You are on page 1of 22

የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ.

፲፥፲፬”

የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

የኦሪት ዘጸአት ትርጓሜ

ሚያዚያ 2014
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 1 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

ምስጋና
 ‹‹ምስጋና በሰማይ ለእግዚአብሔር ይሁን በምድርም ላይ ሰላም ለሰውም እርሱ በሚፈቅደው›› (አንቀጸ ብርሃን)
 ‹‹ቅድስት ሆይ ብፅዕት ነሸ የተመሰገንሽና የተባረክሽ ነሽ……. አምላክን የወለድሽ እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ ከተለዩ የተለየሽ የመለኮት ማደሪያ ነሽ …. ቅድስት ሆይ
ልጅሽን ይቅርታ ያድለን ዘንድ ለምኝልን፡፡›› አሜን (አንቀጸ ብርሃን)

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 2 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ክፍል ፩
የኦሪት ዘጸአት መጽሐፍ መግቢያ
1. ኦሪት ዘጸአት

1.1. የኦሪት ዘጸአት መጽሐፍት ትርጉም

1.2. (ኦሪት ዘጸአት) ጸሐፊው


የኦሪት ዘጸአት ጸሐፊ ሙሴ ነው። ሁለተኛው የሙሴ መጽሐፍ የሙሴ ነው። ሙሴ የኦርት ዘጸአት እንዲጽፍ በእግዚአብሔር ታዘዘ። ሙሴም እርሱ እንደጻፈ በግልጥ
ተጠቅሷል: (ዘጸ. 17፡14፤ 34፡1-5):: የኦሪት ዘጸአት ጸሐፊ ሙሴ መሆኑን ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በግልጥ ተናግሯል:: “ሙሴ። አባትህንና እናትህን አክብር፤
ደግሞ። አባቱን ወይም እናቱን የሰደበ ፈጽሞ ይሙት ብሎአልና።” ማር. 7፡10

1.3. ኦሪት ዘጸአት መጻሕፍት የተጻፉበት ዘመን


የኦሪት ዘጸአት የተጻፈው በ 1400 ዓ.ዓ. አካባቢ ነው። ከክርስቶስ ልደት በፊት በባቢሎን በግዞት ውስጥ እንደተጻፈ ይነገራል::

1.4. ኦሪት ዘጸአት ታርክና ይዘት


ዘጸአት ሁለተኛው የሙሴ መጽሐፍ ሲሆን “ጸአት” ማለት መውጣት ማለት ነው፡፡ መውጣት ሲባል አንድን ቦታ ለቆ መውጣት ወይም ከባርነት ነፃ መውጣት ሊሆን
ይችላል፡፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ለእግዚአብሔር የተለዩት እስራኤላውን ከግብጽ ባርነት ነፃ እንደወጡና ወደ ከነዓን ምድር እንደተጓዙ እናነባለን፡፡ በአጠቃላይ
እስራኤላውያን ከግብጽ የባርነት ኑሮ ነፃ መውጣታቸውንና ወደ ተስፋዪቱ ምድር ጉዞ መጀመራቸውን የሚተርክ መጽሐፍ ስለሆነ “ዘጸአት” ተባለ፡፡ 

1.4.1. የኦሪት ዘጸአት ዋና ዋና ታሪኮች


 ዋናው የኦሪት ዘጸአት ታሪክ የሚጀምረው ከሙሴ ጋር መሆኑን ይታወቃል፡፡

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 3 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

1.4.1.1. የሙሴ ታርክ


ለመሆኑ ሙሴ ማን ነበር? የት ተወልዶ አደገ? ዋና ሥራውስ ምን ነበር?
            ሙሴ እግዚአብሔር እስራኤልን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ እስከ ዮርዳኖስ ድረስ ለማድረስ የተጠቀመበት የእስራኤል መሪ የነበረ ነው፡፡ ሙሴ ከሌዊ ነገድ ግብጽ
ውስጥ በተወለደ ጊዜ እስራኤላውያን በግብጽ ባርነት ነበሩ፡፡ የፈርዖን ሴት ልጅ “ከውሃ አውጥችሃለሁና” ስትል ሕፃኑን ሙሴ ብላ ሰየመችው (ዘጸ 2, 10) ፡፡ ሙሴ አስቀድሞ
በእናቱ እጅ በኋላም እንደ ፈርዖን የልጅ ልጅ ተቆጥሮ ሲያድግ እግዚአብሔርን እየፈራ የግብጽንም ትምህርት እየተማረ “በቃልም በሥራውም የበረታ ሆነ” (ዘጸ 2)፡፡ 
አርባ ዓመትም ሲሞላው በግብጽ ውስጥ በባርነት የነበሩትን እስራኤላውያን ወንድሞቹን ለመርዳት አስቦ ወደ እነርሱ ወጣ፡፡ ነገር ግን አንዱን ግብጻዊ በቁጣ ተነሣሥቶ
ከገደለ በኋላ ወደ ምድያም ሸሸ፡፡ ሴቶች ልጆቹንም ስለረዳቸው የምድያምን ካህን በቤቱ ተቀበለው ፤ ከልጆቹም አንዲትዋን ዳረለት፡፡ ሙሴም እስከ አርባ ዓመት ድረስ
የአማቱን በጎች በምድረ በዳ ሲጠብቅ ቆየ (ዘጸ 2, 11-25 ፤ ዕብ 11, 24-26 ፤ ሐዋ 7, 23-29)፡፡  እንደ አንዳንድ ሊቃውንቶች አገላለጽ ሙሴ ኢትዮጵያዊቷን አገባ ይላሉ ፤
አንዳንዶች ይህች የዮቴር ልጅ ሲፓራ ናት ፤ ሌሎች ከግብጽ አገር ከእስራኤል ጋር የመጣች ሌላ ሴት ናት ይላሉ፡፡
 የሙሴና የእግዚአብሔር ወዳጅነት እንዴት ተጀመረ? ከእግዚአብሔር የተሰጠውስ ተልእኮ ምን ነበር?
            ሙሴ በጎች በኮሬብ አቅራቢያ ሲጠብቅ ሳለ እግዚአብሔር ተገለጠለት ፤ እስራኤልን ከባርነት እንዲያወጣ ወደ ፈርዖን ላከው ፤ ወንድሙ አሮን እንዲናገርለት ፈቀደ
(ዘጸ 3-4)፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ከእግዚአብሔር ጋር ወዳጅነታቸው ተመሠረተ፡፡ የተሰጠው ተግባር እስራኤላውያንን ከግብጽ ባርነት ነፃ ማውጣት ነበር፡፡ ፈርዖንም
ሕዝቡን አልለቅም ባለ ጊዜ እግዚአብሔር በሙሴ እጅ ዐሥር መቅሠፍት በግብጽ ላይ አወረደ (ዘጸ 5-10)፡፡ የግብጽ በኩር ልጆች ሁሉ በሞቱ ጊዜ የፋሲካን ደም በመርጨት
ሙሴ ሕዝቡን በደህና ከግብጽ አወጣቸው (ዘጸ 12-13)፡፡ ፈርዖንም ተከተላቸው ፤ እግዚአብሔርም የሙሴን ጸሎት ሰምቶ የኤርትራን ባሕር በመክፈል ሕዝቡን አዳነ (ዘጸ
14, 1-15 ፣ ዕብ 11, 27)፡፡ በማራ ፣ በኤሊም በራፊዲምም በኩል ወደ ሲና ሲጓዝ ሙሴ የሕዝቡን ማንጐራጐር እየታገሠ በጸሎት የሚያስፈልገውን ሁሉ ሰጣቸው ፤ እጆቹንም
ዘርግቶ በሚጸልይበት ጊዜ ጠላቶቻቸው በውሃ ሰጥመው ተሸነፉ (ዘጸ 15, 22-18, 27)፡፡
 እግዚአብሔር እንዴትና የት ቦታ ላይ ነው ለሙሴ ሕግን የሰጠውና ሙሴም ሕዝቡን ቃል ኪዳን ያስገባው?
            እስራኤላውያን ለአንድ ዓመት ያህል በሲና ሰፍረው ሳሉ በሙሴ አማካኝነት ሕግን ተቀብለው ቅዱስ ሕዝብ እንዲሆኑለት ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ኪዳን ገቡ (ዘጸ
19-24) ፡፡ ሙሴ 40 ቀን በሲና ላይ በመቆየቱ ሕዝቡ ዐምፀው ለወርቅ ጥጃ ሰገዱ ፡፡ ሙሴም ተቆጥቶ ጽላቱን መሬት ላይ ጣለው ፤ ጣዖቱን ሰባበረ ፤ ለሕዝቡ ግን ጸለየ ፡፡
እንደገና 40 ቀን በተራራው ላይ ቆየ ፤ እግዚአብሔርም ይቅር በማለት ቃል ኪዳኑን እንደገና አጸናለት (ዘጸ 32-34) ፡፡ ሙሴም የመገናኛውን የድንኳን መቅደስ አሠርቶ
ተከለ (ዘጸ 35-40) ፡፡ ስለ መሥዋዕትና ስለ ክህነትም ስለሚያደርጉትም ጉባኤ ሁሉ ትእዛዛትን ተቀበለ ፤ ሕዝቡን ቈጠረ ፤ በየነገዳቸውም በመቅደሱ ዙርያ እንዲሰፍሩ
አደረገ ፤ ለጉዞም አዘጋጃቸው (ዘኁ 1, 1-10) ፡፡ እስከ ከነዓን ዳርቻም አደረሳቸው ፤ ከአለማመን የተነሣ አንወጣም ካሉ በኋላ እንደ እግዚአብሔር ትእዛዝ እስከ 40 ዓመት
ድረስ በምድረ በዳ ጠበቃቸው (ዘኁ 13, 1-19) ፡፡
 ሙሴ በተቆጣ ጊዜ ግብጻዊውን እንደገደለና (ዘጸ 2) የተቀበለውንም ጽላት መሬት ላይ በመጣል እንደሰባበረው ተገልጿል (ዘጸ 32, 19) ፤ ይህም ቁጣው እጅግ
በጣም ነዶ እንደ ነበር ያሳያል ፤ ሙሴ በባሕርዩ ምን ዓይነት ሰው ነበር?
            ሙሴ በባሕርዩ እጅግ በጣም ትሑት ሰው ነበር ፤ ግብጻዊውን በንዴት የገደለው ወገኖቹ የሆኑት እስራኤላውያን እጅግ በጣም የከፋ የባርነት ኑሮ ይኖሩ ስለነበርና
እርሱም በወገኖቹ የስቃይ ኑሮ ተበሳጭቶ ስለነበር ነው ፡፡ ሙሴ የእስራኤላውያን መቃወምና ማጉረምረም ብዙ ጊዜ የታገሠ ሰው ነው ፡፡ ራሱንም ለእነርሱ አሳልፎ
ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን በጸሎቱ በመግለጽ እግዚአብሔር እንዳያጠፋቸው ለመነ (ዘጸ 32, 11-14፡፡
 ሙሴ በእግዚአብሔር የተመረጠና የተጠራ ትሑትና ታማኝ አገልጋይ ከነበር የአገልግሎቱ ዋና ዋና ተግባራት የትኞቹ ነበሩ?
-    ሙሴ የህዝቡ መሪና ፈራጅ ነበር (ዘጸ 18, 13-26) ፡፡
 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 4 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

-    እግዚአብሔር በሲና ሕግን ሰጥቶ ከእስራኤል ጋር ላደረገው ቃል ኪዳን ሙሴ መካከለኛ ነበር (ዘጸ 19, 7 ፣ ገላ 3, 19)፡፡
-    እግዚአብሔር የሚመለክበትን ድንኳን መቅደስ አሠራ (ዘጸ 25-31 እና ከ 35-40)፡፡
-    በእጁም አሮንና ልጆቹን ለክህነት የለየ ለሕዝቡም የጸለየ ካህን ነበር (መዝ 99, 6 ፣ ዘሌ 8 እና 9 ዘጸ 32, 30-32)፡፡
-    እግዚአብሔር “አፍ ለአፍ በግልጥ” ያናገረው እግዚአብሔርንም “ፊት ለፊት” ያወቀ ነቢይ ነበር (ዘኁ 12, 6-8 ፣ ዘዳ 34, 10-12)፡፡
-    አብዛኛዎቹ በእጅ ስለ ተጻፉ አምስቱ የኦሪት መጻሕፍት “የሙሴ” ተብለው ይጠራሉ (ሉቃ 24, 27)፡፡
 ሙሴ ታቦት የተባለውን ቅዱስ ነገር እንደሠራ ይታወቃል ፤ ለመሆኑ የዚህ ታቦት አሠራሩ እንዴትና ከምን ነበር? ዋና አገልግሎቱስ ምን ነበር?
      ሙሴ በእርግጥ ከግራር እንጨት ታቦትን እንዲሠራ ታዘዘ ፡፡ አሠራሩም ሣጥን ዓይነት ነበረ ፡፡ ርዝመቱ 125 ፣ ወርዱ 75 ፣ ቁመቱ 75 ሳንቲ ሜትር ያህል ነበረ ፡፡
ታቦቱ በወርቅ የተለበጠ መክደኛውም ከወርቅ የተሠራ ነበር ፤ በላዩም ሁለት ኪሩቤል ተቀርጸዋል ፡፡ 

1.4.1.2. ታቦት
የታቦቱ አገልግሎት የነበረው ፦
1. ዐሠርቱ ቃላት የተጻፉባቸው የሁለቱ ጽላት ማኖርያ
2. ከእስራኤል መሪዎች ጋር የእግዚአብሔር መገናኛ ነበር ፡፡ ስለዚህ ታቦቱ እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር የመኖሩ ምልክት ነበር (ዘጸ 25, 1-22 ፤ 40, 20) ፡፡
ሙሴ ታቦቱን አሠርቶ ሲያበቃ በመገናኛው ድንኳን ውስጥ አኖረው ፡፡ የእስራኤልም ሕዝብ ይዘውት ይጓዙ ነበር ፡፡ በተለይም ዮርዳኖስን ሲሻገሩና ኢያሪኮን ሲዞሩ ካህናት
ተሸክመውት ፊት ፊት ይሄዱ ነበር (ኢያ 3, 16)፤ የእስራኤል ሕዝብ ከኃጢአታቸው ሳይመለሱ በጦርነት እንደ መከላከያ መሣርያ ሲሸከሙት ታቦቱ በመሳፍንት ዘመን
በፍልስጤማውያን ተማረከ ፡፡ ታቦቱ በእግዚአብሔር ስም የተጠራ ስለነበር እግዚአብሔር በፍልስጤማውያን ላይ ብዙ ተአምር አደረገ ፤ ፍልስጤማውያንም መለሱት (1
ሳሙ 4-6) ፡፡ በኋላም ዳዊት ወደ ኢየሩሳሌም አመጣው ፡፡ ሲያመጣውም ዖዛ የተባለው ሰው በድፍረት ስለነካው ተቀሠፈ (2 ሳሙ 6) ፤ ሰሎሞንም ራሱ በሠራው ቤተ
መቅደስ አኖረው (1 ነገ 8) ፡፡ ታቦቱ በኢዮስያስ ዘመን በቤተ መቅደስ ነበረ (2 ዜና መ. 35, 3)፡፡ በዚያን ጊዜ ነቢዩ ኤርምያስ ወደፊት የእስራኤል ሕዝብ ስለ ታቦቱ ምንም
እንደማያስብ ትንቢት ተናገረ (ኤር 3, 16)፡፡
ነቡከደነፆር ኢየሩሳሌምን ሲያፈርስ ታቦቱ የጠፋ ይመስላል ፡፡ ምክንያቱም ዘሩባቤል በሠራው ቤተ መቅደስ ታቦት አልነበረምና ፡፡ በአዲስ ኪዳን የቃል ኪዳኑ ታቦት
በእግዚአብሔር ሰማያዊ መቅደስ እንደታየ ተጠቅሷል (ራእ 11, 19)፡፡
 ሙሴ ከሲና ተራራና ከኮሬብ ጋር በተያያዘ መልኩ ብዙ ጊዜ ይጠቀሳል ፤ ሙሴና ሲና ተራራ ግኑኝነታቸው ምንድን ነው? 
      ሲና ብዙ ጊዜ ተራራ እንደሆነ ሲጠቀስ ይደመጣል ፤ ነገር ግን ሲና ተራራ ሳይሆን ብዙ ተራሮች በውስጡ የያዘ ወይም ያካተተ ከግብጽ አገር በስተምሥራቅና
ከእስራኤል በስተደቡብ የሚገኝ አገር ነው ፡፡ በሲና ምድረ በዳ እስራኤላውያን በሙሴ መሪነት 40 ዓመት እንደ ተጓዙ ይታወቃል (ዘጸ 19, 1) ፡፡ ሌላው ደብረ ሲና
የሚባለው ሲና ውስጥ ከሚገኙት ተራሮች አንዱ ሲሆን ዐሠርቱ ቃላት የተሰጡበት ተራራ ነው (ዘጸ 19, 20) ፡፡ ይህ ደብረ ሲና ኮሬብም ተብሎ ይጠራል (ዘጸ 3, 1 ፣ ዘዳ 4,
9-10) ፡፡ ሙሴም ዐሠርቱ ቃላት በዚህ ተራራ ላይ ሆኖ ስለተቀበለ ስሙ በተደጋጋሚ ከዚህ ተራራ ጋር በተያያዘ መልኩ ይጠራል ፡፡

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 5 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

1.4.1.3. ዐሠርቱ ትእዛዛት


      በመሠረቱ ሙሴ ከእግዚአብሔር ዘንድ በደብረ ሲና የተቀበላቸው ዐሠርቱ ቃላት ሕግ ስለነበሩ ከዚያ ጋር በተያያዘ መልኩ ሲጠቀስ ይታያል (ዘዳ 4, 13) ፡፡ ትእዛዛቱ
በቃል ኪዳን መልክ ተሰጡ (ዘጸ 20, 1-17) ፡፡ ሕግ አምስቱ የሙሴ መጻሕፍትን (ማቴ 5, 17 ፣ ሉቃ 16, 16) እና ብሉይ ኪዳን በሙሉ (ዮሐ 10, 34 ፣ 12, 34) ሊያመለክት
ይችላል ፡፡ ለዚህ ነው ሙሴ ከሕግ ጋር በተያያዘ መልኩ የሚጠቀሰው ፡፡
  ዐሠርቱ ትእዛዛት የሚባሉት የትኞቹ ናቸው? ለምንስ ተሰጡ?
            ዐሠርቱ ትእዛዛት የሚባሉት እግዚአብሔር በሙሴ አማካኝነት በደብረ ሲና ለእስራኤል የሰጣቸው የኪዳን ትእዛዛት ናቸው (ዘጸ 19, 5 - 20, 17) ፡፡ ትእዛዛቱ
በሁለት ጽላት በእግዚአብሔር ጣት የተጻፉ ናቸው (ዘጸ 31, 18) ፡፡ ጽላቱም በታቦቱ ውስጥ ተቀመጡ (1 ነገ 8, 9)፡፡ ከዓርባ ዓመታት በኋላ ወደ አገራቸው ሊገቡ ሲደርሱ
ሙሴ ትእዛዛቱን በድጋሚ አስታወሳቸው ፡፡ ሆኖም የእስራኤል ሕዝብ ሁኔታ አዲስ ስለሆነ ሰንበትን የማክበር ምክንያት ተለወጠ ፤ የባልንጀራንም እርሻ ደግሞ እንዳይመኙ
ታዘዙ (ዘዳ 5, 6-21) ፡፡ በዘጸ 20, 2 መሠረት ዐሠርቱ ትእዛዛት የተሰጡት ደኅንነትን ተቀብሎ በቃል ኪዳን ውስጥ ለሚገኘው የእስራኤል ሕዝብ ነው ፡፡ የተሰጡበትም
ምክንያት ደኅንነት ባለው ሕይወት እግዚአብሔርን እንዴት መከተል እንዳለባቸው የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለቃል ኪዳኑ ሕዝብ ለማስረዳት ነው ፡፡
  ዐሠርቱ ትእዛዛት በመባል ለምን ተጠሩ? ትእዛዛቱስ የትኞቹ ናቸው?
ትእዛዛቱ ዐሥር በመሆናቸው ነው ዐሠርቱ ትእዛዛት በመባል ሊጠሩ የቻሉት ፡፡ 
ትእዛዛቱም የሚከተሉት ናቸው ፦
1. ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ አታምልክ ፡፡ በሰማይም ሆነ በምድር ወይም ከምድር በታች ባለው ውሃ ውስጥ ከሚኖሩት ነገሮች የማንኛውንም ምስል ጣዖት አድርገህ
አታምልክ ፤ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ እጅግ ቀናተኛ ስለሆንሁ ተቀርጾ የተሠራውን ማንኛውንም ጣዖት አታምልክ ፤ አትስገድለትም ፤ እኔ የሚጠሉኝን ሁሉ
እቀጣለሁ ፤ ዘራቸውንም እስከ ሦስትና አራት ትውልድ ድረስ እበቀላለሁ ፡፡ ለሚወዱኝና ትእዛዛቴን ለሚጠብቁ ግን እስከ ሺ ትውልድ ድረስ ዘላለማዊ ፍቅሬን
አሳያቸዋለሁ ፡፡
2. የእኔ የአምላክህ ስም በከንቱ አትጥራ ፤ ምክንያቱም እኔ ስሜን በከንቱ የሚጠራውን ሁሉ እቀጣዋለሁ ፡፡
3. እኔ እግዚአብሔር ባዘዝሁህ መሠረት ሰንበትን አክብር ፤ ቀድሰውም ፡፡ ሥራን ሁሉ የምታከናውንባቸው ስድስት ቀኖች አሉልህ ፤ ሰባተኛው ቀን ግን ለእኔ
ለአምላክህ የተቀደሰ የዕረፍት ቀን ነው ፤ በዚያን ቀን ምንም ዐይነት ሥራ አትሥራ ፤ አንተም ሆንህ ልጆችህ አገልጋዮችህም ሆኑ እንስሳትህ በአገር ውስጥ የሚኖሩ
መጻተኞችም ቢሆኑ ምንም ሥራ አትሥሩበት ፤ አገልጋዮችህም ልክ እንደ አንተው ዕረፍት ያድርጉ ፡፡
4. እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ባዘዝሁህ መሠረት አባትህንና እናትህን አክብር ፤ ይህን ብታደርግ ሁሉ ነገር በመልካም ሁኔታ ይከናወንልሃል ፤ እኔ በምሰጥህ ምድር
የረዥም ዘመን ዕድሜ ይኖርሃል ፡፡
5. አትግደል
6. አታመንዝር
7. አትስረቅ
8. በማንም ሰው ላይ በሐሰት አትመስክር
9. የሌላውን ሰው ሚስቱን አትመኝ ፤

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 6 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

10. የሌላውን ሰው ቤቱን ፣ ርስቱን ፣ አገልጋዮቹን ፣ ከብቱን ፣ አህዮቹንም ሆነ ማናቸውንም ንብረቱን ሁሉ አትመኝ
 ሰንበትን አክብር ፤ ቀድሰውም ሲል የትኛውን ቀን ያመለክታል? ለምንስ መከበር ያስፈልገዋል? አለማክበርስ ምን ሊያስከትል ይችላል?
            ሰንበት በዕብራይስጥ “ማቆም” “መተው” ማለት ነው ፡፡ እስራኤላውያን ሰባተኛውን ቀን ለእግዚአብሔር እንዲቀድሱት ከላይ በተዘረዘሩት ዐሠርቱ ትእዛዛት
ተነግረዋል (ዘጸ 20, 8-11) ፡፡ ከዚህም በላይ ሰንበት በእግዚአብሔርና በሕዝቡ መካከል የቃል ኪዳን ምልክት ነው (ዘጸ 31, 17) ፡፡ በዚህም ምክንያት ሰንበትን አለማክበር
ከባድ ቅጣትን ያስከትል ነበር (ዘኁ 15, 32-36) ፡፡  
ሰንበት የእግዚአብሔር ሥራ እንዲታወስ ያደርጋል ፡፡ በመጀመሪያ እግዚአብሔር ስድስት ቀን ሠርቶ እንዳረፈ ሁሉ ሰውም በዚህ ዓለም ሠርቶ ወደ ዘለዓለም ዕረፍት
አገራቸው ሲደርሱ ዐሠርቱ ቃላት በድጋሚ ተነገራቸው ፡፡ ከዚህም ላይ ሰንበት እግዚአብሔር እስራኤልን ከግብጽ ባርነት እንዳወጣቸው ያመለክታል (ዘዳ 5, 12-16) ፡፡
እስራኤል ቀኑን በሚገባ ባለማክበራቸው በነቢያት ተወቅሰዋል (ሕዝ 20, 12-16 ፣ አሞ 8, 6) ፤ እንዲያከብሩትም ተስፋ ተሰጥቷቸዋል (ኢሳ 56, 2-4 ፣ 58, 13-14) ፡፡
ነህምያ ሰንበትን አስከብሯል (ነሀ 10, 31 ፣ 13, 15-22) ፡፡ ኢየሱስ ሰንበትን አክብሯል (ሉቃ 4, 16 ) ፤ የፈሪሳውያንን የሰንበት አከባበር ግን ተቃውሟል ፡፡ እነርሱ ቀኑ
እንዲከብር ብቻ እሸት ከመቅጠፍ ፣ ድውይ ከመፈወስ እስኪከለክሉ ድረስ ብዙ ሕግና ወግ ደንግገው ነበር ፡፡ ክርስቶስ ግን ከሰው ወግና ሥርዓት ምህረት እንደሚበልጥ
አስተማረ (ማቴ 12, 1-14)፡፡

1.4.1.4. የአስራት በኩራት ታርክ


ከሙሴ ዘመን በፊት ከአብረሃም ጊዜ ጀምሮ ዐሥራት መክፈል የተለመደ ተግባር እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል ፤ ለመሆኑ ዐሥራት ማለት ምን ማለት ነው?
አጀማመሩስ እንዴት ነው?
            ዐሥራት ማለት አንድ ዐሥረኛ ማለት ነው ፡፡ ከቀድሞ ዘመን ጀምሮ ከማንኛውም ገቢ ዐሥረኛው እጅ ለሃይማኖት መሪዎች ወይም ለመንግሥት ይሰጥ ነበር ፡፡
ነገር ግን እንዴት እንደተጀመረ አይታወቅም ፡፡ ከሙሴ ዘመን በፊትና እንዲሁም ከባቢሎን እስከ ሮም ድረስ ይሠራበት ነበር ፡፡ አብርሃም ለመልከ ጼዴቅ ዐሥራትን ሰጠው
(ዘፍ 14, 20) ፡፡ ያዕቆብም ለእግዚአብሔር ዐሥራት ለመክፈል ተሳለ (ዘፍ 28, 22) ፡፡ ሌዋውያን ካህናት እንዲጠቀሙበት (ዘኁ 18, 21-32) ፣ ምድር ከምታፈራውና
ከከብትም ወገን ዐሥራት እንዲሰጥ ታዘዘ (ዘሌ 27, 30-33) ፡፡ የሚከፈልበት ጊዜ ተወሰነ (ዘዳ 12, 5-18 ፤ 14, 22-29) ፡፡ ዐሥራትም ሲከፍሉ እግዚአብሔር ሕዝቡን
ይባርካል (ዘዳ 26, 13-15 ፣ ሚል 3, 10) ፡፡ ፈሪሳውያን ከቅመማ ቅመም ሳይቀር ዐሥራት ይከፍሉ ነበር (ማቴ 23, 23) ፡፡ ሐዋርያት ስለ ዐሥራት አልጻፉም ፤ ሆኖም እንደ
እግዚአብሔር በረከት መጠን በልግስና በውዴታ ዐሥራት መስጠት ይገባል (1 ቆሮ 16, 1-4 ፣ 2 ቆሮ 9, 6-12) ፡፡

1.4.1.5. የክህነት ታርክ


ሙሴ እስራኤላውያንን ከግብጽ ባርነት ማውጣት ጋር በተያያዘ መልኩ የአሮን ስም ሲጠራ ይሰማል ፤ እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ነጻ በመውጣት ሂዳት ትልቅ ሚና
እንደተጫወተ ይታወቃል ፤ ለመሆኑ አሮን ማን ነው? 
            አሮን የሙሴና የማርያም ወንድም ነው (ዘኁ 26, 59 ፣ ዘጸ 6, 20) ፡፡ ስሙ ለመጀመርያ ጊዜ የተጠቀሰው እግዚአብሔር ራሱን ለሙሴ በገለጠበት ጊዜ ነው ፤
በዚያን ጊዜ ሙሴ የእስራኤል መሪ እንዲሆን ተመርጦ ነበር ፤ ነገር ግን ሙሴ “አፌ ኰልታፋ ምላሴም ጸያፍ የሆነ ሰው ነኝ” በማለት ለመታዘዝ አለመውደዱን በገለጠ ጊዜ
እግዚአብሔር “ወንድምህ አሮን አፍ ይሆንልሃል” ብሎ መለሰለት (ዘጸ 4, 14-16) ፡፡
የይሁዳ ነገድ አለቃ እኅት የሆነችውን ኤልሳቤጥ የተባለችውን ሴት አግብቶ ከእርስዋ ናዳብ ፣ አብዩድ ፣ አልዓዛርና ኢታምር የተባሉ አራት ልጆችን ወለደ (ዘጸ 6, 23) ፡፡
ሙሴ ወደ ፈርዖን በቀረበ ቁጥር ከዚያም በኋላ የአርባው ዓመት የምድረ በዳ ጉዞ እስኪያልፍ ድረስ ሙሴ በሚሰራው ሥራ ሁሉ አሮን የቅርብ ረዳቱ ነበረ ፡፡  የእስራኤል
ልጆች ከአማሌቅ ጋር በተዋጉ ጊዜ አሮንና ሖር የሙሴን እጆች ይደግፉ ነበር (ዘጸ 17, 9-12) ፡፡ ሆኖም የእስራኤል ልጆች ይሰግዱለት ዘንድ የወርቅ ጥጃን በመሥራቱ
 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 7 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

እግዚአብሔርን ሳያስቈጣው አልቀረም (ዘጸ 32) ፡፡ አሮን ለተለየ አገልግሎት በእግዚአብሔር የተመረጠ ለመሆኑ በበትሩ ማቈጥቈጥ ታወቀለት (ዘኁ 17) ፡፡ ቢሆንም መሪባ
በተባለው ስፍራ ከሙሴ ጋር ሆኖ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ባለማክበሩ ኃጢአት ሠራ (ዘኁ 20, 12) ፡፡ 
 አሮን ከክህነት ሕይወት ጋር ለምን ተያይዞ ይጠቀሳል? ክህነት ማለት ምን ማለት ነው? ከብሉይ ኪዳን አኳያ ሲታይ አመሠራረቱስ እንዴት ነው? 
በእርግጥ አሮን ሊቀ ካህናት እንዲሆን በመመረጡ ከሌዊ ወገን ካህናት የመጀመሪያው ሆነ (ዘጸ 28, 1) ፡፡ ልጆቹም ካህናት እንዲሆኑ ተቀደሱ (ዘሌ 8, 12- 13, 30) ፡፡ በ 123
ዓመቱ ሲሞት ሊቀ ካህናትነቱ ለልጁ ለአልዓዛር ተሰጠ (ዘኁ 20, 22-29 ፣ 33, 38 ፣ ዘዳ 10, 6) ፡፡ ከዚህም በላይ በአዲስ ኪዳን አሮን የክርስቶስ ምሳሌ ሆኖ ተቈጥሯል
(ዕብ 5, 4-5) ፡፡
ክህነት (ካህን) በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ሆኖ ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኝ ነው ፡፡ ካህን ማለት አገልጋይ እንደማለት ነው ፡፡ ከብሉይ ኪዳን አኳያ ስናይ
አገልግሎቱ መሥዋዕትን በመሠዋትና ጸሎት በመጸለይ ይፈጸማል ፡፡ ካህን በማንኛውም ሃይማኖት አለ (ዘፍ 41, 45 ፣ 1 ሳሙ 6, 2 ሐዋ 14, 13) ፤ በመጀመሪያ እንደ አቤልና
ቃየል ሰው ለራሱ የራሱን መሥዋዕት አቅራቢና ሠዊ ነበር (ዘፍ 4, 3-4) ፤ በኋላም አንደ ኖኅና እንደ አብርሃም አባት ለቤተሰቡ ይሠዋ ነበር (ዘፍ 8, 20 ፣ 12, 7 ፣ 13, 18)
፡፡ ሕግ ሲሰጥ ግን አሮንና ልጆቹ ለእስራኤል ካህናት እንዲሆኑ ተመረጡ (ዘጸ 28, 1) ፡፡ ከአሮን ቤተሰብ ውጭ የሌዊ ዘሮች በመቅደስ ያገለግሉ ነበር እንጂ መሥዋዕትን
አልሠዉም (ዘኁ 3, 5-10)፡፡
ሆኖም ከአሮን ልጆች ያልሆነ ሌላ ሰው ቢሆንም እግዚአብሔር ራሱን ከገለጠለት እንደ ጌዴዎን መሥዋዕት ይሠዋ ነበር (መሳፍ 6, 18-26 ፣ 13, 16) ፤ እንደዚሁም
የእግዚአብሔር ካህናት ሲጠፉ ኤልያስ መሥዋዕት ሠዋ (1 ነገ 18, 30) ፡፡ ከአሮን ልጆችም ነውር ያለበት ከተገኘ አይሾምም ነበር (ዘሌ 21, 16-24) ፡፡
አሮንና ልጆቹ ሲሾሙ ልዩ ልብስ ለብሰው በዘይት ይቀቡ ነበር (ዘጸ 28, 40 ዘሌ 8)  ፡፡ አገልግሎታቸውንም በብዙ ጥንቃቄ እንዲፈጽሙ ታዘዙ (ዘጸ 30, 17-21) ፡፡ በዚያን
ጊዜ የካህናት ሥራ በመቅደስ ማገልገል (ዘኁ 16, 40 ፣ 18, 5) ሕግን ለአሕዛብ ማስተማር (2 ዜና መ. 15, 3 ሕዝ 7, 26) ፣ በኡሪምና ቱሚም የእግዚአብሔርን ፈቃድ
መጠየቅ (ዘጸ 28, 30 ዕዝ 2, 63) ፣ ተላላፊ በሽታ ያለባቸውን መለየት ነበር (ዘሌ 13, 1-3) ፡፡
በአጠቃላይ ካህናት በቤተ መቅደስ የሚፈጽሙትን አገልግሎት በሦስት (3) ይከፋላል ፦
1) ዕለታዊ አገልግሎት ፦ ይህ ጠዋትና ማታ የሚቃጠል መሥዋዕትን የመሠዋት ፣ በቅድስት መብራቶችን የማብራት ፣ ዕጣን የማጠን ፣ ሰው የሚያመጣውን መሥዋዕትም
በያይነቱ የማቅረብ አገልግሎት ነበር (ዘጸ 29, 38-39 ፣ 30, 1-8) ፡፡
2) ሳምንታዊ አገልግሎት ፦ በየሰንበቱ ዐሥራ ሁለት የመገኘቱን ኅብስት በገበታው ላይ የማኖር አገልግሎት ነው (ዘሌ 24, 5-9) ፡፡
3) ዓመታዊ አገልግሎት ፦ በማስተሥረያ ቀን ልዩ ሥርዓትን የመፈጸም አገልግሎት ነው (ዘሌ 16) ፡፡
 ሊቀ ካህናት የሚባለውስ አመጣጡ ከየት ነው? የአገልግሎት ተግባሩስ ምንድን ነው? ከአሮን ጋር ለምን ታያይዞ ይጠቀሳል?
ሊቀ ካህናት ማለት ካህናትን የሚቆጣጠር የካህናት አለቃ ማለት ነው ፡፡ ይህ ማዕረግ በመጀመርያ ለአሮን በኋላም ከአሮን ቤተሰብ ለዋናው ስለተሰጠ ከአሮን ጋር በተያያዘ
መልኩ ብዙ ጊዜ ሲጠቀስ ይሰማል ፡፡ በመጀመርያ ጊዜ እልቅናው እስከ ሞት ድረስ ነበር ፤ በኋላ ግን ነገሥታት እንደፈለጉ ሊቃነ ካህናትን ይሾሙና ይሽሩ ነበር ፡፡
በክርስቶስ ጊዜም እንደነ ሐና ያሉ በሮም መንግሥት የተሾሙ ሊቃነ ካህናት ነበሩ (1 ነገ 2, 26 ሉቃ 3, 2) ፡፡ የሊቃነ ካህናቱ ልብሶች በዕውቅ (በልዩ ዓይነት) የተሠሩ ነበሩ
፡፡ እነርሱም ኡሪምና ቱሚም የተቀመጡበት የደረት ኪስ ፣ ኤፉድ ፣ ቀሚስ ፣ ዝንጉርጉር ሸሚዝ ፣ መጠምጠሚያ “ቅድስና ለእግዚአብሔር” የሚል የተቀረጸበት የወርቅ
አክሊልና መታጠቂያ ናቸው (ዘጸ 28, 1-39) ፡፡
አሮን ሲሾም ሙሴ እንዲያለብሰው በዘይትም እንዲቀባው ታዘዘ (ዘጸ 29, 1-9) ፡፡

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 8 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

 መልከ ጼዴቅ ከሙሴና ከአሮን በፊት እንደነበረና ከክህነታዊም አገልግሎት ጋር በተደጋጋሚ ይጠቀሳል ፤ የመልከ ጼዴቅ ክህነት ከአሮን ክህነት ይበልጣል ወይስ
ያንሳል?
            መልከ ጼዴቅ ማለት የጽድቅ ንጉሥ ማለት ነው፡፡ የሳሌም ንጉሥ ነበር ፡፡ ይህም የሰላም ንጉሥ ማለት ነው ፡፡ ምናልባትም “ሳሌም” ኢየሩሳሌም ይሆናል ፡፡
የእግዚአብሔርም ካህን ነበር (ዕብ 7, 1-3) ፡፡ አብርሃም ከጦርነት በተመለሰ ጊዜ መልከ ጼዴቅ ባረከው ፤ አብርሃምም ከሀብቱ ሁሉ ዐሥራትን ሰጠው (ዘፍ 14, 18-20) ፡፡
ክህነቱ በእርግጥም ከአሮን ክህነት እንደሚበልጥ ተጽፎለታል ፡፡ ይህም አንደኛ በሥጋዊ ትውልድ ሳይሆን በእግዚአብሔር መሐላ በመሾሙ (ዕብ 5, 5-6 ፣ 7, 13-17) ፡፡
ሁለተኛ በሞት ሳይወሰን ለዘለዓለም በማገልገሉ ነው (ዕብ 6, 20 ፣ 7, 3 እና ከ 23-25 ፡፡ ክርስቶስ እንደ መልከ ጼዴቅ በእግዚአብሔር ሊቀ ካህናት በመባሉ የአሮንን
ክህነት አስቀርቷል (ዕብ 5, 7-10 ፣ 7, 11-19) ፡፡ 
 የክርስቶስ ክህነት ከመልከ ጼዴቅና ከአሮን ክህነት(ሊቃነ ክህነት) ጋር በተያያዘ መልኩ እንዴት ሊገለጽ ይችላል?      
    ክርስቶስ  እንደ መልከ ጼዴቅ ካህን ሆኖ ለኃጢአት ሁሉ የሚበቃውን መሥዋዕት አቅርቧልና የአሮን ክህነት አስቀርቷል (ዕብ 7, 11-28) ፡፡ የክህነቱን ሥራ የፈጸመው
በምድራዊ መቅደስ ሳይሆን በሰማያዊ መቅደስ ፣ በእንስሳት ደም ሳይሆን በራሱ ደም ነው (ዕብ 9, 11-12) ፡፡ አሁን ለኃጢአት ሌላ የደም መሥዋዕት ማቅረብ አያስፈልግም ፤
ሆኖም ምእመናን ሁሉ በክርስቶስ ሥራ መሠረት መንፈሳዊ መሥዋዕትን ለእግዚአብሔር ስለሚያቀርቡ የሚሰጡትን ምስክርነትም ሰዎችን ወደ እግዚአብሔር ስለሚያደርሱ
ካህናት ተብለዋል (ሮሜ 12, 1 ፣ ዕብ 10, 19-25 ፣ 13, 15 ፣ 1 ጴጥ 2, 5-9 ራዕ 1, 5-6) ፡፡
            ክርስቶስ የአዲስ ኪዳን ሊቀ ካህናት በመሆን ራሱን አንድ ጊዜ ሠውቶ ወደ ሰማያዊ መቅደስ ገብቷልና የሊቀ ካህናት ሥራ በአዲስ ኪዳን ቀርቷል (ዕብ 9, 1-28 ፣
10, 12-21) ፡፡ 

1.5. የኦሪት ዘጸአት መጽሐፍ አከፋፈል


መጽሐፉ እንዲህ ይከፈላል ፦
1. ምዕራፍ 1 እስራኤላውያን በግብጽ ውስጥ የነበሩበት የጭንቀትና የባርነት ኑሮ
2. ምዕራፍ 2 ስለ ሙሴ መወለድና አስተዳደግ
3. ከምዕራፍ 3- 12, 36) እግዚአብሔር ለሙሴ መገለጥና እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ነፃ መውጣት (የእስራኤላውያን ጉዞ ወደ ሲና ተራራ)
4. ከምዕራፍ 19- 40, 38 እስራኤላውያን በሲና ተራራ አካባቢ መሆናቸውን ይናገራል፡፡    

1.6. የኦሪት ዘጸአት መጻሕፍ ዝርዝርና ይዘት


እግዚአብሔር ከአብርሃም ዘሮች ለራሱ የሚሆን ሕዝብ እንደሚፈጥርና ከነዓንንም ርስት አድርጎ እንደሚሰጣቸው ተስፋ ገብቶ ነበር (ዘፍ፥12:1-3,13:14-16፤ 17:6-8፤ 22:17-
18)።
 የዘፍጥረት መጽሐፍ የሚጠናቀቀው ከ 70 እስከ 75 የሚጠጉ ሰዎች ወደ ግብፅ ምድር ሄደው ነው።

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 9 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

 የተመረጡት የአብርሃም ዘሮች በግብፅ ለም በነበረው ምድር ሰፈሩ። በዚያም በሚቀጥሉት አራት ምዕተ አመታት ወደ ሰሜን ተንቀሳቅሰው ከነዓንን እስከሚይዙበት
ጊዜ ድረስ በዙ፤ በለጸጉም (ዘፍ፥ 15:13፤ ዘጸ፥12:41)።
 ከዚያም ዮሴፍን የማያውቅ አዲስ ንጉስ ወደ ስልጣን እንደመጣ ይነግረናል። የግብፅ ንጉስ ፈርዖንም የእስራኤልን ማደግና መብዛት ሲያዩ እጅግ በመፍራት
ዕድገታቸውን የሚያስቆምበት ዘዴ ፈልጎ "ባሮች" አደረጋቸው።
 ፈርዖንም በእስራኤል ሕዝብ ላይ ግብር አስገባሪዎችን በመሾም አስጨነቃቸው፤ እጅግም አሰቃያቸው፤ "በብርቱ ሥራም ያስጨንቋቸው ዘንድ ግብር አስገባሪዎች
ሾመባቸው"(ዘጸ፥1:11)። ነገር ግን ባስጨነቋቸው መጠን የእስራኤል ሕዝብ ቁጥር መብዛቱን ቀጠለ።
 የዕብራዊያን ሴቶች ሲያዋልዱ ሕፃኑ ወንድ ከሆነ እንዲገደል የሚል ሌላ ትዕዛዝ ለአዋላጆች ተሰጠ። አዋላጆቹ ግን እግዚአብሔርን ስለፈሩ ይህም አልተሳካም።
 ንጉሱ ፈርዖን ሌላ ትዕዛዝ ሰጠ፤ "የሚወለደውንወንድ ልጅ ሁሉ ወደ ወንዝ ጣሉት፤ ሴትን ሁሉ ግን በህይወት አድኑአት"(ዘጸ፥1:22)። በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሁሉ
እግዚአብሔር ሕዝቡን ከቀድሞ ይልቅ እጅግ ማብዛቱን ቀጠለ።
 እስራኤላውያንም ከበዛባቸው ጭቆና እና መከራ የተነሳ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ።
 እግዚአብሔርም የሕዝቡን ጩኸት ሰማ፤ ከአባቶቻቸው ጋር የገባውንም ኪዳን አሰበ። ሕዝቡን ነፃ ያወጣ ዘንድ ሙሴን ሰጣቸው።

ዘጸአት 1-4
የእግዚአብሔር ሕዝብ በባርነት ቀንበር ሥር መሆን እና እግዚአብሔር ሕዝቡን ከባርነት ለማውጣት ሙሴን ስለ መጥራቱ :: ዘጸ. 1-12፡36 እስራኤላውያን በግብፅ ምድር
ዘጸአት 25-40
1. እግዚአብሔርን የማምለኪያ ስፍራ የሆነው የመገናኛው ድንኳን እንዴት መሠራት እንዳለበት የሚናገረው መመሪያ ሰፊውን ክፍል ይዟል። ቀጥሎም የእስራኤል ሕዝብ
የተሰጣቸውን ትእዛዝ ተቀብለው እግዚአብሔር የሚኖርበትን የመገናኛ ድንኳን እንዴት እንደሠሩ ይናገራል።
2. በሁለተኛ ደረጃ የካህናትና የሊቀ ካህኑ አልባሳት እንዴት እንደተሠሩ የሚናገር ክፍል እናገኛለን።
3. ሕዝቡ በእግዚአብሔር ላይ በማመፅ የጥጃን ምስል ሠርተው እንዴት እንዳመለኩ የሚናገር ክፍል እናገኛለን።
በአጠቃላይ የኦሪት ዘጸአት ታሪክ በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል፡:
1. እስራኤላውያን በግብፅ ምድር (ዘጸ. 1-12፡36)
2. ከግብፅ ወደ ሲና ተራራ የተደረገ ጉዞ (ዘጸ. 12፡37- ምዕ. 18) 
3. በሲና ተራራ የቃል ኪዳኑ መሰጠት (ዘጸ. 19-40)
በሲና ተራራ የተደረጉ አራት ዋና ዋና ድርጊቶች በኦሪት ዘጸአት ውስጥ ተገልጸዋል።
አንደኛ፡- እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን በጽላት ላይ የጻፋቸውን ዓሠርቱን ትእዛዛት ሰጣቸው።
ሁለተኛ፥ የተቀደሱ ሕዝቦች ይሆኑ ዘንድ መጠበቅ ያለባቸውን የቃል ኪዳን መመዘኛዎች እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ሰጣቸው።
ሦስተኛ፥ እስራኤላውያን እግዚአብሔርን የሚያመልኩበትን የመገናኛ ድንኳን አሠራር የሚያመላክት ትእዛዝ ተቀበሉ። በተጨማሪ በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ካህናትን
ለአገልግሎት የመመደብንም ትእዛዝ ሰጣቸው። በሲና ተራራ ላይ እያሉ እነዚህን ትእዛዛት ፈጸሙ።
 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 10 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

አራተኛ፥ እስራኤላውያን የጥጃ ምስል ሠርተው በማምለክ በእግዚአብሔር ላይ ኃጢአት አደረጉ፤ የማመንዘር ኃጢአትንም ፈጸሙ፤ እግዚአብሔርም በብርቱ ቀጣቸው።
ከዚህ በታች የኦሪት ዘጸአትን ታሪክ በሚገባ ለማስታወስ የሚረዳ ዝርዝር አስተዋጽኦ ቀርቦአል፡-
1. እግዚአብሔር ሕዝቡን – እስራኤልን ከግብፅ አዳነ (ዘጸ. 1-18)
ሀ. እግዚአብሔር እስራኤልን እንደሚያበዛ የገባውን ቃል ኪዳን ፈጸመ (ዘጸ. 1) 
ለ. እግዚአብሔር ሙሴን ለመሪነት መርጦ አዘጋጀው (ዘጸ. 2-6)፣ 
ሐ. እግዚአብሔር ግብፅን በአሥር መቅሠፍቶች መታ (ዘጸ. 7-11)፤ 
መ. እግዚአብሔር የፋሲካን በዓል ለእስራኤል ሕዝብ ሰጠ (ዘጸ. 12፡1-28)፤ 
ሠ. እስራኤላውያን ከግብፅ ወጡ (ዘጸ. 12፡29-51)፤ 
ረ. በግብፅ የተወለዱት የእስራኤላውያን በኩራት በሙሉ ተቀደሱ (ዘጸ. 13፡ 1-16)፤
ሰ. እስራኤላውያን ቀይ ባሕርን ተሻገሩ (ዘጸ. 13፡17-15፡21)፤ 
ሸ. እስራኤላውያን ወደ ሲና ተራራ ተጓዙ (ዘጸ. 15፡22-18፡27)። 
2. እግዚአብሔር በሲና ተራራ ከእስራኤል ሕዝብ ጋር ቃል ኪዳን አደረገ (ዘጸ. 19-24)
ሀ. አይሁድ ከእግዚአብሔር ጋር ለመገናኘትና ቃል ኪዳን ለመቀበል ተዘጋጁ (ዘጸ. 19)፤ 
ለ. እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ዓሠርቱን ትእዛዛት ሰጣቸው (ዘጸ. 20፡1-17)፤ 
ሐ. እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ስለተቀደሰ አንዋንዋር መመሪያ ሰጣቸው (ዘጸ. 20፡18-23፤ 33)፤ 
መ. እስራኤላውያን በቃል ኪዳኑ ተስማሙ፤ ቃል ኪዳኑም ተረጋገጠ (ዘጸ. 24፡1-8)። 
3. እግዚአብሔር የሚመለክበትን የመገናኛ ድንኳን አሠራር የሚመለከት ትእዛዝ ሰጠ (ዘጸ. 25-40)
ሀ. የመገናኛውን ድንኳን ለመሥራት ዝግጅት ተደረገ (ዘጸ. 24፡9-31፡18)፤ 
ለ. እስራኤላውያን ጣዖትን በማምለክ ኃጢአት ላይ ወደቁ፤ ተፈረደባቸውም (ዘጸ. 32-34)፤
ሐ. የማደሪያው ድንኳን ተሠራና እግዚአብሔር አደረበት (ሕልውናውን ገለጠበት) (ዘጸ. 35-40)። 

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 11 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

1.7. የኦሪት ዘጸአት መጽሐፍ ዋና ዓላማ እና ዋና መልእክት


የዘጸአት መጽሐፍ ዋና ጉዳይ የእስራኤል ህዝብ ከግብፅ ባርነት ነጻ መውጣቱ ነው።
እግዚአብሔር በግብፃዊያን አማልክት ሁሉ ላይ የበላይና እንደ እርሱ ያለ አምላክ እንደሌለ እንድናውቅ
እግዚአብሔር ሕዝቡን ከየትኛውም አይነት ኃይል፣ መከራና ጭቆና ነፃ ማውጣት እንደሚችል
እስራኤልን የመረጠው የእርሱ መልክ በመሆን በሌሎች ሕዝቦች መካከል እንድትወክለውና እንድትገልጠው መሆኑን
እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ህብረት ማድረግ(በህዝቡ መካከል ማደር) የሚፈልግ አምላክ መሆኑን እንድናውቅ ነው።
❖ በዘጸአት መጽሐፍ ኢየሱስ፦ "የፋሲካ በግ"በመሆን በደሙ እስራኤልን ነፃ እንዳወጣ ምሳሌ ሆኖ ቀርቧል።

• በበለጠ ደግሞ በየቤታችሁ መጽሐፍ ቅዱሶቻችሁን በማንበብ የተሻለ መረዳት እግዚአብሔር ይሰጣችኃል።
 ዋና ዓላማ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያለውን የእግዚአብሔር ባሕርይና ሥራ መግለጥ ነው፤ ስለዚህ በዘጸአት በርካታ እውነቶች:
1.እስራኤላውያንን ጌታ ከታደጋቸው በኋላ በስፍራው መድረሳቸውና በሲና መስፈራቸው (ዘፀ. 19፡1-2)
2.እግዚአብሔር ከእስራኤል ጋር የቃል ኪዳን ውል መግባቱ (ዘፀ. 19፡7-8)
3.እስራኤል ቃል ኪዳኑን በመቀበል የሰጠው ምላሽ (ዘፀ. 19፡7-8)
4.ቃል ኪዳኑን በመደበኛ የመቀበል ዝግጅት (ዘፀ. 19፡9-25)
5.የዐሥርቱ ትእዛዛት መታወጅ (ዘፀ. 20፡1-17)
6.ሙሴ እንደ ቃል ኪዳኑ አማላጅ (ዘፀ. 20፡18-21)
7.የቃል ኪዳኑ መርኅዎች መቅረባቸው (ዘፀ. 20፡22-23፡22)
8.የቃል ኪዳኑ መጽናት (ዘፀ. 24፡1-18)

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 12 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

ክፍል ፪
ትርጓሜ
2. የኦሪት የህግ መጽሐፍት ትርጓሜ
ይህንን የትርጓሜ መጻሕፍት ስታነብ የሚከተሉትን ነጥቦች ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል::

2.1. የትርጓሜ አስፈላጊነት


መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው «መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ጽታላችሁ» ማቴ 22፣29 እንዲህ ሲል የሠው ልጅ ነገረ እግዚአብሔር እንደተሰወረበት
የሚያስረዳ ነው፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔርን መልእክታት የያዙ ቅዱሳት መጻሕፍት እንደመሆናቸው ሰው የእግዚአብሔርን ምስጢር እንዲያውቅ እንዲረዳ ትርጓሜ አስፈላጊ
ነው፡፡ ነገረ እግዚአብሔር ተሠውሮበታልና፡፡

2.2. የትርጓሜ ዓይነቶች(ስልቶች)


1. የአንድም ትርጓሜ: የአንድምታ ትርጓሜ የሚባለው አንድ ጊዜ ከተተረጐመ በኃላ መሠረታዊ የሐሳብ አንድነቱን ሳይለቅ እንደገና አንድምታ እያለ እስከ አሥርና አስራ አምስት
ጊዜ የሚያወርዱበት አወራረድ የሚሰጡትን ሐተታ ነው፡፡
2. ነጠላ ትርጓሜ : ነጠላ ትርጓሜ የሚባለው ዘይቤውን ብቻ በቀጥታ የሚተረጉም ምንም ዓይነት ሐተታ የማያደርግ የትርጓሜ ስልት ሲሆን ከአንድ ቋንቋ ወደ ሌላ ቋንቋ
የሚተረጉም ነጠላ ትርጓሜ ይባላል፡፡
3. የሚስጥር ትርጓሜ: ምስጢር ምስጢር ማለት የተሰወረ ግን በውስጥ ያለ ላይ በላይ የማይታይ እንደ ማለት ነው፡፡ ሌላው የምስጢር ትርጓሜ የሚባለው ደግሞ ንባቡን ሳይሻ
አገባቡን ሳይጠብቅ ምሥጢሩን ብቻ በመጠበቅ የሚተረጉም ነው፡፡

2.1. የኦሪት የህግ መጽሐፍት (ኦሪት ዘጸአት) ሐተታ


2.2. የኦሪት የህግ መጽሐፍት ትርጓሜ ከአምስቱ አእማደ ምሥጢራት አንፃር

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 13 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

2.3. የኦሪት የህግ መጽሐፍት ትርጓሜ ከአምስቱ አእማደ ምሥጢራት አንፃር

2.3.1. ምሥጢረ ቁርባን ከኦሪት የህግ መጽሐፍት ትርጓሜ አንፃር


መሥዋእት ማለት መንፈሳዊ አምኃ ፤ሕርድ ፤ቁርባን ፤የእንስሳት ፤ የአዝርእት እና የአትክልት ፤የስንዴ፤የወይን ፤የዘይት፤የዕጣን የመሰለው ሁሉ ፍጡር ለፈጣሪው ከጸሎት እና
ከምስጋና ጋር የሚያቀርበው ፤የሚያቃጥለው ማለት ነው::
ከሥጋም ሲሆን ነውር ከሌላቸው ንጹሓን ከተባሉ እንስሶችና ወፎች መሆን ነበረበት (ዘሌ 22፡ 17-25) ፡፡ይሕም ነውር ነቀፋ የሌለበት የክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡

ከሕገ ልቦናም በኋላ በሕገ ኦሪት ማለትም ከሙሴ ጀምሮ እስከ ክርስቶስ መምጣት ድረስ ብዙ መሥዋእቶች ቀርበዋል በተለይም ይህ የመሥዋእት አቀራረብ ከሕገ ልቦና መሥዋእት
አቀራረብ ለየት የሚደርገው ብዙ የመሥዋእት አይነቶች ስላሉት እና መሥዋእቱም የሚቀርበው በተወሰኑ አካላት/ካህናት/ መሆኑ ነው፡፡( ዘጸ 29፡38፤ ዘሌ 24፡5-9 ፤ ዘጸ 23፡14 ፤
ዘጸ 34፡18 ፤ ዘሌ 23፡23-44 ፤ ፤ዘጸ 23፡16 ፤ዘሌ 23፡9-21 )፡፡
በተለይም እነዚህ መሥዋእቶች በተለያየ ምክንያት የሚቀርቡ ነበሩ፡፡ ከነዚህም መካከል፡- ሰዎች ክህነት ሲቀበሉ ሲነግሱ እና ንዋያተ ቅድሳት ሲከብሩ ሰዎች ለመንጻት ከኃጢአታቸው
ለመላቀቅ ለመቀደስ ከበደል ከርኩሰት ለመንጻት……..( ዘሌ 12፡1፤ ዘሌ 14 ፤ ዘሌ 15፡16 ፤ ዘሌ 4፡1-35 ዘሌ 5፡1-19 ፤ ዘሌ 22፡23 ፤ ዘሌ 22፡23 ፤ዘሌ 11፡18 ፤ ዘሌ 6፡1)
ነበር፡፡
እነዚህ ለተለያዩ አላማ የሚቀርቡት መሥዋእትም በማቃጠል ደም በመርጨት በማጤስ በመጋገር .....ይቀርቡ ነበር፡፡( ዘሌ 7፡37 ፤ ዘሌ 6፡8 ፤ ዘሌ 6፡14 ፤ ዘሌ 6፡24 ፤ ዘሌ 7፡1 ፤
ዘሌ 7፡11-18 ፤ዘሌ 7፡28 ፤ ዘሌ 8፡22 )፡፡

እነዚህ መሥዋእቶች አፍአዊ የኃጢአት ስርየትን ቢያሰጡ እንጂ ዘለአለማዊ ህይወትን የነፍስ አርነትን ማሰጠት አልተቻላቸውም ነበር ምክንያቱ ደግሞ የሚቀርበው መሥዋእት
ፈርሰው በስብሰው ከሚቀሩ እንስሳት እና ከእህል ወገን በመሆኑ ፤ ሞትን ድል መንሳት የሚቻላቸው መሥዋእት ባለመሆናቸው ፤ መሥዋእቶቹም ተደጋጋሚ እና አስልቺ/ሸክም/
ስለሆኑ ነው ::
ዘሌ 17፡11 ፤ ዘሌ 17፡11 ፡፡

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 14 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

የጥጃ ምስል አቁመው ጣኦት በማምለካቸው(ዘጸ 32፡4-35) ምክንያት ከነገድ ሌዋውያንን ለክህነት ማለትም የእለቱ መሥዋእት እንዲያቀርቡ ከቤተሰብ ደግሞ የአሮንን ቤተሰብ
ለሊቀ ካህንነት መርጦ በየአመቱ በማስተስረያ ቀን ወደ ቅድስተ ቅዱሳን እንዲገቡ መሥዋእትን እንዲያቀርቡ የመረጠ ቢሆንም፡፡

ይህ የብሉይ ኪዳኑ የክህነት አገልግሎት በመሐላ የተሾመ ፤ በነገድ የተወሰነ ፤ ፍጹም ያልነበረ ፤ጊዜያዊ የነበረ ፤ አፍአዊ እንጂ ውሳጣዊ ዘለአለማዊ የሆነ የኃጢአት ሥርየትን የማያሰጥ
ነበር ፡፡ካህኑም /ሊቀ ካህኑም /አስቀድሞ ስለ እራሱ ኃጢአት በኋላም ስለ ህዝቡ ኃጢአት መሥዋእት የሚያቀርብ ድካም የበዛበት ህጸጽ ያለበት በሞት የሚወሰድ ነበር፡፡( ዘጸ 4፡10-
17 ፤ ዘጸ 30፡30 ፤ ዘሌ 10፡5 ፤ ዘጸ 28፡1)፡፡

► በብሉይ ኪዳን ሊቀ ክህናትና መሥዋዕት በተያያዘ መልኩ ሲገለጹ ይሰማል ፤ ለመሆኑ መሥዋዕት ማለት ምን ማለት ነው? አመጣጡና አደራረጉስ በምን ዓይነት መልኩ
ይከናወን ነበር?
            እንደ ብሉይ አገላለጽ (የኦሪት መጻሕፍቶች) ሰው ለአምላኩ አንዳች ነገር ቢሰጥ ወይም ቢያቃጥል ያ ነገር መሥዋዕት ወይም ቁርባን ይባላል ፡፡ መሥዋዕቱም እንደ
ሥርዓቱ ዓይነት ሲሠዋ መሠዋቱ ልዩ ልዩ አሳብ ሊገልጥ ይችላል ፡፡ ለምሳሌ በአምላክ ፊት ተቀባይነትን ለማግኘት ወይም ለማጠንከር ይሆናል ፤ እንዲሁም የሰጪውም
እምነት ወይም ንስሓ ምስጋና ወይም ፍቅር ያሳያል ፡፡ መሥዋዕትን ያቀርቡ የነበሩ ሰዎች አንድ እግዚአብሔርን የሚያመልኩት እስራኤላውያን ብቻ ሳይሆኑ አረማውያንም
ደግሞ ለጣዖቶቻቸው ያቀርቡ ነበር ፡፡
            በብሉይ ኪዳን ቃሉ ለመጀመሪያ ጊዜ በዘፍ 4, 4 ላይ ይገኛል ፡፡ እንዲሁም መሠረተ አሳቡ በዘፍ 3, 21 ላይ ተገልጿል ፡፡ ከሙሴ በፊት የጥንት አባቶች
ለእግዚአብሔር ይሠዉ ነበር (ዘፍ 4, 4፣ 8, 20 ፣ 12, 7) ፡፡ በኦሪት ሕግ ግን የካህናት ወገኖች ብቻ እንዲሠዉ ተፈቅዶላቸዋል (ዘኁ 3, 10) ፡፡ የኦሪትም መሥዋእቶች
ከሥጋ ከእህልና ከመጠጥ ነበሩ ፡፡ ከሥጋም ሲሆን ነውር ከሌላቸው ንጹሓን ከተባሉ እንስሶችና ወፎች መሆን ነበረበት (ዘፍ 8, 20 ፣ ዘሌ 22, 17-25) ፡፡
            እግዚአብሔር ከእስራኤል ያዘዛቸው መሥዋዕቶች አምስት ዓይነት ናቸው ፤ እነዚህም የሚቃጠል መሥዋዕት ፣ የእህል ቁርባን ፣ የደኅንነት መሥዋዕት ፣ የኃጢአት
መሥዋዕትና የበደል መሥዋዕት ናቸው (ዘሌ 1-5) ፡፡
የመሥዋዕት አቀራረብ ሥነ ሥርዓት በእንስሳት ሲፈጸም ፦
1) እንስሳው ንጹሕ የሆነና እንከን የሌለበት ነበር (ዘጸ 12, 5 ፣ ዘሌ 22, 24-25 1 ጴጥ 1, 18-19) ፡፡
2) አቅራቢው እጁን በእንስሳው ራስ ላይ ይጭናል (ዘሌ 1, 4) ፡፡ ይህን በማድረጉ በምሳሌነት ራሱን ከእንስሳው ጋር አንድ ያደርጋል ፤ ኃጢአቱንም ያሸክመዋል (ዘሌ 16,
21፣ ኢሳ 53, 6 ፣ 1 ጴጥ 2, 24) ፡፡
3) አቅራቢው ያርደዋል ፤ የኃጢአት ደሞዝ ሞት ነውና (ሮሜ 6, 23 ዕብ 9, 28) ፡፡
4) ካህን የመሥዋዕቱን ደም በእግዚአብሔር ፊት ያቀርባል (ዘሌ 1, 5 ፣ 17, 11 ፣ ዕብ 9, 12) ፡፡
5) ካህን ከእንስሳው እንደ መሥዋዕቱ ዓይነት ልዩ ልዩ ክፍልና ብልት ያቃጥላል ፡፡ ይህ በምሳሌነት አቅራቢው ራሱን ለእግዚአብሔር አገልግሎት እንደሚያቀርብ ይገልጣል
(ዘፍ 8, 21 ፣ ሮሜ 12, 1 ፣ 2 ቆሮ 2, 14-16 ፣ ኤፌ 5, 2) ፡፡

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 15 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

6) ካህን አንዳንድ ጊዜም አቅራቢው ከእንስሳ ያልተቃጠለውን በመሠዊያ አጠገብ ይበላል (ዘሌ 6, 26) ፡፡ ይህም በመሥዋዕቱ መሠረት ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት
እንዳለው ያሳያል (1 ቆሮ 10, 14-22 የይሁዳ መልእክት ቁ.12) ፡፡

2.3.1.1. ሌዋውያኑ ካህናት


ሌዋውያኑ ካህናት በየእለቱ በየሳምንታቱ/በየሰንበታቱ/ መቅረብ ያለባቸውን መሥዋእት ሲያቀርቡ ከአሮን ወገን/ቤተሰብ የሆኑት ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ በማስተስረያ ቀን በአመት አንዴ
ሁለት ፍየሎችን ይዘው ይቀርባሉ የመጀመሪያውን ፍየል አርደው ደሙን በማስተስረያው መክደኛ ላይ ከጊደሩ ደም ጋር ሲረጩት አንድኛውን ፍየል ላይ ግን ሁለት እጃቸውን ጭነው
የህዝቡን ኃጢአት ያሸክሙት እና በተመረጠው ሰው አማካኝነት ወደ ዱር /በረሃ/ እንዲኮበልል ይደረግ ነበር ፡፡የመጀመሪያው ፍየል መታረዱ እስራኤላውያን የኃጢአት ቅጣት ሞት
እንደሆነ እንዲረዱ ሲሆን የሁለተኛው ፍየል ኃጢአታቸውን ተሸክሞ ወደ ዱር እንዲሸሽ መደረጉ ደግሞ ኃጢያታቸውን የሚሸከመው ኃጢአቱን ከነ እርሱ ምን ያክል እንደሚያርቀው
እንዲረዱ ነበር ይህም ለሐዲስ ኪዳን ጥላ መርገፍ ምሳሌ ነበር ፡፡( ዘሌ 10፡12-17 ፤ ዘሌ 16፡23-34 ፤ ዘሌ 16፡32 ) ፡፡ክርስቶስ እንደ ፍየሎቹ ኃጢአታችንን ተሸክሞ ኃጢአታችንን
ከኛ ለማራቁ እና ስለ ኃጢአታችን መሞቱን የሚያመላክት ነበር፡፡

እነዚህ በብሉይ ኪዳን ይቀርቡ የነበሩ የተለያዩ መሥዋእቶች ፍጹም ድኅነትን ያላስገኙ ቢሆንም በጊዜው የሚያስገኙት ጥቅም እንዳለ ሆኖ ለሐዲስ ኪዳን ምሳሌ እና ጥላ ነበሩ ቅዱስ
ጳውሎስ ይህንን አስመልክቶ‹‹ሕጉ ሊመጣ ያለው የበጎ ነገር እውነተኛ አምሳል ሳይሆን የነገር ጥላ አለውና፥

በብሉይ ኪዳን ፭ ዓይነት መስዋዕት ነበሩ፡፡ በ፫ መንገድ ይቀርቡ ነበር


፩ የኃጢአት መስዋዕት ፪ የበደል መስዋዕት ፫ የደህንነት መስዋዕት ፬ የእህል ቁርባን ፭ የሚቃጠል መስዋዕት

2.3.1.2. የፋሲካው በግ (ዘጸ።፩፪÷፩፡፪፭)


እስራኤላውያን በሙሴ መሪነት ከግብጽ ባርነት ከወጡበት ጊዜ ጀመሮ ፋሲካ የሚለው በዓል መከበር እንደተጀመረ ይነገራል ፤ ለመሆኑ ፋሲካ ማለት ምን ማለት ነው ?
አጀማመሩስ እንዴት ነው?
            ፋሲካ በዕብራይስጥ “ፓሳሕ” ማለት ሲሆን ትርጓሜውም “አለፈ” “ተሻገረ” ማለት ነው ፡፡ የእስራኤል ልጆች በግብጽ አገር በግ አርደው ደሙን በደጃፋቸው
በመርጨት ከእግዚአብሔር ቁጣ ዳኑ ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ በዚያች ሌሊት ግብጻውያንን ሲቀሥፍ ደም በነበረበት ቤት አልፎ ስላልገደለ ወይም ደም የተረጨበትን
ቤት ስላለፈ ቀኑ ፋሲካ ተባለ ፡፡ ለፋሲካ የሚታረደውም በግ ፋሲካ ይባላል (ዘጸ 12, 1-13) ፡፡ በየዓመቱ በግ እያረዱ የእስራኤል ልጆች በመጀመርያ ወራቸው በ 14 ኛው ቀን
የፋሲካን በዓል ያከብራሉ ፡፡ ከዚያም ምሽት እስከ አንድ ሳምንት ድረስ የቦካውን ነገር ለመብላት ስላልተፈቀደላቸው የሙሉ ሳምንት በዓል “የቂጣ በዓል” ተባለ ፡፡ የቂጣ
እንጀራ መብላት የእስራኤል ልጆች በችኰላ ከግብጽ መውጣታቸውን የሚያስታውስ የመታሰቢያ ምልክት ነው (ዘጸ 12, 18-20 ፣ ዘዳ 16, 1-3) ፡፡

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 16 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

 እግዚአብሔርም እንዲህ በማለት ትእዛዝ ሰጣቸው ፦


            “ለጉዞ እንደተዘጋጀ ሰው ሆናችሁ ልብሳችሁን በአጭር በመታጠቅ ጫማችሁን አድርጋችሁ ፣ በትራችሁን በእጃችሁ ይዛችሁ በችኮላ (የበግ ወይም የፍየል ጥቦት)
ብሉት ፤ እርሱም እኔን እግዚአብሔርን የምታከብሩበት የፋሲካ በዓል ይሁንላችሁ” (ዘጸ 11, 11) ፡፡
► የመጀመሪያው ፋሲካ እንዴትና የት ተከበረ (ተደረገ)?
የመጀመሪያው ፋሲካ እዛው ግብጽ ውስጥ በችኮላ እንደተከበረ ከዘጸ 12, 1-20 እንረዳለን ነገር ግን ትክክለኛው ፋሲካ ወይም “ማለፍ” ወይ “መሻገረ” የሚለውን ትርጉም
በሚያሳይ መልኩ የተከበረው ግን የግብጽን የባርነት ኑሮ አልፈው ከወጡ በኋላ እንደሆነ ከዘጸ 12, 43- 51 ላይ እንረዳለን ፡፡ በዘጸ 12, 21 በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ
እንደተከበረ እንረዳለን ፦
            ሙሴ የእስራኤል ሕዝብ አለቆች ሁሉ ጠርቶ እንዲህ አላቸው “ቤተሰባችሁ ሁሉ የፋሲካን በዓል እንዲያከብር ከእናንተ እያንዳንዱ የበግ ወይም የፍየል ጥቦት
መርጦ ይረድ ፤ ጭብጥ የሚሞላ የሂሶጵ ቅጠል ውሰዱ ፤ በሳሕን ያለውንም ደም በቅጠሉ እየነከራችሁ የቤታችሁን በር መቃኖችና በላይ በኩል ያለውን ጉበን ቀቡ ፤ እስከ
ማግሥቱ ጠዋት ድረስ ማንም ሰው ከቤቱ አይውጣ ፡፡ እግዚአብሔር ግብጻውያንን በሞት ለመቅጣት በግብጽ ምድር ያልፋል ፤ በጉበንና በመቃኖች ላይ ያለውንም ደም
በሚያይበት ጊዜ አልፎ ይሄዳል ፤ የሞት መልአክም ወደየቤታችሁ ገብቶ እናንተን እንዳይገድል ያደርጋል ፤ እናንተንና ልጆቻችሁ ይህን ሥርዓት ለዘላለም ትጠብቁታላችሁ ፤
እግዚአብሔር ሊያወርሳችሁ ተስፋ ወደ ሰጣችሁ ምድር ስትገቡም ይህን ሥርዓት ትፈጽማላችሁ” (ዘጸ 11, 21-25) ፡፡  
ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ሳምንት የፋሲካ ሳምንት ነበረ (ሉቃ 22, 14-16 ፣ ዮሐ 18, 38-40) ፡፡ እርሱም ንጹሕ የእግዚአብሔር በግ ሆኖ ደሙን ስላፈሰሰልን “ፋሲካችን
ክርስቶስ” ተባለ (1 ቆሮ 5, 7 ፣ 1 ጴጥ 1, 18-19) ፡፡ ስለዚህ የክርስቶስ ትንሣኤ በዓል ፋሲካ ተብሎ ይጠራል ፡፡
ምሳሌነቱ
የእስራኤል ፋሲካ ። ዘፀ ፩፪ ፥ ፩ ። ሞት የዲያብሎስ ፤ እስራኤል የምዕመናን ፤ በጉ የክርስቶስ ምሳሌ ።
– የእስራኤል መና ። ዘፀ ፩፮ ፥ ፩፫ ። መና የጌታችን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም ፤ እስራኤል የምዕመናን ፤ ደመና የእመቤታችን

2.3.1.3. መና (ዘጸ፩፮፥፫፫)
ከእስራኤላውያን የግብጽ የባርነት ኑሮ አልፎ ወደ ተስፋይቱ ምድር ካረጉት ጉዞ (ከምድረ በዳው ጉዞ ጋር) በተያያዘ መልኩ “መና” ስለተባለው ምግብ ይነገራል ፡፡ ለመሆኑ
መና ማለት ምን ማለት ነው? ከሰማይ የወረደ ነው ሲባል ምን ያመለክታል?
            በዕብራይስጥ ቋንቋ መና ማለት “ይህ ምንድን ነው?” ማለት ነው (ዘጸ 16, 15) ፡፡ እስራኤላውያን በተራቡ ጊዜ በምሽት ብዙ ድርጭቶች አየበረሩ መጥተው ሰፈሩን
ሸፈኑት ፤ በማለዳ ደግሞ በሰፈሩ ዙርያ ጤዛ ነበር ፤ ጤዛውም ከተነነ በኋላ ደቃቃና ስስ የሆነ ነገር በበረሓማው ምድር ላይ ታየ ፤ እርሱም በምድር ላይ ያረፈ ዐመዳይ
ይመስል ነበር ፡፡ እስራኤላውያን ባዩት ጊዜ ምን እንደሆነ ባለማወቃቸው “ይህ ነገር ምንድን ነው?” በማለት እርስ በርሳቸው ተጠያየቁ (ዘጸ 16, 13-16) ፡፡ ከዚህ በመነሣት
ነው “መና” የሚለው ስም የተገኘው ፡፡ ስለዚህ መና ማለት “ይህ ነገር ምንድን ነው” ማለት ነው ፡፡
ስለዚህ መና ጠዋት ጠዋት ጠል ካለፍ በኋላ እንደ ደቃቅ ውርጭ ያለ በምድር ላይ ይታይ ነበር ፤ የእስራኤል ሕዝብም ለ 40 ዓመታት በምድረ በዳ ተመገቡት (ዘጸ 16, 35)
፡፡ እስራኤላውያን ጠዋት ጠዋት ያንን እየለቀሙ ይመገቡ ነበር ፡፡ ለማሳደር በሞከሩ ጊዜ ገማ ፤ በስድስተኛው ቀን ግን የተረፈው መና አልገማምና ለሰባተኛው ቀን ምግብ
ሆነ ፡፡ ለተተኪ ትውልድ ምስክር እንዲሆን አሮን ከመናው በጎሞር ውስጥ ከትቶ በቅድስተ ቅዱሳን አኖረው (ዘጸ 16, 13-36 ዕብ 9, 4) ፡፡ ከ 40 ዓመት በኋላ እስራኤል
በኢያሪኮ ምሥራቅ በጌልገላ ሰፍረው ሳሉ ሌላ ምግብ ስላገኙ መናው ቀረ (ኢያ 50, 10-12) ፡፡ እግዚአብሔር መናን ሲሰጥ እንዴት ወይም ምን እንደሆነ አይታወቅም ፡፡

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 17 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

እግዚአብሔር መናን በመስጠቱ ሰው በዚህ ብቻ እንደማይኖር በእግዚአብሔር ቃልም እንደሚኖር (ዘዳ 8, 3-16) ፤ ሰባተኛው ቀን እንዲያከብር አስተማረ (ዘጸ 16, 19-30
ዘጸ 20, 8-10) ፡፡ ክርስቶስ የእስራኤል መና ከጠቀሰ በኋላ የሥጋው ሕይወትነት ከዚያ ይልቅ እጅግ የበለጠ መሆኑን አሳየ (ዮሐ 6, 26-71) ፡፡

2.3.2. ምሥጢረ ሥጋዌ ከኦሪት የህግ መጽሐፍት ትርጓሜ አንፃር


 በዕብራይስጥ ብዙን ጊዜ ጣኦቶቻቸውን በዚህ ስም ይጠሩ እንደነበረም መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። ፨ዘጸ።፩፰፥፩፩፤ ዘዳ።፬፥፪፰፨ “አምላክ፣ አማልክት” ብለው
ሊጠሯቸው ሲፈልጉ።
 ሰዎችም እንዲሁ ተጠርተውበታል፤ ገዦች ነን ሲሉ። ፨ዘጸ።፯፥፩፤ ፪፩
 ዘጸ።፩፮፡፫ እግዚአብሔርም ግድ የለም መና ይዘንብላቸዋል አላቸው። ከሰማይ የተዘጋጀ መና ወረደ።
 ይኸዉም ምሳሌ ነዉ ለጊዜዉ መና ስመግባችዉ አለነበረምን እንዴት ትክዳላችሁ ብለዉ ፍጻሜው ግን መሶበ ወርቅ የእመበታችን ፥ መሶበ ወርቅ እንተ ኤልያስ፤
የኤልያስ የወርቅ መሶብ አንቺ ነሽና ወርቅ፥ የድግልናዋ ምሳሌ ከመሶበ ወርቅ ሚስጢር ሳንወጣ ሊቁ ዕመሶበ ወርቅ እንተ ኤልያስ፤ የኤልያስ የወርቅ መሶብ አንቺ
ነሽዕ ይላታል።
 ይህንን አማናዊ መና (እንጀራ) የሚበላ ግን አይሞትም አለን። “ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም
 በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ…ከሰማይ የወረደ እንጀራ ይህ ነው፤ አባቶቻችሁ መና በልተው እንደ ሞቱ አይደለም። ይህን እንጀራ የሚበላ ለዘላለም ይኖራል
 ኦሪት ዘጸአት ፩፮፥፫፬፥ እግዚአብሔርም ሙሴን እንዳዘዘው እንዲሁ ይጠበቅ ዘንድ አሮን በምስክሩ ፊት አኖረው።
 የተሰወረ መና በውስጧ ያለባት የወርቅ መሶብ አንቺ ነሽ። ከሰማያት የወረደ ኅብስት ለሰው ሁሉ ድኅነት የሚሰጥ” ይላል ትርጉሙ።
ምሳሌነቱ
ለእስራኤል በምድረ በዳ ከደመና የወረደላቸው መና የጌታ ሥጋና ደም ምሳሌ ሲሆን መናው የተገኘበት ደመና ደግሞ ጌታ ከሥጋዋ ሥጋ፣ ከነፍስዋ ነፍስ ነሥቶ ሰው
የሆነባት የድንግል ማርያም ምሳሌ ነው፡፡

 መና ፥ የወልደ እግዝሐብሔር ምሳሌ


 የሙሴ ዕፅ ፥ሐመልማልና ነበልባል ። ዘፀ ፫ ፥ ፪ ። ሐመልማል የእመቤታችን ነበልባል የመለኮት ምሳሌ ። ውዳ ማር አምላክ የተወለደው ከእመቤታችን ሲሆን ፤
ከሷ እንደሚወለድም ፤ በእግዚአብሔር መነንፈስ በተቃኙ ቅዱሳን አማካኝነት አስቀድሞ ፤ ምሳሌ ተመስሏል ፤ ትንቢት ተነግሯል ።
ምሳሌነቱ
 የሙሴ ጽላት ዘፀ ፫፩ ፥ ፩፰ ።
የጽላቱ ማደሪያ የሆነው ታቦት የእመቤታችን ፤ ጽላት የጌታ ምሳሌ ።
የሚወለድበት ጊዜው ከመድረሱ አስቀድሞ በነቢያት አድሮ እንዴት እንደሚወለድ ምሳሌ አመስሏል ትቢት አናግሯል ።

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 18 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

ምሳሌ
እሥራኤል የአዳም ፣ መና የጌታ ምሳሌ ። ዘፀ ፩፮ ፥ ፩፫ ። እግዚአብሔርም ሙሴን አለው። የእስራኤልን ልጆች ማንጐራጐር ሰማሁ። ወደ ማታ ሥጋን ትበላላችሁ፥
ማለዳም እንጀራን ትጠግባላችሁ፤ እኔም እግዚአብሔር አምላካችሁ እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ በላቸው::

2.3.3. ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ከኦሪት የህግ መጽሐፍት ትርጓሜ አንፃር


ከግብጽ ወጥተው ከነዓን መግባታቸው ለትንሣኤያችን ምሳሌ ነው ። ግብጽ የመቃብር ፤ ከነዓን የትንሣኤ (የመንግስተ ሰማያት) ምሳሌ ናትና ። ዘፀ ፩፬ ፥ ፪፩ ።
የኤርትራ ባህር (ቀይ ባህር) ዘፀ ፩፬ ፥ ፪፩ ። ፩ቆሮ ፲ ፥ ፩ ። ሙ ሴ የክርስቶስ ፤ ባህሩን የከፈለባት በትር የመስቀል ፤ ባህረ ኤርትራ የፍርድና የሲኦል ፤ በተከፈለው ባህር
የተሻገሩት እስራኤል በመስቀሉ ላይ በፈሰሰው ደሙ በጥምቀት ከእግዚአ ብሔር ተወልደው ባህረ ኃጢአትን የሚሻገሩ ምዕመናን ምሳሌ ነው ።
ሊቀ ነቢያት ሙሴ ከእስራኤል ሽማገሌዎች ጋር በኮሬብ በነበረው ዐለት ያደረገው ስብሰባ በሐዲስ ዘመን ከተሰበሰቡት ሲኖዶሶች ፨ጉባኤዎች፨ ጋር ይመሳሰላል፡፡
ሙሴ በሌላ ጊዜ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ከእስራኤል ሽማግሌዎችና ከካህናቱ ጋር ወደ ደብረ ሲና ለመውጣት ያደረገው ስብሰባ ከሲኖዶስ ጋር የሚመሳሰል ነው፤፨ዘፀ።፩፱፡
፩፡፪፭፨፡፡ በተለይም የእግዚአብሔርን ክብር ያዩ ዘንድ ሙሴና የእስራኤል ሽማግሌዎች፣ ከካህናቱ ጋር ወደ ደብረ ሲና ወጥተው በሩቅ ቆመው ለእግዚአብሔር ክብር
ስግደት በማቅረብ የተሰበሰቡት ስብሰባ ሲኖዶስን የሚመስል ነው እንላለን፡፡ ፨ዘፀ።፪፬፡፩–፩፩፨፡፡
በሌላ በኩል የእስራኤል ልጆች ወደ ምድረ ከነዓን ለመግባት በሲና ምድረ በዳ በሚጓዙበት ወቅት የሚበላ ዳቦና የሚጠጣ ውኃ ሲያጡ ወደ ሙሴ ይጮኹ ነበር፡፡ ሙሴም
የሕዝቡን ችግር ለእግዚአብሔር እያሰማ ሕዝቡ ማግኘት የፈለጉትን ያሰጣቸው ነበር፡፡ በዚሁ መሠረት አንድ ቀን የእስራኤል ልጆች እጅግ ጎምጅተው «የምንበላው ሥጋ
ማን ይሰጠና፧ በግብፅ ሳለን ያለዋጋ ዓሣውንም፣ ዱባውንም፣ በጢሁንም፣ ነጭ ሽንኩርቱንም፣ ቀይ ሽንኩርቱንም እንደ ልብ እንበላ ነበር፡፡ አሁን ግን ሰውነታችን ደረቀች፣
ዐይናችንም ከዚህ መና በቀር የሚያየው የለም» ብለው አጉረመረሙ፡፡

2.3.4. ምስጢረ ሥላሴ ከኦሪት የህግ መጽሐፍት ትርጓሜ አንፃር


ሥላሴ በአካላት ሦስት ሲሆኑ በባሕርይ በመለኮት አንድ ናቸው፡፡ አንድ እግዚአብሔር፤ አንድ አምላክ ናቸው፡፡ ይህን ሲያስረዱ መጻሕፍት እንዲህ ይላሉ፤ እስራኤል ሆይ
ስማ እግዚአብሔር አምላካችን አንድ እግዚአብሔር ነው፡፡ ዘጸ።፮÷፬ እግዚአብሔር አንድ ነው፡፡
እግዚአብሔር ለሙሴ በተገለጠለት ጊዜ «እኔ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅም አምላክ፣ የያዕቆብም አምላክ እግዚአብሔር ነኝ» ዘጸ።፫፡፮ ሲል «አምላክ፣ አምላክ፣ አምላክ»
ብሎ ሦስትነቱን፣ «እኔ እግዚአብሔር ነኝ» ብሎ ደግሞ አንድነቱን ገልጾ ተናግሯል፡፡
አንድንነቱን ስገልጽ
ኦሪት ዘጸአት ምዕራፍ ፫ እግዚአብሔር ተዋጊ ነዉ፡ ስሙም እግዚአብሔር ነዉ ፡፡ ዘፀ ፩፭፥፫ ‹‹እኔ እግዚአብሔር ነኝ›› (ዘፀ። ፮፥፪)
እግዚአብሔር አምላካችን ሰማይና ምድርን፣ መላእክትን፣ ሰውን እንዲሁም ፍጥረታትን በሙሉ የፈጠረ አምላክ ነው፡፡ ለፍጥረታቱም ህልውናውን እንደብቃታቸው
ይገልጻል፤ በጥንተ ተፈጥሮ እግዚአብሔር አምላክ መላእክትን ለባውያን (አዋቂዎች) አድርጎ ከፈጠራቸው በኋላ በሰጣቸው ዕውቀት ተመራምረው ፈጣሪያቸውን ያመልኩት
ዘንድ እንዲሁም ከባሕርዩ ፍጹም ርቀት የተነሣ በመካከላቸው ሳለ ተሰወረባቸው፡፡ መላእክትም ተፈጥሮአቸውንና ፈጣሪያቸውን መመርመር ጀመሩ፤ አንዱም ለአንዱ
‹‹አንተ ምንድን ነህ፧ ከየጽ መጣህ፧›› ይባባሉ፣ እርስ በርሳቸውም እየተያዩ በተፈጥሮአቸው ይደነቁ ነበር፡፡ በኋላም ‹‹ማን ፈጠረን፧ ከየጽ መጣን፧›› የሚለው የማኅበረ
መላእክት ጥያቄ መበርታቱን የተረዳው ሳጥናኤል ሹመቱ ከሁሉ በላይ ነበርና አሻቅቦ ቢያይ ‹እኔ ነኝ ባይ› ድምጽ አጣ፤ ዝቅ ብሎም ቢያዳምጥ ከእርሱ በክብር ያነሱ

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 19 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

መላእክት ይመራመራሉ፤ ‹ለምን እኔ ፈጠርኳችሁ ብዬ ፈጣሪነትን በእጄ አላስገባም› ብሎ አሰበ፤ ከዚያም ‹እኔ ፈጣሪያችሁ ነኝ› በማለት ተናገረ፡፡ (ዘፍ። ፩፥፩፡፴፩፣ መጽሐፈ
አክሲማሮስ ዘእሑድ ከገጽ ፳፬፡፴፫)

2.3.5. ምስጢረ ጥምቀት ከኦሪት ዘጸአት ትርጓሜ አንፃር


የጥምቀት ምሳሌ በብሉይ ኪዳን ኖኀና ቤተሰቡ ከጥፋት የዳኑባት መርከብ የአማናዊቱ ቤተክርስቲያን ምሳሌ መሆንዋ በመጽሐፍ ቅዱስ የተረጋገጠ ነው፡፡

 የእስራኤል የኤርትራ ባህርን (ቀይ ባህርን) መሻገርም የጥምቀት ምሳሌ ነው (ዘፀ 14፡21) ።
 ሙሴ የክርስቶስ ፤ ባህሩን የከፈለባት በትር የመስቀል፤ ባህረ ኤርትራ የፍርድና የሲኦል ፤ በተከፈለው ባህር የተሻገሩት እስራኤል በመስቀሉ ላይ በፈሰሰው ደሙ በጥምቀት
ከእግዚአ ብሔር ተወልደው ባህረ ኃጢአትን የሚሻገሩ ምዕመናን ምሳሌ ነው ።
 ዘሌ ፩፪÷፫ በዘመነ ሀዲስ ግን በጥምቀት ቢተካም ጌታ ሰው ቢሆንም ኦሪትን ሊሽር አልመጣምና በተወለደ በ፰ ቀኑ ስርዓተ ግዝረት ፈጽሟል፡፡
 (ዘሌ 12፡1-10)፡፡ አዳም በተፈጠረ በ 40 ቀኑ፣ ሔዋንም በተፈጠረች በ 80 ቀኗ ወደ ርስታቸው ገነት እንደገቡ ሕጻናትም በ 40 እና በ 80 ቀናቸው ተጠምቀው
የሰማያዊት ኢየሩሳሌም አምሳል ወደሆነችው ወደ ቤተክርስቲያን ይገባሉ፡፡

2.4. የብሉይ ኪዳን መገናኛው ድንኳን የአድስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናት

2.4.1. መገናኛው ድንኳን


የመገናኛው ድንኳን ‹‹ሦስት ክፍሎች›› እንደነበሩት እንማራለን፡-

2.4.1.1. 1 ኛው ክፍል/ አደባባይ //ዐውደ ምህረት//፡-


 በዚህ ክፍል ውስጥ ለእግዚአብሔር የሚሰግደው ሕዝበ እስራኤልና ካህናቱ የሚገናኙበት ሲሆን፣ ለኃጢአት ምትክ ይሆን ዘንድ በግ በእግዚአብሄር ፊት
የሚሰዋበት ነው፡- ‹‹ማናቸውም ሰው ኃጢአት ቢሠራ፥ እግዚአብሔርም፦ አትሥሩ ካላቸው ትእዛዛት አንዲቱን ቢተላለፍ፥ ባያውቅም፥ ያ ሰው በደለኛ ነው፥
ኃጢአቱንም ይሸከማል። ነውር የሌለበትን አውራ በግ ከመንጋው ለበደል መሥዋዕት እንደ ግምጋሜህ መጠን ወደ ካህኑ ያመጣዋል ካህኑም ሳያውቅ ስለ ሳተው
ስሕተት ያስተሰርይለታል፥ እርሱም ይቅር ይባላል።›› ዘሌ 5፡-17-18፡፡ በዚህ አደባባይ ውስጥ የተለያየ አገልግሎት ነበሩት፡-
 ዘጽ 27፡-5፡፡ የነሐስ መሰዊያ አለበት፡- ‹‹ለመሠዊያውም ከግራር እንጨት መሎጊያዎችን ሠርተህ በናስ ለብጣቸው።›› በዚህ መሰዊያ ላይ ለሕዝቡ በደል ማስተሰርያ
ይሆን ዘንድ በግ የሚሰዋበት ነው::
 ዘጽ 29፡-15-16 “አንደኛውንም አውራ በግ ትወስደዋለህ አሮንና ልጆቹም በአውራው በግ ራስ ላይ እጆቻቸውን ይጭናሉ። አውራውንም በግ ታርደዋለህ፥
ደሙንም ወስደህ በመሠዊያው ላይ በዙሪያው ትረጨዋለህ።”

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 20 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

 ዘጽ 30፡-18-20 ‹‹የመታጠቢያ ሰንና መቀመጫውን ከናስ ሥራ በመገናኛው ድንኳንና በመሠዊያው መካከል እርሱን አድርገህ ውኃን ትጨምርበታለህ። አሮንና
ልጆቹም እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን ይታጠቡበታል። ወደ መገናኛው ድንኳን በገቡ ጊዜ፥ ለእግዚአብሔርም የእሳት መስዋዕት ያቃጥሉ ዘንድ ወደ መሠዊያው
ሊያገለግሉ በቀረቡ ጊዜ፥ እንዳይሞቱ ይታጠቡበታል።››

2.4.1.2. 2 ኛው ክፍል/ ቅድስት


በዚህ በመገናኛው ድንኳን ካለው አደባባይ ከጥሎ ያለው ክፍል ‹‹ቅድስት› ትባላለች፡-
መቅረዝ፡- ከወርቅ የተሰራ መቅረዝ በቅድስት ውስጥ ሲኖር፣ የሚቀመጠውም ከፍ ባለ ስፍራ ላይ ሲሆን፣ ዋና አገልግሎቱም ለክፍሉ ብርሃን መስጠት ነው፡-
 ዘጽ 25፡-31፡፡ ‹‹መቅረዝንም ከጥሩ ወርቅ አድርግ መቅረዙ ከእግሩና ከአገዳው ጋር በተቀጠቀጠ ሥራ ይደረግ ጽዋዎቹም ጕብጕቦቹም አበቦቹም አንድነት በእርሱ
ይደረጉበት።››
የኅብስት መሰዊያ፡- ይህ የአገልግሎት ዕቃ በመቅረዙ ፊት ለፊት ይቀመጣል፤ አገልግሎቱም ደግሞ በእግዚአብሔር ፊት ሁል ጊዜ የሚታዩና የማይለዩ ወይም ሊታዩ የሚችሉ
በቁጥር አስራ ሁለት ኅብስቶችን ወይንም ዳቦዎችን መሸከም ነበር፡- ‹‹ርዝመቱም ሁለት ክንድ፥ ወርዱም አንድ ክንድ፥ ቁመቱ አንድ ክንድ ተኩል የሆነ ገበታ ከግራር
እንጨት ሥራ።
 ዘጽ 25፡-23-30: በጥሩም ወርቅ ትለብጠዋለህ በዙሪያውም የወርቅ አክሊል አድርግለት፤ በዙሪያውም አንድ ጋት የሚያህል ክፈፍ አድርግለት የወርቅም አክሊል
በክፈፉ ዙሪያ አድርግለት። አራትም የወርቅ ቀለበቶች አድርግለት ቀለበቶቹንም አራቱ እግሮቹ ባሉበት በአራቱ ማዕዘኖች አድርግ። ገበታውንም ለመሸከም
መሎጊያዎቹ እንዲሰኩባቸው ቀለበቶቹ በክፈፉ አቅራቢያ ይሁኑ። ገበታውን ይሸከሙባቸው ዘንድ መሎጊያዎቹን ከግራር እንጨት ሠርተህ በወርቅ ለብጣቸው።
ለማፍሰሻም ይሆኑ ዘንድ ወጭቶችዋን ጭልፋዎችዋንም መቅጃዎችዋንም ጽዋዎችዋንም አድርግ እነርሱንም ከጥሩ ወርቅ አድርጋቸው። በገበታም ላይ የገጽ ኅብስት
ሁልጊዜ በፊቴ ታደርጋለህ።››

2.4.1.3. 3 ኛው ክፍል/ ቅድስተ-ቅዱሳን፡-


ሦስተኛዋ ክፍል ቅድስተ-ቅዱሳን ስትባል፣ ከቅድስት ቀጥል የምትገኝ ናት፡፡ በዚህች ክፍል ውስጥ እራሳቸውን ለእግዚአብሔር አስገዝተው ካሉት ካህናት መካከል
የተመረጠው ሊቀ ካህናት ‹‹አሮን›› ብቻ በዓመት አንድ ጊዜ የሚገባባት ክፍል ናት፡- ቅድስተ-ቅዱሳን ክፍል ከቅድስት ክፍል የምትለየው በ**መጋረጃ** ነው፡፡
የዕጣን (የወርቅ) መሠዊያ ወይም የወርቅ ማዕጠንት ምሳሌ
ኦሪት ዘጸአት 25 :8-10
ስለ ቤተ- መቅደሱ ዲዛይን ንድፍ እና አሰራር
8 በመካከላቸውም አድር ዘንድ መቅደስ ይሥሩልኝ። እኔ እንደማሳይህ ሁሉ፥ እንደ ማደሪያው ምሳሌ እንደ ዕቃውም ሁሉ ምሳሌ፥ እንዲሁ ሥሩት።
 ኦሪት ዘጸአት 26:12-14
ከድንኳኑ መጋረጆች የቀረ ትርፍ ግማሽ መጋረጃ በማደሪያው ጀርባ ይንጠልጠል። ማደሪያውን እንዲሸፍን ከርዝመቱ በአንድ ወገን አንድ ክንድ፥ በአንድ ወገንም አንድ ክንድ
ከድንኳኑ መጋረጆች የቀረው ትርፍ በማደሪያው ውጭ በወዲህና በወዲያ ይንጠልጠል።ለድንኳኑም መደረቢያ ከቀይ አውራ በግ ቁርበት፥ ከዚያም በላይ ሌላ መደረቢያ
ከአቆስጣ ቁርበት አድርግ።

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 21 ከ 14
የካልዓይ ትምህርት “መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው” ሮሜ. ፲፥፲፬”

 ኦሪት ዘጸአት 27:21


በመገናኛው ድንኳን ውስጥ በምስክሩ ታቦት ፊት ባለው መጋረጃ ውጭ አሮንና ልጆቹ ከማታ እስከ ማለዳ ድረስ በእግዚአብሔር ፊት እንዲበራ ያሰናዱት፤ በእስራኤል
ልጆች ዘንድ ለልጅ ልጃቸው የዘላለም ሥርዓት ይሁን።
 ኦሪት ዘጸአት 29: 42 ለአንተ እናገር ዘንድ ከእናንተ ጋር በምገናኝበት በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ፥ በእግዚአብሔር ፊት ይህ ዘወትር ለልጅ ልጃችሁ የሚቃጠል መሥዋዕት
ይሆናል።
ከእስራኤልም ልጆች ጋር በዚያ እገናኛለሁ፤ ድንኳኑም በክብሬ ይቀደሳል። የመገናኛውንም ድንኳን መሠዊያውንም እቀድሳለሁ፤ በክህነትም ያገለግሉኝ ዘንድ አሮንንና
ልጆቹን እቀድሳለሁ።

 ዘጸአት 30 ÷ 1-10

የዕጣን መሠዊያውን ሥራ፤ ከግራር እንጨት አድርገው። ርዝመቱ አንድ ክንድ፥ ስፋቱም አንድ ክንድ፥ አራት ማዕዘን ይሁን፤ ከፍታውም ሁለት ክንድ ይሆናል፤ ቀንዶቹም
ከእርሱ ጋር በአንድነትየተሠሩ ይሁኑ። ላይኛውንና የግድግዳውንም ዙሪያ ቀንዶቹንም በጥሩ ወርቅ ትለብጠዋለህ፤ በዙሪያውም የወርቅ ክፈፍ ታደርግለታለህ።

ከክፈፉም በታች ሁለት የወርቅ ቀለበቶች አድርግለት። በዚህና በዚያ በሁለቱ ጎን ታደርጋቸዋለህ፤ ለመሸከምም የመሎጊያዎች ስፍራ ይሁኑ። መሎጊያዎቹንም ከግራር
እንጨት አድርግ፥ በወርቅም ለብጣቸው። በምስክሩ ታቦት አጠገብም ካለው መጋረጃ በፊት ታኖረዋለህ ይህንም አንተን በምገናኝበት ከምስክሩ በላይ ባለው በስርየት
መክደኛ ፊት ታኖረዋለህ።
 ኦሪት ዘጸአት 33:7
ሙሴም ድንኳኑን እየወሰደ ከሰፈር ውጭ ይተክለው ነበር፤ ከሰፈሩም ራቅ ያደርገው ነበር፤ የመገናኛውም ድንኳን ብሎ ጠራው። እግዚአብሔርንም የፈለገ ሁሉ ከሰፈር
ውጭ ወዳለው ወደ መገናኛው ድንኳን ይወጣ ነበር።

2.3. የማጣቀሻ መጽሐፍ (Reference book)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
አሜን

 | የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰ/ት/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ክፍል ገጽ 22 ከ 14

You might also like