Aserina Serateja
Aserina Serateja
በዚህ ህብረት ስምምነት መሠረት የተጠባባቂ አበል የሚሰጠው ለደረጃ አሥርና ከዚያ
በላይ ላሉ የስራ መደቦች ይሆናል፡፡
21.4. በተጠባባቂነት የሚሠራውን ሠራተኛ ከ 6 ወር በላይ ማሠራት አይቻልም፡፡
የተመደበው ሰው ለቦታው ብቁ ከሆነ በቀጥታ ቦታው ይሰጠዋል ብቁ ካልሆነ በ 6 ወር ጊዜ ውስጥ
ቦታው በውድድር ወይም በምደባ መሟላት ይኖርበታል፡፡
አንቀጽ 22
የሥራ አፈጻጸም ምዘና
22.1. የሥራ አፈጻጸም ምዘና ሠራተኛው የተመደበበትን የሥራ መደብ እንዲያከናውን
በተሰጠው የሥራ ዝርዝር መሠረት የአእምሮና የአካል ብቃቱን በመጠቀም የተሰጠውን ሥራ
በአጥጋቢ ሁኔታ ማከናወኑን ለማወቅ የሚደረግ ግምገማ ነው፡፡
22.2. የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ውጤት ከዚህ ለሚከተሉት ዓላማዎች ይረዳል፡-
ሀ. አጥጋቢ የሥራ አፈጻጸም ያገኘን ሠራተኛ ወደ ሚቀጥለው የሥራ ደረጃ ለማሳደግ፣
22.3. እያንዳንዱ ሠራተኛ የሥራ አፈጻጸሙን እንዲያየውና እንዲፈርም ይደረጋል፣ የስራ አፈጻጸም
ምዘናው በዓመት አንድ ጊዜ ይደረጋል፡፡
22.4. በሥራ አፈጻጸሙ ከአምስት ነጥብ 2.5 በታች ያመጣ ሠራተኛ ለዕድገትና ለተለያዩ
ጥቅማ ጥቅሞች ተካፋይ አይሆንም፡፡
ክፍል አምስት
ትምህርት ስልጠና
አንቀጽ 23
ትምህርት
23.1. ሠራተኛው ለድርጅቱ የተሻለ ሥራና እድገት እራሱን ለማዘጋጀት በትርፍ ጊዜው
ለመማር ሲጠይቅ አሠሪው የሙያ ምክር ይሰጣል፡፡ ለሚማርበት ትምህርት ቤትም የትብብር
ደብዳቤ ይጽፍለታል፡፡
23.2. ድርጅቱ ለሥራው አስፈላጊ ነው ብሎ ካመነ ከፍሎ ሊያስተምር ይችላል፡፡
23.3. አንድ ሠራተኛ በእርሻዉወጪ ከተማረ ትምህርት እንዳጠናቀቀ በቀጣይ ሁለት ዓመት
እርሻውን የማገልገል ግዴታ አለበት፡፡
23.4. አንድ ሠራተኛ ሁለት ዓመት ሳያገለግል ቢወጣ ከተማረ በኋላ ያገለገለበት ጊዜ
በንጽጽር (Proportion) ተሰለልቶ የተማረበትን ሂሳብ እንዲከፍል ይደረጋል፡፡ ይህም
ከሚያገኘው ማንኛውም ክፍያ ይቀነሳል፡፡ ሆኖ ሲገኝ ሠራተኛው ከራሱ ቀሪውን ክፍያ
ይከፍላል፡፡ ይህ ካልሆነም ሠራተኛ ውል የገባበትን ጊዜ የማገልገል ግዴታ አለበት፡፡
23.5. ለቋሚ ሠራተኞች ለብሔራዊ ፈታናዎች በግል ተምረው ለሚፈተኑ ሠራተኞች በሚያቀርቡት
ማስረጃ ለአንድ ጊዜ የ 3 ቀን ደመወዝ የሚከፈልበት ፈቃድ ይሰጣቸዋል፡፡
አንቀጽ 24
ስልጠና
24.1. ድርጅቱ ለሥራው ይጠቅመኛል ብሎ ካመነ ለሠራተኛው ወጪውን ሸፍኖ የስልጠና ዕድል
ሊሰጥ ይችላል፡፡
24.2. የድርጅቱ ሠራተኛ በማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ወይም በሠራተኛ ማህበር ፌዴሬሽንና
ኮንፌዴሬሽን በሚያዘጋጀው የሙያ ትምህርት ፕሮግራሞችና ስብሰባዎች ላይ ተካፋይ
እንዲሆን በሚጠየቅበት ጊዜ ሥራን በማይበድል ሁኔታ ድርጅቱ ከክፍያ ጋር ፍቃድ በመስጠት
ይተባበራል፡፡
24.3. ድርጅቱ አንድን ሠራተኛ ለሥልጠና ወደ ውጭ ሀገር ሲልክ የመጀመሪያ 6 ወር ሙሉ
ደመወዙን ለተወካዩ ይከፍላል ወይም በባንክ ያስቀምጣለታል፡፡
ክፍል ስድስት
የሥነ ሥርዓት እርምጃ አወሳሰድና የቅሬታ አቀራረብ ሥነ ሥርዓት
አንቀጽ 25
የሥነ ሥርዓት እርምጃ አወሳሰድ
25.1. በሠራተኛው ላይ የሚወሰድ የሥነ ሥርዓት እርምጃ ሆን ተብሎ ሠራተኛን ለመጉት
የታለመ መሆን የለበትም፡፡
25.2. በዚህ ህብረት ስምምነት መሠረት አንድ ሠራተኛ በጥፋቱ ሲቀጣ የቅጣቱ ወረቀት
ለሠራተኛው መድረስ አለበት፡፡
25.3. የቅጣቱና የማስጠንቀቂያ ዕድሜ ለአንድ ዓመት ይሆናል፡፡ ከዚያ በኋላ ግን ቅጣቱም
ሆነ ማስጠንቀቂያው በግል ማህደር የሚቀመጥ ሆኖ በበጀት ዓመቱ በሚያጠፋው ጥፋት እንደገና
በአዲስ ይጀመራል፡፡ ሆኖም የሠራተኛው የቀድሞ ጥፋቶች በዕድገት ውድድር እንደ አንድ
መመዘኛ ነጥብ ሊወሰድ ይችላል፡፡ /የሁለት ተከታታይ ዓመት ቅጣት በውድድር ወቅት
በመመዘኛነት ይወሰዳል/፡፡
25.4. ማንኛውም ሠራተኛ መከለሉን ሳያውቅ ወይም ሳይሰማ የሥነ ሥርዓት እርምጃ (ቅጣት) ሊወሰድበት
አይችልም፡፡
25.5. ኃላፊው የሥነ ሥርዓት እርምጃ ከመውለዱ በፊት ሠራተኛው በትክክል ማጥፋቱን
ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡
25.6. ማንኛውም ሠራተኛ ከመምሪያው ሥራ ጋር በተያያዘ ጥፋት መፈፀሙን የቅርብ አለቃው
የጥፋቱን ዝርዝር በመግለጽ ፈርሞ ለአስተዳደር ይልካል፡፡ የአስተዳደር ሠራተኛውም
በዚህ ህብረት ስምምነትና በአዋጅ 377/96 የተመለከቱትን የሥነ ስርዓት እርምጃዎች
ይወስዳል፡፡
25.7. በእርሻዉቅጥር ግቢ ያለፈቃድ የ 2 ቀን የ 4 ቀን የ 5 ቀን 1/3 የወር ከሥራ
ለሚፈፀሙ አጠቃላይ ጥፋቶችና የሥነ ወይም ያለበቂ ደመወዝ ደመወዝ ደመወዝ ደመወዝ ስንብት
ሥርዓት ጉድለቶች ለአስተዳደር ምክንያት
ከሠራ 3 ቀን
በተከታታይ
የቀረ
5. ያለፈቃድ ወይም የ 3 ቀን የ 5 ቀን የ 6 ቀን 1/3 የወር ከሥራ
ያለበቂ ምክንያት ደመወዝ ደመወዝ ደመወዝ ደመወዝ ስንብት
ከሥራ 4 ቀን
በተከታታይ የቀረ
6. ያለፈቃድ የ 10 ቀን የ 15 ቀን የአንድ ከሥራ
ሰዓቱን ደመወዝ ደመወዝ ወር ዕገዳ ስንብት
አስሞልቶ
ሥራውን ትቶ
ከእርሻው
ቅጥር ግቢ ውጭ
የሄደ
7. ያለፈቃድ የጽሁፍ የ 1 ቀን የ 2 ቀን የ 3 ቀን የ 5 ቀን ከሥር
ወይም ያለበቂ ማስጠንቀቂያ ደመወዝ ደመወዝ ደመወዝ ደመወዝ ስንብት
ምክንያት
ከሥራ ሰዓት
ከ 20-30
ደቂቃ ዘግይቶ
የገባ ወይም
ቀድሞ የወጣ
8. በሥራ ሰዓት የጽሁፍ የ 1 ቀን የ 2 ቀን የ 5 ቀን ከሥራ
እንዲጠቀምበት ማስጠንቀቂያ ደመወዝ ደመወዝ ደመወዝ ስንብት
የተሰጠውን
የሥራ ልብስና
የአደጋ
መከላከያ
አድርጎ
የማይሰራ
ሰራተኛ
9. በሥራ ላይ ሆኖ የ 2 ቀን የ 3 ቀን የ 5 ቀን ከስራ
ለበላዮቹ ደመወዝ ደመወዝ ደመወዝ ስንብት
ወይም
ለበታቾቹ
ህገወጥ ፀባይ
የሚያሳይ
ሰራተኛ
10. በመጠጥ ወይም የ 5 ቀን የ 10 ቀን የ 15 ቀን ከሥራ
በአደንዛዥ ደመወዝ ደመወዝ ደመወዝ ስንብት
ዕፅ ተመርዞ
ወደ ሥራ የገባ
ሠራተኛ ወደ
ቤት
እንዲመለሰ
ሆኖ
11. በአዋጅ ቁጥር የ 2 ቀን የ 3 ቀን የ 5 ቀን 1/3 የወር ከሥራ
377/96 ደመወዝ ደመወዝ ደመወዝ ደመወዝ ስንብት
መሠረት ትርፍ
ሰዓት
እንዲሠራ
ታዝዞ
ከተስማማ
በኋላ ያለበቂ
ምክንያት
የቀረ ወይም
አልሰራም ያለ
ሰራተኛ
ኃላፊው አሳውቆ ነፃ ፍቃድ ካልተሞላበት በአንቀጽ 29.4 መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
አንቀጽ 30
ቅጣትን ስለማሻሻል
30.1.ድርጅቱ ስለተወሰደው የሥነ ሥርዓት እርምጃ አጥጋቢና በቂ ነው ብሎ ካላመነ
በሠራተኛው ላይ ተወሰደውን የሥነ ሥርዓት እርምጃ የማቅለል ወይም የመሠረዝ መብት
አለው፡፡
ክፍል ሰባት
ስለ ሥራ ስንብት ክፍያና ካሳ
አንቀጽ 31
የሥራ ስንብት ክፍያ የሚሰጥበት ሁኔታ
31.1. የሙከራ ጊዜውን የጨረሰና በአዋጅ ቁጥር 377/96 እና በማሻሻያ አዋጅ ቁጥር
494/98 መሠረት የስራ ውሉ የተቋረጠ ሠራተኛ በአዋጁ መሠረት የሥራ ስንብት ክፍያ
የማግኘት መብት አለው፡፡
31.2. አንድ ሠራተኛ የሥራ ስንብት ክፍያ ከማግኘቱ በፊት ቢሞት የሥራ ስንብት ክፍያ
በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 110/2 ለተመለከቱት ጥገኞች ይከፈላል፡፡
አንቀጽ 32
የስራ ስንብት ክፍያ መጠን
ሀ/ ለመጀመሪያ የአንድ ዓመት አገልግሎት የሠራተኛው የመጨረሻው ሳምንት አማካይ የቀን
ደመወዙን በሰላሳ ተባዝቶ ይከፈለዋል፡፡ ከአንድ ዓመት በታች ያገለገለ ሠራተኛ ግን እንደ
አገልግሎት ጊዜው በንጽጽር እየተተመነ ተሠርቶ ይከፈለዋል፡፡
ለ/ ከአንድ ዓመት በላይ ያገለገለ ሠራተኛ በአንቀጽ 32.ሀ በተጠቀሰው ክፍያ ለእያንዳንዱ
ተጨማሪ የአገልግሎት ዓመት የደመወዙ አንድ ሦስተኛ (1/3) እየታከለ ይከፈለዋል፡፡ ሆኖም
ጠቅላላ ክፍያው ከአስራ ሁለት ወራት ደመወዙ መብለጥ የለበትም፡፡
ሐ/ በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 24/4 እና አንቀጽ 29 መሠረት የሥራ ውል ሊቋረጥ በዚህ
ህ/ስምምነት አንቀጽ 32.ሀ እና ለ ከተመለከተው በተጨማሪ የሠራተኛው የመጨረሻ ሳምንት
የቀን ደመወዙ በ 60 ተባዝቶ ይከፈለዋል፡፡
መ/ በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 32 ንዑስ አንቀጽ 1 (አንድ) መሠረት የሥራ ውሉን
የሚያቋርጥ ሠራተኛ በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 40 ከተመለከተው የሥራ ስንብት
በተጨማሪ የመጨረሻ ሣምንት አማካይ የቀን ደመወዝ በ 30 (ሰላሳ) ተባዝቶ ካሳ
ይከፈለዋል፡፡ ይህም አግባብ ባለው ፍ/ቤት ሲወሰን የሚፈጸም ይሆናል፡፡ ይህ ድንጋጌ
አግባብ ባለው የጡረታ ህግ በተሸፈነ ሠራተኛ ላይ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡
አንቀጽ 33
የምስክር ወረቀት አሰጣጥ
33.1 አንድ ሰራተኛ የሥራ ውሉ ሲቋረጥ ክሊራንሱን አዙሮ ከጨረሰና መረጃው እንዲሰጠው
ሲጠይቅ ወይም በሥራ ላይ እያለ የሥራ ልምድ እንዲሰጠው በደብዳቤ ሲጠይቅ የጠየቀው መረጃ
ይጻፍለታል፡፡
33.2. አንድ የሥራ ልምድ ከተጻፈ በኋላ ሁለተኛ የሥራ ልምድ ለማጻፍ ቢያንስ 6 ወር
መቆየት አለበት፡፡
33.3. የምስክር ወረቀት ወይም የሥራ ልምድ የሚከተሉትን ማካተት ይኖርበታል፡፡
ሀ. የሠራተኛውን ሥም ሐ. የሥ ቦታው ሠ. የሚያገኘው ደመወዝ
ለ. የሥራው ዓይነት መ. የአገልግሎት ዘመን ረ. የስራ ግብር መክፈሉን የሚገልጽ
አንቀጽ 34
በሥራ ምክንያት ስለሚመጡ ጉዳቶች ከሳ ክፍያ /ኢንሹራንስ/
34.1. በአዋጅ ቁጥር 377/96 እና በዚህ ህብረት ስምምነት መሠረት በሥራ ላይ የሚደርስ
ጉዳት ማለት በሥራ ላይ የሚደርስ አደጋ ወይም ከሥራ ምክንያት የሚመጣ በሽታ ነው፡፡ ይኸም
ከዚህ የሚከተሉትነን ይጨምራል፡፡
ሀ/ ሠራተኛው ከሥራ ቦታው ወይም ከመደበኛ የሥራ ሰዓት ውጪም ቢሆን የአሰሪውን ትዕዛዝ
ስራ ላይ ያውል በነበረበት ጊዜ የደረሰ ጉዳት፡፡
ለ/ ሠራተኛው ከቤቱ ወደ ስራ ቦታው ወይም ከሥራ ቦታው ወደ ቤቱ ሲጓጓዝ የደረሰ ጉዳት፡፡
ሐ/ ሠራተኛው ሥራውን በማከናወን ላይ እያለ በድርጅቱ ወይም በሌላ ሶስተኛ ወገን ድርጊት
ምክንያት የደረሰበት ጉዳት፡፡
34.2. በሥራ ላይ ለደረሰ ጉዳት የሚሰጠው የካሳ ክፍያ /ኃላፊነት ወሰን/ እርሻው ለዚህ
ጉዳት ከመድህን ድርጅት ጋር በገባው ስምምነት ወይም የመድህን ዋስትና ውል መሠረት ብቻ
ነው፡፡
34.3. በዚሁ መሠረት የኢንሹራንስ መብት ያለው ሠራተኛ ለደረሰበት ጉዳት በ 24 ሰዓት
ውስጥ ለእርሻው ክሊኒክ ወይም በወቅቱ ላለ የሥራ ኃላፊ በማስመዝገብ በቀጣይ ሶስት
ምስክሮችን አስመስክሮ ፈርመውበት ማቅረብ አለበት፡፡ ሠራተኛው በጉዳቱ አማካኝነት
ሪፖርት ማድረግ ካልቻለ ቤተሰቡ ሪፖርት ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በተወሰነው ጊዜ
ያልተመዘገበ ጉዳት ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
34.4. በራሱ ላይ ሆን ብሎ ማንኛውንም ጉዳት ያደረሰ ሰራተኛ እርሻው ኃላፊነት አይኖረውም፡፡ በተለይም
በሚከተሉት ድርጊቶች የሚመጣ ጉዳት በራሱ ላይ ሆን ብሎ ያደረሰ ጉዳት ሆኖ ይቆጠራል፡፡
ሀ. አካሉን ወይም አእምሮውን ለመቆጣጠር በማይችልበት ሁኔታ በአደንዛዥ ዕጾች፣ በመጠጥ
ደንዝዞ በሥራ ላይ መገኘት፣
ለ. በአሰሪው አስቀድሞ የተሰጠውን የሥራ ልብስና የአደጋ መከላከያዎች አለመጠቀምና
የአደጋ መከላከያ ደንቦችንና መመሪያዎችን መጣስ፣
34.5. ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴሩ በሚያወጣው መመሪያ መሰረት በስራ ላይ የሚመጣ
ጉዳት መድረሱን አግባብ ላለው አካል ድርጅቱ ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡
35.6. በድርጅቱ ሠራተኛ ላይ የደረሰው ጉዳት ሞት ወይም የአካል ጉድለት ያስከተለ
ከሆነ ድርጅቱ የኢንሹራንስ ክፍያውን ለማስፈጸም እገዛ ያደርጋል፡፡
ክፍል ስምንት
አንቀጽ 35
የአደጋ መከላከያ የሥራ ልብስ አሰጣጥ
35.1. እርሻው ለሠራተኛው እንደ ሥራው ባህሪ የሚያስፈልገውን የሥራ ልብስና የአደጋ
መከላከያ ይሰጣል፡፡
35.2. ሠራተኛው ለሥራ ተብሎ የተሰጠውን የሥ ልብስ የአደጋ መከላከያ በመደበኛ የሥራ ሰዓቱ ምንጊዜም
ለብሶ መገኘት አለበት፡፡
35.3. በማንኛውም ሁኔታ የሥራ ውሉ የተቋረጠ ሠራተኛ የሥራ ልብስ፣ ጫማ የአደጋ መከላከያ
ቁሳቁስ ወዘተ አይሰጠውም፡፡
35.4. የአደጋ መከላከያና የሥራ ልብስ የሚያስፈልጋቸው
ሀ. የምርትና ቴክኒክ መምሪያ ሠራተኞች በሙሉ
ለ. የጥራት ቁጥጥር አገልግሎት ሠራተኞች በሙሉ
ሐ. ከአስተዳደር መምሪያ የትራንስፖርት፣ የጥበቃ፣ የክሊኒክ፣ የተላላኪና ጽዳት፣ የሰዓት ቁጥጥርና የመዝገብ
ቤት ፐርሶኔክ ክለርክ ሠራተኞች
መ. ከንግድ መምሪያ የንብረት ክምችት ሠራተኞች፣ ጫኝና አውራጅ ሠራተኞች ይሆናሉ፡፡
ሠ. ከፋይናንስ መምሪያ ፔሮል ሠራተኞች ኮስትና በጀት ሠራተኞች የጠቅላላ ሂሳብ ሰራተኞች
35.5. እርሻው በአመት አንድ ጊዜ ለሠራተኞች በሃገር ውስጥ ባለሙያ የተሰፋ ጥራቱን
የጠበቀ ከሃገር ውስጥ ምርቶች ከኮተን ወይም ከፖሊስተር ኮተን የተሰራ የሥራ ልብስ ወር
በገባ በሐምሌ ወር የመስጠት ግዴታ ይኖርበታል፡፡
ሀ. በዓመት፣ በሁለት ዓመት፣ በሶስት እና በአራት ዓመት ለሚታደሱ ሠራተኞች የአደጋ
መከላከያ መገልገያዎች በሐምሌ ወር የሚታደል ይሆናል፡፡
ለ. ለወንድ ሠራተኞች ቱታ፣
ሐ. ለፈረቃ መሪዎች፣ ሱፐርቫይዘሮች፣ ፎርማኖች እና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ጋዋን፣
መ. ለጥበቃ ሠራተኞችና ለሹፌሮች ድርጅቱ በመረጠው ኮትና ሱሪ አስለክቶና አሰፍቶ
እንዲሁም ሸሚዝና ቆዳ ጫማ፣ ለጥበቃ ሠራተኞች ከዚህ በተጨማሪ አርማ ያለበት ኮፍያ
እንዲሁም የዝናብ ልብስ በ 3 ዓመት አንድ፣ ካፖርት ከብርድ መከላከል የሚያስችል በ 4
ዓመት አንድ እና የባትሪ ቀፎ በዓመት አንድ ጊዜ፣ ባትሪ ድንጋይ በዓመት 4 ጊዜ የባትሪ ቀፎ
በዓመት አንድ ጊዜ ለምርት ፈረቃ መሪ ይሰጣል፣
ሠ. ለቢሮና ለእርሻው ሽንት ቤት ጽዳት ሠራተኞች ቆዳ ጫማና ለወንዶች ቱታ ለሴቶች ቀሚስና
ፕላስቲክ ጓንት ይሰጣል፣
ረ. የቦይለር፣ የንብረት አስተዳደር ሠራተኛ፣ መካኒካል ወርክሾፕ፣ ኤልክትሪክ፣ እሣት
አደጋና የጥገና ክፍል ሠራተኞችን በተመለከተ በሠራተኛና በማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር
ጥናት መሠረት ይሰጣል፡፡ ወደፊትም በጥናት ሚኒስቴሩ ለሚፈቅደው የሥራ መደቦች በጥናቱ
መሠረት ይፈፀማል፡፡
ክፍል ዘጠኝ
አንቀጽ 36
ህክምና
36.1. እርሻው ሠራተኛው ከደረሰበት ህመም ወይም በሽታ እንዲፈወስ በመጀመሪያ በግቢው
ውስጥ ባለው ክሊኒክ ህክምና ይሰጣል፣
36.2. በሽታው ወደ ከፍተኛ ምርመራና ህክምና ሄዶ መታከም እንዳለበት በድርጅቱ ክሊኒክ
ባለሙያ ሲረጋገጥ ድርጅቱ ሥምምነት ከአደረገባቸው የመንግስት ሆስፒታሎችና ጤና
ጣቢያዎች ሄዶ እንዲታከም ይደረጋል፡፡
36.3. ማንኛውም ሠራተኛ በዓመት ዕረፍት ፍቃድ ላይ እና በሌሎች የዕረፍት ቀናት በድንገት
ቢታመም እንዲሁም ሴት ሠራተኛ ምጥ ይዟት ወደ እርሻው ለመምጣት ባትችል በመንግስት ሆስፒታል ወይም
ጤና ጣቢያዎች በአንዱ ታክመው ወይም ወልደው ደረሰኝ ሲያቀርቡ ይከፍላል፡፡
36.4. ሠራተኛው እንዲታከም የተላከበት ጤና ጣቢያ ወይም ሆስፒታል በሃገር ውስጥ በሚገኙ
ሌሎች የመንግስት ጤና ጣቢያዎች ወይም ሆስፒታሎች ሄዶ እንዲታከም ማስረጃ ቢሰጠው እርሻው
ያሣክማል፡፡ ይህም የኤክስሬይ፣ የላብራቶሪ፣ የአልትራሣውንድ የመሳሰሉትን
ያጠቃልላል፡፡ ሆኖም ያለሃኪም ፍቃድ ሠራተኛ በመረጠው የህክምና ማዕከል ሄዶ መታከም
አይችልም፡፡
36.5. ራቅ ወዳለ አካባቢ በዓመት ዕረፍት በመሣሰሉት ፈቃዶች ሄዶ በህክምና ላይ እያለ
ቢሞት በመንግስት ሆስፒታል ወይም ጤና ጣቢያ ለህክምና ያወጣውን ወጪ ህጋዊ ወራሾች በጠየቁ
ጊዜ አሰሪው በደረሰኙ መሠረት አረጋግጦ ይከፍላል፡፡
36.6. ሠራተኛው ታሞ ሆስፒታል የተኛ እንደሆነ የ 3 ኛ ማዕረግ ወጪን እርሻው ይሸፍናል
ሶስተኛ ማዕረግ ከሞላ /ከሌለ/ በሁለተኛ ማዕረግ እንዲታከም ይደረጋል፡፡ የሶስተኛ
ማዕረግ እያለ ሠራተኛው ፈልጎ በሌላ ማዕረግ የተኛ እንደሆነ የማዕረጉን ወጪ ልዩነት
ሠራተኛው ይሸፈናል፡፡ ሆኖም በሽተኛው በተላከበት ሆስፒታል የ 3 ኛ ማዕረግ ካልተገኘ የበሽታው
ሁኔታ ጊዜ የማይሰጥ መሆኑ በሃኪም ከተረጋገጠ 3 ኛ ማዕረግ እስኪገኝ በተገኘው ማዕረግ ተኝቶ ይታከማል፡፡
36.7. ለሕክምና ወጪ ድርጅቱ 60% ሠራተኛው 40% ይሸፍናሉ፡፡ ይህም የአደጋ ሕክምናን
አያካትትም፡፡
36.8. የድርጅቱ ጊዜአዊ ሠራተኞች የመጀመሪያ ደረጃ የድንገተኛ ህክምና 60% ድርጅቱ
40% ሠራተኛው ይሸፍናሉ፡፡
36.9. በድርጅቱ ውስጥ በሥራ ላይ እያለ ድንገተኛ አደጋ ወይም ህመም ሲደርስና በሌሊት ወደ
ሌላ ሆስፒታል ሪፈር ለሚባል ሠራተኛ በደረሰኝ የሚወራረድ በክሊኒኩ ብር 500.00 /አምስት
መቶ/ የሚሆን ገንዘብ እንዲቀመጥ ይደረጋል፡፡
አንቀጽ 37
የህክምና አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት
37.1. የእርሻው ክሊኒክ ለህክምና አገልግሎት 24 ሰዓት ክፍት ይሆናል፣
37.2. የህክምና ወይም የምርመራ አገልግሎት ሠራተኛው የሚያገኝበትን ዕለትና ሰዓት
የእርሻው ክሊኒክ ፕሮግራም ይወጣል፣
37.3. ክሊኒኩ ባወጣው ፕሮግራም ተራ በመያዝ ካርዳቸውን አስወጥተው በሥነ ሥርዓት ክሊኒኩ
ባወጣው ፕሮግራም መሠረት ተራ በመያዝ ካርዳቸውን አስወጥተው በሥነ ሥርዓት ወደ ሃኪም ይቀርባሉ፡፡ ሆኖም
በሥራ ላይ አጣዳፊ ህመምና አደጋ ለደረሰባቸው ሠራተኞች ቅድሚያ ይሰጣል፡፡
37.4. በድንገተኛ ህመም ለህክምና ከሥራው ላይ ወደ ክሊኒክ የመጣ ሠራተኛ ህክምናውን
እንደፈጸመ የክሊኒኩ ባለሙያ ሰዓቱን በቅጹ ላይ ሞልቶና ፈርሞ ለሠራተኛው ይሰጣል፡፡
ሠራተኛውም ወዲያውኑ ወደ ሥራ ተመልሶ ቅጹን ለቅርብ አለቃው ያስረክባል፡፡ ለአፈጻጸም
የሚያመች ቅጽ ክሊኒኩ አዘጋጅቶ ሥራ ላይ ያውላል፡፡
37.5. ክሊኒኩ ለሠራተኛው የህመም ፈቃድ ሲሰጥ በዕለቱ ለክፍሉ ኃላፊና ለሰዓት ቁጥጥር
ያሳውቃል፡፡
37.6. ሠራተኛው በሥራ ላይ እያለ ከሥራ የመነጨ አደጋ ቢደርስበት ለከፍተኛ ህክምና ወደ
ሆስፒታል ለማድረስ እና መመለስ የማይችል ከሆነ ለመመለሻ ትራንስፖርት አገልግሎት
ይሰጣል፡፡
37.7. የእርሻው ክሊኒክ በክሊኒክ ደረጃ በክምችት ሊኖረው የሚገባውን መድሃኒት ገዝቶ
ይይዛል፡፡ ታማሚው ሠራተኛ ሃኪም ያዘዘለትን የመድሃኒት ማዘዣ በማምጣት መድሃኒቱ
በክሊኒኩ ካለ ይወስዳል፡፡ መድሃኒቱ በክሊኒክ ከሌለ ከመንግስት መድሃኒት ቤቶች
መድሃኒቱን ገዝቶ እንዲጠቀም ይደረጋል፡፡ መድሃኒቱ በመንግስት መድሃኒት ቤቶች
አለመኖሩ በህክምና ባለሙ ከተረጋገጠ ወይም ክሊኒኩ ከሌላ ቦታ እንዲገዛ ሊፈቅድ
ከማንኛውም መድሃኒት ቤት ሊገዛ ይችላል፡፡
37.8. በሥራ ላይ በደረሰ ጉዳት ሙሉ ህክምና ይሰጣል፡፡ የጉዳት ካሣ የሚያሰጥ ከሆነ
በህክምና ቦርድ ሲረጋገጥ እርሻው በኢንሹራንስ ድርጅት ጋር በገባው ውል መሠረት የጉዳት
ካሳ ክፍያ ይከፍላል፡፡
37.9. በሥራ ላይ ወይም በሥራ ምክንያት ለደረሰ ጉዳት ሠራተኛው በህክምና ላይ
ለሚያጠፋቸው ጊዜያቶች እርሻው የሚከተለውን ክፍያ በደመወዝ ፋንታ ይከፍላል፣
ሀ. ለመጀመሪያው ሶስት ወራት የወር ደመወዙን 100%
ለ. ለሚቀጥለው ሶስት ወራት የወር ደመወዙን 75%
ሐ. ለሚቀጥሉት 6 ወራት የደመወዙን 50% ይከፍላል፡፡
37.10. በአንቀጽ 37.9 ሥር የተጠቀሰው ክፍያ ከዚህ በሚከተሉት ምክንያቶች በማንኛውም
ዕለት ያቆማል፡፡
ሀ. ሠራተኛው የደረሰበት ጊዜያዊ ጉዳት የተወገደለት መሆኑ በሃኪም ሲረጋገጥ
ለ. ሰራተኛው ሥራ መሥራት ካልቻለ ጡረታ ወይም ዳረጎት ማግኘት ከጀመረበት ቀን ጀምሮ
ሐ. ሠራተኛው ሥራ መሥራት ካቆመበት ቀን ጀምሮ 12 ወራት ሲሞላው፡፡
37.11. አንድ ሠራተኛ በሥራ ምክንያት በደረሰበት አደጋ ወይም ህመም ተገቢው ህክምና
ተደርጎለት እስከ መጨረሻው የማይድን መሆ ወይመ ለተቀጠረበት ሥራ ብቁ ያለመሆኑ በሐኪሞች
ቦርድ ሲረገጋገጥ የሚገባው ተከፍሎት ከሥራው ይሰናበታል፡፡
ክፍል አስር
አንቀጽ 38
የትራንስፖርት አገልግሎት
38.1. ድርጅቱ ለሥራ መግቢያ መውጪያ በተወሰነው ሰዓት ለሠራተኛው የትራንስፖርት
አገልግሎት ይሰጣል፡፡
38.2. የእርሻው ሰርቪስ መበላሸቱ በአስተዳደር መምሪያ ተረጋግጦ በማስታወቂያና
በተለያየ መልኩ ሲገለጽ ሠራተኛው ወደ ሥራ ቦታ ለመምጣትም ሆነ ከሥራ ቦታ ወደ ቤቱ ለመሄድ
ለ 3 ቀን የመተባበር ግዴታ አለበት፡፡
38.3. እርሻው የተበላሸውን የሰርቪስ መኪና በተቻለ መጠን አስጠግኖ አገልግሎት እንዲሰጥ
የማድረግ ግዴታ አለበት፡፡ ሆኖም በ 3 ቀን ውስጥ ትራንስፖርት የሚያቀርብ ከሆነ
የትራንስፖርት ወጪውን በታክሲ ታሪፍ ዋጋ ድረጅቱ ይከፍላል፡፡
38.4. የትራንስፖርት ሰርቪስ ያለ ማስታወቂያ ቢቋረጥ ሠራተኛው ለ 1፡30 ሰዓት ላልበለጠ
ጊዜ ቢያረፍድ ደመወዙ ይታሰብለታል፡፡ ሆኖም ከምሽቱ 6 ሰዓት የሚገቡ ሠራተኞችን
አይመለከትም፡፡
38.5. ከተለመደው ፊርማታ ውጪ አዲስ ፊርማታ ለመፍጠር ካልፈለገ ድርጅቱና ማህበሩ
በሚስማሙት መሠረት ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
39.6. የትራንስፖርት አገልግሎት መሣፈሪያና መውረጃ ቦታዎች ከዚህ የሚከተሉት ይሆናሉ፡፡
ዊንጌት ሳሪስ
ጳውሎስ ጎተራ
ኮልፌ መገናኛ ጎፋ
አየር ጤና ጊዮርጊስ ገነት ሆቴል
መካኒሣ
38.7. የሽሮ ሜዳና የሰሜን ገበያ ፊርማታዎች በዚህ የህብረት ስምምነት እንዲታጠፍ
የተደረገ ሲሆን የዚህ መስመር ቋሚ ሠራተኞች የትራንስፖርት ክፍያ በከተማ ታክሲ ታሪፍ
መሰረት ድርጅቱ ይከፍላል፡፡
38.8. ቁጥራቸው አነስተኛ ሲሆኑ ሠራተኞች ሲባል ሰርቪሱን ረዥም መንገድ የሚያስኬድ ሆኖ
ሲገኝ ሰራተኞቹ በታክሲ እንዲመጡ ወይም እንዲሄዱ ሆኖ የትራንስፖርት ወጪውን በከተማው
ታክሲ ታሪፍ መሠረት ድርጅቱ ይከፍላል፡፡
ክፍል አስራ አንድ
ደመወዝና ልዩ ልዩ ክፍያዎች
አንቀጽ 39
የደመወዝ አወሣሠን
39.1. የሠራተኛው የደመወዝ መነሻ መጠን የሚወስነው በእርሻዉ የደመወዝ ስኬል ወይም
በቅጥር ውል፣ ወይም በህግ መሠረት ይሆናል፣
39.2. ድርጅቱ ትክክለኛና አንድ ዓይነት የደመወዝ ስሌት ለማስፈን የማንኛውም ሠራተኛ
የአንድ ወር ደመወዝ በ 26 የሥራ ቀን ላይ ተመሥርቶ የሚሰራ ይሆናል፡፡
39.3. በዚህ ህ/ስምምነት አፈጻጸም የሚከተሉት ክፍያዎች አንደ ደመወዝ አይቆጠሩም፡፡
የትርፍ ሰዓት፣ ልዩ ልዩ አበሎች፣ ዓመታዊ ጎርሻ፣ የተወካይ ወይም የተተኪነት አበል፣
የማበረታቻ ክፍያ እና የጉድለት ማሟያ፡፡
አንቀጽ 40
የደመወዝ አከፋፈል ደንብ
40.1. ድርጅቱ ደመወዝ የሚከፈለው እ.ኤ.አ ወር በገባ በ 28 ኛው ቀን ሲሆን ይህ ቀን እሁድ
ቀን ወይም በሕዝባዊ በዓል ቀን ከዋለ የመክፈያ ቀን አስቀድሞ በዋለው ቀን ይሆናል፡፡
40.2. በአንዳንድ ልዩ ልዩ ምክንያቶች የሠራተኛው ደመወዝ አስቀድሞ እንዲከፈል አስፈላጊ
መሆኑ ማህበሩ በጽሑፍ ሲጠይቅና ማኔጅመንቱ ሲያምንበት ከተወሰነው የመክፈያ ጊዜ በፊት
የሠራተኛውን ደመወዝ ሲከፍል ይችላል፡፡
40.3. ደመወዝ የሚከፈለው በቀጥታ ለሠራተኛው ሆኖ በልዩ ልዩ አስገዳጅ ምክንያቶች ቀርቦ
ደመወዙን መቀበል ካልቻለ ቤተሰቡን ወይም የሥራ ባልደረባውን በጽሁፍ ሲወክል ውክልና
ለተሰጠው ሰው ይከፈላል፡፡
40.4. መተላለፍ የሚገባው ደመወዝ ነክ መረጃ ወይም ሰነድ በቂ ካልሆነ ምክንያት ዘግይቶ
ሲደርስ ሠራተኛው የሠራበትን ደመወዝ የማግኘት መብቱ የተጠበቀ ሆኖ በጥፋተኛው ላይ የሥነ
ሥርዓት እርምጃ ይወስዳል፡፡
40.5. ደመወዝ የሚከፈለው በሥራ ቀንና በእርሻዉቅጥር ግቢ ውስጥ ነው፡፡
40.6. በህግ፣ በፍ/ቤት ትዕዛዝ በዚህ ህብረት ስምምነት ወይም ሠራተኛው ሲስማማ ካልሆነ
በስተቀር አሠሪው ከሠራተኛ ደመወዝ ሲቀንስ ወይም ሊያቻችል አይችልም፡፡ የሚቀነሰው
የገንዘብ መጠንም ከሠራተኛ ደመወዝ 1/3 መብለጥ የለበትም፡፡
40.7. ሠራተኛው ደመወዙን በሚቀበልበት ጊዜ የደመወዙን መጠን የሚገልጽና የተቀናሽ
ደመወዙን የሚያብራራ ሰነድ አሰሪው አዘጋጅቶ ይሰጣል፡፡ በአሠራሩ ቅር ያለው ሠራተኛ ሲገኝ
አሰሪው ማስረዳትና ስህተት መኖሩ ሲረጋገጥ ከሶስት ቀን ባበለጠ ጊዜ ውስጥ አስተካክሎ መክፈል አለበት፡፡
40.8. ሠራተኛው ለመሥራቱ ዝግጁ ሆኖ ሳለ ለሥራው የሚያስፈልገው ጥሬ ዕቃና መሣሪያ
ሳይቀርብለት በመቅረቱ ወይም በሠራተኛው ችግር ባልሆነ ምክንያት ሣይሰራ ቢውል ደመወዙን
የማግት መብት አለው፡፡ ሆኖም ድርጅቱ ሠራተኛውን አስፈላጊ በሆነበት ቦታ ለጊዜው አዛውሮ
ማሠራት ይችላል፡፡
40.9. ሁሉም የድርጅቱ ቋሚና ጊዜአዊ ሠራተኞች ደመወዝ የሚከፈለው ወር በገባ በ 28 ኛው
ቀን አንድ ጊዜ ብቻ ይሆናል፡፡
አንቀጽ 41
የውጤት ክፍያ
41.1. የውጤት ተከፋይ የሚባሉት በውጤት በሚከፈልበት መኪና /ማሽን/ ላይ ተመድበው
ባመረቱት ምርት መጠን ተሰልቶ የሚከፈላቸው ሠራተኞች ናቸው፡፡
41.2. ማንኛውም የውጤት ተከፋይ ሠራተኛ በዓመት ፍቃድ በወሊድ ፍቃድ በአደጋ ፍቃድ
ወዘተ.. የሚከፈለው ክፍያ በሥራ መደቡ በተሰጠው መደበኛ የወር ደመወዝ መሠረት ነው፡፡
41.3. በመደበኛ የውጤት ተከፋይ ሠራተኛ በሚሠራበት መኪና ላይ ተጠባባቂ ሠራተኛ ተመድቦ
ቢሰራ በሥራው ውጤት መሠራት ክፍያ ያገኛል፡፡
41.4. የውጤት ክፍያ ወደፊት እርሻው በሚያወጣው ዝርዝር አሠራር መሠረት የሚፈጸም
ይሆናል፡፡
41.5. አንድ ሠራተኛ በውጤት ክፍያ ሲሰራ የውጤት ክፍያው ከደመወዙ በታች ከሆነ በውጤቱ
መሠረት ይከፈለዋል፡፡ ይህ የሚሠራው የኢንሴንቲቭ ሲስተም ሲዘረጋ ነው፡፡
አንቀጽ 42
ቦነስ ወይም የደመወዝ ጭማሪ
42.1. ለሠራተኛው የሚሰራው የደመወዝ ጭማሪ የእርሻው ዓመታዊ የምርት ውጤት እንቅስቃሴ
ወጪና ገቢ ተገናዝቦ ከብር 1,000,000.00 /አንድ ሚሊዮን ብር/ ያላነሰ የተጣራ ትርፍ
መገኘቱ ዕውቅና ባለው የውጭ ኦዲተር ሲረጋገጥ የትርፉን 8 የደመወዝ ጭማሪ ለሠራተኛው
ይሰጣል፡፡ አፈጻጸሙም እርሻውና ሠራተኛ ማህበሩ በደረሱበት ስምምነት መሠረት ተፈጻሚ
ይሆናል፡፡
42.2. ቦነስ ወይም የደመወዝ ጭማሪ የሚሰጠው በበጀት ዓመቱ ከ 9 ወር በላይ ለሠራ ሠራተኛ
ነው፡፡
4.2.3. ከአንድ ሚሊዩን በላይ ለሚገኝ የተጣራ ትርፍ ድርጅቱና ማህበሩ በሚደርሱበት
ስምምነት መሠረት ቦነስ ይሰጣል፡፡
አንቀጽ 43
ልዩ ልዩ የአበል ክፍያዎች
43.1. የውሎ አበል ክፍያ፣ ማለት ሠራተኛው ከመደበኛ ሥራ ቦታው ከአዲስ አበባ ከተማ ክልል
ውጭ ወደሆነ ሌላ የሥራ ቦታ ሥራ እንዲያከናውን በእርሻዉሲታዘዝ በሄደበት ቦታ
ለሚያጋጥመው የምግብ የመኝታና ሌሎች ጥቃቅን ወጪዎች እንዲሸፈን የሚደረግ ክፍያ ነው፡፡
43.2. የውሎ አበል ክፍያው የትራንስፖርት ወጪን አይሸፍንም የትራንስፖርት ወጪው
በመንገድ ትራንስፖርት ታሪፍ መሠረት በሚያቀርበው ደረሰኝ/ሪሲት መሠረት የሚወራረድ
ይሆናል፡፡
43.3. እርሻው ለሠራተኛው የውሎ አበል የሚከፍለው ክፍያ ከዚህ እንደሚከተለው ይሆናል፡፡
አንቀጽ 49
የህዝብ በዓላት
አግባብ ባለው ህግ መሠረት የሚከበሩ የሕዝብ በዓላት ከዚህ የሚከተሉት ይሆናሉ፡፡
49.1. በወር ደመወዝ የሚከፈለው ሠራተኛ በህዝብ በዓላት ባለመሥራቱ ምክንያት ከደመወዙ
አይቀነስበትም፡፡
49.2. አንድ የህዝብ በዓል ከሌላ የህዝብ በዓል ጋር ተደርቦ ወይም በአዋጅ ቁጥር 377/96
መሠረት ወይም በማንኛውም ልዩ ህግ በተወሰነ የዕረፍት ቀን ላይ ወይም በዚህ ህ/ስምምነት
በተወሰነው የዕረፍት ቀን ላይ ቢውል ለዚህ ቀን የሠራ ሠራተኛ ክፍያ የሚያደርግበት
በአንዱ የህዝብ በዓል ብቻ ይሆናል፡፡
49.3. የእርሻውን የምርት ሂደት ለመጠበቅ ሲባል በህዝብ በዓል ቀን ማሠራት አስፈላጊ ሆኖ
ሲገኝና በእርሻዉሲታዘዝ ሠራተኛው የመሥራት ግዴታ አለበት፡፡ ይህንንም የእርሻው
አስተዳደር አስቀድሞ በማስታወቂያ ይገልጻል፡፡ ክፍያውም በህዝብ በዓል ክፍያ ስሌት
መሠረት ይፈፀማል፡፡
አንቀጽ 50
የትርፍ ሰዓት ክፍያ የማይከፈልበት ሥራ
ሀ. የውሎ አበል የሚከፈለው ሠራተኛ በውሎ አበል ክፍያ ላይ እያለ፣
ለ. ለሥልጠና የሚላክ ሠራተኛ በሥልጠና ላይ እያለ፣
ሐ. በተተኪነት ወይም በውክልና ላይ ያለ ሠራተኛ፣
ክፍል አስራ ሦስት
ልዩ ልዩ ፈቃዶችን በተመለከተ
አንቀጽ 51
የዓመት እረፍት /ፍቃድ/ መጠን
51.1. የዓመት እርፍት ፍቃድ የሚታሰበው ሰራተኛው የተቀጠረበትን ጊዜ መሠረት በማድረግ
ነው፡፡
51.2. ለመጀመሪያ አንድ ዓመት ያገለገለ ሠራተኛ 14 የሥራ ቀን የዓመት ፍቃድ
ይሰጠዋል፡፡
51.3. ከአንድ ዓመት በላይ ለሆነ አገልግሎት በ 14 ቀን ላይ ለእያንዳንዱ ተጨማሪ ዓመት
አንድ ተጨማሪ ቀን እየታከለ ይሰጣል፡፡
51.4. በዓመት ፍቃድ ላይ የሚገኝ ሰራተኛ የሚከፈለው ደመወዝ ሥራ ላይ ኖሮ ከሚከፈለው ጋር
እኩል ይሆናል፡፡
51.5. ለዓመት ፍቃድ ብቁ የሚያደርገው ቀን ለመወሰን ሲባል በድርጅቱ ለ 26 የሥራ ቀናት
የሠራ ሠራተኛ ለአንድ ወር እንደሰራ ይቆጠራል፡፡
51.6. በዚህ ህ/ስምምነትና በአዋጅ ቁጥር 377/96 መሠረት የሥራ ውሉ የተቋረጠ ሠራተኛ
ያልተጠቀመበት የዓመት ፍቃድ ታስቦ በገንዘብ ይከፈለዋል፡፡
51.7. አንድ ሠራተኛ ያገለገለበት ጊዜ ከአንድ ዓመት በታች ከሆነ በአገልግሎት ዘመኑ ልክ
ተመጣጣኝ የሆነ የዓመት ፍቃድ በዚያው በአገከለገለበት ዓመት ይሰጠዋል፡፡
አንቀጽ 52
የዓመት ፍቃድ አሰጣጥ
52.1. አሠሪው የሠራተኛው የዓመት እረፍት የሚወጣበትን ቀን ፕሮግራም በማውጣት
ይወሰናል፡፡ ይህም አሰሪው ሥራውን በተለመደው ሁኔታ ለመሥራት በሚያስችለው እና በተቻለ መጠን
በሠራተኛው ፍላጎት ላይ የተመሠረቱ እንዲሆን ጥረት ያደርጋል፡፡
52.2. እርሻው በሚያወጣው የዓመት እረፍት ፕሮግራም መሠረት በእያንዳንዱ ዓመት
ለሠራተኛው የሚገባውን የዓመት ፍቃድ ይሰጣል፡፡ ሆኖም ሠራተኛው ያልታሰበና አጣዳፊ
ችግር ሲያጋጥመውና ማኔጅመንቱ ሲፈቅድ ካለው እረፍት ላይ ቀንሶ ሊሰጠው ይችላል፡፡
አንቀጽ 53
የዓመት ፍቃድ ስለመከፋፈልና ስለማስተላለፍ
53.1. አንድ ሰራተኛ ሳይከፋፈል የሚሰጥ የዓመት ፍቃድ ከክፍያ ጋር ያገኛል ሆኖም
ሠራተኛው ተከፋፍሎ እንዲሰጠው ሲጠይቅና አሰሪው ሲስማማ ለሁለት ተከፍሎ ወይም አጣዳፊ
ችግር ሲያጋጥም ከ 5 ቀን የማያንስ የዓመት ዕረፍት ሲሰጠው ይችላል፡፡
53.2. አሠሪው የሥራ ሁኔታ ሲያስገድደው የሰራተኛውን የፈቃድ ጊዜ ሲያስተላልፍ
ይችላል፡፡
53.3. አንድ ሠራተኛ በዓመት እረፍት ላይ እያለ የጋብቻ፣ የወሊድ፣ የሃዘን እንዲሁም
የህመም ፍቃድ ቢያገኝ የዓመት እረፍቱ ጊዜ ባገኘው ፍቃድ መጠን ይራዘማል፡፡
53.4. ሠራተኛው የያዘው የሥራ መደብ ተተኪ የሚይገኝለት ከሆነና ጥያቄው በሥራ ክፍሉ
ቀርቦ በሥራ አስኪያጅ ሲፈቀድ የዓመት እረፍቱ ሊራዘም ይችላል፡፡ ሆኖም የዓመት እረፍት
ፍቃድ ከ 2 ዓመት በላይ ሊራዘም አይችልም፡፡
53.4. ሠራተኛው የያዘው የስራ መደብ ተተኪ የማይገኝለት ከሆነና ጥያቄው በሥራ ክፍሉ
ቀርቦ በሥራ አስኪያጅ ሲፈቀድ የዓመት እረፍቱ ሊራዘም ይችላል፡፡ ሆኖም የዓመት እረፍት
ፍቃድ ከ 2 ዓመት በላይ ሊራዘም አይችልም፡፡
53.5. የዓመት ፍቃድን በመከልከል ወደ ገንዘብ ለውጦ መክፈል የተከለከለ ነው፡፡ ሆኖም
ሠራተኛው ሊስማማና አሠሪው ለመክፈል ሲፈቅድ የዓመት ዕረፍቱን በገንዘብ ለውጦ መስጠት
ይቻላል ይህም የሚሆነው የዓመት ዕረፍቱን ወደ ገንዘብ ለመለወጥ የሚያስችል የሥራ ችግር
ሲያጋጥመው፡፡
አንቀጽ 54
በፍቃድ ላይ ያለ ሠራተኛ ስለመጥራት
54.1. በዓመት ፍቃድ ላይ ያለ ሠራተኛ ተጠርቶ እንዲሰራ ሊደረግ በአዋጅ ቁጥር 377/96
አንቀጽ 80 መሠረት ተፈጻሚ ይሆናል፣
አንቀጽ 55
የጋብቻ ፍቃድ
55.1. አንድ ሠራተኛ ለመጀመሪያ ጊዜ ህጋዊ ጋብቻ ሲፈጽም 3 ቀን ደመወዝ የሚከፈልበት 5
ቀን ደመወዝ የማይከፈልበት ነጻ ፍቃድ ያገኛል፡፡
አንቀጽ 56
የሃዘን ፍቃድ
56.1. የሠራተኛው አባት፣ እና፣ ባል፣ ሚስት፣ ልጅ፣ ወንድም፣ እህት፣ የትዳር ጓደኛ
እናት፣ አባት፣ ልጅ፣ ወንድም፣ እህት ሲሞት 3 የሥራ ቀን ደመወዝ የሚከፈልበት ፍቃድ 5
ቀን የማይከፈልበት ነጻ ፍቃድ ያገኛል፡፡ ስለ እርግጠኝነቱ ሠራተኛው ማስረጃ ከዕድር
ወይም ከቀበሌ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ እንዲሁም ዕድር የሌለውና በቀበሌ ያልተመዘገበ
ሠራተኛ ከላይ ከተጠቀሱት ዘመዶች ሲሞትበት ስለመሞቱ በሶስት ምስክሮች ሲረጋገጥ የሃዘን
ፈቃድ ይሰጠዋል፡፡ ይህም በቤተሰቡ ዝርዝር ውስጥ ሲቀጠር ካለመዘገበው ውስጥ ሆነው
ከተገኙ ነው፡፡
56.2. ከሠራተኛው ቤት ከተጠቀሰው ዝምድና ውቺ አስክሬን ቢወጣ 2 ቀን ከክፍያ ጋር ፈቃድ
ያገኛል፡፡
56.3. የእርሻው ቋሚ ሠራተኛ በሞት በሚለይበት ጊዜ ለቀብር ማስፈጸሚያ የሚሆን ብር
3.000 /ሶስት ሺህ/ ለሠራተኛው ቤተሰብ አሰሪው ይከፍላል፡፡ አፈጻጸሙን ማህበር
ተከታትሎ ያስፈጽማል፡፡
56.4. አንድ የእርሻው ቋሚ ሠራተኛ በሞት በሚለይበት ጊዜ በቀብር ስነሥርዓቱ ላይ የሚገኙ
ከ 10 ለማይበልጡ የእርሻው ሠራተኞች የ 2 ሰዓት ደመወዝ የሚከፈልበት ፍቃድ ሥራ
በማይበደልበት ሁኔታ ይሰጣል፡፡ አንድ የማጓጓዣ ሰርቢስም ይመደባል፡፡
አንቀጽ 57
ለማህበር ሥራ የሚሰጥ ፍቃድ
57.1. የሠራተኛ ማህበር መሪዎች የሥራ ክርክር ለማቅረብ፣ የሕብረት ስምምነት
ለመደራደር፣ በማህበር ስብሰባ ለመገኘት፣ ለሴሚናሮችና በስልጠና ለመካፈል እንዲችሉ፣
የማህበሩን ሥራ ለማከናወን ማህበሩ በጽሁፍ ሲጠይቅና ማስረጃ ሲያቀርብ ፍቃድ ከደመወዝ
ጋር ይሰጣል፡፡
57.2. የማህበር የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ ሥራን በማይበድል ሁኔታ በየ 15
ቀን ከ 3-6 ሰዓት ስብሰባ ያደርጋሉ የስብሰባ ቀኑንም በጽሁፍ ያሳውቃሉ፡፡
57.3. የማህበሩ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴና የምክር ቤት አባሎች በገቢ ውስጥ ለመሰብሰብ
ሲፈልጉ ከ 24 ሰዓት በፊት እርሻው በጽሁፍ ሲጠየቁ በ 6 ወር አንድ ጊዜ ደመወዝ
የሚከፈልበት ፍቃድ ይሰጣቸዋል፡፡
አንቀጽ 58
ልዩ ልዩ ተግባሮችን ለማከናወን ለሠራተኛ የሚሰጥ ፍቃድ
58.1. አንድ ሠራተኛ የሥራ ክርክር ለማሰማት፣ ወይም የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ህጎችን
ለማስፈጸም ስልጣን ያላቸው አካሎች ዘንድ ጉዳዩን ለማስማት ሲቀርብ በሚያቀርበው ህጋዊ
ማስረጃ መሠረት ለዚሁ አላማ ላጠፋው ጊዜ ብቻ ከክፍያ ጋር ፍቃድ ይሰጣል፡፡
58.2 አንድ ሠራተኛ የሲቪል መብቱን ሲያስጠብቅ ወይም የሲቪል ግዴታውን ሊፈጽም
በሚያቀርበው ህጋዊ ማስረጃ መሠረት ለዚሁ ዓላማ ላጠፋው ጊዜ ብቻ ከክፍያ ጋር ፍቃድ
ይሰጠዋል፡፡
58.3. ማንኛውም ሠራተኛ ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ሲደርስበትና ይኸውም በአሰሪው
ሲታመንበት የቅርብ አለቃውን ፍቃድ በመጠየቅ ከክፍያ ነፃ የሆነ ፍቃድ ይሰጠዋል፡፡ ሆኖም
ሠራተኛው የዓመት ዕረፍት ካለውና ከዓመት እረፍቱ እንዲታሰብለት አስቀድሞ ከጠየቀና
ይህም በአሰሪው ከታመነበት ወደ ዓመት እረፍት ሊቀየርለት ይችላል፡፡ ይህ የዓመት ዕረፍት
ከአንድ ቀን በታች የሆነ ሰዓታን አይመለከትም፡፡
58.4. የክፍል አለቃው ከ 5 ተከታታይ ቀን በላይ ከክፍያ ነፃ የሆነ ፍቃድ በአንድ ጊዜ
መስጠት አይችልም፡፡ ከዚህ ጊዜ በላይ ነፃ ፍቃድ የሚያሰጥ ችግር ሊያጋጥም ማመልከቻው
በክፍሉ ኃላፊ አስተያየት ተሰጥቶበት ይኸው በአስተዳደር መምሪያ ተቀባይነት ሲያገኝ ነፃ
ፍቃድ ሊፈቀድለት ይችላል፡፡
አንቀጽ 59
የህመም ፈቃድ
59.1. ማንኛውም የእርሻው ቋሚ ሠራተኛ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በተከታታይ ወይም
በተለያየ ጊዜ ከዚህ የሚከተለውን የህመም ፍቃድ ያገኛል፡፡