Professional Documents
Culture Documents
ሃይማኖትና መንፈሳዊ ሰው
ሃይማኖትና መንፈሳዊ ሰው
ሃይማኖትና መንፈሳዊ ሰው
ኅዳር 2011
0
1. መግቢያ.................................................................................................................................................. 2
ዋቢ መጽሐፍት........................................................................................................................................... 26
1
1. መግቢያ
ሆኖም ግን ምንም እንኳ የእግዚአብሔር ባሕርይና አኗር በራሱ ብቻ የሚታወቅ ረቂቅ አምላክ
ቢሆንም እኛ ፈጽሞ የማናውቀውና ስለ እርሱ ምንም ፍንጭ የሌለን ሆነን እንድንቀር
አልወሰነም፡፡ ከቸርነቱ የተነሳ ዓቅማችን ሊረዳው በሚችለው መጠን ማንነቱን፣ ህላዌውን፣
ባሕሪውን፣ መግቦቱን፣ ፈታሒነቱን፣ ፈቃዱን……… እናውቅ ዘንድ በተለያየ መንገድ
ገልጦልናል፡፡ ሃይማኖት የሚባለውም ይህ እግዚአብሔር በራሱ ፈቃድ እናውቀው ዘንድ ስለ
ራሱ የገለጠው መገለጥ ነው፡፡ ስለሆነም ሃይማኖት እግዚአብሔር ራሱን ለእኛ ያሳየበት መንገድ
የሰው ልጅ ሊቀበለው በሚችለው መጠን ስለ ራሱ ማንነት ለእኛ የገለጠው እውነታ ነው፡፡
2
2. የትምህርቱ ዝርዝር ዓላማ፡
የሰው ክብር የሚጀምረው ገና ከፍጥረቱ ነው፡፡ ከላይ እንዳየነው ሌሎችን ፍጥረታት በኀልዮና
በነቢብ ሲፈጥር ሰውን ግን ገቢርንም ጨምሮ አምሳሉ አድርጎ ፈጥሮታል፡፡ ሰው ማንን
ይመስላል ቢሉ ምላሹ እግዚአብሔርን ይሆናል፡፡ መላእክትን ጨምሮ ሌሎች ፍጥረታት በሙሉ
እግዚአብሔርን አይመስሉም እግዚአብሔርን የሚመስል ሰው ብቻ ነው ይህ ትልቁ ክብሩ ነው፡፡
ሁለተኛው የሰው ክብር ሕይወቱ ነው፡፡ እዚህ ላይ ለማብራራት በሥነ ፍጥረት ሦስት
ሕይወቶች አሉ፡፡ የመጀመሪያው የእንስሳት ሕይወት ሲሆን ሲፈጠሩ ይሰጣቸዋል ሲሞቱ ደግሞ
ሕይወታቸው እንደተወሰደ ይቀራል፡፡ የእንስሳት ሕይወት ሲፈጠሩ ይሰጣል በሞት ደግሞ
ይወሰዳል፡፡ ሕይወታቸው ሲወለዱ ይጀምራል ሲሞቱ ይጠናቀቃል፡፡ ሁለተኛው የመላእክት
3
ሕይወት ነው በተፈጥሮ ይሰጣቸዋል እንደ ተሰጣቸው ይቀራል ምክንያቱም አይሞቱም ሕያዋን
ናቸውና የመላእክት ሕይወት ሲፈጠሩ ይጀምርና እስከ ዘላለም ይቀጥላል፡፡ የሰው ሕይወት ግን
ከሁለቱ ሕይወቶች ተለይቶ እንደ እንስሳትም እንደ መላእክትም መኖር ተሰጥቶታል፡፡ የሰው
ሕይወት ሲወለድ ይሰጠዋል ሲሞት ይወሰዳል፡፡ እንደገና ደግሞ መልሶ በትንሣኤ ያገኘዋል፡፡
እንደ እንስሳት ሲወለድ ይሰጠዋል በሞት ይወሰድበታል እንደ መላእክት ደግሞ እንደገና
በትንሣኤ ሙታን ሲነሳ ይሰጠዋል እንደተሰጠው ይቀራል፡፡ እንደ እንስሳት ጥቂት ጊዜ መኖር
ይችላል እንደ መላእክትም ዘላለም መኖር ይችላል፡፡ ሰው እንደ እንስሳ አጭር ሕይወት ከልደት
እስከ ሞት ይኖረዋል፡፡ እንደ መላእክት ደግሞ በትንሣኤ ዘጉባኤ ጀምሮ ለዘለዘለም ይኖራል፡፡
የሰው ልጅ ምንም እንኳ ክብሩ እንዲህ ታላቅ ቢሆንም ከውድቀት በፊት የዋህና ገራገር
ኃጢአት የሚባለውን ነገር ጨርሶ አያውቀውም ነበር፡፡ አባታችን አዳምና እታችን ሔዋን
ከውድቀት በፊት ሁለቱም እርቃናቸውን ሆነው ሲተያዩ አይተፋፈሩም ነበር፡፡ ዘፍ 2÷25 በዚህ
ጊዜ ክፉውንና ደጉን ከሚያሳውቀው ዛፍ ስላልበሉ ክፉ ነገር አያውቁም ነበር፡፡ እባቢቱ ጥርጣሬ
የማታውቀውን እናታችን ሔዋንን በመዋሸት ያታለለቻት እርሷ ስለ ውሸት ስለ ማታለል ስለ
ጥርጣሬ የምታውቀው ነገር ስላልነበራት ነው፡፡ አዳምና ሔዋን ከውድቀት በፊት የኖሩት
የቅድስና ህይወት የተዋበ ነበረ እንደ መላእክት ምስጋና ምግባቸው ነበረ ድካም ጉስቁልና
መውጣት መውረድ ማጣት ማግኘት ማርጀት መድከም የሌለበት የደስታ ህይወት የነበራቸው፡፡
ነገር ግን ከውድቀት ኃጢአት በኋላ ፀጋቸውን፤ ቅድስናቸውንና መለኮታዊ ገጽታቸውን
አጥተዋል ተጎሳቁለዋል በመጨረሻም ሰውን ከፈጠረበት ጥበቡ ያዳነበት ጥበቡ ይበልጣል
የተባለለትን ታላቅ ድኅነት የተደረገው ለዚሁ የሰው ልጅ ነውና ከዚህ የሚበልጥ ምን ክብር
አለ እንላለን፡፡
4
አስገኝ አሳላፊ የሌለበት በአድነት በሦስትነት ያለ ሁሉን ቻይ የማይለወጥ አምላክ መኖሩን
ማመን ነው፡፡ (ሃይማኖተ አበው መቅደም)
ማመን ማለት በዋናነት እግዚአብሔር ሰውን ለማዳን በፈቃዱ ያደረገውን ነገር ሁሉ ማመን
መቀበል እና በአጠቃላይ እግዚአብሔር በቅዱሳት መጻሕፍት እንዲሁም በሥጋዌው የገለጸውን
የእውነት ትምህርት (ሃይማኖት) ሳይቆነጻጽሉና ሳያጎድሉ በምልአት መቀበል ነው ይኸውም
እግዚአብሔር ወደ ሰው ያደረገው የማዳን ጉዞ (ፍኖተ እግዚአብሔር) ሃይማኖት ይባላል፡፡ዘፍ.3፥
1
ሃይማኖት ማመን መታመን አመኔታ ማለት ነው፡፡ ይኸውም ቅድመ ዓለም ከሁሉ በፊት የነበረ
ፍጥረታትን የፈጠረ ማዕከላዊ ዓለም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛ ድህረ ዓለም ዓለምን ዓሳልፎ
የሚኖር ለእርሱ ግን አስገኝ አሳላፊ የሌለው በአንድነት በሦስትነት ያለ ሁሉን ቻይ አምላክ
እንዳለ ማመን ማለት ነው፡፡
5
ማመን ስንል እግዚአብሔር አንድ መሆኑን፣ በአንድነቱ ውስጥ ልዩና የማይመረመር ሦስትነት
ያለው መሆኑን ከሦስቱ አካላት አንዱ አካላዊ ቃል ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም
ሰው መሆኑን ሥግው ቃል ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ከመወለድ
ጀምሮ ለሰው ሲል ያደረውን፤ መጠመቁን፤ ዞሮ ማስተማሩንና መከራ መቀበሉን በመጨረሻም
በራሱ ፈቃድ ለእኛ ሲል መሞቱን፣ መቀበሩንና በሦስተኛው ቀን መነሣቱን እና በአርባኛው ቀን
ወደ ቀደመ ክብሩ ማረጉን….. ሁሉ ማመን ለመዳን አስፈላጊነ ነው፡፡ በአጠቃላይ ጌታችንና
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያስተማረውን ቃልና ትእዛዝ ማመንን ያዳነን አምላክ ማን
መሆኑን እርሱ ራሱ አምላካችን በገለጠልን መጠን ማወቅና ማመን ለመዳን ወሳኝ መሆኑን
ጌታችን በትምህርቱ ደጋግሞ ተናግሯል፡፡ ለአብነት ያህል ብንመለከት ከሳምራዊቷ ጋር
ሲነጋገር እርሷ “አባቶቻችን በዚህ ተራራ ሰገዱ፤ እናንተም ሰው ሊሰግድበት የሚገባው ስፍራ
በኢየሩሳሌም ነው ትላላችሁ” ባለችው ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ አላት….“እናንተስ
ለማታውቁት ትሰግዳላችሁ እኛ መዳን ከአይሁድ ነውና ለምናውቀው እንሰግዳለን፡፡ ነገር ግን
በእውነት የሚሰግዱ ለአብ በመንፈስና በእውነት የሚሰግዱበት ጊዜ ይመጣል፤ አሁንም ሆኗል፤
አብ ሊሰግዱለት እንደ እነዚህ ያሉትን ይሻልና፤ እግዚአብሔር መንፈስ ነው፤ የሚሰግዱለትም
በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል፡፡”ዮሐ 4፥20-24 እዚህ ላይ ጌታችን
የምናመልከውንና የምንሰግድለትን እንድናውቅና እውቀታችንም በኑፋቄና በስህተት በተበከለ
ትምህርት መሠረት ሳይሆን በእውነተኛ ትምህርት የተመሠረተ እምነት ሊሆን እንደሚገባ
አስተማረን፡፡ አስተምህሮው የተሳሳተ እምነት አምልኮው ትክክል ሊሆን አይችልምና፡፡
የምንሰግድለት አምላክ ሰዎች በኑፋቄ ትምህርታቸው በምናባቸው የሣሉትና በሃሳባቸው
የፈጠሩት ሳይሆን እኛ በሚገባ መንገድ ራሱን ለእኛ የገለጠውና እንድናውቀው ያደረገን
እውነተኛው አምላክ መሆን አለበት፡፡ አለበለዚያ እንደ ሳምራውያን “እናንተ ለማታውቁት
ትሰግዳላችሁ” የሚል ወቀሳ ያስከትልብናል፡፡ ስለዚህ ነው ጌታችን “እውነተኛ አምላክ ብቻ
የሆንህ አንተን የላከውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት”
በማለት እውነተኛ አምላክ የሆነውን እርሱን ማወቅ የዘለዓለም ሕይወት መሠረት መሆኑን
የተናገረው፡፡ ዮሐ 17፥3 ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስም “ሰው በጨለማ ስፍራ የሚበራን መብራት
እንዲጠነቀቅ ይህን ቃል እየጠነቀቃችሁ መልካም ታደርጋላችሁ” በማለት ለመጽሐፍ ቅዱሳዊና
ሐዋርያዊ ትምህርት ታላቅና ከባድ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ አስተምሮናል፡፡ 2ጴጥ 1፥19
6
ሐዋርያዊት የሆነች ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከጌታችንና ከሐዋርያት
የተቀበለችውንና የምታምነውን ሁሉ በፍጹም ልብ ማመን ያስፈልጋል እግዚአብሔር እኛን
ለማዳን ያደረገውን ልዩ ቸርነት እናምነው ዘንድ የገለጠውን እውነት የማያምን ሰው ሊድን
አይችልም፡፡
ማመን መቀበል እንጂ ማወቅ ብቻ አይደለም፡፡ ማመን ማወቅ ብቻማ ቢሆን ኑሮ አጋንንት
ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር መሆኑን ያውቃሉና በጸደቁ ነበር፡፡ (ማር1፥24 ፣
ማቴ 8፥29፣ ሉቃ 4፥34) ክርስቶስን ማመን ትእዛዙን ተቀብሎ እርሱን ተከትሎ መሄድ ነው፡፡
ስለሆነም ሃይማኖትና ምግባር ሰው የሚቆምባቸው ሁለት እግሮች ናቸው፡፡ ይህኛው ቀኝ ያኛው
ግራ ነውም አይባባሉም፡፡ ባንድ እግር አይኬድም አይቆምምና እኩል መታየት አለባቸው፡፡
ሃይማኖት ከራሱ ከእግዚአብሔር የተሰጠ ወይም የተገለጠ ነው፡፡ የሃይማኖት ምንጩ ሰማያዊ
አባት እግዚአብሔር ባይሆን ኖሮ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ማንነት በተመለከተ ደቀ
መዝሙሩ ስምዖን ጴጥሮስ የሚኖረው እውቀት በዘመኑ ከነበሩ ሌሎች ሰዎች የተለየና የተሻለ
7
ሊሆን አይችልም ነበር፡፡ ማቴ 16፥15-17 ነገር ግን ከሥጋና ደም (ከዚህ ዓለም ሥጋዊ
ምርምርና ፍለጋ) ውጭ የሆነው እግዚአብሔር እውነቱን ገለጠላቸው እንጂ፡፡ ለዚህ ነው
ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ ሲያስጠነቅቅ “እምነታችሁ በእግዚአብሔር ኃይል እንጂ በሰው ጥበብ
እንዳይሆን ቃሌም ስብከቴም መንፈስንና ኃይልን በመግለፅ ነበር እንጂ በሚያባብል በጥበብ ቃል
አልነበረም” በማለት የተናገረው፡፡ 1ቆሮ 2፥4-5
8
ሃይማኖት ከምግባር ጋር የተባበረ መሆን አለበት፡፡ ከተግባረ ሥጋ ከተግባረ ነፍስ አስቀድሞ
የቀናት ሃይማኖት ይማሩት ዘንድ ይገባል ሃይማኖት መሠረት ምግባረ ህንጻነውና 1ኛ ቆሮ.3፥
10 “ሃይማኖት መሠረት ናት የቀሩት ግድግዳና ጣሪያ ናቸው” እንዳለ ዩሐንስ አፈወርቅ ቅጽረ
መሠረቱ ያልጸና ቤት ከቀን ወራሪ ከሌሊት ሰባሪ አያድንም፡፡ ይህ ማለት ጥርጥርን ትቶ
ሃይማኖቱ ከጸና ምግባሩ ከቀና መምህር ተምሮ መጻህፍትን ተመልከቶ ሳይጠራጠሩ
በአንደበትም በልብም አሰተባብሮ አስተካክሎ ማመን ይገባል፡፡ ቅዱስ ዳዊት “አመኑህ ስለዚህ
ተናገርሁ” እንዳለ መዝ 115፥1 ቅዱስ ጳውሎስም “ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም
መስክሮ ይድናልና፡፡” እንዳለ /ሮሜ.10፥9፤ ዘዳግ. 30፥14 ለሰው ይምሰል በአፍ አምኖ በልብ
ቢክዱ እንደ ዩሁዳ እነደ አርዮስ መሆነ ነው፡፡ መከራ መቀበልን ፈርቶ በልብ አምኖ በአፍ
ቢክዱ ከንሰሐ በፊት እንደ ቅዱስ ጴጥሮስ መሆን ነው፡፡ ስለዚህ የልብ እመነት ብቻ አያድንም
የአፍ እምነት ብቻም አይጠቅምም ቅዱስ ጴጥሮስ በልቡ አምኖ ሳለ አይሁድን ከመፍራት
የተነሳ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን “አላውቀውም” ብሎ በካደ ጊዜ የልቡ እምነት ብቻውን
አልጠቀመውም፡፡ በአፍ በመካዱ መጸጸቱ እንባው ንስሐው ጠቀመው እንጂ፡፡ ማቴ. 26፥69-75፡፡
ይሁዳም ወደ ኢየሱስ ቀርቦ መምህር ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን ብሎ ጌታችን ኢየሱስ
ክርስቶስን በመሳም አሳልፎ በሰጠ ጊዜ የአንደበቱ እምነት አልጠቀመውም ከጥፋቱም ተምሮ
ንስሐ ለመግባት አልታደለም፡፡ማቴ.26፥14-16-49 ፤27፥3-5፡፡ ሃማኖት የነገር መለኮትን
ትምህርት የአምልኮትን ሥረአት ከእምነት የተነሳ የሚከናወንን ተጋድሎ ያጠቃልላል
2ኛጢሞ.4፥7'ይሁዳ.3፥20/፡፡ “ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃል በአፉም መስክሮ ይድናል”/ሮሜ.10፥
8-10'ማቴ.10፥32-33'ሉቃ.9'26/ የዘላለምሕይወትም ይኖረዋል፡፡/ዮሐ3፥16-18-36'5፥24'6፥40-
47'8፥51'11፥25-26/፡፡ የመንፈስ ቅዱስንም ጸጋ ይቀበላሉ፡፡/የሐዋ2፥38'ኤፌ1፥13-13-14/፡፡
ሃይማኖት /እምነት/ኖሮት ምግባር ባይሠራ ሃይማኖቱን የካደ ትምህርቱን ያሰደበ ነውና፡፡
9
4.1. ሃይማኖት መሠረት ነው፡-
እምነት በአንድ ክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ያሉ የጽድቅ ሥራዎች ሁሉ መሠረት ነው፡፡ ለዚህ
ነው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "አሚንሰ መሠረት ይእቲ ወካልአኒሃ ሕንጻ ውንድቅ እሙንቱ"
ሃይማኖት መሠረት ናት ሌሎች ግን ሕንፃና ግንብ ጣራ ግድግዳ ናቸው ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ
አፈወርቅ በ9ኛው ድርሳኑ በሕንፃና በግንብ መስሎ የተናገራቸውና ሌሎች ብሎ የጠቀሳቸው
ምግባርና ትሩፋት ናቸው፡፡ እምነት/ሃይማኖት/ ግን የእነዚህ መሠረት ናት፡፡ የአንድ ሕንፃ
ጥንካሬና ብቃት የሚታወቀው በመሠረቱ እንደሆነ ሁሉ የሰው ማንነቱ እና ሥነ-ምግባራዊ
ሕይወቱ ጠንካራ መሆኑ የሚታወቀው በእምነቱ ነው፡፡ እንደዚሁም የፈጣሪን መኖር ማመን
በሚሰሩት ምግባርና ትሩፋት የሚያምኑት ፈጣሪ የማያልፍ የማይጠፋ ዋጋን እንደሚሰጥ
ማመንና መቀበል ይቀድማል፡፡ 318ቱ ሊቃውንትም "ከሁሉ አስቀድሞ ሃይማኖት መማር
ይገባል” እንዳሉ፡፡ ይህንንም ቅዱስ ጳውሎስ "ወደ እግዚአብሔር የሚቀርብ ሰው አስቀድሞ
እግዚአብሔር እንዳለ ለሚሹትም ዋጋ እንደሚሰጥ በእምነት መቀበል ይቀድማል፡፡" ዕብ 11፥6 ፤
1ኛ ቆሮ 3፥ 11-15 "መሠረቱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ በዚህ መሠረት" እዚህ ላይ ቅዱስ
ጳውሎስ አለት በተባለው በቅዱስ ጴጥሮስ እምነትና ምሥክርነት ማመን ማቲ 16፥16 ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ የባህርይ አምላክ መሆኑን ማመን የሁሉ መሠረት መሆኑንና ከዚህ በኋላ
ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን በፈተና ጸንቶ ለዋጋ የሚያበቃ ሥራን መሥራት እንደሚገባ
ሲያብራራ ነው፡፡ የቀና ሃይማኖት የሌለው ምግባር ከጸብአ አጋንንት ከሥጋዊ ጠላት ከገሃነመ
እሳት አያድንም ፍጹም ኢአማኒ መሆን ነው፡፡ማር.16፥16 ህንጻው ጣራው ያልጸና ቤት
ከሌሊት ቁር ከመዓልት ሐሩር አያድንም በጎ ምግባር የሌለው ሃይማኖት ከጸብዐ አጋንንት
ከሥጋዊ ጠላት ከገሃነም እሳት አያድንም፡፡ ከዚህም ሌላ ነፍስ የተለየው በድን ማለት ነው፡፡ነፍስ
የተለየው ሥጋ ልንቀሳቀስ ልነሳ ልቀመጥ ልረፍ ሲል እደማይቻለው ሁሉ በጎ ምግባርም
የሌለው ሃይማኖት ድውይ ልፈውስ ሙት ላንሳ ታምራት ልሥራ ቢል አይቻለውም፡፡ ነፍስ
እደተለየው ሥጋ የሞተ ነው፡፡/ያዕ.2፥22/ ቅጽሩ መሰረቱ ህንጻው ጠፈሩ የጸና ቤት ከሌሊት
ሰባሪ ከቀን ወራሪ ከሌሊት ቁር ከመዓልት ሐሩር ያድናል፡፡ የቀና ሃይማኖት ከበጎ ምግባር በጎ
ምግባርም ከቀና ሃይማኖት አንድ ሆኖ የጸና እንደሆነ ከጽብአ አጋንንት ከሥጋዊ ጠላት
ከገሃነመ እሳት ይድናል እናም ፍጹም መንግስተ ሰማያት ይገባል፡፡ /ዮሐ.15፥5'ዕንባ.2፥
4'ት.ኢዩኤል 3፥5' ዕባ.11፥6/
10
4.2. ሃይማኖት ከዕውቀት በላይ ነው፡-
ሰው በስሜት ሕዋሳቱ መርምሮ ያውቃል፡፡ ጨለማውን ከብርሃን በዓይኑ አይቶ ጣፋጩን
ከመራራው በምላሱ ቀምሶ…ወዘተ በስሜት ህዋሳቱ ሲያውቅ ከዚህ ውጭ በርህቀት/ከእሱ
የራቀውን/ እና በርቀት/የረቀቀውን/ ያሉትን በስሜት ሕዋሳቱ መርምሮ በእውቀት ሊደርስባቸው
አይችልም፡፡ ይህም የሰው ልጅ ለእውቀቱ ድንበር ለአእምሮው ወሰን እንዳለበት ያሳያል፡፡ ነገር
ግን ወሰን ያለው ሰው ወሰን የሌለውን እግዚአብሔርን የሚያውቅበትና ከእግዚአብሔር ጋር
የሚገኛንበት እምነት ሊኖረው ይገባል፡፡ ስለዚህ በዚህ እምነት/ሃይማኖት/ ከእውቀት በላይ
መሆኑን እንገነዘባለን ማለት ነው፡፡ ለዚህም ቅዱስ ጴጥሮስ ማመን ከማወቅ በፊት እንደሆነ
መስክሯል፡፡ "እኛስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ አንተ እንደሆንህ አምነናል፤
አውቀናል" በማለትዮሐ 6፥69
11
ከቅዱሳት መጻሕፍት አንጻር ሃይማኖት ብዙ ዓይነት አገላለጽና አፈጻጸም ይኖረዋል፡፡ ሲጠቃለል
ሃይማኖት የሚለው ቃል ለዓለም ፈጣሪ አለው እርሱም ሰማይና ምድርን ፈጥሬአለሁ ብሎ
የተናገረ እግዚአብሔር ነው ብሎ በፍፁም ልብ ማመን ነው፡፡ ስለሆነም ዓለም ፈጣሪ፣ ሠራዒና
መጋቢ፣ መነሻና መድረሻ የተጀመረበትና የሚፈጸምበት አለው ብሎ ማመን ዳግመኛም
ለሚሠሩት ሥራ ሁሉ ዋጋ ከፋይ መኖሩን አውቆና አምኖ መሥራት በሁሉም ሰው ዘንድ
ታምኖ ሊኖር የሚገባው ነው፡፡ ይህም “እስራኤል ሆይ ስማ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ
እግዚአብሔር ነው፡፡” ዘዳ 6፥4 የሚለውን በማስታወስ ይህን አንድ አምላክ የማወቅ ግዴታ ነው፡
፡ ይህን አንድ አምላክ እንደሚገባ ማወቅና ማመን አንድ ነው ኤፌ 4፥4 እምነት የሚገለጽበት
ሥራ የመታመኛ መንገዱ ግን ብዙ ነው፡፡
13
6. ዘለዓለማዊ ደስታንና ክብርን የሚያስገኝ ነው "እርሱ ሳታዩት ትወዱታላችሁ አሁንም
ምንም ባታዩት በእርሱ አምናችሁ የእምነታችሁን ፈፃሜ እርሱም የነፍሳችሁን መዳን
እየተቀበላችሁ በማይነገርና ክብር በሞላበት ሐሴት ደስ ይላችኋል" 1ጴጥ 1፥8 የዚህ
አለም ደስታ አጭርና ጊዜያዊ ነው ጊዜያዊ ደስታ ደግሞ ከሃይማኖት ውጭ የሆኑ
ሰዎች የሚፈልጉትና የሚጠብቁት ነው፡፡ በሃይማኖት የሚኖር ሰው ግን ተስፋ
የሚያደርገው ጊዜያዊ ደስታን ሳይሆን ዘለዓለማዊ ደስታን ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሚገኘው
በእምነት ነው፡፡ "ሃይማኖት ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ የማናየውንም ነገር
የሚያስረዳ ነው፡፡"/ዕብ.11፥1 1ጴ. 1፥8-9
7. ሃይማኖት የሰው ልጅ በኑሮው በሕይወቱ ሁሉ ፈጣሪውን እግዚአብሔርን ደስ
የሚያሰኝበት በዚህም እንደ እግዚአብሔር ቸርነት ከገቡ መውጣት ካገኙ ማጣት
የሌለበትን ሰማያዊት መንግሥት ዘለዓለማዊት ርስት የሚወርስበት ነው፡፡
6. መንፈሳዊነት ለምን?
በሰው ሕይወት እንስሳዊ እና መላእካዊ ሁለት ተቃራኒ ባሕርያት አሉ በእንስሳዊ ባሕሪው
ይርበዋል ይበላል፤ ይጠማዋል ይጠጣል፤ ይታመማል፣ ይሞታል፣ ይፈርሳል ይበሰብሳል፡፡
በመላእካዊ ባሕሪው ደግሞ ምግበ ነፍስ የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል ይመገባል፣ ይዘምራል፣
ይቀድሳል እግዚአብሔርን ያመሰግናል መላእክት ሕያዋን ናቸው ሕያው ሆኖ ይኖራል፡፡ ነገር
ግን እንዚህ ሁለቱ በጣም ተቃራኒ ናቸው ሥጋ(እንስሳዊ ባሕርይው) ልብላ ስትል
ነፍስ(መላእካዊ ባሕሪው) የዘላለም ሕይወትን እያሰበች ልፁም ትላለች ስለዚህ እነዚህ ሁለት
ተቃራኒ የሆኑ የሰውልጅ ባሕሪያትን አጣጥሙ ለመኖር መንፈሳዊ/ክርስቲያን/ መሆን
ያስፈልጋል፡፡
14
መጋደል ነው፡፡ የሰው ልጅ ፍጡርነቱንና ዘላለማዊነቱን ካሰበ ሁል ጊዜ በትህትና ይህንን ዓለም
ለማሸነፍ የሚተጋበትን ጥበብ ይፈልጋል ይህ ጥበብ ደግሞ መንፈሳዊነት ነው፡፡
15
የእምነት ሰው የሚመላለስባቸው መንገዶች መጽሐፍ ቅዱስ የሃይማኖት ሰው እንዴት
መመላለስ እንዳለበት በምልአትና በስፋ ይገለጻል ይኸውም ሰው በእምነት ሲኖር ሊጓዝባቸው
የሚገቡ መንገዶችን ማወቅና መፈፀም እጅግ አስፈላጊና ወሳኝ ነው፡፡
እነዚህም፡-
16
እንደምንመለከተው አንድ እግዚአብሔር በስም በአካላት በግብር ሦስት የሚሉ ስለሆነ
ከቀደሙት ይለያሉ፡፡ ከዚህ አንጻር የሚለይ ይሁን እንጂ እግዚአብሔር የእነርሱ አማላክ ሊባል
የማያፍርባቸው ወዳጆቹ ብዙ ናቸው፡፡ ይሁን አንጂ በሰዎች ውስጥ ያለው መታመን
ስለሚለያይ ሰው የሚያፈራው የሃይማኖት ፍሬም ይለያያል፡፡ ጌታችን በወንጌል “እንዲህ ያለ
ታላቅ እምነት በእስራኤል ስንኳን አላገኘሁም” ማቴ.8፥10 ሲል ማመስገኑ በመታመናችን መጠን
እምነታችን እንደሚወሰን ለማጠየቅ ነው፡፡ ስለዚህ የክርስቲያኖች እምነት፡-
1ኛ. በይስሐቀ በረከት፡- “ይስሐቅ ሊመጣ ስላለው ነገር ያፅቆብና ዔሳውን በእምነት
ባረካቸው፡፡” ዕብ. 11፥20 ይላል፡፡ ፤ በሮሜ.9፥10-3 ላይም “…ይህ ብቻ አይደለም፤ ነገር
ግን ርብቃ ደግሞ ከአንዱ ከአባታችን ከይስሐቅ በጸነሰች ጊዜ ፥ ልጆች ገና ሳይወለዱ ፤
በጎ ወይም ክፉ ምንም ሳያደርጉ፤ከጠሪው እንጂ ከስራ ሳይሆኑ በምርጫ የሚሆን
የእግዚአብሔር ሀሳብ ይጸና ዘንድ፤ ለእርሷ ታላቁ ለታናሹ ይገዛል ተባለላት፡፡ ያዕቆብን
ወደድሁ ዔሳውን ግን ጠላሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ “ስለ አንድ መብል በኩርንቱን
መነጠቁ፡፡” በማለት ገልጦታል፡፡ እነዚህን ታሪኮች በዘፍ 25፥21-34 እና በዘፍ 27፥27-
29 እናገኛችዋለን ይሁን እንጂ ታሪኩን ባጭሩ አሥቀምጠን ወደ ምሥጢሩ እንሄዳን፡፡
19
ይህቺ ቀን በዘመነ አበው ትውፊት አባት ከመሞቱ በፊት ልጆቹን የሚባርክበት
የተለየች እለት ናት፡፡ ከዚህ በኋላ ያዕቆብን ዔሳው እንዳይገድለው ጠፋ ከብዙ ዘመንም
በኋላ በእናት እና አባታቸው ምክር መሠረት ዔሳው ያዕቆብን በአንድ ቀን ተዘርተን
“በአንድ ቀን የታጨድን ነን፡፡” ከታረቀ በኋላ ግን ልጆቹ ቀድሞ አላግባብ ጨጥክ አሁን
ደሞ የማይሆን ዕርቅ ታርቀህ ብለው በመቆጣት ሰይፍ አንሥተው አባታቸውን መንገድ
መሪ አድርገው ያዕቆብን ለመዋጋት ሄዱ፡፡ የአከባቢው ሰዎችም ያዕቆብን ይወዱ ነበርና
ወንድሙ ጦር አሳልፎ መምጣቱን በነገሩት ጊዜ ሁለት መቶ ቤተሰቦች ይዘው አራት
በር ባላት ቤት ሃምሳ ሃምሳውን በእያንዳንዱ ገጽ አሠልፎ ጠበቀው፡፡ ይሁዳ ባለበት
በር በኩል ዔሳው ልቡ ለቀስት ተመጭቶ ታየው፡፡ በማለት አነጣጥሮ ለአባቱ ሰጠው፡፡
ያዕቆብም ዔሳውን ገደለ ጦሩም ተበተነ፡፡ ከዚህ በኋላ የዔሳውን ዘሮች ሲያገብሯው
ኑረዋል፡፡ ታሪካቸውም እንዲህ ይደመደማል፡፡ ኩፋ.26፥47-48፡፡ አስቀድሞ
የተመለከተው ታዲያ ምንድን ነው ከታሪኩስ ያለው ምሥጥር በመጀመሪያ ያዕቆብ
የዔሳውን ብኩርና መግባቱ በእስራዔል አሕዛብ የመግባታቸው ምሳሌ ነው፡፡ ዔሳው
የእስራኤል የዕቆብም የህዝብ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ በኋላም ያዕቆብ ፍጹሙን በረከት
ከአባቱ መቀበል ለሕገ ነፍስ የሚያደላ በመሆኑ ወልደ እግዚአብሔር ከእርሱ ልጆች
ሰው ይሆን ዘንድ አስቀድሞ እግዚአብሔር ግብሩን አውቆ የመረጠው ስለሆነ ነው፡፡
ሁለተኛው ደሞ ያዕቆብ የጌታ ከያዕቆብ ጋር ያሉት የምእመናን ዔሳው የዲያቢሎስ
ከዔሳው ጋር ያሉ የአጋንንት የመስቀል ቀስት የሥልጣነ እግዚአብሔር ምሳሌ ነው፡፡
በድጋሚ ያዕቆብ የታላቁ ሊቅ የቄርሎስ ከእርሱ ጋር ያሉ ሁለት መቶ ሰዎች የሁለት
መቶው ኤጲስ ቆጶሳት'ዔሳው የንስጥሮስ ምሳሌዎች ናቸው፡፡
20
የባረካቸው ወንጌል ተገልጦለት አስቀድሞ አይቶ በሚበልጠው የመስቀል በረከት
ሲባርካቸው ነው፡፡
እነዚህን ሁለት ማስረጃዎች አስርጅ አድርገን የጠቀስነው ኦሪት ከመመስረቷ በፊት በተስፋ
የጸኑትንና ስለ መንግሥት ሰማያትም መከራ የተቀበሉ ቅዱሳን እንደነበሩ ለማሳየት ያክል ነው፡
1. ውስጣዊ ስብእና/ተግባር/
ውስጣዊ ተግባር ማለት በሥጋና በመንፈስ መካከል ከውስጥ የመነጨ መልካምም ይሁን
መጥፎ ስሜት ያስገኘው ሀሳብ ማለት ነው ይህ ሀሳብ ቁርጥ ሀልዮና ነቅዓ ሀልዮ በመባል
በሊቃውንቱ ዘንድ ይታወቃል፡፡ ይህ ሐሳብ እንደ ይዘቱ መጥፎ ከሆነ ያስቀጣል፤ መልካም
ከሆነም ያሸልማል፡፡ ይህን ውስጣዊ ስሜትን ምክንያት በማድረግ በሥጋዊና መንፈሳዊ ሐሳብ
መካከል ጣልቃ እየገቡ ዓላማን ለማስቀየር የሚጥሩ ኃይሎች ብዙዎች ናቸው፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ስለዚህ ጉዳይ "እንግዲያስ መልካሙን አደርግ ዘንድ ስወድ በእኔ ክፉ
እንዲያድርብኝ ሕግን አገኛለሁ፡፡ በውስጡ ሰውነቴ በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለኛልና፡፡ ነገር
ግን በብልቶቼ ከአእምሮዬ ሕግ ጋር የሚዋጋውንና በብልቶቼ ባለ ኃጢአት የሚማርከኝን ሌላ
ሕግ አያለሁ፡፡" ሮሜ 7÷21 በማለት በስብዕና ውስጥ ታላቅ ውጊያ መኖሩን ከራሱ ተሞክሮ
በመነሳት ሰዎች ያውቁት ዘንድ ለሮሜ ሰዎች አስገንዝቦአል፡፡
21
አይውጣ" 1ኛሳሙ2÷ 3 እየጠቀሰ ቻሉ ልባችሁንም አጽኑ ክፉ ንግግር ከአንደበታችሁ
አይውጣ፡፡ ፀሐይ ሳይወጣም ቁጣችሁን አብርዱ የምትሠሩትን ሁሉ የይቅርታ አምላክ
በሚመሰገንበት መልኩ አድርጉ ብሏል፡፡
ሥራ ሁሉ መጥፎ ስሜትን በዝምታ ገትቶ ቁጣን አብርዶ አንደበትን አለዝቦ ለሰው ሳይሆን
እግዚአብሔርን ደስ ያስኛል ተብሎ ከተሠራ እንደ አቤል መሥዋዕት ዋጋን ያሰጣልና በቀልን
በመተው ሊሠሩት ያስፈልጋል፡፡ ክርስቲያን ከአረማውያን የሚለዩበትም ለዘላለም ይኖሩ ዘንድ
በቀልና ፍርድን ለእርሱ ትተው ለክፉዎቹ ሁሉ መልካም በማድረጋቸው ነው፡፡
2. ውጫዊ ስብእና/ተግባር/
ስለዚህ የአንድ ክርስቲያን ውስጣዊ እና ውጫዊ ስብእናዎቹ የሥነ ምግባር መርሆች በሆኑት
ፍቅር፤ ሰላምና ትህትና የተዋቡ ሊሆን ይገባዋል፡፡
1. ፍቅር
23
2. ሰላም
ሰላም በሰዎች ልቦና ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔርን ህብረትና እስከ ፍፃሜ ድረስ ያለውን
ግንኙነት በዚህ የተነሳ የሚገኘውን መረጋጋት ያመለክታል፡፡ ሰላም የማንኛውም መልካም ነገር
መግቢያ በር ነው፡፡ ስለዚህ ሰላም ከሌለ በመልካም ፈንታ ክፉ መልስ እየጸና ይሄዳል እንጂ
መልካም ሥራ ሊኖር አይችልም፡፡ ማንኛውም ሰው ያለ ሰላም የጠየቀውን ማግኘት መውያየት
ወዘተ አይችልም፡፡
24
ስለዚህ አንድ ክርስቲያን የሰው ሕይወት መሰረት የሆነውን ሰላም መጠበቅ፤ ለሰዎች ማሰብ
ከሰውምይሁን ከእግዚአብሔር የሚመጣውን ተግሳጽና ቅጣት ለመቀበል ከልቡና ገርነት
በመነጨ ፍላጎት መዘጋጀት፤ በሰዎቸች አነሳሽነት የሚመጣውን የመጥፎ ሐሳብ ምክር
መቋቋም፤ ከሁሉም በፊት ረስንሰላም አድርጎ ሰዎች ሁሉ ሰላማውያን እንዲሆኑ መጸለይ
ይኖርበታል፡፡ ማቴ 5÷45
3. ትሕትና
25
መቀበል የጊዜውን መከራ በሚመጣው ደስታ መርሳት ራስን በትህትና ዝቅ ማድረግ እና
የመሳሰሉት ከክርስቲያናዊ ስብእና መገለጫዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
ዋቢ መጽሐፍት
ርጢን ከመጋቤ ሐዲስ እሸቱ ዓለማየሁ
አንድ እረኛ አንድ ምንጋ ከቀሲስ አለማየሁ ሞገስ ደረሰ
ኮክሐ ሃይማኖት መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ
ዶግማ ትምህርተ ሃይማኖት ከቀሲስ ታደሰ አይፎክቁ
ሁለቱ ኪዳናት ከመርጌታ ኃየሎም
ክርስቲያናዊ ሥነ-ምግባር በሊቀ ጉባኤ አባ ገ/መስቀል
መድሎተ ጽድቅ ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ
መንፈሳዊ ሰው አያሌው ዘኢየሱስ እንደተረጎመው
ማህቶተ ዘመን በመምህር በሙሉ አስፋው
26