Professional Documents
Culture Documents
@eotc Books by PDF
@eotc Books by PDF
ክፍል ፩(1)
የእግዚአብሔር ቃል አንደበትን የሚያጣፍጥ ህሊናን በበጎ ነገር የሚማርክ ውስጥን እየወቀሰ የሚያርም
ነው! ስለዚ ዘውትር ልንበላውና በአፋችን ሊጣፍጥ ይገባል።መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት ማንበብ
እንዳለብን ወደሚጠቁመን መሠረታዊ ነጥብ ስናልፍ፦ሁለት መሠረታዊ ነገሮች መረዳት አለብን።
1. አፍአዊ(ውጫዊ) ዝግጅት
2. ውስጣዊ(የውስጥ) ዝግጅት
1. አፍአዊ ዝግጅት
አፍአዊ ዝግጅት የሚባለው መጽሐፍ ቅዱስን የሚያነበው አካል ለማንበብ ከመቅረቡ በፊት ከልቦናውና
ከአይምሮው ውጪ ሊያዘጋጀውና ለያመቻቸው የሚገባን የሚያጠቃልል ነው።አፍአዊ ዝግጅትን የግል
ዝግጅትና የማህበር ዝግጅት በማለት በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል።
የግል ዝግጅት (የግል ንባብ) አንባቢው በግሉ ሊያረግ የሚገባውን ሁሉ የሚመለከት ነው።ማለትም
መጽሐፍ ቅዱስ ዕለት በዕለት የኑሯችን የመንፈስ ምግብ በመሆኑ ሊለየን አይገባም።በሕይወታችን ዋጋ
ከፍለን መግዛትም ሆነ ማንበብ ካለብን መጽሐፍ ቅዱስ ነው።መጽሐፍ ቅዱስ ከሌለን እራሳችንን
የምንተረጉምበትን ማብራሪያ አልያዝንም ማለት ነው።ለሰዎች የሕይወታቸው የመጀመሪያው ሀብት
መጽሐፍ ቅዱስ ነው።መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ የመጽሐፍ ቅዱስ ባለቤት መሆን ግድ ነው።
👉ማስታወሻ መያዝ
አበው በብሂላቸው "በቃል ያለ ይረሳል በመጽሐፍ ያለ ይወረሳል" እንዲሉ በቃል ብቻ ማንበብ ለጊዜው
በአንባቢው ህሊና ውስጥ ከሚፈጥረው ስሜት በስተቀር ሊረሳ ይችላል።እንዲህ አይነቱን ችግር
ለመፍታት ማስታወሻ መያዝ ጥቅሙ የላቀ ነው።መጽሐፍ ቅዱስን ሲያነብ ማስታወሻ የሚይዝ አንባቢ
ለሚጠይቁት ሁሉ መልስ ለመስጠት እየተዘጋጀ መሆኑን መዘንጋት የለበትም። መጽሐፍ ቅዱስ
የሕይወታችንን ታላቁን ጥያቄ የምንመልስበት በመሆኑ ተገቢ ነው።
👉የማህበር ዝግጅት
ይህ ዝግጅት መጽሐፍ ቅዱስን በአንድ ቦታና ጊዜ በጋራ የሚያነቡ ሰዎች ሊያደርጉት የሚገባቸውን
ዝግጅት ያጠቃልላል።
2. ውስጣዊ ዝግጅት
ውስጣዊ ዝግጅት የሚባለው አንድ ሰው ቅዱሳት መጻሕፍትን ለማንበብ ከመቀመጡ በፊት በልቦናው
ሊያደርገው የሚገባውን ዝግጅት ነው ሚያመለክተው
ጠቅለል ባለ መልኩ መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ፦
በቀጣይ
📖የግዕዝ ቁጥር
ክፍል ፪(2)
መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ለሚሻ ሰው አከፋፈሉን ማወቅ ግድ ይለዋል የመጽሐፍ ቅዱስ አከፋፈል
ሳይታወቅ የሚደረግ የንባብ ሂደት ወደማያውቁት ሀገር ገብቶ እንደ መቸገር ይቆጠራል።የንባብን አካሄድ
ለማወቅ የመጀመሪያው በር የመጽሐፍ ቅዱስን አከፋፈል ማወቅ ነው።
እነዚህ በሁለት ተከፍለው የምናያቸው ብሉይ ኪዳንና ሐዲስ ኪዳን የሰው ልጅ የሕይወቱ ምስጢር
መገኛ ናቸው።ብሉይ ኪዳንን ለብቻው ከፍለን ስናይ፦
ብሉይ ኪዳን በአራት ይከፈላል
1. የሕግ ክፍል
2. የታሪክ ክፍል
4. የትንቢት መጻሕፍት
ብሉይ ኪዳንን ስናነብ እነዚህን አራት ዓይነት በብሉይ ኪዳን የሚገኝ የመንፈስ ምግቦችን ለይቶ
ማስተዋል ያስፈልጋል።በትክክለኛ አከፋፈላቸው ሲነበቡ አይደባለቁም ግብና አቅጣጫ ያለው ንባብ
እናነባለን።በአራት የከፋፈልናቸውን የብሉይ ኪዳን አከፋፈል እንመልከት!
ብሉይ ኪዳን
1. የሕግ መጻሕፍት፦
=>ኦሪት ዘፍጥረት
=>ኦሪት ዘጸዓት
=>ኦሪት ዘሌዋውያን
=>ኦሪት ዘኁልቅ
=>ኦሪት ዘዳግም
2. የታሪክ መጻሕፍት
=>መጽሐፈ ኢያሱ
=>መጽሐፈ መሳፍንት
=>መጽሐፈ ሩት
=>1 ኛ ሳሙኤል
=>2 ኛ ሳሙኤል
=>1 ኛ ነገስት
=>2 ኛ ነገስት
=>1 ኛ ዜና መዋዕል
=>2 ኛ ዜና መዋዕል
=>መጽሐፈ ዕዝራ
=>መጽሐፈ ነህምያ
=>መጽሐፈ አስቴር
=>መጽሐፈ ኢዮብ
=>መዝሙረ ዳዊት
=>መጽሐፈ ምሳሌ
=>መጽሐፈ መክብብ
4. የትንቢት መጻሕፍት
=>ትንቢተ ኢሳይያስ
=>ትንቢተ ኤርምያስ
=>ትንቢተ ሕዝቄል
=>ትንቢተ ዳንኤል
=>ትንቢተ ሆሴዕ
=>ትንቢተ አሞፅ
=>ትንቢተ ሚክያስ
=>ትንቢተ ኢዩኤል
=>ትንቢተ አብድዩ
=>ትንቢተ ዮናስ
=>ትንቢተ ናሆም
=>ትንቢተ ዕንባቆም
=>ትንቢተ ሐጌ
=>ትንቢተ ዘካርያስ
=>ትንቢተ ሚልክያስ
1. የወንጌል ክፍል
2. የታሪክ ክፍል
3. የመልዕክት ክፍል
ሐዲስ ኪዳን
1. የወንጌል ክፍል
=>የማትዮስ ወንጌል
=>የማርቆስ ወንጌል
=>የሉቃስ ወንጌል
=>የዮሐንስ ወንጌል
2. የታሪክ ክፍል
=>የሐዋርያት ሥራ
3. የመልዕክት ክፍል
=>1 ኛ እና 2 ኛ ጴጥሮስ
=>1 ኛ, 2 ኛ እና 3 ኛ ዮሐንስ
=>የያዕቆብ መልዕክት
=>የይሁዳ መልዕክት
4. የትንቢት ክፍል
=>የዮሐንስ ራዕይ
ከላይ እንደተገለጸው ብሉይ ኪዳንና ሐዲስ ኪዳን እንዴት እንደሚከፈል ግንዛቤ በሚሰጥ መልኩ
አይተናል።መጽሐፍ ቅዱስን የሚያነብ በመጀመሪያ ሊረዳ የሚገባው መጽሐፍ ቅዱስ በሥርአቱና
በየክፍሉ የተቀመጠ መሆኑን ነው።በመቀጠል የሚያነበው ክፍል ምን እንደሆነ ከአከፋፈሉ በስፋት
መረዳት መቻል ነው።የሐዲስ ኪዳንና የብሉይ ኪዳንን አከፋፈል አጠቃለን ስንደምራቸው 8 ናቸው።
የብሉይ ኪዳንና የአዲስ ኪዳንን መጻሕፍት አከፋፈል ለይቶ የሚያውቅ መጽሐፍ ቅዱስ አንባቢ
የሚሄድበትን አቅጣጫ የሚያውቅ ሰው ይመስላል። መጽሐፍ ቅዱስን ስናነብ ከላይ ከተገለጸው
አከፋፈል ተረድቶ መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ወደ ብዙ እውቀትና ጥበብ ያሻግራል።
በቀጣይ
📖የግዕዝ ቁጥር
አቡ ናክ(ወንዴ)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር