፡፡
19.5.3 ገንዘብ ያዥ ከድርጅቱ ሲሰናበት ወይም ከገንዘብ ያዥነት የሥራ መደብ ወደ ሌላ
የሥራ መደብ ሲዛወር ከእዳ ነጻ መሆኑ ተረጋግጦ በስሙ/ሟ የተጠራቀመው ገንዘብ
በአንድ ጊዜ ይከፈለዋል፡፡
19.5.4 በህመም ወይም በዓመት ዕረፍት ምክንያት ገንዘብ ያዥ በምድብ ሥራ ላይ ከ15
ቀናት በላይ በማይኖርበት ጊዜ እና በሌላ ሲተካ የወሩ የመጠባበቂያ ክፍያ ለተተኪው
ይከፈላል፡፡
19.5.5 በየፕሮጀክቶቹ የሚመደቡ ገንዘብ ያዦች የመጠባበቂያ ክፍያ ከላይ ከአንቀጽ 19.5.1
እስከ 19.5.4 መሠረት ይሆናል፡፡
37
19.7 የወተት አበል
ላቦራቶሪ ማዕከል የሚሰሩ ላብ ቴክኒሻኖች፣ ሶይል ኬሚስቶች፣ ሶይል ሚካኒክስ የስራ መደብ ላይ
ተመድበው የሚሰሩ ባለሙያዎች፣ ማቴሪያል መሀንዲሶች (ዳታ አናሊስት ሆነው የሚሰሩትንና
ሀላፊዎችን አያካትትም)፣ ንብረት ኦፊሰር (ዕቃ ግምጃ ቤት ሰራተኛ)፣ መዝገብ ቤት ሰራተኛ፣
ፎቶ ኮፒና ማባዣ፤ በያጆች፤ ብሉ ፕሪነት ሰራተኞች፤ የአካል ቅጥቀጣ ባለሙያ (ቦዲማን)፣
ባትሪ አሲድ የሚሞሉ ሰራተኞች፣ ላይበራሪያን፣ የሂሳብ ሰነድ ያዥ፤ ቆፋሪ/ ድሪለር በሰው ሀብት
አስተዳደር ስር ያሉ መዛግብት ወይም የግል ማህደር ያዥ ሰራተኞች፣ ስራ ላይ ባይሆኑም
ሳይቆራረጥ በቀን አንድ ሊትር ወተት ይሰጠዋል፡፡ ነገር ግን በተለያየ ምክንያት አንድ ወር
ሙሉ ከስራ ገበታው ላይ ከሌለ አይሰጥም/ አይከፈልም፡፡
38
እንዲሁም የመነፀር ሌንስ እንዲቀየር በሀኪም ሲታዘዝ ሙሉ ወጭውን በመሸፈን
ይቀይራል፡፡
20.1.5 የጥርስ ማስሞላት ሕክምና ለሠራተኛው እንዲደረግ ሐኪም ሲያዝዝ የጥርስ ማስሞላቱ
ሂደት በማንኛውም የመንግስትም ሆነ የግል የጤና ተቋማት ሲከናወን ወጪውን 50
(ሀምሳ) በመቶ ድርጅቱ ይሸፍናል፡፡ ሆኖም ግን የስራ ላይ ጉዳት ካልሆነ በስተቀር ሰው
ሰራሽ ጥርስ ማስተከልን አይጨምርም፡፡
20.1.6 የጀሮ ማዳመጫ ሠራተኛው እንዲያደርግ ሐኪም ሲያዝዝ ከብር 5000 (አምስት ሺ ብር)
ያልበለጠ ለአንድ ጊዜ ብቻ ድርጅቱ ይሸፍናል፡፡
20.1.7 ሰራተኛው ሕመሙ በሆስፒታል የሚያስተኛው መሆኑ በሐኪም ከተረጋገጠ በመንግስት
ሆስፒታልም ሆነ የግል የሕክምና ተቋማት ተኝቶ ሊታከም ይችላል፡፡ የወጭ
አሸፋፈኑም በአንቀጽ 20.1.2 እና 20.1.3 መሰረት ይሆናል፡፡
20.1.8 መስክ የሚገኙ ሠራተኞች በአቅራቢያቸው በሚገኙ በመንግሥት ወይም በመንግሥት
እውቅና ባገኙ ማናቸውም የሕክምና ተቋማት መታከም ይችላሉ፡፡ ወጪዉም በአንቀጽ
20.1.2 መሰረት ይሸፈናል፡፡
20.1.9 በመንግስት የሕክምና ተቋማት ወይም ሕጋዊ በሆነ የግል የህክምና ተቋም ትዕዛዝ
(Referal) መሠረት ሠራተኛው ከሚሠራበት የሥራ ቦታ ወደ አዲስ አበባ ወይም ሌላ
ቦታ ሂዶ/ዳ እንዲታከም/ እንድትታከም ቢደረግ ይኸው ማስረጃ ታይቶ ከውሎ አበል
በስተቀር የመጓጓዣውንና የህክምና ወጪውን ድርጅቱ ይከፍላል፡፡ ሆኖም በልዩ ሁኔታ
በድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ካልተፈቀደ ወይም በሀኪም ትዕዛዝ ካልሆነ በስተቀር
የመጓጓዣ ወጭው የሚሸፈነው በየብስ ትራንስፖርት ሆኖ ከህጋዊ የትራንስፖርት
ተቋም ህጋዊ የትራንስፖርት ደረሰኝ ሲቀርብ ብቻ ነው፡፡
20.1.10 በሰራተኛው ላይ የደረሰው ህመም ለሂወት አስጊ መሆኑ በሀኪም ሲረጋገጥና በየብስ
ትራንስፖርት ማጓጓዝ የማይቻል መሆኑ በሀኪም ሲረጋገጥ ድርጅቱ የሰራተኛውን
ሂወት ለማትረፍ ሲባል በሀገር ውስጥ የአየር ትራንስፖርት ወጭውን ይሸፍናል፡፡
20.1.11 ድርጅቱ ሠራተኞችን ለሥራ የሚያሰማራበት ቦታ ቢጫ ወባ ክትባት የሚስፈልግ ሆኖ
ካገኘው የቢጫ ወባ ክትባት ወጭውን ችሎ ያስከትባል፡፡
20.1.12 በስራ ላይ እያለ አደጋ የደረሰበት ሠራተኛ በድርጅቱ መኪና ወደ ህክምና ተቋም
ይወሰዳል፡፡
20.1.13 ከላይ የተጠቀሱት የህክምና ወጭዎጭች የሚሸፈነው ለሀገር ውስጥ ህክምና ብቻ ነው፡፡
የውጭ ሀገር ህክመና አያካትትም፡፡
39
20.1.14 ለእኩላሊት እጥበት (ዲያሊስስ) ድርጅቱ እስከ ብር 20,000.00 (ሃያ ሽህ) ብቻ ወጭ
ይሸፍናል፡፡ ከተጠቀሰው የገንዘብ መጠን በላይ ግን ድርጅቱ ሊሸፍን አይችልም፣
20.1.15 ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ህክምናዎች የህክምና ወጭ በድርጅቱ አይሸፈኑም፡-
ሀ) የኩላሊት እጥበት (ዲያሊስስ) ከተፈቀደው የገንዘብ በላይ፣
ለ) ሰው ስራሽ (አርቴፊሻል) ቀዶ ጥገና ወይም ንቅለተከላ፣ ከስራው ጋር ግንኙነት
ከሌለውና በስራ ላይ እያለ ጉዳት ካልደረሰበት፣
ሐ) ከሰው ጋር በመደባደብ የሚከሰት ጉዳት፣
መ) በመጠጥ፣ በአደንዛዥ ዕጽ… ወዘተ ምክንያት በሚደርሱ በሽታዎች/ አደጋ፤
ሠ) የአባላዘር በሽታዎች፣
ረ) ሰው ሰራሽ ጥርስ ማስተከልን ወይም ማስተካከል፣ ጉዳቱ የደረሰው ከስራው ጋር
ግንኙነት የሌለው ከሆነ፣
ሰ) ሴት ሠራተኛ በራሷ ፈቃድ ሆን ብላ በምታደርገው ውርጃ ለሚመጣ ሕመም፣
20.3 ጡረታ
20.3.1 ማንኛውም የድርጅቱ ላልተወሰነ ጊዜ (ቋሚ)/ የተወሰነ ጊዜ/ሥራ (ኮንትራት) ሠራተኛ
በመንግሥት የጡረታ አዋጅ መሰረት የሚተዳደር ይሆናል፡፡
20.3.2 በመንግሥት ሠራተኞች የጡረታ አዋጅ ቁጥር 714/2003 አንቀጽ 59 1 ’’ሀ’’ ና ’’ለ’’
መሠረት ይሆናል፡፡
20.3.3 ሠራተኛው በጡረታ ከመገለሉ በፊት ሊሰጠው የሚገባና ያልተሰጠው ማንኛውም
ጥቅማጥቅም ተጠናቆ እንዲሰጠው ይደረጋል፡፡
20.3.4 ሠራተኛው በጡረታ የመገለያ ጊዜው ከመድረሱ አስቀድሞ ድርጅቱ ቢያንስ ከአንድ
ዓመት በፊት ማሳሰቢያ ይሰጠዋል፡፡
41
21.1.3 አንድ የድርጅቱ ሠራተኛ በሞት ከዚህ ዓለም በሚለይበት ወቅት ድርጅቱ ለሐዘንና
ለቀብር ሥነ-ሥርዓት ማስፈፀሚያ እንዲረዳ ብር5,000.00 (አምስት ሺህ ብር)
በማሕበሩ አማካኝነት ለቤተሰብ ይሰጣል፡፡ ድርጅቱ በቀብሩም ሥነ-ሥርዓት ላይ
ተገኝቶ የአበባ ጉንጉን ያኖራል፡፡
21.1.4 ከመደበኛ የመኖሪያ ሥፍራ ውጭ ለሥራ ጉዳይ ወደ ሌላ ቦታ የተላከ ሠራተኛ ቢሞት
ድርጅቱ በራሱ መጓጓዣ ወይም የትራንስፖርት ወጪውን በመቻል ወደ መደበኛ
የመኖሪያ ሥፍራ ወይም ቤተሰቡ በሚፈልገው ቦታ ድረስ አስክሬኑን ያጓጉዛል፡፡
21.1.5 በሃዘን ጊዜ የድርጅቱ ስራተኛ/ ቤተሰብ ከዚህ አለም በሞት ሲለዩ ባህርዳር/ ደሴ ከተማ
ከሆነ ለሬሳ መውሰጃ የሚሆን አንድ ፒካፕ እና ለቀብር ስነ ስርዓት ማስፈፀሚያ
ለሰራተኛው የሚሆን አንደ ባስ ይፈቀዳል፡፡
42
22.4 አዲስ አበባ ከተማ ለስልጠና ሳይሆን መኪና ሳይዙ ለመስክ ስራ ለሚላኩ ሰራተኞች አዲስ
አበባ ከተማ ለቆዩበት ቀናት ብቻ ታስቦ በቀን ብር 50.00 (ሀምሳ ብር) የታክሲ/
የትራንስፖርት ክፍያ ይከፈላቸዋል፡፡
43
ክፍል አራት
አንቀጽ ሃያ አራት (24) የዲስፕሊን የእርምጃ አወሳሰድ ሥነ-ሥርዓት
24.1 በአንድ ሠራተኛ ላይ የዲሲኘሊን እርምጃ የሚወሰደው ሠራተኛውን ከጥፋቱ በማረም
ሥራው እንዳይበደል ለመቆጣጠርና ሌሎች ሠራተኞች ከተመሳሳይ ጥፋቶቸ እንዲቆጠቡ
ለማድረግ ስለሆነ የዲሲኘሊን እርምጃ ከመወሰዱ በፊት የጥፋቱ ክብደት፣ ሠራተኛው
ከጥፋቱ በፊት የነበረው ፀባይ፣ ያለው መልካም አገልግሎትና ለጥፋቱ መንስዔ የሆኑበት
ተጨባጭ ሁኔታዎች በጥንቃቄ መመርመር አለባቸው፡፡
24.2 ማንኛውም ሠራተኛ በሥራ ላይ እንዳለ የሚያደርሰው ጥፋት በማስረጃ የተረጋገጠና
ጥፋቱም የዲሲኘሊን እርምጃ የሚያስወስድ ሆኖ ከተገኘ የሚወሰድበት ቅጣት በአዋጁና
በህብረት ስምምነቱ ያለማስጠንቀቂያና በማስጠንቀቂያ ከሥራ ከሚያሰናብቱ ጥፋቶች
በስተቀር በአንድ ሠራተኛ ላይ ዲሲፕሊን እርምጃ ሲወሰድ የሚወሰደው ቅጣት በዚህ
ህብረት ስምምነት ስለጥፋትና ቅጣት ዓይነቶች በሚያመለክተው ሠንጠረዥ መሠረት
ይሆናል፡፡ ሠራተኛው ሲቀጣ የተወሰደበት እርምጃ በወቅቱ በጽሁፍ እንዲደርሰው
ይደረጋል፡፡ በግልባጭም ሠራተኛ ማህበሩ እንዲያውቀው ይደረጋል፡፡
24.3 በድርጅቱና በማኀበሩ የሚወከሉ እኩል አባሎች (ሰብሳቢውን ሳይጨምር) የሚገኙበት
የዲስፕሊን ኮሚቴ በድርጅቱ ዋና መ/ቤት ወይም በሥሩ ባሉ ጽ/ቤቶች ይቋቋማል፡፡
ሰብሳቢው በድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወይም ጽ/ቤት ኃላፊ ይወከላል፤
24.4 ማንኛውም የዲሲፕሊን ጉዳዩች ከአንቀጽ 24.6 በስተቀር በድርጅቱ ወይም በጽህፈት ቤቱ
በተቋቋመው የዲስፕሊን ኮሚቴ አማካኝነት ይታያሉ፡፡ ሆኖም እንደአስፈላጊነቱ
በየደረጃው ማስጠንቀቂያ እየተሰጠ ከሥራ ላይ በመቅረት ምክንያት የሚወሰድ የዲስፕሊን
እርምጃ ከደመወዝ ቅጣት እስከ ሥራ ውል ማቋረጥ (ስንብት) ድረስ ያለው በሰው ሀብት
አስተዳደር ኦፊሰሮች በኩል አስተያየት እየቀረበ በሰው ሀብት አስተዳደር ቡድን መሪ
የሚወሰን ይሆናል፡፡
24.5 ድርጅቱ አንዳንድ መጣራት ያለባቸውን ጉዳዮች በሚመለከት በሰው ሀብት ስራ አመራር
የስራ ሂደት/ ቡድን በኩል ተጣርቶ ለድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ/ ሀላፊ ይቀርባል፡፡
ሠራተኞች ጥፋት መፈፀማቸው ለሰው ሀብት ስራ አመራር ደጋፊ የስራ ሂደት/ ቡድን በጽሁፍ
ሲደርሰው ለዲስኘሊን ኮሚቴ ክስ ይመሰርታል፡፡ የዲስፕሊን ኮሚቴ ያጣራቸውን ጉዳዮች
44
በሙሉ በከፊል ሊቀበለው ወይም ሊሽረው ይችላል፡፡ በመጨረሻም የራሱን ውሳኔ
ያስቀምጣል፡፡
24.6 የሰራተኛው የቅርብ ሀላፊ ወይም ከቅርብ ሀላፊ በላይ ያለ ሀላፊ እስከ ጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
ድረስ ያሉትን የዲስፕሊን እርምጃዎች ለዲስፕሊን ኮሚቴ ማቅረብ ሳያስፈልግ በራሱ
ቀጥታ ሊወስድ ይችላል፡፡
24.7 አንድ ሠራተኛ ያለማስጠንቀቂያ ከሥራ የሚያሰናብት ጥፋት ሲፈፅም አስፈላጊ ሆኖ
ከተገኘ ቅድሚያ እንዲጣራ ይደረጋል፡፡ ሆኖም የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ሥራ
ላይ በመቆየቱ መረጃዎችን የማጥፋት ወይም በድርጅቱ ሥራና ህልውና አደጋ ያደርሳል
ተብሎ ከታመነ ጉዳዩ ተጣርቶ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በዋናው ሥራ አስፈፃሚ ሊታገድ
ይችላል፡፡ ሠራተኛው ከተጠረጠረበት ጥፋት ነፃ ሆኖ ከተገኘ ከሥራ ለታገደበት ጊዜ
ሙሉ ደመወዝ ይከፈለዋል፡፡
24.8 ለውሣኔ መዘግየት ሠራተኛው እራሱ ምክንያት ካልሆነ በስተቀር ከ30 (ሰላሳ) ቀናት በላይ
ከሥራ አግዶ ማቆየት አይቻልም፤ በዚህ የጊዜ ገደብ ውስጥ ውሣኔ ካላገኘ ደመወዝ
እየተከፈለው ውሣኔውን ይጠባበቃል፡፡
24.9 በሠራተኛው ምክንያት በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ውሣኔ መስጠት ካልተቻለም ይህም
በማስረጃ ሲረጋገጥ ድርጅቱ ደመወዝ ሳይከፍለው ከሥራ ሊያሰናብተው ይችላል፡፡
24.10 በዚህ ህብረት ስምምነት አባሪ ሰንጠረዥ ሁለት (2) ላይ በግልጽ ያልተመለከቱት ሌሎች
ጥፋቶች ሠራተኛው ቢፈጽም በሰንጠረዡ ላይ በተመለከተው ተመሣሣይ ጠባይና
ክብደት ባላቸው የጥፋት ዓይነቶች ላይ በተወሰነው የቅጣት መጠን መሠረት የዲሲኘሊን
እርምጃ ይወሰድበታል፡፡ ሆኖም የፈጸመው ጥፋት ዓይነትና ክብደት ከቅጣቱ ሠንጠረዥ
ጋር በማነጻጸር ረገድ አጠራጣሪና መረጃ የሚጠይቅ ሆኖ ሲገኝ እርምጃ ከመውሰዱ
በፊት ጉዳዩ በኮሚቴ ተጠንቶ የውሳኔ ሃሣብ እንዲቀርብ ይደረጋል፡፡
24.11 እንደ ጥፋቱ ዓይነት ቅለትና ክብደት እንዲሁም ድግግሞሽ እየታየ በዚህ ህብረት
ስምምነት የተመለከቱት የዲስፕሊን ጉድለቶች (ጥፋቶች) ላይ ተፈፃሚ የሚሆኑ
የዲስፐሊን ቅጣቶች፡-
ሀ. የቃል ማስጠንቀቂያ፣ መ. ከደረጃና ደመወዝ ዝቅ ማድረግ፣
ለ. የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ፣ ሠ. ከሥራ ማሰናበት ናቸው፡፡
45
24.12 የዲሲፕሊን ቅጣት ወይም አፈፃፀም በሰራተኛው ማህደር ውስጥ በሪከርድነት ተይዞ
በሰራተኛው ላይ ሊጠቀስ ወይም የደረጃ እድገት ሊያሳግድ ወይም ነጥብ ለማስቀነስ
የሚቻለው ከዚህ በታች በተመለከተው ሰንጠረዥ መሰረት ይሆናል፡፡
ሀ/ ከባድ የዲስኘሊን ቅጣትና እስከ አንድ ወር የደመወዝ ቅጣት የሚደርስ ቀላል
የዲስኘሊን ቅጣት የተወሰነባቸው ከዚህ በታች የተገለፀውን የእገዳ ጊዜ እስኪጨርሱ
ድረስ ለደረጃ እድገት ውድድር መቅረብ አይችሉም። የደረጃ እድገት እገዳ ጊዜውን
ከጨረሱ በኋላ ከዚህ በታች በተመለከተው ሠንጠረዥ ላይ የተመለከተው ነጥብ
እየተቀነሰባቸው ሊወዳደሩ ይችላሉ።
ለ/ የጹሁፍ ማስጠንቀቂያ የተወሰነባቸው ሠራተኞች በማንኛውም ጊዜ ከውድድር
የማይታገዱ ሆኖ የቅጣቱ ውሣኔ ከተላለፈበት ቀን ጀምሮ ከዚህ በታች
እስከተጠቀሱት የጊዜ ገደብ ቀን ድረስ በሠንጠረዡ ላይ የተመለከተው ነጥብ
እየተቀነሰባቸው ሊወዳደሩ ይችላሉ።
የቅጣት ጊዜ
ለማህደር
ለደረጃ ለደረጃ እድገት
እድገት ታግደው የቆየበትን ጥራት
ታግደው የቅጣት ጊዜ ከጨረሱ የሚስጥ
ተ. የተወሰደው የዲስኘሊን የሚቆዩበት በኋላ ነጥብ እተቀነሰ የቅጣት ጊዜ ነጥብ
ቁ እርምጃ የቅጣት ጊዜ የሚወዳደሩበት ጊዜ ድምር ከ10%
ከደረጃና ደመወዝ ዝቅ ለ1 ዓመት ለ1 ዓመት ለ2 (ሁለት) 4
1
ማድረግ (ከባድ) ዓመት
ከአንድ ወር በላይ እስከ ለ6 ወር ለ6 ወር ለ1 (አንድ) 6
2 ሦስት ወር የደመወዝ ዓመት
ቅጣት (ከባድ)
እስከ አንድ ወር የደመወዝ ለ3 ወር ለ3 ወር ለ6 (ስድስት) 8
3 ቅጣት (ቀላል) ወር
የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ __ 3 ወር __ 9
4
ቅጣት (ቀላል)
የቃል ማስጠንቀቂያና __ __ __ 10
5 ምንም ሪከርድ
የሌለበት/ባት
24.13 ደረጃ ዕድገት ታግዶ ሚቆይበትን የቅጣት ጊዜ የጨረሰ ሠራተኛ ገደቡ ካለቀበት ጊዜ
ጀምሮ የደረጃ ዕድገት በህብረት ስምምነቱ መሰረት የማህደር ጥራት ነጥብ እየተቀነሰበት
የመወዳደር መብቱ ይጠብቅለታል፡፡
46
24.14 ባለበት የስራ መደብ ከደረጃና ደመወዝ ዝቅ የተደረገ ሰራተኛ የያዘውን የስራ መደብ
እንደያዘ ከደረጃና ደመወዝ ዝቅ ተደርጎ የሚሰራ በመሆኑ አጠቃላይ የቅጣት ጊዜውን
(ከደረጃ ዕድገት ታግዶ የሚቆይበት ሲደመር ነጥብ እየተቀነሰ የሚወዳደርበት) ሲጠናቀቅ
በዚያው የስራ መደብ ላይ ከሆነ ወደ ነበረበት ደረጃና ደመወዝ እንዲመለስ ይደረጋል፡፡
24.15 ካለበት የስራ መደብ ተነስቶ በቅጣቱ መሰረት ዝቅ ያለ ደረጃ ያለው የስራ መደብ ላይ
ተመድቦ እየሰራ ያለ ሰራተኛ በደረጃ ዕድገት አግባብ ካልሆነ በስተቀር ወደ ነበረበት
ደረጃና ደመወዝ ተመልሶ አይመደብም፡፡
24.16 የቃል ማስጠንቀቂያ በሚሰጥበት ጊዜ የጥፋቱ ዝርዝርና ቀን ከሰፈረ በኋላ ሠራተኛው
የቃል ማስጠንቀቂያ ለመሰጠቱ በተለየ መዝገብ ሠራተኛው እና ማስጠንቀቂያ
የሚሰጠው የሥራ ኃላፊ በጋራ ይፈርማሉ፡፡ መዝገቡም በበጀት ዓመቱ በጥንቃቄ
በክፍሉ ይያዛል፡፡ ሆኖም ሠራተኛው ለመፈረም ፈቃደኛ ሆኖ ካልተገኘ የቃል
ማስጠንቀቂያው ወደ ፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ተቀይሮ በፅሁፍ የተሰጠ የቃል ማስጠንቀቂያ
በሚል በጹሁፍ ተሰጥቶ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
24.17 ከቃል ማስጠንቀቂያ በላይ በዚህ አንቀፅ 24.11 “ለ-ሠ” ያለው የሥነ-ሥርዓት እርምጃ
ከሆነ ለሠራተኛው በፅሑፍ ሆኖ ሠራተኛው ፈርሞ እንዲቀበል ይደረጋል፡፡ ሠራተኛው
የማይፈርም ሆኖ ከተገኘ በድርጅቱ የውስጥ ሰሌዳ ላይ ለ5 (አምስት) ተከታታይ ቀናት
ተለጥፎ ይቆያል፡፡ አድራጐቱም ተጨማሪ የሥነ-ሥርዓት ጉድለት እንደፈፀመ
ይቆጠራል፣
24.18 አንድ ሠራተኛ በፈጸመው ጥፋት የተነሣ በዚህ ኀብረት ስምምነት መሠረት የሚወሰዱ
የዲሲፕሊን እርምጃ በወንጀል ወይም በፍትሐብሔር ከመከሰስ አያግደውም፡፡
47
25.2.2 በንብረት እና ገንዘብ ላይ የተመደበ ሰራተኛ ገንዘብ ወይም ንብረት ማጉደሉ በኦዲት
ከተረጋገጠ ቀን ጀምሮ እንደክብደቱ መጠን ታይቶ ውሉ በማስጠንቀቂያ ሊቋረጥ
ይችላል፡፡
48
25.3.7 ለግል ወይም ለሌላ ወገን ጥቅም ወይም ድርጅቱን በሚጎዳ በማናቸውም አኳኋን
በድርጅቱ ስም ወይም በድርጅቱ መታወቂያ ባለሥልጣን በመምሰል የተጠቀመ፡፡
25.3.8 የድርጅቱን ወይም የሥራ ባልደረቦቹን ወይም የደንበኞቹን ንብረት ወይም ገንዘብ
የሰረቀ፣ የዘረፈ ወይም ለመስረቅ የሞከረ ወይም ሆነ ብሎ ያጎደለ ወይም በእነዚህ
አድራጎት የተባበረ፡፡
25.3.9 ለድርጅቱ ሥራ እንዲውሉ የተሰጡትን የአደጋ መከላከያና ሌሎች ንብረቶች የሸጠ
ወይም የለወጠ ወይም ለሌላ ተግባር ያዋለ፡፡
25.3.10 ሆን ብሎ የግል ጥቅሙን በመፈለግ የድርጅቱን ንብረት ከተፈቀደው በላይ ከመጋዘን
ወጪ ያደረገ፡፡
25.3.11 ያልተሰራውን ሥራ ተሰርቷል ብሎ የሐሰት ሪፖርት ያቀረበ ወይም እንዲቀርብ
ያስደረገ፡፡
25.3.12 ሆን ብሎ ወይም በቸልተኝነት የኤሌክትሪክ፣ የውሃ፣ የስልክና የሬዲዮ መገናኛ
መስመሮች እንዳይሠሩ አድርጎ በሥራ፣ በሠራተኛና በድርጅቱ ንብረት ላይ ከባድ
ጉዳት ያደረሰ፡፡
25.3.13 ማንኛውም ሠራተኛ ከሥራ ጋር በተያያዘ ሁኔታ ከባለጉዳዩ ወይም ከሌላ ሠራተኛ
የማይገባውን ልዩ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት አስቦ ከባለጉዳዩ ወይም
ከሠራተኛው መማለጃ ጉቦ በጥሬ ገንዘብ ወይም በዓይነት የተቀበለ ወይም የሰጠ
ወይም መቀበሉም ሆነ መስጠቱ የተረጋገጠበት፡፡
25.3.14 ማንኛውም የድርጅቱ ሠራተኞች በሥራ ቦታ ወይም በሥራ ላይ ግድያ መፈፀሙ
ወይም ለመፈፀም መሞከሩ ወይም ዝሙት መፈፀሙ ወይም ለመፈፀም መሞከሩ
ወይም እርስበርስ መደባደቡ ወይም ለመደባደብ መዛቱ ወይም መሰዳደቡ ወይም
ጠብ ማስነሳቱ ወይም በማናቸውም ሁኔታ ፀጥታና የሥራ ሰላም እንዲደፈርስ
ማድረጉ ወይም የዚህ ድርጊት ቀስቃሽ ወይም አነሳሽ ወይም ምክንያት ሆኖ መገኘቱ
በተጨባጭ ሲረጋገጥ፡፡
25.3.15 በአልኮል ወይም በእጽ ወይም በሌሎች ተመሳሳይ መጥፎ ሱሶች ተመርዞ ወደ ሥራ
የገባ ወይም ወደ ሥራ በመግባት በሚንቀሳቀስ ወይም በማይንቀሳቀስ የድርጅቱ
ንብረት ላይ አደጋ ለማድረስ የሞከረ፣
25.3.16 በሥራና በሠራተኛ ወይም በድርጅቱ ንብረት ላይ አደጋ ሊያስከትል የሚችል
ድርጊት ሆን ብሎ የፈፀመ፡፡
49
25.3.17 በማንኛውም ሁኔታ በድርጅቱ ላይ የተቃጣውን ከባድ አደጋ እያወቀ ሆን ብሎ ወይም
በቸልተኝነት ለድርጅቱ ካላሣወቀ ወይም የተቻለውን ያህል አደጋውን ለመከላከል
(ለመመከት) ጥረት ያላደረገ፡፡
25.3.18 በሥራ ፀባዩ ለስራ የተሰጠውን የጦር መሣሪያ ያበላሸ ወይም ያጠፋ ወይም ያባከነ
ወይም የሸጠ ወይም የለወጠ ወይም ለማይመለከተው ሰው ያስያዘ፤ ያስታጠቀ ወይም
ወንጀል እንዲሠራበት ያደረገና የጥበቃ አባል ሆኖ ለጥፋት፣ ለሌብነት ወይም
ለጉዳት የተባበረና ያመቻቸ መሆኑ በማስረጃ የተረጋገጠበት፡፡
25.3.19 እንዲጠብቅ የተመደበበትን የዘብ ቦታ የቅርብ ኃላፊውን ፈቃድ ሳያገኝ ወይም ተተኪ
ዘብ ሳይኖር ጥሎ የሄደ፤
25.3.20 የሠራተኛው የሥራ ዕቅድ አፈፃፀም ውጤት ለመጀመሪያ ጊዜ ዝቅተኛ ሆኖ ሲገኝ
የድክመቱ ምክንያት እየተጣራ ምክር፣ ስልጠናና የሥራ ላይ ልምምድ ተሰጥቶት
የዕቅድ አፈፃፀም ምዘና ውጤቱ ለ2ኛ ጊዜ ዝቅተኛ ከሆነ፡፡
25.3.21 ዋስትና ለሚጠይቁ የስራ መደቦች ሰራተኛው የመጀመሪያ ዋሱ ዋስትናውን
እንዲያወርድ ከጠየቀበት ቀን አንስቶ ባሉት ተከታታይ 30 ቀን ጊዜ ውስጥ ተተኪ
ዋስ ካላቀረበ፡፡
50
ሁለተኛ ደረጃ
ተ.ቁ የጥፋቱ ዓይነት አንደኛ ደረጃ ቅጣት
ቅጣት
3 በድርጅቱ መኪና ላይ በመኪናው የቴክኒክ በመድን ድርጅት በመድን ድርጅት
ጉድለት ሳይሆን በአሽከርካሪው ቸልተኝነት የማይሸፍነውን ወጭ የማይሸፍነውን
ያለጥንቃቄ በመንዳት ወይም የትራንስፖት ከፍሎ የ15-30 ቀን ወጭ ከፍሎ
ሕግን ባለማክበር በመኪናው ላይ ወይም ደመወዝ ቅጣት ከሥራ ስንብት
በጫነው ንብረት ወይም ሰው ላይ ወይም
በማናቸወም ላይ ጉዳት ያደረሰ
4 በሀላፊነት ከተረከበው የድርጅቱ መኪና የወሰደውን ወይም የወሰደውን
ወይም ለድርጅቱ ሥራ መገልገያ ንብረቶች ያጎደለውን ንብረት ተክቶ ወይም
በመውሰድ ከድርጅቱ ሥራ ውጪ ለሌላ እንደ ጥፋቱ ክብደት እስከ ያጎደለውን
ተግባር ያዋለ ወይም ያጎደለ ወይም ለራሱ አንድ ወር ደመወዝ ንብረት ተክቶ
ጥቅም የተገለገለ ቅጣት ከሥራ ስንብት
5 በድርጀቱ ላይ በድርጅቱ ንብረት ወይም ላደረሰው ጉዳት ኃላፊና ለደረሰው ጉዳት
በሥራ ላይ ከባድ ጉዳትና በደል ተጠያቂ ሆኖ እንደ ጥፋቱ ኃላፊና ተጠያቂ
የሚያስከትል አግባብ ያልሆነ ተግባር የፈፀመ ክብደት እስከ አንድ ወር ሆኖ ከሥራ
ደመወዝ ቅጣት ስንብት
6 የድርጅቱ ሀብት በዓይነት ወይም በገንዘብ እንደጥፋቱ ክብደት ከ15 ከሥራ ስንብት
በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የስርቆት ወይም ቀን እስከ የአንድ ወር
የማታለል ወይም ለግል ጥቅም ሲውል ወይም ደመወዝ ቅጣት
በማናቸውም ሁኔታ ጉዳት ሲደርስበት
እያወቀ ለሚመለከተው ክፍል ያላሳወቀ
51
ሁለተኛ ደረጃ
ተ.ቁ የጥፋቱ ዓይነት አንደኛ ደረጃ ቅጣት
ቅጣት
10 የሚመለከተው የድርጅቱ ባለሥልጣን እንደጥፋቱ ክብደት ከ15 ከሥራ ስንብት
ሳያውቀውና ሳይፈቅድ የድርጅቱን ዶክመንት ቀን እስከ የአንድ ወር
በቀጥታም ሆነ በተዘወዋሪ መንገድ ደመወዝ ቅጣት
ለማይመለከተው ሰው ወይም ድርጅት የሰጠ
11 በስራ ሰዓት ያለ ድርጅቱ ፈቃድ ወረቀት እንደጥፋቱ ክብደት ከ15 ከሥራ ስንብት
እያዞረ ሌሎችን ሰራተኞች ያስፈረመ ወይም ቀን ደመወዝ ቅጣት
ስብሰባ መጥራት ወይም አድማ የሚያስነሳ እስከ ደመወዝና ደረጃ
ወይም በተጠቀሱት ህገወጥ ተግባራት ላይ ዝቅ ማድረግ
መሳተፉ በማስረጃ የተረጋገጠ
12 ተገቢ የመንጃ ፈቃድ ሳይኖረው ወይም አድራጎቱ ያስከተለው ከሥራ ስንብት
ከድርጅቱ የማሽከርከር ፈቃድ ሳይሰጠው ወጪና ጉዳት ካለ ከፋይና
የድርጅቱን መኪና ለማንቀሳቀስ የሞከረ ወይም
ተጠያቂ ሆኖ እንደጥፋቱ
ያሽከረከረ ወይም በኃላፊነት የተረከበውን ክብደት ከአንድ ወር
የድርጅቱን መኪና ተገቢ መንጃ ፈቃድ ላለውደመወዝ ቅጣት አስከ
ወይም ለሌለው ሰው አሳልፎ የሰጠ ደረጃና ደመወዝ ዝቅ
ማድረግ
13 የድርጅቱን ስራ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ለደረሰው ጥፋት ተጠያቂ ከሥራ ስንብት
መጨረስ እየቻለ አጠናቆ ያላስረከበ ወይም ሆኖ እስከ አንድ ወር
በተቀመጠው የጥራት ደረጃ መሰረት መስራት ደመወዝ ቅጣት
እየቻለ የጥራት ጉድለት ያስከተለ
52
ሦስተኛ
ተ.ቁ የጥፋቱ ዓይነት አንደኛ ደረጃ ቅጣት ሁለተኛ ደረጃ ቅጣት
ደረጃ ቅጣት
3 ከድርጅቱ ሥራ ጋር እንደጥፋቱ ክብደት እንደጥፋቱ ክብደት ከሥራ
በተያያዘ ሁኔታ በሥራ 5 እስከ 15 ቀን ከአንድ ወር ደመወዝ ስንብት
ኃላፊዎች ወይም ደመወዝ ቅጣት ቅጣት እስከ ደመወዝና
በማናቸውም የድርጅቱ ደረጃ ዝቅ ማድረግ
ሠራተኛ ላይ ማስፈራራት
ወይም ተጽዕኖና የማስገደድ
ሙከራ ያደረገ
4 በድርጅቱ ደብዳቤዎች እንደጥፋቱ ክብደት እንደጥፋቱ ክብደት ከ15 ከሥራ
ወይም ጽሁፎች ወይም ከጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ቀን እስከ አንድ ወር ስንብት
በማናቸውም ዓይነት ሰነዶች እስከ 10 ቀን ደመወዝ ደመወዝ ቅጣት
ላይ በማናቸውም ሁኔታ ቅጣት
ጉዳት ሊደርስ ወይም
እንደሚደርስ እያወቀ የሥራ
ኃላፊነቱን ያልተወጣ ወይም
ተገቢ ጥበቃና እንክብካቤ
ያላደረገ ወይም ሁኔታው
ከአቅም በላይ ሆኖ በወቅቱ
ለሚመለከተው ክፍል
ያላሳወቀ፡፡
5 በሥራ አጋጣሚ ያየውን እንደጥፋቱ ክብደት እንደጥፋቱ ክብደት እስከ
ወይም የሰማውን ሚስጥር ከጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከ15 ቀን ደመወዝ ቅጣት ከሥራ
ሳይፈቀድለት ለሌላ አካል እስከ 15 ቀን ደመወዝ እስከ ደረጃና ደመወዝ ዝቅ ስንብት
የነገረ ወይም ያሰራጨ ቅጣት ማድረግ
6 በማናቸውም የድርጅቱ እንደጥፋቱ ክብደት እንደጥፋቱ ክብደት ከ15 ከሥራ
የሥራ ቦታ ቁማር መጫወት እስከ 10 ቀን ደመወዝ ቀን እስከ አንድ ወር ስንብት
ወይም ሌሎች ማናቸውንም ቅጣት ደመወዝ ቅጣት
ዓይነት አስነዋሪ ድርጊቶች
መፈጸም
7 በድርጅቱ ማንኛውም መኪና የጭነቱ ኪራይ የጭነቱ ኪራይ ተገምቶ የጭነቱ
ከተፈቀደለት ጭነት ውጭ ተገምቶ ገቢ ገቢ እንዲሆንና ኪራይ
ገቢ በሚያስገኝ ሁኔታ እንዲሆንና እንደጥፋቱ ክብደት ከ15 ተገምቶ
በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እንደጥፋቱ ክብደት ቀን እስከ ከአንድ ወር ለድርጅቱ
መንገድ የግል ጥቅም እስከ 10 (አስር) ቀን ደመወዝ ቅጣት ገቢ
ለማግኘት ሰው ወይም ደመወዝ ቅጣት እንዲሆንና
ንብረት ወይም ሌላ ጭነት ተደርጐ
የጫነ ከሥራ ስንብት
53
26.3. በአራተኛ ጥፋት ከሥራ የሚያሰናብቱ ድርጊቶች
አራተኛ
አንደኛ ደረጃ ሁለተኛ ደረጃ ሶስተኛ ደረጃ
ተ.ቁ የጥፋቱ ዓይነት ደረጃ
ቅጣት ቅጣት ቅጣት
ቅጣት
1 በጊዜው ተሰርቶ መጠናቀቅ የጥፋቱ አፈፃፀም የጥፋቱ የጥፋቱ አፈፃፀም ከሥራ
የሚገባውን ሥራ መወዘፍ ሁኔታ ተገምግሞ አፈፃፀም ሁኔታ ሁኔታ ተገምግሞ ስንብት
ወይም ማቀዝቀዝ ወይም ከጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ተገምግሞ 6-15 16-30 ቀን
ያልተሠራውን ሥራ እስከ 5 ቀን ደመወዝ ቀን ደመወዝ ደመወዝ ቅጣት
እንደተሠራ አደርጎ ማቅረብ ቅጣት ቅጣት
2 ለሚመለከታቸው የሥራ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንደጥፋቱ እንደጥፋቱ ከሥራ
ክፍሎች እንዲደርስ ክብደት አስከ ክብደት አስከ ስንብት
የተሰጠውን የጽሁፍ 15 ቀን 16-30 ቀን
መልዕክቶች ወይም ትዕዛዝ ደመወዝ ደመወዝ ቅጣት
ሆን ብሎ ያዘገየ ወይም
ቅጣት
ያላደረሰ፣
3 አግባበ ባላቸው የድርጅቱ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንደጥፋቱ እንደጥፋቱ ከሥራ
የሥራ ክፍሎች ወይም የሥራ ክብደት አስከ ክብደት አስከ ስንብት
ኃላፊዎች የሚጠየቁትን የቃል 15 ቀን 16-30 ቀን
ወይም የጽሁፍ ማስረጃዎች ደመወዝ ደመወዝ ቅጣት
ወይም መረጃዎች ከአቅም
ቅጣት
በላይ ካልሆነ በስተቀር
በጊዜው ለመስጠት ፈቃደኛ
አለመሆን ወይም ማዘግየት
ወይም በማጉላላት
ትክክለኛውን ያለመግለጽ
ወይም በወቅቱ መቅረብ
የሚገባቸውን ሁኔታዎችና
ጉዳዮች አለማቅረብና
አለማሳወቅ
4 ኃላፊው በቃልም ሆነ በጽሁፍ እንደጥፋቱ ክብደት እንደጥፋቱ እንደጥፋቱ ከስራ
የሚሰጠውን ትዕዛዝ ወይም ከጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ክብደት ከ6-15 ክብደት ከ16-30 ስንብት
መመሪያ ባለማክበር ወይም እስከ 5 ቀን ደመወዝ ቀን ደመወዝ ቀን ደመወዝ
የሥራ ኃላፊነት ለመቀበል ቅጣት ቅጣት ቅጣት
ፈቃደኛ አለመሆን ወይም
ሥራውን ላለመሥራት
ምክንያት መፍጠርና የሥራ
ጊዜን በማባከን
5 አግባብ ያልሆነ ክፍያን
የወሰደውን ተመላሽ የወሰደውን የወሰደውን የወሰደውን
የሚያስከትል የትርፍ ሰዓት አድርጎ የ5 (አምስት) ተመላሽ ተመላሽ አድርጎ ተመላሽ
ሥራ የሠራ ወይም ያሠራ ቀን የደመወዝ ቅጣት አድርጎ እንደጥፋቱ አድርጎ
ወይም ተገቢ ያልሆነ የውሎ እንደጥፋቱ ክብደት ከ30 ከሥራ
አበል የወሰደ ወይም ያስወሰደ ክብደት የ15 ቀን ደመወዝ ስንብት
ወይም እንዲከፈል ያደረገ (አስራ አምስት) ቅጣት እስከ
ሠራተኛ ቀን ደመወዝ ደመወዝና ደረጃ
ቅጣት ዝቅ ማድረግ
6 ለድርጅቱ ሥራ ማስኬጃ የጎደለውን ገንዘብ የጎደለውን የጎደለውን ከሥራ
54
አራተኛ
አንደኛ ደረጃ ሁለተኛ ደረጃ ሶስተኛ ደረጃ
ተ.ቁ የጥፋቱ ዓይነት ደረጃ
ቅጣት ቅጣት ቅጣት
ቅጣት
የተሰጠውን ገንዘብ ያለ በቂ ከፍሎ የ5 (አምስት) ገንዘብ ክፍሎ ገንዘብ ክፍሎ ስንብት
ምክንያት ለግሉ የተጠቀመ ቀን ደመወዝ ቅጣት የ15 (አስራ የ30 (ሰላሳ) ቀን
አምስት) ቀን ደመወዝ ቅጣት
ደመወዝ ቅጣት
7 ለድርጅቱ ሥራ/ ደንብ ልብስ ድርጅቱ ለደንብ ድርጅቱ ድርጅቱ ለደንብ ከሥራ
እንዲውሉ የተሰጡትን የሸጠ ልብሱ ያወጣውን ለደንብ ልብሱ ልብሱ ያወጣውን ስንብት
ወይም የለወጠ ወይም ለሌላ ገንዘብ መልሶ እስከ 5 ያወጣውን ገንዘብ መልሶ
ተግባር ያዋለ (አምስት) ቀን ገንዘብ መልሶ የ30 (ሰላሳ) ቀን
ደመወዝ ቅጣት የ15 (አስራ ደመወዝ ቅጣት
አምስት) ቀን
ደመወዝ ቅጣት
55
አንቀጽ ሃያ ሰባት (27) የሥራ ልብስና የአደጋ መከላከያዎች
27.1 ሠራተኛውን ከሥራ ጋር ከተያያዘ አደጋ ወይም በሽታ ለመከላከል ድርጅቱ የሥራ
ልብስና የአደጋ መከላከያ ቁሳቁሶች ከታች በ27.10 በተገለፀው አግባብ ይሰጣል፡፡
27.2 በየወሩ የሚሰጡ ካልሆነ በስተቀር የሥራ ልብስና የአደጋ መከላከያዎች አዲስ በጀት
ዓመት ከተጀመረበት ዕለት ጀምሮ ባሉት ሦስት ወራት ውስጥ መሰጠት ይኖርበታል፡፡
27.3 ድርጅቱ ተገቢ የሆነ የመፀዳጃ አገልግሎትና ሁኔታ እንዲኖር ያደርጋል፡፡
27.4 የሙከራ ጊዜያቸውን ያልጨረሱ አዲስ ተቀጣሪ ሠራተኞችም ከታች በ27.10 በተጠቀሱ
የስራ መደቦች ላይ ተመድበው የሚሰሩ በዚህ አንቀጽ የተጠቀሱ የአደጋ መከላከያ
መሳሪያዎችን ማግኘት ይገባቸዋል፡፡
27.5 ብትን ጨርቅ ተገዝቶ የሚሰጥ ከሆነ ለኮትና ሱሪ 3.5 ሜትር (ሶስት ሜትር ከግማሽ)
ጨርቅ ለአንድ ሙሉ ልብስ ይሰጣል፡፡ ለካፖርት፣ ለሸሚዝና ሱሪ፣ ለጃኬትና ጉርድ ቀሚስ
ከሆነ 3 (ሶስት) ሜትር ለአንድ ሙሉ ልብስ ይሰጣል፡፡
27.6 የደንብ ልብስ በሚሰጥበት የስራ መደብ ላይ ተመድቦ የሚሰራ አንድ ሰራተኛ የደንብ
ልብስ በሚሰጥበት በጀት ዓመት 9 (ዘጠኝ) ወርና ከዚያ በላይ ከሰራ የተፈቀደውን የደንብ
ልብስ በሙሉ ያገኛል፡፡
27.7 የደንብ ልብስ በሚሰጥበት የስራ መደብ ላይ ተመድቦ የሚሰራ አንድ ሰራተኛ የደንብ
ልብስ በሚሰጥበት በጀት ዓመት ከ9 (ዘጠኝ) ወር በታችና ከ3 (ሶስት) ወር በላይ ከሰራ
የተፈቀደው የደንብ ልብስ መጠን በዓመት 2 (ሁለት) ከሆነ የተፈቀደውን 50 በመቶ
ወይም ግማሹን እንዲሁም የተፈቀደው የደንብ ልብስ መጠን በዓመት አንድ ብቻ ከሆነ
የተፈቀደውን 100% ወይም ሙሉውን ያገኛል፡፡ ነገር ግን አገልግሎቱ ከ3 (ሶስት) ወር
በታች ከሆነ አያገኝም፡፡
27.8 ከታች በ27.10 የተጠቀሱ የደንብ ልብሶች ከድርጅቱ አቅም በላይ በሆነ ምክንያት ካልሆነ
በስተቀር መሰጠት ያለባቸው ተገዝተውን መሰፋት ያለባቸው ተሰፍተው ነው፡፡
27.9 በመደበኛ ትምህርትም ይሁን በሌላ በማናቸውም ምክንያት በበጀት ዓመቱ በመደበኛ
ስራ ላይ ለሌሉ የስራ ሀላፊዎችም ሆነ ሰራተኞች የደንብ ልብስ አያገኙም፡፡
56
27.10 ለሠራተኛው የሚሰጥ የሥራ ደኅንነት መጠበቂያና የሥራ
ልብሶች
ተ. የሠራተኛው የሚሠጠው የሥራና የደንብ ልብስ
ብዛት
ቁ የሥራ መደብ ዓይነት
1 የጥበቃ ሽፍት መሪ እና ላይት ብሎ ቴትሮን ኮትና ሱሪ በዓመት ሁለት
ወንድ ጥበቃ ከተንጠልጣይ ባጅ ጋር
ሸሚዝ በሀገር ውስጥ የተመረተ ነጭ በዓመት ሁለት
57
ተ. የሠራተኛው የሚሠጠው የሥራና የደንብ ልብስ
ብዛት
ቁ የሥራ መደብ ዓይነት
የልብስ ሣሙና 250 ግራም በወር ሁለት
58
ተ. የሠራተኛው የሚሠጠው የሥራና የደንብ ልብስ
ብዛት
ቁ የሥራ መደብ ዓይነት
ከኘላሲቲክ የተሠራ የእጅ ጓንት እንዳለቀ የሚተካ
8 የቢሮ ተላላኪ (ሴት) ነጭ ሸሚዝ በሀገር ውስጥ የተመረተ በዓመት አንድ
የውስጥ ልብስ ጥራት ያለው በሀገር በዓመት አንድ
ውስጥ የተመረተ
ቴትሮን ጃኬትና ጉርድ ቀሚስ በዓመት አንድ
(ላይት ብሉ)
ወጥ ሸሚዝና ሱሪ (ላይት ብሉ) በዓመት አንድ
አጭር ጉርድ ቆዳ ጫማ ጥራት በዓመት ሁለት ጥንድ
ያለው በሀገር ውስጥ የተመረተ
የልብስ ሳሙና 250 ግራም በወር አንድ
9 የቢሮ ተላላኪ (ወንድ) ነጭ ሸሚዝ በሀገር ውስጥ የተመረተ በዓመት ሁለት
ላይት ብሎ ቴትሮን ኮትና ሱሪ በዓመት ሁለት
አጭር ጉርድ ቆዳ ጫማ ጥራት በዓመት ሁለት ጥንድ
ያለው በሀገር ውስጥ የተመረተ
የልብስ ሳሙና 250 ግራም በወር አንድ
10 የቢሮ ጽዳት ሠራተኞች ካኪ ቴትሮን ቀሚስ፣ ከቀሚሱ ጋር በዓመት ሁለት
(ሴት) ተመሣሣይ የሆነ ሙሉ ሽርጥ
እንዲሁም የውስጥ ልብስ፣
አጭር ጉርድ ቆዳ ጫማ ጥራት በዓመት ሁለት ጥንድ
ያለው በሀገር ውስጥ የተመረተ
የልብስ ሣሙና 250 ግራም በወር አንድ
የገላ/ የእጅ ሳሙና ከ175-200 በወር አንድ
ግራም
የጨርቅ ማስክ በዓመት ሁለት
የፀጉር መሸፈኛ ቆብ ጨርቅ በዓመት ሁለት
የዝናብ ልብስ በሦስት አመት አንድ
የመፀዳጃ የእጅ ጓንት /ላስቲክ/ እንዳለቀ የሚተካ
59
ተ. የሠራተኛው የሚሠጠው የሥራና የደንብ ልብስ
ብዛት
ቁ የሥራ መደብ ዓይነት
የፀጉር መሸፈኛ ቆብ ጨርቅ በዓመት ሁለት
ፎጣ በዓመት አንድ
ወተት በቀን አንድ ሊትር
15 ንድፍ ሠራተኞች ¾ ነጭ ቴትሮን ካፖርት በዓመት አንድ
ፎጣ በዓመት አንድ
የገላ/ የእጅ ሳሙና ባለ ከ175-200 በወር አንድ
16 ላቦራቶሪ ቴክኒሽያኖች፣ ግራም
¾ ነጭ ቴትሮን ካፖርት በዓመት ሁለት
ሶይል ኬሚስቶች፣ ሶይል ወተት በቀን አንድ ሊትር
ሜካኒክስ የስራ መደብ ላይ ፎጣ በዓመት አንድ
ተመድበው የሚሰሩ የጀሮ ሴፍቲ በዓመት አንድ
ባለሙያዎች፣ ማቴሪያል ኦሞ በወር አንድ
መሀንዲሶች፣ ዳታ አናሊስት የልብስ ሳሙና 250 ግራም በወር አንድ
እና የላቦራቶሪ ሀላፊዎች፡፡
የገላ/ እጅ ሣሙና ከ175-200 ግራም በወር አንድ
የላቦራቶሪ ሀላፊዎችና ዳታ
ጫማ ከኬሚካል የሚከላከል (አፈር በአመት አንድ ጥንድ
አናሊስት ባለሙያዎች
ኬሚስትሪና ውሀ ጥራት ለሚሰሩ
60
ተ. የሠራተኛው የሚሠጠው የሥራና የደንብ ልብስ
ብዛት
ቁ የሥራ መደብ ዓይነት
ወተት አያገኙም፡፡ ባለሙያ)
ጫማ ከኬሚካል የሚከላከል በአመት አንድ ጥንድ
ከሚያገኙት ባለሙያዎች ውጭ
ለሌሎች ባለሙያዎችና ሀላፊዎች
ሴፍቲ ጫማ በሀገር ውስጥ
የተመረተ
የዝናብ ልብስ በሶስት ዓመት አንድ
የጨርቅ ቆብ በአመት አንድ
የእጅ ጓንት (የፕላሰቲክና የሸራ) እንዳለቀ የሚተካ
የአፍንጫና የአፍ ማሰክ እንዳለቀ የሚተካ
17 ሁለገብ ጥገና ባለሙያ ¾ ካኪ ቴትሮን ካፖርት በዓመት አንድ
61
ተ. የሠራተኛው የሚሠጠው የሥራና የደንብ ልብስ
ብዛት
ቁ የሥራ መደብ ዓይነት
20 ጂኦሎጂስቶች እና ¾ ነጭ ካኪ ቴትሮን ካፖርት በዓመት አንድ
ጂኦፊዚክስ
የዝናብ ልብስ በሦስት ዓመት አንድ
ሴፍቲ ቆዳ ጫማ ጥራት ያለው በዓመት አንድ ጥንድ
በሀገር ውስጥ የተመረተ
21 የጋራዥ ክፍል ቴክኒሽያኖች ቱታ ካኪ ቲትረን ጥቁር ሰማያዊ በዓመት ሁለት
(መካኒኮች፣ ኤሌክትሪሽያን) ሴፍቲ ቆዳ ጫማ ጥራት ያለው በዓመት ሁለት ጥንድ
በሀገር ውስጥ የተመረተ
የእጅ ጓንት ሸራ እንዳለቀ የሚተካ
የልብስ ሣሙና 250 ግራም በወር ሁለት
የገላ/ የእጅ ሳሙና ከ175-200 በወር አንድ
ግራም
ኦሞና አጃክስ እንዳለቀ
ፎጣ በዓመት ሁለት
የአይንና የፊት ማስክ እንዳለቀ
62
ተ. የሠራተኛው የሚሠጠው የሥራና የደንብ ልብስ
ብዛት
ቁ የሥራ መደብ ዓይነት
የእጅ ጓንት የፕላሰቲክና የሸራ እንዳለቀ የሚተካ
(ለላቦራቶሪ ስቶር ሰራተኛ ብቻ)
የአፍንጫና የአፍ ማሰክ (ለላቦራቶሪ እንዳለቀ የሚተካ
ስቶር ሰራተኛ ብቻ)
ፎጣ በዓመት አንድ
29 መሬት አጠቃምና የአካባቢ ሴፊቲ ጫማ ጥራት ያለው በሀገር በዓመት አንድ ጥንድ
ጥናት እና የገበያ ጥናት ውስጥ የተመረተ
ባለሙያዎችና ሀላፊዎች የዝናብ ልብስ በሶስት ዓመት አንድ
63
ተ. የሠራተኛው የሚሠጠው የሥራና የደንብ ልብስ
ብዛት
ቁ የሥራ መደብ ዓይነት
33 የመረጃ ዴስክ ሰራተኛ ¾ ካኪ ቴትሮን ካፖርት በዓመት አንድ
34 ቱልስ ሰራተኛ 3/4ኛ ካኪ ቲተሮን ካፖርት በሀገር በአመት አንድ
ውስጥ የተመረተ
አጭር ጉርድ ቆዳ ጫማ ጥራት በአመት አንድ ጥንድ
ያለው በሀገር ውስጥ የተመረተ
የልብስ ሳሙና 250 ግራም በወር አንድ
የገላ/ የእጅ ሳሙና ከ175-200 በወር አንድ
ግራም
ፎጣ በዓመት አንድ
64
ቅሬታ ሰሚ (ካለ) በፅሁፍ ያቀርባል፡፡ በዚህ ውሳኔ አሁንም ቅር ከተሰኘ ሂደቱን እየጠበቀ
የሚያቀርብ ሲሆን በመጨረሻ ለዋና ሥራ አስፈፃሚ በፅሁፍ ያቀርባል፣
28.2 በየደረጃው ያሉ ቅሬታ ሰሚዎች (ቅሬታውን ተቀብለው የሚያዩ የሥራ ኃላፊዎች)
ውሳኔውን እንደ ጉዳዩ አስቸኳይነት እየታየ ከቀረበበት ቀን ጀምሮ እስከ አምስት (5)
ተከታታይ የሥራ ቀናት ያሳውቃሉ፡፡ በዚህ የጊዜ ገደብ ምላሽ ካላገኘ ለሚቀጥለው የሥራ
ኃላፊ ያቀርባል፡፡ ሆኖም የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ውሳኔ የመጨረሻ ውሳኔ
ይሆናል፡፡
28.3 ደረጃውን ጠብቆ ያልቀረበ ቅሬታ ተቀባይነት የለውም፡፡
28.4 ሠራተኛው ለቅሬታው ምላሽ በፅሁፍ በተሰጠው ውሳኔ ውሳኔውን በተቀበለ በ10 የሥራ
ቀናት ውስጥ ቅሬታውን ለሚቀጥለው የሥራ ኃላፊ ማቅረብ አለበት፡፡ ውሳኔው በቃል
የተሰጠው ከሆነ በ15 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ በፅሁፍ አድርጐ ለሚቀጥለው
ማቅረብ አለበት፡፡
28.5 የተወሰነው የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜ ከማለፉ አስቀድሞ ሠራተኛው በህመም ወይም ህጋዊ
ማስረጃ በሚቀርብበት በሌላ የግል ችግር ወይም በድርጅቱ ለሥራ ታዝዞ ለመስክ ሥራ
በመሄዱ ምክንያት በሥራ ቦታ ባለመገኘቱ ቅሬታውን ማቅረብ ባይችል በሥራ ቦታ እያለ
ያባከነው ጊዜ ካለ ተቀንሶ የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜው ወደ ሥራ ቦታ (ወደ ድርጅቱ)
ከተመለሰበት ቀን ጀምሮ መቁጠር ይጀምራል፡፡
28.6 ሠራተኛው ቅሬታውን በዚህ ሥነ-ሥርዓት በተወሰነው ጊዜ እና ሁኔታ ካላቀረበ ቅሬታውን
በአስተዳደራዊ መልኩ እንዲታይለት ድርጅቱን ለመጠየቅ የሚኖረው መብት በይርጋ
ይታገዳል፡፡
28.7 ቅሬታ የቀረበለት የሥራ ኃላፊ ወይም የሥራ ኃላፊው ፀሐፊ ሠራተኛው በፅሁፍ
የሚያቀርበውን ቅሬታ ፈርመው የመቀበል እና የሥራ ኃላፊው በወቅቱ ምላሽ የመስጠት
ግዴታ አለባቸው፡፡
65
ሠራተኛ ባስመዘገበው የሥራ ውጤት መሠረት ማበረታቻ ለማድረግና የሥራ ውድድር
በሠራተኞች መካከል ለመፍጠር፣ የሥራ ውጤትንም ለማሳደግ፣
29.1.2 ከፍተኛ የሥራ ችሎታና ብቃት ያላቸውን ሠራተኞች ለይቶ ለማወቅና ተገቢውን
ሥልጠና በመስጠት ለከፍተኛ ሀላፊነት ለማዘጋጀት፣
29.1.3 ለተመደቡበት የሥራ ቦታ ውጤታማ ያልሆኑ ሠራተኞችን በመለየት የችግሮቻቸውን
ምንጭ ለይቶ በማወቅ ሥልጠና የሚያስፈልጋቸው ከሆነ የሥራ ላይ ሥልጠና
ለመስጠት፣ ለተመደቡበት የሥራ ቦታ ብቃት የሌላቸውን ሠራተኞች ወደሚመጥኑበት
ሥራ ለማዛወር እንዲሁም በሚመደቡበት የተለያዩ ሥራዎች ላይ ተከታታይ የችሎታ
ማነስ የሚታይባቸውን ከደረጃ ዝቅ ለማድረግና ከሥራ ለማሠናበት፡፡
29.2.4. አፈጻጸም ምዘና ውጤቱ በሠራተኛው የቅርብ ኃላፊ ይሞላል፡፡ ሰራተኛው በተሰጠው
የሥራ አፈፃጸም ምዘና ውጤት ካልተስማማ ቅሬታውና አስፍሮ የሥራ አፈጻጸም ምዘና
ውጤቱ የመፈረም ግዴታ ያለበት ሲሆን የሰራተኛው ቅሬታም ውጤቱን በሞላው ሀላፊ
የቅርብ ኃላፊ ታይቶ ከፀደቀ የሚያዝ ይሆናል፡፡ የቅሬታውን ውጤትም ውጤቱን
ያፀደቀው ሀላፊ ሰራተኛውን አስጠርቶ በአካል ሊያስረዳው ይገባል፡፡ ሰራተኛው
በውጤቱ ላይ ቅሬታ አቅርቦ ተቀባይነት ካላገኘ ውጤቱን እንደተቀበለው ይወሳዳል፡፡
የሠራተኛው የቅርብ ኃላፊ ማለት መስክ ላይ ላሉት የመስክ ተጠሪ መሐንዲሱ ወደ
መደበኛ የሥራ ክፍላቸው እስኪመለሱ ድረስ መመዘኛውን በቅድሚያ ይሞላል፡፡
29.2.5. ለሠራተኛው የሚሰጥ የሥራ አፈፃጸም ምዘና ውጤት እንደሚከተለው ይመደባል፡፡
ከ86ና በላይ A
ከ81-≥86 B+
ከ75-≥81 B
66
ከ65-≥75 C+
ከ50-≥65 C
29.2.6. በተሰጠው የስራ አፈፃፀም ምዘና ውጤት > 86 ላገኘ ወይም ከ60 በታች ለተሰጠው
ሠራተኛ የቅርብ ኃላፊው በቂ መግለጫና ማብራሪያ በግምገማው ቅጽ ላይ በተዘጋጀው
ቦታ ያስፍራል፡፡
29.2.7. የስራ አፈፃጸም ውጤቱ የመጨረሻ ውጤት ላይ ከመድረሱ በፊት ሠራተኛው ነጥቡን
እንዲያየው ወይም እንዲያውቀው አይደረግም፡፡
29.2.8. የሠራተኛው የሥራ አፈጻጸም ውጤት መመዘኛ ቅጽ የሰው ሀብት አስተዳደር አውቆት
ከግል ማሕደሩ ጋር ከተያያዘ በኋላ ለማንኛውም እድገት፣ የደመወዝ ጭማሪ፣
የትምህርት፣ ሥልጠና… ወዘተ መገምገሚያና ለሌሎች ተመሳሳይ ጉዳች ጥቅም ላይ
እንዲውል ይደረጋል፡፡
29.2.9. አንድ ሠራተኛ ቀድሞ ከነበረበት የሥራ ቦታ ወይም መደብ ወደ ሌላ የሥራ መደብና
ቦታ ቢዛወርና የቅርብ ኃላፊው አዲስ ከሆነ ሠራተኛው ከቀድሞው ኃላፊው ጋር አራት
ወርና ከዚያም በላይ ከሠራ የሥራ አፈፃፀሙን የቀድሞው ኃላፊው ይሞላለታል፡፡
አዲስ በተዛወረበት የሥራ ቦታ ከተጠቀሰው ጊዜ በታች እና ከሁለት ወር በላይ ከሠራ
የሥራ አፈፃፀሙን የሚሞላው በአዲስ ሀላፊው ይሆናል፡፡
67
31.2 በዚህ የህብረት ስምምነት ውስጥ ያልተጠቀሱት ጉዳዮች አግባብ ባለው ህግና የድር
መመሪያ መሰረት ተፈጻሚ ይሆናል ፡፡
31.3 በዚህ የህብረት ስምምነት ውስጥ ስለተመለከቱትም ይሁን ስለሌሎች የሥራ ሁኔታዎች
መንግስት የሚያወጣቸው ሕጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
ክፍል አምስት
አንቀጽ ሰላሳ ሶስት (33) ኃላፊነትና የስምምነቱ ተፈፃሚነት
33.1 ኃላፊነት
33.1.1 ይህን ህብረት ስምምነት እያንዳንዱ ሰራተኛ ተግባራዊ የማድረግ ኃላፊነት አለበት፡፡
በትክክል ሥራ ላይ መዋሉን የመቆጣጠር ኃላፊነት የድርጅቱ የሥራ አመራር እና
የሰራተኛ ማህበሩ ይሆናሉ፡፡
33.1.2 በዚህ የህብረት ስምምነት የተመለከቱ መብትና ግዴታዎች ላልተወሰነ ጊዜ (ቋሚ) እና
ለተወሰነ ጊዜ/ ስራ (ኮንትራት) ሠራተኞች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
68
33.3 ተደራዳሪ ወገኖች
በድርጅቱ በኩል
ሙሉ ስም ሀላፊነት ፊርማ ቀን
1. ----------------------------- ----------------------------- ------------------ -------------
2. ----------------------------- ----------------------------- ------------------ -------------
3. ----------------------------- ----------------------------- ------------------ -------------
69