You are on page 1of 4

Poimen Ministry – Email: poimenministry516@gmail.

com

ትምህርት 2- የጋብቻ ዓላማዎች

የትምህርቱ ዓላማዎች
በትምህርቱ መጨረሻ ላይ ተማሪዎች፡
❖ ትክክለኛ የሆኑ የጋብቻና ቤተሰብ ዓላማዎችን ይገልጻሉ፡፡
❖ ሰዎች ወደ ጋብቻ የሚገቡቧቸውን ትክክለኛ ያልሆኑ ዓላማዎችን ያብራራሉ፡፡
❖ ወደ ትዳር የገቡበትን ወይም ለመግባት ያሰቡበትን ዓላማዎቻቸውን
ይገመግማሉ፡፡

ሰዎች ለማግባት ሲያስቡ በጋብቻ ግንኙነት ውስጥ እናገኛለን ብለው የሚያስቧቸው ነገሮች
ይኖራሉ፡፡ እነዚህ የተጋቢዎች ዓላማዎች ወይም ግቦች ይባላሉ፡፡

ትክክለኛ ያልሆኑ የጋብቻ ዓላማዎች

አንዳንድ ጊዜ ተጋቢዎች ወደ ትዳር የሚገቡት በተሳሳተ ዓላማ ነው፡፡ የተሳሳተ ዓላማ ማለት
አሁንም ጥቂት ጊዜ ለጋብቻ ግንኙነታቸው ጠቃሚ ያልሆነ፣ በግንኙነት ላይ ሳይሆን በግንኙነቱ አማካኝነት
ወስዳችሁ ወደ ትዳር በሚገኙ ጊዜያዊ ጥቅሞች ላይ ያተኮረ፣ ተጨባጭ ነባራዊ እውነታን ያላገናዘበና ከአንዱ
የገባችሁበትን ምክንያቶች
የትዳር ጓደኛ የተሰወረ ግብ ነው፡፡
አስቡ፡፡ እናገኛለን ብላችሁ
ያላገኛችሁት ነገሮች ምን
እነዚህን የተሳሳቱ ግቦቻችሁን ከጻፋችሁ በኋላ ሌሎች ሰዎች ወደ ትዳር የሚገቡባቸውን
ምን ነበሩ?
ትክክለኛ ያልሆኑ ምክንያቶችን ተመልከቱ፡፡ እነዚህ ምክንያቶች ሁሉ ሙሉ በሙሉ ስህተት
ናቸው ማለት አስቸጋሪ ነው፡፡ ነገር ግን በእነዚህ ምክንያቶች ብቻ ወደ ትዳር የገባ ሰው
መልካም ትዳር ለመለማመድ ፈተናው ከፍተኛ ይሆናል፡፡ ሰዎች ወደ ትዳር እንዲገቡ
ከሚያደርጓቸው ነገሮች ጥቂቶቹ ከዚህ በታች ተጠቅሰዋል፡-1

❖ የተቸገረ ሰውን አይቶ ለመርዳት ማግባት - የጋብቻ ግንኙነት የዕርዳታ ድርጅት


አይደለም፡
❖ ሀብት ያለውን ሰው አግብቶ ከድህነት/ከችግር ለመውጣት- ጋብቻ የሌላውን
ሀብት በመካፈል ከድህነት የመውጫ መንገድ አይደለም፡፡ በእርግጥ ሁለቱ
ተባብረው ከሠሩ ከድህነት ሊወጡ ይችላሉ፡፡
❖ በሕይወት በመሰላቸት ምናልባት የተሻለ ለውጥ ይመጣል ብሎ ማግባት - ጋብቻ
በራሱ የሕይወት ለውጥ ማምጣት የሚያስችል ተዓምራዊ ኃይል የለውም፡፡
የተጋቢዎች ጥረት ሳይኖር ለውጥ አይመጣም፡፡
❖ በአፍላ ፍቅር ተገፋፍቶ ማግባት - አፍላ ፍቅር የጋብቻ መሠረት አይሆንም፤
ምክንያቱም በጀመረበት ከፍታ ላይ አይቆይም፣ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ይጠፋል፡፡

1
የእነዚህን ዝርዝር ሐሳቦች ማብራሪያ ከፈለጋችሁ ከበደ በከሬ፡ ጋብቻን እንዴት ልጀምር? የሚለውን መጽሐፍ
ማንበብ ትችላላችሁ፡፡

Page 1 of 4
Poimen Ministry – Email: poimenministry516@gmail.com

❖ የቅድመ-ጋብቻ ወሲብ በመፈጸም እርግዝና ሲከሰት፣ ያለዝግጅት ማግባት-


❖ የብቸኝነትን ስሜት ለማስወገድ ማግባት
❖ በጋብቻ ግንኙነት ውስጥ ስውር ዓላማን ለማሳካት (መረጃ ለመሰብሰብ፣ ውጭ
ሀገር ለመሄድ፣ የንግድ ሸሪክ ለመሆን፣)
❖ ከወላጆች ተጽዕኖ ነፃ ለመውጣት ብሎ በችኮላ ማግባት
❖ ቤተሰብን ለማስደሰት ብሎ ማግባት
❖ እንደ ጓደኛ ለመሆን ብሎ ማግባት
❖ በሰዎች ተጽዕኖ ወደ ትዳር መግባት
❖ የወሲብ ፈተናን ለመቋቋም ብሎ ማግባት

እነዚህን የተሳሳቱ ዓላማዎችን ይዛችሁ እግዚአብሔር በጋብቻ/ቤተሰብ ውስጥ


ያስቀመጠውን በረከት ማግኘት አትችሉም፡፡ እናንተ ያሰባችሁት ሐሳብ የእግዚአብሔር ቃል
በሚያስተምረው አቅጣጫ ባለመሆኑ የእግዚአብሔር ወዳለመው ግብ አያደርሳችሁም፡፡

ባልና ሚስት በትዳር ሕይወታቸው ውስጥ ትክክለኛ ያልሆነ ነገር እንዲጠብቁ


የሚያደርጓቸው የተለያዩ መንስኤዎች ይኖራሉ፡፡ እነዚህን መንስኤዎች ማወቅ፣ ትክክለኛ
ያልሆነውን አስተሳሰብና ግምት ለመለወጥ አንድ በጎ እርምጃ ይሆናል፡፡

ትክክለኛ የጋብቻ ዓላማዎች

ጋብቻ ለሰዎች አስፈላጊ የሆነ ተቋም ነው፡፡ ሰዎች ጋብቻን ከመሠረቱ በኋላ በሕይወታቸው
በብዙ ነገር ተጠቃሚዎች ይሆናሉ፡፡ ትክክለኛ የሆኑ ዓላማዎች የሚባሉት ተጋቢዎች በጋብቻ
ውስጥ ሊገኙ በሚችሉ ጥቅሞች ላይ ትኩረት በማድረግ እነርሱን ለማግኘት
የሚያስቀምጡት ግቦች ናቸው፡፡

ሳያገቡ መኖር የራሱ የሆነ በጎ ነገር ቢኖረውም፣ ማግባት ግን ሳያገቡ ከመኖር የተሻለ
ጥቅም አለው፡፡ ጥንዶች እነዚህ በጋብቻ ውስጥ በሚገኙ በረከቶች ላይ ትኩረት ሲያደርጉ
በትክክለኛው መስመር ላይ ናቸው ማለት ነው፡፡

ባልና ሚስት በጋብቻ ውስጥ የሚያገኙአቸውን ዋና ዋና በረከቶች አብረን እንመለከታለን፡፡


የጋብቻ መሥራችና ባለቤት የሆነው እግዚአብሔር በመጽሐፉ ውስጥ ከተናገራቸው
ቁምነገሮች እንጀምራለን፡፡ የመጀመሪያው ዓላማ/ግብ የባልና ሚስት ወዳጅነት ነው፡፡
አሁን ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋብቻ የተመሠረተው ለወዳጅነት ነው፡፡
ውስጥ (ዘፍ2፡18ን)
አንብቡ፡፡ በዚህ ጥቅስ ጋብቻ ለአንድነት
መሠረት ጋብቻ ለሰው ልጅ
የተሰጠው ለምንድነው? እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ጋብቻን የሰጠበት የመጀመሪያው ግቡ ባልና ሚስት
አንድነት/ኅብረት እንዲኖራቸው ነው፡፡ ቃሉ ‹‹ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም
አይደለም›› ይላል፡፡ መልካም ያልሆነው የተፈጠረው ሰው ሳይሆን ሰውየው ብቻውን

Page 2 of 4
Poimen Ministry – Email: poimenministry516@gmail.com

መሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ ሰው ብቻውን እንዳይሆን እግዚአብሔር ሴትን ፈጥሮ ሁለቱን በጋብቻ
አጣመራቸው፡፡

የሁለቱ ጥምረት ደግሞ ከማንኛውም ሰብዓዊ ግንኙነት እጅግ ተቀራራቢና የተጣበቀ ነው፡፡
ሰው ከአባትና ከእናቱ፣ ከወንድምና ከእህቱ ጋር ካለው ግንኙነት ሁሉ የሚቀርብ ወዳጅነት
ነው፡፡ በዚህ ወዳጅነት ውስጥ ሁለንተናዊ ሕይወትን መጋራት ይገኛል፡፡ በዚህ ግንኙነት
ውስጥ ባልና ሚስት አንዱ ለሌላው በሚመች መንገድ አብረው ይኖራሉ፡፡

በባልና ሚስት መካከል ያለው አንድነት ጠንካራ ነው፣ ዘላቂነት አለው፡፡ ሁለቱም
በመደጋገፍና በመተባበር አብረው የሕይወትን ጉዞ ይጓዛሉ፡፡ የተለያዩ ውጣ-ውረዶች
ቢያጋጥሟቸውም ሁለቱ ያላቸውን ችሎታ፣ ጥበብ፣ እውቀት፣ ልምድ፣ …. በመጠቀም
በመክ.4፡9-12 መሠረት፣ ወደፊት ይሄዳሉ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ተጨማሪ ሐሳብ ለማግኘት (መክ4፡9-12) ያለውን
በባልና ሚስት መካከል ክፍል አንብቡ፡፡
ያለው አንድነት ምን
ጥቅም አለው? ባልና ሚስት በኑሮአቸው እርስ በርስ እየተደጋገፉ ይኖራሉ፡፡ ሁለቱም እውቀታቸውን፣
ክህሎታቸውን፣ ጉልበታቸውንና ያላቸውን ነገሮች ሁሉ አንድ ላይ በማቀናጀት ኑሮአቸውን
ለማሻሻል መጣር ይገባቸዋል፡፡ ሁለቱም የምችሉትን ሁሉ ማድረግ ይገባቸዋል እንጂ አንዱ
በሌላው ላይ ጥገኛ መሆን አይጠበቅበትም፡፡

ለመልካም የወሲብ ግንኙነት

ሁለተኛው ጋብቻ የተመሠረተው ባልና ሚስት አብረው ወሲብ እንዲፈጽሙ ነው፡፡


‹‹አንድ ሥጋ መሆን››
እግዚአብሔር ሴትን ሠርቶ ወደ ወንዱ ሲያመጣት፣ ወንዱ ቃል ኪዳን ገብቶ ተቀበላት፡፡
ምን ማለት ነው?
ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር ሰው ከቅርብ ቤተሰቡ ተለይቶ ከትዳር ጓደኛው ጋር እንደሚጣበቅ
ተናገረ፡፡ ከዚያም በ(ዘፍ2፡24) ላይ ‹‹ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ›› ይላል፡፡

ባልና ሚስት አንድ ሥጋ መሆናቸው ከሚገለጽባቸው መሠረታዊ ነገሮች መካከል ዋነኛው


አብረው ወሲብ መፈጸማቸው ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት መሠረት ባል ከሚስቱ፣
ሚስትም ከባልዋ ጋር ብቻ ወሲብ እንዲፈጽሙ ይፈቀዳል፡፡ ወሲብ ባል ለሚስት፣ ሚስትም
ለባልዋ ፍቅራቸውን የሚገልጹበት መንገድ ነው፡፡ የሁለቱ የፍቅር መገለጫ ሲሆን
ሁለቱንም በሚያረካ መንገድ ሲፈጸም ግንኙነታቸውን ወደላቀ ደረጃ ያሳድጋል፡፡

የተፈጠሩ ወንድና ሴት በ(ዘፍ1፡31) ላይም እግዚአብሔር የፈጠራቸውን ሰዎች ባረካቸው ይላል፡፡ የባረካቸውም
እንዴት ተባዝተው ምድርን ‹‹ብዙ ተባዙ፣….›› በማለት ነበር፡፡
መሙላት ይችላሉ?
ወንድና ሴት ተባዝተው ምድርን መሙላት የሚችሉት ልጆችን ሲወልዱ ነው፡፡ ልጆችን
ለመውለድ ደግሞ ሁለቱ ወሲብ መፈጸም ይኖርባቸዋል፡፡ ስለዚህ በዚህም ክፍል ወሲብ
ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ እንደተጠቀሰ መመልከት ትችላላችሁ፡፡ በ(ዘፍ4፡1) ላይም
‹‹አዳምም ሚስቱን አወቀ›› ካለ በኋላ እርሷም ልጅ እንደ ወለደች ይናገራል፡፡ ወሲብን

Page 3 of 4
Poimen Ministry – Email: poimenministry516@gmail.com

በተመለከተ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ወደፊት የምትማሩት ስለሆነ ለጊዜው በዚው ላይ


እናቆምና ወደ ሌላ የጋብቻ ዓላማ እንመለስ፡፡

ዘርን ለመተካት

ሦስተኛው የጋብቻ ዓላማ ዘርን መተካት ነው፡፡ እግዚአብሔር ሰውን ወንድና ሴት አድርጎ
ከፈጠረ በኋላ በመጀመሪያ ሲባርካቸው ‹‹ብዙ ተባዙ ….›› (ዘፍ1፡31) አላቸው፡፡
እግዚአብሔር የወንድና የሴትን የዘር ፍሬ ከባረከ፣ ልጆችን መውለድ በረከት ነው፡፡ ልጆች
የሚወለዱት ባልና ሚስት ወሲብ ሲፈጽሙ ነው፡፡ ወሲብ ደግሞ መፈጸም ያለበት በጋብቻ
ውስጥ ነው ብለናል፡፡ እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ቃል ልጆች መወለድ ያለባቸው በትዳር
ውስጥ ነው፡፡ በዚህ ዐይነት መንገድ ከተወለዱ፣ ልጆች ከወላጆቻቸው ተገቢውን ሁለንተናዊ
እንክብካቤ በማግኘት ማደግ ይችላሉ፡፡

ባልና ሚስት ሁለቱ ብቻ ቤተሰብ ናቸው፡፡ ጋብቻቸው ያለ ልጅ ሙሉ ነው፡፡ ልጆች የጋብቻ


ባልና ሚስት ልጆችን
ውጤት ናቸው፡፡ ባልና ሚስት በተለያዩ ምክንያቶች ልጆችን መውለድ ባይችሉ ጋብቻቸው
ለመውለድ ትዳር
ከመሠረቱ በኋላ ልጅ ጎዶሎ እንደሆነ ማሰብ የለባቸውም፡፡ እግዚአብሔር እንደ አንድ ቤተሰብ ያያቸዋል፡፡ እንደ
መውለድ ባይችሉ ምን ማንኛውም ሰው ተጋብተው ልጅ መውለድ ፈልገው፣ መውለድ ያለመቻል በሕይወት ዘመን
ማድረግ ይጠበቅባቸዋል? ከሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች አንዱ ቢሆንም ልጅ ባለመኖሩ የተመሠረተው ትዳር መፍረስ
የለበትም፡፡ ባልና ሚስት የገጠማቸውን ተግዳሮት እንደ እግዚአብሔር ቃል ገንቢ በሆነ
መንገድ መያዝ ይችላሉ፡፡ ልጆችን በተመለከተ ወደፊት በስፋት ትማራላችሁ፡፡

በጋብቻና ቤተሰብ ውስጥ ባልና ሚስት የሚያገኙአቸው መልካም በረከቶች እነዚህ ብቻ


አይደሉም፡፡ ሌሎች ብዙ በረከቶች አሉ፡፡ ባልና ሚስት እነዚህን ለማግኘት መፈለጋቸው
መልካም ሐሳብ ነው፡፡ ሆኖም ባልና ሚስት እነዚህን በረከቶች ማግኘት የሚችሉት ማድረግ
የሚገቧቸውን ነገሮች በማከናወን ነው፡፡ እነዚህን በረከቶች ስላገቡ ብቻ እንዲሁ ማግኘት
አይችሉም፡፡ በረከቶቹ የግል ሰብዓዊ ድርሻን በማከናወን ይገኛሉ፡፡

ተጋቢዎች በትዳር ውስጥ ከዚህ በታች የተጠቀሱ ግቦችን ለማግኘት ቢሠሩ ደስታና ሰላም
የበዛበት ግንኙነት ይኖሯቸዋል፡፡

በጋብቻ ውስጥ የሚገኙ ሌሎች በርካታ ጥቅሞችን ደግሞ የማግባት ጥቅሞች በሚለው
ርዕስ ሥር ወደፊት እንመለከታለን፡፡

ባልና ሚስት እነዚህን መልካም ግቦችን ስላስቀመጡ ወይም ስለተመኙ ብቻ አያገኙም፡፡


እነዚህን ግቦች ለመምታት ባልና ሚስት ተገቢውን ሚና መጫወት ይኖርባቸዋል፡፡

ጥያቄዎች

❖ ……………………………………………..……….

❖ ………………………………………………………

Page 4 of 4

You might also like