Professional Documents
Culture Documents
B Amhara NNP 2015 Plan
B Amhara NNP 2015 Plan
ነሃሴ/2014 ዓ.ም
ባህር ዳር
1. መግቢያ
0
"ህብረ ብሄራዊ አንድነታችን ለዘላቂ ሰላማችን"
የኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት የፀደቀበትን ህዳር 29 ቀን ለመዘከር እለቱ በየዓመቱ የብሔረሰቦች ቀን ሆኖ እንዲከበር
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሚያዚያ 21 ቀን 1998 ዓ.ም መወሰኑ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ውሳኔ በኋላ እለቱ
ላለፉት አስራ ስድስት አመታት በመከበሩ ህብረተሰቡን በበርካታ ዘርፎች ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ በዓሉ
በተለያዩ ዝግጅቶች በየዓመቱ በመከበሩ በክልላችን የሚገኙ የተለያዩ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ማንነት
በሚገባ እንዲታይና እንዲታወቅ በማድረግ ረገድ የላቀ አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡ በተለይም የክልሉ ህዝብ ከሌሎች
ክልሎች ብሔሮች ጋር የእርስ በእርስ ግንኙነት እንዲጠናከርና ባህላቸው፣ አልባሳቶቻቸው፣ እሴቶቻቸውን
በማስተዋወቅ የእርስ በእርስ ግንኙነት እንዲፈጠር በማድረግ ረገድ የበዓሉ ሚና የላቀ ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር የበዓሉ
መከበር ዋነኛ ፋይዳ በአገራችን ሕገ መንግስትና ሕገ መንግሥታዊ ስርዓት ዙሪያ ህብረተሰቡ የተሻለ ግንዛቤ
እንዲያገኝ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡
በዚህ መሰረት እስካሁን ሲከበር የቆየው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ሁሉም የአገራችን
ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ማንነታቸው እንዲከበርና በቀጣይ ለፍትህ፣ ነፃነትና ለዲሞክራሲ ስርዓት መከበርና
መረጋገጥ በጋራ ጠንክረው እንዲሰሩ የሚነሱበትን መሰረት የጣለ ነው ብሎ መውሰድ ይቻላል፡፡
በኢፌዲሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ መነሻነት በ 1999 ዓ.ም ሕዳር 29 ጀምሮ መከበር የጀመረው የኢትዮጵያ
ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ላለፉት 16 ዓመታት ሲከበር በዓሉን በባለቤትነት በማስተባበር እንደ
ክልል ምክር ቤት ኃላፊነቱን ሲወጣ ቆይቷል፡፡
ስለሆነም የ 17 ኛው በዓል አከባበር ከዚህ ቀደም የተከበሩ በዓላት ልምዶችን ውስንነቶችንና ድክመቶች በማረም
በሲዳማ ክልል አስተናጋጅነት በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት እንዲከበር በፌደሬሽን ምክር ቤት ተወስኗል፡፡ በዚህ
መሠረት በአሉ “ህብረ ብሄራዊ አንድነታችን ለዘላቂ ሰላማችን” በሚል መሪ ቃል ይከበራል፡፡ የኢፌዴሪ
ፌዴሬሽን ምክር ቤት የላከውን እቅድም መነሻ በማድረግ በአማራ ክልል የበዓሉን አከባበር በተመለከተ ይህ
ክልላዊ መሪ እቅድ ተዘጋጅቷል፡፡
2. የእቅዱ መነሻዎች
1
"ህብረ ብሄራዊ አንድነታችን ለዘላቂ ሰላማችን"
2.1. ሕገ መንግስታችን የፀደቀበትን ቀን በመዘከር የምክር ቤቱ ውሳኔ እንደ ዕቅድ መነሻ
ለኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች መብት መከበር ሕገ መንግሥታዊ ዋስትና ያረጋገጠው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ
ሕገ መንግሥት የፀደቀበትን ህዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም ለመዘከር የፌዴሬሽን ምክር ቤት በወሰነው ውሳኔ መሠረት
እለቱ ከህዳር 29 ቀን 1999 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል፡፡ የአገራችን ብሔሮች፣
ብሔረሰቦችና ህዝቦች በሚገኙበት በዚህ በዓል የጋራ መድረክ በመፍጠር ልምዳቸውን፣ ተሞክሮቻቸውን፣
ባህላቸውንና ማህበራዊ አኗኗራቸውን በማሳየት ያለውን ብዝሃነትና ህብር በሚገባ ጐልቶ እንዲወጣና
ኢትዮጵያዊነት የሁሉም ህብራዊነት መሆኑን የሚረጋግጥበት ነው፡፡ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን መከበሩ
ሁሉም ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ማንነታቸው እንዲከበርና በቀጣይ ለፍትህ ነፃነት ለዲሞክራሲ ስርዓት
መከበርና መረጋገጥ በጋራ ጠንክረው እንዲሰሩ የሚነሱበት ሆኗል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የብሔሮች፣
ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ምክር ቤት በመሆኑ በጉዳዩ ባለቤትነት የሁሉንም ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ማንነት
ጐልቶ እንዲወጣ እያደረገ ይገኛል፡፡
በዚህ ረገድ የምክር ቤቱን ውሳኔ በመተግበር ላለፉት 16 ዓመታት በበዓሉ የተገኙት ውጤታማ ተግባራት በተለይም
ህዝባዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ የታየው መነቃቃት ቀላል ባለመሆኑ የፌዴሬሽን ምክር ቤት እለቱ በየዓመቱ
እንዲዘከር መወሰኑ እንደመነሻ ተይዟል፡፡
ቡድን ክልላችን ብሎም አገራችን አደጋ ላይ በመጣል የኢትዩጵያን ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን
ለመበታተን በከፈተዉ የሕልውና አደጋ ለመመከት ሁሉም ኢትዩጵያዉያን በአንድ የቆሙበት ወቅት መሆኑ
በአሉን ለማክበር የራሱ የሆነ ተግዳሮትና መልካም አጋጣሚዎች የነበሩ ቢሆንም ተግዳሮቱን ወደ መልካም
አጋጣሚ በመቀየር የበዓሉን አከባበር ከሕልውና ማስከበር ዘመቻው ጋር በሚመጋገብ ሁኔታ እቅዱን
በመከለስ በዓሉ የሕዝቦችን አንድነትና ወንድማማችነትን የበልጥ ሊያጎለብት በሚችል አግባብ ተከብሯል፡፡
ለዚህም ማሳያ ተደርጎ የሚወሰደዉ የህልዉና ዘመቻዉን ለመደገፍ በዓሉን አስመልክቶ በተደረጉ የንቅናቄ
ስራዎች በደም ልገሳ 9,510 ዩኒት ደም ለማሰባሰብ ተችሏል ፣ የዘማች ቤተሰቦችን ከመደገፍ አኳያ ለ 120
3. የበዓሉ ዓላማ
4. በክልል ደረጃ በትምህርት ሴክተሮች ኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የእርስ በእርስ ትስስር
በማጠናከር በብዝኃነት ላይ የተመሰረተ ሕብረብሔራዊ አንድነትን ሥር እንዲሰድ ለማድረግ የገቡትን ቃል
ኪዳን በማደስ በአዲስ መንፈስ እንዲነሳሱ ማድረግ ነው፡፡
5. የበዓሉ ግብ
በክልል ደረጃ በትምህርት ሴክተሮች የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አከባበር አገራዊ
አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከናወናል፡፡
6. የበዓሉ መሪ ቃል
በ 2015 ዓ.ም ህዳር ወር ላይ የሚከበረው 17 ኛው ኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ወቅታዊ
እና አገራዊ ሁኔታዎችን ከግምት በማስገባት ከአገራዊ የምክክር ሂደቱ ጋር በሚመጋገብ መልኩ ማክበር ያስፈልጋል፡፡
ስለሆነም በዓሉ ኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የሚያቀራርቡ፣ የሚያስተሳስሩ እና በብዝሃነት ላይ
የተመሰረተ ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ስር እንዲሰድ እና እንዲዳብር በሚያደርጉ ተግባራት እና ኩነቶች ላይ
የሚያጠነጥን ለማድረግ ከፌደረሽን ምክር ቤት በተላከው መነሻ መሰረት የበአሉ መሪ ቃል “ህብረ ብሄራዊ
አንድነታችን ለዘላቂ ሰላማችን” ነው፡፡
በዚህ ኮሚቴ ስር የተቋማትን የበዓል አከባበር ሁኔታ የሚያስተባብሩ የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል፡
3
"ህብረ ብሄራዊ አንድነታችን ለዘላቂ ሰላማችን"
6.1.1 በቅድመ ዝግጅት የሚከናወኑ ተግባራት
የክልል ትምህርት ቢሮ እቅድን መነሻ በማድረግ ዞናዊ መሪ እቅድ ማዘጋጀት፣
የዞኑ አብይ ኮሚቴ በእቅዱ ላይ ዉይይት በማድረግ ማጸደቅ
በአብይ ኮሚቴዉ እቅድ መነሻ ልዩ ልዩ ኮሚቴዎችን አደራጅቶ ወደ ስራ ማስገባት፤
ከክልል ትምህርት ቢሮ የሚላከውን ርእስ መነሻ በማድረግ ለሲምፖዚየም እና በየደረጃዉ ለሚደረጉ
በትምህርት ተቋማት ስለሚኖረው የበዓል አከባበር ዝግጅቶች የበዓሉን መሪ ዕቅድ ተከትሎ ያስፈጽማል፡፡
አደረጃጀታቸውን ተከትለው በጋራና በተናጠል በዓሉን ስለሚያከብሩበት ሁኔታ ዕቅድ ያዘጋጃል ያስፈጽማል፡፡
ለትምህርት ተቋማት የሚውሉ የመወያያ ጽሁፍ ያዘጋጃል፣
እያንዳንዱ ተቋም ለበዓል አከባበር የሚያስፈልገውን ወጭ እንዲሸፍን ያደርጋል፡
በ 1 ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ፣ በ 2 ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች ስለሚኖረው
የበዓል አከባበር ዝግጅቶች በበዓሉን መሪ ዕቅድ መሰረት እቅድ ያዘጋጃል፤ ያስፈጽማል፡፡
የስራዎቹን ሪፖርት ለአብይ ኮሚቴው ያቀርባል፤
ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ የዞኑን የሚዲያ አካላት በቂ ኦሬንቴሽን በመስጠት በተለያዩ ፕሮግራሞች
የአስተምህሮ ስራ እንዲሰሩ ማድረግ፣ (ወጣቶችን ሴቶች ወ.ዘ.ተ መድረኮች)
ሁሉም የሚዘጋጁ ሁነቶች እና ውይይቶች በልዩ ሁኔታ የዜና ሽፋንና ፕሮግራሞችን እንዲሰሩ ከሚዲያ
አካላት ጋር አስቀድሞ ስምምነት ላይ በመድረስ የሚዲያ ሽፋን በትኩረት ይሰራል፤
በክልል ትምህርት ቢሮ የሚላኩ የበዓሉን መልዕክት የሚያስተላልፍ ልዩልዩ ህትመቶችን የማሰራጨት
ሥራ ይሰራል፤
ጋዜጣዊ መግለጫዎች እንዲሰጡ ማመቻቸት
የበዓሉ አስተባባሪ ኮሚቴ በየጊዜው እየተገናኘ ስራዎችን ይገመግማል፣ ይከታተላል፣ ድጋፍ ይሰጣል፤
የዞኑ ምክር ቤት የበዓል አከባበሩን እቅድ እሰከታች አደረጃጀት በማውረድ ድጋፍና ክትትል ያደርጋል፤
እቅዱ ወደስራ መግባቱን በግብረ-መልስ፣ በስልክና በአካል ድጋፍ ያደርጋል፤
5
"ህብረ ብሄራዊ አንድነታችን ለዘላቂ ሰላማችን"
እያንዳንዱ የኮሚቴ አባል የሚጠበቅበትን ያለመወጣት፤
በተሻለ የጸጥታ ሁኔታ ውስጥ ባሉ ወረዳዎች እና ትምህርት ቤቶች በትኩረት ተግባራት እንዲፈጸሙ
ማድረግ፤
ሁሉም ባለድርሻ አካላትን ከእቅድ ጀምሮ ማሳተፍ፤
በየወቅቱ መረጃዎችን መለዋወጥ፤
ጠንካራ ድጋፍና ክትትል ማድረግ፤
ግብረመልስ መስጠትና ያልተተገበረውን በግምገማ ማስተካከል
o የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት
የፅዳት ዘመቻ
o የስፖርት ዉድድር ማካሄድ
6
"ህብረ ብሄራዊ አንድነታችን ለዘላቂ ሰላማችን"
ተ.ቁ. ዋና ዋና ተግባራት የክንውን ጊዜ
በግቢዉ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ ከጥቅምት 8-ህዳር 30/2015
5.
የጥያቄና መልስ ዉድድር እና የስነ ፅሁፍ ዝግጅት ማቅረብ እስከ ህዳር 15/2015
6.
7. የአብይ ኮሚቴ አባል የሆኑ የክልል ቢሮዎች የአፈጻጸም ሪፖርት ይቀርባል፤ እስከ ታህሳስ 15/2014
8. የዞኖች የአፈጻጸም ሪፖርት ይቀርባል እስከ ታህሳስ 10/2015
የበዓሉ ክንውን የሚያሳይ አጠቃላይ ሪፖርት በክልሉ አብይ ኮሚቴ ይገመገማል፣ እስከ ታህሳስ 20/2015
9.
ለቀጣይ ዓመት ትምህርት በሚወሰድባቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ይቀመጣል