Professional Documents
Culture Documents
ዝግጅት፡ አደም ጉዬ
ማውጫ .................................................................................................................................. 1
መቅድም ................................................................................................................................. 3
ምእራፍ አንድ.......................................................................................................................... 5
1.እስላማዊ የአምልኮ ተግባራት፤ድንጋጌዎችና ክልከላዎች በሳይንስ መነጽር ...................................... 5
1.1 ሰላት(ስግደት) እና ሳይንስ ............................................................................................................. 5
1.1.1 ሰላት ጭንቀትን በማስወገድ አእምሮን ዘና እንደሚያደርግ በሳይንሳዊ ግኝት መረጋገጡ 5
1.1.2 በግንባር መሬት መንካት (ሱጁድ) የሚያከትለው አስገራሚ ሳይንሳዊ ጠቀሜታው............ 6
1.1.3 ሰላት የደም ግፊት ችግርን ይቀርፋል................................................................................... 8
1.2 እስላማዊ ፆምና ሳይንስ ................................................................................................................. 9
1.2.1 ፆምና ሳይንሳዊ ጠቀሜታው ................................................................................................. 9
1.2.2 የአያመል ቢድ ፆም እና ሳይንስ.......................................................................................... 12
1.3 ኢስላማዊ የእንስሳ አስተራረድ ዘዴ በሳይንስ ሲቃኝ .................................................................. 13
1.4 በተፋታች እና ባሏ በሞተባት ሴት ............................................................................................. 16
1.5 ፂምን ማሰደግ/ማስረዘም በሳይንስ እይታ ................................................................................. 18
1.6 የአሳማ ስጋና ሳይንሳዊ እይታው ................................................................................................ 19
ምእራፍ ሁለት....................................................................................................................... 21
ቅዱስ ቁርኣንና ሳይንስ ............................................................................................................ 21
2.1. ስነ-ፅንስ እና ስነ-አካል ................................................................................................................. 21
2.1.1 የፅንስ ፆታ ........................................................................................................................... 21
2.1.2 የሰው ልጅ ከጥቂት የዘር ፈሳሽ ጠብታ ስለመፈጠሩ ......................................................... 22
2.1.3 የሰው ልጅ አንጎል በቁርኣንና በሳይንስ ............................................................................... 23
2.2 እንስሳት ....................................................................................................................................... 24
2.2.1 ንብ በቁርኣንና በሳይንስ ....................................................................................................... 24
2.2.2 ሸረሪት በቁርኣንና በሳይንስ.................................................................................................. 27
2.2.3 ጉንዳን በቁርኣንና በሳይንስ .................................................................................................. 29
2.2.4 የከብቶች ወተት አመራረት በቁርኣንና በሳይንስ ................................................................. 31
2.3 ስነ -ምድር ................................................................................................................................... 32
2.3.1 የዓለምችን ዝቅተኛ ስፍራ ................................................................................................... 32
1
2.3.2 ብረት(Iron) በቁርኣንና በሳይነስ .......................................................................................... 33
2.4 ውቅያኖግራፊ (የውሃ አካላት ጥናት) ......................................................................................... 34
2.4.1 ሁለት ባህሮች መካከል ያለው ገርዶ................................................................................... 34
2.4.2 ጨለማና መእበል በጥልቅ ውቅያኖስ/ባህር ውስጥ............................................................. 36
2.5 ስነ- ፈለክና ቁርኣን ...................................................................................................................... 37
2.5.1 የፀሐይ መሽከርከር .............................................................................................................. 37
2.5.2 የፀሐይ መጥፋት ................................................................................................................. 38
2.6 ከብናኝ (አቶም) በታች ቁስ አካል ስለመኖሩ በቁርኣንና ሳይንስ ................................................. 38
2.7 የአፅናፉ አለም (Universe) አመጣጥና ህይወት......................................................................... 39
ምእራፍ ሶስት ........................................................................................................................ 41
የነቢዩ(ሰ፡ዐ፡ወ) ንግግሮች እና ተግባራት በሳይንስ እይታ ............................................................... 41
3.1 የጀርባ አጥንት (የጅራት ጎመድ) ................................................................................................ 41
3.2 ዝምብ የሚጠጣ ነገር ውስጥ ቢገባ ............................................................................................. 42
3.3 አልፎ አልፎ በባዶ እግር መሄድ ................................................................................................ 43
3.4 የነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) ወረርሺኝ መከላከያ መንገድ ............................................................................. 43
3.5 ወተት ከተጠጣ በኃላ አፍን በውሃ መጉመጥመጥ .................................................................... 45
ዋቢ መጽሐፍት ..................................................................................................................... 46
2
መቅድም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኘ በሆነው
3
የእስልምና ነገር የጎን ውጋት፤የልብ ፍልጠት የሆነባቸው ሰዎች እስልምናን በተለይም
የእስልምናን የአምልኮ ተግባራት፤ድንጋጌዎች፤ክልከላዎችንና ሌሎችንም ውሃ በማይቋጥር
ስሁት ሙግታቸው ሊያጠለሹ ይሞክራሉ፡፡እውነታው ግን በርካታ ሳይንሳዊ ግኝቶችና
ምርምሮች ከእስልምና የአምልኮ ተግባራት፤ድንጋጌዎች፤ክልከላዎች ጋር ይስማማሉ እንዲሁም
ያበረታታሉ፡፡
ስለዚህ በእስልምና ዙሪያ ብዥታ ያለበት ይህን መጽሐፍ በማንበብ እውነታው ለይ ለመድረስ
የሚያስችለውን የጊዜ ርቀት በጣም ሊያጠብ የችላል፡፡ ሳይደርቅ በእርጥቡ፤ ሳይቃጠል በቅጠል
እንዲሉ ሞት ሳይቀድመን እውነታውን በገለልተኝነት በመረዳት ትክክለኛውን መንገድ እንያዝ፡፡
ልብ ያለው ልብ ይበል!!!
4
ምእራፍ አንድ
1. እስላማዊ የአምልኮ ተግባራት፤ድንጋጌዎችና ክልከላዎች በሳይንስ መነጽር
1.1 ሰላት(ስግደት) እና ሳይንስ
በእስልምና በየቀኑ የሚደረግ ፀሎት በአረብኛ ቋንቋ ሰላት ተብሎ የሚጠራ ሲሆን በአይነቱ
ለየት ያለ አምልኮ ነው። ጸሎት ሲባል አጠቃላይ ልመናን የሚያመለክት ቢሆንም ሰላት ግን
አምላካችን አላህን ለመገዛት የሚደረግ የጸሎት ዓይነት ሆኖ ንግግርንና አካላዊ እንቅስቃሴን
አንድ ለይ ያጣመረ የአምልኮ ተግባር ነው። ይህ የአምልኮ ተግባር በሁሉም ሙስሊሞች ለይ
ግዴታ ሲሆን በእስልምና ሁለተኛ የእምነት ምሶሶ ውስጥ ይመደባል። በቅዱስ ቁርኣን ምእራፍ
4 አንቀጽ 103 እንደተገለጸው ማንኛውም ሙስሊም አምስቱን እለታዊ ሰላት (ስግደት) ወቅቱን
ጠብቆ መፈጸም አለበት።
በ 2014 በማሌዢያ አገር ሰላት ሚያስከትለውን ተጽእኖ ለማወቅ የተደረገ ሳይንሳዊ ምርምር
ነበር፡፡የጥናቱን ግብ ለማሳካት ሲባል 30 ሙስሊም ወጣቶች ለናሙናነት የተወሰዱ ሲሆን
ኤሌከትሮኢንስፓሎግረም (Electroencephalogram) EEG የሚባል የአንጎል እንቅስቃሴ
መለኪያ መሳሪያ የጥናቱን ውጤት ለማወቅ ጥቅም ለይ ውሏል፡፡ ለንጽጽር ያመች ዘንድ
ለናሙና የተመረጡ 30 ዎቹም ሙስሊም ወጣቶች ከሰላት በፊት፣ በሰላት ውስጥና ከሰላት
5
በኃላ በኮምፒወተር ለይ የተመሰረተ የመረጃ ማግኛ ስርኣት ለይ በመመርኮዝ የEEG ምርምራ
ተደረገላቸው። የተገኘውም ውጤት የሚያስደንቅ ነበር።
የተገኘውም ውጤት እንደሚያሳየው በሰላት ወቅት ወይም ደግሞ ሰላት በሚከናወንበት ወቅት
የተመዘገበው የኤሌክትሮይንስፋሎግራፊ (EEG) አንጻራዊ ኃይል (Relative power)
በመካከለኛውና በኃለኛው የአንጎል ክፍል ለይ ከሰላት በፊትና በኃላ ካለው ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ
ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ በሰላት ውስጥ አእምሮዋችን በጭንቀት መወገድ ምክንያት ዘና
እንደሚል ያሳያል፡፡[1]
በሰላት ውስጥ በግንባር መሬት መንካት (ሱጁድ ማድረግ) ልዩ ቦታን ይዟል፡፡ ምንም እንኳን
የሰላት ዋና አላማ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለማድረግ ባይሆንም ለሰው አካል ዘርፈ ብዙ
የህክምና ጠቀሜታዎች እንዳለው ተረጋግጦዋል፡፡ ነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) ኢብኑ ማጃህ በዘገቡት ሀዲስ
ውስጥ ሰላትን አዘውተሮ የሚሰግድ ሰው በተለይም በመስጊድ ዉስጥ የሚሰግድ ሰው ብዙ
ከማያውቋቸው በሽታ እንደሚጠበቅ ተናግሮዋል፡፡ በሰላት ወቅት ግንባርን መሬት ማስነካት
(ሱጁድ ማድረግ) ከእስልምና ፀሎት ጋር ብቻ ተቆራኛ ነው፡፡ ነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) እንዳወሱት
ሙስሊሙ ሰጋጅ ለፈጣሪው በጣም ቅርብ የሚሆነው በዚህ ወቅት ነው፡፡ ኢማሙ ቡኻሪ አቡ
ሁረይራን ጠቅሰው እንደዘገቡት የአላህ መልክተኛ እንዲህ ብለዋል ‘’አንድ ባሪያ ለጌታው በጣም
ቅርብ የሚሆነው በሰላት ውስጥ ግንባሩን መሬት በሚያስነካበት ጊዜ ነው፤ ስለዚህ በዚህ ወቀት
ዱኣ ማድረግን አብዙ’’፡፡እራሳቸው ነቢዩ(ሰ፡ዐ፡ወ) ሱጁድን ያስረዝሙ እንደነበር ተገልጾዋል፡፡[2]
ሳይንቲስቶች እንዳረጋገጡት አሁን ባለንበት ዘመን የሰው ልጅ ከምንም ግዜ በባሰ ሁኔታ
ለኤሌክትሪክ ጨረሮች የተጋለጠ ነው። የዚህ ምክንያት ደግሞ ከሞባይል፤ ከቴሌቪዥን፤
ማይክሮዌቭ እንዲሁም የምንጠቀምባቸው የኤሌክትሮ ማግኔት መሳሪያዎች የሚወጡ
ኤሌክትሮ ማግኔት ጨረሮች አማካኝነት ነው። እነዚህ ጨረሮች በሰው ጤና ለይ በተለይ
በማዕከላዊ ነርቭ ስርዓቶች (Central Nerveous Systems) ለይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳሉ። አንድ
ሰው እነዚህን ጨረሮች እሰካላስወገደ ድረስ ለራስ ምታት፤ለአንገት ህመም፤ለጡንቻ መወዛወዝና
ለመሳሰሉት ጤና ጠንቆች መጋለጡ አይቀሬ የሆነ ሀቅ ነው፡፡
6
ወቅት ደግሞ ከመሬት ጋር ያለን ንኪኪ እየጨመረ ይሄዳል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሰላትን
አዘውትረው የሚያከናውኑ ሰዎች የአዕምሮ ደስታና መዝናናትን እንደሚጎናፀፉ ምንም ጥርጥር
የለውም፡፡[3] ሱብሃነላህ! ሁሌም ከአላህ ትእዛዝ በስተጀርባ ትልቅ ጥበብ አለ፡፡
በሰላት ክንውን ጊዜ የሚደረገው ሱጁድ (በግንባር መሬት መንካት) በሰውነት ውስጥ ባሉ አካል
ክፍሎችና ጡንቻዎች ለይም የራሱ የሆነ ተጽእኖ አለው፡፡ ሱጁድ ማድረግ ለሴቶች መህፀን
በሽታ ጥሩ ሕክምና ነው ተብሎዋል፡፡ ለወንዶችም ጥሩ የሆነ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ነው፡፡
ከሱጁድ በምንነሳበት ወቅት (ግንባራችንን ከመሬት ቀና ስናደርግ) ጡንቻዎቻችን በንቃት
7
ይንቀሳቀሳሉ እንዲሁም ከወንድ ዘር ፍሬ ጋር የተዛማዱ ጡንቻዎችም ይጠነክራሉ፡፡ በሰላት
ወቅት ግንባራችንን መሬት ስናስነካና (ሱጁድ ስናደርግ) ከመሬት ቀና ስናደርግ (ከሱጁድ ስንነሳ)
የሚደረጋው እንቅስቃሴ የጀርባ ጡንቻዎችን መዘርጋትና መኮማተር ስለሚያስከትል
ጡንቻዎቹን ጠንካራ እንዲሆኑ ያደጋቸዋል፡፡ይህ ደግሞ የጀርባ ህመምን ያስወግዳል፡፡ ለዚህም
ነው አዘውትረው ሰላትን የሚያከናውኑ ሰዎች የጀርባ ህመም ብዙም የማይሰማቸው፡፡[2]
በሰላት ወቅት የሚደረገው ሱጁድ ዋናው አላማ አምልኮ ነው እንጂ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ
ለማድረግ አይደለም፡፡ ሆኖም ግን በርካታ ሳይንሳዊ ጥቅሞች እንዳሉት ከለይ በተብራራው
የሱጁድ ጥቅሞች ለይ አይተናል፡፡ ስለዚህ አንድ ሙሰሊም በሰላት ውስጥ ሱጁድ አድርጎ
(ግንባሩን ከመሬት ጋር አገናኘቶ) ሳይነሳ ረጀም ጊዜ በቆየ ቁጥር በርካታ መንፈሳዊና ሳይንሳዊ
ጥቅሞችን እንደሚሸምት እሙንና ቅቡል ነው፡፡ ነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) የሱጁድን ጥቅም ብታውቁ ኖሮ
አስከ የውሙል ቂያማ ወይም እለተ ትንሳኤ ድረስ ከሱ አትነሱም ብለው ነበር፡፡ ሱጁድ ምን
ያህል ጥቅም ቢኖረው ነው ነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) ይህን የተናገሩት፡፡ኢማሙ ቡኻሪ እናታችን ዓኢሻን
(ረ፡ዐ) ጠቅሰው እንደዘገቡት እራሳቸው ረሱል (ሰ፡ዐ፡ወ) አንድ ሰው 50 የቁርኣን አንቀጾችን
የሚቀራውን ያህል ሱጁድን ያስረዝሙ እንደ ነበር ተገልጾዋል፡፡ በሌላ ዘገባ ነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ)
ከእርሶ ጋር በጀነት ውስጥ ጎሮቤት መሆን እፈልጋለው ላላቸው አንድ ወጣት ሱጁድ ማድረግን
አብዛ ብለው ነው የመከሩት፡፡ ስለዚህ ይህ የሰላት ዋናው ክፍል ወይም ቁንጮ የሆነው ሱጁድ
(በግንባር መሬት መንካት) የሁለቱ ዓለም (ምድረዊና ሰማያዊ ዓለም)ስኬት መክፈቻ ቁልፍ ነው
ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ ሰላት ስንሰግድ በፍጥነት ጎንበስ ቀና የምንል ሰዎች ምድራዊም
ሰማያዊም ጥቅም እንዳያመልጠን ይህን ጉዳይ በደምብ ልናጤን ይገባል፡፡
8
1.2 እስላማዊ ፆምና ሳይንስ
1.2.1 ፆምና ሳይንሳዊ ጠቀሜታው
በአውሮፓ ከህዳሴ ዘመን በኃላ የሳይንስ ሊቃውንቶች ሰዎች ምግብን ከመጠን በለይ
እንዳይመገቡ ጥሪ እያደረጉ ይገኛሉ፤ ይልቁንም ከመጠን ያለፈ የምግብ ክምችትን ለመቀነስ
ፆምን ይመክራሉ፡፡ ሆዳምነት ከተንሰራፋ ከወረርሺኝ ወይም ጦርነት የበለጠ ለሞት የሚዳርግ
በሽታ እንደሆነ አፅንኦት ሰጥተው ይናገራሉ፡፡ ስለሆነም ሰውነታችን የሚያስፈልገውን ብቻ
መብላት አለብን፡፡ ሁሉን ቻይና አዋቂ የሆነው አምላካችን አላህ የሰውን ነፍስ ለማፅዳትና
ምግብን ከመጠን በለይ በመመገብ ምክንያት ለሚከሰቱት በሽታዎችና ህመሞች ህክምና ይሆን
9
ዘንድ ፆምን ደንግጓል፡፡ አምላካችን አላህ በቅዱስ ቁርኣን ምእራፍ ሁለት አንቀፅ 184 ለይ
እንዲህ ይላል፡፡[5]
በዚህ አንቀፅ ውስጥ የፆምን ጥቅም ብታውቁ ኖሮ እንደውም ትመርጡታላችሁ እያለን ነው፡፡
የሙስሊሞች ፆም ሳይንሳዊ ጥቅሞች አሁን ባለንበት ዘመን በስፋት እየታወቁ መጥቶዋል፡፡
ከጥቅሞቹ መካከል የተወሰኑት ቀንጨብ ተደርገው እንደሚከተለው ይቀርባሉ፡፡
1. በጾም እና በሰውነት በሽታ የመከላከል ስርዓት መካከል ቁርኝት አለ፡፡ የሰውነት በሽታ
የመከላከል ስርዓት ሰውነቶችን ከብዙ ቫይረሶች እና ከጎጂ ባክቴሪያዎች የሚጠብቅ
የወታደሮች ቡድን ነው፡ በፆም ወቅት የሰውነታችን በሽታ መከላከል አቅሙ እየጨመረ
እንደሚሄድ ሀኪሞች ይናገራሉ። ሳይንሳዊ እውነታዎች እንደሚጠቁሙት ፆምን
ማዘውተር ሊምፍቶድ (lymphocytes) የሚባሉ የነጭ ደም ሴል አይነቶችን በ10 እጥፍ
እንዲጨምሩ ያደርጋል፡፡ እነዚህ ሴሎች ሰውነትን ከሚያጠቁ ጥቃቅን ነፍሳት እና ከውጭ
አካላት የሚከላከሉ የደም ሴሎች ናቸው፡፡ በተጨማሪም በፆም ወቅት ሰውነትን ከተለያዩ
ጥቃት የሚጠብቁ ሴሎች መጠናቸው ብቻ ሳይሆን የጥራት ደረጃቸውም
ይጨምራል፡፡ሰውነትን የሚወር ማንኛንውም ህዋሰትንና እንግዳ አካላትን የሚፋለሙት
የተለያዩ የፀረ እነግዳ አካላት ዓይነቶችም በፆም ወቅት ይጨምራሉ፡፡በሁሉም በሽታዎች
ላይ የሰውነት መቋቋም እየጨመረ በሄደ መጠን ሐኪሞች ጾም በሽታ የመከላከል
ስርዓታችንን እንደሚያነቃ ያረጋግጣሉ፡፡ስለሆነም ጾም ሰውነት ራሱን እንዲከላከል
የሚረዳ ውጤታማ መሳሪያ ነው፡፡[6]
2. በፆምና ከመጠን ያለፈን ውፍረት ለመከላከል በሚደረግ ህክምና መካከል ዝምድና አለ።
ምክንያቱም ውፍረትን ለመከላከል ፆም ሁነኛ የሆነ መፍትሄ ነው። የቅርብ ግዜ
ሳይንቲስቶች ፆም ስብን ለማስወገድ፤ቅባቶችን ለሟሟት እና ሆርሞኖችን ለማደራጀት
እንደሚረዳ ይናገራሉ። ከመጠን በለይ ውፍረት ከአመጋገባችን ችግር፣ከስነ ልቦና እና
ማህበራዊ ጫናዎች ሊመጣ ይችላል። በፆም ምክንያት የሚመጣው የአዕምሮና ስነ ልቦና
መረጋጋት እነዚህ ሁሉ ችግሮች ሊቀረፉ ይችላሉ። በተጨማሪም ፆም ውፍረትን
ተከትሎ የሚመጡትን የደም ግፊት፣ የልብ ህመምንና የመሳሰሉትን በሽታዎች በማከም
ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡[6]
3. ፆም በሰውነት ውስጥ ለተከማቹ መርዞች ፈውስ እንደሆነ ሳይንቲስቶች ያረጋግጣሉ
ምክንያቱም የሰውነት ሴሎችን ከነዚህ መርዞች ለማፅዳት ስለሚረዳ ነው።ከልብ ወለድ
የማይናገሩት ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ፣ዐ፣ወ) ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ ውስጥ ፆም መከላከያ
ነው ብለዋል። ይህ የነቢዩ ንግግር ፆም የብዙ ነገሮች መከላከያ እንደሆነ ይነግረናል ።[7]
ፆም በሰውነት ሴሎች ውስጥ የተከማቹትን መርዛማ ንጥረ- ነገሮች እንዲሁም ደግሞ
በህብረ ህዋሳት መካከል የሚገኙትን መርዛማ ንጥረ ነግሮች ለማስወገድ ይረዳል።እነዚህ
መርዛማ ንጥረ ነገሮች በብዛት የሚመጡት ከታሸጉ ምግቦች፣ ከመድሃኒትና ከተበከለ
አየር ነው።[6]
10
4. የህክምና ባለሙያዎች ከረጅም ህይወት ጀርባ ፆም አንዱ ምክንያት እንደሆነ ይናገራሉ።
ብዙ ሙስሊም ያልሆኑ ሊቃውንቶች ስለ ፆም ልዩ ልዩ ጥቅሞች መፅሐፍን የፃፉ ሲሆን
ብዙ ጊዜ በፆም የሚያሳልፉ ሰዎች ከማይፆሙት አንፃር የበለጠ ረጅም እድሜ አላቸው
የሚል ድምዳሜ ለይ ደርሰዋል፡፡[8]
5. ፆም የወንዶችንም ሆነ የሴቶችን የመራባት ችሎታን ከፍ ያደርጋል። መፆም ብዙን ጊዜ
ተፈጥሮኣዊ የግብረ ስጋ ግንኙነት ፍላጎታችንን ይቀንሳል። ይህ ደግሞ የስነ-ልቦናና
የባህሪ መዛባትን ይከላከላል። የነቢዩ መሐመድ (ሰ፣ዐ፣ወ) ንግግር ለዚህ ማረጋገጫ ነው።
ነቢዩ (ሰ፣ዐ፣ወ) እንዲህ ብለው ነበር ‹‹‹ ወጣቶች ሆይ ከናንተ ማግባት የሚችል ሰው
ጣጣውን ከቻለ ያግባ፣ ማግባት የማይችል ከሆነ ደግሞ ስጋዊ ፍላጎቱን መግታት ይችል
ዘንድ ይፁም ›››።በፆም ወቅት ስሜትን የሚቀሰቅሰው ቴስቴስትሮን የተባለ የወንዱ
ሆርሞን መጠኑ ለብዙ ቀናት ይቀንሳል። ከዚያ በኃላ ከፍተኛ ጭማሪ ያሳያል። በሌላ
አገላለፅ በተከታታይ ቀናት ስንፆም ስጋዊ ፍላጎታችን ይቀንሳል። ስናፈጥር (ፆሙን
ስንፈታ) ስጋዊ ፍላጎታችን ከበፊቱ የበለጠ ስለሚነቃቃ የመራባት አቅምን እንዲጨምር
ያደርጋል፡፡[6]
6. በፆም ወቅት በፆም ወቅት የደከሙና ያረጁ ሴሎች ይሞታሉ። አዳዲስ ሴሎች ደግሞ
መፅደቅ ይጀምራሉ።[6]
ሳይንሳዊ ግኝቶች እስላማዊ ጾም በጣም ቀላል መሆኑን የሚያመለክቱ ሲሆን በፆም ወቅት
ሰውነት ለአሉታዊ ተፅእኖ የማይጋለጥ መሆኑን ጭምር አበክረው ያስረዳሉ።በተቃራኒው ግን
ሰውነት ያለ ጾም ሊያገኙ የማይችሉ ብዙ ጥቅሞችን በፆም ወቅት ያገኛል፡፡ ኢስላማዊ ጾም
ሰውነታችን ላይ በጣም ቀላል ነው። ይህንን በማረጋገጥም ሁሉን ቻይ የሆነው አላህ በቅዱስ
ቁርኣን ምእራፍ ሁለት አንቀፅ 185 ለይ እንዲህ ይላል፡፡
11
ይርቃል። ማታ ደግሞ የመብላትና የመጠጣት ነፃነት አለው። ስለሆነም ጾም የሚያደርገው
አንድ ሰው ምግብና መጠጥ የሚበላበትን ጊዜ መለወጥ እንጂ ሌላ አይደለም። ይህ ደግሞ ጉዳት
አያመጣም። ስለዚህ እስላማዊ ፆም ቀለል ያለ ለሰው ልጅ በሚመች መልኩ በፈጣሪ የተደነገገ
ፆም ነው፡፡ በርካታ ሳይንሳዊ ጥቀሞች እንዳሉትም ሙስሊም ባልሆኑ ሊቃውንት ጭምር
ተረጋግጧል፡፡[6]
1.2.2 የአያመል ቢድ ፆም እና ሳይንስ
ጨረቃ ለፀሐይ በጣም ቅርብ የሆነች የተፈጥሮ ሳታላይት ናት፡፡ ዘመናዊ ስነ ፈለክ ከመምጣቱ
ከረጅም ጊዜ በፊት በበርካታ ጥንታዊ የጥበብ ባለሙያዎችና አፈታሪኮች ስለ ጨረቃ ብዙ ነገር
ተብሎዋል፡፡ የጥንት ሰዎች ጨረቃ በምድር ለይ የሚያሳድረውን ተጽእኖ መገንዘብ ጀምረው
ነበር፡፡ ሆኖም ግን የጨረቃ ሩቅ ክፍል ለረጅም ክፍለ ዘመናት ለጥናት ተደራሽ አልነበረም፡፡
ባለፈው ምዕተ ዓመት ውስጥ ግን የስነ ፈለክና የኮስሞቲክሰ ፈጣን እድገት ተከትሎ በርካታ
በጨረቃ ዙሪያ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ፡፡
እንደ ዘመኑ የስነ ፈለክ ሳይንስ የጨረቃ ዑደት በሰዎች እለት ተዕለት እንቅስቃሴ፤በሰዎች
ባህሪና ጤና ለይ ተፅእኖ ያሳድራል፡፡ በተለይም ጨረቃ ሙሉ (full moon) ሆና በመውጣት
አከባቢውን በደማቅ ብርሃን ስታለብስ ሰዎች በደምብ መተኛት አይችሉም፤ጭንቀትና
ተጋላጭነት በስፋት ይስተዋላል፡፡እንዲሁም በሙሉ ጨረቃ (full moon) ወቅት ሰዎች የችኮላ
ድርጊቶችን ይፈጽማሉ፤አደጋዎች እና ወንጀሎች በብዛት ይከሰታሉ፡፡ በሽታዎችን በተመለከተ
ደግሞ ጨረቃ ሙሉ ሆና በምትወጣበት ቀናት ይባባሳሉ፡፡ በተጨማሪ ሰዎች አሉታዊ
አመለካከቶችን ያመነጫሉ፡፡
በአሜሪካ የስነ-ልቦና ባለሙያ የሆኑት ዶ/ር ሊበር‹‹ በጨረቃ ዑደትና በሰው ልጆች ለይ ወንጀል
ዝንባሌዎችና ስሜታዊነት መካከል ጠንካራ ግንኙነት አለ ብሎዋል፡፡ ዶ/ር ሊበር በሆስፒታሎች
እና በፖሊስ ጣቢያዎች ውስጥ የተለያዩ የስታቲስቲክስ መረጃዎችን ከሰበሰበ በኃላ የመንገድ
አደጋዎችና ወንጀሎች ከጨረቃ ዑደት ጋር የተቆራኙ መሆኑን ደርሶበታል፡፡የሱ ሳይንሳዊ
ጥናቶች ፍቺና ከባድ የሆነ ውዝግብ ጨረቃ ሙሉ በምትሆንበት ቀናት ውስጥ በብዛት
እንደሚከሰቱ ያረጋግጣሉ፡፡[9]
12
ጨረቃ ሙሉ ስትሆንና በሰዎች ለይ የጨረቃ ውጤት ከፍተኛ ደረጃ ለይ በሚደርስበት ወቅት
ለሚከሰቱት ዘርፈ-ብዙ ችግሮች እስልምና ፍቱን የሆነ ነቢያ መድሃኒት አዘጋጅቶዋል፡፡ ይህም
ጨረቃ ሙሉ የምትሆንበትን ሶስቱን ቀናት ማለትም በጨረቃ አቆጣጠር 13ኛ፤14ኛ እና 15ኛ
ቀናትን በፆም ማሳለፍ ነው፡፡ እነዚህን ሶሰቱን ነጭ ቀናት መፆም የወንጀል ድርጊቶችን፤የባህሪ
መዛባትን እና በሽታዎችን ለመከላከል እጅግ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡[9]
በናንተ ላይ እርም ያደረገው በክትንና ደምን፣ የእሪያ ሥጋንም፣ በእርሱም (ማረድ) ከአላህ ስም
ሌላ የተነሳበትን ነገር ብቻ ነው፡፡ሽፍታና ወሰን አላፊ ሳይኾን (ለመብላት) የተገደደ ሰውም በርሱ
ላይ ኃጢኣት የለበትም፡፡ (2፡173)
ይህ የቁርኣን አንቀጽ የሞተን ነገር (በክትን) መመገብ፣ደምን ለምግብነት ማዋል እንዲሁም
ደግሞ የእሪያን ስጋ መመገብ በእስልምና ክልክል መሆኑን ይነግረናል። እዚህ አንቀጽ ውስጥ
ደም ክልክል የሆነበትን ምክንያት በሳይንሳዊ ማስረጃ ጭምር አስደግፈን ለማብራራት
እንሞክራለን። ደምን መብላት ስለመከልከሉ ማብራራት የእስልምና አስተራረድ ዘዴ ለምን
ተመራጭ እንደሆነ ለማስረዳት ያግዛል፡፡
13
ደምን መጠጣት ወይም ለምግብነት ማዋል በእስልምና ክልክል ስለመሆኑ ቁርኣን 2:173
ያብራራል። በተጨማሪም ቁርኣን 16፡115 እና ቁርኣን 6፡145 ለይም ደምን ለምግብነት ማዋል
እርም መሆኑን ተገልጾዋል፡፡ሳይንሳዊ እውነታዎችም ይህንን ክልከላ የሚያጠናክሩ ናቸው።
ከደም ተግባራት መካከል አንዱ አልሚ ንጥረ ነገሮችን ወደ ተለያዩ ሰውነታችን ክፍሎች
መውሰድና ቆሻሻ ነገሮችንና መርዛማና ንጥረ ነገሮችን ደግሞ ከህብረ ከሰውነታችን ክፍል ሰብስቦ
እንዲወገዱ ማድረግ ነው። እነዚህ ቆሻሻ ምርቶችና መርዛማ ንጥረ ነገሮች ለሰውነት ጎጂ ናቸው
እናም በኩላሊት በኩል ይወገዳሉ። ቆሻሻና ጎጂ ነገሮች በሽንት በኩልም ከሰውነታችን ተጣርተው
ወደ ውጪ ይወጣሉ። ይህ አንዱ ቆሻሻ ማስወገጃ መንገድ ነው። ደም የተላያዩ በሽታ አምጪ
የሆኑ ቆሻሻ ነገሮችን ይዞ ይዘዋወራል።ለዚህም ነው ደምን መመገብ ለጤና በጣም ጎጂ ነው
የተባለው። የሚበላ ስጋ ውስጥ ብዙ ደም ካለበት አደጋ ሊያስከትል ይችላል ምክንያቱም ደሙ
በያዘው ቆሻሻና መርዛማ ንጥረ ነገሮች አማካኝነት በሽታ ለይ ልንወድቅ ስለምንችል ነው።
ስለዚህ ስጋቸው ለመብል የተፈቀዱ እንስሳት በሚታረዱበት ወቅት ደሙ ከታረደው እንስሳ
ሙሉ በሙሉ ወደ ውጪ መፍሰስ አለበት ወይም አብዛኛው ደም መፍሰሱን ማረጋገጥ ማቻል
አለበብን፡፡ ምክንያቱም ደምንና በደም የተጨማለቀውን ስጋ መመገብ ለጤና በጣም ጎጂ ነው፡፡
[10]
ነቢዩ መሐመድ (ሰ፡ዐ፡ወ) እንዲህ ብለዋል፡፡‹‹‹ በእውነት አላህ በሁሉም ነገር ማስተካከልን
አዟል። ስትገድሉ አስተካክላችሁ ግደሉ፣ ስታርዱ አስተካክላችሁ እረዱ፣ እያንዳንዳቹ ቢላውን
በደንብ ይሳል፣ የሚያርደውን እንስሳ አያሰቃየው›››፡፡ ስለዚህ ሌላው ቀርቶ እንስሳትን ስናርድ
እንኳማሰቃየት የለብንም። ከማረዳችን በፊትም እህልና ውሃ በመስጠት መንከባከብ አለብን።
[10]
በእስልምና ለእርድ የቀረበ እንስሳ በሚታረድበት ወቅት መተንፈሻው ቱቦውና የደም ጅማቱ
ከፊት ለፊቱ መቆረጡ ደሙ ሙሉ በሙሉ ወደ ውጭ እንዲፈስ ያደርጋል። ከዚህም ባሻጋር
14
የታረደው እንስሳ ሙሉ በሙሉ ራሱን ስለሚስት ህመም ወይም ስቃይ አይሰማውም።ሁለት
አንኳር የሆኑ ቁምነገሮችን ከዚህ መውሰድ እንችላለን።
15
(Electroencephalogram) ወይም (EEG) መሳሪያ በመጠቀም በጋራ በደረጉት ሳይንሳዊ
ምርመራ አረጋግጠዋል። ከምርምሩ የተገኘው ውጤትም እንደሚከተለው ነው። [12]
በምእራቡ ዓለም እንስሳው ለእርድ ሲቀርብ በመጀመሪያ ጭንቅላቱ ለዚሁ ዓላማ ተብሎ
በተዘጋጀ ማደንዘዣ መሳሪያ ይመታና ራሱን እንዲስት ይደረጋል።እንስሳው ራሱን ስቶ
ከወደቀ በኃላ ይታረዳል። በዚህ አይነት ዘዴ የታረደ እንስሳ ህመም እንደሚሰማው
የEEG ምርመራ ውጤት አሳይቷል። በተጨማሪም በምእራቡ ዓለም እንስሳ አስተራረድ
ዘዴ የታረደው እንስሳ በእስልምና መንገድ ከታረደው እንስሳ ጋር ሲነፃፀር የልብ ምቱ
ወዲያው ነውየቆመው፡፡ ይህ ደግሞ ደም ሙሉ በሙሉ ከእንስሳው ሰውነት እንዳይወጣና
ከስጋው ጋር ንኪኪ እንዲፈጥር ስለሚያደርግ የስጋውን ጥራት ይቀንሳል። ስለዚህ
በእስላማዊ መንገድ የታረደው እንስሳ ከምእራባዊያን እንስሳ አስተራረድ ዘዴ ጋር
ሲነፃፀር አንደኛ፣ የታረደው እንስሳ ህመም ወይም ከባድ ስቃይ አይሰማውም ሁለተኛ፣
ደሙ በጠቅላላ ወደ ውጪ ስለሚፈስ የስጋው ጥራት አስተማማኝኛ ከበሽታ አምጪ
ጀርሞችና ቆሻሻ ነገሮች የፀዳ ይሆናል፡፡
1.4 በተፋታች እና ባሏ በሞተባት ሴት
16
አንድ ቁርእ ማለት አንድ የወር አበባ ወቅት ማለት ሲሆን ሶስት ቁርእ ማለት ደግሞ ሶስት
የወር አበባ ወቅት ማለት ነው። ስለዚህ አንዲት የተፈታች ሴት ሌላ ባል ከማግባትዋ በፊት
ሶስት ቁርእ መጠበቅ አለባት ማለት ሶስት የወር አበባ ወቅቶችን ወይም በግምት ሶስት ወር
መቆየት አለባት ማለት ነው።
በባሏ የተፈተች ሴት ሌላ ወንድ ሳታገባ በፊት 3 የወር አበባ ወይም 3 ወር መጠበቅ ግዴታ
ይሆንባታል ምናልባትም አርግዛም ከሆነ እስክትወልድ መጠበቅ ይኖርባታል የሚለው
የእስልምና አስተምህሮ ከዘመኑ ሳይንሳዊ ግኝት ጋር ሙሉ ለሙሉ ተስማምቶ እናገኛለን።
ሳይንስ እንደሚነግረን ከሆነ የወንዱ ዘር ፍሬ 62% ፕሮቲን ያሉት ሲሆን እሱም እንደ ጣት
አሻራችን ከሰው ወደ ሰው ይለያያል። ይህ ነገር ደግሞ የእያንዳንዱን ሰው ኮድ ለመለየት
ይጠቅመናል ልክ ኮምፒውተር ውስጥ አንድን ነገር ለመለየት ኮድ እንድምንጠቀመው ማለት
ነው። አንዲት ሴት ከባሏ ጋር ተፋታ ወዲያውኑ ሌላ ካገበች ልክ ኮምፒዩተራችን ውስጥ ሌላ
ቨይረስ ገብቶ እንደሚያጠቃ ሁሉ የሷንም መህፀን በሌላ ቨይረስ እንዲጋለጥ ያደርጋታል። ይህ
ደግሞ አደገኛ ስለሆነ ላልተመጣጠነና ለተለያዩ በሽታ ያጋልጣታል። ይህ ሳይንስ ያረጋገጠው
ሀቅ ነው። ሳይንሳዊ እውነታዎች እንደሚያሳዩት ከፍቺ በኋላ ያለው የመጀመሪያ ወር አበባ
ከ32-35%፣የሁለተኛው ወር አበባ ከ67-72%፣እንዲሁም የ3ኛ ወር አበባ 99.9% የቀድሞ ባሏን
ዘር ፍሬ ከማህፀኗ ጠራርጎ ያስወጣል። ይህ አካሄድ የሴቷን መህፀን ከ3 ወር በኃላ ንፁህና
ጤናማ አድርጎ ያዘጋጃል። [14] [15]
17
የፅንስ ሀኪሞች በአሜሪካ የሚኖሩ የአፍሪካ ሙስሊም ሴቶች ለይ ጥናት አድርገው ነበር።
የጥናቱ ውጤት እንደሚያሳየው ሁሉም ሙስሊም ሴቶች የባሎቻቸውን ኮድ (የባሎቻቸውን ዘር
ፍሬ) ብቻ ነው በውስጣቸው የያዙት። በተቃራኒው ደግሞ ሙስሊም ያልሆኑ ሴቶች ለይ
የተደረገው ምርመራ ከሁለት እስከ ሶስት የሚደርሱ የተለያዩ የወንዶች ኮድ ሴቶች
እንደተሸከሙ ተረጋግጠዋል። ይህ ደግሞ ለተለያዩ በሽታ እንዲጋለጡ ያደርጋቸዋል። ከዚህም
በመነሳት ሴቶችን በንፅህና መያዝ የሚችለው ብቸኛው ሀይማኖት እስልምና መሆኑን
ተመራማሪዎች መገንዘብ ችለዋል [14] [15]::
ነቢዩ ከዘዙን መካከል አንዱ ፂማችንን እንድናሳድግ ነው። ኢማሙ ሙስሊም አቡሁረይራን
ጠቅሰው በዘገቡት ሀዲስ ውስጥ የአላህ መልእክተኛ (ሰ፣ዐ፣ወ) የሚከተለውን ተናግረዋል። ‹‹‹
ፂማቹን አሳድጉ ከዞራስትሪይንስ (እሳት አምላኪዎች) አትመሳሰሉ።››› አብዛኛውን ግዜ ፂም
ማሳደግ እንደ ሙስሊሞች መለያ ተደርጎ ይታሰባል። ምክንያቱም አብዛኛው ሙስሊሞች
ፂማቸውን ያሳድጋሉ ይንከባከባሉ። ለመንደርደሪያ ይሆን ዘንድ አንድ ምሳሌ ብቻ ተጠቀምን
እንጂ ነቢዩ (ሰ፣ዐ፣ወ) በበርካታ ንግግራቸው ፂምን ማሳደግ እንዳለብን ተናግሯል። በዚህም
ምክንያት ብዙሃኑ ሙስሊም ሊቃውንቶች ፂምን ማሳደግ እንጂ መቆረጥ ክልክል ነው ብለዋል።
በአሁን ግዜ ፂምን ማሳደግ እንደዋነኛ የሙስሊሞች መለያ ተደርጎ ይታያል። ምክንያቱም
ሙስሊሞች ናቸው በብዛት ፂማቸውን የሚያሳድጉትና የሚንከባከቡት። ይህን በማድረጋቸው
የአላህንና መልክተኛውን ውዴታ ያተርፋሉ። ትልቅ ምንዳንም ያገኛሉ። ይህ ነቢዩ (ሰ፣ዐ፣ወ)
ያዘዙት ተግባርና ሙስሊሞች አጥብቀው የያዙት ፂምን የማሳደግ ፈለግ (ሱና) በሳይንሳዊ
እይታ ሲቃኝ ምን ይመስላል? ፂም ማሳደግን ሳይንስ ያበረታታል ወይስ ያወግዛል? ምክንያቱስ
ምንድነው? በዚህ አምድ ይህንንናና የመሳሰሉትን ይዳሰሳሉ፡፡
18
የፂም መኖር የወንዶችን ፊት ከካንሰር ይከላከላል። ቤዝል-ሴል ካንሲኖማስ (Basal-cell
carcinomas) የሚባል ከሁሉም የካንሰር አይነቶች የበለጠ ታዋቂ ካንሰር አለ። በዚህ ካንሰር
ከሚያዙት 5 ሰዎች መካከል 4ቱ ወንዶች ሲሆኑ ካንሰሩ የሚያጠቃው የወንዶችን ፊት፣
ጭንቅላትና አንገት ነው። በአሜሪካ በደቡብ ቂዊስላንድ ዩንቨርስቲ በተደረገው ሳይንሳዊ ምርምር
የፂም መኖር የዚህ ካንሰር አምጪ የሆነውንና ከፀሐይ የሚመነጨውን አልትራ ቫዮሌት ጨረር
(ultra violet rays) እስከ 95 በመቶ ድረስ ይከላከላል፡፡[17] [18] ይህ በጣም ትልቅ ጥቅም
ነው። ስለሆነም ፂም ወንዶችን የሚያጠቃውን ካንሰር ይከላከላል ማለት ነው። ህይወታችንን
ሊያሳጣ የሚችል ገዳይ በሽታን በፂማችን ከመከላከል የበለጠ ምን የተሻለ ነገር ይኖራል?
እስልምና አካላዊ፣መንፈሳዊ እና ስሜታዊ ደህንነትን ከግምት ውስጥ ያስገባ ሀይማኖት ነው። አምላካችን
አላህ ለዓላማ ነው የፈጠረን እናም የማንረጋጋበትና የማንተማመንበት ዓለም ለይ አልተወንም። በዚህ
ዓለምና በመጪው ዓለም የስኬት ባለቤት እንድሆን ዘንድ የመመሪያ መጽሐፍን፤ቁርኣን፤የነቢያት እና
መልእክተኞችን ምሳሌ ሰጠን። አንድ ሙስሊም አምላኩን በማምለክና ሕጎቹን ወይም ደንቦቹን ተግባራዊ
በማድረግ ህይወቱን ያሳልፋል ወይም ማሳለፍ ይጠበቅበታል። ከነዚህ ህጎች አንዱ የአሳማ ስጋ ወይም
የአሳማ ስጋ ምርቶችን ከመመገብ ሙሉ ለሙሉ መታቀብ ነው።
በናንተ ላይ እርም ያደረገው በክትንና ደምን፣ የእሪያ ሥጋንም፣ በእርሱም (ማረድ) ከአላህ ስም ሌላ
የተነሳበትን ነገር ብቻ ነው፡፡ሽፍታና ወሰን አላፊ ሳይኾን (ለመብላት) የተገደደ ሰውም በርሱ ላይ
ኃጢኣት የለበትም አላህ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡ (2:173)
አንድ አንድ ግዜ አላህ ነገሮችን ለምን እንዳዘዘ ወይም እንደከለከለ በጭራሽ ማወቅ ወይም መረዳት
ሊከብደን እንችላለን። ምክንያቱም አላህ ስላዘዘን ብቻ ከዛ ነገር እንታቀባለን። ይህ የመጀመሪያ ምክንያት
ሲሆን ለምን አላህ እንደከለከለን ለማወቅ ጥረትአድርገን ብንደርስበት ይህ እንደ ሁለተኛ ምክንያት
ይቆጠራል። ስለዚህ የአላህ ትእዛዝ እስከሆነ ድረስ ያለምንም ምርመራ ወይም ጥናት የአሳማን ስጋ
ከመመገብ እንቆጠባለን። ቅዱስ ቁርኣን በምእራፍ 33 አንቀጽ 36 አላህና የአላህ መልክተኛ በወሰኑት
ነገር ለይ ምንም አማራጭ እንዳሌለን ግልፅ አድርጎ ይነግረናል።
19
አላህና መልክተኛውም ነገርን በፈረዱ ጊዜ ለምእምናንና ለምእምናት ከነገራቸው ለእነርሱ ምርጫ
ሊኖራቸው አይገባም! የአላህንና የመልክተኛውንም ትእዛዝ የጣሰ ሰው ግልጽ የሆነን መሳሳት በእርግጥ
ተሳሳተ፡፡ (33:36)
አንድ ሙስሊም አማኝ አላህ እጅግ ጥበበኛና እጅግ ፍትሃዊ መሆኑን ይረዳል።ስለሆነም የእርሱ ህጎች
አካላዊ፣ስሜታዊ ወይም መንፈሳዊ ጥቅም እንዲኖራቸው ተደርገው የተቀየሱ ናቸው። ፈጣሪ ለፍጥረኑ
የተሻለውን መንገድ ያውቃል። መልካም በሆኑት ነገሮች እንድንደሰት የፈቀደልን ሲሆን በተቃራኒው
ደግሞ በእምነታችን፣በጤንነታችንና በስነ ምግባር ግን ለይ ጉዳት ሊያስከትሉ ከሚችሉ ነገሮች ደግሞ
ይከለክለናል። በዚህም ምክንያት ሙስሊሞች የተከለከሉትን ነገሮች መብላት የሚያስከትለውን አደጋ
ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ይከለከላሉ። ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ ቢሆንም እንኳ የተፈቀደን ምግብን
ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት ያደርጋሉ።
አንድ ሙስሊም አማኝ ባለማወቅ ወይም በስህተት የአሳማን ስጋ ከበላ በሱ ለይ ምንም ኃጢያት
የለበትም። አላህ በስህተት ወይም በመርሳት በምናደርገው ነገር አይቀጠንም። ሆኖም ግን እያወቀ
የአሳማን ስጋ ወይም የአሳማ ምርቶች የሆኑ ምግቦችና መጠጥ ወይም ደግሞ መድሃኒቶችን መጠቀም
አይፈቀድለትም። ጥርጣሬ ካደረበት የሚያቁትን ሰዎች መጠየቅ ጥረት ማድረግ አለበት።
በአሁን ጊዜ የአሳማ ስጋንና የአሳማ ስጋ ምርቶችን መጠቀም ጤናችን ለይ ጉዳት ሊያመጣ እንደሚችል
ሳይንሳዊ ግኝቶች በሰፊው ያትታሉ። ከዓመታት በፊት በሜክሲኮና በሰሜን አሜሪካ የተከሰተው የአሳማ
ጉንፋን ምክንያት አሳማ ሰው ለይ ጉዳት የሚያደርሱ ጥገኛ ነፍሳትን (parasites) እንደሚይዙ
ታውቆዋል፡፡
ሙስሊሞች አላህ ስለከለከላቸው የአሳማን ስጋ ከመብላት ይታቀባሉ። በአሳማ አካልና አኗኗር ዙሪያ
በተደረገውም ሳይንሳዊ ጥናት አሳማ እርኩስ በመሆኑ ምክንያት ስጋውን መመገብ የጤና ችግርን
እንደሚያስከትል ተረጋግጠዋል።
20
ምእራፍ ሁለት
ቅዱስ ቁርኣንና ሳይንስ
2.1. ስነ-ፅንስ እና ስነ-አካል
2.1.1 የፅንስ ፆታ
እስከ ቅርብ ግዜ ድረስ የፅንስ ፆታ የሚወሰነው በእናት ሴሎች ነው ተብሎ ይታሰብ ነበር። ይህ
ማለት የፅንስ ፆታ መወሰኛ ውስጥ ጉልህ ሚና የምትጫወተው ሴት ናት ተብሎ ይታሰብ
ነበር፡፡[20] በህንድ አገር ወላጆች ከሴት ልጅ ይልቅ ወንድ ልጅ እንዲኖራቸው ይፈልጋሉ፡፡
በዚህም የተነሳ በርካታ ጥንዶች ወንድ ልጅ ለማግኘት ሲሉ መውለዳቸውን ይቀጥላሉ፡፡
ያልተፈለጉ ሴት ልጆች ሲወለዱ እናት የወቀሳ ውርጂብኝ ታስተናግዳላች ምክንያቱም ሴት
የፅንስን ፆታ የመወሰን ጉልህ ድርሻ አላት ተብላ ስለሚታሰብ ነው።[21] የወንዱና የሴቷ
ሴሎች በአንድነት የፅንስን ፆታ ይወስናሉ የሚሉም ሰዎችም አሉ።[20] ቅዱስ ቁርኣን ግን
የፅንስን ፆታ መወሰኛ አስመልከቶ ለየት ዘገባ በምእራፍ 53 ከአንቀጽ 45 እስከ 46 ለይ
አስፍሯል።
21
የሚያፀንሰው በወንዴ ዘር ፈሳሽ ውስጥ ባለው ክሮሞዞም (Chromosomes) በሚባል ኬሚካል
ይወሰናል፡፡ ከለይ እንደተገለፀው የወንዴው XY ሲሆን የሴቷ XX ተብሎ ሊገለጽ በሚችል ነው
ዘር የተሰራው፡፡ የወንዴው ዘርና የሴቷ ዘር ሲገናኙ በመጀመሪያ ደረጃ ህዋሶቹ ይለያያሉ XY
የነበረው የወንዴው ዘር X እና Y ይሆናል XX የነበረው የሴቷ ዘር X እና Y ይሆናል፡፡ Y
ተባእታይ (masculine) ባህሪ ሲኖረው X ደግሞ እንስታይ (feminine) ባህሪ ይኖረዋል። ይህ
ማለት የወንዴው ዘር X እና Yን በውስጡ የያዘ ሲሆን የሴቷ ደግሞ Xን ብቻ ነው በውስጡ
የያዘው፡፡ በዚህም መሰረት ፅንስ የሚፈጠረው X ከሚባለው የወንዴ ዘር ከሆነ ከሴቷ X ብቻ
ስለሚመታ ‹‹ XX ›› ይሆናል ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት ህፃኗ ሴት ሆና ተወለዳላች ማለት
ነው፡፡ ነገር ግን ከወንዴው Y ከመጣ ከሴት X ብቻ ስለሚመጣ ‹‹ XY ›› ይሆናል ማለትም
የፅንሱ ፆታ ወንድ የሆናል፡፡ ስለዚህ የወንድ ዘር ፍሬ የፅንሱን ፆታ የሚወስን ሲሆን የሴቷ
በዚህ ረገድ ምንም ድርሻ የለውም። [20] [21] ይህ ሳይንሳዊ መረጃ ወንድና ሴትን
ከፍትወት ጠብታ(ከወንዱ ዘር ፍሬ) ፈጠረ ከሚለው የቁረኣን አንቀፅ ጋር በትክክል ገጥሞ
እናገኛለን፡፡ ዛሬ ለይ በ20ኛው ክፍለ ዘመን ሳይንስ የደረሰበትን የፅንስ ፆታ መረጃ ከ1400
ለነቢዩ ሙሐመድ (ሰ፣ዐ፣ወ) በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ ማን ነገራቸው?
በተለምዶ በህንድ አገር ውስጥ አማት የልጅ ልጇ ወንድ እንዲሆንላት ጥልቅ የሆነ ፍለጐት
አላት እናም የተወለደው ልጅ የምትፈለገውን አይነት ፆታ ከሌለው ምክንያቷ ምራቷ /የልጇ
ሚስት/ነች በማለት ትወቅሳለች፡፡ የሚወለደው ፆታን በተመለከተ ወሳኙ የወንድ የዘር ፈሳሽ
እንጂ የሴት እንቁላል አለመሆኑን ቢያውቁና መውቀስ አለብን ብለው የሚያምኑ ከሆነ
ምራታቸውን ሳይሆን እራሱ ልጃቸውን ተጠያቂ ማድረግ ነበረባቸው ምክንያቱም በቁርአንም
ይሁን በሳይንስ ለሚወለደው ህፃን ፆታ ወሳኙ የወንድ የዘር ፈሳሽ እንጂ የሴቷ አይደለም፡፡
በነገራችን ላይ አንድ ሙስሉም የወንድ የዘር ፈሳሽ ለፆታው ማንነት ትልቁን ሚና ቢጫወትም
ባልየው (ወንድ) የፈለገውን ጾታ ሳይሆን አላህ (ሱ.ወ) የወሰነው እንደሚሆን ሊያምን
ይገባል፡፡[21]
22
የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን? (75:37)
እዚጋ የተፈለገው ‹‹ ከፍትወት ጠብታ›› (From a drop of semen) የሚል ነው። ፅንሱ
የሚፈጠረው ከጠብታው ወይም ከጥቂት ዘር ፈሳሽ እንደሆነ ያሳያል። [20]
ለብዙ ክፍለ ዘመናት የሰው አንጎል የፊተኛው ክፍል ከአይን አጠገብ ስለሆነ ብቻ የዓይናችንን
ሁኔታ ይቆጣጠራል ተብሎ ይታሰብ ነበር። ሆኖም ግን ይህ አሰተሳሰብ ከእውነታው ጋር አብሮ
ሊሄድ አልቻለም፡፡ እንደውም የዘመኑ ሳይንስ የደረሰበት እውነታ ከጥንቱ ሀሳብ ጋር የሚቃረን
ሆኖ ተገኝቶዋል። ዛሬ ለይ የፊተኛው የአንጎል ክፍል ዓይናችንን ሳይሆን ንግግራችንን
እንደሚቆጣጠር ታውቆዋል።የዓይናችንን ዕይታ የሚቆጣጠረው የአንጎል ክፍል ደግሞ
የአንጎላችን የጀርባው ክፍል ነው። ቅዱስ ቁርኣን ምእራፍ 96 ከአንቀጽ 15 እስከ 16 እንዲህ
ይላል። [22]
አናት ማለት የአንጎላችን የፊተኛው ክፍል (Frontal part of brain, forelock) ነው። ቁርኣን
96፡16 ለይ ‹‹‹ ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን ››› ሲል አናት ከውሸትና ስህተት ጋር
እንዴት ተገናኙ ብለን ጥያቄ ልናስነሳ እንችላለን፡፡
አንጎል የተለያዩ ክፍሎች ያሉት ሲሆን ከዚህም መካከል አንዱ ግንባር ወይም አናት የሚባለው
የአንጎል የፊተኛው ክፍል ነው፡፡ ይህ የአንጎል የፊተኛው ክፍል ግባችንን ለማሳካት የምናስበውን
ሀሳብ ወይም ድርጊቶችን ይወስናል እንዲሁም ይቆጣጠራል፡፡እቅድ፣ችግርን መፍታትና
የእውቀት ሂደቶች በጠቅላላ በዚህ የአንጎል ከፍል ቁጥጥር ስር ናቸው፡፡ በተጨማሪ የውሸት
ንግግርን ጨምሮ ሁሉም የማታለያ ሂደቶች በዚህ የአንጎል ከፍል ውስጥ የሚወሰኑ ናቸው፡፡
ከለይ የተገለፁት የቁርኣን አንቀፆችም ልክ እንደ ዘመናዊ ሳይንስ አናት (ግንባር) ወይም
የአንጎል የፊተኛው ክፍል (frontal part of brain) ውሸትንና ሀጢያትን እንደሚቆጣጠር
ይናገራሉ፡፡[23]
23
ለአንድ ሰው የውሸት ንግግርና ሀጢያት ትልቁን ሚና የሚጫወተው አናት ወይም ደግሞ
ግንባር የሚባል የአንጎል የፊተኛው ክፍል ነው። Essentials of Anatomy and Physiology
የሚባል በርካታ የቅርብ ሳይንሳዊ ጥናትን ያካተተ መፅሐፍ ለይ እንደተመለከተው የፊተኛው
የአንጎላችን ክፍል ለተነሳሽነትና ለጠበኝነት መንስኤ ከሆነ በእርግጥም ውሸትንና ኃጢያትን
ያስከትላል ምክንያቱም አነዚህ ውጤቶች በቀላሉ የተነሻሽነትና የጠበኝነት ውጤቶች ናቸው።
ሳይንስ የፊተኛው የአንጎል ክፍል (አናት) ለውሸትና ኃጢያት መንስኤ መሆኑን ከዛሬ 60
ዓመት በፊት ቢነግረንም ቅዱስ ቁርኣን ግን 1400 ዓመት በፊት ሁሉንም ቀድሞ አለም
ባልሰለጠነበት ወቅት ግንባር/አናት/ የፊተኛው የአንጎል ክፍል ለውሸት ንግግርና ለኃጢያት
መንስኤ ቦታ መሆኑን ተናግሮዋል።[24]
2.2 እንስሳት
2.2.1 ንብ በቁርኣንና በሳይንስ
የማር ንብ ከሌሎች እንስሳት በተሻለ በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ ተጠቅሶዋል። በቅዱስ ቁርኣን
ውስጥ ከተጠቀሱት ነፍሳቶች አሉ ሆኖም ግን የንብን ያህል ላቅ ያለ ሚና አይጫወቱም።
በቁርኣን ውስጥ በሁለት ተከታታይ አንቀጾች ውስጥ የተጠቀሰው ብቻኛው እንስሳ ንብ ነው።
የቁርኣን 16ኛው ምእራፍ በስሙ የንብ ምእራፍ ተብሎ ነው የተሰየመው። እዚህ ጋር አንድ
አስደናቂ ነገር መመልከት እንችላለን። በሳይንስ በጥብቅ እንደተረጋገጠው በሁሉም የንብ
ዝርያዎች ውስጥ ወንድ ንብ 16 ነጠላ ክሮሞዞም (Chromosomes) ሲኖሮው ሴቷ ንብ ደግሞ
16 ጥንድ ክሮሞዞም (Chromosomes) አላት። በተጨማሪም ንግስቷ ንብ እንቁላሉን ሰብራ
የምትወጣው በ16 ቀናተ ውስጥ ነው። በዚሁ የንብ ምእራፍ ውስጥ ‹‹ ንብ››የሚል ቃል
በብቸኝነት የተጠቀሰው በ68ኛው አንቀፅ ውስጥ (16:68) ነው። በዚህ አንቀፅ ውስጥ
ከመጀመሪያው ፊደል ጀምሮ ንብ የሚል ቃል እስካለበት ድረስ 16 ፊደላት አሉ። ይህ ብቻ
አይደለም ‹‹ንብ›› የሚል ቃል ያለበት ብቸኛው አንቀፅ (16:68) ከ16 የተላያዩ የአረብኛ ፊደሎች
ነው የተገነባው።[25] ከለይ የተብራራውን ጠቅለል ስናደርገው ይህን ይመስላል።
24
ንግስቷ ንብ እንቁላል ሰብራ ንብ ሆና የምትወጣው 16 ቀን ውስጥ ነው።
ንቦች በሶስት ይከፈላሉ እነሱም ወንዱ ንብ፣ሰረተኛ ንብና ንግስቷ ንብ ናቸው። ወንዱ ንብ 16
ነጠላ ክሮሞሶም ሲኖረው ሴቷ ንብ ደግሞ 16 ጥንድ ክሮሞሶም ይኖራታል። ወንዱ ንብ ስራው
ከንግስቷ ጋር ግንኙነት ከማድረግ ውጭ ሌላ ስራ የለውም። በጥንት ዘመን በተለይም
በሼኪስፒር ዘመን ሰራተኛ ንቦች ወንድ ንቦች ሲሆኑ የሚተዳደሩት ደግሞ በወንዱ ንጉስ ንብ
ነው ተብሎ ይታሰብ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ከዚህ በፊት የነበሩ መላምቶች እውነት እንዳልሆኑ
ታወቁ፡፡ ከ300 ዓመታት በፊት በንቦች ለይ በተደረገው ዘመናዊ ምርመራ ትክክለኛው መረጃ
ይፋ ሆነ፡፡ በዚህም መሰረት ሰራተኛ ንቦች ሁሉም ሴት ንቦች ሲሆኑ ስራቸው ደግሞ ቀፎ
ማዘጋጀት፤ የአበባ ዱቄትን መሰብሰብና በሱም ማርን መስራት ነው። ንቦች የሚተዳደሩት
በንጉስ ንብ ሳይሆን በንግሰቷ ንብ እንደሆነም ጭምር በዘመናዊ ሳይንስ ተደረሰበት፡፡ ስለዚህ
ሁሉም ሰራተኛ ንቦች ሴት ንቦች ናቸው ማለት ነው። ይህ ዓለም በቅርቡ የደረሰበት መረጃ
መሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም። ከ1400 ዓመት በፊት ወንዱ ንብ እና ሴቷ ንብ ተለይተው
በማይታወቁበት ጊዜ በቅዱስ ቁርኣን በሚያስደምም ሁኔታ ልክ እንደ ዘመኑ ሳይንስ ሰረተኛ ንብ
ሴት ንብ እንደሆነች ተገልጾዋል፡፡[21]
«ከዚያም ከፍሬዎች ሁሉ ብይ፡፡ የጌታሽንም መንገዶች (ላንቺ) የተገሩ ሲኾኑ ግቢ፡፡» ከሆዶችዋ
መልኮቹ የተለያዩ መጠጥ ይወጣል፡፡ በእርሱ ውስጥ ለሰዎች መድኃኒት አለበት፡፡ በዚህ ውስጥ
ለሚያስተነትኑ ሕዝቦች በእርግጥ ተዓምር አልለበት (16:69) ፡፡
(ቁርኣን 16: 68-69) ያዢ፣ብዪ፣ግቢ፣የሚሉ ቃሎችን እናገኛለን።እነዚህ ቃሎች ከሴቷ ንብ ጋር
ነው የሚሄዱት። በሌላ አገላለፅ (ቁርኣን 16፡68 - 69) ስለ ንብ በሚተርክበት ግዜ የሴትን ፆታ
(feminine gender) ነው የተጠቀመው። ያዢ፣ ብዪ፣ ግቢ ተብለው የተጠቀሱ ግሶች የሴትን
ፆታ አመልካች ናቸው። ስለዚህ ከተራራዎች፤ከዛፎችም፤ሰዎች ከሚሰሩትም ቤትን ወይም ቀፎን
ይዛ አበባዎችን በመሰብሰብ ማርን የምትሰራው ሰረተኛዋ ሴት ንብ ናት፡፡ ቁርኣን ውስጥ
የተጠቀሱት የሴቷ ንብ ስራዎች የሚከተለት ናቸው።
1. ቀፎ መገንባት (16:68)
25
2. አበባን መሰብሰብ (16:69)
3. ማር ማዘጋጀት (16:69) [27]
የማር ንብ አካል በሶስት ይከፈላል እነሱም ራስ፣ደረትና ሆድ ናቸው። ቁርኣን (16:69) ውስጥ
‹‹‹ሆዶችዋ››› የሚል ቃል እናገኛለን። ‹‹‹ሆዶችዋ››› ተብሎ የተተረጎመው የአረቢኛ ቃል
‹‹‹ቡጡኒሃ››› የሚል ሲሆን ከቃሉ መጨረሻ ለይ የመጣችው ‹‹‹ሃ›››ነጠላ ሴት ንብን (singular
female bee) የምታመለክት ናት። የብዙ ሴት ንቦችን ሆድ ለማመልከት ቢሆን ኖሮ ቁርኣን
16:69 በ ‹‹‹ሃ››› ፊደል ፋንታ‹‹‹ሁነ››› የሚለውን ቅጥያ ይጠቀምና ‹‹‹ ቡጡኒሁነ››› የሚል
ቃል ይኖረው ነበር። ‹‹‹ ቡጡኒሁነ ›››ማለት ‹‹‹ ሆዳቸው ›››እንደማለት ሲሆን ‹‹‹ የብዙ ሴት
ንቦችን ››› ሆድ ያመለክታል። ቁርኣን 16:69 ግን ሆድን ለመግለፅ የተጠቀመው የአረቢኛ ቃል
‹‹‹ቡጡኒሃ››› የሚል ሲሆን ትርጉሙም ሆዶችዋ ወይም ደግሞ ‹‹‹ የሴቷ ንብ ብዙ ሆድ ›››፡፡
በሌላ አገላለፅ ቅዱስ ቁርኣን ማር የምታዘጋጀው ሴቷ ንብ ከአንድ በለይ ሆድ አላት እያለን
ነው። ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? ይህ የገሀዱን አለም እውነታ ይፃረራል ወይስ አይፃረርም?
በጭራሽ አይፃረርም ምክንያቱም ማር የምታዘጋጀው ሴቷ ንብ የምትበለውን ምግብ
ከምትፈጭበት ሆድ በተጨማሪ ሌላ ማር የምታዘጋጅበት ሆድ እንዳላት ፀሓይ የሞቀው
እውነት ነው። [27]
የማር መድሃኒትነት
በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ ‹‹‹መድሃኒት››› ወይም ደግሞ በአረብኛ ‹‹‹‹ (ሺፋኡን) ››››
የሚለው ቃል አገልግሎት ለይ የዋለው ለሁለት ነገሮች ሲሆን እሱም ለቁርኣንና ማር ነው።
[28] ማር ለምግብም ሆነ ለመድሃኒትናት ካለው ጥቅም አንፃር ‹‹ፈሳሽ ወርቅ›› ተብሎ እስከ
መጠራትም ደርሶዋል፡፡ በዘመናዊ ሳይንስ ማር ለበረካታ ጤና እክሎች ፍቱን መድሃኒት
እንደሆነ ቢታወቅም ከብዙ ዓመታት በፊት በቅዱስ ቁርኣን ከንብ ሆድ የሚወጣው ማር ለሰው
ልጅ መድሀኒት እንደሆነ ተገልጾዋል፡፡
«ከዚያም ከፍሬዎች ሁሉ ብይ፡፡ የጌታሽንም መንገዶች (ላንቺ) የተገሩ ሲኾኑ ግቢ፡፡» ከሆዶችዋ
መልኮቹ የተለያዩ መጠጥ ይወጣል፡፡ በእርሱ ውስጥ ለሰዎች መድኃኒት አለበት፡፡ በዚህ ውስጥ
ለሚያስተነትኑ ሕዝቦች በእርግጥ ተዓምር አልለበት (16:69) ፡፡
ማር ከስኳር የበለጠ ጣፋጭ ሲሆን ለየት ያለ የኬሚካል ባህሪዎች አሉት፡፡ ማር ልዩ ጣእም
ስላለው አንዳንድ ሰዎች ከስኳርና ከሌሎች ጣፋጮች የበለጠ ይመርጡታል፡፡ ከፍተኛ የሆነ
የስኳር ክምችት ስላለው ባክቴሪያዎችን የመግደል አቅም አለው፡፡ የእርጥበት መጠኑ በጣም
ዝቅተኛ ስለሆነ ማንኛውም ዓይነት ፍጡር በውስጡ ሊራባ አይችልም፡፡ የተፈጥሮ የሆነ ጥሬ
ማር የእርጥበት መጠኑ በጣም ዝቅተኛ የሚባል ሲሆን ከ14% እስከ 18% ድረስ ነው፡፡
ስለሆነም ማንኛውም ዓይነት ፍጡር በውስጡ ሊራባ አይችልም፡፡ ተፈጥሯዊ የአየር ወለድ
26
እርሾዎችም (Natural Air Born Yeasts) የማር እርጥበት መጠኑ በጣም ዝቅተኛ ስለሆነ በውስጡ
ንቁ መሆን አይችሉም፡፡
እንደ ሌሎች ቋንቋዎች ሁሉ የአረቢኛ ቋንቋ ቃላት ‹‹ሴት›› እና ‹‹ተባእታይ›› ቅጥያ አሉት።
በእነዚህ ቅጥያዎች በመታገዝ በአንድ ዐረፍተ ነገር ውስጥ አንድ ግስ (verb) የሴት ወይም
የወንድ አመልካች መሆኑን በቀላሉ እንረዳለን። በአረቢኛ በአንድ ግስ (verb) መጨረሻ ለይ
‹‹ት›› ተብሎ የሚነበብ የአረቢኛ ፊደል ከታከለበት ያለጥርጥር ያቃል ሴትን ይጠቁማል ማለት
ነው። [30]
በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ ‹‹የሸረሪት ምእራፍ›› ተብሎ የሚጠራ ምእራፍ ያለ ሲሆን የሚገኘው
በ29ኛው ምእራፍ ለይ ነው። በዚህ የሸረሪት ምእራፍ ወይም ደግሞ በ29ኛው ምእራፍ አንቀፅ
41 ለይ አምላካችን አላህ እንዲህ ይላል።
የእነዚያ ከአላህ ሌላ ረዳቶችን (ጣዖታትን) የያዙ ሰዎች ምሳሌ ቤትን እንደ ሠራች ሸረሪት ብጤ
ነው፡፡ ከቤቶችም ሁሉ በጣም ደካማው የሸረሪት ቤት ነው፡፡ ቢያውቁ ኖሮ (አማልክት አድርገው
አይግገዟቸውም ነበር) (21:41)።
በአንቀፅ ውስጥ ‹‹ሸረሪት›› ተብሎ የተተረጎመው የአረቢኛው ቃል ‹‹አንከቡት›› የሚባል ቃል
ነው፡፡ በዚህ አንቀፅ ውስጥ አላህ ከሱ ውጭ ሌላ ረዳቶችን የሚይዙ ሰዎችን ከሸረሪት ቤት ጋር
አነፃፅረዋቸዋል። ልክ እንደ ሌሎቹ ነፍሳት ሸረሪትም ሴቴና ወንዴ ተብለው ለሁለት ይከፈላሉ፡፡
ነገር ግን የሸረሪት ቤት ወይም ድርን የሚሰራው ወንዱ ሸረሪት ነው ወይስ ሴቷ ሸረሪት ናት?
ወይስ ሁለቱም ናቸው? ስለዚህ ጉዳይ ቅዱስ ቁርኣን ምን ይለናል? ከለይ በተገለፀው አንቀፅ
ውስጥ በአረብኛው ትርጉሙ ለይ ‹‹ኢተከዘት›› የሚል ግስ የምናገኝ ሲሆን ቃሉ ‹‹አንድን ነገር
27
መስራትን›› ያመለክታል። በዚህ የአረቢኛ ግስ መጨረሻ ለይ ‹‹ት›› የሚል ቅጥያ ያለበት ሲሆን
የሴት ፆታን ጠቋሚ ነው። ስለዚህ ከለይ የተብራራው የቁርኣን አንቀፅ ቤትን ወይም ድርን
የምትሰራው ሴት ሸረሪት ናት ብሎ እየነገረን ነው። ባጭሩ ከ1400 ዓመታት በፊት ቅዱስ
ቁረኣን የሸረሪትን ድር የምትሰራው ሴት ሸረሪት እንደ ሆነች በምእረፍ 21 አንቀፅ 41 ለይ
ገልጾዋል፡፡ በዚህ ረገድ በዘመናዊ ሳይንስ ምን ተብሎዋል?
እንደ ጎርጎርሳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር በ1984 ኮስሞስ (Kosmos) የተባለ በዓለም ለይ ታዋቂ
የጀርመን የሳይንስ መጽሔት ስለ ሸረሪት አንድ አንድ አስገራሚ ነገር አስነብቦ ነበር። መጽሔቱ
ለይ ከሰፈሩት ፅሁፎች መካከል የሚከተሉትን መስመሮች ሲያነቡ በቁርኣን ሳይንሳዊ ታዓምር
እንደሚደመሙ ተስፋ አደርጋለሁ።
‹‹ የሸረሪት ድርን መስራትና ምግብን ማደን በሴት ሸረሪት ብቻ የተወሰነ ነው። የእስልምናው
ነብይ ተደብቆበት የነበረውን የዋሻ መግቢያ የሚሸፍን ድር የተሰራው በሴት ሸረሪት ነው። ስለ
ወንድ ሸረሪት ህይወት ብዙ መረጃ የለንም። እኛ የምናውቀው የሸረሪት ድርን መስራት
የሚችሉት ሴት ሸረሪቶች ብቻ መሆናቸውን ነው›› የሚል ፅሁፍ ተጠቃሹ መፅሔት አስነብቦ
ነበር። [30]
በ20ኛው እና በ21ኛው ክፍለ ዘመን የተፈጥሮ እና የዱር እንስሳት ጥናት መስፋፋትን ተከትሎ
የተፈጥሮ ተመራማሪዎች እና የሳይንስ ሊቃውንት በሸረሪቶች ሕይወት ላይ የሚያጠነጥኑ
በእውነት የተንፀባረቁ አስገራሚ፣ የልታሰቡና ከመደበኛ አካሄድ ውጭ የሆኑትን ምልከታዎች
ይፋ አድርገዋል። በዓለማችን ለይ ከ45,000 በለይ የሸረሪት ዝርያዎች ያሉ ሲሆን በሸረሪት ቤት
ውስጥ መገዳደል እንዲሁም እርስ በርስ መበላላት የተለመደ ነው። ከግብረስጋ ግንኙነት በኋላ
ወንድ ሸረሪቶች በሚስቶቻቸው ይገደሉና ለምግብነት ይውላሉ።ሴት ሸረሪቶች ባሎቻቸውን ብቻ
ሳይሆን ማግባት ማይፈልጉትንም ወንድ ሸረሪቶችንም ጭምር ከመግደል ወደኋላ አይመለሱም።
ይህ በሸረሪት ቤት ውስጥ ፍጥጫና አለመረጋጋት እንዳለ ያሳየናል። [31]
28
ቅዱስ ቁርኣን ከ1400 ዓመት በፊት ስለ ሸረሪት ማንም ምንም በማያውቅበት ግዜ ከዘመኑ
ሳይንስ ቀድሞ ከቤቶች ሁሉ ደካማው ቤት የሸረሪት ቤት ነው በማለት ተናግሮዋል። [31]
ተፈጥሮ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ፍጥረታት በውስጧ ይዛ ትገኛለች፡፡ ግዙፍ ከሆኑት እንስሳት
እስከ ትንንሾቹ ነፍሳት ምድርን መኖሪያቸው አድርገው የተለያዩ የህይወት ዑደትን
ያሳልፋሉ፡፡ከነዚህ ነፍሳት ጉንዳን አንዱ ነው፡፡ በዓለም ለይ በርከታ ጉንዳን ዝርያዎች እንዳሉ
ይነገራል፡፡ በአንድ የጉንዳን ስብስብ ውስጥ ሶስት ዓይነት ጉንዳኖች አሉ፡፡ሰራተኛ፤ንግስትና
አውራ (ወንድ) ጉንዳን በመባል ይታወቃሉ፡፡እያንዳንዱ የጉንዳን ዓይነት የራሱ የሆነ ተግባሮች
አሉት፡፡ በውስጣቸው ያለውን አደረጃጀት መሰረት ያደረገ የስራ ክፍፍል ያላቸው ከመሆኑም
በለይ፤ በአንድ የጉንዳን ስብስብ ውስጥ መሰራት ካለበት ምንም ሳይሰራ አይቀርም፡፡
የቅዱስ ቁርኣን 27ኛው ምእራፍ ‹‹የጉንዳን ምእራፍ››ይባላል።በዚህ ምእራፍ ውስጥ አላህ ነቢዩ
ሱለይማንን (ዐ፣ሰ) የወፍ ቋንቋ እንዳስተማረው ይነግረናል።የጉንዳንንም ንግግር በመስማቱም
እየሳቀ ጥርሱን ፈገግ እንዳደረገ ጭምር ያወሳል። በዚህ አምድ ትኩረታችን ስለ ምእራፍ 27
(የጉንዳን ምእራፍ) አንቀፅ 18 ለይ ነው፡፡
29
እኛ ባናስተውልም እንኳ ጉንዳኖች በጣም በተለየ መልኩ በስሜት ህዋሶቻቸው መግባብትና
መነጋገር የችላሉ፡፡ ጉንዳኖች ጎጆቻቸውን ለመገንባትም ሆነ ለእርስ በርስ ጠብ ለመፍጠር ይህን
የስሜት ህዋሶቻተውን ይጠቀማሉ፡፡ ጉንዳኖች በአስደናቂ የግንኙነት ስርኣታቸው የሰው ልጅ
አንዳነዴ ተነጋግሮ መፍታት የማይችላውን ጉዳዮች በተሻለ መልኩ ይፈታሉ ያከናውናሉ፡፡
30
አልባ የሆኑ ሁሉም ሴቶች ናቸው። በሌላ አገላለፅ ሰራተኞቹ ጉንዳኖች ሁሉም ክንፍ አልባ
የሆኑ ሴት ጉንዳኖች ናቸው። እነዚህ ጉንዳኖች አይራቡም ይልቁንም የንግስቷን ዘር
ይንከባከባሉ፣መጠለያ ይሰራሉ፣እንደ ወታደር የጉንዳንን ማህበረስ ከጥቃት ይከላከላሉ እንዲሁም
ሌሎች በርካታ ተግባራትን ይከላከላሉ። የወንዶች ጉንዳኖች አንድ የስራ ድርሻ ብቻ ነው
ያላቸው ይህም ከንግስቷ ጋር ግብረ ስጋ ግንኙነት መፈፀም ብቻ ነው። ግንኙነት ከፈፀሙ በኋላ
ብዙም ሳይቆዩ ሊሞቱ ይችላሉ፡፡[33] ወንዶች ጉንዳኖችና ንግስቷ ጉንዳን ክንፍ አላቸው።
የመራቢያ ጊዜያቸው ሲደርስ አየር ለይ በመብረር ግንኙነት ይፈፅማሉ፡፡ [34]
ብዙውን ግዜ ፍየሎች፣ በጎችና ላሞች ሳር ሲግጡ እናያለን። እነዚህ ከብቶች በሚግጡት ሳርና
ከነሱ ከሚገኘው ወተት መካከል ያለው ትስስር ለማናችንም ግልፅ ያልሆነ ጉዳይ ነበር።
አምላካችን አላህ ሳር እንዲመገቡ ያደርጋቸዋል። ይህ የሚመገቡት ሳር የተለያዩ ሂደቶችን ካለፈ
በኋላ ከአልሚ ምግቦች መካከል አንዱ የሆነውን ወተት እንዲገኝ ምክንያት ሆኗል። [27]
በጥንት ግዜ ሰዎች ከጡት ጫፎች አጠገብ ካለው ነጭ ስብ ውስጥ ወተት እንደሚመረት ያስቡ
ነበር።ዛሬ ለይ ግን ይህ አመለካከት ተቀባይነት ሊያገኝ አልቻለም። ወተት የሚመረተው በወተት
እጢ ውስጥ ሲሆን ለማምረቻ የሚሆኑ ንጥረ ነገሮች የሚወሰዱት ደግሞ ከደም ፍሰት ነው።
የደም ዝረቱ ደግሞ አስፈላጊውን ንጥረ ነገር የሚያገኘው ከተፈጨው ምግብ (ፈርስ) ነው። ይህ
ማለት ከብቶች የሚግጡት ሳር/ቅጠል ከተፈጨ በኃላ ወይም ፈርስ ከሆነ በኃላ አስፈላጊ ንጥረ
ነገሮች በደም አማካኝነት ወደ ወተት እጢ ይጓዛሉ። ከዚያም በእጢው ውስጥ ነው እንግዲህ
ወተት የሚቀነባበረው። ይህ ተፈጥሯዊ የሆነ የወተት ማቀነባበሪያ ሂደት ነው። [35]
ይህ የ20ኛው ወይም 21ኛው ክፍለ ዘመን የከብቶች ወተት አመራረት ግኝት ከ1400 ዓመታት
በፊት የሰው ልጅ ወተትን ከመጠጣት ውጭ እንዴት እንደሚገኝ በማያውቅበት ግዜ ቅዱስ
ቁርኣን ስለ አመራረቱ ምእራፍ 16 አንቀጽ 66 ለይ እንደሚከተለው ገልጾታል።
ለናንተም በግመል፣ በከብት፣ በፍየል በእርግጥ መገምገሚያ አልላችሁ፡፡ በሆዶቹ ውስጥ ካለው
ከፈርስና ከደም መካከል ጥሩ ወተትን ለጠጪዎች ተዋጭ ሲሆን እናጠጣችኋለን፡፡ (16:66)
31
ከለይ የተገለፀው አንቀጽ በሆድ ውስጥ በፈርስ (የተፈጨ ምግብ)ና ደም ጥሩና የሚጠጣ ወተት
እንደሚገኝ ወይም እንደሚመረት ይነግረናል። ይህ ማለት የተፈጨው ምግብ (ፈርስ)ና የደም
ግንኙነት ለወተት አመራረት ምክንያት ሆኗል። ፈርስ (የተፈጨ) ምግብና ደም ለወተት
አመራረት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታሉ፡፡ ይህን አስገራሚ መረጃ ለነቢዩ መሐመድ (ሰ፣ዐ፣ወ)
ማነው የነገራቸው? ዊሊያም ሀርቬይ (William Harvey) ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ፣ዐ፣ወ) ከሞቱ
1000 ዓመት በኃላ ነው የደም ስርጭትን ያገኘው። በነቢዩ ግዜ ደም ከተፈጨ ምግብ
የሚገኘውን ንጥረ ነገር ተሸክሞ ለወተት ማምረቻ ወደ ወተት እጢዎች እንደሚያጓጉዝ ማንም
የሚያውቅ አልነበረም። [27]
አምላካችን አላህ ከብቶች ከሚግጡትን ሳርና ከሚጠጡት ውሃ በራሱ ጥበብና አካሄድ ወተትን
የመሰለ ጣፋጭ ነገር ለሰው ልጅ አስገኘ። በምድር ለይ ሳር + ውሃ = ወተት የሚሰጥ ፋብሪካ
ይኖራልን? በጭራሽ ለዚህም ነው ቁርኣን (16:66) ለናንተ በግመል፣በከብት፣ በፍየል በእርግጥ
ትልቅ መገምገሚያ (ትምህርት) አለላችሁ ያለን። የአላህን ጥበብና ሀይል እንዲሁም ለሰው
ልጆች የዋለውን ትልቅ ውለታ እንገነዘባለን።
2.3 ስነ -ምድር
2.3.1 የዓለምችን ዝቅተኛ ስፍራ
ይህ የሙት ባህር ስፍራ ሌላ አስደናቂ ነገር አለው። ይህ ስፍራ ከባህር ወለል በታች እስከ 412
ጫማ (430 ሜትር) ርቀት ሲኖረው በዚህም ምክንያት የምድራችን ዝቅተኛ ስፍራ
ሆኗል።[37] ይህ ሊታወቅ የቻለው በዘመናዊ ሳይንስና ቴክኖሎጂ በተደረገው ጥናትና ምርመራ
ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች ሀገራት ለይም ዝቅተኛ የሚባሉ ቦታዎች ቢገኙም ሙት
ባህርን የሚስተካከል ግን በጭራሽ አይገኝም። ይህ አስገራሚ ስፍራ ከ1400 ዓመት በፊት
በቅዱስ ቁርኣን ተከትቦ መገኘቱ የበለጠ እንድንገረም ያደርገናል። ቅዱስ ቁርኣን በምእራፍ 30
ከአንቀጽ 1 አስከ 3 ለይ የሚከተለውን እናገኛለን።
32
ሩም ተሸነፈች፡፡(30፡2)
ለዛሬው ርእሳችን ወሳኝ የሆነው የ30ኛው ምእራፍ 3ኛው አንቀጽ ነው። ይህ አንቀጽ
ሮማውያኖች ከማሸነፋቸው በፊት በጣም ቅርብ በሆነችው ምድር እንደተሸነፉ ይነግረናል።
በጣም ቅርብ በሆነችው ተብሎ የተተረጎመው የአረቢኛ ቃል ‹‹ (አድነል አርድ) ››
የሚል ሲሆን ሌላው ትርጉሙ ደግሞ ‹‹በጣም ዝቅተኛ ምድር›› ማለት ነው። ሁለቱም
ትርጉሞች ያስኬዳሉ። ስለዚህ ሮም በፐርሺያ የተሸነፈችበት ቦታ በጣም ዝቅተኛ በሆነው ምድር
ለይ ነው። በጣም ዝቅተኛ የሆነው ምደር (the lowest place of the earth) ደግሞ ፐርሺያኖችና
ሮማውያኖች የተዋጉበት ሙት ባህር ተብሎ የሚጠራ ስፍራ ነው፡፡[20]
ስለዚህ ሙት ባህርና አከባቢው ልክ ዘመኑ ሳይንስ በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ ዝቅተኛ ምድር
ተብሎዋል፡፡ይህ የቁርኣንን ታዓምር ፍንተው አድርጎ የሚገልፅ ነው ምክንያቱም በ7ኛው ከፍለ
ዘመን ሳታላይቶች እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች በወቅቱ ባለመገኘታቸው እንዲህ አይነቱን
እውነታ ማንም ሊያውቅ ወይም ሊገምተው አይችልም፡፡ ስለሆነም የዚህ መረጃ ምንጩ ከፈጣሪ
ሌላ ከየትም ሊሆን አይችልም፡፡
2.3.2 ብረት(Iron) በቁርኣንና በሳይነስ
በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ ከተጠቀሱ ንጥረ ነገሮች አንዱ ብረት (iron) ነው። በስሙ የተሰየ
ምእራፍም አለ። የቀርኣን 57ኛው ምእራፍ የብረት ምእራፍ ወይም ደግሞ በአረቢኛ ‹‹ሱረቱል
ሀዲድ›› ይባላል። በዚሁ ምእራፍ አንቀፅ 27 ለይ አላህ እንዲህ ይላል
33
ዘመናዊ የስነ ፈለክ ግኝቶች ብረት ጠፈር ውስጥ ካሉ ግዙፍ ከዋክብት የመጣ መሆኑን
ገልፀዋል። በምድር ለይ ያለው ብረት ብቻ ሳይሆን በፀሓይ ስርኣት (solar system) ውስጥ
የሚገኘውም ብረት ከጠፈር ውጭ ካሉ ግዙፍ ከዋክብት ነው የመጣው። ምክንያቱም በፀሓይ
ውስጥ ያለው የሙቀት መጠን ብረትን ለመፍጠር በቂ ስላልሆነ ነው። የፀሓይ የውጪው ክፍል
6,000 ዲግሪ የሙቀት መጠን ሲኖረው የውስጡ ዋናው ከፍል የሙቀት መጠኑ ደግሞ
በግምት 20 ሚሊዮን ዲግሪ ይሆናል። ብረት ደግሞ ሊመረት የሚችለው የሙቀት መጠናቸው
መቶ ሚሊዮን የሆኑ ከፀሓይ እጅግ በጣም ትላልቅ በሆኑ ኮከቦች ብቻ ነው። የተመረተው
የብረት መጠን ከተወሰነው በለይ ከፍ ሲል ኮከቡ ማስተናገድ ስለማይችል ትልቅ የሆነ ፍንዳታ
ይፈጠራል። የፍንዳታው ስም ኖቫ (Nova) ወይም ሱፐር ኖቫ (Super nova) ይባላል። በዚህ
ታላቅ ፍንዳታ ምክንያት ብረት ከጠፈር ወደ ምድር ይወርዳል። ቅዱስ ቁርኣን በ7ኛው ክፍለ
ዘመን ማንም ሊያስብ የማይችለውን ሀቅ አስፍሮታል። ይህን መረጃ ለነቢዩ መሐመድ
(ሰ፣ዐ፣ወ) ማን ነገራቸው? [38]
በዘመናዊ ሳይንስ ሁለት የተለያዩ ባህሮች የሚገናኙበትን ቦታና በሁለቱም መካከሌ ማገጃ
ወይም ግርዶ እንዳለ ተደርሶበታል። ይህ ማገጃ ወይም ሁለቱን ባህሮችን ይከፍላል፡፡ እያንዳንዱ
ባህር የራሱ የሆነ የሙቀት፣የጨዋማነትና የውፍረት መጠን አለው። ለምሳሌ የሜዲትራኒያን
ባህር ውሃ በጣሪቅ (Gibraltar) ተራራ አማካኝነት ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ይገባል ይህም
በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን በመጓዝ ነው፡፡ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ ወደ
አንድ ሺህ ሜትር ጥልቀት ከነ ሙቀቱ፤ጨዋማነቱና ከአነስተኛ ውፍረቱ ጋር ይጓዛል፡፡
የሜዲትራኒያን ባህር ጨዋማነቱ ከ36% በለይ ሲሆን የሙቀት መጠኑ ደግሞ 11.5 ዲግሪ
ሴንትግሬድ ነው፡፡ አትላንቲክ ውቅያኖስን ስናይ ደግሞ ጨዋማነቱ ከ36% በታቸ፤የሙቀት
መጠኑ ደግሞ 10.0 ዲግሪ ሴንትግሬድ ሆኖ እናገኛለን፡፡ በመካከላቸው ማገጃ በመኖሩ ምክንያት
ሁለቱ የውሃ አካላት በሚገናኙበት ወቅት ይህንን የሙቀትና ጨዋማነት መጠናቸውን ሳይለቁ
ነው፡፡
(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡ (55:20)
34
ነገር ግን ቅዱስ ቁርኣን በጣፋጭና ጨዋማ ውሃ መካከል ያለውን መለያ ሲናገር ከመለያው
የሚከለክለውን ግርዶሽ መኖሩን መግለጹ ነው፡፡ይህንንም በማስመልከት ምእራፍ 25 አንቀፅ 53
እንዲህ ይላል፡፡
እርሱም ያ ሁለቱን ባሕሮች አጎራብቶ የለቀቀ ነው፡፡ ይህ ጥምን የሚቆርጥ ጣፋጭ ነው፡፡
ይህም የሚመረግግ ጨው ነው፡፡ በመካከላቸውም (ከመቀላቀል) መለያንና የተከለለን ክልል
ያደረገ ነው፡፡ (25፡53)
ምናልባት አንድ ሰው ጥያቄ ልጠይቅ ይችላል፡ አላህ በቁርአን ውስጥ በጣፊጭና ጨዋማ
መካከሌ ያለውን መለያ ሲናገር ለምን ግርዶሽን ገለጸ ነገር ግን በሁለቱ ባህሮች ያለውን መለያ
ሲናገር አልጠቀሰውም?
ዘመናዊ ሳይንስ የወንዞችን መፍሰሻ ቦታ መርምሮ በማግኘት ጣፋጭና ጨዋማ ውሃ
የሚገናኙበትን ቦታ አውቋል፡፡ ሁኔታው ከሁለቱ ባህሮች የመገናኛ ቦታ በጥቂቱም ቢሆን
ይለያል፡፡ ከወንዞች ፌሳሽ ጣፊጭ ውሃ ከጨዋማ ውሃ የሚለይበት መንስኤ ዝቅተኛ አካባቢ
(pycnocline) ለይ መሆኑ ተጠንቷል፡፡በደንሲቲውና በአቋራጭነቱ የሚለይና በሁለቱ
መስመሮች መካከሌ መለያ ያለው ነው፡፡ ይህ መለያ ክልል ከጣፋጭና ከጨዋማ ውሃ የሆነ
የተለያየ የጨዋማነት ደረጃ አለው፡፡
እነዚህ መረጃዎች አሁን ቢሆን እንጂ ከዚህ በፊት አይታወቁም ነበር፡፡የሙቀት፣የጣፋጭና
የጨዋማነት መለኪያ እንዲሁም የደንሲቲንና ኦክሲጅን የሚሟማበትን ደረጃ ለይቶ የሚያሳዩ
መሳሪያዎችንና ዘመናዊ መመሪያዎችን በመጠቀም ነው፡፡
የሰው ልጅ ዓይን በሁለቱ ባህሮች መካከል ያለውን መገናኛ መስመር ለይቶ ማወቅ አይችልም፡፡
ይልቁንም ሁለቱ ባህሮች እንደ አንድ ባህር ሆኖ ይታዩናል፡፡ እንዱሁም የሰው ልጅ ዓይን
በወንዞች የሚፈሰውን የውሃ ክፍፍል ሶስት አይነት እንደሆነ ለይቶ ማወቅ አይችልም፤ይህም
ጣፊጭ ውሃ፤ጨዋማና መክፈያ(መለያ ክልል) ነው።
ጥቁር ባሕር ከአውሮፓና እስያ አሕጉራት መካከል የሚገኝ ትልቅ ባህር ነው። ይህ ባህር
በተለያዩ የዓለማችን ክፍል ጎብኝዎች በየአመቱ ይጎበኛል። ሳይንቲስቶች አንድ አስገራሚና
ያልተጠበቀ ነገር በጥቁር ባህር ውስጥ አግኝተዋል። ይህም ራሱን ያቻለ ከባህሩ ጋር
የማይቀላቀል ወንዝ ጥቁር ባህር ውስጥ ይገኛል። የወንዙ ጥልቀት 40 ሜትር ነው። ይህ
ጥቁር ባህር ውስጥ ያለው ለየት ያለ ወንዝ መልኩ ሰማያዊ ሲሆን ከሌላ ውሃ ጋር
አይቀላቀልም። ይህ ማለት ጥቁር ባህር ውስጥ የማይደባለቁ ሁለት የውሃ አካላት የራሳቸውን
ፀባይ ይዘው አትንካኝ አልነካህም ተባብለው አብረው ይኖራሉ አንዱ የባህሩ ውሃ ሲሆን
ሁለተኛው የወንዝ ውሃ ነው። ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? የጥቁር ባህር ውሃ ውስጥ ሌላ
ሰማያዊ መልክ ያለው የወንዝ ውሃ አለ። የሚገርመው ሁለቱ የውሃ አካላት አለመቀላቀላቸው
ነው። [39]
35
2.4.2 ጨለማና መእበል በጥልቅ ውቅያኖስ/ባህር ውስጥ
ወይም (መጥፎ ሥራዎቻቸውን) ከበላዩ ደመና ያለበት ማዕበል በሚሸፈነው ጥልቅ ባህር ውስጥ
እንዳሉ ጨለማዎች ነው፡፡ (እነዚያ) ከፊላቸው ከከፊሉ በላይ ድርብርብ የኾኑ ጨለማዎች
ናቸው፡፡ (በዚህች) የተሞከረ (ሰው) እጁን ባወጣ ጊዜ ሊያያት አይቀርብም፡፡ አላህም ለእርሱ
ብርሃንን ያላደረገለት ሰው ለእርሱ ምንም ብርሃን የለውም፡፡ (24:40)
ይህ አንቀፅ የከሓዲዎችን መጥፎ ስራ ምሳሌን የሚገልፅ ነው፡፡ጥልቅ ባህር ውስጥ ጨለማዎች
እንዳሉና በውስጣዊ ማእበሎች እንደተሸፈኑ ያሳያል፡፡ አንቀፁ ሁለት አንኳር ነጥቦችን በውስጡ
ይዞዋል፡፡እነሱም የጥልቅ ባህር ጨለማዎችና የጥልቅ ባህር ውስጣዊ መእበሎች ናቸው፡፡
ቅዱስ ቁርኣን ጥልቅ ባህር ውስጥ ስላለው ጨለማ ከዘመኑ ሳይንሳዊ ግኝት ጋር በሚስማማ
መልኩ ገልፆታል።ቁርኣን ከ1400 ዓመት በፊት የገለፀውን የጥልቅ ባህር ውስጥ ጨለማ ዓለም
ከ ከ1930 በኋላ ነው የደረሰበት። በተጨሪም የሰው ልጅ የባህር መእበል የሚገኘው የለይኛው
የውቅያኖስ ወይም ደግሞ የባህር ክፍል ለይ ነው ብሎ በሚያስብበት ወቅት ቅዱስ ቁርኣን
ከባህር ወለል በታች ጥልቅ ባህር ውስጥም ጭምር መእበል እንደለ ገልፆታል። ዓለም ልክ እንደ
ቁርኣኑ ገለፃ ጥልቅ ባህር በሞገዶች/መእበል የተሞላ መሆኑን የተገነዘበው ከ1930 በኋላ ነው።
ይህ እውነታ በ20ኛው ክፍለ ዘመን በሰላሳዎቹ ውስጥ ሰርጓች መርከቦች ከተፈጠሩ በኋላ ነው
የታወቀው። [41]
ከለይ የተጠቀሱትን መራጃዎች ለማግኘት ሶስት ክፍለ ዘመናትን የፈጀ እልህ አስጨራሽና
ከፍተኛ ምርምሮች ተደርጎዋል። በመቶዎች የሚቆጠሩ ተመራማሪዎችና መርማሪዎችም
ተሳትፈውበታል። ታዲያ ሳይንሳዊ ምርምሮች በሌሉበት ወይም ባልተጀመረበት እና ዓለም
በአፈታሪክ በተሞላች ወቅት ስለ ጥልቅ ባህር ሚስጢሮች ለነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) ማን አሳወቀ፡፡
እንኳን ባህር ቀርቶ የመጠጥ ውሃ ለማግኘት አዳጋች በሆነው በአረቢያ ምድረበዳ የኖረና
በህይወት ዘመኑ አንድም ቀን በባህር ተጉዞ የማያውቅ ሰው (ሰ፡ዐ፡ወ) እነዚህን ከባባድ የጥልቅ
የባህርና ውቅያኖስ ትክክለኛ ሚስጥሮች አገኘ? ያገኘውን መረጃ እውነት ስለመሆኑ እንዴት
እረግጠኛ ሆነ? እዚህ ጋር ልብ ያለው ልብ ማለት ይችላል፡፡[41]
36
2.5 ስነ- ፈለክና ቁርኣን
2.5.1 የፀሐይ መሽከርከር
ከነዚህ ሁሉ ግኝት በኋላ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ፀሓይ ልክ እንደ ምድር ሁሉ በራሷ ዛቢያ
አትሽከረከርም የሚል ንድፈ ሀሳብ በሰፊው ተቀባይነት አግኘቶ ነበር።በትምህርት ቤት
በጂኦግራፊ መማሪያ መጽሐፍ ውስጥም እስከ ቅርብ ግዜ ድረስ ይህ ሀሳብ ተካቶ ነበር። እንደ
ኒኮላስ ካፖርኒከስና ዩሓኑስ ኬፕሌር ንድፈ ሀሳብ ፀሐይ የማትቀሳቀስ ወይም የማትሽከረከር
አካል ተደርጋ ብትታይም እንደ ቅዱስ ቁርኣን ግን ፀሓይ የራሷን ሚዛን ጠብቃ ትሽከረከራለች።
ቅዱስ ቁርኣን በምእራፍ 21 አንቀፅ 33 ለይ እንዲህ ይላል።
እርሱም ሌሊትንና ቀንን፣ ፀሐይንና ጨረቃንም የፈጠረ ነው፡፡ ሁሉም በፈለካቸው ውስጥ
ይዋኛሉ። (21:33)
በዚህ የቁርኣን አንቀፅ ውስጥ ‹‹ይዋኛሉ›› ተብሎ የተተረጎመው የአረቢኛ ቃል ‹‹የስበሁን››
የሚል ሲሆን ከማንኛውም ተንቀሳቃሽ አካል የሚመጣውን የመንቀሳቀስ ሀይል ያሳያል። ይህን
‹‹የስበሁን›› ወይም ‹‹ይዋኛሉ›› የሚለውን ቃል እንደ ፀሐይ ላለው ሰማያዊ አካል
ከተጠቀምንበት ‹‹ ፀሓይ በጠፈር ውስጥ ትሽከረከራለች ››የሚለውን ሀሳብ ያሲዛል። ስለዚህ
ቅዱስ ቁርኣን ከ1400 ዓመት የስነ ፈለክ ሳይንስ በማይታወቅበት ወቅት ፀሐይም ጨረቃም
በፈላካቻው ውስጥ እንደሚሽከረከሩ ተናግሮዋል። በዘመኑ ጥልቅ የስነ-ፈለክ ምርምር ውጤት
መሰረት ዓለም በአሁን ሰዓት ልክ እንደ ቅዱስ ቁርኣኑ ገለፃ ፀሓይ ተንቀሳቃሽ አካል ወይም
ደግሞ በራሳ ዛቢያ ለይ የምትሽከረከር መሆኑዋን አምኖ ተቀብሎዋል። የትምህርት ቤት
መማሪያ መጽሐፍትም ይህን ቁርኣኑን እውነታ በማከተት በአዲስ መልክ ብቅ ካሉ ዓመታት
ተቆጥረዋል።
37
በዘመናዊ መሳሪያ በመታገዝ የፀሐይን እሽክርክሪት ለመመልከት ተችለዋል። ፀሐይ በራሷ ዛቢያ
ለመሽከርከር በግምት 25 ቀናት የሚፋጅባት ሲሆን በወተታማው መንገድ (milk way) አንድ
ዙር ተሽከርክራ ለማጠናቀቅ 200 ሚሊዮን ዓመት ይፈጅባታል። [21]
ሌሊትን በቀን ውስጥ ያስገባል፡፡ ቀንንም በሌሊት ውሰጥ ያስገባል፤ ፀሐይንና ጨረቃንም ገራ፡፡
ሁሉም እተወሰነ ጊዜ ድረስ ይሮጣሉ፡፡ ይህ ጌታችሁ አላህ ነው፡፡ ንግሥናው የእርሱ ብቻ ነው፡፡
እነዚያም ከእርሱ ሌላ የምትግገዟቸው የተምር ፍሬ ሽፋን እንኳ አይኖራቸውም፡፡ (35:13)
38
ብናኝ ወይም አቶም ከተከፋፈለ ከአቶም (ብናኝ) በታች የሆነ ሌላ ቁስ አካል አለ ማለት
ነው።ይህ አዲስና የቅርብ ግዜ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ግኝት የሆነው ሀሳብ በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ
ከ1400 ዓመታት በፊት መጠቀሱ ቁርኣን ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር ከመስማማትም አልፎ
የቀደማቸው መሆኑን ያሳያል።
ይህ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በሳይንስ ሊቃውንት የተገኘው አዲስ ግኝት ከ1400 ዓመታት በፊት
በቅዱስ ቁርኣን ተጠቅሶ እናገኛለን። ቅዱስ ቁርኣን በምእራፍ 21 አንቀፅ 30 ለይ እንዲህ
ይላል።
39
እነዚያም የካዱት ሰማያትና ምድር የተጣበቁ የነበሩና የለያየናቸው መኾናችንን አያውቁምን
ሕያው የኾነንም ነገር ሁሉ ከውሃ ፈጠርን፡፡ አያምኑምን (21:30)
የቁርኣኑአንቀፅ መጀመሪያ ለይ ምድርና ሰማይ የተጣበቁና አንድ እንደነበሩ ከዚያም ተለያይተው
የአሁኑን ቅርፅ እንደያዙ ነው የሚነግረን። አንቀፁ ውስጥ የተጣበቁ ተብሎ የተተረጎመው
የአረቢኛ ቃል ‹‹ (ረትቀን) ››የሚል ሲሆን የተዋሀደ፣ የተጣጣመ ወይም ደግሞ የማይነጠል
ማለት ነው።ማለትም ይህ ቃል በአረቢኛ ሁለት በአንድ ለይ የተጣመሩ ነግሮችን ለመግለፅ
ጥቅም ለይ ይውላል።
ዓለም ሰማይና ምድርን ጨምሮ አፅናፉ-አለም መጀመሪያ አንድ አካል እንደነበሩ በኃላ ለይ
ደግሞ እንደተለያዩ በቅርብ ጊዜ የደረሰበት ቢሆንም ቅዱስ ቁርኣንም ይህን እውነታ ከ1400
በፊት አስፍሮታል፡፡ የሚያስገርመው ነገር ቅዱስ ቁርኣን ከሳይንሱ ጋር መስማማቱ ብቻ
ሳይሆን ሳይንሱን በ1400 ዓመታት ቀድሞ መገኘቱ ነው፡፡ ይህን መረጃ ከ1400 ዓመታት በፊት
አለም ባልሰለጠነበት ወቅት በመሃይማን ህዝቦች መካከል በምድረ በዳ የኖረ የማያነብ የማይፅፍ
ሰው (ሰ፡ዐ፡ወ) እንዴት ሊያገኝ ይችላል? ስለዚህ የዚህ መረጃ ምንጩ ከፈጣሪ ውጪ ማንም
ሊሆን አንደማይችል እሙንና ቀቡል ነው፡፡ [43]
ከለይ የተብራራው የቁርኣን አንቀፅ አንድ ሌላ እውነታ በውስጡ አቅፎ ይዞዋል። ይህም አላህ
ህያው የሆነውን ነገር ሁሉ ከውሃ ፈጠርን ይላል። በሳይንስ ሴል (Cell) የህያዋን ፍጥረታት
(ህይወት ያላቸው ፍጡራን) ሁሉ መሰረታዊና መነሻ ክፍል ነው፡፡ ሳይቶፕላዝም (cytoplasm)
የሚባል የሴል መሰረታዊ ንጥረ ነገር ደግሞ 80 በመቶ ውሃ ነው፡፡ የተለያዩ ዘመናዊ
ምርምሮችም አብዛኛዎቹ ፍጥረታት ከ50 እስከ 90 በመቶ ድረስ ውሃ እንደሚይዙ ያሳያሉ፡፡
አስቡት እስኪ ከ1400 ዓመታት በፊት የውሃ እጦት ባለበት የአረቢያ ምድረበዳ የሚኖር
የማያነብ የማይፅፍ እንዲሁም ከአገሩ ወጥቶ የማያውቅ ሰው (አለይሂሰላቱ ወሰላም) እንዴት
እንዴት ልክ ዘመኑ ሳይንስ ህያው ፍጡር ሁሉ የተገኘው ከውሃ ብሎ ሊናገር ይችላል?
በተጨማሪም ቅዱስ ቁርኣን ምእራፍ 24 አንቀፅ 45 ለይም ተንቀሳቃሽ ፍጡር ሁሉ ከውሃ
እንደተፈጠረ ይነግረናል።
ሙስሊም አቡሁራይራን ጠቅሰው በዘገቡት ሀዲስ ውስጥ ነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) እንዲህ ብለዋል፣
የአደም ልጅ ከሞተ በኋላ ምድር ማንኛውንም የሰውነት ክፍሉን ቁርጥም አድርጋ ትበላለች
አንዲት አጥንት ብቻ ስትቀር። የሰው ልጅ ከዚች አጥንት ነው የተፈጠረው እንዲሁም በፍርዱ
ቀንም ከርሷ ነው ኢንዲበቅል የሚደረገው።
የቻይናውያን የሳይንቲስቶች ቡድን በቤተ ሙከራቸው ባደረጉት ፍተሻ ይችን ጥንጥዬ አጥንት
ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት እንደማይቻል አረጋግጠዋል። እነዚህ ሰዎች ይችን አጥንት በሀይለኛ
አሲድ ዉስጥ ዘፍዝፈው በማቆየት ድራሿን ሊያጠፏት ሞክረዋል ግን አልሆነም። እንዲሁም
በማቃጠል፣ በመደብደብ ( በመውቀጥ)ና ለከፍተኛ ጨረር እንድትጋለጥ በማድረግ ከምድረገፅ
41
ሊያስወግዷት ያላደረጉት ሙከራ የለም ይሁን እንጂ ሁሉም ልፋታቸው ከንቱ ነበር
የሆነባቸው። ይህ የሚያሳየን የነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) ሀዲስ ወይም ንግግር በእውነት የተሞላ ብቻ
ሳይሆን ሳይንሳዊ ፍተሻዎችን ሁሉ በብዙ ዘመናት የቀደመ መሆኑን ጭምር ነው።[44]
‹‹አንድ ዝንብ በአንዳችሁ መጠጥ ውስጥ ቢገባ ሙሉ በሙሉ በፈሳሹ ውስጥ መጥለቅ አለበት
ከዚያም ያስወግዱት ፣ ምክንያቱም አንዱ ክንፉ በሽታ አለው ሌላኛው ደግሞ ፈውስ አለው "።
ስለ ዝምብና በህሪዋ ማንም ምንም በማያውቅበት ጊዜ ረሱል ሰ፡ዐ፡ወ ዝምብ በአንድ ክንፏ በሽታ
በሌላ ክንፏ መድሃኒት አላት›› በማለት ተናግረዋል።
የሚገርመው በግብፅና በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ የሙስሊም ተመራማሪዎች ቡድን በውሃ፤በማር
እና በተለያዩ ጭማቂዎች ኮንቴይነሮች ላይ በአንድ ወቅት ጥናት አካሂደው ነበር፡፡ ኮንቴኔሮቹ
ውስጥ ዝምቦች እንዲገቡ ተደረጉ። በአጉሊ መነጽር በተደረገው ምርመራ ዝምቦች ሙሉ
ለሙሉ የጠለቁባቸው ፈሳሾች ከባክቴሪያና ቨይረስ ነፃ ስለሆኑ ለመጠጥ መዋል እንደሚችሉ
ተረጋግጥዋል። ታዲያ ነቢዩ (ሰ፡ዐ፣ወ) ያሉት ይህንኑ አይደል። በአንዳችሁ መጠጥ ውስጥ
ዝምብ ቢገባ ሙሉ ለሙሉ ወደ ውስጥ አጥልቃቹ አውጡትና ጠጡ ነው ያሉት። ነቢዩ
(ሰ፡ዐ፡ወ) ይህን ሁሉ መረጃ እንዴት እውቁ? ቅዱስ ቁርኣን ምእራፍ 53 ከአንቀፅ 3 እስከ 4
ደረስ ለዚህ ጥያቄ መልስ አለው፡፡
42
ነክረክ ብታወጣነ ውሃውን ብትጠጣ ያለምንም የጎንዮሽ ጉዳት ጥምህን ታረካለህ አጅርም
ታገኝበታለክ። በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ማለት እንደዚህ ነው፡፡ የዱንያንም የአኺራንም
ጥቅም ሸመትክ።
ለዚህ ሁሉ መፍትሄ ከሆኑ ነገሮች አንዱ ከመሬት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ማድረግ ነው፡፡ ይህ
ማለት የሰውነት ቆዳችንን ከአፈርን/መሬት/ ከምድር ጋር ንክኪ እንዲኖረው ማድረግ አለብን።
በተለይ አልፎ አልፎም ቢሆን በባዶ እግር መሬት/አፈር ለይ መሄድ ሁነኛ የሆነ መፍትሄ
ነው።ምክንያቱም የመሬት ገፅ ኔጋቲቭ ቻርጅ ስላለው ነው።ሰውነታችን የሚያመነጨው ‹‹free
radicals›› የሚባሉ ኬሚካሎች ፖዘቲቭ ቻርጅ (Positive charges) ስላላቸው ኔጋቲቭ ቻርጅ
(Negative charges) ካለው የምድር ገፅ ጋር ንክኪ ስፈጥሩ ይጠፋሉ ወይም ደግሞ ይቀንሳሉ።
ሰላምችንም ይመለሳል። ጤናችን በእጃችን ነው ያለው።
ነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) አልፎ አልፎ ባዶ እግራቸውን ይሄዱ ነበር ሌሎችንም ያዙ ነበር የሚለውን
ስንሰማ ነገሩ የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የነቢዩ(ሰ፡ዐ፡ወ) ሱና (ፈለግ) ጭምር መሆኑን
እንገነዘባለን። ይህን የመሰለ ለዘመናችን እጅግ አስፈላጊ የሆነ ነገር ጭራሽ የተረሳ ሱና
ሆኖዋል። [46] [47]
ከነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) ባልደረቦች መካከል አንድ ሰው ግብፅ ውስጥ ወደ ነበረው ፈዳላህ ኢብኑ
ዑበይድ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተጓዘ፡፡ ከአጭር ውይይት በኋላ ባልደረባው ፈዳልህ ኢብኑ ዑበይድን
‹ለምን በአንተ ላይ ጫማ አላየሁም?› ብሎ ጠየቀው፡፡ ፈዳላህም ነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) አንዳንድ ጊዜ
በባዶ እግር እንድንሄድ አዘውናል ብሎ መለሰ ((ኢማም አቡ ዳውድ በሂዲስ ቁጥር 3629 ለይ
ዘግቦዋል። ሼይኩል አልባኒ አል ሲልሲላ አሰሂሃ ቁጥር 502 ለይሰሂህ ብሎውታል። እራሳቸው
ረሱል አልፎ አልፎ ባዶ እግራቸውን ይሄዱ እንደነበር ተዘግቦዋል።
ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ፡ዐ፡ወ) ወረርሺኝ በሚነሳበት ጊዜ ማድረግ ያላብንን ስኬታማ የሆነ አካሄድ
ጠቁመውን አልፏል። ቡኻሪና ሙስሊም እንደ ዘገቡት ነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) እንዲህ ብለዋል።
43
‹‹በአንድ ምድር ለይ ወረርሺኝ ከሰማችሁ ወደሱ አትግቡ፣ ወረርሺኑ የተከሰተ ቦታን ደግሞ
አይተው፡፡ በተጨማሪም ኢማሙ አህመድ በዘገቡት ሀዲስ ውስጥም የሚከተለውን ብለዋል።
‹‹ወረርሺን ከላበት ቦታ የሚሸሽ ሰው በአላህ መንገድ ለይ ከመታገል እንደሚሸሽ ሰው ነው።
ትእግስት አድርጎ ባለበት ቦታ የሚቆይ ሰው ደግሞ የሰማእታትን ምንዳ ያገኛል።
ሁለቱ ከለይ የተገለፁት የነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) ንግግሮች ወረርሺኝ በሚከሰትበት ግዜ ለመቆጣጠርና
እንደይስፋፋ ለማድረግ ማድረግ ካለብን ነገሮች አንዱ ወረርሺኝ ወደ ተነሳበት ቦታ አለመጓዝ
ሲሆን እኛ ያለንበት ስፍራ ወረርሺኙ ከተከሰተ ደግሞ ለሌሎች አከባቢ እንዳይሰራጭ ለማድረግ
ያለንበት ስፍራ ለቀን መሄድ እንዳሌለብን ይመክሩናል። ይህ አካሄድ ወረርሺኝ በሚከሰትበት
ወቅት እንቅስቃሴን መግታት እንዳለብን ያሳያል።
44
3.5 ወተት ከተጠጣ በኃላ አፍን በውሃ መጉመጥመጥ
እንደሚታወቀው ጠንካራ አጥንቶችን በመገንባት ረገድ ካልሺየም (Calcium) የሚባል ንጥረ ነገር
በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ወተትና የወተት ተዋፅኦዎች በዚህ ንጥረ ነገር በጣም የበለፀጉ ናቸው፡፡
አንድ ኩባያ ወተት 300 ሚሊግራም ካልሺየም በውስጡ ይዞዋል፡፡ ወተት ጥርስንና የጥርስ
አጥንቶችንም ጭምር ጤንነታቸውን ይጠብቃል፡፡ ስለዚህ ወተት ለጥርስ ጥሩ ስለመሆኑ ምንም
አያጠያይቅም፡፡
ወተት ውስጥ ያለው ካልሲየም የሚባል ንጥረ ነገር ለአጥንት ጥንካሬ እንዲሁም ደግሞ ለጥርስ
ጤንነት በጣም ጠቃሚ ቢሆንምወተት ጠጥተን ስንነሳ አፋችንን በውሃ ማለቅለቅ/መጉመጥመጥ
ወይም ደግሞ ጥርሳችንን መፋቅ እንዳለብን የጥርስ ሀኪሞች ይመክራሉ። ምክንያቱም ወተት
ውስጥ ያለው ላክቶስ (Lactose) የሚባል የስኳር አይነት ጥርሳችን ለይ ለረጅም ግዜ ከቆየ
ጥርሳችንን በግዜ ሂደት የመቦርቦር አቅም ስላለው ነው።
ታዲያ ታለቁ ነቢይ (ሰ፡ዐ፡ወ) ያደረጉት ይህንኑ አይደል፡፡ ቡኻሪ እና ሙስሊም ኢብኒ አባስን
ጠቅሰው እንደዘገቡት ‹‹ነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) ወተት ጠጡና አፋቸው በውሃ ተጉመጠመጡ። ከዚያም
ስብ አለው አሉ››። ይህ ሳይንሳዊ ጥቅም ያዘለ የነቢዩ (ሰ፡ዐ፡ወ) ሱና (ፈለግ) አሁን ለይ እስከ
መረሳት ጭምር የደረሰ ነው፡፡
45
ዋቢ መጽሐፍት
[1] Doufesh H, Ibrahim F., Ismail NA., Ahmad WA (2014). Effect of Muslim prayer (salat) on
α Electroencephalography and its relatiohsip with Automatic Nervous System Activity. The
Journa of Alternative and Complimentary mediine, Volume 20, number 7, Pp. 558 – 562
[3] Amazing Benefits of Prostration in Islam and New Science on “Earthing’’. The Deen show
Greatings of Peace.
[4] Doufesh H, Ibrahim F., Ismail NA., Ahmad WA. Assessment of heart rates and blood
pressure in different salat positions. Journal of Physical Therapy Science, from internate benefit
of Islamic prayer
[16) Dr Gohar Mushtaq (n.d). Scientific and Islamic reasons for growing beard.
[17] Abduldaem Al-kaheel (n.d). Benefits of Beards. www.kaheel7.com/eng
[18] Fetters, K.Alesia (2013).5 lesser known benefits of having a beard
[19] Stacey, Aisha (2011). Why Pork is Forbidden in Islam: Obeying the Law of God.
www.IslamReligion.com
46
[20] Abu Subhan (n.d). Linguistic, Historic, Futuristic, and Scientific Miracle of the Quran.
http://www.hasbunallah.com.au
[21] Dr. Zakir Naik. The Qur’aan and Modern Science. Compatible or Incompatible? Islamic
Research foundation.
[22] Brain functions. https://www.miracles-of-quran.com
[23] Curley, Allison (2013). The Truth about Lies. The Science of Deception. BrainFacts.org
[24]
[25] Binimad Al-Ateeqi (2017). Quran Mathemathical Miracles.An Undeniable Miraculous
Code.
[26] Honey Bees. https://www.miracles-of-quran.com
[27] Taslaman, Caner (2006). The Quran. Unchallengeable Miracle. Citlembic publications
[28] Dr.Tauseef Ahmad Khan (2020).Honey: A cure for man kind? www.alhahkam.org
[32] Harun Yahya (2000). The Miracle in the Ant. Published by Vural Yayincilik, Istanbul,
Turkey.
[34] Lupo, Lisa Jo (2019). Why ants have wings only sometimes during the year?
[39] I.A. Ibrahim (2012). እስልምናን ለመገንዘብ አጭር ስዕላዊ ማስረጃ. www.alukah.net
[41] AL-Shaykh. Abdul-Majeed AZeez AL-Zindani (2009). Interna Waves and ‘’Quran on
Oceanography. quranand science.com
47
[42] Dr. Garry Miller (1992). The Amazing Quran. Abul-Qasim Publishing house (AQPH)
[43] The splitting Asunder of the Earth and the Skies. Retrived from
https://questionsonislam.com
[45] Abduldaem Al-Kaheel (n.d). New facts: the flies have a cure. www.kaheel7.com/eng
[46] Wells, Katie (2019). Earthing and Grounding: Legit or Hype? (How to and When not to).
Retrived from https://wellnessmama.com/5600/earthing-grounding/
[47] Isaac Elias, Kick of your shoes: Surprising MD-Approved Benefits of Walking Barefoot.
Mindbodygreen.com.
48