Professional Documents
Culture Documents
“መቅድም”
ማለፊያ ሥነ ጽሑፍ፣ የአንድ ህዝብ ህይወት እና መንፈስ መልክ ነው። ደራሲዎች፣ ህዝቡራሱን
የሚያይበት መስታወቶች ናቸው። አንድ ማህበረሰብ በደራሲዎቹ ውስጥ ራሱን ያየዋል፤ በዚህም
መንገድ እያንዳንዱ ሕብረተሰብ በሥነ ጽሑፍ ስራዎቹ ውስጥ እጁ አለበት ብሎ አፍን ሞልቶ
መናገር ይቻላል። የፀሀፊዎችን ህይወት ማጥናት ጥበባቸውን ወይም ጥበበኛ ያደረጋቸውን ነገር
አይገልጽም። ነገር ግን እንደዚህ ያለ መረጃ፣ ደራሲዎች የሚጽፉትን ለምን እንደሚጽፉ ያስረዳል።
የሚኖሩበት ማህበረሰብ፣ አካባቢ እና ዘመን የሚጽፉበትን ጭብጥ እና ይበልጡንም
አመለካከታቸውን ይወስናል። ነገር ግን ማህበረሰብ፣ አካባቢም ሆነ ዘመን ጥበብንም ሆነ ጥበበኛ
እንዴት እንደሚፈጠር ሊገልፁ አይቻላቸውም (አንዳንድ ዘመናት በርካታ ጥበበኞችን
ማፍራታቸው የታመነ ሀቅ ቢሆንም ቅሉ።
ይህንን የኢትዮጵያ ደራሲያን የሕይወት ታሪክ ስብስብ እንዲሳካ ለረዱኝ ሁሉ ከባድ ውለታ
አለብኝ። መጽሀፉ የተፃፈው የኢትዮጵያ የሥነ ጽሑፍ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ በደንብ
እንዲታወቅ ለማድረግ በሚል አላማ ነው።
እነኚህ ሁሉ የደራስያን ምስሎች የተከተቡት፣መንግስቱ ኃይለማርያም ገና ስልጣን ላይ በነበረበት
ግዜ ላይ መሆኑ መታወቅ አለበት። ይህ ሁኔታ አንዳንድ ደራሲዎች ስለ ሕይወታቸው እና ሥራቸው
ከልብ እንዳያወሩ አግዶ ይሆናል።
በመጽሑፉ ውስጥ ለሰፈሩት ታሪኮች ሁሉ ሐላፊነቱ የእኔ እንደሆነ መጥቀሱ መቼም ያን ያህል
አያስፈልግ ይሆናል።አንዳንዴ የመረጃ ምንጮቼን በአግባቡ ሳልረዳ ቀርቼ ይሆናል ፤ ወይ ደግሞ
በስማ በለው የተሳሳተ መረጃ ደርሶኝ ይሆናል። ለተፈጠሩ ስህተቶች እየተፀፀትኩ ይቅርታ
እጠይቃለሁ። ይህ መጽሀፍ የተፃፈው የአማርኛንሥነ ጽሑፍ እና ፈጣሪዎቹን ከልብ በማድነቅ
እንዲሁም በሌሎች ? እንዲታወቅ እናእንዲደነቅ በመሻት ነው።
ሬዱልፍ ኬ. ሞልቬር
ኢትዮጵያ ለክፍለ ዘመናት የኖረ የጽሑፍ ባህል አላት። ከክርስትና ?በፊት ጀምሮ በድንጋይ ላይ
የተቀረጹ ጽሁፎች ነበሩ። ነገር ግን ክርስትና በመንግስት ደረጃ እና በሕዝቡም ዘንድ በ4ተኛው
ክፍለ ዘመን ቅቡል ከሆነ በኋላ በተለይ የሐይማኖት መጽሀፍት እየተተረጎሙ መቅረብ ጀመሩ።
መጽሐፍቱ በዘመኑ መግባቢያ በነበረው በግእዝ ቋንቋ የተዘጋጁ ሲሆን ። በየክፍለ ዘመኑ እድገት
ከታየ በኋላ መቀዛቀዝ በመከተሉ እስከ መካከለኛው ዘመን ድረስ የተዘጋጁት አዳዲስ መጽሀፍት
ጥቂት ነበሩ። ግዕዝ የንግግር ቋንቋ መሆኑ ካበቃ በኋላ ከ14ተኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የግዕዝ ሥነ
ጽሑፍ እያንሰራራ መጣ።
ከ1000 ዓ ም አካባቢ ጀምሮ ግዕዝ በሌሎች የንግግር ቅጦች ወይም ቋንቋዎች እየተተካ መጣ።
ጥንታዊው አማርኛ እራሱን ችሎ እንደቋንቋ ያቆጠቆጠው በዚህ ግዜ ሳይሆን አይቀርም። ነገር ግን
የሰለሞናዊ ስርወ መንግስት በ1270 ወደ መንበረ ስልጣን ከተመለሰ ከጥቂት ግዜ በኋላ ገዢዎችን
የሚያወድሱ እስከአሁን ተጠብቀው ከቆዩ ንጉሣዊ መወድሶች በስተቀር አማርኛ ለሥነ ጽሑፍ
(ፋይዳ) እምብዛም ጥቅም ላይ አልዋለም። በጽሑፍ አልሰፈሩም እንጂ ተረቶች፣ መዝሙሮች እና
ሌሎችም ሥነ ቃሎች በአማርኛ ይሰናዱ ነበር።
***
ከኢጣሊያ ወረራ በኋላ ከበደ ሚካኤል የኢትዮጵያ ቀዳሚ ገጣሚ እና ፀሀፊ ተውኔት ሆነው ብቅ
አሉ። ተውኔቶቻቸው የተፃፉት ቤት በሚመቱ ጥንድ ስንኞች ሲሆን ቋንቋቸው ሊኮርጁት
የማይቻል መሆኑን ብዙ ኢትዮጵያውያን እያደነቁ ይናገራሉ። የአውሮፓን ዘመን ተሻጋሪ የሥነ
ጽሁፍ ስራዎች አዛምደው ከመተርጎማቸውም ሌላ ብዙ የታሪክ መጽሀፍት ጽፈዋል።
በእርግጥ ሐዲስ አለማየሁ መፃፍ የጀመሩት ከጠላት ወረራ በፊት ሲሆን በኢጣሊያ በጦር
እስረኝነት ጥቂት ግዜ አሳልፈዋል። በሰዎች ዘንድ የሚታወቁት ግን ከጦርነቱ በኋላ በሰሯቸው
ስራዎች በተለይ በታላቁ "ፍቅር እስከ መቃብር" ነው። ከዚህም በኋላ ሌሎች ሁለት ትልልቅ
መጽሀፍትን አስከትለዋል። ይህ ለአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ያበረከቱት ትልቁ አስተዋጽኦ እንጂ ብቸኛ
አይደለም።
ከነኚህ ፋና ወጊዎች በኋላ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የሥነ ጽሑፍ ስራዎችን ያበረከቱ ደራሲያን ቁጥር
ያለማቋረጥ ጨምሯል። አቤ ጉበኛ ብዙ ቢጽፍም ቅሉ ከምርጦቹ አንዱ ግን አልነበረም። ብርሀኑ
ዘርይሁን እና በአሉ ግርማ ከዘመናዊ ፀሀፊዎች መሀል ተጠቃሾች ናቸው። ነገር ግን ወዲያውኑ
ሌሎች እንደ ማሞ ውድነህ፣ ዳኛቸው ወርቁ፣ መንግስቱ ለማ፣ ፀጋዬ ገብረመድህን የመሳሰሉት
ደራሲዎች ብቅ ብለዋል፦ የደራሲዎችን ስም እዚህጋ መዘርዘሩ የተለየ ዓላማ የለውም ፤ ይልቁንም
መጠቀስ የሚገባቸው ሁሉ የሕይወት ታሪካቸው ከዚህ ቀጥሎ ሰፍሯል።የቲያትር ተመልካቾች
ጥቂት ከመሆናቸውም ባሻገርተውኔቶቻቸውባለመታተማቸው ("ሰዎች ተውኔቶችን አያነቡም"
በሚል ምክንያት) ፤ነጥረው ከወጡጥቂቶች በስተቀር ፀሀፌ ተውኔቶች በብዛት አልተቃኙም።
በ1953 ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ላይ ከተደረገው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ በኋላ በጥብቅ ሳንሱር
ማድረግ ተጀመረ። ነገር ግን በተመሳሳይ ወቅት እውነታዊነት እና ዘመናዊነት ወደ አማርኛ ሥነ
ጽሑፍ እየመጣ ነበር። እስከ 1966ቱ አብዮት ድረስ የቀረቡልብወለዶች እና ተውኔቶች ይህ
መንፈስ የዘለቃቸው ነበሩ።ደራሲዎችም ማህበራዊ ችግሮች ላይ፣ በተለይ ዘውዳዊ ክብር፣ መንግስት
እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ ትችቶችን ለመሰንዘር የሚያመች ልዩ አይነት አፃፃፍ
ፈጠሩ ።
ከ1966 አብዮት በኋላ ሊያከናውኗቸው የሚችሏቸው ተግባሮች እጅግ በጣም ውስን ስለነበሩ
ሰዎች ከበፊቱ የበለጠ ያነባሉ። በንጉሳዊው ዘመን ከነበረው በላቀ ቁጥር መጻሕፍት አሁን መታተም
ጀመሩ። የሐዲስ አለማየሁ ሶስተኛ ልብወለድ "የልምዣት" 50,000 ቅጂዎች ታትሞ ወዲያው
ተሽጦ በማለቁ እንደገና ታትሟል10። የቴአትር ተመልካች ቁጥርም ከአብዮት በኋላ በማደጉ፤
ለወራት ብሎም ለአመታት የሚታዩ ተውኔቶች ነበሩ። ይህ አዲስና ነባርደራሲዎችንም አበረታቷል።
የአማርኛ መጽሀፍት ሕትመት በፍጥነት እያደገ ቢመጣም ለማሳተም ያልሞከሩ ወይንም ያላሳተሙ
ግን አሉ። ይህምከነበረው የፖለቲካ ሁኔታ አንጻርችግር ውስጥ ላለመግባት ከመፈለግ ወይንም
በራስ ችሎታ ባለመተማመን ሊሆን ይችላል።12አርታኢዎች አይተዋቸው ለህትመት ተቀባይነትን
ካገኙና ለአሳታሚዎች ከተሰጡ በኋላ፣ ባለቤቶቻቸው መልሰው የወሰዷቸውም ስራዎች አሉ።
አንዳንድ ደራሲዎች በተለይ አዲሶቹ ከሌሎች ደራሲዎች ዘንድ ምክር ይጠይቃሉ። ነገር ግን ሁሌም
ምክሮቹን ተቀብለው ተግባራዊ ስለማያደርጉ መጽሐፍቶቻቸውን ለማሳተም ብዙ ስቃይ ያያሉ፡፡
ያውም ከታተመላቸው ነው። በዚህ መጽሐፍ የተካተተ አንድ ደራሲ ለምሳሌ፣ የፃፋቸው ብዙ
ረቂቆች ከአብዮቱ በፊትም ሆነ በኋላ በኢትዮጵያ ውስጥ ሊታተሙ እንደማይችሉ ተረድቶ ነበር።
በእርግጥ ቃለምልልስ ካደረግኩለት ጥቂት ግዜ በኋላ አንድ የአጫጭር ታሪኮች ስብስብ ማሳተም
ችሏል።
***
ከእነኚህ ስብስቦች መሀል የማካትተው አንዲት ሴት ደራሲ እንኳን ባለማግኘቴ አዝናለሁ። የሕሩይ
ወልደሥላሴ ልጅ የሆኑት ላቀች ሕሩይ ለወጣቶች የሚሆን ምክር በብእር ስም ጽፈው ነበር፡፡ ነገር
ግን ልጣቸው የራሰ፣ መቃብራቸው የተማሰ እንደሆነ ተነገረኝ። ሌላዋ ስንዱ ገብሩ (የከንቲባ ገብሩ
ደስታ ልጅ) ብዙ ጽፈዋል፡፡የታተመላቸው አንድ መጽሐፍ ብቻ ሲሆን ሌላው በኢትዮጵያ ጥናት
ኢንስቲትዩት አዲስ አበባ ይገኛል። ነገር ግን እኔ ስለእርሳቸው የፃፍኩትን አልተቀበሉትም ፤
ስለራሳቸው ለመፃፍ የገቡትንም ቃል አልጠበቁም። አሮጌው አየር ማረፊያ አካባቢ በሚገኘው
ቤታቸው ብዙ የወዳጅነት ጨዋታዎች ብናደርግም ለቃለመጠይቅ ፈቃደኛ አልነበሩም።
በኢትዮጵያ ውስጥ የበሳል ሥነ ጽሑፍ ተፈላጊነት እየጨመረ መምጣቱ ደራሲዎች ወደፊት የተሻለ
ህይወት እንደሚኖራቸው ተስፋ ሰጪ ነው ፤አንባቢዎችም አማርጠው የሚያነቡት ሰፊ መስክ
ይኖራቸዋል። ምናልባት ደራሲዎች ለጥበብ ብቻ ብለው የሚኖሩበት እና በዚያ ብቻ
የሚተዳደሩበት ጊዜም እየመጣ ይሆናል።
ማስታወሻዎች
6) በመኳንንት ቤተሰብ ውስጥ ልጅ የሚለው ቅጥያ ምንም ማዕረግ ለሌላቸው ሰዎች ይሰጣል።
እያሱ ኢትዮጵያን በመሩበት ወቅት አቤቶ ተብለው ይጠሩ ነበር ፤ ንጉስ ተብለው አልተቀቡም።
10) መጽሀፉ ልክ እንደ ኦሮማይ ከሰው እጅ እየተቀማ ይሰበስባል ብለው በመስጋታቸው ሁለትም
ሶስትም ቅጂዎች የገዙ ነበሩ።
11) የሳንሱረኞቹ ማህተም ካላረፈበት ግን ምንም ነገር ሊታተም አይችልም ነበር። የታተሙ
መጽሀፍት እራሳቸው ከተፈቀደው ውጪ ሌላ ነገር አለማካተታቸውን ለማረጋገጥ በድጋሚ ሳንሱር
ይደረጋሉ ። አንዳንዴ ሳንሱር አድራጊዎቹ በአንደኛው ዙር የፈቀዱትን በሚቀጥለው ዙር
ይከለክሉና በደራሲውእና በአሳታሚው ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ያደርሳሉ።
12)አስተዋፆዎቻቸው ከሥነ ጽሑፍ ይልቅ ለተረት የሚቀርብ የአንድ ታላቅ ደራሲና ሊቅ ታሪክም
አካትቻለሁ። ለተረት መቅረባቸው በስማቸው ብዙ ስለሚባልና ስለሚፃፍ ነው።
13) ወታደራዊው መንግስት ሥልጣን ላይ እስካለ ድረስ፣ የበአሉ ግርማ እጣ፣ ለብዙዎች
የማስጠንቀቂያ ደወል ነበር።
የተርጓሚዎቹ ማስታወሻ
በተረፈ ለበርካታ አመታት ከጎናችን ሳትለዩ በፌስቡክ የንባብ ቡድናችን አብራችሁን ለነበራችሁ
የመላው የBOOK FOR ALL የፌስቡክ ቡድንና የBOOK FOR ALL ETHIOPIA ገጽ
ተከታታዮች በሙሉ ምንም እንኳን ለእናንተ ፍቅርና አክብሮት ብታንስም ይህችን እጅ መንሻ
በመታሰብያ አምሐነት ስናቅርብ እጅግ የላቀ ደስታ እየተሰማን መሆኑን ልንገልጽ እንወዳለን፡፡
እናመሰግናለን
ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው
2 ኅሩይ ወልደሥላሴ…………………………………………………………………………………..26
3 አቤ ጎበኛ……………………………………………………………………………………………..55
4 ተክለሐዋርያት……………………………………………………………………………………….60
5 በእምነት ገብረአምላክ………………………………………………………………………………88
6 ማሞ ውድነህ………………………………………………………………………………………..94
7 ይልማ ሐብተየስ…………………………………………..………………………………………114
9 መኮንን እንዳልካቸው……………………………………………………………………………..141
10 ዳኛቸው ወርቁ…………………………………………………………………………………..152
11 እምሩ ኃይለሥላሴ………………………………………………………………………………167
12 አማረማሞ……………………………………………………………………………………….210
15 ብርሀኑ ዘርይሁን………………………………………………………………………………...249
16 ስብሐትገብረእግዚአብሔር……………………………………………………………………..265
17 አሰፋገብረማርያም ተሰማ……………………………………………………………………….275
18 ፀጋዬ ገብረመድህን………………………………………………………………………………291
19 መንግስቱለማ…………………………………………………………………………………….297
20 ታደለ ገብረሕይወት……………………………………………………………………………..313
21 አለቃ ገብረሃና……………………………………………………………………………………321
22 አበራ ለማ………………………………………………………………………………………..328
23 ተስፋዬ ገሠሠ……………………………………………………………………………………335
24 ሳህለሥላሴ ብርሃነማርያም……………………………………………………………………..361
25 ታደሰ ሊበን………………………………………………………………………………………380
26 ሲራክ ኅሩይወልደሥላሴ………………………………………………………………………..392
27 በዓሉ ግርማ……………………………………………………………………………………..397
28 ከበደሚካኤል …………………………………………………………………………………………………………………….410
ጥቋቁር አናብስት
ሐዲስ አለማየሁ
የፖለቲካ ሰው እና ቁንጮ ኢትዮጵያዊ ደራሲሐዲስ አለማየሁን
ለመጀመሪያ ጊዜ ያየኋቸው በጎርጎሳውያኑ 1970 አካባቢ ነው።
ቦታውም ከአዲስ አበባ100 ኪሜ አካባቢ በምትርቀው ዝነኛ
የመዝናኛ ቦታ ሶደሬ ነበር። በወቅቱ አንዱንም መጽሀፋቸውን
አላነበብኩም፤ ስለእርሳቸው የማውቀውም አንዳች ነገር አልነበረም።
ነገር ግን "ዝነኛው የኢትዮጵያ ደራሲ" መሆናቸው ተነግሮኛል ።
ቀጥዬ በ1978 ዓ.ም እስከማገኛቸው ድረስ፣ የፃፏቸውን ሁሉንም
መጽሀፍት ከማንበቤ ባሻገር ስለ ፖለቲካ ሰውነታቸው በብዛት
ሰምቻለሁ። ከዚህ ቀደም ብዬ እ.ኤ.አ በ1980 ስለ ኢትዮጵያ ሥነ
ጽሑፍ አንድ መጽሐፍ ጽፌ ነበር። በመጽሐፉ የሐዲስ አለማየሁ ሥራዎችን በሰፊው ዳስሼያለሁ።
በወቅቱ መጽሐፉን ልኬላቸው ስለነበር ሀዲስ አለማየሁ ስለእርሳቸው የፃፍኩትን አንብበው
እንደወደዱት ኋላ ነግረውኛል። “ሙገሳው ቢበዛም በደስታ ተቀብዬዋለሁ” ነበር ያሉኝ። በ1978
ዓ.ም ሊያገኙኝ ተስማሙ፤ በእርግጥ ይጽፉት የነበረውን መጽሐፋቸውን ረቂቅ ለማረም፣
ለመጨረስና ለአታሚዎቹ መላክ ይፈልጉ ስለነበር የቀጠሮአችንን ቀን፣ማስተላለፍ መረጡ። ሁሉም
ተሳክቶ በመጨረሻ በህዳር 1978 ስንገናኝ የደከሙና የተሰላቹ መስለው አገኘኀቸው፤ረዥም
ቃለመጠይቅ ለማድረግም አመነቱ። ነገር ግን አንዴ በቀላል ጥያቄዎች ካስጀመርኳቸው በኋላ፣
ሁለታችንም ጨዋታውን ለማቆም ቸገረን። እያንዳንዳቸው ረዥም ሰአት የፈጁ ብዙ
ቃለመጠይቆችን አደረግን።በቆይታችን ወቅት ሁሉ ሐዲስ ግልጽ፣ ሰው ወዳድ፣ ቀጥተኛና ተግባቢ
ነበሩ።
ሐዲስ አለማየሁ አዲስ አበባ1 ውስጥ አስመራ መንገድ ላይ ከቡልጋሪያ ኤምባሲ አጠገብ፣ በግንብ
በታጠረ ና በእጽዋት በተሞላ ደስ የሚል ግቢና ቤት ውስጥ ።ከሶስት ዘመዶቻቸው ጋር አብረው
ይኖሩ ነበር። ሁሌም የምንገናኘው ማረፊያ ክፍላቸው ውስጥ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ባህላዊ ምንጣፍና
ሁለት ሶፋዎች ክፍሉን አሳምረውታል። ግድግዳው ላይ ያለው ብቸኛ ጌጥ፣ በእሳት ማንደጃው
ትክክል የተሰቀለው የጢስ አባይ ፏፏቴ ቅብ ስእል ብቻ ነው። አቶ ሀዲስ አቅም እንደሚያንሳቸውና
እንደሚደክማቸው ቢናገሩም ጤነኛ ይመስሉ ነበር። የጤናቸውን ሁኔታ ለመከታተል ሀኪም ጋር
ሄደውፀረ–ሕዋስ መድኀኒት ታዞላቸው ነበር። መድኀኒቱ እንደውም ድካማቸውን አባባሰባቸው።
በጭንቅላታቸው ጎን፣ በግራና በቀኝ፣ ፀጉራቸው እንደ መሸበት ብሏል፤ ግን ከዚህ ይልቅ ጎላ ብሎ
የሚታየው ከግንባራቸው ገለጥ ያለ በራቸው ነው። ከላይ የፊት ፍንጭታቸውበቀር ጥርሳቸው
ሙሉ ነው። ደግሞም በደንብ ይሰማሉ፣ ያያሉ፣ ያወራሉ። አእምሮአቸው ንቁ ነው፣ የማስታወስ
1
ጥቋቁር አናብስት
****
ሐዲስ አለማየሁ የተወለዱት በ1902 ዓ.ም አካባቢ ሳይሆን አይቀርም። በዛኔይቱ ኢትዮጵያ ልደት
አይመዘገብም ነበር፤ ስለዚህ የትውልድ ዘመናቸውን በግምት 1906 ዓ.ም ብለው በሕጋዊ ሰነዶች
ላይ አስፍረዋል። ኋላ ግን አንድ ነገር ጥርት ብሎ ታወሳቸው። እናታቸው በልጅነታቸው “ሰዎች
እድሜህን ከጠየቁህ፣ በሰገሌ ጦርነት ጊዜ ሰባት አመቴ ነበር ብለህ መልስ”ያሉት ትዝ አላቸው። ይህ
ጦርነት በ1909 ዓ.ም እንደመካሄዱ የሐዲስን የትውልድ ዘመን 1902 ዓ.ምያደርገዋል።
እንደውም ቀኑ እራሱ የሰገሌ ጦርነት በተካሄደበት የጥቅምት ወር እና ቀን ሳይሆን አይቀርም።
ሐዲስ የተወለዱት በጎጃም ክፍለ ሐገር፣በደብረ ማርቆስ አውራጃ፣ በጎዛምን ወረዳ፣ እንዶዳም2
በምትባል ትንሽ መንደር ነበር። በመንደሩ አጠቃላይ የሚኖሩ ቤተሰቦች ከ100 ያንሳሉ፤ እንደውም
ግፋ ቢል ከ50 ወይ 60 አይበልጡም።
አባታቸው አቶ አለማየሁ ሰለሞን ቅድሚያ ካህን፣ ከዚያም አለቃ ሆነዋል። ትውልዳቸው ኤልያስ
ቢሆንም አግብተው የወለዱት እንዶዳም ነው። ቢሆንም ሐዲስ ገና ሁለት ዓመታቸው እያለ
ጨቅላውንና እናቱን ጥለው ወደ ኢሊባቦር ተሻገሩ፤ በቅስናው ለመቀጠል ሳይሆን አይቀርም።
አለቃ የሚለውን ማእረግ ያገኙትም እዛው ኢሉባቡር እያገለገሉ ሳለ ነው3። እናታቸው ደስታ
አለሙ የእንዶዳም ተወላጅ ሲሆኑ በ16ተኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያ ግማሽ በአህመድ ግራኝ
ወረራ ወቅት በነበረው የኦሮሞ እና የአማራ ጋብቻዎች የተነሳ በደማቸው ውስጥ የኦሮሞ ዝርያ አለ።
አባቷ የዜማ መምህር እና መራቂ ሲሆኑ ይኸም ተማሪዎች ዜማ ካጠኑ በኋላ የሚፈትን ሊቅ ማለት
ነው። ሐዲስ በእናቶቹ ወላጆች፣ በአያቶቹ ቤት፣ በእናቱ እጅ አደገ። ለእናቱ እና አባቱ ብቸኛ ልጅ
ቢሆንም፣እናቱ ከሁለተኛ ጋብቻቸው ሁለት ወንድ እና ሶስት ሴቶች ልጆች ወልደዋል። ከነዚህ
መሐል አንድ ወንድ እና ሁለት ሴት ልጆች፣ እስከ 1978 ዓ.ም ድረስ በሕይወት የነበሩ ሲሆን
ሐዲስ ወንድሜ እና እህቶቼ እያሉ በአክብሮት ይጠሯቸዋል። አባታቸው ዳግመኛ ቢያገቡም ሌላ
ልጅ አልወለዱም። ሐዲስ ከእናታቸው አባት ዘንድየዜማ ትምህርታቸውን በ6 ዓመታቸው
ጀምረው እስከ 15 ዓመታቸው ድረስ ቀጠሉ። ፆመ ድጓን አጠናቀው ጨርሰዋል ፤ አሁንም ቢሆን
ጥሩ የዜማ አዋቂ አድርገው እራሳቸውን ይቆጥራሉ። ከዚያም ወደ አባታቸው ሐገር ኤልያስ
አቅንተው ቅኔ ተማሩ። ቀጥሎም ወደ ደብረወርቅ ከዚያ ዲማ በመሄድ የቅኔ ትምህርታቸውን በ17
2
ጥቋቁር አናብስት
ወይም 18 ዓመታቸው አጠናቀቁ። የቅኔ ትምህርታቸው ከተለመደው ሁለት ዓመት ወይም ትንሽ
በለጥ የሚል ጊዜ ወስዶባቸዋል። ሀዲስ ያደጉበት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ስርአት ቅባት በመባል
ሲታወቅ፣ በጎጃም ስር የሰደደ ነው።
ሐዲስ ደስ የሚል የልጅነት ጊዜ ያሳለፉ ሲሆን፣ በተለይ የእንዶዳሙ የተለየ ነበር። በዚያች ትንሽ
መንደር ከብቶችን እያገዱ፣ ከወንድ እና ሴት ልጆች ጋር በመጫወት ጣፋጭ ጊዜ ያሳልፉ ነበር።
ከእኩያዎቹ ጋር መጫወት በመውደዳቸው ሃላፊነታቸውን አልተወጡም፣ ጨዋታ እና ቧልት
አብዝተዋልበሚል ይደርስባቸው የነበረውን ግሳፄና ቅጣትያስታውሳሉ።እንዲህም ሆኖ ሐዲስ
ደስተኛ ህፃን ነበሩ፤ጥሩ የልጅነት ትዝታዎችም አሏቸው። ከተማሪነት ሕይወታቸው ይልቅ
በመንደር ሕይወታቸው ሀሴት አድርገዋል። ትምህርታቸውን በቁምነገር ጉዳዬ ብለው የያዙት፣
አዲስ አበባ መጥተው ዘመናዊ ትምህርት ከጀመሩ በኋላ ነው። እዚህ ፈተናዎች ስለሚኖሩ፣
በርትተው መማርና ማጥናት ይጠበቅባቸው ነበር።የደብረወርቅና የዲማ4 ትዝታዎቻቸው
የሚያጠነጥኑት በቤተ ክርስቲያን እና በትምህርታቸው ዙሪያ ነው።ቅኔ ቢወዱም፣ በዚህ ዐይነት
የሥነ ግጥም ዘርፍ አልገፉበትም፤ምንም የቅኔ መጽሐፍም አላሳተሙም።
በቅኔ ከተመረቁ በኋላ፣ ሐዲስ በ1918 ዓ.ም በዋና ከተማዋ በሚገኘው የቅዱስ ገብርኤል
ቤተክርስቲያን የአለቃነት ማእረግ ከተሰጣቸው የቀድሞ መምህራቸው ጋር ወደ አዲስ አበባ መጡ፡
፡ሐዲስ በመካነ እየሱስ ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ በሚገኘው የስዊድን ሚስዮን ትምህርት ቤት
ገቡ።ትምህርት ቤቱ የአምስት ኪሎ አደባባይ ከሚገኘው የቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅርብ
ነበር። ሐዲስ እዚህ ትምህርት ቤት ገብተው ትምህርታቸውን ከአንደኛ ክፍል ለመጀመር ተገደዱ።
ምክንያቱም እስካሁን ከባህላዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት ፈቅ አላሉም፤ከግዕዝና አማርኛ ቋንቋ
በስተቀር አያውቁም።አዲሱ ትምህርት ቤታቸው ደግሞ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ነበር የሚያስተምረው።
ርእሰ መምህራቸው ፔር ሶጆርን ሲባሉ መምራኖቻቸው ደግሞ ኤሪክሰን እና ኒልሰን ነበሩ።ሁሉም
ቄሶች ነበሩ። ሐዲስ ትምህርት ቤቱንም ሆነ መምህሮቻቸውን ወደዋቸው ለሁለት ዓመት ያህል
ቆዩ። ከዚያም የሶስተኛ ክፍል ትምህርታቸውን ለመቀጠል ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ገብተው
የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን እስከሚጨርሱ በዚያው ቆዩ። ከዚህ በኋላ በምኒልክ ትምህርት
ቤት የሚሰጠውን የመምህራን ማሰልጠኛ ትምህርት ከ6–8 ወር ለሚሆን ጊዜ ተከታተሉ። በ23
ወይም 24 ዓመታቸው ቀድሞ በተማሩበት የስዊድን ሚስዮን ትምህርት ቤት 1 ዓመት (8 ወይም
9 ወር) ለሚሆን ጊዜ በደስታ አስተማሩ።
3
ጥቋቁር አናብስት
ይህ ተውኔት ሀዲስ አለማየሁን ከቀደምት የኢትዮጵያ ፀሐፌ ተውኔቶች አንዱ ያደርጋቸዋል። ነገር
ግን ሐዲስ በተማሪነታቸው ወቅት፣ የብላቴንጌታ ኅሩይወልደሥላሴን “ወዳጄ ልቤን” ስላነበቡ፣
“ኅሩይ ቀዳሚ ነው” ይላሉ5።በተጨማሪም ዮፍታሔ ንጉሴ ከእርሳቸው ቀደም ብለው ተውኔት
ይጽፉ እንደነበር ይናገራሉ። ሐዲስ ይህንን ተውኔት ከፃፉ በኋላ መላኩ በጎሰው6 የተባሉ ፀሐፊ፣
ተውኔት መፃፍ ጀመሩ። በ1922 ዓ.ም የታተመው የብርሀንና ሰላም ጋዜጣ የሐዲስን ተውኔት
ጠቅሶጽፏል።
4
ጥቋቁር አናብስት
***
በ1924 ዓ.ም ሐዲስ ወደ ጎጃም ተመለሱ።ከ1918 እስከ 1924 ዓ.ምድረስ ያለፈው ጊዜ፣ ሐዲስ
ከሰሯቸው ስራዎች አንፃር አጭር ነበር። ቀኖቹን ያስቀመጥኩላችሁ ግን እሳቸው እንደነገሩኝ ነው።
1925 ዓ.ም ግንቀጥሎ ከሚሆነው ሁነት ጋር ይበልጥ የሚጣጣም ይመስለኛል።በመጀመሪያ
በዳንግላ የጉምሩክ ጽህፈት ቤት ጸሐፊ ሆነው ለ ሁለት ዓመትሰሩ።በዳንግላ የእንግሊዝ ቆንስላ
ጽህፈት ቤት ነበር። ነገር ግን ጽህፈት ቤቱ ተዘግቶ ቆንስሉ ወደ ሀገሩ ሲመለስ፣ ቆንስላ ጽህፈት ቤቱ
ወደ ትምህርት ቤትነት ተቀየረ። ሐዲስም ትምህርት ቤቱን ስራውን እንዲያስጀምሩና በርእሰ
መምህርነት እንዲያስተዳድሩ ተመረጡ። ከ1ኛ―3ኛ ክፍል የሚያስተምር አንደኛ ደረጃ
የመንግስት ትምህርት ቤት ነበር።ሐዲስ በዚህ የስራ ቦታ የቆዩት ለአንድ ዓመት ብቻ (ከ1926–
1927) ሲሆን።በአብዛኛው ሥራቸው መቆጣጠር እና ማስተዳደር ቢሆንም አልፎ አልፎ
እንግሊዝኛ ያስተምራሉ፤ለተማሪዎች የሚሆን መዝሙርም አዘጋጅተዋል።
ከዚያም በ1927 ዓ.ም ወደ ጎጃም ዋና ከተማ ደብረማርቆስ ተዘዋውረው በርእሰ መምህርነት ፈንታ
እንግሊዝኛ እና ሂሳብ ለሦስትና አራተኛ ክፍሎች ማስተማር ጀመሩ።ይኼም በወልወል ግጭት
ወቅት ሲሆን፤ እዚያ በቆዩበት አንድ ዓመት ከጣሊያን ጋር ጦርነት ሊኖር እንደሚችል ብዙ ይወራ
ነበር። በዚህ መሐል "የሀበሻና የወደኋላ ጋብቻ" የተባለ ተውኔታቸው ማስተካከያ ተደርጎበት፣
በደብረ ማርቆስ ለመድረክ በቃ። አስተዳዳሪው ራስ እምሩ ኃይለሥላሴ ሐዲስን ለአርበኝነት
የሚያነሳሳ አጭር ተውኔት እንዲጽፉ ጠየቋቸው።አዲስ የተጠየቁትን ከማድረጋቸውም ባሻገር
"የኢትዮጵያና የኢጣሊያ ጦርነት በአድዋ" የሚል መነባንብም ጨምረው አዘጋጁ። ትርኢቱ
የተዘጋጀውየሕዝቡን መንፈስ በወታደሮች ፉከራ ለማነቃቃት ሲሆን በአጠቃላይ ቀስቃሽና
5
ጥቋቁር አናብስት
***
6
ጥቋቁር አናብስት
***
7
ጥቋቁር አናብስት
ዘውዴ በችኮላ ወደ ውጭ ሐገር ለሥራ ሲሄዱ አቶ ኦሊቨር ስኮት ለሚባሉ ግለሰብ ሰጧቸው።
ሐዲስ እንደሚሉት እነዛ ግጥሞች ከዛ በኋላ ዳግመኛ አልታዩም ፤ ጠፍተው ቀሩ።
ሐዲስ ወዲያውኑ በፕሬስ እና ፕሮፓጋንዳ መስሪያ ቤት (ወይም የጋዜጣ እና መረጃ መስሪያ ቤት፣
በመጨረሻ የማስታወቂያ ሚኒስቴር በተደረገው) ስራ ተሰጣቸው፤ እዚያም ለ5 ወይም 6 ወር ሰሩ።
ከዚያም ለጥቂት ወራት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሰሩ።ሁለቱም ቦታ የሰሩበት ጊዜ ባንድነት
ቢቆጠር ከዓመት አይበልጥም።ከዚያም በየካቲት 1937 ዓ.ም በጊዜው በእንግሊዝ አስተዳደር ስር
በነበረችው በእየሩሳሌም የኢትዮጵያ ቆንሲል ሆነው ለሁለት ዓመት ሰሩ።በዚህ ወቅት ምንም
አልፃፉም።ነገር ግን እዚያው እየሩሳሌም ያደጉትንና እዚያው የሚኖሩትን ክበበ–ፀሐይ በላይን
አገቡ።
ከእየሩሳሌም በቀጥታ የተላኩት የኢትዮጵያ ዋና እና ብቸኛ የመገናኛ ተወካይ ሆነው፣ በአለም አቀፉ
የቴሌኮሙኒኬሽን ጉባኤ ለመካፈል ወደ አትላንቲክ ሲቲ፣ ሰሜን አሜሪካ ነበር። በጦርነቱ ጊዜ
እንዲህ ዐይነት ጉባኤ ስላልነበርና፣ ነገሮች ስርአት ባለመያዛቸው የሚሰራ ብዙ ስራ በመኖሩ
ከሃገራቸው ብቸኛ ተወካይ በመሆን ሁሉንም ስብሰባዎች(የፍሪክዌንሲ፣የአስተዳደርና የዲፕሎማቲክ
ጉባኤዎች)በአንድ ላይ መካፈል ነበረባቸው። ይህም ለአምስት ወራት ያህል ቆየ።
በኒውዮርክ በነበራቸው አስደሳች ጊዜ፣ ሐዲስ በተለይ ከማይረሷቸው ሁነቶች አንዱ፣ “የኢትዮጵያ
ቁርጥ ሀሳብ” ዋነኛው ነው። ከአዲስ አበባ ባለሥልጣኖች ጋር ብዙ አለመግባባት ውስጥ የዶላቸው
ይህ “ቁርጥ ውሳኔ” የኔውክሌር ሀይልን ለጦር መሳሪያነት መጠቀምን የሚከለክል ነው። ይኼም
በሁለት ክፍል የተከፋፈለ ነበር። የመጀመሪያው ክፍል በጠቅላላ ጉባኤው የኒውክሌር መሳሪያን
ለጦርነት እንዳይውል መግለጫ ማወጅ ነው፤ይህንን ተላልፎ መገኘት አለምአቀፍ ወንጀል ሲሆን፣
ተሳታፊዎቹም አለምአቀፍ ወንጀለኛ ይሆናሉ ማለት ነው።ይህ መግለጫ ህጋዊ ሀይል አይኖረውም።
የቁርጥ ውሳኔው ሁለተኛ ክፍል ጠቅላላ ጉባኤው ይህን ጉዳይ በተመለከተ አባላቱን ስብሰባ
እንዲጠራ ይጠይቃል።ይህ መግለጫ በዚያን ጊዜ በስምምነት ከተፈረመ፣አስገዳጅነት ይኖረዋል።
ብሪታኒያ፣ሰሜን አሜሪካናፈረንሳይ፣ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ ያሳየቸውን አቋም ለመቃወም በአዲስ
አበባ ተወካዮቻቸውን አስቀመጡ።ይህም ሩስያ ብዙ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ በማከማቸቷ፣
ምእራብያውያን ተመጣጣኝ መሳሪያ ከማከማቸት በስተቀር ሩስያ መሳሪያዎቿን እንዳትጠቀም
ለማገድ ሌላ የመከላከያ አማራጭ የሌላቸው መሆኑን በመግለጽ ነው።ስለዚህ ሐዲስ ከገዛ
መንግስታቸው ይህንን ቁርጥ ውሳኔ እንዲያቆሙ ብዙ ግፊት ተደርጎባቸዋል፤ሀዲስ ግን ቁርጥ
ውሳኔን እንደ ቀላል ማቅረብና መተው እንደማይችሉ ገለፁ። የዚህ ሁሉ እሰጥ አገባ መጨረሻ፣ጉዳዩ
ለድምጽ አሰጣጥ ይቅረብ የሚለው ጥያቄ በሚቀርብበት ጊዜ ሀዲስ ድምፀ ተዐቅቦን መምረጣቸው
ሆነ።
9
ጥቋቁር አናብስት
ከሁለት ዓመት በኋላ በ1953 ዓ.ም፣ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ብራዚልን ጎበኙ።ይህም በአዲስ አበባ
መፈንቅለ መንግሥት የተሞከረባቸው ዓመትማለት ነው።ሐዲስ በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ
በተባበሩት መንግሥታት የነበራቸውን ስራ ለቀው ነበር፤ አሁን ግን ለጠቅላላ ጉባኤው ምክትል
ተወካይ ሆነው፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ደግሞ ዋና ተወካይ ሆነው ላጭር ጊዜወደ የተባበሩት
መንግስታት ተመልሰዋል።ከግርማዊነታቸው ጋር አብሮ የሚጓዘው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ
በቅድሚያ ወደ ኒውዮርክ አቀና።ሐዲስም በጠቅላላ ጉባኤው የነበሩትን የኢትዮጵያ አባላት
ከመምራታቸው ባሻገር ከሚኒስትሩ ጋር በመሆን "የኢትዮጵያ ቁርጥ ውሳኔ" ሃሳብ ዳግም
እንዲያንሰራራ አደረጉ። ይህንንም ለማስፈፀም ሚኒስትሩ ፈቃደኛበመሆን በጠቅላላ ጉባኤው ፊት
ንግግር አደረጉ። ሐዲስም እንደውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነታቸው ቁርጥ ውሳኔው ፣ በጠቅላላ
ጉባኤው በከፍተኛ ድምጽ ፀደቀ። በጊዜው የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ ዳግ ሀመርስክጆልድ
የምክር ቤቱ አባላት በሸንጎ ተሰባስበው ቁርጥ ውሳኔውን እንዲፈርሙ እንዲጠሩ ተጠየቁ።
ጸሐፊውም ለሁሉም አባላት ተዘዋዋሪ ደብዳቤ በመላክ፣በተቆረጠ ቀን በሸንጎው ላይ ለመገኘት
ፍላጎት እንዳላቸው ጠየቁ። ከአባላቱ ሶስት አራተኛዎቹ ቢስማሙ፣ ይህንን ዐይነት ሸንጎ ማድረግ
ይቻላል። ለሁለት ወይም ሶስት ዓመታት ለሚሆን ጊዜ ከአባል ሀገራቱ የተገኘው አዎንታዊ ምላሽ
ሦስት አራተኛ አልሞላም። ስለዚህ ጉዳዩ ቀርቶ ሸንጎውም ሳይካሄድ ቀረ።
ግን በጠቅላላ ጉባኤው የፀደቀው መግለጫ አሁንም እንደፀና ነው። በዚህም የተነሳ አየርላንድ
የኒውክሌር ጦር መሳሪያ በፍጥነት መስፋፋትን የሚቃወም የቁርጥ ውሳኔ ሃሳብ ለማቅረብ ቻለች።
ይህ ውሳኔ በብዙ አባል አገራት ቢፈረምም ለማስፀደቅ የሚሆን ሸንጎ አልተካሄደም ይላሉ ሐዲስ።
የጦር መሳሪያ ቅነሳ ጉባኤው ከቁርጥ ውሳኔው ጀርባ የነበሩ ኢትዮጲያውያንን በሙሉ በአባልነት
ሲያሳትፍ ሐዲስም በዋና ተወካይነት ተመረጡ። ይህን ሀላፊነትም በለንደን አምባሳደር ሆነው
በቆዩበት ጊዜም ይዘውት ቀጥለዋል።
ሐዲስ በዚህ የተነሳ በታህሳስ 1953ቱ መፈንቅለ መንግሥትሙከራ ወቅት በኒውዮርክ ነበሩ።
ስለዚህተገደውም እንኳን ቢሆን ጎራ ለመለየት በሚያበቃቸው ስፍራ አልነበሩም።። ይልቁንም
ሁነቱን፣ንጉሡን ካስወገደውና የመንግሥት ለውጥ ካስከተለው የ66ቱ አብዮት ፍፁም
የተለየየህዝቡ ተሳትፎ ወይም ድጋፍ ያልነበረው “የቤተ መንግሥት ብጥብጥ” አድርገው
ይቆጥሩታል።
***
የተባበሩት መንግስታትን በ1953 ከለቀቁ በኋላ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታነት
ተሾሙ።ነገር ግን ይህን ሐላፊነት ይዘው ፍፁም አልሰሩም ምክንያቱም ወዲያው የትምህርት
10
ጥቋቁር አናብስት
በነኚህ ወራት ንጉሠ ነገሥቱን በተደጋጋሚ በማግኘት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። በዚህን
ጊዜ ነበር ሐዲስ ከጓደኞቻቸው በተሻለ ኃይለሥላሴን በቅርቡ የማወቅ እድል ያገኙት። ኃይለሥላሴ
ከሰዎች ጋር ብቻቸውን ሲሆኑ ልክ እንደ ተራ ሰው ተጫዋችና ፍልቅልቅ ሲሆኑ። እራሳቸውን
ለመግለጽ የሚጠቀሙት ተውላጠ ስምም “እኛ” ሳይሆን “እኔ” ነበር። ነገር ግን ሌሎች ሰዎች
ሲገቡ፣ በፍጥነት ይለወጡና አንድ እራሳቸውን “እኛ” ብለው በመጥራት ግርማዊነታቸውን
ይላበሳሉ።በግል ሲጫወቱ ስለ ግል ሕይወታቸው ያወራሉ፤ ስለ ሌሎች የግል ጠባይም ይጠይቃሉ።
ሁለገብና አስገራሚ ሰብእና ያላቸው ሰው ናቸው።ከአንድ ማንነት ወደሌላ ማንነት በቀላሉ
ይሸጋገራሉ።ሐዲስ እንደሚያስታውሱት መልካቸው ሳይቀር በተመሳሳይ ጊዜ በተወሰዱ የተለያዩ
ፎቶዎች ላይ ይቀያየራል።
11
ጥቋቁር አናብስት
ቀጥሎ በ1953 ዓ.ም መጨረሻ ሐዲስ የታላቋ ብሪታኒያ እና የኔዘርላንድ አምባሳደር ሆነው ወደ
ለንደን ተጓዙ። በዚያም ወደ ኢትዮጵያ እስከተጠሩበት 1958 ዓ.ም ድረስ ቆዩ። ይህ ቆይታቸው
ለሀዲስ አለማየሁ በጣም ጥሩ ጊዜ ነበር። እንግሊዝንና ለንደንን ወደዋቸዋል፤ኔዘርላንድንም
እንዲሁ―እንደውም ዘ ሄግንም በተደጋጋሚ ጎብኝተዋል ።
12
ጥቋቁር አናብስት
በ1961 ዓ.ም ሐዲስ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባል ሆኑ። በዚያም የ’66ቱ አብዮት እስኪፈነዳ
ድረስ አገልግለዋል። ከዚያ በኋላ ግን ጡረታ የወጡ ቢሆንም በጡረታ ላይ ግን ከሁለት ወይም
ከሶስት ወር በላይ አልቆዩም። ምክንያቱም ደርግ እንዲበተን የተደረገውን የቀድሞ ፓርላማን
ለመተካት ባቋቋመው የመማክርት ሸንጎ አባል እንዲሆኑ ስለተመረጡ ነው። እርሳቸው እንዴት
እንደተመረጡ ባያውቁም ´የጎጃም ህዝብ´ በዚህ ሸንጎ እንዲወክሉት እንደመረጣቸው ተነገራቸው።
ሐዲስ በመጀመሪያ እንዳረጁ፣ ጡረታም እንደወጡ በመግለጽ ራሳቸውን ለማግለል ሞከሩ። ደርግ
ግን በምትካቸው ሌላ ሰው እስኪገኝ ድረስ በሸንጎው እንዲቀመጡ አስገደዳቸው። ነገር ግን ምንም
ተተኪ ስላልተቀመጠ፣ ሐዲስ የሸንጎው አባል ሆነው ለሁለት ዓመት መቆየት ግድ ሆነባቸው።
ከሁለት ዓመት በኋላ ግን ሸንጎው ተበተነ። ሐዲስም ዳግመኛ ወደጡረታ ተመለሱ። ከዚያን ጊዜ
ጀምረው ቋሚ ጡረተኛ ሲሆኑ የሚኖሩትም በጡረታ ድርጎአቸው እና ከመጽሐፍቶቻቸው በሚገኝ
13
ጥቋቁር አናብስት
ገቢ ነው። እንደ እርሳቸው ሀሳብ ከሆነ በመጨረሻ ያገለገሉበት ሸንጎ አንዳች ጠቃሚ ስራ
አልሰራም።
ነገር ግን ቀጣይ አመቶቻቸው ፍፁም የተለዩ ሊሆኑ ይችሉ ነበር። በ1966 ዓ.ም ሐምሌ ወይም
ነሐሴ አካባቢ፣ ሐዲስ አለማየሁ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ ተጠየቁ14። የድሮው
ስርአት የካቲት 1966ቱ ከፈረሰ በኋላ ግርማዊነታቸው ለዚህ ሐላፊነት፣እንዳልካቸው መኮንንን
መረጡ።ደርግ ግን ሐዲስ አለማየሁን ፈለገ።ሐዲስም ደርግ ከእርሳቸው ምን እንደሚፈልግና
ከደርግ ጋር ያላቸው የስራ ግንኙነት ምን እንደሚሆን ጠየቁ። እንዳልካቸው መኮንን
በመንግስታቸው ውስጥ አዲስ ሰው በሾሙ ቁጥር፣ ደርግ ይወስድና ያን ሰው ያስረዋል። ሐዲስ
ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆኑ ይህ ነገር በእርሳቸው ላይም ይደገም እንደሆን ጠየቁ―እንዲያ ከሆነ
ምንም የማከናውነው ነገር አይኖርም ብለው ቁርጥ አድርገው ተናገሩ። ደርግ በራሱ እና
በሚኒስትሮች ምክር ቤት መሀል ሆኖ እንደ አገናኝ የሚሰራ አንድ ቡድን አዋቅሮ ነበር። ሐዲስ
ደርጎች በዚህ ቡድን በኩል ትእዛዛቸውን እየላኩ በማስፈፀም ምኞታቸውን ማሳካት ነው
የሚፈልጉት የሚል እምነት ነበራቸው። ማንኛውንም ነገር ለማስፈፀም የደርግመልካም ፈቃድ
መገኘት አለበት። ደርጎች የሚመሩበት እቅድ ካላቸውና ይህ እቅድ ምን እንደሚመስል ሐዲስ
ጠየቁ፤ አክለውም እርሳቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆኑ የደርግ ስራ ምን እንደሚሆን ለማወቅ
ፈለጉ። ሁሉም “ለውጥ ያስፈልጋል” በሚለው ሀሳብ ተስማሙ።ሀዲስ ቀላልና ተግባራዊ የሚሆን
የመንግሥት ስርአት እንዲመሰረት ሀሳብ አቀረቡ።ነገር ግን ምንም ዐይነት እቅድ ስላልነበረ፣ እቅድ
እንዲዘጋጅ አሳሰቡ። ያለ እቅድ ግን የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ሹመት እንደማይቀበሉ አስታወቁ።
ደርግ እና ሌሎች የጦር ሰራዊት አባላት ወደ የጦር ሰፈራቸው ተመልሰው ህዝብ እና መንግስት
የጣሉባቸውን ሀላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ ጠየቁ። አለበለዚያ ማንኛውም ዐይነት መንግሥት
ስራውን በአግባቡ ሊወጣና ውጤታማ ሊሆን እንደማይችል አውቀዋል፤ ተናግረዋልም። ሌላው
ደግሞ በመንግሥት ስራ ላይ ልምድ ያላቸው ሰዎች/ግለሰቦች ሁሉ እስር ላይ መሆናቸውን
ተቃውመው የመንግሥትን ስራ በአግባቡ ለመከወን የስራ ልምዳቸው እንደሚያስፈልግ ጠቆሙ፤
ከነሱ መሐል ወንጀል የፈፀሙ በአግባቡ ለፍርድ እንዲቀርቡ ተደርጎ ሌሎቹ ነፃ መውጣት
እንዳለባቸው ሀሳብ አቀረቡ።
14
ጥቋቁር አናብስት
****
በ1958 ዓመት የታተመው የመጀመሪያ ትልቁ ልብወለዳቸውን ፍቅር እስከ መቃብርን መፃፍ
የጀመሩት በግምት ከ20 ዓመት በፊት በዋሺንግተን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዋና ፀሐፊ እያሉ
(ከ1939–1943) ነበር። መጀመሪያ የፃፉት በእንግሊዝኛ ሲሆን ተጽፎ ሳያልቅኒውዮርክ ለሚገኝ
አሳታሚ ልከውት ለማሳተም ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። ከዚያ በአማርኛ ይጽፉ ጀመር። የተፃፈው
በረዥም ጊዜ ሂደት ሲሆን በየመሀሉ ለረዥም ጊዜ ተቋርጧል። በእንግሊዝ አምባሳደር ሳሉ
(1953–1958) ሚስታቸው ከሞቱ በኋላ መፃፉን እርግፍ አድርገው ተዉት፤ከአንድ ዓመት
የሐዘን እረፍት በኋላ መፃፉን እንደገና ቀጠሉ። ከስራ ወደስራ በተዛወሩ ቁጥር ሌሎችም ረዣዥም
መቆራረጦች ነበሩ። ሲጨርሱት ግን ጥሩ መጽሐፍ መስሎ አልታያቸውም።ብዙ ጊዜ እያቋረጡ
ስለጻፉት ያልተስተካከለ ሆኖ ተሰማቸው።
15
ጥቋቁር አናብስት
ያለምንም ማቋረጥ ሲጽፉ፣ ፍሰቱ ጥሩ እንደሚሆን፣ ነገር ግን የሚያቋርጣቸው ነገር ሲኖር እንደገና
ካቆሙበት ለመቀጠል ሀሳባቸው ስለሚበታተን፣ ፍሰቱን እንደነበር ለመቀጠል እንደሚያዳግታቸው
ያስረዳሉ። ስለዚህ መጽሐፉ በአስቸጋሪ ወራቶች የታጀቡ ብዙ ቅጥልጥል ደስተኛ የድርሰት ወቅቶች
ውጤት ነው።ይህ አለመመጣጠን ባለቀው መጽሐፍ ላይ በጉልህ ይታያል ባይ ናቸው። ነገር ግን
መጽሀፉን ጽፎ ለመጨረስ ብዙ ጥረት ስለጠየቀ፣ መጽሐፉን ለማሳተም መሞከር ትክክለኛ ውሳኔ
ሆኖ ታያቸው። መጽሀፉን ለማሳተም ገንዘብ መበደር ነበረባቸውና፤17ታትሞ እንደወጣ በጥሩ
ሁኔታ በመሸጡ ተደስተውም ተገርመውም ነበር። በመጀመሪያ ህትመት 5,000 ቅጂዎች ብቻ ነበር
የታተሙት። በሚቀጥለው ጊዜ 7,000 ቅጂዎች ታተሙ። እስከ 1978 ዓ.ም ድረስ ባለው ጊዜ
ስድስት ጊዜ ተደጋግሞ ታትሟል። መጽሐፉ በሕዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ሲያገኝ፣ ከታተመ
ከጥቂት ዓመታት በኋላም በኢትዮጵያ የትምህርት ስርአት ውስጥ ገብቶ ለሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች
የማስተማሪያ መጽሐፍ ሆነ።
በፍቅር እስከ መቃብር ውስጥ ብዙ ክፍሎች ከደራሲው ሕይወት የተቀዱ ናቸው። በጎጃም
ደብረወርቅ እና ዲማ ያሉት ታሪኮች ደራሲው በቅኔ ተማሪነታቸው ያሳለፉት ሕይወት ግልባጭ
ነው። በዛብህ ወደ አዲስ አበባ ሲመጣና በከተማው ውስጥ የሚያጋጥሙት ሁነቶች፣ሐዲስ
እራሳቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በ1918 ዓ.ምከጎጃም ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ የታዘቡት ገጠመኝ
ጥርቅም ነው። በአጠቃላይ ሀዲስ ልብወለዱ ውስጥ በሚገኙ ሁለት ገፀ ባህሪያት ውስጥ
እራሳቸውን በተወሰነ መልኩ እንደሚያዩ ይናገራሉ።የመጀመሪያው ወደ አዲስ አበባ ከመምጣቱ
በፊት የቤተክርስቲያን ትምህርት የቀመሰው እና እንደ ሐዲስ ለቤተሰቡ ብቸኛ ልጅ የሆነው
የልብወለዱ ዋና ገፀ ባህሪ በዛብህ ሲሆን፣ሌላው ደግሞ በማህበረሰቡ ሳይሆን በራሱ ሀሳብ
የሚመራው፣ ይኼም ዘወትር ከራሱ ወገኖች እና ከመደብ ፍላጎቶቹ ጋር ቅራኔ ውስጥ የሚያስገባው
´ጠቢቡ ሞኝ´፣ ጉዱ ካሳ ነበር።
16
ጥቋቁር አናብስት
***
ፍቅር እስከ መቃብር ከመታተሙ ከ10 ዓመት በፊት፣ ሐዲስ ሌሎች ሁለት መጽሀፍትን ለገበያ
አቅርበው ነበር። አንደኛው በተረት መልክ የቀረቡ 12 ታሪኮችን የያዘ ሲሆን የታተመው በ1948
ዓ.ም ነው። ከነዚህ ተረቶች መሐል አንዱ ብቻ በከፊል ነባር ሲሆን ሌሎቹ የራሳቸው ፈጠራ
ናቸው።መጽሐፉ ተረት ተረት የመሰረት18 ይሰኛል።ይህም በኢትዮጵያ ባሕልተረት መንገር
ሲጀመር እንደ መግቢያ የሚያገለግል ነው።በዚያው ዓመት ሀዲስ በኢትዮጵያ የትምህርትና
የትምህርት ቤቶች ስርዓት እንዴት መደራጀት አለበት በሚለው ላይ ያላቸውን አስተሳሰብ
“የትምህርትና የትምህርት ቤት ትርጉም” በሚል ርእስ ባሳተሙት መጽሐፍ ውስጥ ገልጸዋል።
ሐዲስ በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት “ኢዝም” የሚባል ነገር አይጠቅምም ይላሉ። እድገት ለማምጣት
የሚያስፈልገው እንደ ጤና፣ ትምህርት፣ትራንስፖርት፣ ኢንደስትሪ፣ መገናኛ እና በመሳሰሉት ዘርፎች
ተጨባጭ ስራ መስራት ነው። እያንዳንዱ "ኢዝም" ከእድገት አኳያ ምን ማለት እንደሆነ ይጠይቁና
“ኢዝም” በማደግ ላይ ያሉ ሐገራት ሊተገብሩት የማይቻላቸው ቅንጦት እንደሆነ ይቆጥሩታል፤
ወደእዛ ለመሸጋገር ሀገራት ቢያንስ መሰረታዊ የሆነ እድገት ማምጣት አለባቸው። ምን ዐይነት
አላማ እንደሚያሻና ያንን አላማ ለማሳካት የሚነደፈው እቅድ―ለምሳሌ የአስር ዓመት የግብርና፣
የኢንዱስትሪ፣ የትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ መገናኛ እቅድ―ምን መምሰል እንዳለበት ያስቀምጣሉ።
ለ“ኢዝም” እና ለሌሎች የማይጨበጡ ሃሳቦች ዋጋ አይሰጡም። ማንኛውም ዐይነት መንግስት
ህዝቡን ወደተሻለ ደረጃ ከፍ ለማድረግ ተጨባጭ የሆኑ እቅዶች ያስፈልጉታል። ህዝቡ ወደ አንድ
ዐይነት የእድገት ደረጃ ከደረሰ በኋላ፣ከተለያዩ የ”ኢዝም” ዐይነቶች የፈለገውን እንዲመርጥ ምርጫ
ከተሰጠው በኋላ ሕገመንግሥት ቀርቦ ህዝቡ በሪፈረንደም ሊወሰን ይችላል። ሐዲስ ይህንን ሀሳብ
ስለ አስተዳደር ወይም መንግስት በፃፉት መጽሀፍ አቅርበዋል ፤ እስካሁን ድረስ (በቃለመጠይቁ
ወቅት) በመጽሀፉ መልእክት ያምናሉ። ይሁን እንጂ ከአብዮቱ በኋላ አዳዲስ ሀሳቦች
በመምጣታቸው መጽሐፉ ወደጎን እንደተገፋ ይናገራሉ።19
***
18
ጥቋቁር አናብስት
ዳኛ" አይደግምም። የ"ወንጀለኛው ዳኛ" መቼት ከኢጣሊያ ወረራ በኋላ ይጀምርና አብዮቱ
ከመፈንዳቱ በፊት ይጠናቀቃል።
***
19
ጥቋቁር አናብስት
ሐዲስ አለማየሁ ከ"የልምዣት" በኋላ ትልቅ የሚባል የሥነ ጽሑፍ ስራ የሚሰሩ አልመሰላቸውም፤
ሆኖም ትውስታቸውን በተለይ ስለ ጦርነቱና ስለተዋጉበት ግንባር ትዝታቸውን መፃፍ እንደሚፈልጉ
ይናገራሉ። ግለታሪካቸውን እንዲጽፉ ቢጠየቁም መጻፍ አለመጻፋቸውን እርግጠኛ አይደሉም።
የመጨረሻ የፈጠራ ስራቸው ተለጥጦ የተዘጋጀው "ተረት ተረት የመሰረት" ሊሆን ይችላል።
በ1977 ኩራዝ አሳታሚ ለሁለተኛው እትም ተጨማሪ ታሪኮችን እንዲያዘጋጁ ስለጠየቃቸው ያንኑ
በመስራት ላይ ነበሩ። አንድ ታሪክ ጨርሰው ሌሎች ሁለት ታሪኮችን ደግሞ አጽመ-ታሪካቸውን
አዘጋጅተዋል። በአጠቃላይ ለዚህ እትም አምስት አዳዲስ ታሪኮች ለማዘጋጀት አስበዋል።ሐዲስ
በልቦለዶቻቸው በከፊል እንጂ ሙሉ በሙሉ እንዳልረኩ ይናገራሉ። መንፈሳቸው ሲነቃቃ መፃፍ
ያስደስታቸዋል፤ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜየተበጣጠሱ ታሪኮችን ገጣጥሞ ማቀናጀቱ፣ የተፃፈው
ታሪክ ስህተቶች ካሉት ያንን ለመንቀስ ደጋግሞ ማንበቡ እና የመሳሰሉት ከባድና አሰልቺ ስራ
ናቸው።ይሁን እንጂ ሐዲስ የሰዎችን አስተያየት ተንተርሶ እርማት ማድረግን አይወዱም፤
ምክንያቱም ከሰዎች ማሻሻያ ከተቀበሉ ሙሉ በሙሉ የራሳቸው ስራ መሆኑ ቀርቶ በከፊል የሌላ
ሰው ስራም ጭምር ይሆናል የሚል እምነት ነበራቸው።የመጽሐፍቶቻቸው ህትመት፣ ለምሳሌ
የየልምዣት ህትመት፣ ከሌሎች የሚቀበሉትን ማሻሻያ ማካተት የሚኖርበት ቢሆን ኖሮ ረቂቁን
ቁምሳጥናቸው ውስጥ ቆልፈውበት ሳይታተም ቢቀር ይመርጡ ነበር።20
***
ምንም እንኳን ከበደን በአካል ያወቋቸው ከጣሊያን ከተመለሱ በኋላ ቢሆንም፣ ጣሊያን፣ ፖንዛ
ውስጥ እያሉ ግጥሞቻቸውን በጋዜጣ ላይ እያነበቡ ይደነቁ ነበር። ገና ተማሪ እያሉ የብላቴንጌታ
ሕሩይን መጽሀፍ ያነበቡ፣ በአካልም አንድ ሁለት ጊዜ ያገኟቸው ቢሆንም፣ ኅሩይ ጥልቅ ተጽእኖ
ያሳደሩባቸው ግን አይመስልም።
20
ጥቋቁር አናብስት
****
ሌላው ደግሞ ከ1933–1966 ባለው ጊዜ በመላው ሀገሩ ሰላም በመስፈኑ ለኢትዮጵያ እድገት
ረድቷል። ከዚህ ውጪ ባለው ዘመን፣ ኢትዮጵያ ከጦርነት ተላቅቃ ስለማታውቅ ሰዎች የሚኖሩት
ድንኳን ውስጥ ወይም ወዲያውኑ ሊፈርሱ በሚችሉ ጊዜያዊ መጠለያ ውስጥ ነበር። ለዚህ ነው
ኢትዮጵያውያን ከተማን በስርአት መገንባት ሳይችሉ ቀርተው በዘፈቀደ ያለ እቅድ የሚሰሩት።
ሐዲስ የድሮውንም አዲሱንም አይተውት ከ1933 ወዲህ የመጣው ለውጥ ትልቅ መሆኑን
21
ጥቋቁር አናብስት
ይመሰክራሉ። ምንም እንኳን ስህተቶች ቢሰሩም፣ እንከኖች ባይጠፉም፣ ከአብዮቱ በፊት ኢትዮጵያ
በእድገት ጎዳና እየተንደረደረች ነበር።
የኃይለሥላሴ ትልቁ ችግር ገንዘብና ስልጣን አለመጠን መውደዳቸው ነበር። (“እንደ ኃይለሥላሴ
ገንዘብ የሚወድ ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም”)፤ሌላ ሰው ሲሳካለት ወይም ክብር ሲያገኝ ማየት
አይወዱም።“የትኛውም ኢትዮጵያዊ ዶክተር እንኳ ውጤታማ ሲሆን ማየትአይፈልጉም”።ደህና
አድርጎ የሚሰራውን ሁሉ ወይ ያባርሩታል አልያም ያዛውሩታል። ስለ ሁሉም ነገር ማወቅና
መቆጣጠር ስለሚፈልጉ ነገሮች እንዲዘገዩ ያደርጉ ነበር። ሲያረጁ ሁሉንም ልጓሞች መጨበጥ
ስላልቻሉ፣ ነገሮች ከቁጥጥራቸው ውጪ ሆኑ። ሐዲስ ከኃይለሥላሴ ጋር ጠንካራ ቅራኔ የነበራቸው
ቢሆንም፣ ለሀገሪቱ ያመጡትን እድገትና መሻሻል አይክዱም። ሐዲስ ኃይለሥላሴ አንዳንድ
እምነቶቻቸውን እና አመለካከቶቻቸውን፣ በተለይ የመጨረሻዎቹ ዓመታት ላይ ቢለውጡ ኖሮ ፤
በዛ ላይ በህዝብ ዘንድ ያላቸውን ክብር ቢጠቀሙት ኖሮ ለሳቸውም ለሀገራቸውም በረከት በሆነ
ነበር ብለው ያምናሉ። ነገር ግን እሳቸውም አልተለወጡም ፤ ለሀገሪቱም አልበጀም። ይሁን እንጂ
ሀዲስ በኃይለሥላሴ ጊዜ የመጣውን ትልቅ እድገት መካድና፣ ሀገሪቱ የደረሰባትን ክፉ ነገር ሁሉ
እሳቸው ላይ ማላከክ ተገቢ ሆኖ አይታያቸውም።ሐዲስ የመንግሥት ባለሥልጣን ሆነው
አገራቸውን ያገለገሉት በኃይለሥላሴ ዘመን ሲሆን ረዥም ሕይወታቸውን ወደ ኋላ ዞር ብለው
ለሀገራቸውና ለሕዝባቸው ማድረግ የቻሉትን ነገር ሲመለከቱት፣ በደስተኝነትናበምስጋናስሜት
ነው።
ማስታወሻዎች
5) የኅሩይ ተውኔት ግብረገብን በሚያስተምሩ ንግግሮች የተሞላና ድርጊት አልባ ሲሆን ለመድረክ
የሚመች አይደለም። ለተመልካች በቀጥታ ቀርቦ የሚያውቅ አይመስልም።
6) ዮፍታሔ እና መላኩ ሁለቱም የዳግማዊ ምኒልክ መምህራንና ቀሳውስት ወይም ደባትር ነበሩ ፤
ሁለቱም የመጡት ከጎጃም፣ ኤልያስ ነው። ኤልያስ የሐዲስ አባት የትውልድ ስፍራ ሲሆን
በተጨማሪም ሐዲስ የቅኔ ትምህርታቸውን የጀመሩት እዚህ ነው።
11) የእምሩ እና የግርማቸው አባቶች የቅርብ ጓደኞች ስለሆኑ ግርማቸው ከእምሩ ጋር አብሯቸው
እንዲሆን ሲጠየቅ ተስማማ። ነገር ግን ጣሊያንን የሚወጉ ሃይሎች ሞሮኮ ሲደርሱ፣ እምሩ እና
ግርማቸው ከሌሎቹ ጋር ሉንጎ ቡኮ ውስጥ ተቀመጡ።
23
ጥቋቁር አናብስት
13) የተባበሩት መንግስታቱ ንዑስ ጉባዔ አሁን ህልውናው አክትሟል። ይህ ንዑስ ጉባዔ እንደ
ጠቅላላ ጉባዔው ሁሉንም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አባላትን ይዟል። የሚሰበሰበውም
ጠቅላላ ጉባዔው በሚያርፍበት ጊዜ ነበር። በመሆኑም በጠቅላላ ጉባኤው ተከታታይ ስብሰባዎች
መሀል ያለውን ክፍተት ይሞላል።
14) ለዚህኛው የሕይወታቸው ክፍል የተለየ ግምት ይሰጡ እንደሆነ አላውቅም። ምክንያቱም
የሕይወት ታሪካቸውን እርሳቸው በሚፈልት መንገድ ከተረኩልኝ በኋላ እኔ እራሴ ነጥዬ ስለዛ
ወቅት እስከምጠይቃቸው ድረስ ምንም አልነገሩኝም ነበር።
24
ጥቋቁር አናብስት
20) መጽሐፉ በመጽሐፍት መደብሮች በ1980 ታየ። ከመውጣቱ በፊት በኢሠፓ ማእከላዊ
ኮሚቴ በጥንቃቄ ምርመራ ተደርጎበት በርዕዮተ አለም ጠበብቶች ተገምግሟል።በ1979 መጨረሻ
አካባቢ ታተመ ፤ ኩራዝ ለህትመት እንደሚያልፍ እርግጠኛ ስ ለነበር 50,000 ቅጂዎች
እንዲታተሙ አዘዘ ። በኢትዮጵያ ውስጥ አንድ መጽሐፍ ለመጀመሪያ ህትመቱ በዚህን ያህል
ቅጂዎች ሲዘጋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን ይህ ሁሉ ቅጂ በጥቂት ወራቶች ውስጥ ተሽጦ አለቀ (
አንዶንዶች በኦሮማይ ጊዜ የደረሰውን በማሰብ ሁለት እና ከዚያ በላይ ቅጂዎችን ገዝተዋል)
ወዲያውኑ ለድጋሚ ህትመት ገብቶ አሁንም 50,000 ቅጂዎች ታትሟል።
25
ጥቋቁር አናብስት
ኅሩይ ወልደሥላሴ
የአማርኛ ስነጽሁፍ አባትየአማርኛ ስነ-ጽሁፍ ቅርጽ በሚይዝበትወቅት
የኅሩይ ወልደሥላሴ ሚና በጣም ከፍ ያለመሆኑ ስለታወቀላቸው ከዚህ
ቀደም ብዙ ሰዎችስለ እሳቸው ጽፈዋል::ከኅሩይ የልጅ ልጆች አንዱ
ግርማሥላሴ አስፋው1ለተወሰኑ አመታት ግለታሪካቸውን ለመጻፍ ተነሳስቶ
የነበረ ቢሆንም በቅጡ ስራውን ሳይጀምረው እ.ኤ.አ በመስከረም 1987
በአስመራ ከተማ አቅራቢያ የአውሮፕላን አደጋ ቀደመው፡፡ በ1970ዎቹ ግርማ ኅሩይ የጻፉትን
የግል ማስታወሻዎች ላይ ምንባቦችንና ማጠቃለያዎችን አሳይቶኝ ነበር፡፡እስካሁን ድረስ ስለ ኅሩይ
ህይወት ስለእሳቸው ማወቅ በሚፈልው ህዝብ ዘንድ ብዙ ያልተሰሙ ነገሮች እንዳሉ ግልጽ ነው፡፡
ስለኅሩይ ብዙ ጭምጭምታዎችን የሰማሁ ቢሆንም የተሻለ የተጨባጭ መረጃ እጥረት ግን አለ፡፡2
***
በወቅቱ ማንበብ፤በቃል ማነብነብና መድገም እንጂ መጻፍ ብዙም ትኩረት አይሰጠውም ነበር፡፡
የቤተክህነት ምሁር መለኪያም አልነበረም፡፡ቢሆንም ኅሩይ ከረቂቆች ላይ ደብዳቤዎችን በመገልበጥ
እራሳቸውን ጽህፈት ማስተማር ችለዋል፡፡ቀለም ከእንጀራ ምጣድ ጥላሸት ያዘጋጁ ነበር፡፡ብእርም
ከሸምበቆ ይቀርጻሉ፤መጻፍያም ከበሬ ቆዳ በለፋ ብራና፡፡13
27
ጥቋቁር አናብስት
አባትና ልጅ በዚህ ወቅት በስሬ መድሃኒዓለም በችግር ነበር የቆዩት፡፡በኋላ ግን የስሬ መድሃኒዓለም
አለቃ የነበሩት ወይዘሮ ጸሃይ ወርቅ ዳርጌ 14ትንሽም ብትሆን የማትቆራረጥ የምግብ እርዳታና
አመታዊ ተቆራጭ አደረጉላቸው፡፡
እንዲህ ባለ ሁኔታ ለሁለት አመታት ከዘለቁ በኋላ ወልደሥላሴ በ53 አመታቸው ደብረ ሊባኖስ
ገዳም ገብተው መንኩሰው ወደ ልጃቸው ተመለሱ፡፡ሚስትየው(የኅሩይ ወይም የገብረመስቀል
እናት) ልጃቸው ስለናፈቃቸው እሚማሩበት ድረስ ሄደው ለአንድ ወር ቆይተው ጎበኟቸው፡፡
የአባታቸው ጤንነት ግን በዚህ ወቅት እየተዳከመ መጥቶ ነበር፡፡ወደ ደብረ ሊባኖስም በተደጋጋሚ
ለጠበል ተመላለሱ፡፡ነገር ግን ሳይሻላቸው ቀርቶ ገብረመስቀል(ኅሩይ) የ13 አመት ታዳጊ ሳሉ
አባታቸው ሞተው በደብረ ሊባኖስ ተቀበሩ፡፡አንድ ወቅት ኅሩይ(በወቅቱና ከዛ በኋላ ለረዥም ጊዜ
በዚሁ ስም ይጠሩ ነበር)የአባታቸውን መቃብር ለመጎብኘት ሄደዋል፡፡በዚያ ወቅትም የገዳሙ
አስተዳደር የነገሯቸው የአባታቸው የመጨረሻ ቃላትና ምክር እንዲህ የምትል ነበረች “ገብረ
መሰቀል የሚወርሰው ነገር የለም፡፡ወደ ቤቱ የሚመለስበት ጉዳይም የለም እዚያው ትምህርቱን ግን
ሳያቋርጥ መቀጠል ነው ያለበት፡፡“
በኢትዮጵያ በ1881 አ.ም ብዙ ከብት ካለቀ በኋላ15በሃገሩ ላይ ርሃብ ጸንቶ ስለነበር ወይዘሮ ጸሃይ
ወርቅ ለገብረ መስቀል ቀለብ መስፈር ስላቆሙ እራሳቸውን መቻል ነበረባቸው፡፡ድቁናቸውን
ለመቀበል በሚማሩበት ወቅት አንድ ገበሬ የየ በተባለ ስፍራ የቤተክህነትን መሬት ያርስ ስለነበር
እሱን እያገዙ እንዲቆዩ ሆነ፡፡በሂደት ጥሩ ለመኖር ቻሉ፡፡ለእራሳቸውም ትንሽ መሬት ማረስ ችለው
ነበር፡፡ምንም እንኳን ጥሩ ጋላቢ ባይሆኑም ገቢያቸው ከፍ ስላለ ፈረስ እስከመግዛት ደረሱ፡፡በክፍያ
ለሰዎች እየጸፉም ትርፋማ ሆኑ፡፡ዝናቸው እየናኘ ስለመጣ የሰላሌው ገዢ ደጃች በሻህ ጸሃፊ
ባስፈለጋቸው ወቅት ገብረ መስቀል መጻፍ እንደሚችሉ ስላወቁ ቀጠሯቸው16፡፡ከበሻህ ጋር ግን
ብዙም አልቆዩም፡፡ወድያውኑ ለራስ 17መኮንን ታማኝ ሎሌዎች ከነበሩት ለአንዱ ቀኛዝማች
መቅረጭ ሲሞ የሚባል አካባቢ አዳአ በርጋ ላይ ተቀጠሩ፡፡የተቀጠሩት በጽሁፍ ችሎታቸው ስላሆነ
ከጊዜ በኋላ ችሎታቸውን ያወቁት ቀጣሪያቸው ቀርበው ችሎታቸውን እንዲያስመሰክሩ ጠየቋቸው
28
ጥቋቁር አናብስት
ኅሩይ ከደጃች መቅረጭ ጋር ደህና በቆዩበት ወቅት ነገሮች በኢጣልያና በኢትዮጵያ መሃል እየሻከሩ
ነበር፡፡በሰኔ 1887 ዓ.ም ዳግማዊ ሚኒልክ ለአድዋ ጦርነት እንዲከተት “ታቦታችሁን ይዛችሁ
ስንቃችሁን ሰንቃችሁ እንድትመጡ ይሁን ”ሲሉ አዋጅ አስነገሩ፡፡ ወታደሩንና መሪውን የጎሳ
ግጭታችሁን ትታችሁ እንደ ኢትዮጵያዊነታችሁ ሁኑ ሲሉ መከሩ፡፡ቀኛዝማች መቅረጭ ዘመቻውን
በመስከረም 1888 ዓ.ም ተቀላቀሉ፡፡ኅሩይም በልማዱ መሰረት ከሜታ በቾ አቅራቢያ እስከ
አዋሽ ወንዝ ድረስ ተከትለዋቸው ወደ አሳዳሪያቸው ቤት ተመለሱ፡፡ኅሩይ ወድያውኑ ከአዲስ
አበባ እንጦጦ ቅዱስ ራጉኤል ቤተክርስትያን ከመጡት አራት ደባትር ጋር በመሆን እንጦጦ
ራጉኤል ቤተክርስትያንን ማገልገል ጀመሩ፡፡ከነሱ መሃልም አለቃ (መምህር) ወልደግዮርጊስ እና
አቶ ማህደር ይገኙበታል፡፡20ኅሩይ ቅዳሴን በሚያቆሙበት መንገድ ተመስጠው ስለነበር ቅዳሴው
ካለቀ በኋላ አቶ ማህደርን ቀርበው ትምህርታቸውን እነሱ ዘንድ መቀጠል ይችሉ እንደሆን ጠየቁ፡፡
ጥያቄው በአራቱም ተቀባይነት ስላገኘ ኅሩይም ለአሳዳሪያቸው ቤተሰብ የት እንደሚሄዱና
መሄዳቸውንም21 ጭምር ሳይናገሩ ቤቱን ለቀው ወጡ፡፡ወደ አዲስ አበባ በእግር እየመጡ ሳለ
ከሰዎቹ ጋር ይበልጥ ተቀራረቡ፡፡
'የሆነው ፍሬ' ለምን እንደተባሉም ጠየቋቸው፡፡እሳቸውም ለምን እንደዛ እነደተባሉ ሲናገሩ አለቃ
ወልደግዮርጊስ ጎንደር ሳሉ ኅሩይ (የተመረጠው) ተብለው ይጠሩ እንደነበርና የሆነው ፍሬም
ይህንን ስም መውሰድ እንደሚገባቸው ተናገሩ፡፡'የሆነው ፍሬ' የተባለው ስማቸው ግን ኅሩይ
በህይወታቸው የላቀ ስኬት እስከተቀዳጁበት ወቅት ድረስ ለመጠርያነት ይውል ነበር፡፡
በኩራዝ ማጥናት ቀጠሉ፡፡በወቅቱ ዳግማዊ ሚኒሊክ ትንሽ ዳረጎት ለቀሳውስቱ ቤት መስርያ ችረው
ነበር፡፡ገንዘቡ እንደ ቤቱ መጠን በመከፋፈሉ ኅሩይ የደረሳቸው እስከ 15 ብር ድረስ ያነሰ እንደነበር
አንዳንዶች በግምት ይናገራሉ፡፡23ኅሩይ በሆድ ህመም ይሰቃዩ ስለነበር ወደ ደብረ ሊባኖስ ለጠበል
ይመላለሳሉ፡፡24
የአጼ ሚኒሊክ የግል ጸሃፊ ጸሃፌትእዛዝ ገብረ ሥላሴ25የእንጦጦ ራጉኤል አለቃም ስለነበሩ
ከጊዜጊዜ ብቅ እያሉ ነገሮችን ይቃኙ ነበር፡፡በመስከረም 1989 አ.ም የቅዱስ ራጉኤል ቀን የኅሩይን
ለመልአኩ የተቀኘ ቅኔ መወድስ ሰምተው በጣም ተደሰቱ፡፡ከድግሱም በኋላ ኅሩይ አዲስ አበባ
እንዲመጡና እንዲያዩዋቸው ነገሯቸው፡፡ጃኖ ሸልመው ፡ቁና እህል (5ኪሎ)እንዲሰፈርላቸው
አምስት ብር ወርሃዊ የመንግስት ደሞዝም26 እንዲቆረጥላቸው አዘው ከሳቸው ጋር ለመኳንንቱ
በሚሾመው መሶበ ወርቅ ቅዱስ ራጉኤልን በጎበኙበት ወቅት ሁሉ አብረዋቸው እንዲቆርሱ ፈቀዱ፡
፡ወደ ቤተመንግስትም ለጉብኝት በፈቀዱበት ወቅት ሁሉ እንዲመጡ ታዘዘላቸው፡፡ይህ ታላቅ
ክብር ነበር፡፡
ለሁለት አመታት ኅሩይ የአዲስ ኪዳን 27 መጻህፍት አንደምታ ሲያጠኑ ቆዩ፡፡ይህም የመጻህፍቱን
ሀይለቃላትን ሆነ ትርጓሜ በልቦና ማጥናትን ይጠቀልላል፡፡27ይህንን ትምህርት ሲያጠናቅቁ
እሳቸውና ሌሎች አራት ሰዎች ከአጤ ሚኒሊክ ካባ በሽልማት ተበረከተላቸው፡፡ ኅሩይ በመምህር
ወልደ ግዮርጊስና በሌሎች ስር በአጠቃላይ ለ12 አመታት ተምረዋል፡፡የብሉይን አንደምታ
ቢሞክሩም ያን ያህል አልተራቀቁበትም፡፡ቆይቶ ፍትሐ ነገስቱን አጠኑ ወደ ቤተመንግስቱም
እግራቸውን ማዘውተር ቀጠሉ፡፡በዛም ሆነ ሌላ ቦታም ላይ ከተለያዩ ጠቃሚ ሰዎች ጋር መተዋወቅ
ጀመሩ፡፡በኢትዮጵያ እንጀራ መጋገርያው ብቸኛ መንገድ ጠቃሚ ሰዎችን ማወቅ ነውና፡፡
አንድ ወቅት በገብረ ሥላሴ ቢሮ ሳሉ ኅሩይ የእንጦጦ ማርያም ቤተክርስትያን አለቃን መልክዐፀሃይ
አፈወርቅን አገኙ፡፡
30
ጥቋቁር አናብስት
***
****
ካገቡና ስኬታማ መሆን ከጀመሩ በኋላ ብዙ ሰዎች እርዳታቸውን በመሻት መምጣት ጀመሩ፡፡
እሳቸው ደግሞ ሁሌም ለጋስ ነበሩ፡ይሄ ደግሞ ለእሳቸውና ለቤተሰቡ ችግርን አመጣ፡፡ሚስታቸው
ጠንካራ ሰራተኛ ነበረች፡፡ወደ መስክ በመውጣት ለማገዶነት የሚውል ኩበት ስትለቅም ውላ
መለስ ብላ ቀኑን ሙሉ በቤት ስራ ተጠምዳ ትውል ነበር፡፡
1881 ዓ.ም ኢትዮጵያ ውስጥ ድርቅ ገብቶ ብዙ ከብት አለቀ፡፡ፈረንሳይ ሶስት የእንስሳት ሃኪሞችን
ላከች፡፡ጉለሌ አካባቢ ያለው የቀድሞ የንጉስ ተክለሃይማኖት ቤት ለስራቸው ተለቀቀላቸው፡፡
በከንቲባ (በኋላም ቢትወደድ )ወልደ ጻዲቅ ስር ሆነው በእርሻ ሚንስቴር መስራት ጀመሩ፡፡ከንቲባ
ወልደጻዲቅ ትሰሜ ዳርጌን ያገቡ ሲሆን ፈረንሳዮቹ ወደ ሃገራቸው የመሄጃ ጊዜያቸው ሲደርስ
እነሱን የመተካት እቅድ ነበራቸው፡፡ስለዚህ በፈረንሳዮቹ የሚሰለጥን ተማሪ ያስፈልጋል፡፡ሚኒልክ
የፈረንሳዮቹ መሄጃ ሲቃረብ ለወልደ ጻዲቅ ስራውን አስቀጥሎ ምትክ የሚሆን ሰው እንዲፈልጉ
ነገሯቸው፡፡እሳቸውም ኅሩይን ጠቆሙ፡፡ይሄ አደራ ሲጣልባቸው ከአጤ ሚኒሊክ ጋር በስራው
መክንያት በተደጋጋሚ የመገናኘት እድል ገጥሟቸው ነበር፡፡ኅሩይ የአንድ ደብር አለቃ እንጂ የከብት
ሃኪም መሆን አይፈልጉም፡፡ነገር ግን ስራውን ሊሰሩ ተስማሙ፡፡እንደ ጸኃፊ በሚሰሩበት ወቅት 10
ብር የሚከፈላቸው ሲሆን በየቀኑ ባዶ እግራቸውን ከስራ ቦታቸው እንጦጦ እስከ ጉለሌ ድረስ
ይሄዱ ነበር፡፡ሲቆይ ግን ይሄ አድካሚ እየሆነ መጣ፡፡ከሶስተኛው ልጃቸው መወለድ በኋላ
መድሃኔአለም ትምህርት ቤት አካባቢ አንዲት በሳር ወደ ተሰራች ቤት ተዛወሩ፡፡በወቅቱ ሰላሳ አንድ
አመት ከ4 ወራቸው ነበር፡፡ብላታ ሲራክ ሁለተኛው ልጃቸው በ1903 የተወለደው እዚህ ነበር፡፡
32
ጥቋቁር አናብስት
አንዳንድ የእድሜ ባለጸጎች ከዚህ ቤት የሚያስታውሱት ነገር ቢኖር ከበሩ ትይዩ በግልጽ በሚታይ
ሁኔታ በተቀመጠች ወንበር ላይ የሚቀመጥ ጠርሙስ ሙሉ ውሃና ብርጭቆ ነበር፡፡
በአንድ ወቅት የእንስሳት ህክምና ሆስፒታል ውስጥ በሚሰሩበት ወቅት በአቡነ ማቴዎስና40 በአፈ
ንጉስ እስጢፋኖስ41 መሃል በነበረ የተጭበረበረ ደብዳቤ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው
ተወንጅለው ታስረው በእግረ ሙቅ ገብተው ስስ ፍራሽ ላይ ለአንድ ወር ተኝተው አሳልፈዋል፡፡
በኋላ ነገሩ ጠራ እሳቸውም ተለቀው ወደስራቸው ተመለሱ፡፡
***
ኅሩይ ትንሽ እንግሊዘኛ እንደቻሉ ወደ አውሮጳ ስለመሄድ ማለም ጀመሩ ፡፡ከአደዋ ጦርነት በፊት
ኢትዮጵያውያን ከግብጽና እየሩሳሌም ውጪ ስለውጪው አለም የሚያውቁት ትንሽ ነበር፡፡ከጥቂት
አመታት በኋላ ግን ዶክተር ወርቅነህ እሸቴ (ወይም ዶክተር ማርቲን) አንድ የጂኦግራፊ መጽሃፍ
ከእንግሊዘኛ ወደ አማርኛ መለሱ፡፡አማርኛቸው ብዙም ስለማያወላዳ በትርጉሙ ወቅት ኅሩይና
ሌላ አንድ ሰው አግዘዋቸዋል፡፡እዚህ መጽሐፍ ላይ መስራታቸው የውጪውን አለም የሚያዩበት
አይናቸውን ከፈተላቸው፡፡መጽሐፉ በ1904 ተዘጋጅቶ ያለቀ ቢሆንም በገንዘብና ሌሎች ችግሮች
ምክንያት(በአንደኛ የአለም ጦርነትም) ሳይታተም ለብዙ አመታት ቆየ፡፡ የኅሩይን መሄድ ፍላጎት
ግን ቀሰቀሰው፡፡ወደ ውጭ የመሄድ አድል የመጣላቸው ለጆርጅ አምስተኛ የዘውድ ክብረበአል
በሰኔ 15 1903 ነበር፡፡
ልጅ(አቤቶ)እያሱ ደጃች (በኋላ ራስ) ካሳን (የወይዘሮ ትሰሜን ልጅ) ጨምረው ልኡካኑን
እንዲመክሩ ላኳቸው፡፡ኅሩይም በጸሃፊነት ተከተሉ፡፡ወደ ድሬዳዋ ባቡር ለመሳፈር ሄዱ፡፡በጊዜው
የባቡሩ መንገድ ማለቂያው እዚያ በመሆኑ ኅሩይ ወደ አውሮጳ በመሄዱ ጉዳይ በጣም ተሳክረው
ስለነበር ምንአልባት አንዳች የሚያድዳቸው ነገር እንዳይፈጠር በመስጋት እስከ ሞጆ(በግምት 75
ኪ.ሜ) ከሌሎች ተነጥለው ሔደው እዚያ ሲደርሱ ከዋናው ቡድን ጋር ተቀላቀሉ፡፡
ነጋድራስ በኋላ (ቢትወደድ)ኀይለ ግዮርጊስ የአዲስ አበባ ከንቲባ ሲሆኑ ኅሩይንና አንድ
ገብረክርስቶስ የሚባል ግለሰብን ፍትሐነገስቱን እንዲያስተረጉሙላቸው ጠየቁ፡፡ ለዚህም
እያንዳንዳቸው 200 ብር ተከፈላቸው፡፡ይህ የሆነው ኅሩይ እንጦጦ እያሉ ነበር፡፡ከዚህ በኋላ
በኀይለዮርጊስና በኅሩይ መሃል ወዳጅነት ተፈጠረ፡፡ወደኋላም ለኅሩይ ይሄ ጓደኝነት ረድቷቸዋል፡፡
ኀይለግዮርጊስ ጠቅላይ ሚንስትርነትን በአቤቶ እያሱ ተሾሙ፡፡ይሄም ለኅሩይ ጥሩ በር
ከፈተላቸው፡፡የኀይለግዮርጊስ ሚስት ስህን ሚካኤል ይባላሉ፡፡(የራስ ሚካኤል ልጅ)ኀይለ ግዮርጊስ
የከተማ መስተዳደር ቢሮ አዲስ አበባ ላይ መሰረቱ፡፡ኅሩይም ይሄን ቢሮ እንዲመሩ በ1907
ተሾሙ፡፡ሌሎች አቤቶ እያሱን ለምነው የነበር ቢሆንም ኅሩይ ግን በወር 50 ብር ሊቀጠሩ ቻሉ፡፡
ኀይለ ግዮርጊስ እና ኅሩይ አብረው መስራትና መቀራረብ ቻሉ፡፡አቤቶ እያሱም ኅሩይ ቢሮ
34
ጥቋቁር አናብስት
***
35
ጥቋቁር አናብስት
***
አዲስ አበባ ላይም የተፈሪና የኅሩይ ወዳጅነት እንደቀጠለ ነበር፡፡ኅሩይ ከተለያዩ የመንግስት መስርያ
ቤቶች ባደረጓቸው ግንኙነቶች መጨረሻ ላይም (ይህ የአልጋ ወራሽ ትእዛዝ ነው) የሚሉ ቃላት
ይገኙባቸው ነበር፡፡የኅሩይ ቢሮ ከቤታቸው ይርቃል፡፡እናም ወደ ቢሯቸው ለመሄድ የሚያደርጉትን
ጉዞ ጫና ለማካካስ ያህል በ1919 የልኡል አልጋ ወራሽ ልዩ አማካሪ ሆኑ፡፡ያም ቢሆን ግን
37
ጥቋቁር አናብስት
ብላታ ኅሩይ ልዩ አማካሪ ከሆኑ ከአንድ አመት በኋላ የብላቴን ጌታ መአረግ ተሰጥቷቸው በ1920
የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ጠቅላይ ዳይሬክተር ሆኑ፡፡ደሞዛቸው በወር 300 ብር ሲሆን ውጪ
ጉዳይ ሚንስቴሩ እራሳቸው ተፈሪ ነበሩ፡፡የኅሩይን ትጋትና ታማኝነት ካዩ በኋላ ግን ሚንስትርነቱን
ተውላቸው፡፡ስራ ሲበዛባቸው በበቅሎ ወደ ቤት ለምሳ የሚሄዱት ኅሩይም ሰአት ላለማባከን
መኪና መከራየት አስፈለጋቸው፡፡ይህም ወጪ የሚሆነው ከሚንስትሩ ነበር፡፡የተመደበለት መጠን
ግን በወር50 ብር ነበር፡፡የኅሩይ ስራና አስተዋጽኦ እውቅና ያገኘና የተመሰገነ በጽህፈት ሚንስትርም
የተመዘገበ ነበር፡፡ብዙ ክብርንም ተቀዳጅተዋል፡፡
***
ንግስት ዘውዲቱ በድንገት ታመው በመጋቢት 24 1922 አረፉ፡፡አልጋ ወራሽ ተፈሪም ቀዳማዊ
ኀይለሥላሤ ተብለው ተቀቡ፡፡የዚህ ዝግጅት ሃላፊነትም በብላታ ኅሩይ ትከሻ ላይ ወደቀ፡፡
ተጨማሪ ስራ ቢጠይቅም ኅሩይ በትጋት ሊወጡት ችለዋል፡፡ኅሩይ ከኀይለሥላሴ በዐለ ሲመት
በኋላ በውጪ ጉዳይ ዋና ዳይሬክተርነታቸው አልቆዩም፤በሚያዝያ 12 የውጪ ጉዳይ ሚንስትር
ሆነው ሲሾሙ ደሞዛቸው 1000 ብር ደረሰ መኪናም ተሰጣቸው፡፡48 ወደ ጉለሌ ቤታቸው
መዳረሻም መንገድ ተሰራ፡፡በጊዜው ለእንደዚህ አይነት ክብር የመጀመርያው ነበሩ፤49በህይወታቸው
ሙሉ አንድ ሹፌር ብቻ ሲሆን የነበራቸው እ.ኤ.አ በ1987 እንደተነገረኝ ከሆነ ይህ ሹፌራቸው
ከጥቂት አመታት በፊት ነበር ያረፈው፡፡
38
ጥቋቁር አናብስት
***
ኅሩይ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር እንደነበሩ በኢትዮጵያና በጣልያን መሃል የነበረው ግንኙነት
እየሻከረ መጣ ፡፡በውጭ ሃገር የሚገኙ ጋዜጦች ኢትዮጵያን አስመልክቶ ብዙ አሉታዊ ጽሁፎችን
ማውጣት በመጀመራቸው በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ይህንን ማስተባበል አስፈላጊ ሆነ፡፡ይህንን
የኢትዮጵያ እይታ ለማስረገጥም የአጥብያ ኮከብ የተሰኘ ጋዜጣ በ1926 ዓ. ም በጎሃ ጽዮን
ማተምያ መታተም ጀመረ፡፡ሳምንታዊ የስምንት ገጽ ጋዜጣ ሲሆን በአማርኛና በፈረንሳይኛ
የሚታተም በኅሩይ ሰብሳቢነት እና ፕሬዝዳንትነት የሚመራ የአርትኦት ቦርድ ነበረው፡፡ሰዎች
“የብላቴን ጌታ ኅሩይ ጋዜጣ ”ብለው ይጠሩት ነበር፡፡ኅሩይ ከዚህ ቀደም ብሎ የብርሃንና ሰላም
ጋዜጣን ከቤተክህነት ምሁራን ጋር በመሆን እንዲቋቋምም እርዳታ አድርገዋል፡፡ ከህዝቡ ጋር
ለመተዋወቅ ገና ድክድክ በሚልበት ወቅትም በጦርነቱ ሳብያ ተቋረጠ፡፡ለጦርነቱ ዝግጅትም
ኢትዮጵያ ከውጪ የጦር መሳርያ በብዛት በመግዛት ላይ ነበረች፡፡ኅሩይም ከደመወዛቸው አንድ
አምስተኛውን ለዚሁ ግዢ አውለው ነበር፡፡የውጪ ሃይሎች ለኢትዮጵያ ባላቸው አመለካከት
በአብዛኛው ግድየለሽና ጠብ አጫሪ ነበሩ፡፡ምንም እንኳን በርካታ መንግስታት ኢትዮጵያን በጦር
መሳርያና በወታደር ሊረዱ ቢፈልጉም የቤልጅየም መንግስት ግን ወደ ኢትዮጵያ የሚላኩትን
ጭነቶችና ሽያጮችን ለማከላከል ሞከረ፡፡በዚህም ኅሩይ የኢትዮጵያን ቅር መሰኘት ገልጸዋል፡፡
በሮም የኢትዮጵያ አምባሳደር ኢጣልያ ወደ ጦርነት አታመራም ብለው አስበው ነበር፡፡በአጠቃላይ
ኢትዮጵያ ውሱን የውጭ ድጋፍ ነበር ያገኘችው፡፡ኅሩይ በ1929 መስከረም 22 ዓ.ም በተጻፈ
ደብዳቤያቸው በአዲስ አበባ የሚገኘውን የኢጣልያንን ልዑክ ቴሌግራም ወደ ጣልያን ከመላክ
እንዲቆጠቡ አሳስበዋል፡፡በስተመጨረሻም ከጣልያን ጋር ያለው ግጭት በሰላማዊ ሁኔታ ያለ
ጦርነት ይፈታል ብለው ተስፋ አድርገው ነበር፡፡ጦርነቱ አይቀሬ መሆኑን ሲያውቁ ግን “ያለን ብቸኛ
ተስፋ ሊግ ኦፍ ኔሽንስ ነው” ብለዋል፡፡
በዚህ ቀውጢ ሰአት ውስጥ እንኳን (የውጪ ጉዳይ ሚንስትር በጄኔሬተር ሃይል እያገኘ
በሚሰራበት ወቅት) ኅሩይ በሃምሌ 27 ለተቋቋመው የቀይ መስቀል ማህበር የመጀመርያው
39
ጥቋቁር አናብስት
የኅሩይ ስደት የታወቀ የስነ ጽሁፍ ሙያቸው ማሳረግያ ነበር፡፡ከ1904 ጀምሮ እስከ ጣልያን ወረራ
ወቅት ድረስ ኅሩይ ፍሬያማ የነበሩ ሲሆን ጥቂት ኢትዮጵያዊያን ብቻ ነበሩ የሳቸው መሳ ሆነው ያን
ያህል መጻፍ የቻሉት፡፡አንድ ግዜ በ1903 ኅሩይ በባቡር ከኦክስፎርድ ወደ ሎንዶን እየተጓዙ ሳለ
ነበር አንድ ስኮትላንዳዊ አልፍሬድ ጆን የሚባል ሰው ተዋውቀው በኢትዮጵያ ምን መጻሕፍት
እንዳሉ የጠየቃቸው፡፡ኅሩይ ከሃዲስና ብሉያት መጻሕፍት ውጪ ሌላ ዝርዝር እንደሌለ ተናገሩ፡፡
አልፍሬድ ጆን ኅሩይን በኢትዮጵያ ያሉ የመጻሕፍትን ዝርዝር እንዲጽፉለት ጠየቃቸው፡፡ወደ
ሃገራቸው ሲመለሱም ከሊቃውንቱ የሰሟቸውን በኢትዮጵያውያን ሊቃውንት የተጻፉ መጽሐፍት
በ9 ገጽ ዝርዝር ይዘው መጥተው በኢትዮጵያ ማተምያ ቤት በ1904 ዓ.ም ሊታተም በቅቷል፡፡
40
ጥቋቁር አናብስት
ከዚያ ቀደም ግን የመጀመርያና በአዲስ አበባ የታወቀውን በ1904 ዓ.ም በማዘጋጃ ቤቱ ማባዣ
የተባዛና (በዝርዝሩ ውስጥ የተካተተውን) ወዳጄ ልቤ የተሰኘውን ጽሁፍ አበርክተዋል፡፡ነገር ግን
እስከ 1915 ዓ.ም ድረስ በወጉ አልታተመም፡፡በነጻ ነበር ያከፋፈሉት፡፡በዝርዝሩ ከተካተቱ መሃል
የራሳቸው ስራና ሳይታተም የቀረው ወይዘሮ ጥበብና የለቅሶ ዜማ ግጥም ይገኙበታል፡፡
9መጽሃፈ ቅኔ 1918
41
ጥቋቁር አናብስት
10 ጎህ ጸባ 1919
11 የለቅሶ ዜማ 1919
12 ዋዜማ 1921
ያልታተሙ
25 ከሳቴ ብርሃን
42
ጥቋቁር አናብስት
27 አዲስ አበባ
28የአማርኛ ስዋሰው
ይህን በማየት ኅሩይ በአመት አንድ መጽሐፍ እየጻፉ ለብዙ አመታት አሳትመዋል ማለት ይቻላል፡፡
43
ጥቋቁር አናብስት
……
ኅሩይ ወልደሥላሴ ምን ዐይነት ሰው ነበሩ? የድሮ ባህሎችን የሚሰብሩ አዲስ ሃሳብ አመንጪ
ዐይነት ሰው ነበሩ (ሌላው ቀርቶ በኢትዮጵያውያን የሚወደደውን ጥሬ ስጋ ከምላስና ሰንበር ውጪ
ሳይበስል የማይመገቡ ሲሆን የበሰለና የተጠበሰ ስጋ ግን ምርጫቸው ነበር)ክርክር የማይወዱ ሲሆን
የጸብ መነሳት አዝማምያ ካዩ ዝምታን ይመርጣሉ፡፡በትርፍ ጊዜያቸው ያነባሉ ይጽፋሉ፡፡ጋዜጣን
በንቃት የሚከታተሉ ሲሆን ያልተመቻቸው ነገር ባገኙበት ጊዜ ሁሉ ምላሽ ለጋዜጣው ከመጻፍ
አይቆጠቡም፡፡በዚህ የተነሳም የአንድ ክፍለ ሃገር አስተዳደር በመስተዳድሩ ውስጥ እየተዟዟረ
በሚጎበኝበት ወቅት ሃገሬው ለእሱና ለ500 ሰዎቹ ምግብና መኝታ ብሎም ለአፍራሳትና
በቅሎዎቻቸው ጥሬ የማቅረብ ግዴታ መግባታቸውን ነቅፈው ገበሬው ላይ ሸክም የሚሆንና
ምንም ፋይዳ የሌለው የበፊት ልማድ ቢሆንም መደረግ ያለበት ከሆነም ደግሞ በገበሬዎቹ ጥያቄና
ወጪው በመንግስት ተሸፍኖ ነው መሆን ያለበት ሲሉ ጽፈዋል፡፡ኅሩይ እንዲህ ባለ ይዘት በብዛት
የመንግስት ሹሞችን እንኳን የሚያስጠይቅ ጽሁፍ ይጽፉ ነበር፡፡
44
ጥቋቁር አናብስት
የሆነው ከአድልዎ በጸዳው ባህርያቸው የተነሳ ነው፡፡ ሁልጊዜ ጠዋት ጉዳያቸውን ለንጉስ
እንዲያቀርቡላቸው አቤት በሚሉ ባለጉዳዮች የቤታቸው በረንዳ ይጨናነቃል፡፡
ኅሩይ ሲበዛ ዝምተኛና ገለል ያሉ ነበሩ፡፡ወደ ድግስ ቦታዎች አይሄዱም፡፡ግን ጥሩ ቀልደኛ የሚባሉ
ዐይነት ሰው ሲሆኑ ቀልድ ማውራትና የመልስ ምት መስማት የሚያስደስታቸው ሰው ነበሩ፡፡
54
በጊዜው አብዛኛው ሰው እንደሚያደርገው ሰው ሲከተላቸው ወይም ሲያጅባቸው አይወዱም ፡፡
በእርግጥ ግን ኦፊሴላዊ ከሆነ ወይም የልዑክ ቡድን ከሆኑ ወዘተ ይስማማሉ፡፡
45
ጥቋቁር አናብስት
ኅሩይ ቀጥ ብለው ነበር የሚሄዱት እቃ ቢወድቅባቸው እንኳን ጎንበስ ብለው ማንሳት አይችሉም፡፡
የጀርባ ችግር ሳይኖርባቸው አይቀርም፡፡ሁሌም በደንብ የሚለብሱ ሲሆን የሃገር ባህል ልብስ ነበር
የሚለብሱት፡፡(ሻውል ቶጋ እጀጠባብ ከላይ ካባ)ወደ ውጪ አገር ሲሄዱ ግን የአውሮጳውያንን
አልባሳትን ይለብሳሉ፡፡ንግግራቸው ግልጽ የማይጮሁ ነገር አዋቂ ሲሆኑ ለብዙዎች መልካም
እርዳታ አድርገው ስራ አስገብተዋቸዋል፡፡ በምላሹም ምንም ነገር አይጠብቁም፡፡መጽሐፍቶቻቸው
የወጡበትን ጊዜ የሚያስታውሱ ሰዎች መጻሕፍቱ በጥሩ ሁኔታ እንደተሸጡ ይናገራሉ፡፡የኅሩይ
ማህተም በግራና ቀኝ የንብ ምስል አለው፡፡መፈክሩም "መልአክ ያልሆነ" የሚል ሲሆን እንደ
መልአክ ባይኮንም እንደ ንብ በታታሪነት መስራት እንዳለበት ለማጠየቅ ነው ይላሉ ልጃቸው ብላታ
ሲራክ፡፡
ጣልያኖች በወራራው ወቅት በአዲስ አበባ ውስጥ ለወረሷቸው ንብረቶች ካሳ ከፍለው ነበር፡፡አንድ
ኢጣልያዊ በአስመራ ለጋዜጣ እንደተናገረውና እውነት እንደሚመስለውም መኳንንቶቹ ሁሉ
“ከንጉሱ ከንግስቲቱና ከራስ እምሩ ውጪ” ካሳ ተቀብለው ነበር፡፡ይህ ቢሆንም የካቶሊክ ቤተ
ክርስትያን የበላይ ሃላፊን ሞንሲኞር ካስቴሌኒን እስካገኙበት ድረስ የኅሩይ ባለቤት ወይዘሮ ሐመረ
46
ጥቋቁር አናብስት
ምንም ያገኙት ነገር አልነበረም(ኅሩይ በወረራው ወቅት ነበር የሞቱት) ፡፡እናም በየወሩ የተወሰነ
ሊሬ እንዲያገኙ አደረጉ፡፡በስደት ወቅት ኅሩይ ኀይለሥላሴ ስለ ኢትዮጵያ እንዲናገሩ እስከ
እለተሞታቸው ድረስ ይገፋፉ ነበር፡፡ነገር ግን የስደትን ስራ አስፈቺነት አድካሚ ሆኖ ሳያገኙት
አልቀሩም፡፡በሎንዶን የኦርየንታል ጥናት (አሁን የኦርየንታልና አፍሪቃዊ ጥናት ትምህርት
ቤት)አማርኛና ግእዝን ማስተማር ጀመሩ፡፡ኅሩይ በሎንዶን በሚኖሩበት ወቅት ኀይለሥላሴ
በፌርፊልድ ባዝ በመንግስት ቤት ውስጥ ይኖሩ ነበር፡፡58
ኅሩይ በጣልያን ኢትዮጵያን መውረር አእምሯቸው ተጎድቶ ነበር፡፡በተለይ በሃገሪቱን መጻኤ እድልና
የነጻነት አለመታወጅ ሲብሰከሰኩ በስተመጨረሻ ታመሙ፡፡ኀይለሥላሴ በመንግስት ቤቱ ግቢ
ውስጥ ክፍል ተሰጥቷቸው እንዲኖሩ ወደ ባዝ ጠሯቸው፡፡ጤናቸው መጓደል ጀመረ፡፡
በመጨረሻም መንቀሳቀስ አቅቷቸው በባለጎማ ተሸከርካሪ ወንበር ነበር የሚሄዱት፡፡
እንደጠበቁትም በጣልያንና ጀርመን ሽንፈት ለኢትዮጵያ የነጻነት ተስፋ ፈንጣቂ ሊሆን ስለሚችል
በማለት ሁለቱ ሃገራ በፈረሙት ስምምነት ተደስተው ነበር፡፡የጤናቸው ጉዳይ ግን ባሰበት፡፡
በመስከረም 9 በ60ኛ አመታቸው በ1931 ዓ.ም አረፉ፡፡ልጃቸው ሲራክና አባ ገብረሃና ጂማ
ምናልባትም ሌሎች ጥቂቶች በመሞቻቸው ሰአት ከጎናቸው ነበሩ፡፡
ከመሞታቸው ጥቂት ቀናት በፊት ኅሩይ ልጃቸውን ሲራክ ስነጽሁፋዊ ስራዎቻቸውን ወይም
ቅርሶቻቸውን እንዲንከባከብ አደራ ብለውት ነበር፡፡ኀይለሥላሴ “ካገዷቸው” መጻሕፍት በስተቀር
አሁንም በመደበኛ መጻህፍት መደብሮ መጻህፍቶቻቸውን ማግኘት ቢከብድም በአዲስ አበባ
መንገዶች ላይ መጽሐፍቶቻቸው ይሸጣሉ፡፡ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ብላቴንጌታ ኅሩይ በሚለው
ስማቸው የሚያውቃቸው ሲሆን ተወዳጅም ነበሩ፡፡
47
ጥቋቁር አናብስት
ማስታወሻ
2 ምሳሌ 1 ታዋቂው የስነ-ሰብ ምሁር ሲ.ኩን በአንድ ወቅት የኅሩይን የራስ ቅል መጠን ለመለካት
ሞክሮ ነበር፡፡ኅሩይ ግን በሳቸው ምትክ አንዱ ሰራተኛቸውን ላኩ፡፡(2)አንድ ዘመዳቸው ጠንካራ
መጠጥ (ውስኪ)ይወዱ ነበር ብለዋል፡፡ ይህ አባባል ግን በቅርበት በሚያውቋቸው ሰዎች ተቃውሞ
ገጥሞታል፡፡ (3)በቤተሰቦቻቸው ዘንድና በሚተዋወቋቸው መሃል ስጠይቅ ወጣት ሴቶችን የሚወዱ
መሆኑንና ብዙ እቁባቶች በከተማው ውስጥ እንዳሏቸው ነግረውኛል፡፡ከህጋዊ ጋብቻ ውጭ ግን
የተወለዱ የታወቁ ልጆች የሉም፡፡(4)ብዙዎች ትምህርት ይገልጻል ብለው የሚያስቡትን አብሾ
እንደጠጡ ያምናሉ
6 ከሸዋ መርሃቤቴ ነች
7ሴቶች በአንዳንድ ገዳማት አለቃ መሆን ይችላሉ፡፡ወንዶች ብቻ ይሁን የሚለው ለሌሎች ገዳማት
ነው የሚሰራው በአንዳንድ ቦታዎች ደግሞ መነኮሳት ይሾማሉ አለቃ ለብዙ አግባቦች የሚያገለግል
ቢሆንምትክክለኛው ስራቸው ከቦታ ቦታ ይለያያል፡፡
9ጽህፈት በተለይ የቁም ጽህፈት በተወሰኑ ትምህርት ቤቶች ብቻ የሚሰጥ የተለየ ጥበብ ነው፡፡
መጻፍና ማንበብ አብረው አይሰጡም፡፡ አብዛኞቹ ማንበብ የተማሩ ሰዎችም መጻፍ አልተማሩም
48
ጥቋቁር አናብስት
10የኅሩይ አባት በሳቸው ስልጣን ደረጃ ሆነው ማንበብ ስለማይችሉ ተሰድበው ያውቃሉ፡፡በአንድ
ወቅት ኅሩይ አባታቸው እንዲህ ባለ ሁኔታ ሲሰደቡ ሰምተው ነበር፡፡የዚህ ትዝታ ደግሞ
በአእምሯቸው ተቀርጾ ቀርቷል፡፡(ምንም እንኳን ሰዳቢውን በኋለኛ ዘመኑ አግኝተው ይቅር
ቢሉትም)ይህ ሁኔታ አባትየው እሳቸው እንዲማሩ የመፈለጋቸውን ቁርጠኝነት ሳይወልድ
አልቀረም፡፡
14 በጊዜው ከኀይለኞች ሴቶች መካከል አንዷ ስትሆን በአቤቶ እያሱ የስልጣን ሽሚያ ዙርያ
የራስዋን ሚና ተጫውታለች
15እ.ኤ.አ ከ1888 እስከ 1892 ድረስ በአካባቢው የተዛመተ ድርቅ ነበር፡፡አንበጦችና አረም
ኢትዮጵያና አካባቢውን አጠቁ፡፡የሪቻርድ ፓንክረስትና የዲ.ኤች ጆህንሰን "the great
drought and famine of 1888-1892 ገጽ 44-70 ጆህንሶን እና ዲ.አንደርሰን the
ecology of survival case studies from northeast African history London
1988 ኢትዮጵያውያን ይህንን ጊዜ "ክፉ ቀን " ሲሉ ይጠሩታል፡፡የ ጎጃሙ አለቃ ተክለኢየሱስ
የኢትዮጵያ ያልታተመ ታሪክ፡፡
16ኅሩይ ሰርክ ስለዚህ ጉዳይ ያመሰግኑ ነበር፡፡በኋላ ለበሻህ ልጆች ጊዜው ሲከብድባቸው መሬት
ገዝተውላቸውም ነበር፡፡
17ራስ ከንጉስ ቀጥሎ ያለ ታላቅ መአረግ ነው፡፡ራስ መኮንን የአጤ ምኒሊክ ጠንካራ ደጋፊና
የሃረርጌ ገዢ ነበሩ፡፡
18ይሄ በቤተክህነት ምሁራን መሃል የእጅ ጽሁፍ ችሎታ ምን ያህል ከባድ እንደነበር ያሳያል፡፡
49
ጥቋቁር አናብስት
23 ብር በወቅቱ አባባል የማርያ ቴሬዛ ዶላር ማለት ነው፡፡በወቅቱ እንደ መገበያያ የሚጠቅም
ሲሆን ጥሩ የመግዣ አቅም ነበረው፡፡
29እንደ ኅሩይ ቤተሰቦች አነጋገር ከሆነ ከዚህች ላም የሚወለዱ ዝርያዎች ይህ መጽሐፍ እስከ
ተጻፈበት ጊዜ ድረስ ነበሩ፡፡
34 ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ወጣት ሴቶች በተቀረው አለም የወጣት እድሜ ግንዛቤ መሰረት ያሉ
አይደሉም፡፡እሳቸውም የጋብቻ የእድሜ ጠለሉ አስር አመት እንዲሆን በኋለኛ እድሜያቸው
ታግለዋል፡፡ከዛ ቀደም በሳባትና በስምንት አመታቸው ሴቶችን ለጋብቻ ማጨት የተለመደ ነበር፡፡
51
ጥቋቁር አናብስት
40 አቡን የኢትዮጵያ ቤተክህነት ታላቁ ሹመት ነበር፡፡እስከ 1951 አ.ም ድረስ ከእስክንድርያ
እናት ቤተ ክርስትያን ነበር የሚሾመው፡፡ከዚያ ወዲህ ግን ቤተክርስትያኒቷ እራስዋ ነች
የምትሾመው
47ይህ በኋላ የፓስተር ኢንስትትዩት ቆይቶ ደግሞ የብሄራዊ ጤና ምርምር ተቋም ሆኗል፡፡
52
ጥቋቁር አናብስት
49ቆይቶ ሁሉም ሚንስትሮች ባለመኪና ሆኑ፡፡ከዚያ በፊት ባለመኪና ከነበሩት መሃል ራስ ሃይሉና
የተወሰኑ አርመኖች ይገኙበታል፡፡አብዛኞቹ መኪናዎች የጣልያን ስሪት ነበሩ፡፡እናም በአብዛኛው
በታክሲነት ከባቡር ጣብያ በማመላስ ይሰሩ ነበር፡፡
50 በሳቸው የልኡካን ቡድን ውስጥ ከነበሩት ሌሎች በተጨማሪ ዳባ ብሩና አርአያ አበበ
ነበሩበት፡፡
52 በኢትዮጵያ በግልና በጋራ መሃል ያለው መስመር ቀጭን ነው፡፡እሱም በብዙ ሁናቴ ውስጥ
ከተገኘ ነው፡፡ውለታ በብዙ ግንኙነቶች መሃል ጠቃሚ ነው፡፡
53ይሄ ጉዳይ በአንዳንዶች ከሚባለው በላይ ትኩረትን የሚሻ ነው፡፡ ስለ ወንጀለኛው መረጃ
አቅራቢ እና የተወሰኑ ሰዎች በጽሁፉ ውስጥ እንደጠቀሱት ከሆነ አቶ አለመ ሥላሴ ሃብተ መስቀል
የጉምሩክ ተቀጣሪ ነበሩ፡፡እሳቸው አንድ ስሙ አቶ ሃዲስ የሚባል ግለሰብ እና ሌላ አንድ ሰው
ተፈሪ እነሱ ወደ ሚሰሩበት ከመጡ ለመግደል ተስማምተው ነበር፡፡አቶ ሃዲስ በኢትዮጵያ ንግድ
ባንክ ነበር የሚሰሩት፡፡ሶስተኛው ሰው የተፈራረሙበትን ሰነድ ለተፈሪ አሳያቸው ፡፡ ሌሎቹ ሁለቱ
በቁጥጥር ስር ውለው እንዲገረፉ ተፈረደባቸው፡፡ነገር ግን አቡነ ማቴዎስ ጣልቃ ገብተው ቅጣቱ
ወደ እስራት ተለወጠ፡፡ሌሎች ሁለት ሰዎች አንዱ አጋፋሪ በቀለ አቦዬ የዘመናዊ ኢትዮጵያ ታሪክን
የጻፉትና (ያልታተመ ሲሆን በዙፋን ቤተመዝገብ የነበረ ሲሆን የተሰረቀም ሊሆን ይችላል)
ቀኛዝማች ድፋባቸው የአቡነ ማቴዎስ ዳኛ በሴራው እንዲሳተፉ ተጠይቀው ፍቃደኛ የነበሩ ሲሆን
በጉዳዩ ተስማምተው የደገፉ ቢሆንም አንፈርምም ብለዋል፡፡ጉዳዩን ባጋለጠው ሰው ስማቸው ሲነሳ
ግንኙነት እንደሌላቸው ተናግረው ካዱ፡፡ተፈሪም ነገሩን አለፉት፡፡አለመ ሥላሴ በሰላ ድንጋይ
ሲታሰር ሃዲስ ደግሞ ሙሎ ሰላሌ ውስጥ ታሰሩ፡፡ቆይቶ ሁለቱም ይቅርታ ተደረገላቸው፡፡አለመ
ሥላሴ ሚስቱ የግብጽ ዝርያ ስላለባትና ከአቡነ ማቴዎስ ጋር ስለሚዛመዱም እሳቸው ቤት
በሰራተኞች አዛዥነት ቆይቶ ንጉሱ ከስደት ተመልሰው ጎጃም ላይ ሲደርሱ ህይወቱ አልፏል፡፡ሃዲስ
ግን ብዙ ቆይተው እ.ኤ.አ በ1960 አካባቢ ህይወታቸው አልፏል፡፡
54የኢትዮጵያ አዝናኝ ታሪኮች ባለ ሁለት አጽቅ ምላሾችን ያካተቱ ናቸው፡፡ይህ የሃበሻ ቋንቋ
ተወዳጅ አጠቃቀም ነው፡፡
53
ጥቋቁር አናብስት
54
ጥቋቁር አናብስት
አቤ ጎበኛ
ብቸኛው የሙሉጊዜ ደራሲ/እንጀራውን በመጻሕፍቱ
የጋገረብቸኛው ኢትዮጵያዊ ደራሲከብዙ ዓመታት በፊት በአማርኛ
ሥነጽሑፍ ላይ ፍላጐት ማሳደር ስጀምር ፣ብዙ ወጣት
ኢትዮጵያውያን "የአቤ ጉበኛን መጽሐፍት አንብበሀል?" እያሉ
ይጠይቁኝ ነበር።ወዲያውኑ አንዳንዶቹን ማንበብ ጀመርኩ፤ቀስ
በቀስ ሁሉንም አንብቤ ጨረስኩ።ነገር ግን የጠበቅኩትን ነገር
አላገኘሁም። ይሁን እንጂ መጪው ጊዜ ብሩህ እንደሚሆን፣እነሱም
ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱ ለሚጠብቁ ወጣት (በተለይ በፖለቲካ
ረገድ)እና ገና በመማር ላይ ላይ ያሉ ያልበሰሉ አንባቢዎች፣አቤ ለምን ማራኪ ሊሆን እንደቻለ
መረዳት አይከብድም፡አቤ በአንድ ታታሪ መሪ የሕይወት ዘመን ውስጥ ሐገሪቱ ከፍተኛ የእድገት
ማማ ላይ መውጣት እንደምትችል የሚያሳይ አስደሳች ምስል መቅረጽ ችሏል።ሁሉም ነገር
ቀላልነው፤ይሁን እንጂ መሰናክሎችን ሁሉ ችሎ ለማለፍ አንድን ሰው "ከባድ ስራ" ይጠይቀዋል።
ሐብት እና "ስልጣኔ" ሃገሪቱን ያጥለቀልቃታል፤ ባህል ያብባል።ይህ ሁላችንም መኖር
የምንፈልግበት የምኞት አለም ነው።ይህ ነበር አቤ ጉበኛ ለወጣቶች ቃል የገባላቸው ፍፁም አለም።
አቤን ስለሥነጽሑፍ ስራዎቹ ሳላነጋግረው በፊት በ1972 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።አቤ
ሁለገብ ነበር፤ልብወለድ፣ተውኔት፣ወግ፣አጭርልብወለድ፣ባህላዊ እና ዘመናዊ ሥነግጥም ይጽፍ
ነበር። ከመሞቱ ከአስር ዓመታት በፊት የኢትዮጵያውያንን የንባብ ልምድና ምርጫ በተመለከተ
በተደረገ ጥናት፣አቤ ቁጥር አንድ ተነባቢ ደራሲ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል።
አቤ ጉበኛ የተወለደው በሰኔ 25ቀን 1925 ዓ.ም ወይም በሰኔ 19ቀን 1926 ዓ.ም (ከሁለት
የተለያዩ ምንጮች በተገኘ መረጃ መሰረት) በጎጃም ክፍለሀገር፣በባህርዳር አውራጃ፣በአቸፈርወረዳ፣
ቆረንጭ (ቆረንጭ አቦ) በምትባል መንደር ነበር።ወላጆቹ ጉበኛ አምባዬ እና ይጋርዱ በላይ
ይባላሉ። “በጠራ” የአማራ ሀገር የተወለደውና ያደገው።1
አቤ ቅድሚያ ፊደል የቆጠረው በቄስ ትምህርት ቤት ሲሆን፣ በስድስት ዓመቱ ማንበብ ቻለ።ከዚያ
ወደ ቤተክርስቲያን ትምህርት ቤት ገብቶ፣በዚያ የሚሰጠውን ባህላዊ ትምህርት ተከታትሏል።
የቤተክርስቲያን ዜማ እና ወረብ እንዲሁም ቅኔ ተማረ።በተለይ ቅኔ አዋቂነቱ የተመሰከረለት ሲሆን
"ሊቅ" የሚል ማዕረግ አሰጥቶታል።በቤተክርስቲያን ውስጥ አባቶች "የልጆችን አእምሮ ለመክፈት"
፣ይበልጥ ብሩህ ለማድረግ፣ትምህርት እንዲቀበሉ እና ቅዱስ መጽሐፍትን በቃላቸው እንዲያውቁ፣
55
ጥቋቁር አናብስት
አብሾ የተባለ አንዳች መድሐኒት ያቀምሷቸው ነበር።በተለይ ደግሞ የአቤ አባት ልጃቸው የተሻለ
ተማሪ እንዲሆን ይህንኑ "መድሃኒት" እንደሰጡትይነገራል።ይህ ጉዳይ እውነትም ይሁን ውሸት፣አቤ
ጎበዝ ተማሪ እንደነበር ያስታውቃል።
56
ጥቋቁር አናብስት
አቤጉበኛበአማርኛ ከ20 በላይ መጽሐፍትን ሲጽፍ፣ ሌሎች ሁለት ደግሞ በእንግሊዝኛ አሳትሟል።
ብዙ ከፃፉ ኢትዮጵያዊ ደራሲያን መሐል አንዱ ነው።ሁለት ተውኔቶቹ በአዲስአበባ ለመድረክ
በቅተውለታል።አባቱ እንደሚሉት አቤ ትምህርት በጣም መውደዱ ብቻ ሳይሆን ገና ከለጋነቱ
ጀምሮ ብእርና ወረቀት ከእጁ እንደማይለይ ይናገራሉ።አቤ በጫካ ውስጥ ብቻውን መዘዋወር
መውደዱ ከልጅነቱ ጀምሮ "ህልመኛ"ሳይሆን እንዳልቀረ ያሳያል።ለድሆች ሀዘኔታ እንደሚሰማው
መግለጽ የጀመረው በለጋነቱ ነው፤በተለይ ውሀ ቀድተው ሩቅ መንገድ ለሚሸከሙና ሌላ ከባድ ስራ
ለሚሰሩ ሴቶች ያዝናል።በተጨማሪም በደንብ የሚያውቁት ሰዎች "ለሴቶች የተለ የፍቅር ነበረው"
ይላሉ።
ሁለት መጽሐፍቱ በሚገባ እንደሚሸጡ በመተማመን ከቁጥር በላይ አሳትሞ ሽያጩ በውስኑ
የኢትዮጵያ ገበያ ምክንያት እንደተጠበቀው ሳይሆን ቀረ። በሕይወቱ የመጨረሻ ወራት ላይ፣ነፍስና
ስጋውን ለማቆየት ከጓደኞቹ ገንዘብ እስከመበደር ደረሰ።ከዚህ ጥቂት ቀደም ብሎ ከባህርዳር
ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ፣ የፋብሪካው ምርቶችን በእርካሽ እንዲያገኛቸው ተደርጐ፣ይህንን እየሸጠ
የተወሰነ ትርፍ ማግኘት ቻለ።ነገር ግን ለኑሮ፣ ለምግብ እና ለልጆች የትምህርት ወጪ በቂ
አልነበረም። ትንሿ የመጽሐፍትና የጽሕፈት መሳሪያዎች መደብሩ ሙሉ ለሙሉ ልጆቻቸውን
የማሳደግ ሃላፊነቱን በተረከበችው በቀድሞ ባለቤቱ እጅ ነበር።
ለመግባት ይሞክራል፤ መጠጥ ቤቱ ግን ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ እስከ አስራ አንድ ሰአት2 ድረስ
በሚዘልቀው ሰአት እላፊ ምክንያት ሊዘጋ ነበር። ጠባቂዎች መግባት ቢከለክሉትም3 ነገሩ ተጋግሎ
ወደ ጠብ በማምራቱ አቤ ጭንቅላቱን ተመቶ ራሱን ሳተ። ይህ የሆነው አዲስ አበባ ውስጥ ጎጃም
በረንዳ በሚባለው አካባቢ ነው።
የተርጓሚው ማስታወሻ
ማስታወሻዎች
58
ጥቋቁር አናብስት
59
ጥቋቁር አናብስት
ተክለሐዋርያት
ተክለማርያም እና ግርማቸው ተክለሐዋርያት የተረት አባትና ተራኪ
ግርማቸው ተ/ሐዋርያት ስለ ሕይወቱ ላነጋግረው በተገናኘንበት
አጋጣሚ በጸና ታሞ ነበር፡፡በአብዮታዊው መንግስት ለ8 አመታት
ከታሰረ በኋላ የተለቀቀውም በዚሁ እያስቸገረው በመጣው የጤና
መጓደል መንስኤ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ልጆቹ በሙሉ የሚኖሩት ከሃገር
ውጪ ነበር፡፡ አንዱ ልጁ
በእርሱና በአባቱ ዙርያ የተሰሩ ታሪኮች የተወሰነ አስቸጋሪነት አላቸው። በጦርነቱ ወቅት ጣልያን
ስለነበረበት ጊዜያት የነገረኝ ሃዲስ አለማየሁም ሆነ ሚካኤል እምሩ(ትውስታዎቻቸው ላይ
ተመስርተን)ካወጉኝ ጋር አይጣጣምም፤ሶስቱም ደግሞ በዚያን ወቅት አብረው ነበሩ። ግርማቸው
ለእውነታው በቂ ትኩረት ሳይሰጠው "ሞቅ ያለ ታሪክ" ሊነግረኝ ስለፈለገ በአበይትም ሆነ ጥቃቅን
በሆኑ ጉዳዮች እውነታዎችን ሳይዘረዝር ያጫወተኝን ነገሮች ሙሉ በሙሉ አልተቀበልኳቸውም፡፡¹
60
ጥቋቁር አናብስት
***
ከበርካታ የአውሮጳ የትምህርት ቆይታ በኋላ የዘር ሀረጋቸውን የማወቅ ፍላጎት አድሮባቸው ይህንኑ
የቤተሰቦቻቸውን ትውልድ አመጣጥ ከሚያውቁ አእሩግ ጠይቀው ይዘው የነበር ቢሆንም
ከ1928-1933 ዓ.ም በነበረው የጣልያን ወረራ ወቅት ጠፍቶ ቀርቷል፡፡ግለታሪካቸውን መጻፍ
በጀመሩበት ወቅትም ማስታወስ የቻሉት ከአያቶቻቸው ፈቅ አይልም፡፡አያቶቻቸው ዋየህ እና
ይጠይቁሽ 6 ሴት ልጆች የነበራቸው ሲሆን (ስማቸው አይታወቅም) ሁለት ወንድ ልጆችም
አሏቸው። አብዬ (ትንሽ ጊዜያት የሚፈልገውን መሰረታዊ ትምህርት አጥንቶ ቀሰሰ)ተክለማርያም
ደግሞ ከሚስታቸው በለጥሻቸው አራት ልጆችን መውለድ ችለዋል፡፡ ገብረ ጻዲቅ፣ገብረ መድህን፣
ሃብተ ማርያም እና ተክለሐዋርያት።ተክለሐዋርያት የወልደማርያምን ልጅ ሳህለ ማርያምን አገቡ፡፡
ሳህለማርያም በእንጀራ አባቷ ስም ሳህለማርያም ንጋቱ ተብላ ነው የምትጠራው፡፡የተክለሐዋርያት
ዘሮች ኦሮሞ ፈረሰኞች ሲሆኑ ወደ መንዝ ተሻግረው ኑሯቸውን እዚያው የመሰረቱ(የቤተክርስቲያን
ሰዎችም የሆኑ)ቤተ ክርስቲያንም ጭምር ያነጹ ነበሩ።ዋየህ”ትልቅ ሰው”ለመሆን በቅቶ በአካባቢው
ቤተ ክርስቲያን ለመታወቅ በቃ፡፡⁴
61
ጥቋቁር አናብስት
ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅት ሚኒሊክ ሃገር አቀፍ የጦር ጥሪና ንቅናቄ ባደረጉበት
1888 ዓ..ም ራስ መኮንን ወደ ጦርነቱ የሄዱት የያኔውን የ12 ዓመት ልጅ ተክለሐዋርያትን (በጉዞ
ወቅት በእርሳቸው ፈረስ ላይ ለመሄድ አንዳንዴም ከጀርባቸው ለመፈናጠጥ በቅተዋል)6እና ገብረ
ጻዲቅን ይዘው ነበር፡፡ራስ መኮንን ባሸነፉበት የመቀሌው የህዳር 28 1888 አ.ም ጦርነት
ባለቅኔው፣ ምሁሩና በቀጥታ በመናገር ባሕርይው የሚታወቀው ገብረጻዲቅ ተገደለ፡፡
62
ጥቋቁር አናብስት
63
ጥቋቁር አናብስት
ሚኒሊክ በዚህ ወቅት ከአልጋ ውለዋል፡፡ለውጥ ማምጣት የሚችለው ሃይልም በልጅ ልጃቸው
በእያሱ (የወሎው ራስ ሚካኤልና የምኒሊክ ሴት ልጅ ወ/ሮ ሸዋረጋ ልጅ)እጅ ላይ ነበር፡፡
ተክለሐዋርያት የኋላኋላ በሕይወታቸው ቆይታ ከእያሱ ጋር ለመግባባት ስለፈለጉ የላፎንቴይንን እና
የክሪሎቭን ተረቶች በመተርጎምና በማላመድ በ1913 እ.ኤ.አ አካባቢ ወደ አሰማርኛ እንደመለሱ
ጽፈዋል፡፡ እንዳንዶች ግን የሃገረሰብ ተረቶችንም እንደተጠቀሙ ይናገራሉ፡፡ይህን ይህን አድርገው
የተሰናሰለ ታሪክ በመፍጠር ልጅ እያሱን በምሳሌ ለማስተማር ነበር ያልታተመ ረቂቁን ፋቡላ
የአውሬዎች ኮመድያ11ሲሉ ሰይመው በግምት በ1913 የጻፉት፡፡እሳቸው እንደ ኢትዮጵያውን
አቆጣጠር በ1904 ና በ1906 በአውሮጳውያን አቆጣጠር በ(1911/2 እና በ1913/4)ቢሉም
በልማድ ደረጃ ግን በብዛት የሚታመነው በንግስት ዘውዲቱ የአገዛዝ ዘመን እ.ኤ.አ (1916-
1930) እንደተጻፈ ነው፡፡ እኔም በዚሁ ትክክለኛነት ወደማመን አደላለሁ።¹²በእያሱ ዘመን
(1913-916) እንደተመደረከ ቢጽፉም እውነቱ ግን ይኀው ተውኔት በዘውዲቱ ዘመን ለመድረክ
በቅቶ መልሶ መታገዱ ነው፡፡ንግስቲቱ በአጠቃላዩ በንቅዘት በሚታሙና በችሎታ ባልበቁ
ባለስልጣናት ላይ እንደ ተሰነዘረ ሂስ ነበር የቆጠሩት፡፡ተውኔቱ በድጋሚ በአጼ ኃይለሥላሴ ዘመን
ለመድረክ ቢበቃም በህትመት መልክ ግን ወጥቶ የማያውቅና ለማግኘትም አስቸጋሪ ነው፡፡ 13
64
ጥቋቁር አናብስት
በ1914 እ.ኤ.አ ተክለሐዋርያት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ የነበሩት ቢትወደድ ሃይለጊዮርጊስ
ዘንድ እንዲሰሩ ቢጠየቁም ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተው በ1915 እ.ኤ.አ ከእንግሊዝ አሳሾች ጋር ወደ
ጣና አቅንተዋል፡፡ እንደእሳቸው ከሆነ በዚያው ዓመት የምድር ባቡርተቆጣጣሪ ሆነው ቢሾሙም
ልጅ እያሱ በሃገር አስተዳደር እርዳታቸውን ስለሚፈልጉ እንዳስጠሯቸው ፤በዚያን ወቅትም የእያሱ
የቅርብ አማካሪ እንደነበሩ፤ከቅርብ ወዳጃቸው ከተሰማ እሸቴ(ዘመዳቸውን ጸሃይ ወርቅ ዳርጌን
ከዳሩላቸው)ሳይቀር እንሚያስበልጧቸው ያስቀምጣሉ፡፡በዚሁ ግለ ታሪካቸው ላይ በተጨማሪም
ከልጅ እያሱ ጋር የፈረንሳዊውን ገዢ ሙሴ ሳይመንን ለማግኘት ወደ ጂቡቲ አብረው ባደረጉት ጉዞ
የተገለጸልኝ ነገር ቢኖር "እያሱ ኢትዮጵያን የመምራት ክህሎት እንደሌላቸው ነው"ሲሉ ያክላሉ፡፡
እያሱ ለውሳኔዎች ፈጣን፤ሰዎችን ለመሾም ለመሻር የማይጠበቁና ሃላፊነት የማይታይባቸው
ብያኔዎች እንደሚሰጡ ለእርሳቸውም ይሄን ጉዞ ተከትሎ ከፍተኛ ሃላፊነት በሐረርጌ እንደሰጧቸው
(ተፈሪ አስተዳዳሪ በሆኑበት)ጽፈዋል የሚታመን ከሆነ፡፡እያሱ በርካታ ሰዎችን መሾማቸውን
ቀጠሉበት በርካቶቹም ሙስሊሞች መሆናቸው ተክለሐዋርያት እያሱ ሙስሊም¹4መሆናቸውንና
ሃገሪቱን ወደ እስልምና15 የመቀየር ፍላጎት እንዳላቸው እንዲጠራጠሩ አደረጋቸው፡፡እያሱ
ተክለሐዋርያትን “እንደ ቅርብ አማካሪያቸው” ቆጥረዋቸው ሳለ መልሰው ደግሞ ከኔ ይልቅ ከተፈሪ
ጋር ይቀራረባል ሲሉ እንደሚጠረጥሯቸውም ጭምር ቀጥለውም በእያሱ ያለመብሰል፤ችሎታ ማነስ
65
ጥቋቁር አናብስት
በእያሱ ታሪክ ላይ ፍላጎት አሳድሬ በእርሳቸው ዘመን የነበሩ እኩዮቻቸውን ጠይቄ ነበር ፡፡ በተለይ
እርግጠኝነቱን ያመንኩበት አንድ (ምስክር)“እንኳን በነዚህ ነገሮች ላይ ተጽእኖ ሊያሳድሩ ቀርቶ
ተክለ ሐዋርያት ከማእከላዊው ስልጣን የራቁና እየሆነ ያለውን የማያውቁ ናቸው16 ”ብሎ ነግሮኛል፡
፡በዚህ ወቅት የነበራቸውን ሚና አጋነው ለማቅረባቸው እርግጠና ነኝ፡፡እራሳቸውን ሲያዋድዱ
አልያም ስልጣኑ ወዳጋደለበት ሊጠጉ ሲፈልጉ ካልሆነም የልጅ እያሱ ወገን ስለነበሩ እራሳቸውን
ሊያድኑ ወይም አፋሮቹን ወርረው ለዘረፉባቸው ከብትና እድሜ ልካቸውን ለከበሩበት ዘመቻ
ማስተባበያ ፍለጋ ይሆናል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ተክለሐዋርያት ከቀርሳ ሃረርጌ የተገኘቸውን ከራስ መኮንን ወታደሮች መሃል
የአንዱ ልጅ የሆነችውን ወ/ሮ ሳህለ ማርያምን በተክሊል አገቡ፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ
ክርስቲያን ህግጋት መሰረትም ጋብቻው መፍረስ አይችልም፡፡ብዙ መከራ ባዩባቸው የስልጣን
ሽግግሮች ቢቸገሩም በደስታ የተሞላ “ከሚመስል” የትዳር ኑሮ አራት ወንዶችና አራት ሴቶች
ልጆችን አፍርተው ኖረው ወ/ሮ ሳህለ እ.ኤ.አ በ1959 አርፋለች፡፡ልጆቻቸው ግርማቸው፤ላቀች፤
66
ጥቋቁር አናብስት
****
በ1923 መጀመርያ አካባቢ ተፈሪ ወደ አዲስ አበባ አስጠርተዋቸው (ሂርናን ጨምሮ) ጨርጨር
ላይ በገዢነት ሾሟቸው፡፡ ሹመቱን ግን ከመቀበላቸው በፊት ተክለሓዋርያት ቅድመ ሁኔታዎችን
አስቀመጡ፡፡በመንግስት መሬት ተተክለው ጭሰኞችን ክራይ እየተቀበሉ ያሉ መልከኞች ተነስተው
በምትካቸው ችሎታ ያላቸው ሰዎች እንዲተኩ፤የአዳል መሬት በእርሳቸው ስር(ወደ ጨርጨር)
እንዲጠቃለል፤አዲስ ህግ ለአካባቢው ወጥቶ በስራ ላይ እንዲውል ሲሆን የዚህ ቅድመ ሁኔታ
ግልባጭም ለሃረሩ አውራጃ እንደራሴ ለእምሩ ኃይለሥላሴ እንዲደርስ ጠየቁ፡፡ በተፈሪ ሂርናን
መናገሻ የማድረግ ፍላጎታቸውን ከተከለከሉ በኋላ መስተዳድሩን ከቁኔ ይመቻል ብለው ወዳሰቡት
በ1923 እ.ኤ.አ መስርተውት አልጋወራሽ ተፈሪ አሰበተፈሪ ተብሎ እንዲሰየም ወደወሰኑት ጭሮ
አዞሩት፡፡17ከተማዋም በፍጥነት ተገንብታ ለሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞችም ሞዴል እንድትሆን
ታስባ ነበር።18 ተክለሐዋርያት ጨርጨርን ለ7 አመታት አስተዳደሩ፡፡ በድጋሚም አውራጃውን
ለማሻሻል ሲሉ ለ10 ንኡስ ወረዳዎች ከፈሉት፡፡ በወቅቱ በኢትዮጵያ አዲስ በሆነው አሰራር ቋሚ
ደሞዝ ለሰራተኞች መክፈልና የዓመት ግብርን (ህጉ እስከዚያ ግዜ ድረስ እንደተደነገገው)በገንዘብ
መሰብሰብን አስጀመሩ፡፡ ቀረጥ የሚተመነው በመሬት ስፋትና ጥራት ተዋረድ ልክ ስለነበር ይሄም
የተለመደውን የገባሮችን የኩዳድ ስራ የሚያስቀር ነው፡፡ተፈሪ ግን በተሰበሰበው ግብር ስላልረኩ
በህዝቡ ላይ ግብሩን እጥፍ እንዲተምኑባቸው አዘዟቸው፡፡ተክለሐዋርያት ግን ድልድይ በማስገንባት
67
ጥቋቁር አናብስት
68
ጥቋቁር አናብስት
አንዳንዴ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ይሸጣል፡፡ ከእስር ከተፈቱ በኋላ እንቅስቃሴያቸው ሂርና ላይ
ባለው እርሻቸው ተገደበ፡፡
***
ብዙም ሳይቆይ ግን ወዲያውኑ በ1930 እ.ኤ.አ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ተብለው በተቀቡት ንጉስ
ለአዲስ ስራ ተፈለጉ፡፡ኃይለ ሥላሴ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማያውቀውን ሕገመንግስት
እንዲቆም ፈለጉ፡፡ተክለሐዋርያት ለመንገሻ ገሠሡ በመስከረም 1963 በሰጡት ቃለ መጠይቅ
“ሕገመንግስቱ ያስፈለገበት ምክንያት ለውጪ መንግስታት ኢትዮጵያ ህገመንግስት እንዳላት፤
መንግስቷም ህገመንግስታዊ እንደሆነ፤በስርአት አልበኝነት ላይ የሚነሱ ውንጀላዎች፤ የፊውዳል
ህጎችን፤ ያልተብራሩ የአስተዳደር ቅደም ተከተሎችንና፤ ትርምስምስ መንግስታቸው ላይ የሚሰነዘሩ
ውንጀላዎችን ለመመከት እንዲመቻቸው ነበር” ብለዋል፡፡ ሲጀመር ባለ 55 አንቀጹ ሕገመንግስት
የህዝቡን ጸጥታናየሃገሪቷን አንድነትና የንጉሱን ሃይል ለማጋፈር ነው የተቀረጸው፡፡ ተክለሐዋርያት
የተለያዩ ሕገመንግስታትን ቢመረምሩም (የጣልያን፤ጀርመንና፤የእንግሊዝ) የተመቻቸውን “ደብዛ”
ግን ያገኙት ከጃፓኑ የ1889 ህገመንግስት ነበር፡፡በመጀመርያ ይህ ስራ ካቅሜ በላይ ነው ብለው
ስላሰቡ ቢያንገራግሩም በኃይለሥላሴ ግፊት ተቀብለዋል፡፡ ከጃፓኑ ሕገመንግስት ጋር ካሉት
ልዩነቶች መሃል ለምሳሌ(በኢትዮጵያው ህገመንግስት ላይ የንጉሱ ስልጣን መላቅ)የመናገር፤
የመሰብሰብና የሃይማኖት ነጻነት(ጭርሱን በሳቸው ህገመንግስት ውስጥ አልተነሱም) ይገኛሉ፡፡(ስለ
ውጪ ግንኙነት በህገ መንግስቱ ያለው ነገር“ዋጋ የሌለው”ነበር ሲሉ እራሳቸው ተናግረዋል )
በታላቁ3፟ ቤተመንግስት ከቤተሰባቸው ጋር አብረው ተቀምጠው ሕገ መንግስቱን እያረቀቁ የጻፉት
ተክለሐዋርያት “ኃይለሥላሴ የእርሳቸውን ፍላጎት ያማከለ ሕገመንግስት እንዲረቅ ይሻሉ፡፡ሰርቼ
በጨረስኩ ጊዜ ንጉሱ ከባለሟሎቻቸው ራስ ካሳ፤ብላቴንጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ እየተማከሩ
የሚስማማቸውን ማሻሻያዎች ካገቡበት በኋላ ጸድቆ ተፈረመ፡፡መብትና ስልጣናቸው
በሕገመንግስቱ እውቅና ስላልተሰጠው ሰነዱን በጣም የተቃወሙት መኳንንቱ ናቸው”ሲሉ
ይጽፋሉ፡፡ተክለሐዋርያት ቆይተው ስለ ሕገመንግስቱ የሚያብራራ (ስልጣኑ በሕግ
ያልተረጋገጠ)ዲስኩር አዘጋጁ፡፡ በዲስኩሩም(በፓርላማ በማህተመሥላሴ ወልደ መስቀል የተነበበና
በዝክረ ነገር ድጋሚ የወጣ ነው)ስለ “መተካካት ህግና”ስለ ፓርላማው ስልጣን (ሕገመንግስቱ
ከሚለው በላይ እንደሚሆን“ ቃልበመግባት”)አውስተዋል፡፡ሕገመንግስቱን እንዲቀበሉ
ለማስተማመን ሲባል አንዳንድ መብቶች ለመኳንንቱ ተሰጥተዋል፡፡ ተክለሐዋርያት እንደጻፉት
ኃይለሥላሴ ህገመንግስቱ በምንም አይነት ከሳቸው በላይ እንደሆነ እንደማያምኑና “የቤተሰባቸውን
69
ጥቋቁር አናብስት
70
ጥቋቁር አናብስት
ተክለ ሐዋርያት ስለ እ.ኤ.አ 1934ቱ የወልወል ግጭት ከንጉሱ በመስማታቸው በሊጉ ውስጥ
ነገሩን በማንሳት ኢትዮጵያ ነገሩን በሰላም ለመፍታት እንደምትሻ ተናግረዋል፡፡እንግሊዝና ፈረንሳይ
ከጣልያን ጋር በማበር ኢትዮጲያ አንዳንድ ነገሮችን እንድታለሳልስና ነገሩ እንዲራዘም ለሊጉ አጀንዳ
ሳታስይዝ በሽምግልናው እንድትስማማ የመሳሰሉ ግፊቶችን አደረጉ፡፡ የሊጉ ዋና ጸሃፊ ጆሴፍ
አቬኖል፤ፒየር ላቫል እና አንቶኒ ኤደን የእንግሊዝና የፈረንሳይ የውጪ ጉዳይ ሚንስትሮች በቀጥታ
ከተክለ ሐዋርያት ጋር ተገናኙ፡፡እሳቸው በዚህ አይነት ጉዳዮች ላይ ልምድ ከማጣታቸው የተነሳ
ነገሩ ሲጓተት ጣልያን ሁኔታዋን ለማጠናከር ክፍተት ስታገኝ ኢትዮጵያ ከተጣለባት ማእቀብ አኳያ
መሳርያ ማስገባትም ሆነ ራሷን ለመከላከል አልቻለችም፡፡ ተክለ ሐዋርያት ከዚህ በኋላ “ተስፋ
ቆርጠውና ተማረው”ንጉሱን ወደ ሃገርቤት እንዲመልሷቸውና ጣልያንን በመከላከሉ ስራ ለማገዝ
ጠየቁ፡፡በጥር 1935 ወደ ሃገር ቤት እንዲመለሱ ታዘዙ፡፡ እርሳቸው እንደጻፉት ከሆነ ነገሮች
የአድዋ ጊዜ በ1988 እንደነበሩ ባለመሆናቸው ኢጣልያንም ባላት የተሻለ መሳርያ አማካኝነት ፊት
ለፊት መጋፈጥን በማስወገዷ ለመከላከል የሽምቅ፤የጋዱ፤የፋኖ(የጌርያ) ስልት ተመራጭ መሆኑን
ለዘውድ አማካሪዎች ተናግሬያለሁ ብለዋል፡፡ይህ ሃሳብ(ኢትዮጵያ ከተሸነፈች ኋላ የብዬ ነበር
ካልሆነ በቀር) አማካሪዎቹ የኢትዮጵያን መሸነፍ ይፈልጉ ይመስል ተቀባይነት አላገኘም፡፡
ግርማቸው እንደሚለው ከሆነ ጦርነቱ ሲጀመር ንጉሱ በሃገሪቷ ካሉ በከፍተኛ ደረጃ በጦርነት
ከሰለጠኑ ባለሙያዎች አንዱ ስለሆኑ አብረዋቸው ወደ ሰሜን እንዲሄዱ ፈልገው የነበረ ሲሆን
71
ጥቋቁር አናብስት
ቆይቶም ኃይለ ሥላሴ ተክለሐዋርያትን ወደ አውሮጳ መጥተው የቀድሞ የሊግ ኦፍ ኔሽንስ ክርክር
ላይ ያላቸውን እውቀት እንዲያካፍሏቸው በእውቀታቸውም እዚያ ያለውን የኢትዮጵያ አላማ
እንዲረዱ ቢልኩባቸው ተክለሐዋርያት ሃገራቸውን ለማገልገል ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተው በጅቡቲ
(ኦቦክ)ለአንድ ዓመት ተቀመጡ፡፡
72
ጥቋቁር አናብስት
***
***
ተክለ ሐዋርያት ግብርና ከንግድም ሆነ ከኢንዱስትሪ በላይ የኢትዮጵያ መሰረት ነው ብለው ያምኑ
ነበር፡፡ይህንንም ለመነን መጽሔት ከስብሃት ገብረአግዚአብሄር ጋር ባደረጉት የግንቦት 1967 ቃለ
-መጠይቃቸው ገልጸው የነበረ ሲሆን እስከ 90 አመታቸው ድረስ እርሻቸው ላይ ይሰሩ ነበር፡፡ ራስ
እምሩ ከማሞ ውድነህ ጋር በ1966 ባደረጉት ቃለመጠይቅ ተክለሐዋርያት የማይለሳለስ ተፈጥሮ
ይዘው በርካታ ጠላት ፈጥረው ከፖለቲካው ቢገለሉም “የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያንን ወደኋላ
መቅረት”ያሳዝናቸው እንደነበር አይነተኛ ፍላጎታቸውም የኢትዮጵያ አንድነት እንደነበርተናግረዋል፡
፡ተክለሐዋርያትአማርኛ፤ኦሮሚፋ፤አፋር፤ሶማሊ፤ሩስኪ፤ፈረንሳይኛ፤እንግሊዘኛ፤አረብኛና ማላጋሲ
ቋንቋዎችን ይችላሉ።
***
ግርማቸው ተክለሐዋርያት - ያደገው በ“ስነ ጽሑፋዊ ባህል” በተቃኘ ቤተሰብ ውስጥ ነበር፡፡ከአባቱ
ሌላ አጎቱ ገብረጻዲቅም26የአያቱ ወንድም (ምንአልባትም የአንድ ቤተ ክርስተያን አለቃ)የሆኑት
አብዬም ነበሩ፡፡የግርማቸው የድርሰት ዝና በሁለት መጻህፍት ህትመት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡
በአንድ ተውኔትና በአንድ ልብ ወለድ ላይ፡፡በተለይ ልብ ወለዱ በከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት
ቤቶች እንደ አማርኛ ማስተማርያ ተደርጎ ከ 1966 አብዮት በፊት ይቆጠር ስለነበር ተጽእኖው
ይጎላል፡፡በሕይወቱ የመጨረሻ ጊዜያት ግርማቸው እስከ ዛሬ ከሰራቸው በጥራትም ሆነ በብዛት
ይበልጥ በተሻለ ለመጻፍ እንደሚመኝ ነግሮኝ ነበር፡፡የራሱን ስራዎች ጨምሮ ለአማርኛ ስነ ጽሑፍ
ያለው አመለካከት እምብዛም ነው፡፡
***
ግርማቸው ተክለሐዋርያት የተወለደው ሂርና ውስጥ ህዳር 21 1915 ሲሆን አድጎ ለትምህርት
ወደ ድሬዳዋ እስከሚሄድበት የዘጠኝ አመት እድሜው ድረስ እዛው ቆይቷል፡፡አባቱ ተክለሐዋርያት
ከመጀመርያ ወንድ ልጃቸው ብዙ ስለሚጠብቁ ይመስላል ግርማቸው በልጅ አእምሮው
ሲያስታውሳቸው ቆፍጣና፤ሀይለኛ፤ለልጅ ጭንቅላቱ የሚከብድ የጭቆና ቀንበር እንደጫኑበት ሆኖ
ይሰማዋል፡፡ይሄ በአባትና ልጅ መሃል ምንአልባት እድሜ ልካቸውን የዘለቀ ቅራኔ ያስነሳ
ይመስላል።ምንአልባትም ግርማቸው የሟች አባቱን መልካም ዝና ለማናኘት ደፋ ቀና ቢልም ይሄ
ቅሬታ ግን ፈጽሞ የተፋቀለት አይመስልም፡፡ከሌሎች ጋር ሲሆን ተግባቢና ጨዋታ ወዳድ
ቢመስልም የአባቱ ጥብቅነት እሳቸው ባሉበት ቦታ አይናፋር እንዲሆን አስገድዶታል፡፡ከሌሎች
ሰዎች ጋር ግን ቀጥተኛና ሃይለኛ አንዳንዴም ምንአልባትም ከአባቱ የወረሰው የግትርነት ባሕርይ
ይታይበታል፡፡ተክለሐዋርያት የሚታወቁት በጭምትነት ሲሆን ግርማቸው ግን ቀልደኛና ተጫዋች
ነበር፡፡ ²⁷ሃይለኝነቱና ጠበኝነቱ ከአባቱ ጨቋኝ ባሕርይ የተነሳ የመጣ የቅሬታው መግለጫ ሊሆን
75
ጥቋቁር አናብስት
ከማህተመ ስላሴ ታደሰ የተዋስኩት መጣጥፍ ግርማቸው ትምህርቱን በ1924 ዓ.ም ሲጨርስ
ያቀናው አባቱ ጉዳይ አስፈጻሚ ሆነው ወደሚያገለግሉበት በፓሪስ የኢትዮጵያ ኤምባሲነው፡፡
የተክለሐዋርያት ግለ ታሪክ የሄዱት በአምባሳደርነት ነው ያስቀምጣል፡፡በፈረንሳይ ሳለም
በስታኒስላስ²⁸ ትምህርተ መለኮት በማጥናት የባችለር ድግሪ (ባካሎርያ)አግኝቷል፡፡ የሚወዳቸውና
የሚልቅባቸው የትምህርት አይነቶች ግን ፈረንሳይኛ ቋንቋና ስነጽሑፍ ነበሩ፡፡”ኃይለሥላሴ ሁለት
(የወርቅ ሜዳልያ)ለጥረቴ እና ኣካዴሚክ ውጤታማነቴ አበርክተውልኝ ነበር፡፡የተለያዩ
መጣጥፎችን መጻፍ የጀመርሁት በዛን ወቅት ነው የሕይወት ታሪኬንም እንዲሁ (በዛ የልጅነት
ወቅት የቀን ውሎ ማስታወሻዎቹን ሳይሆን አይቀርም)”ሲል ይናገራል ግርማቸው፡፡
ግርማቸው ወደ ደሴ²9 ንጉሱን ተከትሎ ቢዘምትም ገና የ20 ዓመት ልጅ ነው ተብሎ ከአልጋ ወራሽ
መርእድ አዝማች አስፋ ወሰን ጋር ንጉሱ መልሰውታል፡፡ከመመለሱ በፊት ለ3 ወራት ለስዊድናዊው
የጦር አሰልጣኝ በአስተርጓሚነት አግልግሏል፡፡ጣልያኖች ጦርነቱን አሸንፈው አዲስ አበባን
ሲቆጣጠሩ ግርማቸው ጅቡቲ አባቱ ዘንድ ሄደ፡፡እዚያም ብዙም አልቆየም፡፡ከሙቀቱ አንጻር
76
ጥቋቁር አናብስት
ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ ብዙም አልቆየ ሞገስ አስገዶምና አብርሃ ደቦጭ የካቲት 12 ቀን በግራዝያኒ
ላይ ቦምብ ጥለው ስላቆሰሉት በዚህ ምክንያት በተደረገው አሰሳ ተይዞ ወደ ጣልያን ለ7 አመታት
ግዞት ተላከ፡፡ይህም ከኢትዮ-ኢጣልያ ግጭት በላይ ለሆነ ጊዜ ሲሆን መጀመርያ በሰሜን ሳርዲንያ
አሲናራ ቆየ ፤ቀጥሎ በሃዲስ አለማየሁ ጥያቄ መጥቶ ራስ እምሩን ጨምሮ ሶስቱ በሊፓሪ የሚገኝ
በመሃከለኛው ዘመን በመስቀል ጦረኞች በተሰራ የግምብ ቤት አብረው ተቀመጡ፡፡³¹
ከጥቂት አመታት በኋላ ወደ ትንሽ ካላብርያ ወደ ምትባል መንደር ተወስደው በአንድ ሳጅንና በ10
ወታደሮች እየተጠበቁ ነጻነት በሌለበት ሁኔታ ተቀመጡ። በሊፓሪ ውደ ውጭ መውጣት
ባይፈቀድላቸውም ቢያንስ በግምብ ቤቱ ውስጥ ለመንቀሳቀስ ይፈቀድላቸዋል፡፡እዚህ አዲሱ
መንደር ላይ ግን እንደዚህ አይነት ነጻነት አይሰጣቸውም፡፡³²
ጣልያን ከኢትዮጵያ ከወጣ ከብዙ ቆይታ በኋላ ጣልያን ውስጥ በነበረው በ(ጄኔራል ዊልሰን
በሚታዘዝና በሞንት ጎምሪ በሚመራው የ8ኛው የብሪታንያ ጦር)ነጻ እንደወጣ ግርማቸው
ያስታውሳል፡፡ወደ ኢትዮጵያ በሰሜን አፍሪካ በካይሮ በምጽዋ አድርጎ አስመራ ሲደርስ
በአውቶቢስ ወደ አዲስ አበባ ተወሰደ፡፡ይህ የሆነው ጣልያን ከኢትዮጵያ ከተባረረች ከ2 ዓመት
በኋላ በ1935 አ.ም ነው፡፡
***
ከግዞት ከተመለሰ በኋላ የኢትዮጵያን መንግስት እስከ 1966ቱ የመንግስት ግልበጣ ድረስ
አገልግሏል፡፡ የመጀመርያ ስራው በግዜው ትልቅ ስልጣን በሆነው ጋዜጦችና በመረጃ ቢሮ ውስጥ
በድሬክተር ጄኔራልነት ነበር፡፡በነዛ ቀናት ጋዜጦቹ ውስን ሲሆኑ የሚወጡት በሳምንት አንዴ
የሚያነባቸውም ሰው ጥቂት ነበር፡፡ይህ ቢሮ ከጊዜ በኋላ በውጭ ጉዳይ ስር ሆኖ የዜና
77
ጥቋቁር አናብስት
ሪፖርተሮችም በዋና ዋና የክፍለ ሃገር ከተሞች ለዜና ዘገባ ተልከዋል፡፡ በተጨማሪም ሬድዮ
ፕሮግራሞቹን ለማሻሻል ጥረቶች ይደረጉ ነበር፡፡ በ1937 ዓ.ም ግርማቸው በውጪ ጉዳይ
ሚኒስቴር የአውሮጳ ቢሮ ዳይሬክተር ሆኖ ተሾመ፡፡
ግርማቸው እንደ አባቱ ብርቱ ሰራተኛ ቢሆንም ቅንጦትና ምቾትን ስለሚወድ በኢሉባቡር ቆይታው
“ተሰቃይቷል”፡፡³³
ግርማቸው በመቀጠል የእርሻ ሚኒስትር ሆነ፡፡ 1958-1960 ዓ.ም ኋላቀሩን ባህላዊ ዘዴዎችን
የሚጠቀመውን(አሁንም ይጠቀማል) ግብርና ለማሻሻል ጠንክሮ ሰራ፡፡ ³4
በመቀጠል የጤና ሚኒስትር በመሆን ከ1960-1962 ዓ.ም ለሁለት አመታት ሲሰራ ሃምሳ አዳዲስ
ክሊኒኮች ሲያስገነባ የነጻ ህክምናንም ለማስተዋወቅ ጥረት አድርጓል፡፡
***
78
ጥቋቁር አናብስት
ከግዞት ተመልሶ ብዙም ሳይቆይ ግርማቸው በ1938 ዓ.ም በአባቱ መልካም ፍቃድ እሱም
ተስማምቶበት ሽማግሌዎችን በባህሉ መሰረት በመላክ ወ/ሮ ምንትዋብ ሃይለሚካኤልን አገባ፡፡
(ጋብቻ የሃገር መሰረት ነው ብሎ ያምናል)ስኬታማ ያልሆነ ትዳርም እንዲሁ የትዳርን አባላትንም
ሆነ ሃገርን ይጎዳል ሲል ያምን ነበር፡፡ቤተሰቦቹ እሱ በሚፈልገው ሁኔታ አቻው የሆነች ሴትን
ስላጩለትና ስለዳሩት ደስተኛ ነበር፡፡ትዳርን ያህል ውስብስብ ነገርን በዚህ መልኩ በመፈጸሙ
ይደሰታል፡፡መልካም ባሕርይን ከተላበሰችው ባለቤቱም ጋር በጋራ አምስት ልጆችን አፍርተዋል፡፡
በለጥሻቸው፤(ከተጋቡ ከሶስት ዓመት በኋላ) ዘውዴ፤ወንዱ፤ጉስታቭ(ግርማቸው በስዊድን
የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ ሆኖ በተሾመ ቀን ስለተወለደ በስዊድን ንጉስ ስም የተጠራ)
እና መቅደላ ናቸው(ግርማቸው የንጉስ ቴዎድሮስን ለማስታወስ ነው ቢልም የእህቱ ባል የሆነው
ሚካኤል እምሩ ግን የመጽሐፍ ቅዱሷን ማርያም መቅደላዊትን ተከትሎ የተሰጠ ነው ይላል)፡፡
ግርማቸው ልጆቼን መትቼም ሆነ ተቆጥቻቸው አላውቅም ይላል፡፡መልካም ዜጎች እንዲሆኑለት
ይልቁን በምሳሌ ማስተማር እንደሚሻል ሚስቱንና ልጆቹን በጣም እንደሚወድ (ልጆቹም
እንደሚያከብሩት እንጂ እንደማይፈሩት ስሙን ሲጠሩትም በአማርኛ የ(የ እንግሊዘኛው´ዳዲ´አቻ
ቃል ተጠቅመው) እንደሆነ ይናገራል ሚስቱም በሌጣው ስሙ ብቻ ነው የምትጠራው።ይህም በሱ
ደረጃ ላሉ ሰዎች ያልተለመደ ነው።³5እሱም በቁልምጫ ስም ነበር የሚጠራት።ግርማቸው ልጆቹ
ለሃገራቸው ጠቃሚ እንዲሆኑ ለፈርጀ ብዙ ችግሮቿም መፍትሄ በማፈላጉ እንዲረዷት ይመኛል፡፡
³6
ወጣቱ ግርማቸው ስፖርት ይወድ ነበር፡፡ በአብዛኛው በንጉሳውያኑ ዘንድ ተወዳጅ የሆኑትን አደን፤
ግልቢያ ፤ገናና፤ኳስ ጨዋታ ወደኋላ ላይም ቤተሰቦቹን ይዞ ለበአል ከአዲስ አበባ ወጣ ወዳሉ
መናፈሻዎች ይሄዳል፡፡ በአትክልት ስፍራውን በመንከባከብ ራሱን በስራ መጥመድ ስለሚወድም
"ጥቂት ጓደኞች" ብቻ ነበሩት፡፡³7ለዋሾ፣ለቀጣፊ፣ለሰነፍ፣ለስስታም ሰዎች ትእግስት አልነበረውም፡፡
በተጨማሪም የራሳቸው (ፍልስፍና) የሌላቸውን (ፍልስፍና ሲል ለማለት የፈለገው የራሳቸው
አቋም ለማለት ይመስላል) ይጠላ ነበር።ከልጅነቱ ጀምሮ "መምራት "ነው እንጂ "መከተልን"
አይወድም፡፡ አብሯቸው የሰራ የስራ ጉዋዶቹ ብርቱ፤ሰው የሚረዳና ሩህሩህ ሲሆን ሰዎች የመንፈስ
ልዕልና እንዳለው ይመሰክራሉ፡፡ግርማቸው ከቀልደኛነቱ የተነሳ ሰዎች ቻርሊ ቻፕሊን³8 ሲሉ
ይጠሩት ነበር፡፡የዛኑ ያህልም የበታቾቹ እንዲታዘዙት ይጠብቃል፡፡ያሰበውን በነጻነት የሚናገር
ቀጥተኛ ሰው ነበር፡፡ከእርሱ ጋር በማስታወቅያ ሚንስትር አብረውት የሰሩት ሰዎች በፍቅር
የሚያስታውሱትና (በቅርቡ አመታት ከመጡ ምርጡ የማስታወቅያ ሚኒስትር የሚሉት )ሰው ነው፡
79
ጥቋቁር አናብስት
፡ሰራተኞች በስራ ሰአት ለስራ ካልወጡ በስተቀር በቢሯቸው ውስጥ እንዲገኙ ይፈልጋል፡፡ይሄ
ደግሞ በኢትዮጵያ ያልተለመደ ነው፡፡
***
80
ጥቋቁር አናብስት
እንደ እሱ አስተሳሰብ አንድ ደራሲ የሞራል ግዴታዎች ያሉበት ሲሆን ለሃገሩና ለህዝቡ ጠቃሚ
ነው ያለውን መጻፍ፤ጎጂ ነው የሚለውን ደግሞ ማስወገድ ይገባዋል፡፡ሳንሱሩም ቢሆን በጊዜ ሂደት
እየላላ ይምጣ እንጂ አስፈላጊ ነው ባይ ነው፡፡ የፈረንሳይ ባህልና ታሪክን ያደንቃል፡፡ ከፈረንሳይ ስለ
ነጻነት እኩልነት ወዘተ የሚሰነዘሩ የተራማጅ እና የቡርዡዋ በርካታ ሃሳቦችን አምጥቷል፡፡ ከነዚህ
ውስጥ የተወሰኑት በአርአያ ተንጸባርቀዋል፡፡ለባህሉ ያለው ስሜትና መኖርያ ቤቱ ሳይቀር ከፈረንሳይ
እና ከተቀረው አውሮጳ ጋር ያለውን ቁርኝት ያሳብቃሉ፡፡
ባይታደልም በመስከረም 1980 ግርማቸው ከህመሙ አገግሞ ስለ መጻፍ ያስብ ነበር፡፡ ጽሑፉ
በኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍ ውስጥ የራሱን አሻራ ትቶ አልፏል ፡፡በደራሲነቱም ከፍተኛ አስተዋጽኦን
ካደረጉ ቀደምት የአማርኛ የልብወለድ ጸሐፍት ስር ይጠቃለላል፡፡
***
የግርማቸው ቴዎድሮስ ቴአትር መጀመርያ በመዘጋጃ ቤት ውስጥ በ1939 አ.ም ለመድረክ በቃ፡፡
ቴዎድሮስን ወክሎ የሚጫወተው መኮንን አበበ ሲሆን በቴዎድሮስ 120ኛ የሙት ዓመት
መታሰብያ እ.ኤ.አ ሚያዝያ 14 1988 በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ያለው ራስ መኮንን አዳራሽ
አግኝቼው እንደነገረኝ ወደገነተ ልኡል ተዘዋውሮ በሚመደረክበት ወቅት ንጉሱና መኳንንቱ
በተገኙበት ሊታይ በቅቷል፡፡በመቀጠልም ወደ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ቴአትር(ያሁኑብሔራዊ)
ቴአትር ተዘዋውሯል፡፡በመጀመርያ አካባቢ በተደጋጋሚ ቢታይም በቀጣዮቹ አመታት ለአጫጭር
ግዜያት በየአመቱ ይታይ ነበር፡፡የመጨረሻው ግዜ በ1952 በመፈንቅለ መንግስቱ አካባቢ ነው፡፡
በክፍላተሃገራት በበጌምድር፤ ትግራይ፤በወሎ፤በሃረርጌ፤እስከ ጂጂጋ ድረስም ታይቷል፡፡ከቴዎድሮስ
120 ዓመት የሞት መታሰቢያ ጋር በማገናኘት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ባህል አዳራሽ ለመድረክ
81
ጥቋቁር አናብስት
የተርጓሚ ማስታወሻ
ዓ.ም ታትሞ የወጣ ሲሆን በዚህ መድብል ከተጻፉ ታሪኮች ጋር በተወሰኑ ቦታዎች ላይ ልዩነት
አግኝተንባቸዋል፡፡
1----
፟ ተክለ ዋዬህ ሳይሆን በግለ ታሪካቸው ተክለ አብዬ ነው የሚለው ገጽ 111
2----
፟ በ1922 ዓ.ም በ179 ገጾች ለህትመት በቅቷል ኦቶባዮግራፊ ገጽ 395
3-----
፟ ባለ አንድ ፎቅ ቤት በፍልውሃ አካባ ባለ መሬታቸው ላይ ሰርተው እንደተቀመጡ ይናገራሉ
ገጽ 401
4-----
፟ ወደ ድሬ ዳዋ በሄዱበት ወቅት ሞልቪየር የሚለው መሬታቸውን አደራ ያሉ እነደሆነ ነው፤
በእርሳቸው ኦቶባዮግራፊ ላይ ግን ንብረትና ሀብታቸውን ወታደሮቻቸው እንዲወስዱ መናገራቸው
ተጽፏል፡፡ መግቢያ xxvi
ማስታወሻ
2)ቀኑ ያከራክራል፡፡ የህሩይ ወልደ ስላሴ ወዳጄ ልቤ ከዚያ በፊት ተጽፎ ነበርና የተክለሐዋርያት
ተውኔት ያህል በተውኔትነት ሊወሰድ ይችላል፡፡
82
ጥቋቁር አናብስት
ነበር ይላሉ፡፡ ለዚህ አይነት ጠቃሚ ላልሆነ ቦታ ያልተለመደ ቢሆንም፡፡ (ምንአልባት ተፈሪ በታላቅ
ወንድምነት ሊረዷቸው አስበው ይሆናል)
5)ሃረርጌና ሃረር በአጼ ምኒሊክ ነበር የተያዙት፡፡ (ወይም በራስ መኮንን ለምንሊክ ) እ.ኤ.አ
በ1887 መስከረም ላይ
12)የዚህ አይነት ስነጽሀፍ ለመጻፍ የመጀመርያ የመሆን ፍላጎት አድሮባቸው ሊሆን ይችላል፡፡
ወይም እያሱ ከስልጣን ሲወርዱ መክሬው ነበር ለማለትም ሊሆን ይችላል፡፡
15)ይህ እያሱ በጊዜው ለምን እንደወረዱ የተነሳውን ክርክር መልሶ የሚያሳይ ይሆናል፡፡ በ1916
እያሱን ከስልጣን ለማስወገድ የህዝቡንና የቤተክህነትን ሰዎች ድጋፍ ማግኘት ነበረባቸው፡፡ ክሶቹ
ቢጋነኑም የመፈንቅለ መንግስቱ መሪዎች ስም እና ቀናቱ ግን ትክክለኛ አይመስሉም፡፡
21)የእያሱ ልጅ መልአከ ጸሃይ በጦርነቱ ወቅት በንግስና ተቀብቶ ነበር፡፡ ነገር ግን ከበአለ ሲመቱ
ከአንድ ዓመት አለፍ እንዳለ ሊሞት በቅቷል፡፡ (በኃይለሥላሴ ወኪሎች ተገድሎ ነው ሲሉ ብዙዎች
ያምናሉ)፡፡
84
ጥቋቁር አናብስት
23)ይሄ ለእሳቸው አሳፋሪ መሆን አለበት፡፡ እንደ ግርማቸው አባባል ከሆነ ጅቡቲ አብረው
በነበሩበት ወቅት ግርማቸው እንዲታከም ሳይፈቅዱ ቀርተዋል፡፡ በተክለሐዋርያት እምቢታ የመጣ
ግርማቸው ወደ አዲስ አበባ ሊመለሱ ችለዋል፡፡ እዚም ሲደርሱ በኢጣልያኖች ተይዘው ለ7 ዓመት
ግዞት ወደ ኢጣልያ ተልከዋል፡፡
24)ከልጆቻቸው አንዱ ማደጋስካር የነበረ ሲሆን እዚያው ቀርቷል፡፡ የማደጋስካር ዜግነት ወስዶ
ማላጋሲ ሚስት አግብቶ በገበሬነት ይኖር ነበር፡፡ ቢያንስ እስከ ጎሪጎሮሳውያን 1988 ድረስ፡፡
26)የቤተ ክህነት ትምህርት ነበር የተማረው፡፡ ለቤተክህነት ሰዎች እድሜ ልካቸውን በማንበብ
በቃል በመያዝና በመድገም ለሚማሩት ያልተለመደ ነው) በባህላዊው ዘመን እንደ ባለቅኔ ነበረ፡፡
30)ግርማቸው ከአባቱ ጋር የነበረውን ግንኙነት ያማርሩ የነበር ሲሆን በተቻለ ከራሱ ልጆች ጋር
ያለውን ግንኙነት ጥሩ እንዲሆንና እሱ ከአባቱ ጋር የነበረው አይነት በጥላቻ የተሞላ እንዳይሆን
ይጥር ነበር፡፡ቤተሰብ ሲመሰርት ለጤናና ትምህርታቸው ትኩረት ሰጥተው በፍቅር ላይ የተመሰረተ
85
ጥቋቁር አናብስት
31)ግርማቸው ስለዝውውሩ መራር ስሜት ይሰማው የነበር ሲሆን ሃዲስ አለማየሁን ለዚህ ጉዳይ
ይወነጅላል፡፡
33)በአዲስ አበባ ያለው ቤታቸውን ጎብኝቼው የነበር ሲሆን ጥሩና ምቹ ነው፡፡ መናፈሻው በአበባና
እጽዋት ያጌጠ ሲሆን ሳሎኑ በጥሩ እቃዎች ያመረ አውሮጳዊ ዘዬን ተከትሎ የተጌጠ ነው፡፡ በእንግዳ
ክፍሉ እንደ ጎበኘሁት እንደሌሎች የኢትዮጵያ ታላላቅ ሰዎች ቤት ሳይሆን አንዳችም ኢትዮጵያዊ
የእደጥበብም ውጠትም ሆነ ቁሳቁስ አላየሁም ፡፡
34)ምንም እንኳን ማረሻ ለብዙ ክፍለዘመናት በኢትዮጵያ ከሰሃራ በታች ካሉት ሃገራት በላይ
ለረጅም ጊዜ ጥቅም ላይ ቢውልም አሁንም ተራ ስሪት ያለው ነው
37)ከነሱ መሃል አንዱ ጄኔራል አብይ አበበ ነበሩ(ልዕልት ጸሃይን ያገቡ ሲሆን እሳቸው በ1948
ሲሞቱ ለረዥም ጊዜ የጦር ሚኒስትር የነበሩት የሴኔቱ ፕሬዝደንት እና በተለያዩ ቦታዎች ተሹመው
የነበሩትና በደርጉ ህዳር 23 ቀን 1974 ዓ.ም የተገደሉት የደጃዝማች ነሲቡን ልጅ አማረችን አገቡ)
38)አጭር ተክለ ሰውነቱ የአባቱን ያህል ባያጥርም ቅጽል ስሙን ተገቢ ያደርገዋል
86
ጥቋቁር አናብስት
87
ጥቋቁር አናብስት
በእምነት ገብረአምላክ
ብስጭት ምኞቱን በአጭር የቀጨበት ደራሲ በእምነት ገብረአምላክ
በ1967ዓ.ም ሲሞት፣በኢትዮጵያ ውስጥ ነበርኩ። ነገር ግን የመተዋወቅ
እድሉ አልገጠመኝም። በዚያን ወቅት የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች አማርኛ
የሚማሩበትን"ልጅነት ተመልሶ አይመጣም" የሚለውን መጽሐፉን እዚህም
እዚያም አየው ነበር። ነገር ግን ወዲያውኑ አላነበብኩትም። ይህ መጽሀፍ
በተለይ ለኢትዮጵያውያን ተብለው ከተጻፉ መጽሐፍት መሀል ያነበብኩት
የመጀመሪያው መጽሀፍ ነው። ለውጪ ሀገር ሰዎች አማርኛ ማስተማሪያ ተብለው የሚዘጋጁ
መጻሕፍት፣ ጋዜጣ እና መጽሄትን ከማንበብ አንድ ደረጃ ከፍ ብዬ "ሥነ ጽሑፍ" ወደ ማንበብ
ያደግኩበት አጋጣሚ ነው ። ነገር ግን በ1950ዎቹ መጀመሪያበአንድ የፕሮቴስታንት ቄስ እጅ
በጥብቅ ክርስቲያናዊ ስርአት አድጎ በገዛ እጁ ሕይወቱን ስላጠፋ አንድ ደራሲ አዲስአበባ ውስጥ
ሰዉየሚቀባበላቸውን አሉባልታዎች ሰምቼያለሁ።1
በእምነት ገብረአምላክ በኤርትራ ሐማሴን ውስጥ አማድር በምትባል መንደር ወይም በአቅራቢያ
በምትገኝ አዲ ኡግሪበተባለች ከተማ በጥቅምት 16 1913 ዓ.ም ተወለደ። አባቱ አማድርን
የለቀቁት በዚህ ጊዜ አካባቢ ነው። አቶ ገብረአምላክ ሩፋኤል እና ወይዘሮ ጋብሬላ ወልደአብ እዝጊ
ከወለዷቸው አስራ ሁለት ልጆች መሀል በእምነት ሁለተኛ ልጅ ነው። የመጀመሪያ አምስቱ ልጆች
ሁሉም ወንዶች ሲሆኑ የተወለዱት ኤርትራ ውስጥ ነው፣ የተቀሩት (ሶስቱ ሴቶች ናቸው)
የተወለዱት አዲስአበባ ነው።4 ገብረአምላክ ድሀ ገበሬ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ቤተክርስቲያን ቄስ ነበሩ።5 ልጆቻቸውን ለማሳደግና ለማስተማር ያሉበት አካባቢ ብዙም
ስለማይመች፣ የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ወደ አዲስአበባ ለመሄድ ወሰኑ። መጀመሪያ ለብቻቸው ሄደው ስራ
ከያዙ በኋላ ለሚስታቸው ሃብት፣ ንብረታቸውን (እርሻ እና ከብቶቹን) ሸጠው፣ ልጆቻቸውን
88
ጥቋቁር አናብስት
ይዘው እንዲመጡ መልእክት ላኩባቸው። በቃ ካሁን በኋላ ቤታቸው አዲስአበባ ሊሆን ነው።
ገብረአምላክ ሩፋኤል ከዚህ አለም በሞት የተለዩት በ1977 ዓ.ም ነበር።ከመጠን ያለፈ
በእምነት የተወለደው ገጠር ውስጥ ሲሆን ልጅነቱንም ያሳለፈው እዚያ ነው፣ ትምህርት የጀመረው
ግን ወደ አዲስአበባ ከመጣ በኋላ ነው። አዲስአበባ ከመጡ ወዲህ አባቱ በተፈሪ መኮንን ትምህርት
ቤት የግብረገብ መምህር ሆኑ። ነገር ግን ከትንሽ ጊዜ በኋላ በአንድ የስዊድን ሚሲዮን ውስጥ
ፓስተር ወይም ሰባኪ ሆኑ። አንደኛው ልጃቸው እንደነገረኝ ኤርትራ እያሉም ከነዚህ የስዊድኖች
ሚስዮን ወይም ቤተክርስቲያን ጋር ቅርበት ነበራቸው።በዚሁ መሰረት በአምላክ፣ምናልባትም
ከሚማርበት የዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት ወጥቶ ከታላቅ ወንድሙ እና ከሁለት ታናናሾቹ ጋር
በሚስዮኑ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገባ።ነገር ግን ከሶስት ዓመት በኋላ ኢጣሊያ ኢትዮጵያን
በመውረሯ ትምህርት ቤቱ ተዘጋ።በወረራው ወቅት ትምህርታቸውን በቤት ውስጥ ቀጠሉ ፤
እህታቸው እንደነገረችኝ ልጆቹ ለማወቅና ለማንበብ ጉጉ ስለነበሩ ለማጥናት ብዙም ገፋፊ
አያስፈልጋቸውም ነበር። ነገር ግን ከትንሽ ጊዜ በኋላ በእምነት ራስ ደስታ ሆስፒታል አቅራቢያ
ከሚገኘው የኢጣሊያ ኮንሶላታ ትምህርት ቤት ገባ፤በመጀመሪያ ግን ኢጣሊያንኛ ቋንቋ መማር
ነበረበት። በዚህ ትምህርት ቤት ለሶስት ዓመት ከተማረ በኋላ ትምህርቱን ለማቋረጥ ተገደደ ፤
ምክንያቱም ይሄንን ትልቅ ቤተሰብ ለማስተዳደር ስራ ይዞ አባቱን ማገዝ ነበረበት። ለአንድ
ጣሊያናዊ ፎቶ አንሺ ተቀጠረና ስለ ፎቶ ማንሳት ጥበብ ተማረ።
የኢጣሊያ ወረራ በ1933 ዓ.ም ካበቃ በኋላ፣ በእምነት በአዲስ አበባ የፖሊስ ሀይልን ተቀላቅሎ
ለስድስት ዓመት ሰራ፤እስከ ሻምበልነት ማዕረግም ደርሷል። ከፖሊስ ሀይል እንደለቀቀ በ1939
ዓ.ም ለተጨማሪ ትምህርት ወደ ሰሜን አሜሪካ አቀና።ነገር ግን የነብራስካ አየር ሁኔታ
ስላልተስማማው ታመመ።ዶክተሩም ወደ ሀገሩ ቢመለስ እንደሚሻል ነገረው፤እንደተመከረው
በሰሜን አሜሪካ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ለአንድ ዓመት ብቻ ከተከታተለ በኋላ ወደ ሀገሩ
መጣ። በ1940 ዓ.ም በብሔራዊ ቤተመፃህፍት (ከብሔራዊ ሙዝየም ጋር የተያያዘ) ውስጥ
መስራት ጀመሮ ለአምስት ዓመታት ቆየ። ቀጥሎ አስመራ ውስጥ በሚገኘው ባህር ሀይል አገናኝ
መኮንን ሆኖ ለአምስት ዓመት ሰራ። ከዚህም ለቀቀና የላይብረሪ ሳይንስ ለመማር ወደ
አውስትራሊያ ሄደ። ይሄ የሆነው በ1950 ዓ.ም ነበር። አውስትራሊያ ለሁለት ዓመት ቆይቶ
ሲመለስ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ገባ። በዛም አማርኛን በዋነኛነት ተማረ። ከዛ ለአምስት
ዓመታት አማርኛ እያስተማረ፣ ማታ ማታ ደግሞ ይማራል። እንደገና ደርቦ ቤተመፃሕፍት ውስጥ
ቀን ቀን ይሰራል። ቤተሰብ ስለመሰረተ ይህ ሁሉ ጫና ከብዶት ነበር።
89
ጥቋቁር አናብስት
ትዳር የመሰረተው ጥር 7 1942 ዓ.ም ሲሆን ባለቤቱ ውህበት ተወልደብርሃን (ራሷን ውቢት ብላ
መጥራት ትወዳለች)ትባላለች።ሶስት ወንዶችና ሁለት ሴቶች ልጆች ስለወለዱ፣ ልጅ ማሳደግና
ቤተሰቡን በአግባቡ ማስተዳደር ይጠበቅበት ነበር። ሚስቱ የቤት ውስጥ ስራ እና ልጅ ማሳደግ
እንዲያው በአጠቃላይ የቤተሰብ ሕይወት አትወድም ብለው የሱ ቤተሰቦች ያስባሉ። ስለዚህ
በእምነት ከማንኛውም አባወራ በበለጠ ብዙ ሃላፊነት መሸከም ነበረበት። የሆነው ሆኖ በእምነት
ትምህርቱ ላይ ጎበዝ ነው። በ1958 ዓ.ም በማዕረግ ሲመረቅ ከመጠን በላይ ተደሰተ። በኢትዮጵያ
ቋንቋዎች እና ሥነ ጽሑፍ የትምህርት ክፍል ያገኘው የመጀመሪያ ዲግሪ በፈጠረለት ደስታ የተነሳ
ያን ሌት እንቅልፍ ባይኑ ዝር ሳይል እንዳደረ ቤተሰቦቹ ያስታውሳሉ።
ነገር ግን ሁለተኛ ዲግሪ የመያዙ ነገር ሳይሳካ ቀረ። በሰሜን አሜሪካ አንድ ዓመት እንኳን
ሳይሞላው በተፈጠረ የቤተሰብ ችግር ምክንያት ልጆቹን ለማሳደግ ወደ ሀገር ቤት ተመለሰ።
እንደተነገረኝ ከሆነ ሚስቱ ልጆቹን ለብቻዋ ማሳደግ አልቻለችም ወይም አልፈለገችም። ስለዚህ
በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ትምህርቱን ሊቀጥል የሚችልበት መንገድ አልነበረም። በሕይወቱ ውስጥ
ሊያሳካቸው ከሚፈልጋቸው ነገሮች መሀል አንዱ በመምከኑ ድብርት ውስጥ ወደቀ። ይህ
“ውድቀት”፣ከቤተሰብ ችግሮቹ ጋር ተደራርቦ ከአቅሙ በላይ ሆነበት፤ ከዚህ በላይ ሊሸከመውም
አልቻለም። ስለዚህ በህዳር 19 1960 ገና በ47 ዓመቱ ሕይወቱን በገዛ እጁ አጠፋ። አዲስ አበባ
ጉለሌ ውስጥ በሚገኘው የቅዱስ ጳውሎስ እና የቅዱስ ጴጥሮስ (ጳውሎስ ወጴጥሮስ)
የፕሮቴስታንቶች የመቃብር ስፍራ ተቀበረ። ለቤተሰቦቹ ሕይወቱ በዚህ ዐይነት መንገድ ማለፉን
መቀበል ከባድ ሆኖባቸዋል።በሰንበት እስከ መስበክ የደረሰ "ጥሩ ክርስቲያን" ነበር ፤ ደግሞም እንደ
እህትና ወንድሞቹ ብሩህ አእምሮ እንደነበረው ተነግሮኛል።
***
ከላይ የተጠቀሱት መጽሐፍትን ካዘጋጀ በኋላ በእምነት እረፍት ቢጤ ወሰደ። ከዚያ መልስ የሉዊጂ
ፒራንዴሎ ስራዎችን ተረጎመ፤ይህ መጽሀፍ የታተመው በ1960 ከተርጓሚው ሞት በኋላ ሲሆን
አሳታሚው የኢጣሊያ ባህል ተቋም ነው።ሌሎች ስራዎቹን በተመለከተ በ1955 ዓ.ም በታተመው
በ"The Ethiopian Observer" ቁጥር ሶስት፣ ቅጽ ሁለት ላይ በታተመ "Foreign
Borrowings in Amharic" የተሰኘ መጣጥፍ የአማርኛ ቋንቋ እድገት ላይ ለመስራት ትልቅ
ፍላጎት እንደነበረው ያሳያል።
በእምነት መጽሐፍቱን በሚጽፍበት ወቅት ጠንክሮ ስለሚሰራ፣ ሲታተሙ የድካሙን ውጤት ማየት
በጣም ደስ ይለዋል። ለመጽሐፍቱም ሆነ ለሕይወት ጠቃሚ የሆኑ ሃሳቦችን የሚያገኘው
ከመጽሐፍት በመሆኑ፣ ሰዎች እንዲያነቡ ዘወትር ይመክራል። ሰዎች ግን “በራሳችን ጊዜና ሕይወት
ስለምናደርገው ነገር አያገባህም ”ብለው እንደሚመልሱለት ተነግሮኛል። እሱም ራሱ፣ በሕይወት
ዘመኑ በርካታ መጻሕፍትን የሰበሰበ ሲሆን፣ ለሰበሰባቸው መጽሐፍት ትልቅ ቦታ ይሰጥ ነበር።
ጥልቅ ምኞት ስላለው፣ ጠንካራ ሰራተኛ ስለሆነ፣ ሀሳባዊነት ስለሚያጠቃው፣ ምናልባት ደግሞ
ጥብቅ አስተዳደግ ስለነበረው ሳይሆን አይቀርም ሽንፈትንና ውድቀትን መቀበል ይከብደው ነበር።
በመጨረሻ ከሕይወት ቤት በገዛ እጁ ሕይወቱን በማጥፋት ወጣ። ነገር ግን ወደ መጨረሻ አካባቢ
ጭንቅላቱ በትክክል መስራቱ አጠራጣሪ ነው ይላሉ ቤተሰቦችና ወዳጆቹ ፦ ልጆቹን ለመንከባከብ
ሲል ስራውን አደጋ ላይ ጥሎ ትምህርቱን ከአሜሪካ አቋርጦ የተመለሰ ሰው፣ እንዴት ሕይወቱን
በማጥፋት ልጆቹን ያለ አባት ያስቀራል?
ከ1966 ዓ.ም አብዮት በፊት በመላው ኢትዮጵያ በስፋት የተሰራጨው አንድ ልብወለዱ አንድዬ
ትውልድ ላይ ተጽዕኖ ሳያሳርፍ አይቀርም፤ በእርግጥ ይህ ልብወለድ አሁን አንባቢ የለውም።
ከ1966 በኋላ ታትሞ አያውቅም፤ ከዚህ ወዲህም ላይታተም ይችላል። ነገር ግን መጽሐፉ አሁንም
በጎዳና ላይ ወይም በትናንሽ የግል መጽሐፍት መደብሮች ይገኛል። የትርጉም ስራዎቹም ዳግም
ላይታተሙ ይችላሉ። ወደፊት በአማርኛ ሥነ ጽሑፍ እድገት ውስጥ "ልጅነት ተመልሶ አይመጣም"
በሚለው ልብወለዱ ሲታወስ ይኖራል።
ማስታወሻዎች
1) የበእምነት ወንድምም ራሱ ከሁለት ዓመት በኋላ ራሱን ሲያጠፋ ሀሜት በረከተ። የበእምነት
ልጅና (የኔም የቀድሞ የስራ ባልደረባዬ) ከፍቅረኛው ጋር በተፈጠረ ግጭት እሷን ተኩሶ ገድሎ
ራሱንም በማጥፋቱ ሰዎች እዚህ ቤተሰብ ላይ በወረደው መአት ተሳቀቁ።
2)ይህ ከ66ቱ አብዮት በኋላም ቀጥሎ ነበር። በ1970ዎቹ በሙሉ የመጽሐፉ ቅጂዎች
በአዲስአበባ አውራጎዳናዎች ላይ ለሽያጭ ይቀርቡልኝ ነበር።
92
ጥቋቁር አናብስት
3)አብዛኛውን እርዳታ ያገኘሁት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከምትሰራው የበእምነት እህት ነበር ፤ ነገር
ግን እሷም ቢሆን ጥያቄዎቼን ከመመለሷ በፊት ሌሎች የቤተሰብ አባላትን ታማክር ነበር።
6)ይህ አባባሉ የሚያመለክተው፣ ህሊናው ውስጥ የኖረ ጉዳይ መኖሩን የሚገልጥልን ፍሩይዳዊ
ምሁር ማግኘታችንን እንጃ፤ ምናልባት በልጅነቱ ሳያደርገው ቀርቶ የሚፀጽተው ነገር ነበር ማለት
ይሆን?
93
ጥቋቁር አናብስት
ማሞ ውድነህ
የስለላ የስነ ማህበረሰብዊ ታሪኮችና ልብወለዶች ደራሲ ተርጓሚ
የኢትዮጵያ ጸኃፍትን አጫጭር ግለታሪኮች የያዘ መድበል
ለማዘጋጀት ሳስብ ገና ከመጀመርያው ቃለመጠይቅ
ካደረኩላቸው ደራሲያን መሃል ማሞ አንዱ ነበር፡፡እንደ እውነቱ
ከሆነ ማሞ የምሰራውን ሲሰማ እራሱ መጥቶ ነበር ለበርካታ
ጊዜያት ስለ ህይወቱና ስራዎቹ ለመጨዋወት የበቃነው፡፡
94
ጥቋቁር አናብስት
ማሞ በቄስ ትምህርት ቤት ለአራት ወይም አምስት አመታት ቆየ፡፡አስራ ሶስት ወይም አስራ
አራት አመቱ አካባቢ ሲደርስ መዝሙረ ዳዊትን በቃሉ መውጣት ጀመረ፡፡ህይወት በቄስ
ትምህርት ቤት ከባድ ነበር ደበሎ ለብሶ አኩፋዳ ተሸክሞ በቀፈፋ ለሁለት አመታት ቆይቷል፡፡
አክስቱ ይህንን በመጥላት ከትምህርት አስወጣችው፡፡ማሞ ግን ይሄ ነገር “አስተማሪ”ነበር
ይላል፡፡ “በአካል ከማጠንከሩም በላይ ከሰው ያግባባል፤ ችግር ያስተምራል ፤ ምግብ ማግኘቱም
ያን ያህል አያስቸግርም፡፡ ቀፈፋ ራስን ለመስዋእትነት ማቅረብን ያስተምራል መንደርተኛውንም
የቆሎ ተማሪዎችን እንዲደግፉ ያስለምዳል፡፡ተማሪን መርዳት (ለነፍስ እንደማደር)ይቆጠራል
ተብሎ ስለሚማሩና ቤተክርስትያንም ሲመጡ ልዩ መስተንግዶ እንዲደረግላቸው ስለሚሹ እኛን
ለመዘከር ይገደዳሉ፡፡የእለት እንጀራችንን ማግኘትን መካፈልን ያስተምራል፡፡እንደ አውነቱ ከሆነ
ትምህርቱን ወድጄው ነበር ስነ ምግባራዊ ሃላፊነቶችን ግብረ ገባዊ ህግጋትን ለሰው ዘር ሁሉ
መልካም መሆንን የመሳሰሉ በዘመናዊ ትምህርት ቤቶች የማይገኙ ነገሮችን ያስጨብጣል፡፡
አማርኛ በትክክል መጻፍ ማንበብን፤የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን እንዴት ሃገሪቷን
እንዳገለገለች ያየሁበት ቀሪ ህይወቴ ላይም ተጽእኖ ያሳደረ፤መጸለይ ለቤተሰብም ሆነ ለሃገር
የሃላፊነት ስሜት ማሳደርን፤ ታማኝነትን፤ ሰው ማክበርን፤ የተማርኩበት ብቸኛ ስፍራ ነው”
ይላል ማሞ፡፡
በትምህርት ቤት ሳለም ሆነ ከወጣ በኋላ በአንድ ዘመዱን ባገባ የወረዳ ገዢ ይበልጥ መጻፍና
ማንበብ እንዲችል ይረዳው እንደነበር ያክላል፡፡
በ1939 ወይም በ1940 ዓ.ም አልጋ ወራሽ አስፋ ወሰን ሰቆጣንና አካባቢውን ሲጎበኙ 20
የሚጠጉ ልጆችን ደሴ ወስደው እንዲያስተምሩ ተሰጣቸው፡፡የተሰጡት ልጆች የተሰዉ የአርበኞች
ልጆች ሆነው አባቶቻቸው በጦርነት የሞቱ ናቸው፡፡የማሞ መንደር 20 ኪ.ሜ አካባቢ ይርቅ
ስለነበር የመመረጥ እድል አላገኘም፡፡አክስቱ ግን ይህን ወሬ ሰምታ ኖሮ ሰዎችን እዚህ ከቆየ
ሰውም አይሆን ይልቅ ለራሱም ለዘመድም እንዲያገለግል ደሴ ከልዑል አልጋ ወራሽ ጋር
ውሰዱልኝ ስትል እንዲረዱት ለመነችለት፡፡ከላይ የጠቀስነው ዳኛ ዘመዱ ግን ደሴ ገብቶ ልዑል
95
ጥቋቁር አናብስት
አልጋ ወራሽ ጋር ላይሳካለት ይችላል ካልተሳካለት ደግሞ ዱርዬ ይሆናል ይልቁን እዚህ እኔ ዘንድ
ጸኃፊ ቢሆን ይሻላል ሲል አከላከለ፡፡ ስለዚህ ማሞ እሱ ዘንድ ቆየ ከከተማ ከተማ በመዘዋወር
ራቅ ሲል እስከ ኮረም ድረስ ለስራ ይሄዳሉ፡፡ ዳኛው ለማሞ እንደ ጽህፈት አስተማሪ በመሆን
የጸሃፊነትን ስራ አስለመደው፡፡
አንድ ሁለት ሳምንት በኮረም ከጓደኞቹ ጋር ከቆየ በሁዋላ የአውራጃው አስተዳዳሪ ዋግሹሙን
የማየት ሃሳብ ብልጭ አለለት፡፡ጠባቂዎችን ማለፍ አልቻለም፡፡ስለዚህ ዋግሹሙ ወደ ቢሮው
ለመሄድ ከቤታቸው ሲወጡ እስኪያገኛቸው ድረስ ጠበቆ እራሱን የአቶ ውድነህ ልጅ ነኝ ሲል
አስተዋወቀ፡፡ግን የተጠቀመው በታወቀው ስም ውዱ ተፈሪ ብሎ ነበር፡፡አባቱን የሚያውቁት
ዋግሹም በጣም ተገርመው እዚያ ምን እንደሚያደርግ ጠየቁት፡፡ 2 ማሞ አልጋ ወራሽን
ቢያገናኙኝ ትምህርቴን እንድቀጥል እንዲረዱኝ እፈልጋለሁ ቢልም አልጋ ወራሽ በወቅቱ አዲስ
አበባ ሄደው ስለነበር ዋግሹም እንደማይቻል ነገሩት፡፡ይልቁንም ማሞ አብሯቸው እየሰራ
ከተቻለም እየተማረ እንዲቆይ ነገሩት፡፡ከዚህ በኋላ (እንደ ተወዳጅ የቤት ልጅ)ከዋግሹም ጋር
በየቦታው አብሮ መዞር ጀመረ፡፡ትምህርቱን ግን መቀጠል አልቻለም፡፡ትምህርቱን መቀጠል
96
ጥቋቁር አናብስት
እንደሚፈልግ ለዋግሹሙ ሲናገር ዋግሹሙ አዲስ አበባ ካለች ሚስታቸው ዘንድ ለቤት ልጅነት
ላኩት ፡፡ማሞም በዚህ አድል ተደሰተ አዲስ አበባም ጥሩ አቀባበል ተደረገለት፡፡
ከትንሽ ወራት ቆይታ በኋላ ልኡል አልጋ ወራሽ የት እንደሚኖሩ አጣርቶ የአስተምሩኝ
ተማጽኖውን አስገባ፡፡የዋግሹሙ ሚስት ይህንን ከትንሽ ወራት በኋላ ስትሰማ ለስራ ነው እንጂ
ለመማር እንዳልመጣ ነግራው በጣም ተናደደችበት፡፡ማሞ አብሮ ለመቆየት ቃል ቢገባም
በሳምንቱ አካባቢ ቆይቶ ጠፍቶ ሄደ፡፡
ከአንድ አመት ትግል በኋላ ቀንቶት ልኡል አልጋ ወራሽ ዘንድ ቀርቦ ማመልከት ቻለ፡፡በዛ ወቅት
15 አመቴ ነበር ይላል ማሞ(ምን አልባትም ሳይሳሳት አይቀርም ከሌሎቹ ከላይ ከተሰጡት ቀናት
ጋር በቄስ ትምህርት ቤት እስከ 13 ወይም 14 ድረስ ቆየሁ ካለበት ጊዜ ጋር ተጨምሮ በሌላ
ጉዳይ የሚያሳልፈው ጥቂት ጊዜ ተደማምሮበት ብናሰላው ይጣረሳል) ልዑል አልጋ ወራሽ
ሊረዱት ተስማምተው መልእክት አስይዘው ወደ ደሴ ቤተመንግስታቸው ሰደዱት፡፡“ያ ነበር
የመጀመርያ ድሌ” ሲል ያስታውሳል ማሞ፡፡ደብደቤውን ይዞ ደሴ ቤተመንግስት ተመለሰ ዋና
አስተዳደሩ አቶ አለባቸው ገሰሰ የሚፈልገውን ሁሉ አሟሉለት፡፡የሰቆጣ ልጆች ወዳሉበት የንጉስ
ሚካኤል ትምህርት ቤትም መልእክት ተልኮለት ማሞ ተመዘገበ፡፡
97
ጥቋቁር አናብስት
ከአንደኛ ክፍል የጀመረ ቢሆንም አማርኛና ግዕዝ በቤተክህነት ትምህረት ቤት በመቻሉ በነዚህ
ትምህርቶች የ4ኛ ክፍልን ትምህርት መከታተል ቻለ፡፡ወድያውኑ ወደ 2ኛ ክፍል አደገ፡፡አዚያም
ሁሉንም የትምህርት አይነቶች አማርኛና ግዕዝን ጨምሮ ከመከታተሉም በላይ በአማርኛና ግዕዝ
የትምህርት ዐይነት ሁልጊዜ የበላይ ነበር፡፡አንዳንዴ መምህራኑን በማስተማር ሂደቱ ያግዛቸዋል፡
፡ በአማርኛ መምህሩ መምህር አለማየሁ ዘንድ ተወዳጅ ከመሆኑም በላይ ወደ መምህራን
ማሰልጠኛ ገብቶ አማርኛ አስተማሪ እንዲሆን መከሩት፡፡ የሂሳብና አማርኛ መምህራኑ አቶ
አለማየሁና አቶ አበራ አለማየሁ በተለይ በአማርኛ ትምህርት እንዲታትር ይገፋፉታል፡፡እስከ
6ኛ ክፍል ማብቂያ ድረስ በዚህ ትምህርት ቤት ነበር፡፡ማሞ በጣም ረዥም ልጅ ስለነበር 3(ልኡል
አልጋ ወራሽ እራሳቸው ከእድሜው በላይ ነው ይላሉ) በትምህርት ቤት ሰልፍ ላይ ሰንደቅ አላማ
የሚይዘው እርሱ ነበር፡፡
98
ጥቋቁር አናብስት
***
በዚህ ጊዜ ነበር በአስተማሪነቱ አልፎ አልፎ ጀምሮት የነበረውን ለጋዜጦች የመጻፍ ልማድ
በተከታታይነት አጠንክሮ የገፋበት፡፡ለአዲስዘመን፤የዛሬይቱ ኢትዮጵያ፤ሰንደቅ አላማችን፤
የኤርትራ ድምጽ ላይ በመጻፉ ጥረቱ ፍሬ አፍርቶለት ሌላ ምእራፍ በህይወቱ ለመጀመር በቃ፡፡
99
ጥቋቁር አናብስት
ማሞ በወቅቱ ለአዲስ ዘመን ሲጽፍ አርታኢው ብላታ ወልደ ግዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ ነበሩ፡፡
ታዋቂ ጸኃፊ ሲሆኑ 6“ጋዜጠኛ እንድሆን አሰለጠኑኝ”ይላል ማሞ “ለእሳቸው ነበር የምጽፈው
ተቀራረብንም” ከጻፋቸው ታሪኮች መሃል ግን አንዱ ችግር አስከተለ፡፡የ “የአስራ ሁለት ልጆች
አባት”የሚል ከሪደርስ ዳይጀስት የተተረጎመ የአረብ ታሪክ ሲሆን በከፊል ታትሞ ነበር፡፡ቀጣዩ
ክፍልስ ብሎ ማሞ ሲጠይቅ“ብዙ ባለስልጣኖች አልወደዱትም”ተብሎ ተነገረው “አጼ
ኃይለሥላሴንና አስራሁለቱን ሚንስትሮችን ለመንካት ተብሎ የተጻፈ” እንደሆነ አስበው
ስለነገሩት ትንሽ ተደናገጦ ከዚያ በኋላ መጻፉን ባያቆምም ይበልጥ ተጠነቀቀ፡፡
ከአመታት በኋላ በአንድ ወቅት በ(USIS)የዜና ጥንቅር እየሰራ አንድ ማሽን በእሳት ስለተያያዘ
ማሞና ጓደኛው በመስኮት በማምለጥ ለእርዳታ ተጣሩ፡፡እሳቱ ´ምንም ጉዳት´ ሳያደርስ ጠፋ፡፡
ማሞ ግን ተጎድቶ ነበር በግራ ክንዱ ላይም እስካሁን የቆየ ጠባሳ አለው፡፡ለጥቂት ቀናት
በኢምባሲው ወጪ በሆስፒታል ጭምር ታክሞ ወደ ስራ ሲመለስ አለቃው አቶ ሊሊኮ በአደጋው
ወንጅለውት ከስራ እንደሚባረር ነገሩት ፡፡ማሞ ይህንን ቢቃወምም ስራውን ግን ለቀቀ ፡፡ብዙም
ሳይቆይ በሩስያ ቋሚ አውደርዕይ ሃላፊ ጋር ተዋውቆ በፊልም እና በላይብረሪ ክፍል ውስጥ
ተቀጠረ፡፡ 7
ትንሽ ቆይቶ ማሞ ከሩስኪ አለቃው ጋር ተጋጨ፡፡አለቅየው ማሞን በአንድ አሮጌ ፊልም መጉዳት
ሲወነጅለው፤መጨረሻው የሁለቱ ሰዎች መጯጯህ ሆነ፡፡ማሞ ክፍሉን ለቆ ሲወጣ ውጪ አንድ
ሌላ ሩስኪ የካሜራ ቀራጭ ድሃና አካል ጉዳተኛ ኢትዮጵያውያንን ሲቀርጽ አግኝቶት ለምን
ደህናውንስ አትቀርጽም በማለት ዙርያውን ለከበቡት ሰዎች “የሚቀርጻችሁ ሀገሩ ወስዶ
መሳለቅያ ሊያደርጋችሁ ነው ”ብሎ በመናገሩ ለጸብ ተጋበዙ አለቅየውም በእዚህ ነገር ውስጥ
ገባ፡፡ማሞም አውደርዕዩን ለቀቀ አልተመለሰምም፡፡ቤቱ ተቀምጦም ስለ ሁለተኛው የአለም
ጦርነት መጣጥፎቹን መጻፍ ቀጠለ፡፡
100
ጥቋቁር አናብስት
ከጥቂት ቀናት በኋላ ሶስት እንግሊዛውያን ዜጎችን እየተከተለ በኢትዮጵያ ዙርያ የሚጎበኙትን
በሪፖርት መልክ እንደመጣጥፍ እንዲዘግብ ታዘዘ፡፡ይህ ለማሞ ሃገሩን ይበልጥ እንዲያውቅ
እድል ፈጠረለት፡፡አብሯቸው ከሚሰራቸው የእንግሊዝ ኤክስፐርቶች ብዙ ነገርን ተማረ፡፡ወደ
ምእራብ ቀጥሎም ምስራቅ በኋላም ወደ ኤርትራ ተጓዙ፡፡ማሞ በኤርትራውያን ምድር ላይ ሆኖ
ኤርትራውያንን ሲያገኝ ለመጀመርያ ጊዜው ነው፡፡ኤርትራውያን አማርኛ መናገር ያን ያህልም
ባለመፈለጋቸው ለመግባባት እንግሊዘኛን መጠቀም ግድ ነበር፡፡ (ጣልያንኛ ስለማይችል ነው
እንጂ ይቀለው ነበር)
(ጋብቻቸው ብዙም ከበርቻቻ በሌለበት በጥቂት ውስን ጓደኞች ኑባሬ የተፈጸመ ነበር)ስለዚህ
ጉዞ የጻፋቸው መጣጥፎች ተወዳጅ ነበሩ፡፡ስለኤርትራዊያን እውነተኛ ኢትዮጵያዊነት የጻፈውም
በኤርትራውያን ተደንቆ ነበር ይላል ማሞ፡፡
***
ይህ ዝውውር በማሞ ውድነህ ህይወት ውስጥ አዲስ ምእራፍ ከፈተ፡፡አዲስ ጋዜጣ ማቋቋም
ታላቅ እድልም ተግዳሮትም ነበር፡፡ለሃገሪቱ ጥሩም ጠቃሚምም እንዲሆን ፍላጎት ነበረው፡፡
ስራው በሃገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች በጋዜጠኛነት ስለሚወስደው (በተለይ የኦጋዴን አካባቢ
መስጦት ነበር)ከከተማ ውጪ ያሉ የጦር ሰራዊትና የፖሊስ አባላት እንዴት እንደሚኖሩና
እንደሚሰሩ የማየት እድል አጋጠመው፡፡እዚህ እየሰራ ሳለ ነበር በሁለተኛው የአለም ጦርነት
ዙርያ የሚያጠነጥኑት መጻሐፍቱ የመጀመርያው በ1954 ዓ.ም ሁለተኛው ከአምስት አመታት
ገደማ በኋላ በ1958 ዓ.ም መታተም የጀመሩት፡፡
102
ጥቋቁር አናብስት
ማሞ በኤርትራ ለ9 አመታት ቆየ፡፡በዚህ ወቅትም በዚያ ያለውን ሁኔታ አጥንቶ ከመቶ የበለጡ
ጽሁፎችን ጻፈ፡፡“(ስለ ኤርትራ ችግርና ያለጦር መሳርያ ግርግር የሚፈታበት ዘዴ) በመጻፌ
ኤርትራውያን ጽሁፌን ያውቁት ነበር ብዙዎች ከእኔ ሃሳቦች ጋር የሚስማሙም ነበሩ ሌላው
ቀርቶ አማጽያኑ እራሳቸው የኔን መጣጥፎች በገንቢነት ይወስዷቸው ነበር ”ይላል፡፡የኤርትራው
ገዢ ራስ ካሳ በችግሩ አፈታት ላይ በኔ ሃሳብ ቢስማሙም “በተቃዋሚዎች መኖር አናምንም”
ብለው መኖራቸውን ከሚክዱት የአዲስ አበባ ባለስልጣናት ተቃውሞ መጣ፡፡ማሞ ጌታቸው
መካሻ፤ዶ/ር ምናሴ ኃይሌ፤ዶ/ር ተስፋዬ ገ/እግዚ ከመሳሰሉ የማስታወቂያ ሚንስትሮች
ባለስልጣናት ጋር በዚህ ጉዳይ የከረረ አለመግባባቶች ውስጥ ገባ፡፡በመጨረሻም ማሞ ሃሳቡን
በረጅም ጽሁፍ ለንጉሱ አቀረበ፡፡ንጉሱም በሃሳቤ ተስማምተው በወቅቱ ለኤርትራ ጠቅላይ ገዥ
ለነበሩት ጄኔራል ደበበ ኀይለማርያም “በጽህፈት ሚንስትር በኩል (ትእዛዝ የሆነ)የኤርትራ
ጉዳይ ከማሞ ሃሳብ አንጻር ተጠንቶ ድርድር እንዲጀመርና ከባለጉዳዮቹ ጋር በንግግር
እንዲፈታ” የሚል ደብዳቤ አስጽፈው ላኩ፡፡ማሞ ለኤርትራ በሰራው ስራ ኩራት እንደሚሰማው
ይናገራል፡፡የኤርትራታሪክ መጽሐፉን በ1962 ዓ.ም ጻፈ፡፡ስለታዋቂው ጀግና ራስ አሉላ አባ
ነጋም ተውኔት ደርሶ አሉላ አባ ነጋ ተብሎ በ1966 ዓ.ም ለመድረክ በቃ፡፡ቃለመጠይቅ
በምናደርግበት ወቅትም የመንግስት አሳታሚ የሆነው 11 ኩራዝ ማተምያ ቤት ስለ ራስ አሉላ አባ
ነጋ የጻፈው መጽሐፍ ለመታተም ገብቶ የነበረ ሲሆን 10 አመታትን የአሉላን ታሪክ በማጥናት
አሳልፌያለሁ ይላል፡፡
***
105
ጥቋቁር አናብስት
***
በግርግሩ መጀመርያ በ1965 ዓ.ም ማሞ ወደዋናው የጦር ጣብያ ፎርቶ የጉዳዩን “ግልጽ
ምስል ለማግኘት” ሄደ፡፡በዚህ ጊዜ ማሞ “የህብረት እዝ” የሚባል ወይም ጂ5 የሚባል ቡድን
አመራር ነበር፡፡የተዋቀሩትም ከ ባህር ሃይል ፤ፖሊስ፡ከምድር ጦር፤ ከአየር ሃይል እና ከሲቪል
ሰርቪስ ነው፡፡ከዚያ በፊት እነዚህ ቡድኖች በማሞ አማካኝነት ለአንድ ስራ ተገናኘተው የነበሩ
ሲሆን ከዚህ በኋላ ግን አንድ እዝ አቋቁመው ከሽኩቻና ከፉክክር ይልቅ በትብብር ለመስራት
በመፈለጋቸው ይህ ሃሳብ በ ልዑል አስራተ ካሳ ተወዳጅ ሆነ፡፡ይህ የጂ5 ጅማሮ ሲሆን ማሞም
“አዛዡ” ሆኖ ነበር፡፡ ስለዚህም በጸጥታና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ከ ፎርቶ መሪዎች ጋር
ለመወያየት ወደ እዚያው አቀና፡፡እዚያም ደርሶ ላሉት ሰዎች ሃሳቡን አቀረበ፡፡ የፖሊስ ጄኔራሉ
እጅ ለመስጠት ሳይስማማ ቀርቶ ፈጥኖ ደራሽ ኮማንዶዎችን 12ለጥበቃ ሲጠራ ማሞ ሃይል
እንዳይጠቀሙ መከረ፡፡በመጨረሻም ንጉሱ አስማሚ ሽማግሌ በመላክ ነገሮችን ሊረጋጉ
ችለዋል፡፡
106
ጥቋቁር አናብስት
ንጉሱ ወርደው ደርግ ስልጣኑን በ1966 ከያዘ በኋላም ማሞ ጥያቄውን ለአዲሱ መንግስት
ማቅረቡን አላቋረጠም፡፡“ደርጎች ሃሰቤን ቢሰሙም በመሃላቸው አለመግባባት ስለነበር
በተለመደ መልኩ ስራቸውን ሊከውኑ አልቻሉም”ይላል፡፡ማሞ ጄኔራል አማን አንዶምን
(ኤርትራዊ ጄኔራልና ለተወሰነ ጊዜ የኢትዮጵያ መራሄ መንግስት የነበሩትን)“ከሃይ ሃይ በስተቀር
በቁም ነገር አማጺያኑን ለማናገር ዝግጁ አልነበረም”ሲል ይተቻቸዋል፡፡
107
ጥቋቁር አናብስት
***
በኤርትራ ችግር ላይ ያለው ጠንካራ ተሳትፎ ሃሳቡን በሙሉ ሰርቆት ነበር በነዚህ አመታት፡፡
በርካታ ሰዎችም “ትክክለኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል”ይሉኛል ሲል በዚህ ወቅት ግን እነዚህን
የትርጉምና የራሱ ስራዎችን ለመጻፍ ግዜ ማግኘቱ ያስገርማል፡፡በንግግራችን ወቅትም ስለ
ስነጽሁፍ ስራዎቹ በአጭሩና እንደማጠቃለያ አድርጎ ከኤርትራ ፖለቲካ ተሳትፎው በኋላ
ማንሳቱም ስነ ጽሁፍ በሃሳቡ ተከታይ ቦታ መያዟንና አልያም ተቀዳሚ ከሆነችም በፖለቲካዊ
ክርክር ውስጥ እንደ አንገት ማስገቢያ መላ የመሆንዋን ሃቅ ያጠይቃል፡፡ለማንኛውም ከኤርትራ
በኋላ ስላለው አበርክቶት ስናነሳ ከ20 በላይ መጻህፍት ተርጉሟል፡፡ከነዚህም መሃል ወደ አስሩ
በቃለመጠይቃችን ወቅት ለህትመት በቅተዋል፡፡አስራ አንድ ያህሉ ደግሞ በሳንሱር ታንቀዋል፡፡
ከነሱ መሃልም የ ኤም.ኤች ሃይካል THE ROAD TO RAMADAN እና ስለ ሳይኪክ እውቀት
የተጻፈው IS DEATH THE END ?ይገኙበታል፡፡ስለ ሲአይ ኤ ዩፎ ወዘተ›..የተጻፉም አሉ፡፡
108
ጥቋቁር አናብስት
በማሞ የስነ ጽሁፍ ታሪክ ውሥጥ መጀመርያው ምንም ያህል ያልተጤነ ቢሆንም አዲስ በርን
መክፈት ችሏል፡፡
ሌላው የእርስበእርስ መረዳጃ የሆነው የኢትዮጵያ የማህበር ዐይነት ደግሞ እድር ነው፡፡ማሞ
ደግሞ በነዚህ ማህበራት ላይ የተመረኮዙ ስነ ማህበራዊ ልብወለዶችን መጻፍ በመጀመሩ
እድርተኞቹን ጻፈ፡፡እኛ በምንጨዋወትበትም ወቅት በህትመት ላይ ነበር፡፡ቀጥሎ ደግሞ
ስለሌላው የማህበር ዐይነት"ማህበርተኞቹ" የሚል መጽሐፍ እንደ አውሮጳውያኑ አቆጣጠር
1985 ላይ ጽፎ አጠናቀቀ፡፡
ከጎንደር ዩንቨርሲቲ ተመርቆ የህክምና ዶክተር ሆኗል አንዱ በ 1978 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ
የመጨረሻ አመት ተማሪ ሲሆን አንድ ወንድና ሴት ልጆቹ ግን ገና ህጻናት ናቸው፡፡
ማሞ እስከ 1978 ዓ.ም ከ2000 በላይ መጣጥፎችን ከ27 አመታት በላይ ለተለያዩ ጋዜጦች
አበርክቷል፡፡በእንግሊዘኛ (ሌላው የሀገሪቱ ኦፊሴል ቋንቋ) ግን ብዙም አልጻፈም፡፡
እንደ የአሮጊት አውታታ ያሉ በበፊቱ ስርአት በሳንሱር የተያዙ ረቂቆቹን ኣሳትሞ ለማውጣት
ይፈልጋል፡፡ ትርጉሞቹን ጨምሮ በዚህ ጊዜ ከ30 በላይ መጻሕፍትን በስሙ ሰርቶ አውጥቷል፡፡
***
በዚያን ወቅት በሳንሱር አድራጊዎችን እጅ ነበር ለመጽሐፉም ´የድራማ ቅጽ´ እየሰራለት ነበር፡፡
ጎን ለጎን በተጓዳኝ ጊዜም የማጠናቀቅያ ስራዎች እየሰራለት የሚገኘው በአንድ ኢትዮጵያ ውስጥ
ያደገ የመናዊ አረብ ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ልብወለድ ስራው ነበር፡፡ወደ የመን ከተመለሰ በኋላ
አንዲት ኢትዮጵያዊትን አግብቶ አሜሪካን ሃገር አንድ ልጅ ከወለዱ በኋላ ተፋቱ፡፡ መጽሐፉን
የደጎመውም እራሱ ይሄው ሰው ነው፡፡ተመልሼ በ1982 ዓ.ም ስመጣም የማሞ አዳዲስና ዳግም
የታተሙ መጻሕፍትን ብመለከትም እሱን ግን አላገኘሁትም ፡፡
110
ጥቋቁር አናብስት
ማስታወሻ
2ማሞ ከአክስቱና ከሌሎች አርበኞች እንደሰማው ከሆነ አባቱ የአርበኞች መሪ ከነበረው ዋግሹሙ
ጋር ቅርበት ነበራቸው፡፡ ከጣልያኖች ጋር የሚተባበሩ ባንዳዎች ዋግሹሙን በቁጥጥር ስር ለማዋል
ጓጉተው ነበር፡፡አንድ ቀን ተሳክቶላቸው በቁጥጥር ስር ሊያውሉት ተቃርበው የነበር ቢሆንም
የማሞ አባት ተኩሰው ከማሃከላቸው አንዱን ጥለው የተቀሩትን ስላባረሩ ላይሳካ ችሏል፡፡ዋግሹሙ
ለዚህ ስራቸው ወሮታ አንድ ረጅም የጣልያን ሽጉጥ ሸልሟቸዋል፡፡እስከመጨረሻውም
ባለውለታቸው ሆነው ዘልቀዋል
5“ከሃይሌ ፊዳ ቀጥሎ ሁለተኛ የመኢሶን ሰው የነበረው የዶክተር ነገደ ጎበዜ አባት ነበሩ”ሲል ማሞ
ያብራራል
111
ጥቋቁር አናብስት
12በዚህ ወቅት የኤርትራ ክፍለሃገር አስተዳዳሪ የነበሩት ጄኔራል ደበበ ሀይለማርያም በቁጥጥር ስር
ውለው በጦር ካምፕ ውስጥ ታስረው ነበር፡፡
14ማሞ እንደሚለው ከሆነ ደበበ አዲሱን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዳልካቸው መኮንንን ስለጉዳዩ
ለማናገር ቢደውልላቸውም እሳቸው በተራቸው በወቅቱ የማስታወቂያ ሚንስትር ለነበሩት ታዋቂው
ጋዜጠኛ አሃዱ ሳቡሬ ሳይነግሯቸው ቀርተዋል
17እዚህ ኮሚቴ እያለ ማሞ በተፈሪ በንቲ ቢሮ ይሰራ የነበር ሲሆን ተጠሪነቱ ለሱ ነበር
112
ጥቋቁር አናብስት
19ማሞ እራሱ በአንድ ወቅት እቁብ ይጠጣ ነበር፡፡ያልተመቸው አንድ ነገር ስለነበር እቁቡን ጥሎ
ወጥቶ የእድር አባል ሆነ፡፡“ያለ እድርማ መኖር አይቻልም”ሲል ያክላል
113
ጥቋቁር አናብስት
ይልማሐብተየስ
በኢትዮጵያ ቀደምት የወንጀል ክትትል ታሪክ ጸሐፊ
ከኃይለሥላሴ ጊዜ ጀምሮ የይልማ ሐብተየስን ስም አዲስ
አበባ መጽሀፍት መደብር ውስጥ ያሉ መጽሀፍት ሽፋን ላይ
አየዋለሁ። ከመጽሀፍቱ መሀል አንዳንዶቹን ላነብባቸው
ከመቻሌ በፊት ሁሉ እንዲሁ ገዝቼ አስቀምጪያቸው ነበር።
በጊዜው በወንጀል ነክ ድርሰቶች ቢታወቅም፣ የሚጽፈው
ያንን ብቻ አልነበረም። ወንጀል ነክ ታሪኮች እንደ "ደንበኛ
ሥነ ጽሑፍ" አይቆጠሩም ነበር፤ይልማ ሐብተየስም
መጽሀፎቹን የሚያያቸው በተመሳሳይ መነጽር ነበር።አላማው አንባቢዎቹን ማመራመር ሳይሆን
ማዝናናት ነው።ነገር ግን በቋንቋው ውበት እና በአፃፃፍ ዘይቤው ስለሚደነቅ ላነጋግረው ወሰንኩ።
መጀመሪያ ያገኘሁት በ1979 አጋማሽ ሲሆን ወዲያውኑ የሕይወት ታሪኩን ነገረኝ።
ቤተሰቦቹ ከመራህቤቴ ናቸው። እነሱም እንደ አብዛኛዎቹ የመራህቤቴ ሰዎች የእጅ ጥበብ ባለሙያ
ናቸው።መራህቤቴዎች በብዛት ሸክላ ሰሪ፣ ቀጥቃጭ፣ ሸማኔ የመሳሰሉት ናቸው። ነገር ግን አባቱ
ከሌላው የበለጠ የቤተክርስቲያን ትምህርት በማግኘታቸው ዲያቆን ብሎም ነጋዴ ነበሩ። አባቱ
በ75 ዓመታቸው በ1978 ሲሞቱ፣ያልተማሩት ባለቤታቸው ሶስት ዓመት ቀደም ብሎ በ70
ዓመታቸው አርፈዋል። በይልማ ቤተሰብ ውስጥም እንዲህ ዐይነት ሰዎች አሉ።ቤተሰቡ ወደ አዲስ
አበባ መጥተው በቀጨኔ መድሐኒአለም ቤተክርስቲያን አካባቢ ሰፈሩ። ይህ አካባቢ መርሀቤቴዎች
በተለይ ሸማኔዎች የሚኖሩበት ነው።
ይልማ ሐብተየስ የተወለደው በአዲስአበባ በ1930ዓም ነበር። እስከ ሰባት ዓመቱ“በጨዋታ ብቻ”
አደገ። አምስት ዓመት ሲሆነው አባቱ የይልማን እናት ፈትተው ቀሪውን ዘመን በድጋሚ ሳያገቡ
ኖረዋል። በዚህ ጋብቻ ውስጥ የተፈጠረው ብቸኛ ልጅ ይልማ ነበር፤ይሁን እንጂ አባቱ
ከውሽማቸው ሴት ልጅ ወልደዋል።አብራቸው ግን አልኖረችም።እናቱ ደግመው ካገቡ በኋላ
እየሄደ ይጠይቃቸው ነበር። እናቱ “በጣም ደግ” ሲሆኑ አባቱ “ግትር እና“አክራሪ ሀይማኖተኛ”
ነበሩ። ዘወትር ወደ መርካቶ ለስራ ጉዳይ ከመሄዳቸው በፊት የሐይማኖት መጻሕፍትን ይደግማሉ ፤
ዘወትር እሁድ ደግሞ ቤተክርስቲያን ይሄዳሉ።
ሰባት ዓመት ሲሆነው “በራስ ደስታ ሆስፒታል መንገድ ላይ” በሚገኘው የዮሐንስ ቤተክርስቲያን
ትምህርት ቤት ገባ።በዚያ ዳዊት እና ሌሎች የጸሎት መጽሐፍትን መድገም፣መፆምና ቤተክርስቲያን
መሄድ ተማረ።እንዲህ ያሉ ነገሮች ወላጆች በቤት ውስጥ ለልጆቻቸው የሚያስተምሩት ነገር
114
ጥቋቁር አናብስት
አንድ ዓመት ከፈጀው ስልጠና በኋላ በ1949 ይልማ በራስ ደስታ ሆስፒታል1እንዲሰራ ተመደበ።
በዚያ ለአንድ ዓመት ተኩል ከሰራ በኋላ በጎንደር የህብረተሰብ ጤና ኮሌጅ በከፍተኛ ላቦራቶሪ
ቴክኒሺያንነት ለመሰልጠን ገባ።ይህ ኮርስ በአይነቱ የመጀመሪያ ቢሆንም የጤና ጥበቃ መኮንነት
115
ጥቋቁር አናብስት
ስልጠና ከጀመረ ግን ሁለት ዓመት አስቆጥሮ ነበር።ይህ በUSAID የሚሰጠው ኮርስ ሁለት ዓመት
ይፈጃል።ትምህርቱ የሚሰጠው በእንግሊዝኛ ቋንቋ ነበር። ነገር ግን በሊሴ ይህንን ቋንቋ ከመማሩም
በላይ በአርበኞች ትምህርት ቤት ለአምስት ዓመታት የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት ስለተከታተለ፣
ትምህርቱንለመረዳት ምንም አልከበደውም።ትምህርቱ ለላቦራቶሪ ቴክኒሺያኖች የሚሰጥ
“አጠቃላይ” የሚባል ስልጠና ሲሆን በክፍሉ ውስጥ ያሉ ተማሪዎች በሙሉ ተመሳሳይ ኮርስ
ይወስዳሉ።
ይልማ ጎንደርን ወዶት ነበር። ከተማውን እንዲሁም የፋሲልን ግንብ ቢጎበኝም በኢትዮጵያ ታሪክ
ላይ ከፍተኛ ፍላጎት አልነበረውም። ኮሌጁ የትምህርት መርጃ መሳሪያዎች የተሟሉለት ሲሆን
“በአሜሪካኖች የሚሰናዳው ምግብ በየቀኑ ስጋን ያካተተ ነበር”ጎንደር እያለ የፈጠራ ሥነ ጽሑፍን
ለማንበብ ለመጀመሪያ ጊዜ ፍላጎት አደረበት። ይህ መነቃቃት የተፈጠረው ዙሪያውን ከከበቡት
ተማሪዎች ሲሆን በዚህ በኩል መምህራኑ ምንም ግፊት አላሳደሩበትም። በዚህ ጊዜ ካነበባቸው
ኢትዮጵያዊ ደራሲያንን መካከል እንዳልካቸው መኮንንን ይጠቅሳል፤"ጥሩ እና ሀይማኖተኛ ጸሐፊ"
ነው ይለዋል። ካነበባቸው የደራሲው ስራዎች መካከል "አልሞትኩም ብዬ አልዋሽም"፣ "ጸሐይ
መስፍን" እና "የደም ዘመን" ይገኙበታል። ከከበደ ሚካኤል ስራዎች መሀል "ሮሚዮ እና ጁልየት"
(ከሼክስፒር የተዛመደ)፣"ታሪክና ምሳሌ"፣ "ከይቅርታ በላይ" (Beyond Pardon)፣"አቶ
በላይነህ" (Faustንመነሻ ያደረገ) እና"ታላላቅ ሰዎች"ን አንብቧል። ከውጪ ደራሲዎች አጋታ
ክሪስቲን፣ኧርል ስታንሌይ ጋርድነር፣ፒተር ቼኒይ ካነበባቸው መሀል ናቸው።እነዚህ ሶስት ደራሲዎች
ይብዛም ይነስምይልማ በኋላ መፃፍ ሲጀምር የሚከተለው የሥነ ጽሑፍ “ዘውግ” ተከታይ
ጸሐፊዎች ናቸው። ቀስ በቀስ ይልማ እንደ ዶስቶቭስኪ፣ ቶልስቶይ፣ ጎርኪ፣ ዲክንስ፣ ሔሚንግዌይ
ያሉትን“ደንበኛ ጸሐፍት”ማንበብ ጀመረ፤ይህ ዐይነቱ ንባብ ግን “ቀስ በቀስ፣ ዘግየት ብሎ”
የተጀመረ ነው።
ወደ መዲናይቱ ከመጣ በኋላ ይልማ “በመጠጥ ቤትና በልጃገረዶች ዙሪያ የማንዣበብ” ሕይወት
ይበልጥ እየሳበው መጣ። ነፃ ጊዜውን ሁሉ እዚህ ማጥፋት ጀመረ።
116
ጥቋቁር አናብስት
ቀጥሎ የልጆች የሥነ ምግብ ጥናት ክፍል(በኋላ የኢትዮጵያ የሥነ ምግብ ጥናት ኢንስቲትዩት)
ተቀላቅሎ እስከአሁን ድረስ እዛው ይሰራል። በስዊድናዊ ዳይሬክተር ስር የላቦራቶሪ ቴክኒሺያን ሆኖ
ስራ ጀመረ። በ1956 መጨረሻ ወደ ስዊድን አቅንቶ በኡፕሳላ ኬሚካል ኢኒስቲትዩት ለሁለት
ዓመት ያህል ከተማረ በኋላ ወደ ድሮው የስራ ቦታው ተመለሰ። ስዊድን ቢበርድም ወዶት ነበር፤
እዚያ ሀገር ብዙ ጓደኞች ሲኖሩት፣ ከፊሎቹ አዲስአበባ እያለ የሚያውቃቸው ናቸው። ስዊድናውያን
ቀዝቃዛ እና ከሰው የማይቀላቀሉ ቢሆንም እነሱንም ወዷቸው ነበር፤“ግለኝነት የሚያጠቃቸው ግን
ማንንም የማይጎዱ” ናቸው ይላል። በስዊድን“ጥሩ ጊዜ”ሲያሳልፍ ቋንቋቸውንም ለምዶት ነበር
የተመለሰው።ነገር ግን በስዊድን ለመቆየት አላሰበም። ምናልባት ዳግመኛ የመጎብኘትና በዚያው
የመቅረት ፍላጎት ሳይኖረው አልቀረም(ይህን ያለው መንግስቱ ሐይለማሪያም ገና በሥልጣን ላይ
እያለ ነው)።
***
117
ጥቋቁር አናብስት
የሚገኝ አንዱ እንደ ቀልድ "እንደዚህ መፃፍ ከቻልክ ለምን ደራሲ አትሆንም?"ይለዋል።ይህ ጥያቄ
አብሮት ቀረ፤ጊዜውን በከንቱ ከማባከን እንደ መዝናኛ መፃፍ ጀመረ።የመጀመሪያውን መጽሀፍ
ሲጽፍ“ደስታ ተሰማው”፤ገና መፃፍ ሲጀምር “የገንዘብ ኪሳራ ቢደርስበትም ለመንፈሱ የሚያረካ
ነበር።” የኢትዮጵያ ደራሲያንን ሁኔታ ስለሚያውቀው፣ ከድርሰት ስራ ገንዘብ አተርፋለሁ ብሎ
አልተነሳም።የሚጽፈው ሁሌም በአማርኛ ነበር፤በሌላ ቋንቋ የመፃፍ ሀሳብ ተከስቶለትም አያውቅ።
ይህም "ለአርባስምንት ሰአት ተጋቡ" የተሰኘው መጽሐፍ በ1957 ዓ.ም ታተመ። ታሪኩ ስለ
አንዲት የታጨች ሙሽሪት ነው። ሙሽራው ሰርጉ ላይ ሳይገኝ ቀረ። የቤተሰቡ ጓደኛ የሚያገባት
ሌላ ወንድ ቢያገኝላትም የደረሰች እርጉዝ ስለነበረች በሰርጉ ምሽት ምጥ ያዛት። የሰርጉ ቬሎ
እርግዝናዋን ደብቆላታል።ሙሽራውና ሙሽሪት ጭራሽ አይተዋወቁም፤በጊዜው በኢትዮጵያ ይህ
የተለመደ ነበር። ባል የህመሙን መንስኤ ሳያውቅ ሚስትን ወደ ሆስፒታል ይዟት ይሄዳል። ዶክተሩ
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ባልየው የተወለደው ልጅ አባት መስሎት "እንኳን ደስ አለህ!" ሲለውክው
ይላል። ጋብቻው ለ48 ሰአታት ብቻ የቆየው በዚህ ምክንያት ነው።መጽሐፉ “አዝናኝ” ሲሆን
ከፍተኛ ተቀባይነት አግኝቶ የታተሙት 3,000 ቅጂዎች ወዲያው ተሽጠውለታል። ከካናዳ ማክጊል
ዩኒቨርስቲ ዲግሪ ያገኘው መብራህቱ ዮሐንስ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ለዚህ መጽሀፍ ቅኝት
ሰርቶለት ነበር። በቅኝቱ መጽሐፉ ጥሩ እንደሆነና ፀሐፊው ተሰጥኦ እንዳለው፣ እንዲሁም የተሻለ
መፃፍ እንዳለበት መፃፉን ይልማ ያስታውሳል።
118
ጥቋቁር አናብስት
በሚቀጥለው መጽሀፉ ይልማ በሰፊው የሚታወቅበትን የወንጀል ታሪክ ፃፈ።ይህ "እሱን ተይው"
የተባለ መጽሐፍ በ1958 ዓ.ም ጀምሮ ከአንድ ዓመት በኋላ ተጠናቀቀ።ታሪኩ ባልፈፀመው
ወንጀል፣ አባቱን በመግደል ስለተከሰሰ ሰው ነው። እውነታኛው ገዳይ በመጨረሻ ሲያዝ ተከሳሹ ነፃ
ይወጣል።
በጊዜው የወንጀል ታሪኮች ለኢትዮጵያ አዲስ ነበሩ፤ማንም እንደዚህ ዐይነት መጽሀፍ ለመፃፍ ሞክሮ
አያውቅም ይላል ይልማ። ይሁን እንጂ በቃለመጠይቃችን ወቅት ጥሩ መጽሐፍ እንዳልነበር
ተሰምቶታል፤ተቀባይነትን ያገኘው “አዲስ ዐይነት መጽሀፍ በመሆኑ ብቻ ነው” ይላል።እንደዚህ
ዐይነት “ልብ አንጠልጣይ” ታሪኮችን ለመፃፍ ተበረታታ። መጽሀፉ በሰባት ወይም በስምንት ወር
ውስጥ 3,000 ቅጂዎች ተሸጠ።ነገር ግን እርሱ ራሱ በመጽሐፉ ስላልረካ ከቃለመጠይቃችን ጥቂት
ቀደም ብሎ "ሶስተኛው ሰው" በሚል ርዕስ አሻሽሎ ጽፎታል።
እንደ ወንጀል ታሪክ ፀሐፊነቱ አጋታ ክሪስቲ እና ኧርል ስታንሌይ ጋርድነር ተጽእኖ አሳድረውብኛል
ይላል።
119
ጥቋቁር አናብስት
"ደስ ያለው ሀዘንተኛ" ደግሞ በ1964 ወጣ። ታሪኩ 5,000 ብር ሰርቆ ከሚወዳት ባለትዳር
ፍቅረኛው ጋር ስለሚኮበልል ሰው ነው። ከዚያ ሞቶ ይገኛል። በመጨረሻ ግን ሞቶ የተገኘው ሰው
የወንጀለኛው መንታ ወንድም ሆኖ ይገኛል። ወንድሙን የገደለው ወንጀለኛ ራሱ ሲሆን፣
አላማውም እሱ ላይ የሚደረገውን ክትትልለማስቆም ነበር። በመጨረሻ፣ ፍትህ ይሰፍናል።
****
ይልማ ገና ጀማሪ ጸሐፊ እያለ፣ በጊዜው እንደነበሩ ሌሎች ኢትዮጵያዊ ደራሲያን መጽሀፎቹን ራሱ
ማሳተም ነበረበት። ለማስተየብ፣ ሳንሱር ለማስደረግ፣ ለማተም ራሱ ወጪውን ይሸፍንና ለመጽሀፍ
ሻጮች ራሱ ያከፋፍላል። ከመጽሀፍ ሻጮች የድርሻውን እየዞረ የሚሰበስበውም ራሱ ነው። ይህ
ስራ ከባድና ተስፋ የሚያስቆርጥ ነው፤“ምንም ትርፍም የለውም”። በዚህ የተነሳ ይልማ ለተወሰነ
ጊዜ መፃፍ አቁሞ ነበር። ይሁን እንጂ ለ"ጸደይ" መጽሔት ሁለት አጫጭር ታሪኮችን ጽፏል።
አንደኛው "የአብየቅየለሽ ኑዛዜ" ሁለተኛው ደግሞ "ደም የነካው እጅ" ይሰኛሉ። ይሄ ሁሉ
ከ1966ቱ አብዮት በፊት ነበር።
አብዮቱ ሲፈነዳ ይልማ ለሁለት ዓመት ያህል ሙሉ ለሙሉ መፃፍ አቆመ።ፖለቲካ ውስጥ ገብቶም
ሆነ ለመግባት ፍላጐት ኖሮት አያውቅም።በአብዮቱ የመጀመሪያ ደረጃ ወቅት ብዙ ግራ መጋባት/
ውዥንብር ስለነበረ እሰከናካቴው መፃፉን ተወው።
አብዮቱ ከፈነዳ ከሁለት ዓመት በኋላ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሚሰራ አዘጋጅ የቴሌቪዥን ድራማ
እንዲጽፍ ሲጠይቀው ተስማማ። ይልማ ለ"ጸደይ" መጽሔት የፃፈውን አጭር ታሪክ "ደም የነካው
ጎጆ" ለቲቪ ድራማ እንዲመች አድርጎ ፃፈው። በተመሳሳይ ርእስ በ1968 ተዘጋጀ።
ከዚያ በኋላ ቀይ ሽብር መጣ። የፖለቲካ ባለጋራዎች ጠላቶቻቸውን መግደል ሲጀምሩ የአዲስ አበባ
ጎዳናዎች በሬሳ ተሞሉ። በዚህ የተነሳ ይልማ “የመፃፍ ፍላጎቱ ለሶስት ዓመት ጠፋ።” ከዚህ በኋላ
"ያልተከፈለ እዳ" የተሰኘውን ከዚህ በፊት የተጠቀሰውን የቴሌቪዥን ድራማ መሰረት አድርጎ
ልብወለድ ፃፈ።
120
ጥቋቁር አናብስት
***
በፈጠራ ስራው፣ ረዥም ልብወለድን ይመርጣል። በተውኔት መልክ የፃፈውን ብቸኛ መጽሀፍ፣
ባህል ሚኒስቴር ውስጥ ለሚገኝ ኮሚቴ ለግምገማ ልኮታል።እነሱም “አሳለፉትና” መርካቶ አካባቢ
ወደሚገኘው ራስ ቲያትር እንዲዘጋጅ “ላኩት”። ነገር ግን ይልማ “ቲያትር ቤቱን ስላልወደደው
አስወጥቶ ወሰደው።” ከዚያ በልብወለድ መልክ እንደአዲስ ፃፈውና በ1978 "አጋጣሚ" በሚል
ርዕስ ታተመ። ይልማ የፃፋቸው አጫጭር ልብወለዶች ጥቂት ናቸው።
***
ማስታወሻዎች
123
ጥቋቁር አናብስት
አባቱ ገበሬ ሲሆኑ ነጋሽ አብሯቸው ለጥቂት አመታት የኖረው የእንጀራ አባቱ ደግሞ ዳኛ ነበሩ፡፡
በኋላ ነጋሽ የእናቱ አባት ከሆኑት ከወሎ ከመጡት ከእስልምና ወደ ክርስትና ወደተጠመቁት
ከፊትአውራሪ አሊ ቡሊ ዘንድ ለመኖር ሄደ፡፡እኚህ አያቱ በገበሬነት ከወሎ ወደ ሃረርጌ የሄዱት
በራስ መኮንን ዘመነ ግዛት ነው፡፡በሳቸው ጊዜ የፊትአውራሪነትን ትልቅ መዕረግ ቢያገኙም ቅሉ
ለመኮንን ሳይሆን ለሌላ ጌታ ነበር ያደሩት፡፡አሊ ቡሊ በርካታ መሬት ማግኘት ችለው የነበር ሲሆን
ከአዲስ አበባ የጎጃም ሴት በሚስትነት አስመጥተው ከሷም ሶስት ልጆችን ሲወልዱ የነጋሽ እናት
ሁለተኛዋ ነበረች፡፡
124
ጥቋቁር አናብስት
ነጋሽ በአያቱ ቤት በኖረበት ወቅት የቤተ ክህነት ትምህርት ለተወሰኑ አመታት ተምሯል ወንድሙ
አሰፋ ግን በአምስት አመት ከነጋሽ የሚበልጥ ሲሆን3ነጋሽ እዚያ በሚማርበት ወቅት ዘመናዊ
ትምህርት የማግኘት እድል አጋጥሞታል፡፡መክንያቱም ካናዳውያን ሚስዮኖች በቃጠሎው የኢብሳ
ክልል አካባቢ“አረማውያንንና ዘላኖችን አስተምሮ ለመለወጥ” በሚል የሚስዮን ጣብያና ትምህርት
ቤት በመቻራ ስላቋቋሙ ነበር፡፡ከአሊ ቡሊ መኖርያ እስከ ሚስዮኑ በበቅሎ ወይም በእግር የግማሽ
ቀን መንገድ ነበር፡፡አሊ ቡሊ ነጫጮቹን ቤቶች ሲመለከቱ የማወቅ ጉጉት አድሮባቸው ወደእዚያው
አቀኑ፡፡የውጪ ሃገር ዜጎቹ አርብቶ አደሮቹን ለማስተማር ቢመጡም እንደ ልባቸው እነሱን
ለማግኘት ከእንቅስቃሴያቸው አኳያ መቸገራቸው ተነገራቸው፡፡ስለዚህም አሊ ቡሊ ስድስት ወይም
ሰባት የቤት ልጆቻቸውን ቤተሰቦቻቸውን ጨምረው ለመላክ ተስማሙ፡፡የነጋሽ ወንድም አሰፋም
ከተላኩት መሃል ነበር፡፡የነጋሽ ግን ምን አልባትም በእድሜው ማነስ መክንያት አልተላከም ፡፡
ከላይ እንደጠቀስነው እ.ኤ.አ በ1939 የጣልያን ወረራ ከማብቃቱ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ነጋሽ
ከታላቅ ወንድሙ ጋር ለመኖር ሄደ፡፡4ከስድስት ወራት በኋላ ነጋሽ በአካባቢው በተጀመረው
የጣልያን ትምህርት ቤት ትምህርቱን ሲጀምር አሰፋ5 ግን ከአንድ ወር በኋላ ግን እዚያው ሃረርጌ
ውስጥ ወዳለው ወደ መሰላ ተዛወረ፡፡ሌላ የጣልያን ትምህርት ቤት በአካባቢው ስላልነበረ ነጋሽ
ወደ ቄስ ትምህርት ቤት መመለስ ነበረበት፡፡በቄስ ትምህርት ቤቱም ወንጌል፤ዳዊትና ዜማን አጠና፡፡
የኔታው ችሎታቸው እስከዚህም ስለነበር ነጋሽ ግዕዝን በአግባቡ አላጠናም፡፡6 እንደነገረኝ ከሆነ
አሁን ምንም ግዕዝ አያውቅም ፡፡ተማሪዎቹ ምንም ሳይገባቸው እንዲሁ በደመነፍስ ነበር የሚማሩት
ብሎኛል፡፡ነጋሽም ከጊዜያት በኋላ የቄስ ትምህርቱን ሲያስታውስ እንደባከነ ጊዜ ነበር የሚሰማው፡፡
ከጣልያን መውጣት በኋላ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት ጎልቶ መታየት ጣልያኖቹንም በሲጋራ ማጨስ
፤ስኳር መጠቀምና ሴተኛ አዳሪነትን በማስተማር መወንጀል የጊዜው ፋሽን ሆነ፡፡ይህ የሴተኛ
አዳሪዎቹ ሃሳብ ጣልያኖቹ የአርበኞቹን ሚስቶች እነሱ ዱር ቤቴ ብለው በወጡበት ወሽመው
በመተዋቸው የተስፋፋ ነው፡፡ነጋሽ እንደሚለው ከሆነም “እነዚህ ሴቶች ከዛ በኋላ ቡና ቤቶችን
ከፍተው ስራዬ ብለው ሴተኛ አዳሪነቱን ተያያዙት በዛም የተነሳ ሽርሙጥና ተስፋፋ ሴተኛ አዳሪነት
ከዚያ በፊትም የነበረ ሲሆን ኢትዮጵያውያን በዚህ ጉዳይ በፊትም ሆነ አሁን እንዝህላል ናቸው”
125
ጥቋቁር አናብስት
አሰፋ ገብረማርያም በጣልያን ጊዜም ሆነ በኋላ ስለነበረው የሴተኛ አዳሪነት ችግር የጻፈው መጽሐፍ
ነበር፡፡ይህ መጽሐፉ ለሴት ልጃገረዶች ሞራላዊ ይዘት ያለው የሴተኛ አዳሪነት ህይወትን መጥፎነት
ለሴት ልጆች የሚሰብክ እነሱንም በሚያስጠነቅቅ ሁኔታ የተጻፈ ነበር፡፡ነጋሽ ወንድሙ አሰፋ
ከጣልያኖች ጋር የነበረውን የቅርርብ ኃጥያቱን በዚህ ብቸኛ ስራው ከትከሻው የማውረድ ስርየትን
ለመፈጸም ያደረገው እንዳልሆነ ነው የሚያስበው፡፡ከወንደሙ ጋር ስለ ብቸኛ ልብ ወለዱ "እንደ
ወጣች ቀረች" ተነጋግረው ስለማያውቁ እርግጠኛ መሆን አልቻለም፡፡
አሰበ ተፈሪ ላይ አሰፋ ለክፍለ ሃገሩ አስተዳደር በጸሃፊነት ተቀጠረ፡፡ይህንን ስራም ከ 7 ወር እስከ
አንድ አመት ለሚደርስ ግዜ እዚያው አሰበ ተፈሪ ላይ ሆኖ ሰርቶታል፡፡8 ነጋሽ ደግሞ ለመጀመርያ
ጊዜ በእንግሊዘኛ ትምህርት ወደ ሚሰጥበት ትምህርት ቤት ሲገባ በዚያም እንደ አዲስ ሆሄያቱን
በእንግዳ ቅደም ተከተል ተምሮ ሌሎች ላይ መድረስ ተቸገረ፡፡ነገር ግን እንግሊዘኛን ለመማር
ስለጓጓ ውጤታማ ሆኗል፡፡ታፈሰ አስራትና አንድ ሌላ ጥላሁን የሚባሉ መምህራንን በተለይ
ያስታውሳል፡፡
በአሰበ ተፈሪ ቆይታው ማሳረግያ ላይ ነጋሽ ወባ ይዛው ለህክምና ወደ ሃረር ከወንድሙ ጋር ሄደ፡፡
ከሁለት ሳምንት ቆይታ በኋላ ወደ አዲሳ አበባ ተጉዘው ከአጎታቸው ኮሎኔል አባተ አሊ ዘንድ
ተቀመጡ፡፡9አጎታቸው ኮሎኔል አባተ የፖሊስ መኮንን ሲሆን በኋላም የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ
ሆኖ ነበር፡፡መኖርያው አሜሪካ ኤምበሲ አካባቢ ከአምሐ ደስታ ትምህርት ቤት ትይዩ ነበር፡፡አሰፋ
በጸሃፊነት በጦር ሚንስቴር ውስጥ ሲቀጠር ነጋሽ ወደ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ገባ፡፡ከሶስተኛ
ወይም አራተኛ ክፍል ቢጀምርም መምህራኑ ጥሩ የእንግሊዘኛ እውቀት አልነበራቸውም፡፡
አንዳንዶቹ በኬንያ በስደት በወረራው ወቅት የለቃቀሟት ስለነበረች ነጋሽ ጥሩ ውጤት ለማግኘት
ቀሎታል፡፡ ከጥቂት ወራት በኋላ ከፍ ወዳሉ ክፍሎች ተዘዋወረ፡፡እዛም መምህራኑ የተሻሉ ሲሆኑ
አንዳንዶቹ እንግሊዛውያን አብዛኞቹ ሃበሾች ነበሩ፡፡ከትምህርት መማርያ መጽሐፍቶች መሃል
የሚያስታውሰው አንዱ መጻሐፍ Ethiopian lives ይሰኛል፡፡
ከተወሰኑ አመታት በኋላ ከብሪቲሽ ካውንስል የመጣች ወይዘሮ ቡከር የተባለች እንግሊዛዊ ሴት
የመምህራን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት እንደምትጀምር ጥሩ የተባሉ ተማሪዎችም ወደ አውሮጳ
ተጉዘው የመማር እድል እንደሚያገኙ ገለጸች፡፡እሱ ከሚማርበት ክፍል አራት ወይም አምስት
ተማሪዎች የመምህራን ማሰልጠኛውን በ1944 እ.ኤ.አ ተቀላቀሉ፡፡ነጋሽም ከነሱ መሃል አንዱ
ነበር፡፡እስከ 1946 እ.ኤ.አ አቆጣጠር እዚያው አጠና፡፡ የሁለት አመቱ ኮርስ ለአንደኛ ደረጃ
126
ጥቋቁር አናብስት
በወቅቱ ጥቂት የአማርኛ ስነ ጽሁፍ ስራዎች ነበር ማግኘት የሚቻለው፡፡ነጋሽ ደግሞ ከዛ ውስጥ
የተወሰኑትን አንብቧል፡፡በዚህ ወቅት ነበር ከከበደ ሚካኤል ታሪክና ምሳሌ ጋር ለመተዋወቅ ፤
የተክለ ጻዲቅ ታሪክ መጻሕፍትን ለማንበብ የበቃው፡፡(እኚህ ደራሲ እንደውም አንድ ክፍል
አስተምረዋቸው ነበር፡፡መጻሐፎቻቸው በግሩም አማርኛ የተጻፉ ሲሆኑ አንዳንዶች ከታሪካዊ
ይዘታቸው በተጨማሪ ባላቸው ስነጽሁፋዊ ጥራት ይመዝኗቸዋል፡፡)የአለቃ ታዬ የኢትዮጵያ ታሪክ
(እንደ ነጋሽ ትውስታ ከሆነ አለቃ ታዬ ለኦሮሞ የነበራቸው አመለካከት የወረደ ነበር) እና ታዋቂው
አማርኛ ስዋሰው መማርያ የሆነው የመርስኤ ሀዘን ወልደቂርቆስ ኢትዮጵያውያን በወቅቱ ማግኘት
የሚችሏቸው መጻሕፍት ነበሩ፡፡ነጋሽ ስለ አማርኛ ጽሁፎቹ እስከዚህም ስለሆነ ፈተናን ለማለፍ
እንጂ ለመዝናናት አልነበረም የሚያነባቸው፡፡
ከመምህራን ማሰልጠኛ እ.ኤ.አ በ1946 ዓ.ም ከተመረቀ በኋላ ነጋሽ ጅማ ወደ ሚገኘው (the
sudan interior mission missionaries) ትምህርት ቤት ተልኮ ለማስተማር እንዲችል
ሚስዮናውያኑን በመጠየቅ ማመልከቻ አስገባ፡፡ይህንን ስራ የፈለገበት መክንያት የተሻለ እንግሊዘኛ
ለመማርና በእነሱ በኩል የሚመጣ የውጪ እድል ካለ ለማግኘት ሲል ነበር፡፡ስራው ተሰጥቶት 24
ተማሪዎች የነበሩበትን ክፍል ለአንድ አመት አስተማረ፡፡ሚስዮናውያኑ ጥሩና ሃይማኖተኛ ሆነው
አገኛቸው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በየቀኑ ማንበብ በትርፍ ሰአቱም የስብከት ዘዴዎችን ማጥናት ጀመረ፡፡
ይህ ለነጋሽ አይከብድም፡፡(ሃይማኖተኛና ከቤቱ አጠገብ ያለው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ
ቤትክርስትያን የሚሄድ ቢሆንም ያን ያህል ጠንካራ አማኝ አይደለሁም ይላል፡፡በንፋስ ስልክ
አካባቢም ከቪላ ቨርዴ አጠገብ የያሬድ ትምህርት ቤትን ለማሰራት የተቋቋመው ኮሚቴም
ሊቀመንበር ስለነበር ትንሽም ብትሆን የሃይማኖተኝነት እርሾ ውስጡ ሳትኖር አትቀርም)
ከአንድ አመት የጅማ ቆይታ በኋላ ነጋሽ ለስራው ተስማሚው ሰው እንዳልሆነ እየተሰማው መጣ ፡፡
ስለዚህ ኮተቤ ለሚገኘው ለቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አመልክቶ
127
ጥቋቁር አናብስት
(በወንድሙ አሰፋ ተጽእኖ) የመግቢያ ፈተናውን አለፎ ለመግባት ቻለ፡፡በዚያ ከ 1948 እ.ኤ.አ
ጀምሮ እስከ 1950 መጨረሻ ድረስ ለሶስት አመታት 10ኛና 11ኛ ክፍልን እየተከታተለ ቆየ10
አስተማሪዎቹ በአብዛኛው ስዊድናዊያን ሲሆኑ የተወሰኑ ካናዳውያን ነበሩ ይላል፡፡
ከሁለተኛ ደረጃ በኋላ በ1950 እ.ኤ.አ የተመሰረተውን የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ኮሌጅን ተቀላቀለ፡
፡ ከኮተቤው ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ፤ ከጄኔራል ዊንጌት፤ ከተፈሪ መኮንን ከነበሩ ተማሪዎች
ተመርጠው ነበር እዚህ ኮሌጅ የገቡት፡፡በካናዳውያን ጀዝዊቶች የሚመራና ሁሉም ሰራተኞችም
ካናዳዊያን ጀዝዊቶች ነበሩ፡፡ዳይሬክተሩ ደግሞ ከንጉሱ ጋር ቅርበት የነበራቸው የተከበሩት ሉሲየን
ማት ነበሩ፡፡(ማት በቅርብ ግዜ እንደሞቱ ይናገራል)አንድ ለተፈጥሮ ሳይንስ ሌላው የጥበብ እውቀት
ጥናት በዩንቨርሲቲ ኮሌጁ ሁለት ፋከልቲዎች ነበሩ፡፡ በንግግራችን ወቅት ግን ምርጫዬ “ስህተት
ነበር” የሚለውን ለጥበብ እውቀት ጥናት ፋከልቲ ለመቀላቀል ነበር ነጋሽ የመረጠው፡፡ ሙያ
መልመድ ይሻላል በማለት፡፡በመጀመርያው አመት ኢኮኖሚክስ፤የአፍሪቃቅኝት(ታሪክና ጂኦግራፊ)፤
ፍልስፍና፤ስነአእምሮ፤አጠቃላይ ሳይንስ ወዘተ ወሰዱ፡፡
128
ጥቋቁር አናብስት
***
ከዚያ በኋላ ወደ አሜሪካን ተልኮ በሞንታና ግዛት ዩንቨርሲቲ የጋዜጠኝነት ትምህርት ቤትን
ተቀላቀለ፡፡ለዚህም መክንያቱ ለመጻፍ በመፈለጉ ነበር፡፡ትምህርት ቤት ሳለ በድርሰቶቹ ይሞገስ
ነበር፡፡ላነበባቸውም ደራስያን አድናቆት ይሰማዋል፡፡“ምንም እንኳ ሰነፍ ብሆንና ግፊት ብፈልግም
በአግባቡ ከተከፈለኝ ቀበቶዬን አጥብቄ ለመጻፍ ዝግጁ ነኝ መጻፍ በራሱ ጠቃሚ የሆነ የመማር
ሂደት ነው”ይላል፡፡በዛ ረገድም ተሰጥኦው እንዳለው ስለሚያምን ነበር ጋዜጠኝነትን ማጥናት
የጀመረው፡፡በመጀመርያ በቋንቋው እና ነገሮች በሚጓዙበት ፍጥነት የተነሳ ዩንቨርሲቲ ውስጥ ግር
ቢሰኝም እርዳታ ግን አገኘ፡፡ሰዎች መልካም እንደነበሩለትም ያምናል፡፡የውጪ የትምህርቱ እድሉ
ለሁለት አመታት ቢቆይም ነጋሽ ከዛም በላይ ለመቀጠል ፈለገ፡፡ለኢትዮጵያ መንግስት ስለ ጉዳዩ
ጻፈ፡፡ወንድሙ አሰፋም ጉዳዩን በወቅቱ ትምህርት ሚኒስቴር ከነበሩት ከበደ ሚካኤል ዘንድ
እያስጨረሰ ቆየ፡፡መንግስት በጉዳዩ ቢስማማም ለድርጊቱ ግን ቀሰስተኛ ስለነበር ነጋሽ ከሁለት
አመታት የአሜሪካ ቆይታ በኋላ መመለስ ነበረበት፡፡በማስታወቅያ ሚንስቴርም ስራ ጀመረ፡፡
በወቅቱ ልማድ እንደነበረው ከውጪ ተመላሽ ተማሪዎች ንጉሱን እጅ ለመንሳት ይሄዳሉ፡፡ ለንጉሱ
በተነገራቸው መሰረት ከበደ ሚካኤል ነጋሽን ጨምረው ሌሎች ተማሪዎችን አቀረቡ፡፡በዚህ
ስነስርአት ላይ ነበር ከበደ ሚካኤል ለንጉሱ ከተማረው ትምህርትና ከስራው አንጻር ለዚህ ተማሪ
ተጨማሪ የትምህርት እድል እንዲሰጠው ሲሉ ለነጋሽ የጠየቁለት፡፡ንጉሱ ከተወሰነ ማቅማማት
በኋላ 2 አመት እንዲጨመርለት ስለወሰኑ ነጋሽ ከ 4 ወራት በኋላ ወደ አሜሪካ ሲራኩስ
129
ጥቋቁር አናብስት
በ1959 ወይም በ1960 እ.ኤ.አ ወደ ሃገሩ ተመልሶ በኢትዮጵያ ሄራልድ ላይ መስራት ጀመረ፡፡
በወቅቱ ዶ/ር ታልቦት ነበር በማስታወቂያ ሚንስቴር ስር የሚታተመው የእንግሊዘኛ ጋዜጣ
አርታኢ፡፡ዶ/ር ታልቦት በኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ አመታትን የቆየ አፍሪቃ አሜሪካዊ ሲሆን በብዙ
መልኩ ደግ የሆነ ሰው ሲሆን ነጋሽ ግን አሜሪካን ካየው ጋር ሲያነጻጽረው ታልቦት ያን ህልም ጥሩ
የሚባል ጋዜጠኛ ባይሆንም በባለስልጣናቱ ዘንድ ጠቀሜታው የጎላ፤ተጽእኖ ፈጣሪ፤ደግ፤ ሁልጊዜም
ለእርዳታ በሩ ክፍት የሆነ ነበር ይላል፡፡
ግን በንጉሱ ላይና በመንግስት መስርያ ቤቶች ላይ የሚሰነዘር ትችት ስለሚከለከል ሰዎች ወደ ንጉሱ
በመሄድ ቅሬታቸውን ሲያቀርቡ ንጉሱ በመሃል ጣልቃ ይገባሉ፡፡እንደ ነጋሽ አባባል ከሆነ
ግርማቸው ተክለሐዋርያትና አሃዱ ሳቡሬ የፕሬስን መሻሻል የሚፈልጉ ምርጦቹ የማስታወቂያ
ሚንስትሮች ነበሩ፡፡ነጋሽ በስዩም ሃረጎት (ጊዜያዊ) እና ማሞ ታደሰ ስርም ሆኖ ሰርቷል፡፡ ያኔ
ዲፕሎማቶች በጊዜያዊ ማስታወቂያ ሚንስትርነት ይሾሙ ነበር፡፡ ለአብነትም ተስፋዬ
ገብረእግዚ11የመጨረሻው የኃይለሥላሴ ጊዜ ሚንስትር ሲሆኑ ነጋሽም በእሳቸው ስር ሰርቷል፡፡
ነጋሽ ገብረማርያም ለኢትዮጵያ ሄራልድ ለበርካታ ወራት ለአዲስ ዘመን ደግሞ ለጥቂት አመታት
ከሰራ በኋላ የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር የሶማሊያ ክፍል አደራጀ፡፡ የአምስት ወይም ስድስት ሰዎች
ቡድን አዋቅሮ ስለ ሱማልያ የተጻፈውን ሁሉ እንዲያጠኑ ተደረገ፡፡12 ነጋሽ በቡድኑ ውስጥ
´የሚድያ ወኪል´ በመሆን ተመረጠ፡፡ቡድኑ በተጠኑት ግብአቶች ላይ ተመስርቶ ጥቆማዎችን
እንዲሰጥ እንዲያማክር ሪፖርቶቹ ደግሞ ለውጪ ጉዳይ ሚኒስትር እንዲልክ ንጉሱም ዘንድ
እንዲቀርቡ ነበር የተፈለገው፡፡ነገር ግን በወቅቱ ሚኒስቴር የነበሩት ስዩም ሃረጎት ነጋሽን ወደ
ማስታወቂያ ሚንስቴር እንዲመለስ በመፈለጋቸው ለአመት ጥቂት ፈሪ ሲሆን ተመለሰ፡፡በደመወዙ
ላይም 200 ብር ጭማሪ ተደረገለት፡፡ በዚህም ወቅት የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እየተመሰረተ
ቢሆንም ነጋሽ ግን ለቴሌቪዥን ሳይሆን በሬድዮ ላይ ነበር የሚሰራው፡፡ለራድዮ ስራ አስኪያጁ
ረዳት ሆኖ በንጉሴ ሃብተ ወልድ ስር በማስታወቂያ ሚንስትሩ ውስጥ ይሰራል፡፡በዚህ ቦታ ነጋሽ
የፕሮግራም አስፈጻሚ ሲሆን በተጨማሪም በሚንስቴሩ ለውስጥ ሰራተኞች የአዘጋገብ ስልጠናን
ይሰጣል፡፡ነጋሽ በዚህ ስራ ላይ ከሶስት እስከ አራት አመታትን ቆየ፡፡ጌታቸው መካሻ በዚህ ወቅት
አዲሱ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ሆነው ተሾሙ፡፡13ነጋሽንም ዳግም ወደ አዲስ ዘመን ጋዜጣ
መልሰው ላኩት፡፡
***
ነጋሽ ገብረ ማርያም የስነ ጽሁፍ ስራውን የጀመረው 1956 በታተመው በታዋቂው እና በወጉ
በተጻፈው ልብወለዱ ሴተኛ አዳሪ ነው፡፡ለአዲስ ዘመን በሚሰራበት ወቅት ግን መጣጥፎችና
ግጥሞችን (በስሙ)ይጽፋል14፡፡እዚያው እየሰራ ባለበት ወቅት ነበር ይህንን መጽሐፍም የጻፈው፡፡
የመጀመርያ ሙከራው ሲሆን ወድያውኑ ነበር የታተመለት፡፡
***
131
ጥቋቁር አናብስት
እዚህች ላይ አረፍ ብለን ስለ ወንድሙ እንቃኛለን፡፡ ከጥቂት አመታት በፊት ወንድሙ አሰፋ
በ1956/7 ዓ.ም አካባቢ ብቸኛ ስራውን "እንደወጣች ቀረች"ን አበረከተ፡፡ከዚያ በኋላ ዳግመኛ
ልብወለድ የመጻፍ ሙከራ አላደረገም፡፡ይህም ምናልባት መጽሐፉ ከታተመ በኋላ በተጫነበት
የስራ ሸክም ይሆናል፡፡በሃገር ውስጥ ጉዳይ ሚንስትር የበላይ አስተዳዳሪ ሆኖ የቆየ ሲሆን ከጥቂት
ግዜ በኋላ ሙሉ ምክትል ሚንስቴርነቱን ተሾመ፡፡በስተመጨረሻም በህንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር
ሆኖ በኒው ዴልሂ ህንድ ለሁለት አመታት ቆየ፡፡እዚያ በነበረበት ወቅት በድባቴ ህመም ክፉኛ
ይሰቃይ ስለነበር የህክምና እርዳታ ህንድ ውስጥ ለማግኘት ሞክሯል፡፡ወደ እየሩሳሌምም በ1959
ዓ.ም አካባቢ ለመሄድና ለመፈወስ ቢሞክርም ሁሉም ውጤት አልባ ሲሆኑ ለምክክር በወንድሙ
ነጋሽ ወደ ኢትዮጵያ ተጠርቶ በ1960 ዓ.ም አካባቢ ተመልሶ መጣ፡፡ነጋሽ አብሮት ቆየ፡፡ ወደ
አማኑኤል ሆስፒታል አብረው ሄዱ፡፡ቤተሰቦቹም ከነበረበት ሁኔታ እንዲወጣ በጸበል ቢሞከሩም
ምንም ሳይረዳው ቆይቶ አሰፋ ገብረ ማርያም በጥቅምት 21 1961 ዓ.ም እራሱን በመሳርያ ተኩሶ
አጠፋ፡፡
***
በ1964/65 ዓ.ም አካባቢ ነጋሽ በኢትዮጵያ ሬድዮ በሚሰራበት ወቅት "የድል አጥቢያ አርበኛ"
የሚል ተውኔት ጽፎ ነበር፡፡ጭብጡ በጣልያን ወረራ ማብቂያ አካባቢ ወደ አርበኞች ጎራ
ስለተቀላቀሉ አርበኞች ሲሆን በተውኔቱ የተሳለውን አርበኛ ቆንጆ ሚስት አንድ የጣልያን ወታደር
ይመኛታል፡፡ባል ቢጎሳቆልም ግን ጣልያኑ ስለተገደለ ባልየው አምልጦ ጣልያኖቹ እጅ
ከመስጠታቸው በፊት ኢትዮጵያንም ሳይለቁ ወደ አርበኞቹ ጎራ ተቀላቀለ፡፡ሚስቱ ከጣልያኑ ልጅ
አርግዛ ስለነበር ወለደች፡፡ልጁንም ባልየው በጉዲፈቻ መልክ ወሰደው፡፡ይህ ቴአትር በቀዳማዊ
ኃይለሥላሴ ቴአትር(አሁን ብሔራዊ ቴአትር) ለመድረክ በቃ፡፡
ነጋሽ በዚህ ወቅት ነበር በዋርሳው በአሰፋ ሚስት የወንድሙን ሃሳብ ሰርቋል የሚል ክስ የቀረበበት፡
፡ነጋሽ የዚህ ክስ መነሾ ወንድሙ የተናዘዘለትን የ20000 ብር ኑዛዜ ስለፈለገችው ነበር ይላል፡፡ነገሩ
ፍርድ ቤት ደርሶ ብዙም ተቀባይነትን ሳያገኝ የተጣጣለ ሲሆን እሷም ተሸነፈች፡፡ ምንም እንኳን
ቢረታም ነጋሽ 20000 ብሩን አላገኘም፡፡የኔ "ጀግኖች" በወንድሜ መጽሐፍ ላይ ከተሳሉት ይለያሉ
ሲል የሃሳብ ስርቆት ክሱን ያስተባብላል፡፡
***
132
ጥቋቁር አናብስት
***
ነጋሽ ጡረታ ሲወጣ ለመጻፍ የተሻለ ጊዜን አገኘ፡፡እንደ ጡረተኛ ሽማግሌ በተቆጠረበት ወቅት ነበር
በአዲሱ ችግሩ ላይ ባተኮረውና በብሄራዊ ቴአትር ለመድረክ በበቃው ተውኔት ብቅ ያለው፡፡
ተውኔቱ በኢትዮጵያ ልኬት የአመቱ ምርጥ ተውኔት ሊባል ይችላል፡፡ሃሳቡን ያገኘው ከእውነተኛ
የጡረታ ህይወት ተሞክሮ ነበር፡፡ከእሱ ጋር ተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ሰዎች የሚያዘወትሩባት
ቡና ቤት ውስጥ እየተገናኙ እንደ ምሁርነታቸው ምን ማበርከት እንደሚችሉ ሲወያዩ አብዛኛው
ተስፋ አስቆራጭ ሃሳቦችን በህይወትና በጊዜያቸው ምን ለመስራት በሚያደርጉት ውይይት ዙርያ
ቢሰነዝሩም አንዳንዶች ግን ካፌ ወይንም ክለብ ከፍተው ተጋባዥ እንግዶችን የመጋበዝ ዐይነት
ሃሳብ ነበራቸው፡፡ ቢሆንም በተለይ የኢትዮጵያ ባንኮች በጡረታ ለወጡ ሰዎች ማበደር
ስለማይችሉ ያለ ገንዘብ መስራት አስቸጋሪ ነበር፡፡ከመሃላቸው ካለ አንድ ሃብታም ሰው ለመበደር
ቢጠይቁ እሱም አሻፈረኝ አለ፡፡ከዛ በኋላ አንዲትን ጥሩ ቤት ያላትን አሮጊት ሴትዮ ሌላ ቤት ያለው
ሽማግሌ አግብቶ የእሷን ቤት ለቡድኑ የመገናኛ ቦታ የማድረግ ሃሳብ መጣ 15ተውኔቱ በቡና ቤቱ
133
ጥቋቁር አናብስት
ነጋሽ ገብረ ማርያም በተውኔት ጽሁፍ ላይም ሆነ በቴአትር ምንም ትምህርት አልነበረውም፡፡
እንደሱ እምነት ከሆነ ግን የሰዎችን ልማድና ጸባይን ማወቁ ተውኔቱን ለመጻፍ ጠቃሚ እንደሆነለት
ይናገራል፡፡በተለይም በትውልድ ቦታው ሃረርጌ ከተለያዩ ብሄር የተገኙ ሰዎችን በአንድ ቦታ ሲኖሩ
አስተውሏል፡፡ይህንንም በመመንዘር ለጽሁፍ ስራው ግብአትነት ተጠቅሞበታል፡፡በቴክኒኩ ረገድ
ድክመቶች እንዳሉበት ያውቃል፡፡በአብዮታዊት ኢትዮጵያ ለመጻፍ ያየው ችግር ይሄ ብቻም
አልነበረም፡፡ሌላ ከባድ ተግዳሮትም ነበር፡፡በሚቀጥለው "ሐመልማል" በተሰኘ ተውኔቱ
የጠበቀው፡፡
ተውኔቱ ስለ ቤተሰብ ችግሮች ነበር ፡፡ሀመልማል 18 አመት ሲሞላት ወጣት ስትሆን እናቷ አንድ
የመንዝ ፊትአውራሪ ለማግባት የታጨች ወይዘሮ ነገር ግን ሃብታም ጉራጌ ያገባች ነበረች፡፡
የሐመልማል ወላጆች ሌሎችን ልጆችንም አላፈሩም፡፡ ከሐመልማል ገጽታ መመሳሰል ጋር ተደርቦ
የሐመልማል እናት የአሁኑ በሏ መሃን መሆኑንና ልጇ ከበፊት ወዳጇ የተወለደች እንደሆነች
ባወቀች ጊዜ ህመም ላይ ስለነበረች ትክከለኛ አባቷ ማን እንደሆነ ለመንገር ታሪኩን ለልጇ
ሐመልማል በጀመረችበት ወቅት ባልየው ቢገባም መናገሩን አላቋረጠችም፡፡16ባልየው በሚሰማው
ነገር ተቆጣ፡፡ከዚያ በኋላ ሚስትየው ወደ ሆስፒታል ተወስዳ ዳነች፡፡በቁርባን በቤተክርስቲያን
ስለተጋቡም መለያየት አልቻሉምና በምትኩ ባልየው ሐመልማልን ከቤት አስወጥቶ አባሯት
134
ጥቋቁር አናብስት
ተቸገረች፡፡ነገር ግን በመጨረሻ የአባቷ ነብስ አባት የሆኑ አንድ ቄስ ባልና ሚስቱን በማስታረቃቸው
ባልየው ይቅርታ አድርጎ የእንጀራ ልጁን ይቀበላል፡፡ሰላምም ወደ ቤታቸው ይመለሳል፡፡
የርእዮተ አለም ወጣቶቹ ኮሚቴ ትያትሩን ከገመገሙ በኋላ የቄሱን ክፍል ቆርጦ እንዲያወጣ
ይነግሩታል ነጋሽ ግን ጠቃሚ በመሆኑ አይሆንም አለ፡፡ቀጥለው ቄሱ እንደ ቂላቂል ገጸ ባህርይ ሆኖ
በማርክሲስት ሌኒኒስት አስተሳሰብ አራማጅነት እንዲወከል ፈለጉ፡፡ነጋሽ ግን ቄሱ ጠቃሚ ሚና
በተውኔቱ ውስጥ እንዳላቸው ከከባድ ቁምነገሮች ዙርያ የሚገኙና መቀየር የማይችሉ መሆናቸውን
ተናገረ፡፡የመጨረሻውን እርቀ ሰላም የማያወርዱ ከመሆናቸው ሌላ እርሱ እራሱ የማርክሲስት
ሌኒኒስት ርእዮት አራማጅ ባለመሆኑ ከነሱ ጋር እንደማይስማማ ነገራቸው፡፡
እ.ኤ.አ በ1990 የጻፈው አዲሱ ተውኔት "አስመሳይ ሃኪሞች" ይሰኛል፡፡ስለኤድስ በሽታ የተጻፈ
ሲሆን በሽታው ገና አፍላ በነበረበት ወቅት ወይም በታወቀ ሰሞን ሁሉን እናድናለን ስለሚሉ የባህል
ህክምና አዋቂዎች ነበር የጻፈው፡፡በተውኔቱ የባህል ሃኪሙ ወጣት ልጅ17እና ጓደኞቹ ኤች.አይ.ቪ
ኤድስን እናድናለን በማለት ክሊኒክ ይከፍታሉ፡፡18ምንም ላቦራቶሪም ሆነ ሌላ ቁሳቁስ አልነበረም፡፡
አንድ ዶክተር እንዲሁም የወንጀል ፍርድ ቤት አማካሪ የነበረ ሰው ህመምተኛ ተመስሎ ይሄዳል፡፡
በክሊኒኩ ያሉ ወጣቶች ትክክለኛ ያልሆነ መድሃኒት ለሰዎች እንደሚሰጡ ይደረስበትና ለጤና
ጥበቃ ሚኒስቴር ሪፖርት ይደረጋል፡፡ተከሰውም ወደ ፍርድ ቤት ይሄዳሉ፡፡ ዶክተሩም
ይመሰክርባቸዋል፡፡ምንም እንኳን በባህላዊ ህክምና ቤተ ሙከራ የሚባል እንደሌለ በማስረዳት
ለመከራከር ቢሞክሩም ሃሳዊ ሃኪሞቹ ተቀጥተው ይታሰራሉ፡፡ነጋሽ መልእክት ያለው ኮመዲ ነው
ይለዋል፡፡
135
ጥቋቁር አናብስት
ስለዚህ በአሁን ሰአት በአእምሮው ከሚብላሉት ሁለት የልብወለድ ሃሳቦች ውጪ ሌላ የተለየ እቅድ
የለውም፡፡
ነጋሽ ገብረማርያም እድሜ ልኩን ወንደላጤ ነበር፡፡ነገር ግን ከ1982 እ.ኤ.አ ጀምሮ ከአንዲት ሴት
ጋር መኖር ጀመረ፡፡በ1986 አቆጣጠር የመጀመርያ አጋማሽ ላይም ወንድ ልጅ ወለዱ፡፡ከዛ ቀደም
ወደ ሌሎች ሴቶች ቢሄድም ሌላ ልጅ ግን እንዳለው አያውቅም፡፡ቢያረግዙ እንኳን ከኑሮዋቸው
አንጻር ሃላፊነትን ወስዶ ይቀበል ነበር ለማለት ያዳግታል፡፡“ተራ ህይወት”ነበር የኖርኩት ይላል፡፡
ነጋሽ ከእናት አባት ወንድሙ አሰፋ ጋር በጣም ይቀራረቡ ነበር፡፡ከሱም ብቻ ሳይሆን ከእናቱ
ከሚወለዱት ኤልያስ (ጋብቻውና ጊዜው ደራሲ)እና ከአቶ በሻህና ከነሱ እናት ከሚወለዱ ሁለት
እህቶቹ ጋርም ቅርርብ አለው፡፡የነጋሽ የመጀመርያ ስራው ሴተኛ አዳሪ ሲሆን እናኑ "አጎናፍር"
በሚል የብእር ስም የተጻፈና በጥልቀት ስለ ሴተኛ አዳሪ ህይወት የሚዳስስ ነበር፡፡በተለይ
ስለምታዘወትራቸው የወሲብ ስልቶችና ከደንበኞች ስለምትማራቸው ወይም ከሌሎች ሴተኛ
አዳሪዎች አልያም ከመጻሕፍት (እንግሊዘኛንም ሆነ አማርኛ ማንበብ ትችላለች)ስለምታገኛቸው
136
ጥቋቁር አናብስት
ማስታወሻ
1ከመንዝ ሲሆን በሐረርጌና ቆይቶም በወለጋ የአውራጃ አስተዳደር የነበሩት የቀኝ አዝማች ተስፋ
ልጅ ነው፡፡
3 በግምት እ.ኤ.አ በ1919 ወይም በ1920 ሲሆን የተወለደው እለተ እረፍቱ ጥቅምት 21 1961
ነው፡፡
138
ጥቋቁር አናብስት
10ከእሱ ጋር አብረው ከተማሩት መሃል በህይወት ጎዳና የተሳካላቸው እንደ በትሩ አድማሱ ያሉ
የኢትዮጵያ ቴሌኮሚዩኒኬሽን ስራአስኪያጅን የመሳሰሉ ስኬታማ ሰዎች ይገኙባቸዋል፡፡
በጨዋታችን ወራትም በኬንያ የሚገኘው አለምአቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ ነበር፡፡ነገር ግን
ይህንን ስራ የተረከበው ከስልሳ ስድስቱ አብዮት መፈንዳት በኋላ አምስት ወይም የስድስት አመታት
እስርን ተከትሎ ነበር፡፡ሌላኛው አብረውት ከተማሩት መሃል የተሳካለት ሰው የሚባለው ከበደ
አካለ ወልድ ሲሆን የአሰብ ማጣርያ ሃላፊ ነበር፡፡እንዲሁም ሌሎች አሉ፡፡
11እዚህ ላይ በግርማ ታደሰ የተጻፈ የግጥም ስብስብ የሆነው "ተናገር አንተ ሐውልት" እንዴት
በተስፋይ ገብረእግዚ እንደታገደ እገልጻለሁ፡፡በገበያ ላይ ለተወሰነ ጊዜ ከቆየ በኋላ መድበሉ
መጠርያ የሆነው ግጥም እኔ የስርጭት አርታኢ ሆኜ በምሰራበት ራድዮ ላይ በኔ ፍቃድ ተነበበ፡፡
ተስፋዬ ገብረእግዚ ቅሬታውን ለማሰማት መልእክተኛ ላከ፡፡እኔም መጽሐፉ በኢትዮጵያ የሳንሱር
ክፍሎች ታይቶ ይለፍ እንደተሰጠውና በገበያ ላይ እንደሚገኝ ሳንሱር አድራጊዎችን ሳንሱር
የማድረግ ስራ የኔ እንዳልሆነም አያይዤ ተናገርኩ፡፡ወድያውኑ መጽሐፉ ታገደ ከመጻህፍት መሸጫ
ቤቶችም ተለቀመ፡፡ተስፋዬ የግጥሙ ትርጉም እንደተረዳውና ለንጉሱ እንደተሰነዘረ ስድብ ነው
የቆጠረው፡፡በግጥሙ ውስጥ ያለው ሰው የረጀና ብዙ ያየ የአክሱምን ሃውልት ብልሃት
እንዲስተምረው የሚጠይቀው ኃይለሥላሴን ለማለት ነው ይሄ ደግሞ ንጉሱን ደደብ ለማለትና
የተሻለ ብልሃት እንደሚያስፈልጋቸው ያሳያል እንደማለት ነው የታሰበው (ይሄ ሁሉ በተስፋዬ
መልእክተኛ ነበር የሚገለጽልኝ)«ብልሁ»ተስፋዬ በዶክትሬት ዲግሪው የሚኮራና በክብር
ስሙ«ዶክተር»ካልተባለ ሰዎችን የማያናግር ሰው ከሌሎች በተሻለ ስውር ትርጉሞችን የማወቅ
ችሎታ እንዳለው ለማሳየት ፈለገ፡፡ስለዚህ በራድዮው በተላለፈ ሌላ መንደራችን በተሰኘ ግጥምም
መናደዱን ነገሩኝ፡፡ከመንግስታዊው ጋዜጣ የዛሬይቱ ኢትዮጵያ መወሰዱን ስናገር ምንስትሩ
ከጋዜጣው አርታኢ ጋር መጋጨታቸውን ተነገረኝ፡፡በመሃከላቸው ያለውን ችግር እራሳቸው
እንዲፈቱ እና እኔ ጋር ለዳኝነት እንዳይመጡ ነገርኳቸው፡፡ተስፋዬ ገብረ እግዚ ትግሬ ሲሆን
በ1966 ተገድሏል፡፡
139
ጥቋቁር አናብስት
18)ያን ያህል በኢትዮጵያ ሩቅ የሚባል አይደለም ፡፡ምንአልባትም ሶስት አራተኛው ህዝብ በባህላዊ
ህክምና የሚያምንና አድርግ የተባለውንም የሚያደርግ ነው
140
ጥቋቁር አናብስት
መኮንን እንዳልካቸው
መሳፍንታዊው ፖለቲከኛና፣ ወግ አጥባቂው ፀሀፊ
ራስ ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸውእኔ ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣቴ
ከሁለት አመታት በፊት ስለሞቱ የመገናኘት እድል አልነበረንም፡፡
ከመጣሁም በኋላ በአማርኛ ስነጽሁፍ እስክሳብ ድረስም ጥቂት
አመታትን ወስዶብኝ ስለነበር እዚህ በነበርኩባቸው የመጀመርያዎቹ
አመታ ለእሳቸው ቃለ-መጤቅ ለማድረግ እንኳን ምናልባት
ባላሰብኩም ነበር፡፡ስለሆነም እዚህ ያሰፈርኳቸው ማስታወሻዎችና
በሌሎች ሰዎች ማስታወሻዎችና ትውስታዎች ላይ የተመሰረቱ ናቸው፡
፡ምንም እንኳን አንዳንድ ሰዎች በጭምጭምታ ደረጃ ስለሳቸው የሚነገሩና የተጻፉ ነገሮች ቢኖሩም
እዚህ በአማርኛ የተጻፉና በቀላል ሊገኙ የማይችሉ ምንጮችን መጠቀም ነው የፈለግሁት፡፡ዋቢ
ምንጮቼ ለአርባ ቀን መታሰብያቸው የታተመች ማስታወሻና በደምሰው በቀለ የተሰራ ያልታተመ
ጽሁፍ ነው፡፡መኮንንም በመጽሐፍቶቻቸው ስለራሳቸው የተወሰኑ ነገሮችን ይናገራሉ፡፡የልብወለድ
ስራዎቻቸውም በእራሳቸው የህይወት ልምድና ታሪክ ዙርያ የተከተቡ ናቸው፡፡1
141
ጥቋቁር አናብስት
***
መኮንን እንዳልካቸው በሰሜን ሸዋ ተጉለት ውስጥ አዲስጌ ላይ የካቲት10 1883 ዓ.ም ተወለዱ፡፡
አባታቸው ባላምባራስ እንዳልካቸው አብሪቅ ይባላሉ፡፡የታወቁ ጦረኛ፤ፈረስ ጋላቢና አዳኝ ሲሆኑ
በምኒሊክ የግዛት ማስፋት ጦርነቶች መሃል መኮንን በተወለዱበት አመት1883 ወደ ወላይታ
ዘምተው በ30 አመታቸው በዚያው ጦርነት ሞተዋል፡፡መጀመርያ እዚያው ቢቀበሩም በ7 አመቱ
አጽማቸው ተሰብስቦ ወደ ታዋቂው ደብረ ሊባኖስ ገዳም ተዛውሯል፡፡
የመኮንን እናት ወይዘሮ አቦነሽ ተክለማርያም ከንጉሳውያን ቤተሰብ ነበሩ ባላምባራስ ከሞቱ ከብዙ
አመታት በኋላም ደጃዝማች ተሰማ ዳርጌን አግብተው ነበር፡፡እሳቸው ሲሞቱ ደግሞ ራስ ደምሰው
ነሲቡን አገቡ፡፡ራስ ደምሰው ወይዘሮዋን ያገቡት የራስ ቢትወደድ ተሰማ ናደው እህት በመሆናቸው
142
ጥቋቁር አናብስት
ነው ይባላል፡፡ ተሰማ ናደው በምኒሊክ ጊዜ ሃያል ሰው የነበሩ ሲሆን የአቤቶ እያሱ ሞግዚትና
እንደራሴ ነበሩ፡፡ተሰማ ናደው ሲሞቱ ደምሰው አቦነሽን ፈትተው የአቤቶ እያሱን እህት የሆነችውን
ወይዘሮ ስህንን ለማግባት ጠየቁ፡፡ እሷ ግን ስሌቱን ተረድታ በጣም ጠላቻቸው፡፡ ሌላው ምክንያት
ደግሞ ሟቹ ባሏ ደጃች ብሩ ኃይለማርያም የወይዘሮ አቦነሽ ወንድም ስለነበሩ ነው፡፡ወድያው
ደምሰው እንደፈቷት አቦነሽ ሞተች፡፡
ከአባታቸው ሞት በኋላ እናታቸው መኮንንን ከመምሬ አካሉ ኪዳነ ማርያም ዘንድ ሰላ ድንጋይ
አምጥተው እንዲያስተምሯቸው ጠየቁ፡፡በጣም ጎበዝ ተማሪ ነበር ሲሉ መምህሩ ለዘመዶቻቸው
ይናገራሉ፡፡ቆይቶም መኮንን ከአያታቸው ወይዘሮ ቆንጂት ጋር በአዲስጌ ለተወሰኑ አመታት መኖር
ጀመሩ፡፡ ከዚያ በኋላ ወደ ደብረ ሊባኖስ ተልከው ተጨማሪ የቤተክህነት ትምህርትን ቀስመዋል፡፡
ከመምህሮቻው አንዱ ወልደ ጻዲቅ ወልደ ሃዋርያት የሴት ሃያታቸው ሰራተኛ ነበር3፡፡በሃገርኛ
እውቀቱም የበለጸገ እሙር እንደነበር ሰዎች ይናገሩለታል፡፡
143
ጥቋቁር አናብስት
ምኒሊክ ህመሙ እየጠናባቸው ስለሄደ በደጃች ተሰማ ናደው እንደራሴነት አልጋውን ለልጅ
ልጃቸው አቤቶ እያሱ አወረሱ፡፡ተሰማ ሚያዝያ 11 በ1903 ዓ.ም ወድያውኑ አረፉ፡፡መኮንንም
አቤቶ እያሱን በቀብሩ ጊዜ የተመለከቷቸው ሲሆን በሌላ ብዙ ሁኔታዎች ውስጥም ሰፊ የመገናኘት
እድል ነበራቸው፡፡6
የራስ ተሰማ መሞት ሃገሪቱን ለውዥንብር ዳረጋት፡፡የሸዋ መኳንንት እያሱን ከሃላፊነት አስወግደው
የምኒሊክን ሴት ልጅ ዘውዲቱን በምትኩ ወደ አልጋው ለማምጣት ፈለጉ፡፡የእያሱም ደጋፊዎች
የዋዛ አልነበሩም፡፡ ከነሱም መሃል አንዱ መኮንን እንዳልካቸው ነበሩ በአንድ መጽሐፋቸው ላይ
እንዳሰፈሩት፡፡ራስ አባተ (የመኮንንን አክስት የሚያገቡ) ለአቤቶ እያሱ ጠባቂ ለመሆን ቢሞክሩም
አልቻሉም፡፡ቆይቶ ራስ አባተ ተይዘው ለእስር ወደ ደሴ ተላኩ7 መኮንን አባተ ወደ ደሴ ሊያቀኑ
ሲሉ ሄደው ተሰናበቷቸው፡፡በዚህ ወቅት ነበር ከአባተ ጋር ሆኖው ሳሉ እያሱ ሊያዩዋቸው የቻሉት፡
፡ ከዚህች ክስተት በኋላ ብዙ አዳዲስ ሰዎች ተሾሙ፡፡መኮንን ግን እያሱን መደገፋቸውን ቢቀጥሉም
144
ጥቋቁር አናብስት
በ1907 ዓ.ም መኮንን የራስ ቢትወደድ መንገሻን ልጅ ወይዘሮ ዘውዲቱ መንገሻን አገቡ፡፡ጎበዝና
ታጋሽ ሴት የነበረች ቢሆንም10 መኮንን ግን በመጀመርያ ትዳራቸው ብዙም ደስተኛ አልነበሩም፡፡
የልጅነት ፍቅራቸውን (የመጨረሻውን የግርጌ ማስታወሻን ይመለከቷል)ሳያስታውሱ አይቀርም፡፡
የወለዷቸው በርካታ ልጆችም ሞቱባቸው፡፡ከተወለዱላቸው አስራስድስቱ ሁለቱ ብቻ ነበሩ
ሊተርፉ የቻሉት፡፡ልጅ እንዳልካቸው መኮንንና ወይዘሮ ብርሃኔ መኮንን፡፡ሚስታቸው ዘውዲቱ
በትዩበርክሎሲስ ታማ በፍልውሃ ሆስፒታል ታክማለች፡፡በዚህ መክንያት በሀኪሞች ትዕዛዝ
አብረው እንዳይተኙ ተከልክለው ነበር፡፡ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜ መኮንን በ20 ህዳር
1928 ዓ.ም ወደ ጦር ግንባር ሲዘምቱ ሚስታቸው በጠና ታማ ነበር፡፡ወደ ድሬዳዋ ከመሄዳቸው
በፊትም በጣም ሊቀርቧት ቢሞክሩም ወድያውኑ ወደ ሃረር ሄዱ፡፡እዚያም እያሉ በታህሳስ19 ቀን
መሞቷን ተረዱ፡፡ ለጊዜው ግን መኮንን ካገቡ በኋላ ወዳሉበት ጊዜ እንመለስ፡፡
ተፈሪ መኮንን ወደ አውሮጳ ሲሄዱ የአልጋ ወራሽ ልዩ አማካሪ በመሆን አብረዋቸው ተጉዘዋል፡፡
በ1919 ዓ.ም መኮንን በነጋድራስነት ማዕረግ የንግድ ሚንስትር ሆነው ተሾሙ፡፡ወደ ሎንደንም
ኢትዮጵያን ወክለው እንዲሁም በሚንስትርነት ተጉዘዋል፡፡
አብረው በአጓጉል ቦታዎች ከተነሷቸው ፎቶዎች መሃል አንዱን ለባልየው ራስ ጉግሳ አርአያ
በመላኩ እሳቸው ለንጉሱ አሳዩዋቸው፡፡ንጉሱ መኮንንን በጥድፊያ “ታስረው” እንዲመጡ ካስደረጉ
በኋላ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ታግደው አቃቂ ባለ መኖርያቸው በጥበቃ ቆዩ፡፡ልዕልት የሻሽወርቅም
ሆለታ እናታቸው ወይዘሮ አሰለፈች ወንዴ ዘንድ (የጣይቱ አባት የብጡል ውላጅ ናቸው )እንዲቆዩ
ተደረገ፡፡እናታቸውም ንጉሱን ለምነው ወደ አዲስ አበባ አስመጧቸው፡፡ከመኮንን ጋር በሚስጥር
መገናኘታቸውን ቀጥለው በተወሰነ መልኩ ሊረዷቸው ቻሉ፡፡በመጨረሻም በብላቴን ጌታ ኅሩይ
ወልደሥላሴ አማላጅነት መኮንን ከንጉሱ ይቅርታን ቢያገኙም የሻሽ ወርቅን እንዳያዩ ተከለከሉ፡፡
የሻሽወርቅና ራስ ጉግሳም ቢሆን ተፋቱ፡፡ግን ከዚያ በኋላ ለቢትወደድ መኮንን ደምሰው እንዲዳሩ
ተወሰነ፡፡
ከሶስት አመታት በኋላ ነጋድራስ መኮንን በ1924 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ሆኑ፡፡ከአንድ
አመት በኋላ በ1925 ዓ.ም የሃገር ግዛት ሚንስቴር ምክትል ወይም ተጠባባቂ ሚንስትር ሆነው
ተሾሙ፡፡የሲቡ፤ጉዳያ እና የገንጂ ገዢም የሆኑት በዚህ ወቅት ነበር፡፡ በ1927 ዓ.ም በደጃዝማች
ማዕረግ የኢሉባቡር ገዢ ሆነው ተሾሙ፡፡
ቀጣዩ 1928 የነውጥ አመት ነበር፡፡ጣልያኖቹ ኢትዮጵያን ለመውረር በሚዘጋጁበት ወቅት መኮንን
ወደ አዲስ አበባ ጣልያን ልትወረን ስለምትችል ሃገሬውን ማንቀሳቀስ ያስፈልጋል ብለው መልእክት
ቢልኩም ጣልያን የሊግ ኦፍ ኔሽንስ አባል ስለሆነች አትወረንም የሚል ምላሽ ደረሳቸው፡፡
በግትርነት አቋማቸውን ገፍተውበት በሚቀጥለው የኃይለሥላሴ ልደት ሲከበር ኢሉባቡር ጎሬ ላይ
ሰብስበው የጣልያንን የወረራ ፍላጎት ለህዝቡ ነገሩ፡፡ እንደተነበዩትም በዚያው አመት በ1928
ጣልያን ኢትዮጵያን ወረረች፡፡
146
ጥቋቁር አናብስት
***
147
ጥቋቁር አናብስት
በስደት እያሉ መኮንን ሁለት መጻህፍትን ጽፈዋል፡፡why was the lion of Juda
defeated እና አትፍሩ ስጋችሁን ለሚበድሉ ይሰኛሉ፡፡(ማቴዎስ 10፤28 )በስደት ወቅት
መኮንን የኢትዮጵያን ስደተኞች ፍላጎት ለማሟላት የተቋቋመ ቆንስላ ፕሬዝደንት ነበሩ፡፡ ይህ
ቆንስላ የንግስት ዘውዲቱን 92 ክፍል ያለው ቤተመንግስት የሚጠቀም ሲሆን ኢጣልያም ለረዥም
ጊዜ የይገባኛል ክርክር አንስታበታለች ፡፡
***
149
ጥቋቁር አናብስት
የግርጌ ማስታወሻ
4)ከዚያ በፊት ከራስ ተሰማ ናደውና ከአንድ አጎቱ ማለትም ልጅ እንጥሊ ተክለ ማርያም ከሚባል
የእናቱ ወንድም ጋር ለአጭር ጊዜ ቆይቶ ነበር፡፡ከአጤ ምኒሊክ ጋርም ቅርበት ነበራቸው፡፡የቆንጂት
እህት የሆኑት የሴት አያቱ መድፈርያሽ ወርቅ ዘሮቻቸው የንጉሳውያን ቤተሰቦችን ያገቡ ሲሆን
መኮንንንም በማሳደጉ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡
.7)የዚህ መጽሃፍ አባዜ እስከ ህይወቱ መጨረሻ ተከትሎት ሊቆይ ይችላል፡፡ በብዙ የድርሰት
ስራዎቻቸውም ላይ ተንጸባርቆ ይታያል፡፡በአንድ ወቅት በጣም የሚያምረውን የእሳቸው የነበረ
ያልተለመደ የክርስትናና የድግምት ቅልቅል የሆነ መጸሀፍ እንድገዛ ተጠይቄ ነበር፡፡በወቅቱ ግን
አቅሜ አልፈቀደም ነበር፡፡(ምንም እንኳን ዋጋው ፍትሃዊ የነበር ቢሆንም)ምንአልባት የይምሰል
ሀይማኖተኛ የመምሰል ነገር ሳይኖርበት አይቀርም፡፡
8)ከሁለት አመታት በፊት በ1905 መኮንን የተፈሪ መኮንን ወንድም (በኣባታቸው በኩል ) ሴት
ልጅ ጎብኝቶ ነበር፡፡(ማለትም የይልማ መኮንንን)የሻሽ ወርቅ ይልማን፡፡በታመመችበት ወቅት፡፡
በወቅቱ በፍቅሯ ወድቆ ነበር፡፡ከብዙ አመታት ውጣ ውረድ በኋላ ግን ሁለተኛ ሚስቱ ልትሆን
150
ጥቋቁር አናብስት
9)ተፈሪ እንደራሴ ነበሩ ወይስ አልጋወራሽ የሚለው የሹመታቸው ሁኔታ ላይ ያከራክር ነበር፡፡
ወይም ይሄ በቆይታ ይከሰት የሚለውን ለማየት
በዚህ ወቅት የ800 ተመላሽ ወታደሮቹ ቤት በራስ እምሩ ወታደሮች መያዙን ሰማ፡፡ለመልቀቅም
አሻፈረኝ አሉ፡፡መኮንንን ለእርዳታ ቢጠይቁትም ምንም ማድረግ አልቻለም ነበር፡፡
11)ተፈሪ እንደራሴ ነበሩ ወይስ አልጋወራሽ የሚለው የሹመታቸው ሁኔታ ላይ ያከራክር ነበር፡፡
ወይም ይሄ በቆይታ ይከሰት የሚለውን ለማየት
14)በዚህ ወቅት የ800 ተመላሽ ወታደሮቹ ቤት በራስ እምሩ ወታደሮች መያዙን ሰማ፡፡
ለመልቀቅም አሻፈረኝ አሉ፡፡መኮንንን ለእርዳታ ቢጠይቁትም ምንም ማድረግ አልቻለም ነበር፡፡
15)የንጉሳዊ ዝርያ ያላቸው መኳንንት ልኡል ራስ ተብለው ሲሾሙ ከነሱ በላይ ንጉሱ ብቻ ነበር
ያሉት
151
ጥቋቁር አናብስት
ዳኛቸው ወርቁ
በአጻጻፍ ዘይቤ እና ቋንቋ ተመራማሪናፈልሳፊ የዳኛቸው ወርቁ ታሪክ
ከማንም በበለጠ መልኩ ከአባቱ ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ነበር።
ዳኛቸው ራሱ እንደነገረኝ፣ አባቱ ወርቁ በዛብህ በወጣትነታቸው
ጀብደኛ እና በብዙ መለኪያም ለየት ያሉ ሰው ነበሩ።በ1906
በድሬዳዋ በኩል ጅቡቲ ገብተው ወደ ፈረንሳይበመሻገር፣በአንደኛው
የአለም ጦርነት ላይ በፈረንሳይ ጦር ሰራዊት ተመልምለው ጀርመንን
ወግተዋል። ሶስት ጊዜ ያክል በቀላሉ ቢቆስሉም እስከ ጦርነቱ
መጨረሻ ድረስ በፓሪስ፣ ማርሴይና ቤልጂየም ውስጥ እየተዘዋወሩ ተዋግተዋል። በውጪ
ቆይታቸውም ፈረንሳይኛን አቀላጥፈው መናገር ችለዋል።ከተራ የገበሬ ቤተሰብ የተገኙ በመሆናቸው
ምንም ዐይነት መደበኛ ትምሕርት አልተከታተሉም ነበር። አማርኛ ማንበብና መጻፍ የተማሩት
እዚያው ፓሪስ ሲሆን ፈረንሳይኛንም መጻፍና ማንበብ ጨምረው ተምረዋል።የተወለዱት
በ1889ዓ.ም ይፋት፣አጋም በር ውስጥ ነበር። ፈረንሳይና ቤልጂየም ውስጥ ማዕድን ማውጫ እና
የመጠጥ ፋብሪካ ውስጥ ሰርተዋል።ቀጥለውም የሆቴል ቤት አስተናጋጅ ሆኑ። ራስ ተፈሪ(በኋላ
ቀዳማዊ ሀይለስላሴ)ልዑል እና እንደራሤ ሆነው ፓሪስን ሊጎበኙ ሲመጡ፣ ባጋጣሚ አቶ ወርቁ
ከዋና አስተናጋጆቹ አንዱ ሆነው ከሚሰሩበት ሆቴል ያርፋሉ።በወቅቱ ልዑሉ እና አጃቢዎቻቸው
ከረባት ማሰር ስለማይችሉ ከአቶ ወርቁ ከሀላፊነቶች መሀል አንዱ የእንግዶቻቸውን ከረባት ማሰር
ነበር። ዳኛቸው እንደነገረኝ ከረባት ካሰሩ የመጀመሪያዎቹ ኢትዮጲያውያን መሀል አቶ ወርቁ አንዱ
ናቸው። ከልዑል ተፈሪ ጉብኝት በፊት ወርቁ በማርሴይ እየሰራ ሳለ አስፋው ወልደጊዮርጊስ ከተባለ
ኢትዮጵያዊ ጋር ተገናኘ።አስፋውና ወርቁ የተገናኙት አስፋውን ወደ ፈረንሳይ በቤት ሠራተኝነት
ካመጡት ፈረንሳውያን ጥንዶች ጋር ተጣልቶ ከቤት ሲወጣ ነው። ወርቁ አስፋውን ወደ መኖሪያው
ወስዶ አብረው መኖር ጀመሩ። በጣም የሚዋደዱ ባልንጀሮች ሆኑ። በኋላም ወደ ፓሪስ አብረው
ተጓዙ።ልዑል ተፈሪ ለጉብኝት ወደ ፓሪስ ሲመጡ ወርቁና አስፋውም እዚያው ነበሩ።ራስ ተፈሪ
አቶ ወርቁን "እንድናስተምርህ ትፈልጋለህ?"ብለው ቢጠይቋቸው "እኔ እንኳን አልፈልግም፤
ባልንጀራዬን በኔ ምትክ ያስተምሩልኝ" አላቸው።ልዑሉም አስፋው የሚማርበትን ሁኔታ አመቻቹ።
አስፋው ወልደጊዮርጊስ ወደ ጦር ትምህርት ቤት ገብተው፣ ኋላ ላይ የኢትዮጵያ የመጀመሪያው
ጀነራል ሆኑ።ከፍዬ ላስተምርህ ቢባሉ አሻፈረኝ ያሉት ወርቁ ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ፤ ሹመትም
ሊሰጧቸው ቃል ሲገቡላቸው አቶ ወርቁ ይህንንም ተቃወሙ።በኢትዮጲያ ባህል መሰረትም ይህ
እንደ ታላቅ ብልግና/ነውር የሚቆጠር ነበር። በዚህም ምክንያት አቶ ወርቁ ዘይግተው ወደ
ሀገራቸው ከተመለሱ በኋላ ብዙ እንግልት ደርሶባቸዋል። ብዙዎች ራስ ተፈሪን እንደዚያ
ካሳፈሯቸው በኋላ ወደ ሀገራቸው እንዳይመለሱ በጥብቅ መክረዋቸው ነበር። ወርቁ ምክሩን ወደ
152
ጥቋቁር አናብስት
ጎን ትተው በመጨረሻ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ ግንወደ ገጠሩ ገለል ብለው “ከራስ ተፈሪ መደበቅ”
ነበረባቸው።በ1918 በደጃዝማች ወዳጄ፣ኋላ ሊጋባ(ወደ ንጉሱ ለመቅረብ ደጅ ተጠንቶ ፍቃደኝነቱ
የሚጠየቅ ባለማእረግ)እና የክቡር ዘበኛ ኃላፊ እርዳታ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ።ሊጋባ ወዳጄ፣ወርቁ
ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲቆዩቢመርጡም፣እሳቸው ግን ወደ ፈረንሳይ መመለስ ፈለጉ። ስለዚህ
በ1919 ዓ.ም ዳግም ወደ ፈረንሳይ“ኮበለሉ”። ኢትዮጵያ ውስጥ እያሉ አሸሼ ገዳሜ እያሉ
ብራቸውን ሁሉ ጨርሰዋል። ከሁለት ዓመት በኋላ በ1921/22 ዳግም ፈረንሳይን ላለመርገጥ
ቆርጠው ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ፣1000 የማርትሬዛ ጠገራ ብር ይዘው ነበር። አሁንም ወደ
ገጠርገቡ። በ1922 ውሀ–ጠገብ በምትባል መንደር ጠቅልለው ገብተው፣ዘመናዊ ልብሳቸውን
"አሽቀንጥረው ጣሉና"፣ "በባዶ እግሩ የሚያርስ ገበሬ" ሆኑ። ውሀ–ጠገብ በአብዲላቅ ወረዳ፣
ከደብረሲና በደቡብ በኩል 20 ኪሜ ርቀት ላይ የምትገኝ ትንሽ መንደር ነች። "እንደ ደብረሲና
ብርዳማ አልነበረችም (ደብረሲና በኢትዮጵያ በጣም ብርዳማ ከሆኑ ቦታዎች አንዷ ናት)።ውሀ–
ጠገብ ጥሩ፣ሞቃትወይናደጋ የአየር ንብረት አላት። ውሀ–ጠገብ ላይ ከአሰገደች ሀብተወልድ ጋር
ተገናኝተው በ1926/27 ዓ.ም ተጋቡ። ከብዙ ዓመት የፈረንሳይ ቆይታው በኋላ ወርቁ ሃይማኖቱን
የተወ ወይም "የኮተለከ" (ካቶሊክ የሆነ) ስለመሰላቸው ዳግም እንዲጠመቅ ወይም በሌላ አነጋገር
"እንዲነፃ" ይገፋፉት ጀመር።አሰገደችን ከማግባቱ በፊት የተለመደውን "የቄደር" ወይም
"የመንፃት"ስርአት መፈፀም ነበረበት። አሰገደች ያልተማረች፣የአካባቢው ገበሬ ልጅ ነበረች።
በቃለመጠይቃችን ወቅት በ1979 ዓ.ም አሰገደች በደብረሲና ትኖር ነበር።
የዳኛቸው ቤተሰቦች እስከ 1932 ዓ.ም ድረስ በውሃ–ጠገብ ይኖሩ ነበር።ነገር ግን ዳኛቸውን
ለማስተማር ወደ ደብረሲና ተዛወሩ።ዳኛቸው የተወለደው በየካቲት 16 ቀን 1928 ዓ.ም ነበር።
ከ40 ቀን በኋላ ሲጠመቅ የክርስትና ስሙ ኪዳነ ማርያም ተባለ።አቶ ወርቁ በከተማው ትንሽ ሱቅ
ከፍተው ጨው፣ልብስ የመሳሰሉትን መነገድ ጀመሩ።
ገና መንደር ውስጥ እያሉ፣ ዳኛቸው በጊዜው ኢትዮጵያን ወረው የነበሩት ጣሊያኖችን (1928–
1933) ያስታውሳል።አባቱ በ"መንግሥት ሰላይነት" ተጠርጥረው ደብረሲና ቢታሰሩም ኋላ
ተፈተዋል። ያኔ ቤተሰባቸውን ይዘው ደብረሲና ከተሙ። ዳኛቸው አስቸጋሪ እና ቀዥቃዣ ልጅ
ነበር። አንዴ አንድ ጣሊያን እየጋለበወደ ሰሜን ሲመጣ፣ዳኛቸው ተንቀዥቅዦ መሀል መንገድ
ይገባል።ጣሊያኑም ዳኛቸውን አፈፍ አድርጎበማንሳት በፈረስ ከመረገጥ ለጥቂት ያድነዋል።
አባትየው ተጠርተው ይመጡና ልጃቸውን በአግባቡ ስላልጠበቁ ዱላ ይቀምሳሉ።ዳኛቸው አባቱ
153
ጥቋቁር አናብስት
ዳኛቸው ለወላጆቹ የበኩር ልጅ ነው―ቀጣይ ታናሽ እህት፣ ሁለት ወንድሞችና የሁሉም ታናሽ ሌላ
እህት ነበሩት። በአራት ዓመቱ ወደ ከተማ ከመግባቱ በፊት ለአጭር ጊዜ በገጠር እረኛ ነበር።
ደብረሲና እንደመጣ ያለምንም ሀሳብ “እንደልቡ ይጫወት” ነበር።ስድስት ወይም ሰባት ዓመት
ሲሆነው ትምህርት ቤት ገባ። እንደሌሎች ልጆች ማንበብና መፃፍ ለመማር የቄስ ትምህርት ቤት
ደጃፍ ሳይረግጥ ቀጥታ የመንግሥት ትምህርት ቤት ገባ።አባትየው ለቤተክርስቲያንብዙም ቦታ
ስለማይሰጡ ወደ ዘመናዊ ትምህርት ቤት ወሰዱት። እናትየው ግን ማታ ማታ ወደ ቤተክርስቲያን
ስትሄድ አብራ ትወስደውና ግዕዝ እንዲማር ታደርገዋለች።ይሁን እንጂ አባትየው ካህናትን
እምብዛም ስለማይወዱ ይህንን ጉዳይ ስራዬ ብሎ የነገራቸው የለም።የቀሳውስቶች ነገረ–ስራ
አይጥማቸውም። እስከ ስድስተኛ ክፍል ደብረሲና በሚገኘው የመንግስት ትምህርት ቤት ከተማረ
በኋላ፣ ኮተቤ በሚገኘው የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሰባተኛን ዘሎ
ስምንተኛ ክፍል ገባ።
ከዚያ በፊትም ቢሆን፣ ለጥቂት ወራት በሀገሪቱ መናገሻ ቆይቷል።ገና ሶስተኛ ወይም አራተኛ ክፍል
እያለ፣ ጄነራል አስፋው ወልደጊዮርጊስ አቶ ወርቁ በፈረንሳይ ለዋሉላቸው ውለታ ብድር
ለመመለስ፣ዳኛቸውን ወደ አዲስአበባ ይዘውት መጥተው ሊሴ ገብረማርያም ትምህርት ቤት
አስገቡት።ነገር ግን ማዕድ ከሰራተኞች ጋር እንዲቋደስ ስለሚደረግ፣ዳኛቸው የአቶ አስፋው ቤት
“የአኗኗር ሁኔታ” ስላልተመቸው፣ በግምት ከአምስት ወራት በኋላ ጠፍቶ ወደ ደብረሲና ተመልሶ፣
የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን እስኪያጠናቅቅ በዚያው ቆየ።
ዳኛቸው ለተጨማሪ ትምህርት እስኪለያቸው ድረስ ወላጆቹ ለ12 ዓመታት ያህል ብርቱ ተጽዕኖ
አሳርፈውበታል። አባት በጣም ስራ ወዳድ ሲሆኑ ዘወትር ጠዋት 12፡30 ከእንቅልፋቸው ይነቁና
ዳኛቸውንም ይቀሰቅሱታል። እናቱም እቤት ውስጥ እስካለድረስ ለልጃቸው ተረት መንገር የዘውትር
ስራቸው ነበር።ዳኛቸው በልጅነቱ ግጥም መጻፍ የጀመረው ለዚህ ሳይሆን አይቀርም፤ ገና የአንደኛ
ደረጃ ተማሪ እያለ፣ በርካታ ግጥሞችንጽፏል።እናቱ የነገሩትን ተረቶች እንዳሉ በጽሑፍያሰፍርና
ፍጻሜያቸውን ብቻ ምናቡ እንደመራው አድርጎ ይቀይራቸዋል።ተረቶቹን ለማሳተም አሳታሚ
ሲያፈላልግ የነበረ ቢሆንም በኋላ "ይኼንን ሀሳቡን ተወው"።ግጥሞቹን ለክፍል ጓደኞቹ
154
ጥቋቁር አናብስት
የዳኛቸው ቤተሰቦች ጥሩ የኑሮ ደረጃ ቢኖራቸውም፣ በእሱና በሌሎች ልጆች መሐል ለምን ልዩነት
እንዳለ አይገባውም።ጓደኞቹ አብረውት እንዲኖሩ ይፈልግ ነበር። አንድ ጓደኛው ከ3 እስከ 4
ሳምንት አብሯቸው ሲቆይ ሌላኛው ደግሞ ከ6 እስከ 7 ወር ከርሟል።አባቱ ግን ይህንን
የሚፈቅዱት የዳኛቸው ጓደኞች በስራ በማገዝ ቆይታቸውን ከደጎሙ ብቻ ነበር። ልጆቹ ግን ሰነፍ፣
በዚያ ላይ ሌባ ሆነው፣ዳኛቸው ላይ ክፉ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ዐይነት ሲሆኑ፣ የዳኛቸው አባት
ቆይታቸውን በብርቱ ይቃወማሉ። በዚህ ምክንያት ዳኛቸው ተቀይሞ "ከነዚሁ ልጆች" ጋር ጠፍቶ
ደብረብርሃን ለስድስት ወር ከረመ። አባቱ ለነዚህ ልጆች ያላቸው መጥፎ አመለካከት ምንም ግልጽ
አልሆነለትም። ይህንን ገጠመኙን በኋላ "ሰው አለ ብዬ" በተሰኘ ተውኔቱ ተንጸባርቆሊሆን
ይችላል። በተቀረ ወላጆቹ “ነጻ አስተሳሰብ የነበራቸውና ታጋሽ” ነበሩ። በቤት ውስጥ ውሻ እና
ድመት እንዲያሳድግም ይፈቀድለት ነበር። ዳኛቸው ከለማዳ ድመቶች ይልቅ የዱሮቹ ይበልጥ
ይስቡታል።እናቱ “የማይከብዱ እና ቤተሰባቸውን ወዳድ” ናቸው። አባቱ በቤታቸው
የዘፈን/የሙዚቃ ሸክላማጫወቻ ስለነበራቸው ሙዚቃ ከፍተው ከልጃቸው ጋር ይደንሱ ነበር፤
“ዳንስ አዋቂም ናቸው።”ቤተሰቡ “መበታተን እስከጀመረበት”ጊዜ ድረስ በጋራ ተደስቶ ይኖር
ነበር።ዳኛቸውትምህርት መማር እንዳለበት አባትየው አበክረው ስለሚያስቡ፣ደብተሩን ዘወትር
155
ጥቋቁር አናብስት
****
ዳኛቸው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን እስከ 11ኛ ክፍል ድረስ በኮተቤ ተከታተለ። በኮተቤ
ቆይታው ስለ ትምህርት ቤት ሕይወት ግጥሞች ይጽፍ ነበር።ልክ ስምንተኛ ክፍልን እንደጨረሰ
እረፍቱንበተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት አሳለፈ። በነዚያ ሶስት ወራት "ሰው አለ ብዬ"ን ፃፈ።
ተውኔቱ በ1950 ታትሞ ሲወጣ “ብዙም አልተለወጠም።”ይሁን እንጂ በመድረክ ላይ አንዴም
ቢሆን ለእይታ አልበቃም።
ዳኛቸው ልክ አስራ አንደኛ ክፍልን ከመጨረሱ በፊት ከባድ የጉሮሮ ህመም ያጋጥመውና ለሶስት
ወር በጽኑ ይታመማል።ወደ ዳግማዊ ምኒልክ ትምሕርት ቤት ክሊኒክ ይዘውት ቢመጡም
ሊፈውሰው የሚችል መድሐኒት አልነበራቸውም። ጉሮሮው ፍጹም ተዘግቶ ምግብ እንኳን መመገብ
አይችልም ነበር።ወላጆቹ ተጠርተው ለአንድ ወር ከግማሽ ያህል ከዛሬ ነገ ይሞታል ተብሎ ሲጠበቅ
ቆየ።ራሱም ሞቱን እየጠበቀ ነበር። እንደሚሞት ”ያውቅ“ ነበር፤ ይህም በቀረው ሕይወቱ የማይፋቅ
አሻራ አትሞበት አልፏል። ወላጆቹን ጨምሮ ማንም እንዳይጠጋው የተከለከለ ስለነበር፣ ከተቀረው
አለም ጋር የነበረው ግንኙነት በመስታወቱ መስኮት አሻግሮ በማየት ብቻ ተወሰነ። ከዚያም እንደ
እድል ሆኖ አዳዲስ መድሀኒቶች ተገኙ፤ በጠና የታመሙ በሽተኞች ላይም ይሞከሩ ጀመር። ከነዚህ
አንዱ ዳኛቸውን ፈወሰው፤ ከሞትም ተረፈ።ዳኛቸው አሁን ያንን ጊዜ ሲያስታውስ ”ከመቃብር
የመውጣት፤ እንደገና የመወለድ ያክል ነበር“ ይላል።ከተሻለው በኋላ ለሁለት ሳምንት ያህል በኮተቤ
በክትትል ከአልጋ ሳይወርድ ከቆየ በኋላ ወደ ወላጆቹ ሀገር ወደ ደብረሲና ሄደ። ከዚህ ክፉ
አጋጣሚ በኋላ ወደ ኮተቤ መመለስ አልፈለገም። ይልቁንም አቶ ካራማይክል የተባለ ግለሰብ
በኮከበጽባህ (የሚገኘው ኮተቤ መንገድ ላይ ነው) ባቋቋመው የመምህራን ማሰልጠኛ ለአንድ
ዓመት ሰለጠነ። በዓመቱ መጨረሻ ለሁለት ፈተና ተቀመጠ፦ ለመምህራን ስልጠና ፈተናውና
ለአስራ ሁለተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና። ይሄም ሳይበቃው በእንግሊዝ የለንደንን
156
ጥቋቁር አናብስት
ለእለታዊው አዲስ ዘመንና ለሳምንታዊው የዛሬይቱ ኢትዮጵያ መፃፍ የጀመረውም በዚህ ወቅት
ነበር። በብዛት ይጽፍ የነበረው ስለ ሥነ ጽሑፍ፣ ስላነበባቸው መጽሀፍት፣ ስላያቸው ተውኔቶች፣
ስለተመለከታቸው ፊልሞች ነው። በዚሁ ወቅት አወዛጋቢ ርእስ ስለነበረው የፀሐፊዎችገቢ ማነስ
ለመፃፍም ብዕሩን አንስቶ ነበር።ፀሐፊዎችየተሻለ ገቢ ማግኘት አለባቸው ብሎ ሽንጡን ገትሮ
ተከራክሯል።በጊዜውየነበረው አሰራር ግን ትያትር ቤቶች አብዛኛውን ትርፍ ለራሳቸው
የሚያስቀሩበት ነበር።
በ1953 ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ገባ። ዩኒቨርስቲ ኮሌጁ የተመሰረተው በ1943 ሲሆን በ1953 ቀዳማዊ
ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ተብሎ ተሰየመ።ከአራት ዓመት በኋላ የመጀመሪያ ዲግሪውን አገኘ።
ለሁለት ዓመት የተማረው አጠቃላይ ማህበራዊ እውቀት የሚያስጨብጡ ትምህርቶችን ብቻ ነበር።
በኋላ ግን የኢትዮጵያ ቋንቋዎች እና ሥነ ጽሑፍን ማስተማር በመጀመራቸው፣ ግዕዝ እና
አረብኛንም ጨምሮ ለሁለት ዓመት ተማረ።"ምኞቴን ያሳካሁባቸው" ስለሆኑ በሚል
የመጨረሻዎቹን ሁለት ዓመታት እንደሚወዳቸው ይናገራል። በዩኒቨርስቲ ቆይታው የተቃውሞ
157
ጥቋቁር አናብስት
ግጥሞችን መፃፍ ጀመረ። "እምቧ በሉ" በሚለው የግጥም መድብሉ ውስጥ የተካተቱት አብዛኛዎቹ
ግጥሞች በነዚህ አራት ዓመታት የተፃፉ ነበሩ።"ሁሉም የተቃውሞ ግጥሞች ነበሩ" ይላል።
እንደውም የተቃውሞ ግጥም መፃፍ ፋሽን ሆኖ ሁሉም ይጽፍ ነበር። ይህ የተቃውሞ ግጥም
መበራከት መንግስትን እጅግ ስላስጨነቀው “አጼው” ተማሪዎቹ በዩኒቨርሲቲው “እንዳያድሩ”
ከለከሉ። ለወጪያቸው መሸፈኛ ገንዘብ እየተቆረጠላቸው ቀን ቀን ብቻ እንዲማሩ ተደረገ።
ግጥሞቹ ከሚዳስሷቸው "ማሕበራዊ ጉዳዮች" መሐል የመሬት ስሪት ለውጥ ("መሬት ላራሹ")፣
"ፍትህ ለደሀው"፣ "ለተመሳሳይ ስራ ተመሳሳይ ደሞዝ"፣ "በመንግሥት ስራ እኩል ተቀጣሪነት"
―በአጠቃላይ ለሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች እኩል እድል እንዲሰጥ የሚጠይቁ ነበሩ።2ዳኛቸው
“ይፋት ውስጥ ከሁሉም ብሔረሰቦች ጋር ተቀላቅሎ” በማደጉ “የብሔርተኝነት ስሜት የለኝም”
ይላል። በኢትዮጲያ ውስጥም የጠራ/የነጠረ ጎሳ አለ ብሎ አያምንም—ካለም የጎሳ ማንነት
የሚገለጸው “በቋንቋ” ነው ብሎነው የሚያስበው።ቤተሰቡ በብዛት “አማራ ይመስላሉ።”ነገር ግን
የአባቱ እናት ኦሮምኛን አቀላጥፈው ይናገራሉ ፤ ያደጉት ጋሞ ጎፋ ቢሆንም በከፊል ወይም በሙሉ
ኦሮሞ ሳይሆኑ አይቀርም።
ዳኛቸው ዩኒቨርሲቲ እያለ የሥነ ጽሑፍ እንቅስቃሴዎቹ ግጥም በመፃፍ ብቻ የተወሰኑ ነበሩ።
የግእዝ ቅኔን በተመለከተ ብዙ ጥናት አድርጎ፣ የአራተኛ ዓመት ተማሪ እያለ በኋላ ደግሞ
የዩኒቨርስቲው ሰራተኛሲሆን በስፋት ጽፎበታል። ትምህርቱን በከፍተኛ ውጤት ስላጠናቀቀ
በዩኒቨርሲቲው ውስጥ መጀመሪያ ተመራቂ ረዳት፣ ከዚያም ረዳት ሌክቸረር፣ ኋላም ሌክቸረር
ሆኗል።
158
ጥቋቁር አናብስት
***
በ1962 መጀመሪያ ዳኛቸው ለሶስት ዓመትሥነ -ጽሑፍን “በአለም አቀፍ ጸሐፍት አውደጥናት”
ላይ ለመማር ሰሜን አሜሪካ ከሚገኘው አዮዋ ዩኒቨርስቲ ነጻ የትምህርት እድል አግኝቶ ወደዚያው
አመራ።ትምህርቱየመምህራን አቅም ማጎልበቻ ሳይሆን ብቁ የወደፊት ደራስያንን ለማፍራት ያለመ
ነው። ለአብዛኛዎቹ ተማሪዎች እንግሊዝኛ የመጀመሪያ ቋንቋ ነው፤ ለጥቂቶች ሁለተኛ ቋንቋቸው
ሲሆን ዳኛቸውም ከነዚህኞቹ የሚመደብ ነበር። አስከትሎም በሥነ ጥበባት ሁለተኛ ዲግሪውን
በመስራቱ፣ትምህርቱን ለማጠናቀቅእንደ ቅድመ ሁኔታ ከተቀመጡ መስፈርቶች መሀል ሊታተም
የሚችል ወጥ የሆነ ድርሰት ማዘጋጀት አንዱ ነበር። ዳኛቸው የፈጠራ ጽሑፍ ፕሮግራምን
ከመቀላቀሉ በፊት፣በእንግሊዝኛ ቋንቋ የትምህርት ክፍል ለሁለት ዓመት ተምሮ የሁለተኛ
ዲግሪውን መያዝ ይጠበቅበት ነበር።ትምህርቱን በ1964 ዓ.ም ካጠናቀቀ በኋላ ወደ ሀገሩ
ተመለሰ። በዚህ ወቅት ሁለት ታሪኮችን ("ማሚቴ" እና አንድ ሌላ ርዕሱ ያልታወቀ) ያሳተመ ደራሲ
ሆኗል። የመመረቂያ ጽሑፉ በእንግሊዝኛ የተዘጋጁ ስምንት ታሪኮች ስብስብ ነበር። ነገር ግን ሌሎች
ታሪኮችን መጨመር ስለሚፈልግ ቃለ መጠይቃችንን እስካደረግንበት ጊዜ ድረስ አላሳተማቸውም።
እነዚህ ታሪኮች "በማንኛውም ጊዜ" ሊታተሙ የሚችሉ ናቸው ብሎ ያምናል።
ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሰ በኋላ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንድ ዓመት ያህል ሲያስተምር ቆይቶ
"ከዩኒቨርስቲው ሹመኞች ጋር ተጋጨ"።"ችግሩ" የጀመረውየዳኛቸው ለአራተኛ ዓመት ተማሪዎች
የሚሰጠውን ጨምሮ፣ ክፍል ገብቶ ምንም ትምህርት ተከታትሎ የማያውቅ ልጅ "22 ክሬዲት
ሰአት" እንደወሰደ ተደርጎ መያዙን ሲቃወም ነው።ሹመኞቹ "ነገሩን አለባብሰው፣ ተማሪው
የተወሰኑ ትምህርቶችን በዚያ ሴሚስተር እንደማይወስድ አድርገው ፎርም አስሞልተው ለማለፍ
ቢሞክሩም" ዳኛቸው በጄ አላለም። ስለዚህ ዳኛቸውን "የዩኒቨርስቲውን ስም በማጥፋት" ከሰሱትና
በህጉ መሰረት "የስድስት ወር ቅድመ ማስታወቂያ" ተሰጥቶት በዘዴ እንዲለቅ ተደረገ። የተባለው
ተማሪ "ትልቅ ስልጣን ያለው የታዋቂ ቤተሰብ ልጅ" ቢሆንም ከዚህ ሁሉ ግርግር በኋላ "በስርአቱ
አጥንቶ" “ከሁለት ዓመት” በኃላ ዲግሪውንአግኝቷል።"ይህንን ሁሉ የሚያደርገው የዩኒቨርስቲው
ፕሬዚዳንት የነበረው አክሊሉ ሀብቴ ነው" ይላል ዳኛቸው፤"ከአብዮቱ በኋላ ስለፈራኝ ሀገር ጥሎ
ፈረጠጠ፤ አሁን ዩናይትድ ስቴትስ፣ በአለም ባንክ ውስጥ ጥሩ ስራ አለው" ይላል ጨምሮ።ከአራት
159
ጥቋቁር አናብስት
ዳኛቸው ዳግም የመንግሥት ስራ ከመያዙ በፊት አራት ዓመት ተኩል አልፎት ነበር። ከአራት ወይ
አምስት ወራት በኋላ ስራፈትነቱን ተለማመደው። ያኔነው አንድ ዓመት ተኩል ያህል የፈጀበትን
ታላቁን ስራውን "አደፍርስ"ን የፃፈው።ዳኛቸው ራሱን "የአንድ መጽሐፍ ደራሲ" ብቻ አድርጎ ነው
የሚቆጥረው። ምንም እንኳን ዳኛቸው ሌሎች ሥነ ጽሑፋዊ ስራዎች ቢኖሩትም፣ ለ"አደፍርስ"
የሚሰጠው ግምት ምን ያህል ላቅ ያለ እንደሆነ ለመረዳት አያዳግትም። ቀደምት ስራዎቹን፣ ለዚህ
መጽሀፍ እንደ መንደርደሪያ ወይም መዘጋጃ አድርጎ ሳይቆጥራቸው አይቀርም። አደፍርስ የተፃፈው
በጣም በተወሳሰበ አማርኛ ቢሆንም፣ ዳኛቸው በትውልድ ቀዬው የሚነገረውና እየተነገረም ያለው
አማርኛ እንዲህ ያለ መሆኑን ይናገራል። ለማሳተሚያ የሚሆነውን ገንዘብ ያገኘው ከቤተሰቦቹና
ከጓደኞቹ ሲሆን እርማቱን፣ አርትኦቱንና የመሳሰለውን የሰራው እርሱ ራሱ ነው። አደፍርስ
10,0003 ቅጂዎች ታትሞ በደንብ በመሸጡ አሁን እንኳን አዲስ፣ አሮጌውን ራሱ ለማግኘት
በጣም ከባድ ነው።
ከዚህ በኋላ በሐገሪቱ ለሚገኙት ሁሉምጋዜጦች በአማርኛና በእንግሊዘኛ መፃፍ ጀመረ።ስለ ቅኔ፣
ስለልብወለድ የአጻጻፍ ዘዴ5፣እንዲሁም በብዛት የ“ቤሳ ልብወለድ” መጽሀፍትን ቅኝት ይጽፍ ነበር።
ቀጥሎ በEcole Normal Superieure/ከተወረሰ በኋላ ጥቁር አንበሳ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት
ቤት በሆነው/ "ሥነ ጽሑፍ እና ሥነ ግጥም"ን ለአንድ ዓመት ተኩል አስተማረ።ሁለተኛ ደረጃ
ተማሪ እያለ በፈረንሳይኛ ማንበብ ቢሞካክርም፣አሁን ግን የፈረንሣይኛ ቋንቋ ችሎታው ብዙ
እንደማያወላዳ ይናገራል።እንኳን ፈረንሳይኛዬ የተሻለ የማውቀው እንግሊዝኛ እንኳን “አዘውትሬ
ስለማልጠቀመው፣ዝጓል/እየጠፋኝ ነው”ይላል።ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በትርፍ ጊዜው በኢትዮጵያ
160
ጥቋቁር አናብስት
****
አብዮቱ ከፈነዳ በኋላ በሚያዝያ 1966ዓም፣ በኢትዮጵያ ደረጃዎች ድርጅት የሙሉ ጊዜ ሠራተኛ
ሆኗል። በዚያው ዓመት ለአንደኛ ዲግሪ ተማሪዎች፣ ከአራት ዓመትበኋላ ደግሞ ለሁለተኛ ዲግሪ
ተማሪዎች ፈታኝ ሆኖ እስከ 1977 ዓ.ም ድረስ ሰርቷል። (በመጀመሪያው ዓመት አንድ ተማሪ ብቻ
ነበር የፈተነው።)
ጥናት እያደረገ ነበር።አንድ ማኅበረሰብ እንዴት አምባገነናዊ እየሆነ እንደሚመጣ ይታዘባል። በፊት
ህልሞቹ ሁሉ "ለውጥ፣ ለውጥ" የሚሸቱ ነበሩ።አሁን ግን "ሰዎችን ባሉበት፣ በሚያስቡበት
በሚኖሩበት ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ መረዳት" ነው የሚፈልገው። በቃለ -መጠይቃችን ወቅት
"ለሰው ልጅ ከፖለቲካ የሚልቁ እውነቶች እንዳሉት፤ሰው ፖለቲካዊ እንስሳ ከመሆን የሚሻሉ
መሻቶች እንዳሉት" መረዳት የጀመርኩበት ወቅት ነውብሎኛል።
እንደ ዳኛቸው አባባል በመጽሀፎቹ ማስተላለፍ የሚፈልገው መልእክት “የጋራ ሀገር እንዳለን፣
ልዩነቶች ቢኖሩንም አብሮነታችንን ሊያስቀጥሉልንየሚችሉት ብቸኛዎቹ ነገሮች ለዘመናት በጋራ
ያፈራናቸው እሴቶች መሆናቸውን ነው። እነዚህ እሴቶች እንደ አሮጌ እቃ በአንድ ቀን አውጥተን
የምንጥላቸው አይደሉም። ሕይወታችንን ሙሉ የኖርንባቸውን እሴቶች በአንድ ጊዜ የምንተካቸው
አይደሉም።ወደፊት የሚገፉን ሃይሎች እነዚህ በዘመናት ጥረት የተገነቡት እሴቶች ናቸው። አዳዲስ
የግፊት ሃይሎችን ከስሜታችን እና ከልምዳችን ጋር ለማዋሃድ በጣም ብዙ ጊዜ ይወስዳል። የሥነ
ጽሑፍ ስራዎቼ ማዕከላዊ ማጠንጠኛ ሴማ ይኸው ነው።”
ጎሳ፣ነገድ፣ ዘር የሚባሉ ነገሮች ለእሱ ዋጋ የላቸውም። "ብዙ እሴቶች ያሉት ማኅበረሰብ ፈጥረናል።
ለዚህ ማህበረሰብ እና እሴቶቹ መጎልበት ሁሉም አስተዋጽኦ አድርጓል―የአንድ ወይም የሁለት
ጎሳዎች ብቻ ሳይሆን የሁሉም አስተዋጽኦ ድምር ውጤት ነው።ልቤ መምታቱን እንዲቀጥል
የሚያደርገው ይሄ ነው።ያለዚህ ሕይወት ለኔ ትርጉም የላትም። ይህ የያንዳንዳችን የግል ሕይወት
አካል እስኪሆን ብዙ ጊዜ ፈጅቷል፤በአንድ ቀንም የሚፈርስ አይደለም።እሴቶች በአንድ ቀን
ቢገነቡና ቢፈርሱ ምኞቴ ነበር፤እውነታው ግን ከዚህ ይለያል።ገና ኋላ ቀር እና በማደግ ላይ ያለን
ስለሆንን ለውጥ ያስፈልገናል፤ነገር ግን በ3,000 ዘመን የገነባነው ሁሉ በቀላሉ አይፈርስም።
የበለፀግነው በመንፈስ ብቻ ነው። በኪነ–ጥበብና በሥነ –ውበት ረገድ አይናችንን ገና
አልገለጥንም። በየቀኑ አዳዲስ ሀሳቦችን ከሕይወታችን ጋር እያዋሃድን፣ የሕይወታችን አካል
ልናደርጋቸው ይገባል። ሰዎች እንዲያስተውሉና እንዲማሩ ማድረግ እንችላለን ፤ ነገር ግን ስሜት
ካልሰጣቸው በስተቀር የተማሩትን ጥቅም ላይ አያውሉትም።
ስለ አብይ የሥነ ጽሑፍ ስራው አደፍርስ ደግሞ እንዲህ ይላል (የልብወለዱ ዋና ገፀባህሪም
አደፍርስ ይባላል)፦ "አደፍርስ ተራማጅ ወጣት ነው―ነገር ግን ከሕዝቡ ተለይቶ ብቻውን ነው።
ሁሉን ነገር በብርቱ አመክንዮ ለመተንተን ይሻል።የተግባር ሰው አይደለም። ከተግባር ይልቅ ልፈፋ
ያበዛል።አመክንዮ ጥሩ ቢሆንም ሁሉም ነገር በልኩ መሆን አለበት።አደፍርስ ዛሬ በመሃከላችን
እንደምናያቸው ሰዎች ያለ ነው።አብዮቱ ሰዎችን በአንድ ሌት አንቅቶ ለማደር ይቋምጣል፤ያ ግን
የሚቻል አይደለም―ቢቻል ምኞቴ ነበር።የብኄርተኝነት ስሜት7እንኳን ለማዳበር ሕዝብን ማመን
162
ጥቋቁር አናብስት
የግድ ይላል ይባላል።ይህ ምን ማለት ነው? ሕዝቡ ባንድ ሌት ተለውጦ ማደር ይችላል ለማለት
ነው?ሕዝባችን ለውጥን መቋቋም ቢችልም በዚህ ፍጥነት መለወጥ ግን አይችልም። ለአደፍርስ ግን
ከሞት ውጪ ከዚህ ቅዠት መውጫ በር የለውም―ብዙ መብሰል ይቀረዋል፤ ጥራዝ ነጠቅ ነው።
ዙሪያውን የከበበውን እውነታ ማስተዋል አልቻለም―እሱ የሚናገረው አንድ ቋንቋ፣ ሀገሪቱን
መለወጥ የሚችለው ይህ ሕዝብ ደግሞ የሚያወራው ሌላ። አብዮቱ ያልተሳካው ለዚህ
ነው―ሁላችንም እንደ አደፍርስ ዐይነቶች ነን። አደፍርስ በ1950ዎቹ ሳይፈለጉ እንደ አሸን
የፈሉትን ዐይነት ሰዎች ይወክላል።የድሮ ሰዎች እሴቶች ነበሯቸው― ለሃይማኖታቸው፣
ለመሬታቸው፣ለሃገራቸው ሞተዋል።እኛ ግን አሁንምንም እሴቶች የሉንም። እነዚህን እሴቶች ንቀን
ከተውናቸው፣ ምን ይቀረናል? የሰዎች ሕይወት አካል የሆነ ምንም ነገር አይቀርም።"
163
ጥቋቁር አናብስት
ማስታወሻ
164
ጥቋቁር አናብስት
የተርጓሚው ማስታወሻ የዳኛቸው ወርቁና የአምሳሉ አክሊሉ ፈሊጣዊ አነጋገር መጽሐፍ ታትሞ
ለንባብ የቀረበ ሲሆን፤፤አጫጭር ታሪኮቹም ጭጋግና ጠል ላይ ወጥተዋል፡፡
ማስታወሻዎች
2) በጊዜው የነበረው የዘር ጭቆና አማራዎችን የሚጠቅም ነበር። ስለዚህ የሌላ ጎሳ አባላት
የመንግስት ስራ ለማግኘት ሲሉ ስማቸውን ይቀይራሉ። በንጉሱ ዘመን የመንግሥቱ ኃይለማርያም
አባት የጦር ሰራዊቱ አባል ለመሆን ስማቸውን ቀይረዋል ፤ በክርስትና ተጠምቀዋል።
3) በጊዜው ይሄ ብዙ የሚባል ነበር። "ሰው አለ ብዬ" በ5,000 ቅጂዎች ሲታተም "እምቧ በሉ"
ደግሞ በ2,000 ቅጂዎች ታትሟል። ( "አደፍርስ" የታተመው በ1962 ስለሆነ የዳኛቸው ወርቁ
የቀኖች ትውስታ የተሳሳተ ሳይሆን አይቀርም)
165
ጥቋቁር አናብስት
ተባባሪ የነበረው ግርማሥላሴ አስፋው መጽሀፉን ሲያነበው ምንም አልገባውም ነበር። የማይታወቁ
ቃላትን ትርጉም ስሰጠው ግን የከበዱኝን ምንባቦች ከማህበራዊ እና ባህላዊ አንደምታቸው አንፃር
አብራራልኝ። ሌሎቹን ለጥናት ወረቀቴን የመረጥኳቸውን መጽሀፍት ለመረዳት ችዬ ነበር።
አደፍርስ ግን፣ እኔና ግርማሥላሴ አስፋው መተባበር ባንችል ኖሮ፣ሚስጥር ሆኖብኝ በቀረ ነበር።
ሌሎች ኢትዮጵያውያንም መጽሀፉን ለመረዳት ችግር እንደገጠማቸው ነግረውኛል።
166
ጥቋቁር አናብስት
እምሩ ኃይለሥላሴ
እምሩ ኃይለሥላሴ የለውጥ
ከምንሊክ ጊዜ ጀምሮ በልጅ እያሱና ዘውዲቱ ብሎም ከኃይለሥላሴ እስከ አብዮቱ ጊዜያት
በሕይወት የቆዩ ሲሆን፤በቆዩ ቁጥር ደግሞ ይህንን እውቅና የማንበር ጥሩ እድል አጋጥሟቸዋል።
167
ጥቋቁር አናብስት
ቢሆንም ከስነ ጽሑፋቸው በላይ እዚህ የፃፍኩት በእርሳቸው ዙርያ በሌሎች ቦታዎች ከሚነገሩ
የተወሰኑ ታሪኮች ጥቂቱን “ያስተካክላሉ” ብዬ አምናለሁ።3
***
እምሩ ለተወሰኑ አመታት በጉርሱም ቆዩ።አራት ዓመት ከሞላቸው በኋላ ብዙ ሳይቆይ ከሌሎች
የመኳንንት ልጆች ጋር አብረው ትምህርታቸውን እንዲቀስሙ ወደ ኃይለሥላሴ አባት ወደ ራስ
መኮንን ተላኩ።እዚያ የነበሩት የመኳንንት ልጆች ኃይለ ሥላሴን(ተፈሪን) ጨምሮ (እናታቸው
በወሊድ ጦስ የሁለት ዓመት ልጅ ሳሉ አርፈዋል)፡፡10በአብዛኛው እናቶቻቸው የሞቱባቸው ነበሩ።
በመኮንን ቤት ያሉ ህፃናት ለቤተክህነት ትምህርት የ5 ሰአት መንገድ ያህል ጉዞ ወደ ምታስኬደው
ጃርሶ ተልከው ዳዊትንና ሌሎች ሃይማኖታዊ መፃሕፍትን ይደግማሉ፤ያጠናሉ።አለቃ ወልደ ኪዳንና
አባ ወልደስላሴ ነበሩ በአብዛኛው በግዕዝ የሚያስተምሯቸው።
እምሩ ራስ መኮንን ሲያርፉ የ13 ዓመት ታዳጊ ሲሆኑ ልጆቹ ወደ አዲስ አበባ ምንሊክ
ቤተመንግስት ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ተጠሩ።እዚህ ነበር በዙፋን ጉዳዮች እየሰለጠኑ ከነበሩት
ከሚኒሊክ የልጅልጅ እያሱ ጋር የተገናኙት።17
የዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እ.ኤ.አ በ190818 ሲከፈት እዚያ ገቡ፡፡ በአንድ ዓመት
ቆይታቸውም ከሌሎች ልጆች ቀድመው ከሃረር ቀለም ቆጥረው ስለመጡ ልዩ ክፍል 'ከሀረርጌ
ለመጡት' ልጆች ተከፍቶ ስለነበር በስርአተ ትምህርቱ ያሉትን አራት ትምህርቶችን ፈረንሳይኛ፤
169
ጥቋቁር አናብስት
በሰኔ 1903 ከሲዳሞ ወደ ሀረር እንደተመለሱ ተፈሪ የልጅ እያሱ የእህት ልጅ የሆኑትን21 ወ/ሮ
መነንን አገቡ እያሱ በአምቻ አመኻኝተው ሊዛመዱ ይፈልጉ ነበር።ራስ ተሰማ የእያሱ ሞግዚት
የነበሩ ሲሆን በሚያዝያ 1903 ስላረፉ እያሱ ሌላ ሞግዚት አልቀበልም አሉ።ራስ አባቴ አዲሱ
ሞግዚት ለመሆን በቤተመንግስት ስልጣንን ለመውሰድ በሃይል ፈልገው የነበሩ እንደውም የተወሰኑ
ሃይሎችን ይዘው ከቤተመንግስቱ ገብተው የነበሩ ቢሆንም በፊትአውራሪ ሃብተጊዮርጊስ እና በራስ
ሚካኤል (የኢያሱ አባት) እርዳታ የእያሱ ስልጣን ከእጃቸዉ እንዳትወጣ አደረጉ።22እያሱን
በግንቦት 1901 አልጋወራሼ ነው ብለው ሚኒሊክ አዋጅ ስለስነገሩላቸው ምኒልክም በቂጥኝ
በሽታ ተይዘው ከአልጋ ከዋሉ23 ስለሰነበቱ እያሱና ሞግዚታቸው ከምንሊክ የየጎርጎሮሳውያም
አቆጣጠር የታህሳስ 13 1913 ሞት24 በፊትም ቢሆን ሃገሪቱን ማስተዳደር ችለዋል።በዚህ
አስቸጋሪ ወቅት እያሱ የተፈሪንና የእህታቸውን ልጅ መነንን ጋብቻ አዘጋጅተው ሰለነበር እምሩ
መነንን ከአዲሳባ ወደ ሃረር የማምጣት ስራ ተሰጣቸው።በቤተመንግስቱ ከተከተሏቸው የሰራዊቱ
አባላት ጋር በውስጥ ጉዳዮች ጣልቃ በመግባት ተጠርጥረው ቢቆዩም በመጨረሻ ተሳክቶላቸው
መነንን ከአዲስአበባ አስወጥተው ተፈሪን ወዳገቡበት ሃረርጌ ይዘዋቸው ሄዱ።
ከጥቂት አመታት በኋላም 21ኛ አመታቸውን ሲይዙ በአባታቸውና በሚስታቸው አባት በተመከረ
ትዳር እምሩ ራሳቸው አገቡ።ሚስታቸው ጽጌ ማርያም ሲሰኙ የልጅ ገብረ ሩፋኤልና የወይዘሮ
ላቀች(የራስ መንገሻ አቲከም የዳሞት ቡሬው)25 ልጅ ናቸው።እምሩና ጽጌ ማርያም ያላቸው አንድ
ወንድ ልጅ አምስተኛው ልጃቸው ሚካኤል ሲሆን የተቀሩት በሙሉ ሴቶች ናቸው።ይህ መጽሐፍ
በተጻፈበት ወቅት እ.ኤ.አ በ1988 ሁሉም በሕይወት ነበሩ።እናታቸውም በ90 አመታቸው
በህይወት ነበሩ፡፡(ራስ እምሩ በ1980 ቢሞቱም)26
170
ጥቋቁር አናብስት
እያሱ ከስልጣን ከተነሱ በኋላ የምንሊክ ልጅ የሆኑት ዘውዲቱ በየካቲት 1 1917 ተፈሪ መኮንንን
በአልጋ ወራሽነት30 አስከትላ ነገሱ።ተፈሪ የግልበጣውን ሴራ ቀደም ብለው ሳያውቁ አይቀሩም ነገር
ግን ከጅማሮው አልነበረም ቀንደኛ ተሳታፊም ሳይሆኑ እንደ አጃቢ ነበሩ።
አዲሲቱ ንግስት ዘውዲቱ31 ሃይላቸውን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያጡ በአንጻሩ ደግሞ የተፈሪ እየፈረጠመ
መጣ።ከእያሱ መወገድ በኋላ ለተፈሪ ፍላጎታቸውን ያሳዩ የተፈሪ ታማኝ ተከታዮች እምሩን ጨምሮ
እያበቡ መጡ።
ተፈሪ ከሃረር በእያሱ ትእዛዝ ከመነሳታቸው በፊት ሃረር የሚገኘውን የተፈሪ ቤተሰብ በእምሩ
ጥበቃ ስር ነበሩ፡፡32
ከጥቂት ሳምንታት በኋላ የተፈሪን ሚስትና ሁለት ልጆች ይዘው(አንዷ ትልቋ ልእልት ተናኜ ወርቅ
ስትሆን ሁለተኛው ልኡል አልጋ ወራሽ ትልቁ ወንድ ልጃቸው በወቅቱ 40 ቀን ሞልቶት ክርስትና
እንደተነሳ ነበር)33ወደ አዲስ አበባ ተፈሪን እንዲያገኙ ይዘዋቸው መጡ።ልክ አዲስአበባ ደርሰው
ከተፈሪ ጋር ሲገናኙ ነበር እምሩ ልጅ እያሱን ከስልጣን ስለማስወገድ እና ስለአዲስ መንግስት
የማቋቋም ሴራ ሊሰሙ የበቁት።እያሱ የሆነ ተንኮል እየተጠነሰሰ እንደሆነ ስለጠረጠሩ ይመስላል
ተፈሪን ወደ ከፋ ለመላክ የተፋጠኑት።
34
እያሱም እምሩ ወደ ሃረር በፍጥነት በመመለሳቸው ስለገነገኑ ከተፈሪ በወሰዱት ቤተመንግስት35
ውሥጥ በሰንሰለት አስገብተው በእስር አቆራኟቸው።36 እምሩ ቤተመንግስቱን አብጠርጥረው
ሲለሚያውቁ37ሲመሽ በጨለማ አመለጡ።ሰንሰለታቸውም የተፈታው ከሀረር ግንብ ወጥተው
ነው።38
171
ጥቋቁር አናብስት
እምሩ ነፃ ሆነው የግልበጣው ታማኝ ወታደሮችን ሲያገኙ ሁሉም የሀረር በሮች ተዘግተው
እንዲጠበቁ አዘዙ።መልሰው ወደ ሀረር ለመግባት ሲችሉ በእያሱ የታሰሩ ሰዎችን ከእስር
አስፈትተው አስታጠቁ።በእነርሱም እርዳታ ሁኔታውን ለማረጋጋት ቻሉ።ከዚያም በአብዛኛው
(የሱማሌ ወታደሮች) የነበሩበትን የልጅ እያሱ ታጣቂ ተከታዮቻቸውን የማደን ስራ ተጀመረ ።39
እምሩ በሃረርጌ የራስ መኮንን ደጋፊዎች የነበሩትን ሰዎች ስም በዝርዝር ይዘው ነበር።ለምሳሌ
ፊትአውራሪ ባንቲ፤ደጃዝማች ገብሬና ደጃዝማች ወልደስላሴ የነበሩባቸው ሲሆን ቆይቶም ወደ
ሃረር ከእያሱ ጋር አብረው የመጡት ደጃዝማች ባልቻም አዲስ አበባ ካሉት ከአዲሱ መንግስት
(ከመፈንቅለ መንግስት ሴረኞቹ ጋር) ተቀላቀሉ፡፡ከመነሾው እምሩ ከአዲስ አበባ ትእዛዝ
ስላልመጣላቸው የመንግስት ግልበጣው ጊዜ ያልተነገራቸው ሲሆን የራሳቸው ፈጠራ ተጠቅመው
ለመንቀሳቀስ የተገደዱ ቢሆንም በስተመጨረሻ ግን ህግና ስርአትን ለማስፈን ችለዋል።
***
172
ጥቋቁር አናብስት
****
173
ጥቋቁር አናብስት
መፈንቅለ መንግስቱ ተከናውኖ እያሱ ከስልጣን ከተወገዱ በኋላ እምሩ በቀድሞ መንግስት አገዛዝ
ደስተኛ እንዳልነበሩ ሆነው የአዲሱ መንግስት ደጋፊ በመሆን በታማኝነት ብቅ አሉ።ሙሉ በሙሉ
በኢያሱ ተስፋ ባይቆርጡም "የቅሬታ ስሜት"ነበራቸው።እምሩ ልጅ እያሱ ለሃላፊነት ብስለት
ይጎድላቸዋል ብለው ቢያስቡም ከስልጣን ማስወገዱ ግን ሌላ አስከፊ እርምጃ ነው።እምሩ ልጅ
እያሱን ከትምህርት ቤት ጀምሮ እንደሚያስታውሷቸው ስልጣን ላይ ካልቆዩባቸው ምክንያቶች
መካከል ፈር የለቀቁ ቁጥጥር በጎደለው ሁኔታ በምንሊክ ቤተመንግስትና በዳግማዊ ምንሊክ
ትምህርትቤት ለአስተማሪዎቹም አስቸጋሪና44 "የተበላሹ" ልጅ ስለነበሩ ነው።እያሱ እዩኝ እዩኝ ባይ
ከመፃህፍቱ ወደ እስፖርቱ የሚያዳሉ ለዲስፕሊን ተግዥ ያልሆኑ ሰው ናቸው።ወደ ስልጣን
ሲመጡ ራስ ተሰማ ናደውን ለሞግዚትነትና ለእንደራሴነት ተሰጥቷቸው የነበር ቢሆንም ተሰማ ግን
ደካማ በመሆናቸው እያሱን መምራት ተሳናቸው።እንደ እምሩ አስተሳሰብ በራስ ተሰማ ፈንታ
ፊትአውራሪ ሃብተግዮርጊስ ሆነው ቢሆን ኖሮ ውጤቱ ለእያሱ የተለየ ይሆን ነበር።ሃብተጊዮርጊስ
ብልህና ጠንካራ ሰው ስለነበሩ እያሱን ወደ ትክክለኛው የንግስና አቅጣጫ ይመሯቸው ነበር ሲሉ
ይገምታሉ።
በመፈንቅለ መንግስቱ ጊዜ ተፈሪ ከሃረርጌ እምሩ ደግሞ ከጅግጅጋ ገዥነት ስልጣናቸው ተነስተው
ነበር።እምሩ ከተፈሪ ጋር ወደ ከፋ መሄድ ነበረባቸው።ምንም እንኳን በህግ የታወቀ ትእዛዝ
ባይሰጥም ቅሉ…. እምሩ ግን “የተፈሪ ሰው”ተባሉ።45 እያሱ ወደ ሃረርጌ ከመመለሳቸው
ከመንግስት ግልበጣው አንድ ወይም ሁለት ወር በፊት ተፈሪ ወደ አዲስ አበባ መጡ።እያሱ
ከስልጣን ሲወርዱ ሀረር የነበሩ ሲሆን ተፈሪ ግን አዲስ አበባ ነበሩ።
174
ጥቋቁር አናብስት
እምሩ ሀረርን ካረጋጉ ከአዲስ አበባም ሃይል ከመጣላቸው በኋላ ሃረርን ኋላ ገዥ ለሆኑት
ለደጃዝማች ገብሬ ጥለው ወደ መናገሻው ተመለሱ ።የእያሱ አባት የወሎው ንጉስ ሚካኤል
አልጋውን ለልጃቸው ለመመለስ ተንቀሳቀሱ።ራስ ልዑልሰገድም ከደጃዝማች ተሰማ ገዝሙና
ከአሳላፊ አብዬ እና ከሌሎች ጋር በመሆን ንጉስ ሚካኤልን ለመግጠም ሄዱ።ልኡል ሰገድ እና
ተሰማ ቶራ መስክ ላይ ቃፊር አንኮበር አካባቢ እ.ኤ.አ በጥቅምት 13 1916 በተደረገው ጦርነት
ተሸንፈው ተገደሉ።እምሩ በዚህ ወቅት ከሀረር ጦራቸውን ይዘው ሳይንቀሳቀሱ አልቀረም ሚካኤል
ግን ለዘመቻ ከደሴ እስኪንቀሳቀሱ ድረስ ሀረር ውስጥ ነበሩ።
ለእምሩ ሹመት መነሻ እርሾው በአዲስ አበባ የነበረው የስልጣን ሽኩቻ ነበር።ሃይላቸውን አጥተውና
የኢያሱ ጊዜ ስልጣናቸውን ተነጥቀው የነበሩ ነባር ወገኖች ቦታቸውን ለማስመለስ ንግስቲቱን
የሚደግፉ በማስመሰል እንደራሴውን ተፈሪን ለመቃወም ተጣጥረው ነበር።ይህ ደግሞ ከጦር
ምኒስትሩ ሃብተግዮርጊስ ውጭ ያሉት በ1918 እንዲባረሩ ምክንያት ሆነ።በወቅቱ የሀረርጌ ገዥ
175
ጥቋቁር አናብስት
የነበሩት ደጃዝማች ገብሬ የንግድ ሚኒስትር በሆኑት የደጃዝማች ይገዙ ወንድም ነጋድራስ አሰበ
እየታገዙ በዚሁ ጥልፍልፍ ውስጥ ገቡ።47ገብሬ በዚሁ የተነሳ ተባረው በግዛታቸው ውስጥ በቁም
እስር ስር ዋሉ።ተመሳሳይ እጣ ለሌሎች ሚንስትሮች ገጥሟቸዋል።ሌሎቹም ታሰሩ።ሰለዚህ የሀረርጌ
የአስተዳደሪነት ቦታ ክፍት ሆነ።እምሩም ሀረርን ከአባታቸው የባሌ ሹመት ጋር በተመሳሳይ ወቅት
ተሾሙ።
እምሩ የሀረርጌ ገዥ ሆነው ከ1918 እስከ 1929 ድረስ ለ 11 አመታት ቆዩ።በፊት በሀረርጌ
በውትድርና ሃላፊነቶች ነበር የቆዩት።ከዚያ ቀደም ብሎም የጃርሶና የጅግጅጋ ገዥ ነበሩ።ተወልደው
ስላደጉበትም አካባቢውን በደንብ ያውቁታል።የተፈሪን ተራማጅ ፖሊሲዎችን ይደግፋሉ። እንደ
ገዥነታቸውም ሀረርጌ ላይ ለውጥን ለማምጣት ጥረዋል።ህግ ላይ አትኩሮታቸውን ስላሳረፉ
በአካባቢያቸው “የፍትህ ሰው”በመባል ይታወቁ ነበር።አንዳንዴ ጥብቅና ጨከን ያሉ ውሳኔ
ያሳልፋሉ።የግብር አጣጣል ስሪቱን ለገበሬው በሚመች መልኩ ለመለወጥ ቢሞክሩም እራሱ
ገበሬው የለመደውን ላለመልቀቅ ሲል ተቃወመው።ቀስ በቀስ ግን በዝባዥ ከነበረው
ስሪትአላቀቁት።
ከዚህ ጊዜ በፊት ታላላቆቹ ደሚኖችና ገራዳዎች የፈለጉትን ያህል ክፍያ በገንዘብም በጉልበትም
መልክ ሲቀበሉ፡ ማንም ኃይ ባይ አልነበረባቸውም። ይሄ ደግሞ ለገባር ትከሻ ሌላ ሸክም
ይደርባል።በዚህ ላይ የፈለገውን የሚቀለብ እና የሚወስድ ወታደር ይታዘዝላቸዋል።ይሄ ደግሞ
ሁኔታውን ያባብሳል።በተጨማሪም ለመንግስት የሚከፈለው ትንሽ ቢሆንም አመታዊ የአንድ ብር
ክፍያ ነበር።እምሩ ይህንን ሁሉ ቁርጥ አመታዊ የገንዘብ ክፍያ ለማስቀየር በማሰብ ወደ 300
የሚጠጉ አርሶ አደሮችን በተወካይነት በመውሰድ ሰበሰቡ።ስለ አዲሱ የግብር ስሪት ማሻሻያ
እቅዳቸው ባዋዩዋቸው ወቅትም ከዚህ በፊት ለበለጠ ግብር ተታለው ይሁን ወይም ከአንዳንድ
ጉልተኞች ማስፈራሪያና ጉቦ ወስደው ይሁን ባልታወቀ ሁኔታ ነገሩን በተጣመመ መልክ ነበር
የተረዱት።48በውጤቱም የእምሩ ሃሳብ በውስን ሰዎች ዘንድ ተቀባይነት እንዲያጣ ሆኖ እሳቸውም
ሀሳቡን ለጥቂት ጊዜ ለመተው ተገደዱ።ቆይቶ ግን በተፈሪ ይሁንታ ገበሬዎቹን ሳያማክሩ
በጨርጨር እና በሌሎችም የሀረርጌ ክፍሎች ስሪቱን ስራ ላይ አዋሉት።
በአዲሱ ስሪት ሁሉም ግብር በመንግስት ሰብሳቢዎች ተሰብስቦ በዓመት ቁርጥ ለመንግስት ገቢ
የሚሆን ሲሆን በፊት ለሚቆርጡት ለወታደር ወይም ለጉልተኛ አይሰጥም።49 የዚህ ስሪት አንዱ
መዘዝ ለወታደር የሚሰጥ ቋሚ ደመወዝ ሲሆን እምሩ ከጀመሩት በኋላ በተቀረው የሀገሪቱ ክፍል
ሊሰራበት ቻለ።ይህ በመንግስትም ወይም በክልሉ ገዥዎች (የራሳቸው ጦር ስላላቸው) የሚተገበር
ነበር።ከግብር ስሪቱ ጋር አብሮ የጉልበት ስራም ተከለከለ።ተክለሐዋርያትም ሆነ ዶ/ር ወርቅነህ
ማርቲን በእምሩ ስር ሆነው ነው የጨርጨር ገዥ የሆኑት።አዲሱን ስሪትም ለአርሶአደሩ
176
ጥቋቁር አናብስት
በእምሩ የሀረርጌ ገዥነት ጊዜ ነበር እያሱ በመጀመርያ እ.ኤ.አ 1921 የተያዙት።ለራስ ካሳም
ተላልፈው ተሰጡ።እሳቸውም ልጃቸው ደጃዝማች አበራ ፍቼ ሰላሌ ውስጥ እንዲያስቀምጧቸው
አደረጉ።ከፍቼ እስር በ1932 አምልጠው በድጋሚ ሽመሎ ገቦ ጎጃም ላይ አባይን ተሻግረው
51
በፊትአውራሪ ገሠሠ በተያዙበት ወቅትና በሀረርጌ ጋራ ሙለታ52ለመታሰርያ ወደ ተዘጋጀላቸው
ቦታ ተወሰዱ፡፡እምሩ ግን ከዚህ ጊዜ ቀደም ብሎ ከሀረርጌ ወደ ወሎ እ.ኤ.አ በ1929 ሄደው ነበር።
በዛን ወቅትም ደጃዝማች ገብረማሪያም ነበሩ እምሩን ተከትለው የሀረርጌ ገዥ የሆኑት።
***
ከድርቁ በኋላ በወሎ ውስጥ አለመረጋጋት ነበር፡፡ ደጃዝማች ስዩምና ራስ ጉግሳ አርአያ(የዮሐንስ
አራተኛ የልጅ ልጅ)አመጹን እንዲያበርዱ በተለይ የራያና አዘቦ የኦሮሞ ነዋሪዎች በአዳል አካባቢ
የሚያደርጉትን ወረራ እንዲያስቆሙ ሲሆን በውድባን እየቀጡ እምቢኝ ያለ እንደሆን እንዲወጉ
ቢታዘዙም አልተሳካላቸውም፡፡57እምሩ ወሎ ሲደርሱ ግን የወሎ ጦር መሪ በሆኑት በፊትአውራሪ
(በኋላም ደጃዝማች)ፍቅረ ማርያም እየታገዙ ህግን ማስፈን ቻሉ፡፡58 ወሎ ውስጥ ወሳኞቹ
ጦርነቶች የተደረጉት እ.ኤ.አ በመጋቢትና በሚያዝያ 1930 ሲሆን እምሩ ራሳቸው ጦሩሜዳ መሃል
ገብተው አልተዋጉም፡፡ነገር ግን የዘውዲቱ የቀድሞ ባለቤት የነበሩትን የራስ ጉግሳ ወሌን ጦር
ለመመከት እንዲረዳ ጦር በማደራጀትና (ሶስት?)ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ ለዚሁ ስራ የተላኩ
አውሮፕላኖችን በመጠቀም ጦሩን ያሰለሉ ነበር፡፡ጦርነቱን የመሩት የወቅቱ አዲስ የጦር ሚንስትር
ራስ ሙሉጌታ ነበሩ፡፡እምሩ እዚያም በተደረገው ጦርነት ላይ አልተሳተፉም፡፡ጉግሳ በጦርነቱ
ተገደሉ፡፡ ዘውዲቱም ብዙም ሳይቆዩ እ.ኤ.አ በሚያዝያ 2 1930 አረፉ፡፡ ተፈሪም አጼ ኃይለሥላሴ
ተብለው ነገሱ፡፡
178
ጥቋቁር አናብስት
እንደ ልጃቸው ሚካኤል አመለካከትም ምንአልባት በራስ መኮንን ቤት ያደጉበት ከአክራሪነት ይልቅ
በክርስትያናዊ ወግ የታሸው ባህል ሊሆን ይችላል ለዚህና ለተቀሩት የሕይወት እንዲሁም የፖለቲካ
አመለካከቶቻቸው አስተዋጽኦ ያደረገው፡፡ እምሩ ከመኮንን ችሎት የወረሱት እድሜ ልካቸውን ልክ
የሆነውን ካልሆነው ለይተው የሚመሩበት የፍትህ መርሆ ነበራቸው፡፡ አንዳንዶች እንዲያውም
እምሩ ከልጃቸውም ከተፈሪም በላይ የመኮንን ጸባይ ወርሰዋል፤ምሳሌያቸውንም ተከትለዋል ይላሉ፡
፡ (መኮንን ፍትሐዊ የሆኑ ገዢ ሲሆኑ ለምሳሌ ለሀረር ኦሮሞዎች ጥቅም የሰሩ ሀቀኛ አስተዳዳሪ
ነበሩ) በፍትሕም ረገድ በንጉስ ሚካኤል ተደንግጎ የነበረውን የሽፍታ ቤተሰቦችን ለሽፍታው ጥፋት
የመቅጣት ህግ አስወግደው በድርጊቱ ተባባሪ ከሆኑ ብቻ እንደሚቀጡ ደነገጉ፡፡
***
ለተወሰነ ወቅት እምሩ በጉረሮ ቁስለትና በሆድ ህመም ታመው ተሰቃዩ። የወሎ ገዥነታቸው ልክ
እንዳበቃ እ.ኤ.አ በ1932 ወደ አውሮጳ ለህክምና የመጀመሪያውን የውጭ ጉዞዋቸው አደረጉ።
60
ቀዶ ጥገና ወደ ተደረገላቸው ወደ ፓሪስ አቀኑ ቀጥሎ ወደ ጄኔቭ ተጉዘው ኢትዮጵያ በቅርብ ወደ
ተቀላቀለችው (የተባበሩት መንግስታት)የሊግ ኦፍ ኔሽንስን ቢሮዎች ጎብኝተው የኢትዮጵያ ተወካይ
ዘለቀን አግኝተው ጥሩ ጊዜን በአውሮጳ አሳለፉ፡፡እቃዎች ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡበት የባቡር
መስመር ስለሆነና ከጅቡቲ የሚነሳው ባቡር በድሬዳዋ ስለሚያልፍ ሐረር ሳሉ የተዋወቋቸውን
ሰዎች አገኙ። እምሩ ስለአውሮፓ ለማወቅ ፍላጎት አድሮባቸው ለመጎብኘት ይፈልጉ ነበርና ጉብኝቱ
ያሳደረባቸው ስሜት በጣም አዎንታዊና አስደሳች ሆነላቸው፡
***
የእምሩ ቀጣይ ሹመት ጎጃም ሲሆን የተሾሙት እ.ኤ.አ በህዳር 1932 ነበር።ራስ ሃይሉ
ተክለሃይማኖት የሚያስተዳድሩት ግዛት የነበረ ቢሆንም እሳቸው ግን ከግንቦት 1932 ጀምሮ
179
ጥቋቁር አናብስት
አንጋፋዎቹ ቤተሰቦች የሳቸውን መሾም እንደ ስድብ ነበር የቆጠሩት።እምሩ በተደጋጋሚ “ጎጃም
ጉልበቴን ጨረሰው” ሲሉ ይሰሙ ነበር።ከታወቁ ችግር ፈጣሪ መኳንንት መሃል ማሞ
ሃይለሚካኤል (ቆይቶ ወደ ኢጣልያ የገባውና ከጦርነቱ በኋላ በስቅላት የተቀጣው)እና አድማሱ
መስፍን ይገኙበታል።ከዚህ ውጭ በርካታ ትናንሽ አመፆች ነበሩ።
180
ጥቋቁር አናብስት
***
181
ጥቋቁር አናብስት
ከጣልያን ጋር በነበረው ጦርነት ራስ ስዩም መንገሻ የሰሜኑን ግንባር ሲይዙ ከ1930 ጀምሮ የበጌ
ምድር ገዥ የነበሩት ራስ ካሳ ሃይሉ እና ራስ ሙልጌታ የጦር ሚኒስትሩ ወድያውኑ ተቀላቀሏቸው ።
ከጥቂት ጊዜ በኋላ ኃይለሥላሴ ራስ ካሳን የሰሜን እዙ ጠቅላይ አዛዥ አደረጓቸው።ይሄ ውሳኔ
አንዳንዴ የጦር ሚኒስትሩን ለምን ጠቅላይ አዛዥ አላደረጓቸውም? በሚል ይተቻል።
የእምሩ ምድብ ከራስ ስዩም እና ከሌሎቹ ጋር መገናኘት ሳይሆን በስተሰሜን ምእራብ በማቅናት እና
በመመሸግ ጣልያኖች መቀሌን ያጠቁበታል ተብሎ በሚገመተው በሰቲት ኦም ሀጃር ወይም ራስ ካሳ
ያሉበትን አካባቢ ካልሆነም እስከ ተከዜ እና የራሳቸውን የእምሩን አካባቢ መሽገው መጠበቅ ነበር።
እምሩ በስራቸው ወደ 40000 የሚገመት ጦር የነበራቸው ሲሆን 20000 ከጎጃም ከ3000 እስከ
4000 የራሳቸው ሰው ሲሆን በመከዳት ስሜት ውስጥ እየዋለሉ ቢሆንም ግን ጣልያንን ለመውጋት
የላይላዩንም ቢሆን 74በመጡት የንግስት ጣይቱ የቅርብ ዘመድ በደጃዝማች አያሌው ብሩ
የሚመራው የጎንደር ጦር ጠቅላይ አዛዥም እሳቸው ነበሩ።አያሌው ቢዋጉም ያን ያህልም በፍላጎት
አልነበረም ሲሉ አንዳንዶች ይገልጻሉ፡፡ጣልያኖች እንደተጠበቁት በሰቲቱ (በእምሩ) ግንባር በኩል
አላጠቁም።እምሩም እራሳቸውን በምሽግ አጥረው የጣልያንን ይዞታዎች ማጥቃት ችለዋል።
ሽሬ ካሉበት ሆነው እምሩ የሽምቅ ተዋጊዎች እስከ ኤርትራ ድረስ ይልካሉ።ጣልያኖች የእምሩ ጦር
እንደ መንገድ ሰራተኛ ያለውን ያልታጠቀውን ዜጋ ሁሉ እያጠቃ እንደሆነ በመናገር ቅሬታ አሰሙ።
እንዳስላሴ ላይ ያሉት እምሩ አብዲ አዲ ላይ ካሉት ካሳና ስዩም አምባ አራዶም ላይ ካሉት
ሙልጌታ ጋር ተርራቀዋል።ጣልያኖች ካሳን በማስለቀቅ ከሙሉጌታ ጋር እንዳይገናኝ ለመቁረጥ
አሰቡ።ከተለያዩ ጦርነቶች በኋላ አንዳንድ ጊዜ ኢትዮጵያውያኖች ሲያሸንፉ 76ሌላ ጊዜ ጣልያኖቹ
ድል ሲቀናቸው ቆይቶ ካሳ ቦታቸውን ለቀው ወደ ደቡብ አፈገፈጉ።ሙሉጌታ በተለያዩ ጥቃቶች
ተሸንፈው ሲሸሹ ሳለ በኢትዮጵያውያን የራያና አዘቦ የጎሳ ሰዎች ተገደሉ።
***
ከሰለክላካ ጦርነት በኋላ እምሩ ማንኛውንም ግንኙነት ከኃይለሥላሴ ጋር ሃገሪቱን ለቀው በስደት
እስኪሄዱ ድረስ ማድረግ አልቻሉም።
184
ጥቋቁር አናብስት
***
ኃይለሥላሴ ሀገር ከመልቀቃቸው በፊት በራስ ካሳ የተጠራ ሸንጎ ንጉሱ ምን አይነት አካሄድ
መምረጥ እንዳለባቸው ለመምከር ተሰበሰበ። አንዳንዶች መናገሻው በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ
ከሌላ ቦታ ሆኖ ጦርነቱን ለመቀጠል ሃሳብ ሲያቀርቡ ጎሬ የአዲሱ የመንግስት መቀመጫ እንድትሆን
ሃሳብ ቀረበ።የሀገር ውስጥ ሚንስትርና የሴኔት ፕሬዝዳንት የነበሩት ቢትወደድ ወልደፃድቅ
84
ለመዋጋት ቢያረጁም መኮንን እንዳልካቸው ኢሉባቡርን ለቀው ወደ ግንባር ሲሄዱ እሳቸውን
ተክተው ጎሬ መናገሻዋ የሆነችው የኢሉባቡር ገዥ ስለሆኑ ኢሉባቡር ደግሞ የወልደፃድቅ ግዛት
እንደመሆኗ አዲሱ መንግስትንም እንዲመሩ የታጩት እሳቸው ነበሩ።ኃይለ ሥላሴ እንደእምሩ ያሉ
አርበኞችን ተቀላቅለው በመሪነት እንዲዋጉና እንዲያዋጉ የቀረበው ሃሳብ ተቀባይነት አጥቶ ወደ
ውጭ በመሄድ ለሊግ ኦፍ ኔሽን አቤት እንዲሉ ተመከረ።እሳቸውም አቤቱታቸውን ያጠናክር
ይመስል በእርሳቸውም ትዕዛዝ ሀገሪቱ እየተዋጋች እንደሆነች ለማጠየቅ ሲባል ምንም ቢሆን
የአርበኝነት ትግሉ እንዳይቋረጥ አዘዙ። ደጃዝማች መኮንን እንዳልካቸው ፣ራስ ጌታቸው አባተ
የዋግሹም አባተ ልጅ እምሩን ተቀላቅለው ጦርነቱን እንዲቀጥሉ ታዘዙ።እነሱ ግን አሻፈረኝ ብለው
ሀገሪቱን ጥለው ሸሹ፡፡ 85
86
"ሽቅርቅሩ መልከመልካሙ፣ግዙፉና፣ልፍስፍሱ"መኮንን ወደ እየሩሳሌም ራስ ጌታቸው ደግሞ
ካይሮ ገብተው ቆይተው ከጣልያኖቹ ጋር አበሩ።
እምሩ በአዲስ አበባ ስለነበረው ምክክር የሚያውቁት ነገር አልነበረም።ነጋድራስ (በኋላ ደጃዝማች)
ይገዙ በሃብቴ 87ኃይለሥላሴ ጦር ግንባር ላይ ሳሉ መንግስቱን በአደራ ተረክበው ያስተዳድሩ ነበር።
ኃይለሥላሴ ግንባር ሳሉ ቢሸነፉ ወይንም ቢሞቱ የመጠባበቂያ እቅዶችን የሚያዘጋጀው ቡድን
ሊቀመንበር ነበሩ።ንጉሱ ሃገር እንዲለቁ ከተመከረ በኋላ የወልደ ፃዲቅ እጣፈንታ ግልፅ አልሆነም።
የታቀደው በኢትዮጵያ እየተዋጉ እንዲቆዩ ነበር።ይህም እቅድ ቀረ።በጎሬ የመንግስቱ መሪ የነበሩት
ወልደፃዲቅ በጦርነቱ መግፋት ባይፈልጉም በአርበኝነት ለመቀጠል ለሚፈልጉት የሽንገላ ይሁንታ
185
ጥቋቁር አናብስት
በርካታ የጦር መሪዎች ኃይለሥላሴ በሽሽት ሲሄዱም ሆነ በዚያው አካባቢ አብረው ለቀቁ።
የምስራቅ እዙም አመራር እንዲሁ።ፊትአውራሪ ተክለሐዋርያት እቴጌይቱ ከነ ልጆቻቸው ጋር ወደ
ጅቡቲ በባቡር በማቅናት ላይ መሆናቸው ተነግሯቸው በአፍደም ጣብያ ላይ እንዲያገኟቸው
ተጠይቀው ወደ ባቡሩ ሲገቡ ንጉሱን በማግኘታቸው ተደነቁ።ንጉሱ በሽሽት ላይ መሆናቸውን
አላወቁም።(ይህ አንዳንድ ፀሃፍት ባቡሩን አስቁመው ኃይለ ሥላሴን እንዳይሄዱ ለማስገደድ ሞከሩ
ከሚሉት በተቃራኒ ነው)ንጉሱ በባቡር ወደ ውጭ በመውጣትላይ እንዳሉ ሲሰሙ በውሳኔያቸው
አልተደሰቱም።ሁለቱ ወደ ድሬዳዋ እየሄዱም በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ተወያዩበት። ንጉሱ ግን
በአማካሪዎቻቸው ምክር ፀንተው(21ለ3 በሆነ ድምጽ በተወሰነው)ወደ ጅቡቲ አቀኑ ምንም እንኳ
አርበኞቹ ቆይተው በጦርነቱ እንዲቀጥሉ ፈልገው ቢስማሙም።ድሬደዋ ላይ ተክለሐዋርያት ከባቡር
ወርደው ወደ ጦር መሪዎቹ በመመለስ ጦርነቱን እንዲቀጥሉበት ለማደፋፈር ሞከሩ።ነገር ግን ሀረር
186
ጥቋቁር አናብስት
እና በድሬዳዋ በተካሄደው ጦርነት የሚሸሸውን ህዝብ ቀልብ መሳብ ሳይችሉ ቀርተው ንጉሱ ቢኖሩ
ግን ይህን ስደት ለማስቆም በተቻለ ነበር ብለው እያሰቡ በስተመጨረሻም እሳቸውም ወደ ጅቡቲ
አመለጡ።
****
በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ እምሩ ውጊያውን ቀጠሉ።ብላታ ታከለ ወልደሐዋርያት ሌላኛው የጦር
መሪ ወዲያውኑ እምሩን ትተው ከበርካታ ጦር ጋር ወደ ጎንደር (በጌምድር) አቀኑ።ጣልያኖቹ ጅማን
ሲይዙ እዚያ የነበረው መሪ አባጆቢር አባዱላም ለጣልያኖቹ አደረ።91 ሰለዚህ እምሩ ወደ ጅማ
መግባት አልቻሉም።ከዚያ የመጡ ብዙ ስደተኞች የሳቸውንናየጥቁር አንበሳ ተዋጊዎች ጥበቃን
ሽተው መጡ። ከስደተኞቹ መምጣት በፊት በእምሩና በጣልያኖች መሃል አጋሮ ላይ ሀይለኛ ጦርነት
ተደረገ ።ከዚህ ጦርነት በኋላ የተወሰኑ የጦሩ አባላት ወደ ጅማ ገፍተው የነበር ቢሆንም ነገር ግን
ከስደተኞቹ ጋር ተገናኙ ።ከመሃላቸውም ታቦት የያዙ ካህናት ነበሩ ።እነዚህ ተሰዳጆች የጦሩን ጉዞ
ገቱት።እምሩ ከፋ ቦንጋ ለነበሩት ለደጃዝማች ታዬ ጉልላቴ ሊልኳቸው በማሰብ ወደ አጋሮ
ተመልሰው የጎጀብን ወንዝ አቋረጡ።ጌራ ሲደርሱ ጣልያኖች ደረሱባቸው። እዚያም በጣም ከባዱ
ውግያ ተደረገ።ከሁሉ የከፋው ጦርነት ቀኑን ሙሉ ዋለ።92ጣልያኖች በአየር ቢታገዙም ውሃ
አግኝተው መትረይሶቻቸውን እንዳያቀዘቅዙ ከውሃው በመቆረጣቸው ተቸግረው እየተዋጉ ውለው
ቢያሸንፉም ከሁለቱም ወገን ብዙ ሰው አለቀ።ጣልያኖች ጦርነቱን ቢያሸንፉም ኢትዮጵያኖቹን
በዝግታና ባልተቀናጀ መልክ ለማሳደድ ችለዋል።93እምሩ ከነጦራቸው ጎጀብ ሲደርሱ ከማዶ
የደጃዝማች ጉልላቴ ግዛት ላይ ጣልያኖችን አሻግረው መመልከት ቻሉ። የዛን ጊዜ ነበር ደጃዝማች
ታዬ እጃቸውን ሰጥተው ሊሆን እንደሚችል ምንአልባትም ከጣልያኖች ጋርም ተባብረው እየሰሩ
ሊሆን እንደሚችል ያወቁት።ታዬ በዘመቻው ወቅት ከጣልያኖች ጋር ተገናኝተው በሀሰት
ጣልያኖችን እየወጉ እንደሆኑ ከጣልያኖች ጋር ካበሩ በኋላ ለእምሩ እንደፃፉላቸው ነው የተነገረኝ።
ቅዳሜ ላይ እምሩ ሰፈራ አደረጉ።ከፊታቸው ያልተዋጋ ትኩስ ከከፋ የመጣ የጣልያን ጦር
ከጀርባቸው እያነከሰ የሚከተላቸው የጅማ ትርፍራፊ ጦር አጣብቋቸዋል፡፡ነገር ግን ምንም ጦርነት
አልተካሄደም።በምትኩም ድርድሮች ተካሄዱ።እምሩ በጦርነቱ ህፃናት፣ሴቶች፣አእሩግ፣ የቤተክህነት
ንብረት የያዙ ካህናት ስለነበሩበት ለማይዋጉት ከጅማ ለመጡት ስደተኞች ደህንነት ፈለጉ።ለጊዜው
በዚህ በኩል መስማማት ላይ የተደረሰ መሰለ ።ስደተኞቹም ወደ ከፋ ወንዙን ማቋረጥ ጀመሩ።
በኋላ በቦታው ላይ የነበረው ባለስልጣኑ ኮለኔል እምሩ ስድተኞቹን ከራሳቸው ካወረዱ በኋላ
ከተዋጊዎች ጋር ሲቀሩ እንደገና መዋጋት ለመጀመር አስበው ነው በማለት ስደተኞቹን ወደ እምሩ
ሰፈር (ኮረብታ ላይ ያለ ነበር) መለሳቸው።ከዚያ በኋላ እምሩ እጅ እስኪሰጡ ድረስ ድርድሩ ለ3
ቀናት ቀጠለ።በዚህ ወቅት ጥይት እያለቀባቸው ነበር።ጣልያኖች ግን ይህንን አላወቁም ።በእጅ
187
ጥቋቁር አናብስት
***
ግራዝያኒ ኢጣልያ ውስጥ ጓደኛ ማንን ላምጣሎት ቢላቸው ሃዲስ አለማየሁን (ረዳታቸውን) ታዬ
ጉልላቴን ፣ይልማ ደሬሳን ቢሉም ከጥቂት አመታት በኋላ ታዬ ጉልላቴና ይልማ ወደ ኢትዮጵያ
እንዲመለሱ ጠየቁ ። በተለይ ታዬ ከጣልያን ጋር እንዳልተዋጉ በማስመስል የንግስና ዝርያ
ስላላቸው ጣልያኖቹ ቢያነግሱኝ ብለው ተመኝተው ነበር።እነሱ ከለቀቁ በኋላም እምሩ ግርማቸው
ተክለሐዋርያትን አገኙ።በዚህኛው የአብሮነት ቆይታቸው እምሩ እንደፃፉት ከሆነ ግርማቸው
ተክለሐዋርያት ከነገረኝ በተቃራኒው በተወሰነ ደረጃ የመንቀሳቀስ ነፃነት ተሰጥቷቸዋል።እምሩ
እሁድ ሲሆን ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ ደሴቷ ላይ የካቶሊክ ቄስ ያነጋግራሉ፡፡የተወሰነ
ጣልያንኛም ያውቃሉ።ሊፓሪ ላይ ሳሉም የጣልያንኛ አማርኛ መዝገበ ቃላት አዘጋጅተው ሁሉ
ነበር።የደሴቲቱን ነዋሪዎችንም ሌሎችንም ታሳሪዎችንም መግባባት ችለው ነበር።አብዛኞቹ
ጣልያኖች ሲሆኑ አፍቃሪ ሶሻሊስት ወይም ማርክሲስት ነበሩ።የተወሰኑ የዩጎዝላቪያ ዜጎችም ነበሩ
።97 በምን ያህል እንደሆነ መናገር ባይቻልም ርዕዮታቸው በእምሩ ላይ ተፅእኖ አሳድሮ ሊሆን
188
ጥቋቁር አናብስት
እምሩ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ካላቸው ከፍተኛ ቦታ አንፃር በስነ ፅሁፍ ሊሰጣቸው ከሚገባው
ቦታ በላይ በዚህች መድብል ላይ ተሰጥቷቸዋል ።ጣልያን በሊፓሪ ደሴት በግዞት ሳሉ ነበር
የስነፀሑፍ ስራቸውን የጀመሩት የመጀመሪያ ልብወለድ ስራቸውን በንፁህና በሚነበብ የእጅ
ፅህፈት የፃፉት በ1933 "የአለም ትግል"የሚል ርዕስ ነበረ።98የመፅሐፉ ታሪክ አንድ ውጭ ቆይቶ
በመጣ ተራማጅ እና በባህል ተጽእኖ በታሰሩ ኢትዮጵያውያን መካከል ያለ በእድገት እና ስልጣኔ
ዙርያ የሚደረግ ውይይት ነው።99ምንም እንኳ ይህ የእምሩ የመጀመሪያው መፅሐፍ ቢሆንም
የታተመው መጨረሻ ላይ ነበር።(በሕይወት ሳሉ ከታተሙት ለማለት ነው ።ግለታሪካቸው ለምሳሌ
በሕይወት እያሉ አልታተመም፡፡ምንአልባት በኋላ ሊታተም ይችላል) ኃይለሥላሴ ረቂቁን እምሩ
ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ አንብበውት ለመታተም ጊዜው ገና እንደሆነ አሰቡ። ስለዚህ የታተመው
በ1967 አብዮቱ ሲፈነዳ እና ኢትዮጵያ ለአዳዲስ ሃሳቦች በሯን ክፍት ባደረገችበት የመንግስት
ለውጥ የመጀመሪያው ዓመት ነው።“አለማዊ ትግል” በሚል ርእስ ነበር የወጣው ።ከዚህ መፅሐፍ
በፊት እምሩ ግጥሞችን ጽፈው ቤት ውስጥም ለቤተሰቦቻቸው ያነቡላቸው፤ በሚሰበሰቡበት
ስብሰባዎች ማስታወሻ እየያዙ በልዩ ልዩ ጉዳዮች ዙርያ ፅሁፎችን ይፅፉ ነበር።ታትመው ግን
አያውቁም ።እምሩ ከትውስታቸው ባለ ሁለት ቅፅ የግልታሪካቸውን የመጀመርያ ክፍል በሊፓሪ
ደሴት ላይ ሳሉ ፅፈዋል።100
በአንድነት ሀይሎች ግስገሳ ምክንያት እምሩ ወደ ደቡብ ጣልያን ካሊብራ ውስጥ ወዳለችው ሉንጎ
ቡኮ ተዘዋውረው ለመጨረሻዎቹ የ6 ወራት የጣሊያን ቆይታቸው በግዞት ተቀመጡ።101በጣልያን
ቆይታቸው በጥሩ ሁኔታ እንደተያዙ ይናገራሉ።በአንድነት ሀይሎች ከእስር ነፃ ወጥተው እ.ኤ.አ
በጥቅምት 1943 ንጉሱ ወደ ኢትዮጵያ በተመለሱ በሁለት ዓመት ከግማሹ እ.ኤ.አ በግንቦት 5
1941 ወደ ሀገራቸው ተመለሱ።
189
ጥቋቁር አናብስት
ካሳለፉ በኋላ ወደ እየሩሳሌም ሄደው ቆዩ።ህፃናቱም ለስድስት አመታት እስከ ህዳር 1942 ድረስ
ትምህርት ቤት ገቡ።የእምሩ ባለቤት፤ የታላቅ ሴት ልጃቸው ሴት ልጅ፤ የጉዲፈቻ ልጃቸው፤
(ጫማሽ ወርቅ ሀዋዝ )እና የተወሰኑ ጥቂቶች በሻህ ጊራህ ይህን ወቅት አሳልፈዋል።102
***
አዲስ አበባ ከተመለሱ በኋላ እምሩ በመናገሻ ከተማዋ ለጥቂት ወራት ተቀመጡ ።ምንም እንኳ
ለሌላ የገዥነት ሹመት ፍላጎት ባይኖራቸውና ለወጣቶች እድል መስጠት ቢፈልጉም ምንአልባትም
በንጉሱ ግፊት ለበጌምድር ገዥነት ተሹመው እ.ኤ.አ በግንቦት 1944 ለ10 ወራት በሹመት ወደ
ቆዩበት ጎንደር ሄዱ።ጎንደር ላይ አመፃዎችና ሌሎች ችግሮች ነበሩ።ነዋሪዎቹም ለመተዳደር
ያዳግታሉ።እምሩ ጨከን ያሉ እርምጃዎችን በመውሰድ ህግና መረጋጋትን አሰፈኑ።ወደ ክፍለሀገሩ
ለመግባት እራሱ የራሳቸውን ጦር ይዘው መሄድ ነበረባቸው።
***
190
ጥቋቁር አናብስት
የእምሩ በመሬት ስሪቱ ላይ ያለውን ጥያቄ የመመለስ ፍላጎት ከሀረር የጀመረ ነበር።የጎሳ የመሬት
አጠቃቀም ጥያቄዎች በመጡበት ጊዜያት የመሬት ጥያቄዎች በድጋሚ በወሎ መነሳት ጀመረ።
በባለይዞታ ገበሬዎችና በዘላኖች መካከል ተነስቶ እስከ ዘመቻ እና ዝርፍያ የደረሰ ችግር አስከተለ፡፡
በጎጃም የነበሩ ፊውዳል ጌችቶም መሬት ለሌለውና ተከራይቶዋቸው በሚያርሰው በገበሬው ላይ
ኑሮውን አክበዱበት።በጦርነቱ ወቅት የመሬት ጉዳይ ቀደም ብሎ አንድ መፍትሄ ቢያገኝ ኖሮ
የመከላከል ጦርነቱ የተሻለ እንደሚሆን ያስባሉ።በእስር ላይ እያሉም በዚህ ጉዳይ ላይ በጣም
አስበውበታል።ስርነቀል የመሬት ማሻሻያ ሀሳቦቻቸው እንደ ራስ ካሳ ቤተሰብ፤ ራስ መስፍን
ስለሺ(አርበኛና ቀጥለው የሸዋ ገዥ)ምንም እንኳ ከቤተክህነት ጋር ቅርበት ቢኖራቸውም ቅሉ
ቤተክርስቲያኗን ጨምሮ የሀብታም ባለመሬት ከበርቴዎችን ጠላትነት ገዝቶላቸዋል። የመሬት
ማሻሻያ ሀሳባቸውን የሚደግፍ አላገኙም።የግላቸውን መሬት ማደል ጀመሩ።(በተለይ በአርሲና
በሌሎቹ ቦታዎች) ለድሀ ገበሬዎች ለጭሰኞች ለራሳቸውም ቤተሰብ ጭምር አከፋፈሉ።እምሩ
በመሬት ባለይዞታነት ወሰን መጠን እንዲበጅለት፤ብዝበዛን ለማስቀረት ሲባል ከጭሰኞች
በሚሰበሰበው የግብር መጠን ላይ ወሰን እንዲበጅም ይፈልጋሉ።104
191
ጥቋቁር አናብስት
***
ምንአልባትም ንጉሱ ካሉበት አጣብቂኝ ሁኔታ ለመገላገልም ፈልገው ይሆናል በዲፕሎማሲ ተልእኮ
ከሀገር ውጭ የላኳቸው።እ.ኤ.አ በሚያዝያ 1946 እምሩ በአምባሳደርነት ማእረግ ወደ አሜሪካ
ተልከው እስከ የካቲት 1954 ድረስ ቆዩ።አሜሪካ እያሉ እምሩ ሁለተኛ ልብወለዳቸውን ፃፉ።
ርእሱ "ፊትአዉራሪ በላይ" ሲሆን የመጀመሪያው የታተመው መፅሀፋቸው ነው ።በ1948 አ.ም
ታትሞ ወጣ።በ1956 አ.ም በድጋሚ ታተመ።ቀጥሎም በ1976 አ.ም ለሶስተኛ ግዜ ሲታተም ወደ
እንግሊዘኛ ቋንቋም ተተርጉሟል ።
***
ከአሜሪካ ሲመለሱ ለእሳቸውና ለሚስታቸው ልኡልና ልእልት የሚል መአረግ ተሰጣቸው ። እነዚህ
በጊዜው አዳዲስ መአረጋት ሲሆኑ የነገሥታት ዘር ላላቸው በዘውዲቱ ጊዜ ለነበሩ የሚሰጡ ናቸው
።106 ቢሆንም ከተመለሱ በኋላ ምንም አይነት የመንግስት ስልጣን አልተሰጣቸውም።
ምልከታቸውን የማይጋሩ ሰዎች ይህ እንዳይሆንና በተቻለ ትንሽ ተፅዕኖ እንዲኖራቸው ከመታተር
አልቦዘኑም። አብዛኞቹ መሬታቸውን መስጠት ሲጀምሩ ስጋት ቢገባቸውም በተራማጆች እና
በህዝቡ ዘንድ ታዋቂነትን አትርፎላቸዋል።
የእምሩ ቀጣይ ሹመት የህንድ አምባሳደርነት ነው።ይህም እ.አ.አ ከግንቦት 1954 እስከ 1959
አጋማሽ ለአምስት አመታት ያህል ነው።ሌሎች ሹመቶችንም ለምሳሌ እንደ ኤርትራ ገዥነት ያሉ
ወይንም ጠቅላይ ሚንስትር በመሆን ሁሌ የሚያወዛግበውን የህገመንግስት ጉዳይ ለመከለስ
ቢፈልጉም ንጉሱ አልተቀበሏቸውም። ምንአልባት ብዙ ማሻሻያዎችን ፈልገው ሊሆን ይችላል።
በወቅቱ ባለው ህገመንግስት ስር በሚኒስትርነት መስራት አለመፈለጋቸውም ኃይለሥላሴን
አስቆጣቸው።እምሩ ስለ ዘውድ መማክርቱ ያላቸው ምልከታ ዝቅተኛ የነበረ ሲሆን አባልም መሆን
አይፈልጉም።ሰለዚህ ወደ ህንድ ተላኩ፡፡ህንድና ባህሏን ወደዷት ኔህሩንና የኮንግረስ ፓርቲውንም
አደነቁ።
192
ጥቋቁር አናብስት
****
በ1953 ታዋቂው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ በግርማሜ ንዋይ በወንድሙ መንግሥቱ ንዋይ እና
በወርቅነህ ገበየሁ መሪነት ተካሄደ።ገርማሜ በአሜሪካ ቆይታው እምሩን ኮለምብያ ዩንቨርስቲ
ከመግባቱ በፊት በዋሽንግተን ጎብኝቷቸዋል።እምሩ መንግስቱን ከርቀት ወርቅነህን ግን በተሻለ
ያውቁታል።108እምሩ ስለመፈንቅለ መንግስቱ እቅድ የሚያውቁት ጉዳይ አልነበረም።
አላማከሯቸውምም፡፡በመፈንቅለ መንግስቱ አመራሮች ለጠቅላይ ሚኒስትርነት መታጨታቸውን
በሬድዮ ሲነገርም አልሰሙም።እምሩ ለለውጥ የቆሙ አረጋዊ የፖለቲካ ሰው ናቸዉ ።በመስተዳድሩ
ውስጥ ያሉ ወጣት ተራማጆች ለመሪነት የሚመለከቷቸው ሰው ነበሩ። አሮጌውን ቡድን እንዲሻሻል
የሚጥሩ በቢሮክራቶችና በባለስልጣኖች ለተበደሉ ገበሬዎች የሚያዝኑ ሰው ናቸው።በዚህም
መክንያት ሳይሆን አይቀርም አማፅያኑ በጠቅላይ ሚኒስትርነት የሾሟቸው።
በመፈንቅለ መንግስቱ መሪዎች መካከል እንኳን የቀኝና ግራ ዘመም ክፍፍሎች ነበሩ፡፡ ወርቅነህ ወግ
አጥባቂ የነበሩ ሲሆን ግርማሜ ስርነቀል ለውጥን የሚፈልጉ አምባገነናዊ ሌኒናዊ እንዲያውም
ስታሊናዊ ጸባይ ያላቸው ናቸው ዲሞክራትም አልነበሩም፡፡109ጠንካራ ሰራተኛ፤ ጥሩ ተናጋሪ እና
በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ጥንቁቅ በስልጣን መባለግንም የሚቃወሙ ነበሩ፡፡ መዋቅሩ ሚስጥራዊ
ስላደረጋቸው እሳቸውን አውቆ ለመገምገም አዳጋች ነው፡፡ 110መፈንቅለ መንግስቱ የተለየ ጉዳይ
ስለሆነ እዚህ አናነሳውም፡፡111እምሩ ንጉሱ ከተመለሱ መፈንቅለ መንግሰቱም ከከሸፈ በኋላ ዳግም
ከንጉሱ ጋር ሊቀራረቡ ቻሉ፡፡
193
ጥቋቁር አናብስት
***
ከመፈንቅለ መንግስቱ ሙከራ በኋላ በኢትዮጵያ ይደረጉ የነበሩ የፖለቲካ ክርክሮች ቆሙ፡፡ ነገሮች
በብዙ መልኩ እየጠበቁ መጡ፡፡ለአብነትም መገናኛ ብዙሃን ይበልጥ ጫና ተደረገባቸው፤ታፈኑ፡፡
የመጽሐፍ ሳንሱርም እየጠበቀ እና አዳዲስ ሃሳቦችን የማያሳልፍ እየሆነ መጣ፡፡ ከብዙሃኑ አይንና
ጆሮ ቢርቅም ቅሉ የኢኮኖሚው ክርክር ግን እንደቀጠለ ነበር፡፡
እ.ኤ.አ በ1965 ወይም 1966 አካባቢ ኃይለሥላሴ የመሬት ማሻሻያ ጥያቄውን የሚመለከት
ኮሚቴ አቋቋሙ፡፡ በፓርላማው ስልጣን ዙርያ ጠቅላይ ሚንስትሩ ሌሎች ሚንስትሮችን ይሹም
ተጠሪነታቸው ለሱ ይሁን ወይም ለንጉሱ በሚሉትም ዙርያም ክርክር ተካሄደ፡፡ አብዛ,ኞቹ ጉዳዮች
የተነሱት እ.ኤ.አ በ1965 አካባቢ ነው፡፡ እምሩም በነዚህ ጉዳዮች ላይ በንቃት ይንቀሳቀሱ ነበር፡፡
ንጉሱ ለሙከራ ያህል ሶስት እጩዎችን አቅርበው በፓርላማው አብዛኛውን ድምጽ የሚያገኘውን
እንዲሾሙ ፤ጠቅላይ ሚንስትሩም እራሱ ሚኒስትሮቹን እንዲሾም ፤በሃገሪቱ ስላለውም የአስተዳደር
ሁኔታ ተጠያቂ እንዲሆን የሚል ሃሳብ አቀረቡ፡፡ በነዚህ ድርድሮች ዙርያ ለመከራከር ታላላቅ
ጉባኤያት ቢደረጉም በመጨረሻ ንጉሱ ግን ሁሉንም አልተቀበሉም፡፡112ነገር ግን እ.ኤ.አ በ1966
ሃሳባቸውን ቀይረው አክሊሉ ሃብተወልድን በጠቅላይ ሚኒስትርነት በመሾም የራሳቸውን
ሚንስትሮች እንዲሾሙና ለመንግስቱ ስራ ሃላፊ እንዲሆኑ አደረጉ፡፡ይህ የወረቀት ውሳኔ ብቻ ሆኖ
እውነታው ግን ነገሮች ባሉበት መቀጠላቸው ነው፡፡ ሁሉንም ነገር እራሳቸው ይወስናሉ እያረጁም
ሲሄዱ በነገሮች ላይ ያላቸው ቁጥጥር እየላላ ሄደ፡፡
የእምሩ ኃይለሥላሴን ያህል ፈርጀ ብዙ ስኬት የተጎናጸፉ ሰዎች ጥቂት ናቸው፡፡ ከደህና ቤተሰብ
የመጡና ሲጀመር ጀምሮ ጥሩ እውቂያ የነበራቸው ናቸው፡፡ ይሄም ወደ ስልጣን ማእከሉ እንዲጠጉ
የእድሜ ልክ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ነገር ግን የራሳቸው አስተሳሰብ ያላቸው ሰው ስለነበሩ ይሄ
በስልጣን ላይ ከነበሩት ጋር ባመጣው መቃቃር፤የበጎ አድራጎት ስራቸውም በህዝቡ ዘንድ ታዋቂ
194
ጥቋቁር አናብስት
ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉም ሆነ በውጭ የሚኖሩ የውጭ ዜጎች ለእምሩ ያላቸው ከበሬታ ከፍ ያለ
ነው፡፡ክብራቸውን የጠበቁ ጌታ፤ዝነኛ ጦረኛ፤አስተዳዳሪና ፖለቲከኛ ነበሩ፡፡ ይሄ በጠላቶቻቸው
ሰፈር እንኳን ክብርን እንዲቀዳጁ አስችሏቸዋል፡፡ ቁጥብ ፤ልታይ ልታይ የሚል ባሕርይ
ያልነበራቸው ቢሆንም በቅርብ ጓደኞቻቸው ዘንድ ተግባቢና የሚከበሩ ሰው ናቸው፡፡116
እርዳታቸውን ለሚሻ ቅርብ ላገኙት ሁሉ መልካም ነበሩ፡፡ ባስተዳደሯቸው ግዛቶች ከሳቸው ቀደም
ብለው ይሰሩባቸው የነበሩ የደም ካሳና ላለመታሰር የሚፈጸም ክፍያን አስቀርተዋል፡፡አንዳንዶች
በዚህ ምክንያት ጨካኝና ምህረት የለሽ ቢያደርጓቸውም ሁሉንም በእኩል አይን እንደሚያዩና
ፍትሐዊ እንደሆኑ ያምናሉ፡፡እያሱ በተወገዱበት ጦርነት ብዙ ሙስሊሞችን ሀረር ላይ
ጨፍጭፈዋል ብለው የሚወነጅሏዋቸው ሙስሊሞች እራሳቸው«የፍትህ ሰው»ነበሩ ሲሉ
ቃላቸውን ይሰጣሉ፡፡ልጃቸው ሚካኤል እንደሚያምነው ተገቢ ያልሆኑ የጭካኔ ድርጊቶች
ተፈጽመዋል የሚለውን ውንጀላ የተጋነነ እንደሆነና ምንም አይነት ማስረጃ የሌለው እንደሆነ
ይገልጻል፡፡ 117 ምንም ይሁን ምን ግን እነዚህ ውንጀላዎች የእኒህን ሰው ምስል እና ዝና
ሊያደበዝዙት አልቻሉም፡፡ከንጉሳዊ ቤተሰብ ስለመወለዳቸው ተኩራርተው ሲናገሩ አይደመጡም
ትሁት ናቸው፡፡ ለሰራተኞቻቸው፤ለተከታዮቻቸውናለረዳቶቻቸው በጣም ጥሩ ሰው ነበሩ፡፡
118
ፍትሕ የተጓደለች መስሎ ከተሰማቸው በጣም ሊናደዱ ይችላሉ፡፡ከዚህ ባለፈ ከልጃቸው ጋር
ደግሞ ቼዝ ሲጫወቱ መሸነፍን ይጠላሉ፡፡
በሳቸውም ሆነ በሚስታቸው የዘር ግንድ ውስጥ ታዋቂ ስሞችን ማግኘት ይቻላል፡፡ ንጉስ
ሳህለሥላሴ፤ራስ መኮንን፤ኃይለሥላሴ፤ራስ ጎበና አቲከም ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ልጃቸው ሚካኤልን
ለምን የእምሩን የአባት ዘር አልተከታተላችሁም ብዬ ጠይቄው ለምን እንደሆነ አያውቅም ፡፡
የእምሩ ቅምአያት እርገጤቃል መንዝ ውስጥ በመሬት ተጣልተው ሰው ገድለው በቀል እና ከገደሉት
ሰው ቤተሰቦች ጋር የሚካሄደውን እሰጥ አገባ ለመሸሽ ሊሆን ይችላል ወደ ተጉለት ሄዱ፡፡ ሚካኤል
ይህን አያውቅም፡፡ታሪኩን ስነግረው ቤተሰቡ በሃይለኝነታቸው በጦረኝነትና በአደን ስለሚታወቅ
ሊሆን እንደሚችል ያምናል፡፡ እምሩም የዘር ሆኖባቸው ይሄን መንፈስ ይጋሩታል፡፡ አጎታቸው
ቀኛዝማች ታፈሰ አባይነህ በፊትአውራሪ ገበየሁ ይታዘዙ ከነበሩት ሁለት የጦር ምክትል አዝማቾች
አንዱ ሆኖ በአጼ ምኒሊክ ስር አድዋ ላይ ሲዋጋ ሞቷል፡፡ አባቱ ቀኛዝማች አባይነህ እርገጤቃልም
በጦርነቱ ሞተዋል፡፡እምሩ ስለዚህ የዘር ግንዳቸው የማይናገሩበት ምክንያት አይታወቅም
ምናልባትም የእርገጤቃል ትዝታ ያሳፍራቸው ይሆናል፡፡ ቤተሰባቸው ግን ቀድሞም ሆነ አሁን
መንዝ ካሉት ዘመዶቻቸው ጋር በጥሩ ሁኔታ ይገናኛሉ፡፡
195
ጥቋቁር አናብስት
እምሩምንም እንቅፋት ቢያጋጥማቸው መዘዙ ቢከፋም ላመኑበት ነገር የሚቆሙ የማይናወጥ አቋም
ያላቸው ሰው ናቸው፡፡የልጅነት የሃያል ጦረኝነታቸውና ጥብቅ ገዢነታቸው ምስል በተራማጅ
ለውጦቻቸውና በፍትሓዊ አስተሳሰባቸው ተሸርሽሮ ጠፍቷል፡፡ ቆይቶ «ከጊዜያቸው የቀደሙ»
የሚያስብላቸውን ሀገርን የማዘመን ትግል በሁኔታዎች ለመርጋት ፍላጎት ካላቸው ሃያላን በስተቀር
በተቀሩት ዘንድ ሁሉ ይበልጥ ታዋቂ አድርጓቸዋል፡፡ ኃይለሥላሴ ከስልጣን ተነስተው ለውጦች
ሲመጡ እንደ 1967 የመሬት አዋጅ ያሉ እምሩ ከገመቷቸውም በላይ ነበሩ፡፡ ቢያንስ በአብዮቱ
ለጋ አመታት በአንዳንዶቹ ለውጦች ሳይደሰቱ አይቀሩም፡፡ በአብዮቱ መሪዎች ሳይቀር እስከእለተ
ሞታቸው ድረስ ተከብረው ነው የኖሩት፡፡
ማስታወሻ
3)ምንም እንኳን ምንጬ በታሪኮቹ ውስጥ ሸሪክ የነበረና ለማሰማመር ቤተሰባዊ ፍላጎት
ቢኖረውም፡፡ቀጥተኛ እውነታዎቹን ለማጣመም የሚያበቃ ነጥብ ያለ አይመስለኝም፡፡ ግምት ግላዊ
ነው፡፡ የአንድ ሰው እይታ ደግሞ የሌላውን ያህል ዋጋ ሊኖረው ይችላል፡፡
4)ሚካኤል እምሩ የኔን የታሪኩን ክፍል አላነበበውም፡፡ የነገረኝን ታሪክም እና በእራሴ ቃላት
በድጋሚ የተናገርኳቸው አህጽሮት ነው፡፡ ምንአልባትም የተወሰነውን መቀየር ፈልጎ ሊሆን ይችላል፡
፡
5)ጥናቴን የጀመርኩት በቀድሞ የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ተማሪ ጥናት በማንበብ ነው፡፡ተማሪው
መረጃዎቹን ያገኘው ከተለያዩ ምንጮች ሲሆን ሚካኤል እምሩንና ራሳቸውን እምሩ ጨምሮ
196
ጥቋቁር አናብስት
ልጆቻቸውን ለማግኘት ይችል የነበር ቢሆንም ጥናቱ ግን በስህተት የተሞላና ለታሪካዊ ሰነድነት
መብቃትም የማይችል ነበር፡፡ ይሄ መሆኑ የሚያሳዝን ነበር፡፡
6)ኦክስፎርድ የተማሩት ሚካኤል እምሩ ከዚያ በፊት በተለያዩ ሹመቶች ላይ የሰሩ ቢሆንም
በUNCTAD የኢትዮጵያ ተወካይ ሆነው ሳለ ነበር ወታደራዊው መንግስት ኃይለሥላሴን ገልብጦ
ስልጣን የያዘው፡፡ አዳዲሶቹ መሪዎች ከጄኔቫ ጠርተውት ለተወሰነ ወቅት ጠቅላይ ሚንስትር
ቀጥሎም የፖለቲካ አማካሪ ሆኖ ሳለ ነበር ራስ እምሩ እ.ኤ.አ በ1980 ያረፉት
7)የአጼ ኃይለ ሥላሴ የመጀመርያ የአክስት ልጅ ነች፡፡ እናቷ እህተ ማርያም የራስ መኮንን እህት
ነበረች፡፡ እናታቸው ተናኜ ወርቅ የሸዋው ንጉስ የሣህለሥላሴ ልጅ ነበረች፡፡
8)አባቱ (የእምሩ አያት)ቀኛዝማች አባይነህ ከመንዝ ተጉለት የተገኙ የንጉስ ሚኒሊክ ታዋቂ ጭፍራ
ናቸው፡፡ኃይለሥላሴ ተወዳጁ ልጃቸውም ፈጣን አእምሮ የነበራቸው ጠንካራ ነበሩ፡፡
10)ራስ መኮንን በኋላ የጣይቱን ወንድም ሴት ልጅ የሆነችውን ምንትዋብ ወሌን በጣይቱ ምክር
አገቡ፡፡“ምክንያቱም የመኮንንን ዝምድና ስለሚፈልጉ” ምንትዋብ በጣም ወጣት ነበረች ምንአልባት
13 ወይም 14 አመት መኮንንም ከመጋባታቸው በፊት ጥቂት መጠበቅ ፈለጉ፡፡ ይሄ ጣይቱን
አስከፋቸው፡፡ እንዲፋቱም አስገደዱ፡፡ ምንአልባት ምንትዋብ ቅሬታዋን ነግራቸው ሊሆን ይችላል፡፡
(በኋላ ራስ ከበደ መንገሻን ያገባች ሲሆን ሳትወልድ በልጅነቷ ነው የሞተችው)
12)ሃረር ከባቡር መንገዷ ከተማ ድሬ ዳዋ አቅራቢያ የምትገኝሞቅ ያለች ከተማ ስትሆን ከአዲስ
አበባ የተሻለች ዘመናዊ ከተማ ነበረች፡፡ የካቶሊክ ሚስዮኖች ከአዲስ አበባ በ1979 ተባረው ሀረር
ላይ በ1980 ስራቸውን ሲጀምሩ መኮንን የትምህርታዊ እንቅስቃሴያቸው ደጋፊ ነበሩ፡፡ ተፈሪን
(ከመጀመርያ ጋብቻቸው የተገኘ ብቸኛ ልጃቸውንና)እምሩን እንዲማሩ ላኩ፡፡ እነዚህ ሁለቱ
በትምህርት ቆይታ ዘመናቸው እኩል ትምህርት ነው ያገኙት፡፡
13)በኋላ በሀሮማያ ሀይቅ ከተፈሪና ከሌሎች ሶስት ሰዎች ጋር የሚጓዝበት መርከብ ሲሰምጥ
የሞተ፡፡ በዚያ ጉዞ ላይ ተፈሪ ሚስታቸውን ይዘው በቅርብ የሞተ ዘመዳቸውን ለመቅበር ወደ
197
ጥቋቁር አናብስት
አለማያ እያመሩ ነበር፡፡ ተፈሪ ለጥቂት ከሞት የተረፉ ሲሆን ግሪካዊው ዶክተር ዜርቮስ ሙሉ
በሙሉ ተዳክመው የውሃው ዳርቻ ሲደርስ ነፍስ እንዲዘሩ አግዟቸዋል፡፡
14)ይልማ መኮንን በልማድ ጋብቻ ወይም በመሳሰሉት የሚወለዱ የተፈሪ በአባት በኩል የሚገናኙ
ወንድም ናቸው፡፡ በጥቅምት 12 1907 ከአባታቸው ሞት በኋላ የሃረር ገዢ በሆኑ (መስከረም
1906)ከአንድ አመት በኋላ ሞቱ፡፡
21)የእያሱ እህት ስህነና የአምባሰሉ ዣንጥራር አስፋው ልጅ ነች፡፡ በእድሜ በብዙ ከሚበልጥዋት
ራስ ልኡል ሰገድ ጋር ልታደርገው የነበረውን ጋብቻዋን እያሱ ከሰረዙባት በኋላ ነበር ለተፈሪ
የተሰጠችው
198
ጥቋቁር አናብስት
24)እያሱ ወደ ስልጣን ያደረጉት ጉዞ አልጋ በአልጋ አልነበረም፡፡ ንግስት ጣይቱም ከሃይል አሰላለፉ
ተወግደው በእንጦጦ ማርያም ቤተ ክርስትያን እስከተቀመጡበት ጊዜ ድረስ ስልጣኑን ለማግኘት
ይፈልጉ ነበር፡፡ ወደ እንጦጦ የሄዱበት መንገድ ሰላማዊና ምንም ደም ያላፋሰሰ ነበር፡፡
25)በተጉለት ገዢ የነበረና የታዋቂው የምኒሊክ ጄኔራልና የሸዋና የኦሮሞ ህብረት መሀንዲስ የራስ
ጎበና ልጅ ነበር፡፡
199
ጥቋቁር አናብስት
29)በወቅቱ በልጅ በኋላ ራስ ደስታ ትግራይ ውስጥ ነበር የተያዙት፡፡ በራስ ካሳ አማካኝነትም ፍቼ
ላይ እ.ኤ.አ በ1921 ታሰሩ፡፡ አምልጠው ጎጃም ውስጥ በ1932 ተያዙ፡፡ ቀሪውን የእድሜ
ዘመናቸውን በእስር አሳልፈው በ1936 ምናልባትም በግድያ በኢጣልያ ወረራ ዋዜማ ሞቱ፡፡
ምንአልባትም ብዙዎች እንደሚገምቱት ጋራ ሙለታ ሳይሆን አዲስ አበባ ውስጥ ነው የተገደሉት፡፡
31)መጀመርያ ለ ንጉስ ዮሃንስ ልጅ ለራስ አርአያ የተዳረች ሲሆን ነገር ግን እሳቸው እ.ኤ.አ
በ1888 ሞቱ፡፡ (ያልተወለደው ልጃቸው አንዳንዶች የጨነገፈ ልጅ ወልዳለች ቢሉም እንደዚያ
ከሆነ ብቸኛው የዘውዲቱ እርግዝና ይሆናል)የምንሊክን አልጋ ሊወርስ የታሰበ ነበር ማለት ነወ፡፡
በርካታ ባሎች የነበሯት ቢሆንም ግን ንግስት ስለሆነች ግን አሁን አልቻለችም፡፡ ስለዚህም ለዙፋኑ
አልጋ ወራሽ ወይንም እንደራሴ ተመደበላት፡፡
32)ተፈሪ ሀረርን እንዲለቁ በእያሱ ተነግሯቸው ነበር፡፡ ቆይቶም አዲስ አበባንም እንዲሁ ለቀው
ወደ ከፋ በፍጥነት እንዲሄዱ ተነገራቸው፡፡ መነን ግን በእምሩ አማላጅነት ቆይታ ልጇን
እንድትገላገልና እንድታስጠምቅ ተፈቀደላት፡፡ እያሱ ሃረርን በቀጥታ ተቆጣጠሩ፡፡ ይህም
አካባቢውን በማእከላዊ መንግስት ስር በቀጥተኛ ቁጥጥር ስር የዋለ “መአድ ቤት ”አደረገው፡፡
ሃይሎች ጋር አንድነት ሲገቡ እያሱ በታጠቁ ሶማሌ የሀረሪና የኦሮሞ ሃይሎች መከላከያ ሀይላቸውን
ገንብተው ነበር፡፡ ነገር ግን በጦርነት ምንም የድል ተስፋ እንደሌለ ገብቷቸው ነበር፡፡ ስለዚህ
ለማምለጥ ሞከሩ፡፡ ይሄ ሁሉ ሲሆን ግን እምሩ በእጀ ሙቅ ተቀፍድደው ነበር፡፡
35በባህሉ መሰረት በእጀ ሙቅ የተቆራኙት ከአንድ ታማኝ ተከታያቸው ጋር ነበር፡፡ አበበ ወልዴ
ይባላል፡፡
36)እያሱ ተፈሪን የከፋ ገዢ አድርገው ሾመዋቸው ነበር፡፡ ተፈሪ ደግሞ በጊዜው አዲስ አበባ
ውስጥ ሆነው ወደ ከፋ ለመሄድ በመዘጋጀት ላይ ነበሩ፡፡ ነገር ግን የሴራው ዋና ጠንሳሽና የጦር
ሚንስትሩ ሃብተግዮርጊስ አዘገዩዋቸው
40)ከዚህ በኋላ ጦራቸው ወዳለበት ጨርጨር ሲመለሱ ባልቻ በእያሱ ደስተኛ አልነበሩም
201
ጥቋቁር አናብስት
41)አባተ የብዙ ችሎታዎች ባለቤት ነበር። ሀገር ወዳድና አርበኛ ከመሆናቸውም በተጨማሪ
ለምኒሊክ እንደ መሃንዲስም ነበሩ፡፡ እራሳቸውን በራሳቸው ያስተማሩ ተወዳጅ ሰው ነበሩ፡፡
42)አባተ በእያሱ የመውደቂያ ጊዜ ተለቀቁ፡፡ ለአጭር ወቅት በ1917 እስከ ሚሞቱም ድረስ
የወሎ ገዢ ሆኑ፡፡ ደብረ ሊባኖስም ተቀበሩ
43)ቤተክርስቲያኑ በራስ ጎበና የተሰራ ሲሆን ንግስት ዘውዲቱ ከንግስናዋ በኋላ አሳድሳዋለች
46)በእርግጥ እምሩ ነበሩ ለአባታቸው ይሄንን ነገር ያዘጋጁት፡፡ እምሩ ደጃዝማችነትን ሲሾሙ ገና
ወጣት ነበሩ፡፡ በመጀመርያ ከሳቸው በእድሜ የሚበልጡ ስላሉ ላለመሾምም አመነቱ፡፡ እምሩ «የኔ
ታላቅ የሆኑ ይህ ስልጣን የሚገባቸው ብዙ ሰዎች አሉ»ሲሉ ተናገሩ፡፡ ለተፈሪ ጠባቂ የነበሩትና
የተፈሪ ታላቅ ወንድም ይልማ በሃረር ገዢነት ሲላኩ እንደ አማካሪያቸው የነበሩትቀኛዝማች ቆለጭ
አንዱ ነበሩ፡፡ እምሩ በተጨማሪም ከአባታቸው የሚበልጥ ክብርን ላለማግኘትም ፈልገው ነበር፡፡
ይህ ችግር ሁለቱንም አባቱንና ቆለጭን ወደ ደጃዝማችነት በማሳደግ ሊፈታ ችሏል፡፡
51)የራስ ሃይሉ በለው ታላቅ ወንድም ሲሆኑ የጎጃሙ ንጉስ ተክለሃይማኖት የልጅ ልጆች ነበሩ
52)ራስ ሃይሉ ተክለሃይማኖት (ቀደም ብለው ስዩም በሚለው መጠርያ ይታወቁ የነበሩ ሲሆን
በምልኪ ምክንያት ስማቸውን ቀይረዋል)የጎጃሙ ንጉስ ተክለሃይማኖት ልጅ ሲሆኑ እ.ኤ.አ
በግንቦት 27 1932 ተይዘው ታስረዋል፡፡ እያሱ እንዲያመልጡ ረድተዋቸዋል ተብለው ተከሰሱ፡፡
ወደ ሃረርጌም በእስረኝነት ተላኩ፡፡ ነገር ግን እሳቸውና እያሱ በአንድ ቦታ አልታሰሩም ነበር፡፡
የሃይሉ ልጅ ሰብለ ወንጌል ከእያሱሚስቶች መሃልና የአለም ጸሃይ እናት ነበሩ፡፡አለም ጸሃይን
በ1988 ጉለሌ ያለው ቤቷ አግኝቻት ነበር
53)የእምሩ ቀጣይ ሁለት ልጆች አዲስ አበባ ውስጥየተወለዱ ሲሆን የመጨረሻው እምሩ ጦር
ግንባር ላይ እያሉ በጦርነቱ ወቅት አምቦ ነው የተወለደው፡፡
54) እንደ ንጉስነታቸው ሙሉ ኢትዮጵያ የሳቸው ግዛት ነች፡፡ የበፊት ነገስታት ማንኛውም ሰው
እንደሚኖረው አይነት የግል መሬት አልነበራቸውም፡፡
55)ከዚያ ቀደም ብሎ በ1926 ተፈሪ ከበደ መንገሻ አቲከምን ከተመሳሳይ ገዚነት ስልጣን ላይ
አንስተዋቸው ነበር
58)ሌሎች ከየጁ የመጡ ሰራዊቶች ደግሞ በአበበ ዳምጠው ይታዘዛሉ(የፊት አውራሪ ዳምጠው
ልጅና በሩስያ ቅዱስ ፒተርስበርግ የሚኒሊክ ወኪል የራስ ደስታ ዳምጠው ታላቅ ወንድምና የኃይለ
ሥላሴ ታላቅ ልጅ ተናኜ ወርቅ ባል)አበበ በኋላ በነሲቡ ስር ሆነው ጣልያኖቹን በሃረርጌ ወግተው
በኋላ ወደ ስደት ሄዱ ፡፡ ወደ ወረራው ማብቂያ ላይ ካርቱም ያሉትን የጌድዮን ሃይሎችን ተቀላቀሉ
203
ጥቋቁር አናብስት
60)ከዚያ በፊት ወደ ውጭ ሃገር ወጣ ብለው የነበር ሲሆን እሳቸው ተፈሪና ሌሎች ሆነው እያሱ
ጅቡቲን ሊጎበኙ በ1915 በሄዱበት ወቅት አጅበዋቸው ሄደው ነበር
61)ከዚያ ቀደም የአዲስ አበባ ከንቲባ የነበሩ ሲሆን ቆይተው ደጃዝማች ሆኑ፡፡ ደብረታቦር
ተወልደው በ1947 አ.ም ጎንደር ሞቱ
65)የእምሩ አብዛኛው መሬት እሳቸው ባላስተዳደሩበት አሩሲ ይገኛል፡፡ ሃረርጌ ውስጥም የከተማና
የገጠር ቦታ አላቸው፡፡ ድሬ ዳዋም እንዲሁ ቤቶችና መሬት አላቸው፡፡ ጉደር አምቦ አቅራቢያ ለድሃ
ጭሰኞችና ገበሬዎች የሰጡት ቦታ ከራስ መኮንን የወረሱት ነበር፡፡ የተወሰነውን ክፍል ለእርሻ
ትምህርት ቤት ሲሰጡገሚሱን የወይን መሬት ለሴት ልጆቻቸው ሰጥተዋል
71)በኢትዮጵያ ያሉ የውጪ ሃገር ዜጎች ካዩት የቆየ ቢሆንም ግኮቹና ፈረንሳዮቹ የሃረርጌ ገዢ ሳሉ
ሸልመዋቸዋል፡፡
73)ኋለኛው የተለመደ ድርጊት ሲሆን ገዢው የለቀቀበት ክፍለ ሃገር ውዥንብር ውስጥ የሚገባበት
ልምድ አለ
76)ደጃዝማች ሃይሉ ከበደ የዋግ ሹም ከበደ ልጅ ሲሆኑሌላው ቢትወደድ መኮንን ደምሰው በዚህ
ጦርነት መልካምጀብድ ፈጽመዋል
205
ጥቋቁር አናብስት
82)ደብረ ማርቆስ እያሉ አድርገውት ሊሆን ይችላል ወይንም እምሩን ለማግኘት መጥተው ከተማ
ከመግባታቸው በፊት ሊሆንም ይችላል
83)በራሳቸው ፍቃድ ከሾሟቸው ሹመቶች አንዱ ይሄ ሊሆን ይችላል፡፡ ነጋሽ በዛብህ ብዙውን ጊዜ
የንጉስ ተክለሃይማኖት ልጅ በመባል ይታወቃል ፡፡ እውነቱ ግን የበዛብህ ሴት ልጅ ልጅና
የፊትአውራሪ ወልደ ማርያም ልጅ መሆኑ ነው፡፡ ለማንኛውም ግን ያደገው በበዛብህ በራስ ሃይሉ
ታላቅ ወንድም በአያቱ ቤት ውስጥ ሲሆን ስሙንም ያገኘው ከዚያ ነው፡፡ ነጋሽ በነሃሴ 1964
አ.ምአርፏል
84)ትሰሜ ዳርጌን ማለትም የሚኒሊክ የአጎት ልጅን የገባ ሲሆን የራስ ካሳ ሃይሉ የእንጀራ አባት
ነበር
87)የነጋድራስ በሃብቴ ልጅና የታምራት ይገዙ የልጅ ልጅ ሲሆን ከእምሩ ልጆች መሃል አንዷን
ሊያገባ የታጨ ነበር
88)በጋምቤላ በኩል ያለው መንገድ እስከ እ.ኤ.አ ታህሳስ 1936 ድረስ ክፍት ነበር
89)ከእነሱ መሃል ሻለቃ በኋላ ቀኛዝማች በልሁ የነበረበት ሲሆን በኃላ በየካቲት 12ቱ ጭፍጨፋ
ሞቷል፡፡
90)ፍቃደስላሴ ህሩይ ከጥቁር አናብስት ተዋጊዎች መሃል የነበረ ሲሆን፡፡ ደራሲዋ ስንዱ ገብሩ
ደግሞ ከጥቁር አንበሳ ተዋጊዎች ነርሶች መሃል ነበሩ
91)ከጦርነቱ በፊት በኃይለ ሥላሴ ታስሮ የነበር ሲሆን በኋላ በጣልያኖቹ ነጻ ወጥቷል፡፡
206
ጥቋቁር አናብስት
93)ወደ እምሩ ማረፍያ አካባቢ ለመድረስ በርካታ ጥረቶችን በረግረጉ በኩል ቢያደርጉም
በመትረየስ ተኩስ ተመልሰዋል
94)ከጅማ የመጡትን ሃይሎች የመራው ጄኔራል ፐሪንስቫሊን ባናደደ መልኩ ጄኔራል የተደረገው
የእምሩን የእጅ መስጠት ስላደራደረ ነው፡፡
95)የእዚያ እለት ያየሁት ፎቶላይ ታህሳስ201936 የተነሳ ሲሆን ፎቶው ከጀርባው ቀን አለው
98)መጻፍን ያስተማሩት የሃረሩ አባ ሳሙኤል ወልደ ካህን ናቸው፡፡ የዚህ መጽሃፍ ዋናው ቅጂ
በልጁ እጅ ይገኛል
207
ጥቋቁር አናብስት
105በዚህ ከራስ ሃይሉ በጣም ይለዩ ነበር ራስ ሃይሉ ለምሳሌ ያህል የብር ማርያ ቴሬዛ ማየቱ ብቻ
ያረካቸው ነበር፡፤
107)በዚያ ዓመት ፋሲካ ላይ ልጃቸው ሚካኤል ከእምሩና ከራስ አበበ አረጋይ ጋር በመሆን ወደ
እየሩሳሌም ለስድስት አመታት የቆዩበትን ቦታ ለማሳየት ሄዶ ነበር፡፡ ወድያውኑ እንደተመለሱ
የእምሩ ሹመት ተነገረ
109)ግርማሜ ከታላቅ የሸዋ ቤተሰብ ነበር የመጣው፡፡ አያቱ (የእሳቸውም ስም ግርማሜ ነዋይ
ነው)የሚንሊክ ታማኝ ተከታይ ሲሆኑ የሸዌ ያልሆኑ መኳንንት ከስልጣኑ ተነስተው ራቅ ወዳለ
ገጠራማ አካባቢ የመላኩንና የሸዌ መኳንንት ወደ ስልጣን ከፍ ከፍ የማስደረግእቅድ ተካፋይና
አስፈጻሚ ናቸው፡፡ ይህ ሁኔታ እስከ ኃይለ ሥላሴጊዜ መጨረሻ ድረስ ቆይቷል፡፡
110)ምን ያህሉ የእምሩ ምን ያህሉ ደግሞ የልጁ ምዘና እንደሆነ እርግጠኛ አይደለሁም፡፡
111)የምእራቡ ወይም የውጪው አለም ሪፖርቶች የተጋነኑና የተጣመሙ ናቸው፡፡ እንደ ሚካኤል
እምሩሃሳብ ያልታተሙ የኢትዮጵያ ምንጮች ያሉ ሲሆን ተአማኒም ናቸው፡፡ ለምሳሌ እንደዱብ
እዳ ያሉ በታዋቂው ጦማሪ ማህተመ ስላሴ ወልደ መስቀል ቅጂው ያለኝ ሲሆን፡፡ ለnortheast
African studies በማጠቃለልአቅርቤዋለሁ
208
ጥቋቁር አናብስት
209
ጥቋቁር አናብስት
አማረማሞ
ለሥነ ጽሑፍ የተሰጠ ሕይወት አማረ ማሞ በሲዳሞ ክፍለሀገር፣
በደራሳ አውራጃ (አሁን ጌዴኦ አውራጃ)፣ በዲላና ሀገረማርያም
መሀል በምትገኝ፣ ፍስሀገነት በምትባል ትንሽ ከተማ በህዳር 12ቀን
1931ዓም ተወለደ። አባቱ በአካባቢው ገዢዎች መሬት የተሰጣቸው
ከሌላ ቦታ የመጡ ሰፋሪ ነበሩ።የሞቱት አማረ ገና የሰባት ዓመት ልጅ
እያለ ነው።ስማቸው ጐዳና አሚሮ ሲባል በትውልዳቸው ሶዶ ጉራጌ
ናቸው።1አማረ እንደደንቡ በአባቱ ስም ከመጠራት ይልቅ
ከሚስታቸው ጋር ሆነው ባሳደጉት ልብስ ሰፊ የክርስትና አባቱ ማሞ
ደበላ ስም ተጠራ።አማረ ንፁህ የመንዝ አማራ በሆኑት በእናቱ ሰልፍየለሽ ወልደሚካኤል እጅ
አላደገም። አማረ ባደገበት የደራሳ አካባቢ የሚነገረው የጉጂ ኦሮምኛ ስለነበረ፣ምንም እንኳን ቤቱ
ውስጥ አማርኛ ይነገር የነበረ ቢሆንም፣ አማረ አፉን የፈታው በኦሮምኛ ነው። የክርስትና አባቱ
የሚኖሩት በዲላ እና ይርጋለም መሀል በምትገኘው አለታ ወንዶ(ወንዶ ብቻ ተብሎም
ይጠራል)ሲሆን ከይርጋለም በስተደቡብ 30 ኪሜ ላይ ትገኛለች።አማረ ወደ አለታ ወንዶ ከመጣ
በኋላ ሲዳምኛ ቋንቋንም ለመደ፤አሁን ድረስ ከአማርኛ ቋንቋ ቀጥሎ አቀላጥፎ የሚናገረው ቋንቋ
ነው።
አማረ በሰባት ዓመቱ ወደ አለታ ወንዶ እንደመጣ ወዲያውኑ የቄስ ትምህርት ቤት ገብቶ ለሶስት
ዓመት ያህል ማንበብና ዳዊት መድገም ተማረ።ከዚያ በኋላ ወደ የመንግሥት ትምህርት ቤት ገብቶ
የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በጊዜው እንደነበረው ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እስከ ስምንተኛ ክፍል
ድረስ አጠናቀቀ።አሁን የአስራ ስምንት ዓመት ጎረምሳ ሆኗል። ጥሩ ውጤት ቢያመጣም ትምህርት
ግንአይወድም ነበር።
210
ጥቋቁር አናብስት
ይርጋለም እያለ ካነበባቸው ታሪኮች በተጨማሪ የአንደኛ ደረጃ ተማሪ እያለ ያነበው የአማርኛ ሥነ
ጽሑፍ ተጽዕኖ አሳድሮበታል።በተለይ ሁለት ርእሶችን ያስታውሳል።የመጀመሪያው “የእንስሳት
አገልግሎት ለህፃናት በረከት” ነው።ደራሲው ያሬድ ገብረሚካኤል2 ሲሆን በግጥም መልክ የቀረበ
የእንስሳት ታሪክ ነው።አማረ አሁን ደረስ ለልጆች ከተፃፉ ታሪኮች ሁሉ የሚበልጥ ምርጥ ነው
ይላል።ታሪኮቹ የደራሲው ፈጠራ ናቸው፣ አንዳንዶቹ ተረት የሚመስል ገጽታ ቢኖራቸውም
መጽሐፉ ወጥ የፈጠራ ስራ ነው።አማረ ከአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ጋር ሲተዋወቅ ይህ የመጀመሪያው
ነው።ሌላኛው የጠቀሰው ተከታታይ መጽሐፍ የከበደ ሚካኤል "ታሪክ እና ምሳሌ" ነው፤ይህ
መጽሐፍ በከፊል በከበደ ሚካኤል የተፃፉ ታሪኮችንና ግጥሞችን ይዟል። በተጨማሪ ሌላኛው
የከበደ ሚካኤል መጽሐፍ፣"የእውቀት ብልጭታ"አስደንቆታል።የተክለፃዲቅ መኩሪያ የታሪክ
መጽሐፍትንም ወዷቸው ነበር።
***
ከዚህ በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚኖሩ የውጪ ሀገር ሰዎች ጋር ከነበረው ጉድኝት ውጭ፣ ወደ
ኖርዌይ ያደረገው ጉዞ ከውጪው አለም ጋር የፈጠረው የመጀመሪያው ትልቁ ግንኙነት ነው።
በኖርዌይ ቆይታው ለሥነ ጽሑፍ ያለው ፍላጎት ይበልጥ ጠነከረ፤የኖርዌጂያን ቋንቋ እውቀቱም
በኋላ ወደ አማርኝ ቋንቋ ለሚተረጉማቸው መጽሐፍት ጠቃሚ ሆኖ አግኝቶታል።ኖርዌጂያኖቹ
የሚወደዱ ሰዎች ሆነው አግኝቷቸዋል።"ደግ እና ቅን ሰዎች"ናቸው ይላል፤እነሱም በሚገባ
ተንከባክበውታል።በአጠቃላይ በኖርዌይ ጥሩ ቆይታ ነበረው።
ሌላው በኖርዌይ ቆይታው ያጋጠመው ያልተጠበቀ ነገር፣ በሕይወቱ ለመጀመሪያ በሀገሩ ኢትዮጵያ
ጉዳይ ላይ ከፍተኛ ፍላጎት ማሳደሩ ነው።ሀገሩን ከመልቀቁ በፊት ስለ ኢትዮጵያ ብዙ አላነበበም
ነበር።ኖርዌጂያኖች ስለ ኢትዮጵያ ለሚጠይቁት ጥያቄዎች ለመመለስ ሲሞክርና ኖርዌጂያኖች ስለ
212
ጥቋቁር አናብስት
በ1960 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰና በኢትዮጵያ ወንጌላዊት አብያተ ክርስቲያን መካነ እየሱስ
የብዙሃን መገናኛ ማእከል ውስጥ መስራት ጀመረ።ማእከሉ“የምስራች ድምጽ” በመባል
ይታወቃል። ለአምስት ዓመት በዚያ ስራ ቆይቷል። በዚህ መሀል፣ በ1963 የየምስራች ድምጽ የሥነ
ጽሑፍ ዝግጅት ዋና አዘጋጅነትን ደርቦበ1965 ወደ ዛምቢያ እስከሚሄድበት ጊዜ ድረስ ሰርቷል።
ሲመለስ የየምስራች ድምጽ የሥነ ጽሑፍ ክፍል ዋና ዳይሬክተር ሆኖ ተሾመ። በ1970 ዓ.ም ወደ
ሰሜን አሜሪካ እስኪሄድ ድረስም በዚሁ ስራ ቆየ። ስራውን በጣም አስደሳች ሆኖ አገኘው።
ከሀይማኖታዊ እና አስተማሪ ጽሑፎች ባሻገር የኢትዮጵያ ፕሮቴስታንት አብያተ ክሪስቲያናት፣
መሀይምነትን ለማጥፋት ከሚያደርጉት ዘመቻ ጋር በቅንጅት መሰረታዊ የትምህርት መርጃ
መሳሪያዎችን ያዘጋጁ ነበር።በቤተክርስቲያን ፖለቲካ ውስጥም እጁን አስገባ።
***
በ1970 ከሉተራን የአለም ፌዴሬሽን የአራት ዓመት ነፃ የትምህርት እድል አግኝቶ ሎስ አንጀለስ
በሚገኘው የካሊፎርኒያ ሉተራን ኮሌጅ ሥነ ጽሑፍ ለመማር ወደ ሰሜን አሜሪካ ሄደ። ከሁለት
ዓመት በኋላ የመጀመሪያ ዲግሪውን በማእረግ ተቀበለ። የነፃ የትምህርት እድሉን ቀሪ ሁለት
ዓመታት ሁለተኛ ዲግሪውን በመስራት መጠቀም ፈለገ ፤ እንደውም በካሊፎርኒያ የሎስ አንጀለስ
ዩኒቨርሲቲ(UCLA) የአፍሪካንሥነ ጽሑፍ ለመማር ቦታ አግኝቶ ነበር። ነገር ግን ኢትዮጵያ ውስጥ
የሚሰራበት ቤተክርስቲያን ጥሪ ስላደረገችለት በ1972 ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰ። በድሮው ስራ
ላይም እስከ 1978 ድረስ ቆየ።
አማረ ኖርዌይ እያለ ሚስቱ ቦታ ተከራይታ ከኖርዌጂያን ሉተራን ሚስዮን ያገኘችው እርዳታ
ተጨምሮበት ካዛንቺስ ላይ እስከ 1967ዓም የኖሩበትን ቤት ሰርታ ነበር።ይኼኔ ኃይለሥላሴን
በመስከረም 1966 ከዙፋናቸው አሰውግዶ በምትኩ የሶሻሊስት ስርአት ያሰፈነው አብዮት አንድ
ዓመት ሞልቶታል።አማረ ደግሞ ወደ ሰሜን አሜሪካ ከመሄዱ በፊት ቦሌ መንገድ ላይ በገዛው ቦታ
በ1967 ዓም ቤት ሰርቷል። በ1967 አጋማሽ ቤቱ አልቆ ዝግጁ ሆኗል። ነገር ግን ቤቱን ለመስራት
ሲል ከመካነ እየሱስ ቤተክርስቲያን የወሰደውን ብድር ለመመለስ ቤቱን አከራየው። በሐምሌ
1967ትርፍ ቤቶችንና መሬትን የመንግስት ንብረት የሚያደርገው አዋጅ ወጣ። ይህ ማለት አማረ
ተከራዮችን ማስወጣት አይችልም ማለት ነው። በነሐሴ1967 ዓም ላይ ቤተክርስቲያኗ የአማረን
ደሞዝ በ300ብር ቀነሰች። የቤት ኪራዩን ገንዘብ ደግሞ መንግስት ይወስደዋል። ስለዚህ በጠባቧ
የካዛንቺስ ቤቱ ውስጥ ተጨናንቆ መኖር ግድ ሆነበት። የቤቱ ተከራዮች ከ16 ወራት በኋላ ሲለቁ
አማረ ገባበት። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ በ1969 መጨረሻ ላይ የነበረበትን የመካነእየሱስ
ቤተክርስቲያን7 እዳ ለመክፈል ሲል ሸጠው። ከዚያ አብዮት አደባባይ(መስቀል አደባባይ)ጀርባ
ወዳለ የቀበሌ ቤት ገብቶ እኔ ኢትዮጵያን እስከ ለቀቅኩበት እስከ 1981 ድረስ በዚያው ይኖር
ነበር።
እነኚህ የግል ጉዳዮች እዚህ የሰፈሩት በሕይወቱ ውስጥ ፈታኝ የነበሩትን ወቅቶች ለመግለጽ ነው ፤
እንጂከገንዘብ ጋር በተያያዘ የገጠመውን ችግር ብቻ ለመዘገብ አይደለም። አማረም የደረሰበትን
መከራ የገለፀው እንዲህ ነው።
214
ጥቋቁር አናብስት
በዚህ ወቅት ብዙዎች ከቤተክርስቲያኗ እየተለዩ ነበር፤ምክንያቱም ነገሮች ፖለቲካዊ እና ጎሰኛ ቅርጽ
እየያዙ መጥተው ተመሳሳይ ወገንተኝነት እና ጎሳ (አብዛኛው በኋላ ደግሞ ሁሉም መሪዎች
ኦሮሞዎች ነበሩ)―የሌላቸውን ሁሉ ማስወገድተፈለገ።አማረ እንዳስቀመጠው፣ማስወገድ
የፈለጓቸውን ሰዎች ደሞዝ መቁረጣቸው ይህንኑ ሁኔታ ያስረዳል።የደሞዛቸው መቆረጥ ህገወጥ
ድርጊት ነበር። አማረ የምስራች ድምጽየመገናኛ ብዙኃን ማዕከል ቦርድን ደሞዙን በመቁረጣቸው
ፍርድ ቤት ከሰሳቸውናረታቸው። ነገር ግን “በዚህ ሂደት የሰው ልጅ ክፋት―በመካነ እየሱስ
ቤተክርስቲያን እንዲሁም በከፊል በሌሎች ሚስዮኖች ውስጥ―የት ድረስ እንደሆነ
ተመለከትኩበት”8 ይላል አማረ። መጀመሪያ ላይ የምስራች ድምጽ መገናኛ ብዙኃን ማዕከል ቦርድ
ጉዳዩን ጠምዝዞ በቤተክርስቲያኗ ላይ የተፈጸመ ጥቃት አስመሰለው።
አማረበፍርድ ቤት ከረታቸው በኋላ ከስራው ተባሮ በዚያውም ለሀያ ዓመት ያህል የሰራበትን
የጡረታ መብት አጣ። በመጀመሪያ ግን ውሳኔው ላይ ይግባኝ ብለው፣ ከረጅም ክርክር በኋላ አማረ
ዳግመኛ አሸነፈ። እንደገናም ይግባኝ ብለው፣አሁንም ለአማረ ተፈረደ። በአጠቃላይ የፍርድ ቤት
ክርክሩ ሁለት ዓመት ተኩል ሲወስድ፣ቤተክርስቲያኗ ለጠበቃ በየወሩ 750 ትከፍል ነበር ፤ በአማረ
በኩል ግን እንደነገረኝ ከሆነ ጉዳዩን የተከታተለው ራሱ ነው። ምንም እንኳን ቤተክርስቲያኗ ራሷ
የተከሰሰች ይመስል ጉዳዩን ስትከታተል ብትቆይም (አማረበፍፁም ቤተክርስቲያኗን አልከሰሰም) ፣
የአማረን የሁለት ዓመት ተኩል ደሞዝ ከነወለዱ መክፈል ያለበት የምስራች ድምጽ ነው አለች፤ ነገር
ግን ክሱ በሂደት ላይ እያለ የምስራች ድምጽ በመንግስት ተወርሶ ነበር። ቤተክርስቲያኗ አማረ
ገንዘቡን አሁን የመንግስት ንብረት ከሆነው የየምስራች ድምጽ እንዲቀበል ላኩት! ይሁን እንጂ
አማረ በየምስራች ድምጽ ስም በባንክ የተቀመጠ ገንዘብ እንዳለ በማወቁ፣ ፍርድ ቤቱ ገንዘቡን
እንዲከፍለው ባንኩን አዘዘው፤ነገር ግን የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ የያዘው ደብዳቤ ባንክ ከመድረሱ
በፊት ገንዘቡ ወጥቷል።“እንደ አጋጣሚ የባንኩ ስራ አስኪያጅ፣ የመካነእየሱስ ዋና ጸሐፊ የሆነው
የጉዲና ቱምሳ ዘመድ ነበር” ይላል አማረ።ከዚህ በኋላ አማረ ወደ መገናኛ ሚኒስቴር ሄዶ
በየምስራች ድምጽስም የተመዘገበ ተሽከርካሪ እንዳለ ሲያጣራ፣ ሁለት መኪኖችን አገኘ። ይሄ
ለፍርድቤቱ እንደተነገረ፤ወዲያውኑ እርምጃ ተወሰደ። አንደኛው ለፍርድቤቱ ገቢ ተደረገና አማረ
በመጨረሻ ገንዘቡን አገኘ።
ከዚያ በመላው ሀገሪቱ ያሉ የመካነ እየሱስ ቤተክርስቲያን አባላት ለስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አስቸኳይ
ስብሰባ ተጠሩ። አማረ ቤተክርስቲያኗን (አሁን ደግሞ የተከሰሰችው ቤተክርስቲያኗእንጂ የምስራች
ድምጽ አይደለም እየተባለ ነው!) በመክሰሱ፣ ስራውን ለመልቀቅ 24 ሰአት ተሰጠው (ቀደም ብሎ
ከዚህ ስራ ተባሮ ነበር―ፍርድቤቱ ደግሞ መባረሩን ህገወጥ ነው ብሎታል)።አማረእንደሚለው፣
215
ጥቋቁር አናብስት
***
አማረ የራሱን የሥነ ጽሑፍ ስራ የጀመረው ገና በዲላ የመጽሀፍ ቅዱስ ጥናት ትምህርት ቤት ውስጥ
እያለ ነበር። የመጀመሪያ መጽሐፉ "ማርቲን ሉተር"55 ገጽ ብቻ ነበረው።ሁለተኛ መጽሀፉ "የስጋ
አርነት"ም የተፃፈው ዲላ እያለ ነበር።ቃለመጠይቃችን እስከተካሄደበት ድረስ በነበረው ጊዜ፣ 25
ያህል መጽሐፍትን በመፃፍ፣ በማዛመድ ወይም በመተርጎም አሳትሟል።ሕይወቱን በሙሉ የራሱን
መጽሐፍት በመፃፍ ብቻ ሳይሆን፣ የሌሎችን መጽሐፍት አርትኦት በመስራትና በማሳተም ሕይወቱን
216
ጥቋቁር አናብስት
ለሥነ ጽሑፍ ስራ በመስጠቱ አማረ የተለየ ነው። ከየምስራች ድምጽ መገናኛ ብዙኃን መእከል ጋር
በሚሰራበት ወቅት 150 የሚሆኑ የልብወለድ፣የባህል፣የሐይማኖትና የትምህርት ህትመቶች ውስጥ
ተሳትፎ ነበረው። አማረ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ የአርትኦት እና የእርማት ስራ ከሚሰሩ ሰዎች ሁሉ
በጣም ጠንቃቃውና የካበተ ልምድ ያለው ሆነ።ብዙ መጽሐፍት በእጁ የሚያልፉት ደራሲዎች
መጽሐፍቶቻቸው በብዙ ጥንቃቄ እና ያለ ብዙ እንከንእንደሚታተሙ ስለሚያምኑ ነው።ብዙ
ደራሲዎች አማረ ማሞ የመጽሐፍቶቻቸውን የህትመት ሂደት እንዲከታተል የሚፈልጉት ውጤቱ
ያማረ እንደሆነ ስለሚያውቁ ነው። ከዚህም በላይ ወጣት ጸሐፍትን ማማከርና መርዳት ችሏል፤
ይህም እርካታ ፈጥሮለታል። ብዙ ደራሲዎችም ደራሲ ያደረጋቸው አማረ እንደሆነ በመግለጽ
ያመሰግኑታል፤ ለእኔም ይህንኑ ነግረውኛል።
አማረ ከራሱ ፈጠራዎች ውስጥ "የልብወለድ ድርሰት አፃፃፍ"ን ይጠቅሳል። የታተመው በ1968
ሲሆን በደንብ ተሽጧል።በሁለት የመምህራን ማሰልጠኛ ተቋሟት የመማሪያ መጽሀፍ ሆኖ
ሲያገለግል በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ደግሞ የፈጠራ ጽሑፍን ለማስተማሪያ ይጠቀሙበታል።
እነኚሁ ተቋማት "የቀለም ጠብታ" የተሰኘ መጽሐፉን ኢልብወለድ አፃፃፍን ለማስተማር
ይጠቀሙበታል።በጊዜው በዘመናዊ የኢትዮጵያ ደራሲዎች ዘንድ የአጻጻፍ ስርአት መልክ የያዘ
ስላልነበረ እና በዘርፉ ከፍተኛ ፍላጎት ያሟላሉ ብሎ ስለታሰበ ሁለቱን መጽሐፍት ሲያዘጋጅ
በከፍተኛ ጥንቃቄ እና በትጋት ነበር።
የአማረ ማሞ የአጭር ታሪኮች ስብስብ ውስጥ የተካተቱ አንዳንድ አጫጭር ልቦለዶች፣ በአዲስ
አበባ ዩኒቨርስቲ የፈጠራ ጽሑፍ ትምህርቶች ውስጥ እንደ ጥሩ ምሳሌዎች ተጠቅሰው ጥቅም ላይ
ይውላሉ።
ከመጽሐፍቶቹ ውስጥ በአለን ፓተንን Cry the Beloved Country ወይም "እሪ በይ አገሬ"ን
እና Martyrs of the Catacombs ወይም "የካታኮምብ ሰማእታት"የተሰኙትን የትርጉም
ስራዎች፣ታላቅ ስራዎቹ እንደሆኑ ይገልፃል።ሁለቱም መጽሐፎቹ በሰፊው ከመነበባቸውም ባሻገር፣
በሬዲዮ በተከታታይ ተተርከዋል።
217
ጥቋቁር አናብስት
Cry the Beloved Countryን ለማንበብ እና ለመተርጎም የተነሳሳው ኖርዌይ እያለ ነበር፤
በጊዜው የደቡብ አፍሪካ ጉዳይ ሞቅ ያለ የመዋያያ ጉዳይ ከመሆኑም በላይ አማረ፣ ከደቡብ አፍሪካ
ከመጣ አንድ ስደተኛ ጋር ስለ ሀገሩ ሲወያዩ እጅግ ተደንቆ ነበር (ከዚህ ሰው ጋር በኋላ ላይ
ኢትዮጵያም ውስጥ ተገናኝተዋል)።በጊዜው ኢትዮጵያውያን ስለ ተቀረው አፍሪካ ብዙም
አያውቁም፤ስለዚህ የደቡብ አፍሪካንም ሁኔታ በደንብ አይገነዘቡም ነበር።አሁን ግን ይህ ሁኔታ
ተለውጧል፤ አማረየለውጡ ከፊል ምክንያትየተረጎመው መጽሐፍ ተጽእኖ መሆኑን ያምናል።
10
ምንም እንኳን የትርጉም ስራ ቢሆንም፣አንድ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪ የመጀመሪያ
ዲግሪዋን የመመረቂያ ጽሑፍ "እሪ በይ ሐገሬ" ላይ ሰርታለች።ወደ ኢትዮጵያ ባህላዊ አውድ
ስለተዛመደከቃል በቃል ትርጉም በላይ ነው፤እንዲሁም የቋንቋ ውበት አለው በማለት
አድንቃዋለች።
የዋልተር ትሮቢሽን ሁለት መጽሀፍትም ተርጉሟል፤I Loved a Girl እናI loved a Young
Man። አላማው ለወጣቶች የወሲብ ጉዳይ ትምህርት ለመስጠት ነው።በኢትዮጵያ ይሄ
በትምህርት አይሰጥም።ብዙ ሰዎች ስለጉዳዩ ያላቸውን እውቀት የሚያገኙት ከመጠጥ ቤት ወሬ
ወይም በሙከራ ነው።በዚህም የተነሳ ያልተፈለገ እርግዝና እና በግብረ ስጋ ግንኙነት የሚተላለፉ
በሽታዎች ይከተላሉ።ብዙ ሠዎች ስለዚህ ጉዳይ በማንበባቸው ቢደነግጡም 11መጻሕፍቱ በሬዲዮ
መነበባቸው አልቀረም።
1)አቤ ጉበኛ
2)አማረ ማሞ
3) መኮንን እንዳልካቸው
4) ሀዲስ አለማየሁ
ከዚያ ወዲህ በእርግጥ ሁኔታዎች ተለዋውጠዋል። ቢሆንም እነዚህ ደራሲዎች አሁንም በደንብ
የሚታወቁና የሚነበቡ ናቸው።
አማረ ማሞ በጣም ተነባቢ ደራሲ ቢሆንም፣ኑሮ ለኢትዮጵያ ጸሐፍት ከባድ እንደሆነ ይናገራል።
ከመጽሀፎቻቸው የሚገኘው የመብት ክፍያ በጣም ትንሽ ስለሆነ ለአንድ ደራሲ፣በተለይ ቤተሰብ
ላለው በቂ አይደለም።ከመጽሐፉ በሚገኝ ገቢ ብቻ ለመኖር የሞከረው አቤ ጉበኛ እንኳን ሲሞት
የማተሚያ ቤቱ 100,000 ብር እዳ ነበረበት። አቤ በጊዜው ከማንኛውም የኢትዮጵያ ደራሲ በላይ
የፃፈ እና የሸጠ ነበር።ታዲያ ደራሲዎች በዚህ ዐይነት ሁኔታ ውስጥ መፃፋቸውን ለምን
ይቀጥላሉ?ኢትዮጵያዊ ደራሲዎች የሚጽፉት ስለ ኢትዮጵያ ሁኔታ የሚሉት ነገር ስላላቸው ነው።
አማረ የምጽፈው ማለት የምፈልገውን ለመግለጽ ነው ይላል። በመጽሐፉ አማካይነት ህዝቡ
ያላወቀውን በማሳወቅ ለመርዳት ከመፈለግ ነው።
በቅርቡ ከዶክተር እዝራ ገብረመድህን ጋር የአዲስ ኪዳንን ዘመናዊ እና የተሻሻለ ትርጉም "ህያው
ቃል" ን ሰርተዋል። ከመንግሥቱ ለማ ጋር ደግሞ ብሉይ ኪዳንን በከፊል ወደ አማርኝ መልሰዋል።
ማስታወሻዎች
220
ጥቋቁር አናብስት
10)ብርሀኑ ዘርይሁንስለ ደቡብ አፍሪካ የሻርፕቪል እልቂት የፃፈው መፅሀፍ "ድል ከሞት በኋላ"
በዚህ ረገድ ተፅእኖ ፈጣሪ ነበር።የብርሃኑ ዘርይሁንን የሕይወት ታሪክ እዚሁ መፅሀፍ ውስጥ
ታገኙታላችሁ።
11)አንድት ተያቢ የሴቶች ብልት በወሲባዊ እርካታ ወቅት እርጥብ ይሆናል የሚል ጽሑፍ
ስላጋጠማት ስራዋን
221
ጥቋቁር አናብስት
ወልደ ግዮርጊስ በቀድሞ አጠራር በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ምንጃር ወረዳ ጉብሌ ውስጥ በ1887 ዓ.ም
ተወለዱ፡፡ለአባታቸው ወልደ ዮሃንስ ደባልቄ እና ለእናታቸው ያድንቁሽ መኩርያ የበኩር ፍሬያቸው
ሲሆኑ ወላጆቻቸው ከመኳንንት ዘር የተገኙ ቢሆኑም ያልተማሩ አርሶ አደሮች ነበሩ፡፡
እንደማንኛውም የኢትዮጵያ የገጠር ልጅ በልጅነታቸው ከጥጃና ፍየሎች ጀምሮ ከብት አግደዋል፡፡
ለአባታቸውም ከእርሻ ቦታ ምሳ አድርሰዋል፡፡ለእናታቸውም የማገዶ እንጨት ለቅመዋል ውሃ
ቀድተዋል፡፡ብዙም ሳይቆይ አባታቸውን በእርሻ ማገዝ ጀመሩ፡፡
222
ጥቋቁር አናብስት
223
ጥቋቁር አናብስት
***
በ1913 ዓ.ም አለቃ ኅሩይ ወደ አዲስ አበባ በአልጋ ወራሽ ተፈሪ መኮንን ተጠሩ፡፡የተጠሩበት
ምክንያትም በግዕዝ የተጻፉ መፃህፍትን ወደ አማርኛ እንዲመልሱ ተፈልገው ነበር፡፡1አለቃ ኅሩይ
ወልደግዮርጊስን ጨምሮ ሌሎችንም ወደ አዲስ አበባ አስመጡ፡፡ወልደግዮርጊስ ከመጡም በኋላ
አለቃ ኅሩይ ወልደግዮርጊስን ይሄ ምርጡ ተማርዬ ነው ብለው ከታዋቂው ፖለቲከኛና ምሁር
ኅሩይ ወልደ ሥላሴ ጋር አስተዋወቋቸው፡፡ኅሩይ በተራቸው ደግሞ ወልደ ግዮርጊስን ከልኡል አልጋ
ወራሽ ጋር አስተዋወቋቸው፡፡የግእዝ ቅኔያቸውም ላቅ ያለ ሆኖ ስለተገኘ በተለያዩ
አብያተክርስትያናት ቅኔ እንዲቀኙ ሆኖ ገቢያቸውን ከእንጦጦ ቁስቋምና ቅዱስ ማርቆስ እና
ከሌሎች ቦታዎች እያገኙ ቆዩ፡፡ቀጥሎ ማስተማር ጀመሩ፡፡ደሞዛቸውም በቀን አንድ እንጀራና አንድ
ብርጭቆ ጠላ ተቆረጠላቸው፡፡በተጨማሪም ከጎንደር ከመጡ ከ1913 ጀምሮ እስከ 1917 ድረስ
ለኅሩይ ወልደሥላሴ በመንግስት ግምዣ ቤት ጸሃፊ በመሆን አገልግለዋል፡፡ለዚህ ስራቸው ደግሞ
በወር የአምስት የማርያ ትሬዛ ብር ምንዳ ይከፈላቸዋል፡፡
የኢትዮጵያን ጋዜጠኝነት በመመስረትና በማሳደጉ በኩል እስከ ፋሺስት ጣልያን መምጫ 1928
ዓ.ም ድረስ አስተዋጽዖ አድርገዋል፡፡የጦርነቱ ነገር እርግጥ እየሆነ ሲመጣ ሃገራዊ ስሜትን ያዘሉ
በራሪ ወረቀቶችን የጋዜጣ መጣጥፎችን መጻፍ ጀመሩ፡፡በ1927 ዓ.ም በግላቸው መጀመርያ
ያሳተሙትየወንድ ልጅ ኩራት ስለ ሃገር ልጅ መሞትን ሲሆን ሙያ በልብ ደግሞ ብዙም ሳይቆይ
ተከተለ። በ1928 ዓ.ም ጀግና ሰው ተጋዳይ ለጠላት አልሞት ባይ ወጣ፡፡
በ1927 ዓ.ም አቶ መኮንን ሃብተወልድ እና የአዲስ አበባ መስተዳድር የሃገር ፍቅር ማህበርን
መሰረቱ፡፡ወልደግዮርጊስ ደግሞ በመክፈቻው ዝግጅት ጽሁፋቸውን እንዲያቀርቡ ከተጋበዙ
ደራስያን መሃል አንዱ ነበሩ፡፡እንደሚባለው ከሆን በሚነበብበት ወቅት ሰዎች ጎራዴያቸውን
አውጥተው ቀረርቶና ሽለላውን ተያያዙት በጠላት ላይም መፎከር ጀመሩ፡፡
***
መሃል ወልደ ግዮርጊስ ወልደ ዮሃንስና አቶ ሰሎሞን ዮሐንስ ይገኙበታል፡፡ምንም ያህል ሳይቆይ
በአቶ ይልማ ደሬሳ አደራዳሪነት ወደ ጋዜጠኝነቱ ተመለሱ፡፡አዳዲስ ጋዜጦች ለመጀመር ስለታሰበም
ወልደ ግዮርጊስ የአማርኛው ጋዜጣ አዲስ ዘመን ተብሎ እንዲሰየም ሃሳብ አቀረቡ፡፡ ኃይለሥላሴም
ቆይተው አርእስቱን አጸደቁት፡፡በግንቦት 1933 ዓ.ም ተጀመረ፡፡በሚቀጥለው ወር ሰኔ 14 1933
ዓ.ም ይዞት በወጣው ጽሁፍ ላይ ኃይለሥላሴ ከስደት ወደ አዲስ አበባ ከተመለሱ በኋላ በሚያዝያ
27 1933 ዓ.ም ባደረጉት ንግግር “ይህ ቀን ለአዲስቷ ኢትዮጵያ የአዲስ ዘመን ጅማሮ ነው” ስላሉ
አንዳንዶች የጋዜጣው ስያሜ ከዚህ የመጣ ነው ይላሉ፡፡ለ18 አመታትም ሳምንታዊ ሆኖ ከቆየ
በኋላ በታህሳስ 11 1951 ዓ.ም ከጅማሮው አንስቶ በአርታኢነት የሰሩበት ወልደግዮርጊስ ስለ
ለውጡና ተገቢነቱ መክረው ወደ እለታዊነት እንዲቀየር ተወሰነ፡፡ ወልደግዮርጊስ ከብርሃንና ሰላም
ለጣቂ ነው በሚባለው አዲስ ዘመንና ባንዲራችን (በኋላ ሰንደቅ አላማችን) በተከታታይ በየቀኑ
መጻፋቸውን ቀጠሉ፡፡ የነዚህ ሁለት ጋዜጦች ዳይሬክተር በመሆን ከ1952-1954 ዓ.ም ድረስ
ቆይተው፤በረዳት ሚንስትርነት መአረግ ለሁሉም ጋዜጦች ሃላፊና ተጠሪ በመሆን ሲሾሙ በ1952
ዓ.ም ለታዋቂ ምሁራንና የንጉስ አማካሪዎች የሚሰጠውን የብላቴንነት ማዕረግን አገኙ፡፡አዲስ ዘመን
25ኛ ልደቱን ባከበረበት 1958 ዓ.ም ወልደግዮርጊስ ወልደዮሐንስ ይፋዊ “የኢትዮጵያ ጋዜጦች
አባት”የሚል ማዕረግም በማስታወቂያ ሚንስትር ተሰጥቷቸዋል፡፡ይሄ በህይወታቸው የሚልቀውና
እንደ ጀግንነት መታሰብያ የሚቆጥሩት ክብር ነበር፡፡እንደ ቤተሰቡ አባባልም ከሆነ ከዚህ ሌላ ብዙ
ማዕረጎችን ቢቀዳጁም የሚያስበልጡት ይሄንን ነበር፡፡በሚቀጥለው አመት በ1959 ዓ.ም
ለማስታወቂያ ሚንስትር አማካሪ ሆነው በምክትል ሚንስትርነት ማዕረግ እስከ 1964 ዓ.ም ድረስ
ቆዩ፡፡
226
ጥቋቁር አናብስት
ወልደ ግዮርጊስ ለኃይለሥላሴ ታማኝ ባለሟል በመሆን ከዘመነ ተፈሪ መኮንን የአልጋ ወራሽነት
ጊዜያቸው ጀምሮ እስከ ንግስና አገዛዛቸው ጊዜያት በታማኝነት ለበርካታ አመታት በጥቅሉ
አገልግለዋል፡፡ በአገልግሎታቸውም ይኮራሉ፡፡ሃገሪቱን በማዘመኑና በማሸጋገሩ ላይም የበኩላቸውን
እንዳደረጉ ያምናሉ፡፡ይሄም እድገትም ለመጭው ብሩህ ጊዜያት መምጣት ትክክለኛው መንገድ
እንደሆነ፡ የንጉሱ አመራር ለኢትዮጵያም ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪቃ ትክክለኛው አመራር
እንደሆነ ያምናሉ፡፡ወልደ ግዮርጊስ ከሌላው ኢትዮጵያዊ በተለየ ጊዜያቸውን የቀደሙ ነበሩ። ሌላው
ኢትዮጵያዊ “ስልጣኔ ፤ክርስትና በአጠቃላይ ማንኛውም ነገር ኢትዮጵያ ነች” ብሎ በሚያስብበት፣
የአፍሪካን መኖር በማያውቅበት ወቅት የአፍሪካ ግንዛቤ የነበራቸው ሰው ነበሩ፡፡ ስለዚህም ወደ
ሌሎች አፍሪካውያን በመሄዳቸውና ቡድን ፈጥረው ለኋለኛው የአፍሪካ ህብረት መሰረት ስላስጣሉ
227
ጥቋቁር አናብስት
***
ከነጻነት በኋላ በ1941 እ.ኤ.አ እንደገና መጻህፍትን መጻፍ ሲጀምሩ ስለንጉሳውያን ቤተሰቦችና
ንጉሱን ለማወደስ በዝርው እና በግጥም መልክ መጻፋቸውን ቀጠሉ፡፡እነሱም 1ኛ ገራ መንግስት ዘ
ኢትዮጵያ በ23 ጥቅምት 1937 ዓ.ም የታተመው ረዥም ግጥም ስለ ዘውድ አከባበሩ የተጻፈ
ሲሆን ንጉሱን የሚያወድስ የፋሺስትን ወረራንም የሚኮንን ነበር፡፡2ኛ ክብረ ነገስት 1938 የዘውድ
በኣል የተጻፈ ረዥም ግጥም ነው፡፡3ኛ ታሪክ ያለው አይሞትም ለ1939 የዘውድ በአል የተጻፈ
ሲሆን ይሄኛው በተለይ ረዘም ያለ የመታሰብያ መጽሐፍ ሲሆን ከርእሱ ጋርም የሰመረ ነበር።
በግራኝ አህመድ ስለደረሱት ውድመቶች ስለቴዎድሮስ ጀግንነት ፣የራስ አሉላ አባ ነጋ ጀብዱ፣
የአንዳንድ አርበኞች የጀግንነት ስራዎች(ዘርአይ ድረስ፤አብርሃ ደቦጭ ፣እና ሞገስ አስገዶም
በግርያዝያኒ ላይ ፈንጂ የጣሉት) ታሪክ ያካተተ በምስልም የዳበረ ነበር፡፡(ከላይ የተጠቀሱት ሁለት
መጻህፍት መጀመርያ በጋዜጣ ተከታታይ መጣጥፎች መልክ የታተሙ ነበሩ)4ኛ አምሐ ፍቅር ወ
ሰላም ለንጉሱ ልደት በሃምሌ 16 1939 የቀረበና ኃይለሥላሴን ለህዝቡ ስላላቸው ፍቅር
ስላመጡት ሰላም የሚያወድስ ነው፡፡5ኛ ሌላ ተመሳሳይ መጽሐፍ በ1942 ለ ንጉሱ 58ኛ
ልደታቸው የተጻፈና ለመሪነት በእግዚአብሔር መቀባታቸውን አንስቶ የሚያሞካሽ ነው፡፡6ኛ
በጥቅምት 23 1949 ዓ.ም የታተመው አምሐ ንጉስ ለንጉሱ 25ኛ የዘውድ በአል የተጻፈና
ከልጅነት እስከ ዘውድ ክብረ በኣል የተነሷቸውን ፎቶዎች ይዟል፡፡7ኛ ዘርዐ ብሩክ 37 ግጥሞችን
ያካተተው ስለ ኃይለሥላሴ ህይወትና እድገትን በኢትዮጵያ ለማምጣት ስለሰሩት ስራ ሲሆን
ለ38ኛው የዘውድ ክብረበኣል በ1961 ዓ.ም የታተመ ነው፡፡፣ምንአልባትም ሌሎች ሁለት ወይም
ሶስት መጻህፍት አሉ፡፡የድል ኮከብ ፤ገጸ በረከት ታሪክና ስራ በዚሁ ዘርፍ ስለንጉሳውያኑ ቤተሰብ
የሚያትቱ ናቸው፡፡
229
ጥቋቁር አናብስት
ምንም እንኳን እነዚህ መጻሕፍቶቻው ለተወሰኑ የታሪክ ድርሳኖቻው ሲባል ተፈላጊ ሲሆኑ በሌሎች
ሴማዎች ላይ የሰሯቸው ስራዎች ለመጪው ግዜ የሚፈለጉና የሚዘከሩ ናቸው፡፡መክንያቱም
ከኪናዊ ዋጋቸው ይልቅ ከጻፏቸው መሃል ምንአልባትም የተወሰኑት በቀደመው እና ፋናወጊ
በሆነው የስነጽሁፍ አጻጻፍ ባሕል የተጻፉ ስለነበሩ ነው፡፡በጦርነቱ በፊትና መሃል ከጻፏቸው
ትናንሽ የግጥም መጻሕፍት በኋላ በውጪ ጉዞዋቸው ባደረባቸው ተጽእኖ ለሃገራቸው እድገት
በሰነቁት ራእይ ተነሳስተዋል፡፡ወድያው እንደተመለሱም ብልጽግና በግብርናን ጽፈው በ1941 ዓ.ም
ታተመ፡፡ወልደግዮርጊስ ስለዚህ መጽሐፍ ያላቸው አስተያየት ከፍተኛ ነው፡፡ስለእርሻና እንስሳት
ርቢ ስለኢትዮጵያ ያለፈ ታሪክና ስለመጻኤ እድገቷ እምቅ ችሎታ የሚያነሳ ነው፡፡በመጽሐፉ መሃል
ግጥሞችም ተቃይጠውበታል፡፡ በቀጣዩ አመት ሌላ ስለንጉሳውያን ቤተሰቦች ከጻፉት መጽሐፍ
ውጪ ስለ ንጉሳውያን ቤተሰቦች(ከ1948 እና ከ1961 በስተቀር)ሌላ ስራ አልሰሩም፡፡ በ1941
ከስራ በኋላ ስትፈቱ እንቆቅልሽ ተጫወቱ የሚል የእንቆቅልሽ ስብስብ መጽሐፍ አሳተሙ፡፡
በስብስቡ ውስጥ የተካተቱት ጥቂት እንቆቅልሾች ቢሆኑም ተብራርቶ መልስ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
በተመሳሳይ አመትም የአለም ጸባይ እና ስነምግባር የተባሉ ሁለት መጻሕፍትን በማሳተም በዝያን
አመት ያሳተሙትን የመጽሐፍ ብዛት ሶስት አድርሰዋል፡፡ስነምግባር ትልቅ ግምት ከሚሰጧቸው
መጻሕፍቶቻቸው መሃል አንዱ ነው፡፡በክርስትያናዊ ህግጋትና ስነምግባራት እንዴት መኖር
እንደሚቻል ምክር ይለግሳል፡፡ ወልደግዮርጊስ በርካታ ምሳሌዎችንም ይሰጣሉ፡፡በ1948 ዓ.ም
በድጋሚ ታትሟል፡፡ሌላው በኢትዮጵያና ኤርትራ ቅልቅል ዙርያ በ1945 ዓ.ም የታተመው
ስራቸው አዲሲቱ ኢትዮጵያ ነው፡፡8በ1949 ዓ.ም የባልና ሚስት ጭውውት በእንካ ሰላንትያን
አሳተሙ፡፡መጽሐፉ በኢትዮጵያ አይነተኛ የስነቃል ጨዋታ ዙርያ ያጠነጥናል፡፡ወልደ ግዮርጊስ
በእንካ ሰላንትያ የሚነሱትን መረን የለቀቁና ጽርፈት የተሞላባቸውን ምልልሶች በመግደፍ ደገኛ
ምሳሌዎችን አካተዋል፡፡ቀጣዩ መጽሓፋቸው በ1954 ዓ.ም ከአምስት አመት በኋላ ነው
የታተመው፡፡አምስት መንገደኞች ይሰኛል፡፡9 (በዝርው የተጻፈ ሲሆን)ገጸ ባህርያቱ ”አጠቃላይ
የዚህን አለም ሰዎች“ን በትዕምርታዊ መልኩ ይወክላሉ፡፡ ጉዞዋቸው በአጠቃላይ የተሰጠው
ለመጽሐፍ ቅዱስና ለሳይንስ ነው፡፡ቀጥሎ በ1957 ዓ.ም ግብረገባዊ የሆነው መጽሐፋቸው
አትስረቅ ወጣ፡፡እንደ ስርቆት፡ማመንዘር፤ምንፍቅና፤እብለት፡የሌሎችን ንብረት ማውደም
የመሳሰሉትን ወንጀሎች በመንቀፍ የተጻፈ ነው፡፡በዝርው እና በግጥም መልክ ተዛንቆ በመልካም
ቋንቋ የተጻፈው ዝርዋዊ ትረካ የሆነው ታሪክ አይሙት እንዲያጫውት የኢትዮጵያን እድገት ዘጋቢ
በሆነ መልኩ በተመሳሳይ አመት ታተመ፡፡ቀጣዩ መጽሐፍ የእስማኤል ቁጥቋጦ ነው፡፡ሀይማኖታዊ
ይዘት ያለው ሲሆን የደግነት ትሩፋትን የመሳሰሉትን ያነሳል፡፡(በመጽሐፍ ቅዱስና በቅዱስ ቁርአኑ
ስለተጠቀሱት)በእስማኤል በእናቱ ሃጋር እና በአባቱ አብርሐም መካከል ስላለው ግንኙነት ያትታል፡
230
ጥቋቁር አናብስት
፡የተወሰኑ ግጥሞች በዝርው መሃል ተዘርተው ይገኙበታል፡፡በ1957 ወይም በ1959 ዓ.ም ነበር
የወጣው፡፡(ልዩነቱ የመጣው በደራሲው መጻህፍት የተጠቀሱ የተለያዩ ቀኖች መሰረት ነው)
ከሁሉ የታወቀውና የተነበበው መጽሓፋቸው አግአዚ በመጽሐፍ መልክ የታተመው በ1961 ዓ.ም
ነው፡፡የተጻፈው ግን ከዚያ በፊት ነበር፡፡ከ1938 ሀምሌ 27 አንስቶ በተለያዩ ወቅቶች አዲስ ዘመን
ጋዜጣ ላይ የወጡ አስራ ሰባት ያህል ተከታታይ ስራዎች ስብስብ ነው፡፡በዚህ መጽሐፍ
ወልደግዮርጊስ ኢትዮጵያውያን ለልብወለድ ጽሁፍ ፍላጎት እንዲያሳድሩ ጥረዋል፡፡ በግል
ማስታወሻቸውም ላይ እንዳሰፈሩት ከሆነ ግርማቸው ተክለሐዋርያት አርአያን10ከመጻፉ በፊት
ጽፈውት ነበር፡፡ወልደግዮርጊስ በዚህ መጽሐፍ ኢትዮጵያ “ለውጪው አለም በሯን ስለመክፈቷ”
የጻፉ ሲሆን ብዙ ነገሮች በትንቢት መልክ ተዘርዝረውበታል፡፡በ1961 ዓ.ም በታተመበት ግዜ
መጽሐፉ ሲጻፍ ከተተነቡት በርካታ ነገሮች ውስጥ አብኛዎቹ ይዘዋል፡፡አግአዚን በመጽሐፍ መልክ
ያሳተሙት ሌሎች ስለገፏፏቸው ነበር፡፡መጽሐፉ ስለ ዘመናዊ እድገት፤እና ስለኢትዮጵያ የባህር በር
ፍላጎት እንዲሁም በባህል እና በዘመናዊነት መካከል ስላለው ቅራኔ ነው የሚያነሳው፡፡
ወልደ ግዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ በአሁኑ ወቅት ብዙም ተነባቢነት ባይኖራቸውም በተለይ በአግአዚ
መጽሐፍ ለአማርኛ ስነጽሁፍ እድገት ይበልጡኑ በሁለት እግሩ ለመቆም ድክ ድክ በሚልበት
የልጅነት ዘመኑ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡
231
ጥቋቁር አናብስት
233
ጥቋቁር አናብስት
***
ምንም እንኳን ከ25 የስራ አመታት በኋላ በ1958 አ.ም ጡረታ ለመውጣት ቢፈልጉም (1933
ጀምሮ እስከ ግንቦት 33 1966 ድረስ) የመንግስት ለውጡ 3 ወራት እስኪቀረው ድረስ
አልቻሉም፡፡ ወልደግዮርጊስ በአዲሱ መንግስትም ጊዜ በሰላም ለመኖር ቻሉ፡፡ጡረታ ከወጡ በኋላ
ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ በትጋት መጽሐፍ መጻፍ ጀምረው የነበር ሲሆን በጽሁፋቸውም ያላቸውን
ተስፋ ገልጸው እንዲታተም ቢፈልጉም ሳይታተም ቀርቷል፡፡ወልደ ግዮርጊስ ጽፈው የጨረሱት
በሰባዎቹ ማገባደጃ ነበር፡፡መጨረሻ ላይ ከቤተሰባቸው ውስጥ አንድ ሰው ረቂቁን ችግር ይፈጥራል
ብሎ በቤት ከማኖር አቃጠለው፡፡17
በ1972 ዓ.ም አይናቸው ማየት ተሳነው፡፡ይህ ክስተት በሳቸው ላይ ታላቅ ጭንቀትን ፈጠረ፡፡
እድሜ ልካቸውን ሲጽፉና ሲያነቡ ኖረው በዚህ ሰአት ፈጣሪ ለምን ብርሃኑን ነሳቸው?ይሄን
ስነልቦናዊ ቅራኔ የማስታረቅ ችግር ደረሰባቸው፡፡የፈጣሪ ፍቃድ ነው ብለው ለመቀበል ቢሞክሩም
መልሶ ግን በፈጣሪ የመማረር ስሜት ይመጣባቸዋል፡፡ቤተሰቦቻቸው እንደሚያስቡት ችግራቸውን
ተቀብለው አዕምሯቸው ከመረጋጋት ይልቅ እንደውም እያገረሸበት እንደተናወጠ የመጨረሻዎቹን
እድሜያቸውን ገፍተዋል፡፡መጻፍም ሆነ ማንበብ እንዲሁም መራመድ አቃታቸው፡፡ስለዚህ የመኖር
ትርጉም ምንድን ነው?በአካልም ሆነ በመንፈስ ድቅቅ አሉ፡፡ ለ2 አመታት አልጋ ላይ ዋሉ፡፡
234
ጥቋቁር አናብስት
ያገለገሉባቸው የነበሩ አድባራት ቀሳውስት የደብረ ሊባኖስን አፈር መቅመስ አለባቸው ስላሉ
ከቤተመቅደሱ አቅራቢያ ቤተሰቡን በሚያኮራ ሁኔታ ታላላቅ ባለስልጣናት፤የቤተ ክህነት ሰዎችና
በርካታ ሀዘንተኛ በተገኘበት ልጃቸው አምባሳደር አያሌውም ከሎንደን በራሱ ወጪ ተሳፍሮ
በመጣበት ስርዐተ ቀብራቸው ተፈጽሟል፡፡
ማስታወሻ
1)አለቃ ህሩይ የታወቁ የቤተልሄም በጌ ምድር ምሁር ነበሩ፡፡መስከረም 15 1855 ዓ.ም ሲሆን
የተወለዱት አመተ እረፍታቸው በ1948 ዓ.ም ነው፡፡
2)እነሱም መምህር ሃይለማርያም በኋላ አቡነ ጴጥሮስ የሆኑት አቶ ሊቄ በኋላ አፈ ንጉስ ገብረ
ክርስቶስ የሆኑት አለቃ ለማና መልዐከ ገነትክፍሌ ናቸው፡፡
3)ሌላ ታዋቂ ድራሲ ሆነው ለኢጣልያ መንግስት “በውብ አማርኛቸው መክንያት” በስርጭት ስራ
የተሳተፉት ደግሞ ከበደ ሚካኤል ሲሆኑ በዚህ ስራ ላይ የሰሩበት ሁኔታ በፍቃደኝነት ይሁን
አይሁን አይታወቅም፡፡አንዳንድ“ተባባሪዎች” እጃቸውን ተጠምዝዘው ከወራሪው ጋር እንደሰሩ
ይናገራሉ፡፡ ምናልባትም እንዲረሳላቸው ፈልገው ይሆናል፡፡
4)በዚህ ጉዞ ብርሃኑ ዘርይሁን በአሉ ግርማ ጳውሎስ ኞኞ እና አንድ ሌላ ጋዜጠኛ አብሯቸው ነበር፡
፡
235
ጥቋቁር አናብስት
7)ንጉሱ በቤተመንግስቱ ውስጥ ለሚገኘው ቅዱስ ማርቆስ ለሚሰሩ ቀሳውስት መሬት ይሰጡ ነበር፡
፡ወልደ ግዮርጊስ በልጅ እያሱ ከተሰራው ቀጨኔ መድሃኒያለም ከመስራታቸው በፊት አሁን
ዩንቨርሲቲው አጠገብ ከሚገኘው ቅዱስ ማርቆስ ያገለግሉ ነበር፡፡
8)ይህ መጽሐፍ በሌላ ቆየት ብሎ በወጣ መጽሃፍ አትስረቅ የሳቸው ለመሆኑ ከጀርባው ተጠቅሷል፡
፡መጽሐፉ ራሱ ግን የደራሲውን ስም አይጠቅስም፡፡
12)የያሬድ ገብረ ሚካኤል እናት የወልደግዮርጊስ የአባታቸው እናት ነበረች ወይም እንደዚህ
አይነት ዝምድና ነበራቸው፡፡የያሬድ ልጆች ወልደግዮርጊስን አጎት በማለት ይጠሯቸዋል፡፡ያሬድ
236
ጥቋቁር አናብስት
13)የብርሃኑ ዘርይሁንና የያሬድ ገብረ ሚካኤል እንዲሁም የሌሎች ጋዜጠኞች እድሜ ያጠረው
በመጠጥ ጦስ ነው ብለው ወልደ ግዮርጊስ መገመታቸው አይቀርም ነበር፡፡
16)በርካታ የግል ጽሁፎችና ምስሎች ከንጉሱ ግዜ በኋላ ባለው የድህረ አብዮት ግዜ በካድሬዎችና
ለደህንነታቸው ፍርሃት ባደረባቸው ሰዎች ወድመዋል፡፡
17)አንዳንድ ኢትዮጵያኖች በዚህ ርእስ ቅኔያዊ ይዘት አለው ይላሉ፡፡በኮምዩንስት አገዛዝ የፈሰሱ
የእንባ ዘለላዎችን በአጽንኦት ለማንሳትና ሌላ መራር ሃዘንንም ለመግለጽ ዘይቤያዊ ስልትን
ተጠቅሟል በማለት (መጽሐፉ ከማርክሳዊው አገዛዝ ውድቀት በኋላ ዳዊትም ወደ ሃገሩ
በተመለሰበት ወቅት ወደ አማርኛ ተመልሷል)
18)ደብረ ሊባኖስ ገዳም ስለሆነና ቤተክርስትያኒቱም የዛ አካል ስለሆነች ወዳጆቹ የሆኑት ካህናት
በቀብሩ ስነ ስርአት ሊካፈሉ አልቻሉም፡፡ባህታዊዎች ብቻ ናቸው በሃይማኖታዊ ስርአቶች መሳተፍ
የሚችሉት በደብረ ሊባኖስ ፡፡ያላገቡ ንቁ ወጣት ዲያቆናት ግን ማገዝ ይችላሉ፡፡በጣም ወጣት
አልያም በጣም የሸመገሉ መሆን አለባቸው፡፡(የወሲብ ስሜት እንዳይኖራቸው ተብሎ)ይህ የቅድስና
መገለጫ ነው፡፡(ዲያቆናት የወሲብ ስሜት ባደረባቸውም ወቅት በአገልግሎት ላይ እስካላገቡ
መሳተፍ አይችሉም)፡፡
237
ጥቋቁር አናብስት
ይህ የቃላት አደን ጠቀሜታ ያለው ባህላዊ ስራ የሚሆነው ሃገራዊ ስነጽሁፉ በፍጥነት ሲስፋፋ
ነው፡፡የዚህ ስራ አንዱ ውጤት ደግሞ አዳዲስና የተሻሻሉ መዛግብተቃላት መዘጋጀት ነው፡፡ባለፉት
ጥቂት አስርት አመታት የተዘጋጁ መዛግብተቃላት ደግሞ ታላቅ አስተዋጽኦን ለአማርኛ(ለትግርኛና
ኦሮምኛ ቋንቋዎች) አበርክተዋል፡፡ ጠቀሜታው ለነዚህ ቋንቋ ተማሪዎችና በነዚህ ቋንቋዎች
በተለያዩ መንገድ ለሚጠቀሙባቸው ሁሉ ነው፡፡ መዝገበ ቃላትን እያነበቡ የቃላት እውቀታቸውን
ለማስፋትና ትክክለኛውን ትርጓሜ ለማግኘት ለሚፈልጉ ደራስያንም ከፍተኛ እገዛ ያደርጋሉ፡፡ስለ
ባህላዊ እሴቶችና ያለፉ ልማዶችም የምናውቅባቸው አስተማሪ መዛግብተ ቃላት ናቸው፡፡ቃላቱን
ብቻ ስለማይፈቱና ከአውድ አንጻር ስለሚያዩት እንዴት ባለና በምን ሁኔታ ውስጥ መጠቀም
እንደምንችል ስለሚያሳዩ ታሪካዊ መረጃዎችንም ማግኘት ይቻላል፡፡እምነቶች እደ ጥበባዊ ቅርሶች
አባባሎች ትውፊት ሁሉ ከሞላ ጎደል በጥሩ መዝገበ ቃላት ውስጥ ይካተታሉ፡፡በሌላ መንገድ
እነርሱ እራሳቸው ለአያያዝ የሚመቹ ኢንሳይክሎፔድያ ናቸው ማለት እንችላለን፡፡
እዚህ እገዛቸውን ካገኘሁባቸው ሁለት መዛግብተቃላት አዘጋጆችን አጭር የህይወት ታሪክና አንድ
በትግርኛ ተማሪዎች ስሙ የሚመሰገን የትግርኛ መዝገበ ቃላት አዘጋጅን ለማካተት ሞክሬያለሁ፡
238
ጥቋቁር አናብስት
ተሰማ ሀብተሚካኤል
በመዝገበ–ቃላቱ የተነሳ "ብርሃን ፈንጣቂ" ተብሎ የሚጠራ
239
ጥቋቁር አናብስት
አንዱ ግጽው² ይሰኛል፡፡ተሰማም የዚህን መጻሐፍ ገልብጦ መጨረስን ተከትሎ በመከተል (ግጽው)
ተብሎ ይጠራ ጀመር፡፡
ከደመወዙ ማነስ የተነሳ ከስራ የመልቀቅያ ደብዳቤ አስገብቶ የነበረቢሆንም መዝገበ ቃላቱ
በቀዳማዊ ኀይለሥላሴ በመፈለጉ ምክንያት ተቀባይነት አጥቷል፡፡
አቶ ተሰማ ጡረታ ሲወጣ አድካሚ የሆነ ደምግፊት አስቸግሮት ነበር፡፡በዚህም የተነሳ ከፍተኛ
ድካም ይሰማው ነበር፡፡በ80 አመቱ በመስከረም 30 1962 አ.ም ከማረፉ ከስድስት ቀናት በፊት
በጥልቅ የምርምር ስራ³ የቀዳማዊ ኀይለሥላሴን ሽልማት እንዳሸነፈ ተነግሮታል፡፡ በአዲስ አበባ
ውስጥ በቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን ተቀበረ። ካረፈ ከ23 ቀናት በኋላ ልጁ ሰላማዊት
ተሰማ የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን ሽልማት በአባቷ ስም ተቀብላለች።
241
ጥቋቁር አናብስት
ደስታ ተክለወልድ
ደስታ ተክለወልድ በሃምሌ 1893 ዓ.ም ሸዋ ተጉለት ውስጥ በቡልጋ አውራጃ ከአባታቸው አቶ
ተክለወልድና ከወይዘሮ ወለተማርያም ጎሽውሃ ወግዳ ውስጥ ተወለደ፡፡በአቅራቢያው ካለ
ቄስትምህርት ቤት ገባ፡፡ቀጥሎም በደብረሊባኖስ ገዳም ከአለቃ ኪዳነማርያምና ከመምህር
ገብረኢየሱስ ስር ቅኔና ዜማን ቀጽሏል፡፡ደስታ በጊዜ ነበር ተለይቶ መውጣት ያስቻለው ተቀባይ
243
ጥቋቁር አናብስት
አለቃ ደስታ ተክለወልድ ታላቅ ምሁርና በባህልና ትውፊት ዙርያ እንዲሁም ስለ ሁለቱ
ሆሄያትም ሰፊ እውቀት የነበረውና የጻፈም ሰው ነበር፡፡⁶ መዝገበ ፊደልና አቡጊዳ ፤ገበታ ሃዋርያ
፤ረብሃ ስም (ታላቅ ስም) የሚሉ ሌሎች ስራዎችን ቢሰራም ተለይቶ እሚታወቀው ግን በልጨኛ
የ1283 ገጽ በ523 ምስል በረዥም የስዋሰው መግቢያውና በአማርኛ ፊደላትና ቋንቋ ታሪክን
ባቀፈው መዝገበ ቃላት አበርክቶቱ ነው፡፡እዚህ መዝገበ ቃላት ላይ ከ1921 -1950 ዓ.ም
ድረስ ደክሞበታል፡፡ የታተመው በአርቲስቲክ ማተምያ ቤት በ1962 ነው፡፡ትልቅ ስኬት
ቢሆንም ለመስፋፋትና ለማሻሻል እያሰበ በነበረበት እ.ኤ.አ በ1977 ዓ.ም በ84 አመቱ
አርፏል፡፡
ለማተምያ ቤቶች ለ46 አመታት ሰርቷል ግን ስሙ ሲጠቀስ የሚኖረው በመዝገበ ቃላቱ ነው፡፡
ከሌሎች መዛግብተ ቃላት በላይ ባቆራቸው ቃላትም ብቻ ሳይሆን በባህላዊ እውቀትና እምነቶች
አፈታሪኮች(አንዳንዶቹ እምነቶች በታሪክ ብቻ እንጂ በሳይንስ ባይረጋገጡም) በፈሊጥ የዳበረ
244
ጥቋቁር አናብስት
245
ጥቋቁር አናብስት
ግርማ–ጽዮን መብራህቱ
***
ግርማ ጽዮን መብራህቱ በሲፋጉላ ወረዳ በሰራዬ አውራጃ ኤርትራ ውስጥ በ1919 ዓ.ም ነው
የተወለደው፡፡ በመጀመርያ ትምህርት የጀመረው ከአቅራቢያው ካለ የቄስ ትምህርት ቤት ነው፡፡
በጊዜው ባልተለመደ መልኩ (በባህላዊ መንገድ የቤተ ክርስትያን ትምህርት)የተማሩ እናት
ስለነበሩት ግርማጽዮንን በትምህርቱ ይረዱት ነበር፡፡የቁም ጽህፈት መጻፍና ከቆዳ ብራና ማሰናዳትን
የተማረው ከእርሳቸው ነው፡፡ስማቸውም እማሆይ አምለሰት ማሉ ይሰኛል፡፡በመቀጠል ግርማጽዮን
በአቅራቢያው ወደሚገኙ ገዳማት በመሄድ ተጨማሪ ትምህርትን በተለይ የጽዋትወ ዜማን ቀሰመ፡፡
በመቀጠል ትምህርቱን ለማስቀጸል ወደ ጎንደር በማቅናት የሙሉ ደብተራነትን አገኘ፡፡ ዜማን፤
አቋቋምን፤ተምሮ ወደ ሃገሩ ተመለሰ፡፡እዚያም ከተመለሰ በኋላ በርካታ የብራና ጽሁፎችን ጽፏል፤
ቅጂዎችን ገልብጧል፡፡ለዚህ ስራ የበግ ፤ የፍየል ወይም የላም ቆዳን ማግኘት እንደ ብራና
እንዲያገለግሉ ማልፋት ወደ መጽሐፍትነት መጠረዝ፤የቀስም ብእርና ቀለም ማዘጋጀት ይጠይቃል፡፡
246
ጥቋቁር አናብስት
ማስታወሻ
1)አጭር የህይወቱ ታሪክ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ነበር፡፡ብርሃኑ ገብረ ጻዲቅ የሚባል የአዲስ
አበባ ዩንቨርስቲ ተማሪም መመረቂያ ዲማጹን በሱ ላይ ሰርቷል፡፡
247
ጥቋቁር አናብስት
2)ግጽው የሚባለው መጽሐፍ ግማሽ ሲሆን የኢየሱስ ክርስቶስን ታሪክ የሚናገርና በቤተክርስትያን
የሚነበብ የሚዜምበት ነው፡፡
3)ይህንን ሽልማት ለማሸነፍ የበቁት ሁለት የመዝገበቃላት አዘጋጆች ሲሆኑ ተሰማ ሀብተ ሚካኤልና
ደስታ ተክለወልድ ናቸው
5)በአጼ ዮሐንስ አራተኛ ዘመነ መንግስት በቦሩ ሜዳ ላይ በተደረገው ክርክር በወግ አጥባቂ
ቀሳውስት ለዳተኛ ተብለው ተከሰው ያውቃሉ፡፡ሚኒሊክ ወደ ሚያስተዳድሩት ሸዋም አምልጠው
እንዲሄዱ ተመክረው ነበር፡፡ኪዳነ ወልድ ያኔውኑ በሱዳን አድርገው በግብጽ አቆራርጠው ወደ
ጣልያን አቀኑ፡፡ለኢግናዝዮ ጉዊዲ እና ሌሎች ሰዎች ግዕዝና አማርኛን ማስተማር ጀመሩ፡፡
ቀጥለውም ወደ እየሩሳሌም ሄደው ሳለ ወደ ኢትዮጵያ ተጠርተው በስነጽሁፍ ላይ እንዲሰሩ ጥሪ
ሲቀርብላቸው ተቀብለው መጥተው እስከ እለተ ሞታቸው በዚሁ ዘርፍ አገልግለዋል፡፡
248
ጥቋቁር አናብስት
ብርሀኑ ዘርይሁን
የልብወለድ ደራሲ፣ጸሐፊ ተውኔት፣ጋዜጠኛ እና የአዳዲስ አጻጻፍ
ዘዴ ፈርቀዳጅ ብርሀኑ ዘርይሁንን ታሪኩን ለመፃፍ ከማሰቤ በፊት
ጀምሮ ለዓመታት አውቀዋለሁ። ለቃለመጠይቅ ስጠይቀው
ወዲያውኑ ቢስማማም ሰፋ ላለ ጊዜ ተገናኝተን እንድናወራ ስፈልግ
ግን ጭራው አልያዝ አለኝ። እረፍት ማጣት የከያኒያን ጣጣ ሳይሆን
አይቀርም። ወይም ሌሎች የበለጡ ጉዳዮች አእምሮውን
አጨናንቀውት ይሆናል። ይህ ቃለመጠይቅ ከመካሄዱ በፊት
ብርሀኑ ለዓመታት በርካታ ጠቃሚ የሥነ ጽሑፍ ስራዎችን ሲያበረክት ቆይቷል። ምናልባት በንጉሱ
መጨረሻ ዘመናት ለዓመታት ታፍኖ የቆየውን ድምፁን በማሰማት፣ ከዛ በፊት በከንቱ የጠፋውን
ጊዜ እያካካሰ ይሆናል።
ብርሀኑ ዘርይሁን በ1926 ዓ.ም በጎንደር ከተማ እንደተወለደ ነግሮኛል። ነገር ግን ዜና እረፍቱና
አንዳንድ የመንግስት መዛግብት በ1925 ዓ.ም እንደተወለደ ይጠቁማሉ።አባቱ ዘሪሁን መርሻ
"የቤተክርስቲያን ሰው" ሲሆኑ፣ የአካባቢውን የቤተክርስቲያን የዝማሬ እና የወረብ ቡድን ይመሩ
ነበር። ከዚህም ባሻገር ብራና እያዘጋጁ ቅዱስ ድርሳናትን ይገለብጣሉ። የብርሀኑ እናት አልጣሽ
አግደህ የቤት እመቤት ቢሆኑም፣ ጌሾ እየሸጡ ትንሽ ገቢ ያገኛሉ። ብርሀኑ ከቤተሰቡ ስድስት ልጆች
መሀል የመጨረሻ ነው። ቃለመጠይቃችንን ባደረግንበት በ1979 ዓ.ም ከአንዲት እህታቸው በቀር
ሁሉም በሕይወት ነበሩ። ብርሀኑ በወላጆቹ እንክብካቤ ነው ያደገው። ስድስት ወይም ሰባት ዓመት
ሲሆነው የቤተክርስቲያን ትምህርት መማር ጀምሮ እስከ አስራሁለት ዓመቱ ቀጠለ። ያን ጊዜ ግዕዝ
ቢማሩም ብርሀኑ ፍላጎት ኖሮት በደንብ ስላልተከታተለ፣ የግእዝ እውቀቱ የሚያወላዳ አይደለም።
ነገር ግን ከአማርኛ መጽሐፍት ጋር መላመድ ጀምሮ ነበር። ከአፈወርቅ ገብረየሱስ "ዋህድ" ( በኋላ
"ጦቢያ") እንዲሁም ከደብተራ ዘነብ "መጽሀፈ–ጨዋታ ስጋዊ ወመንፈሳዊ" ጋር ተዋወቀ።
መጽሐፍቱን ያመጣለት አዲስአበባ የሚኖር አጎቱ ሲሆን፣ በተለይ የአፈወርቅን ልብወለድ ታሪክ
ወደደው። ሁለተኛው መጽሐፍ ጥቅሶችና ምክሮች ያሉት የግብረገብ መጽሐፍ ነበር። ብርሀኑ
እነኚህን መጽሐፍት ሲያነብ የ10፣ ግፋ ቢል የ11 ዓመት ልጅ ቢሆን ነው።
249
ጥቋቁር አናብስት
ቤት ሲደርስ እናቱ በጠና ታመዋል። ብርሀኑ ሞቷል ብለው ስለደመደሙ ልባቸው ተሰብሮ፣
በጭንቀት ተዳክመዋል።ብዙም ሳይቆዩ አረፉ።ብርሀኑ ራሱን ለዚህ ሁሉ ጥፋተኛ አድርጎ
ስለቆጠረ፣ ፀፀቱ አሁን ድረስ ይለበልበዋል። ነገር ግን ጠፍቶ መሄዱ አባቱን ጠልቆ ስለተሰማቸው፣
ብርሀኑ የመንግስት ትምህርት ቤት እንዲገባ ተፈቀደለት።አሁን ብርሀኑ ታታሪ አንባቢ ሆነ፤ በተለይ
ታላቅ ወንድሙ የሚያመጣለትን ጋዜጦች በፍቅር ያነብ ጀመር።በዚሁ ወቅት የከበደ ሚካኤል
መጽሐፍት ታትመው መውጣት ጀምረው ነበርና እነኚህ መጽሐፍት ያለመጠን አስደነቁት።
በደንብ ማንበብ ስለሚችል ትምህርቱን ከሁለተኛ ክፍል ጀመረ።አንድ ሁለት ክፍሎችን እንዲያልፍ
ስለተደረገም በአራት ዓመት ውስጥ ስምንተኛ ክፍል ደረሰ።የመጀመሪያ ግጥሙን የፃፈው
የስድስተኛ ክፍል ተማሪ እያለ ነው።ግጥሙ አቶ ብሩ ስለተባለ ጉቦኛ ዳኛ ሲሆን፣በ"የዛሬይቱ
ኢትዮጵያ" ጋዜጣ ላይ ታትሞ ወጥቷል።ግጥሙ መታተሙ ብርሀኑ ላይ ጥልቅ ስሜት
ስለፈጠረበት፣አንዳንድ ሁነቶችን ተመርኩዞ አዘውትሮ መፃፍ ጀመረ።በመጀመሪያ ዓመት በብዛት
የሚጽፈው ግጥሞችን ሲሆን።ግጥሞቹ ማኅበራዊ ጉዳዮችን የሚዳስሱ ነበሩ፤ ስለ ፍቅር መፃፍ
የጀመረው ወደ አዲስ አበባ ከመጣ በኋላ ነው። ከ1940—44 ዓ.ም ድረስ በጎንደር የአንደኛ
ደረጃ ትምህርቱን ሲከታተል ያበረታታው ወይም በአፃፃፍ ተጽእኖ ያሳደረበት አንድም መምህር
የለም። በ1945 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ትምህርቱን እንዲከታተል ነፃ እድል አገኘ።
250
ጥቋቁር አናብስት
የአዲስ አበባ ኑሮው ከድሮው ሲነጻጸር ለብርሀኑ ትልቅ ለውጥ ነበረው። በትምህርት ቤቱ በዋነኛነት
"ሬዲዮ መካኒክስ" አጠና። በቋንቋ ጥሩ ችሎታ ስላለው ኢራናዊው የእንግሊዝኛ መምህሩ
እያበረታታው ጭምር ከእንግሊዝኛ እና ከአውሮፓ ሥነ ጽሑፍ ጋር አስተዋወቀው። ከነዚህም
መሀል ሼክስፒር እና አሌክሳንደር ዱማ በጣም ማረኩት።የብሮንት እህትማማች (የትኛዋን እንደሆነ
ግልጽ አላደረገም)፣ ኤፍ. ስኮት ፊትዝጄራልድ፣ ዲክንስ፣ ፍሉቤር የመሳሰሉትን ጨምሮ ሁሉንም
ቀለል ባለ እንግሊዝኛ የተዘጋጁትን አነበበ። የስፖርት መምህራቸው "ቴክኒ–ኤኮ" የሚል መጽሔት
ማሳተም ሲጀምር ብርሀኑን ለማበረታታት ዋና አዘጋጅ አደረገው። መጽሔቱ በሁለት ቋንቋ
የሚዘጋጅ ስለሆነ፣ ብርሀኑ በአማርኛም በእንግሊዝኛም ይጽፍ ነበር፤ነገር ግን "የእንግሊዝኛው
ጽሑፍ" በመምህራኑ ነው አርትኦት የሚሰራበት። መጽሔቱ ወርሀዊ በመሆኑ ብዙ ጊዜውን
የሚሻማ አልነበረም።ከዚህ በተጨማሪ ለአዲስ ዘመን፣ለየዛሬይቱ ኢትዮጵያ እና ለኤርትራ ድምጽ
ጋዜጣዎች ላይ ይጽፍ ነበር።የኤርትራ ድምጽ የሚታተመው አስመራ ሲሆን፣አዲስ አበባ ውስጥ
ቢሮ አላቸው። በ1947 ማህበራዊ ጉዳዮችን የሚመለከት አንድ አጭር ተውኔት ፃፈ፤ርእሱን
አያስታውሰውም። ተውኔቱ በትምህርት ቤቱ ግቢ ውስጥ ለአንድ ጊዜ ብቻ ታይቶ፤ ተመልካቾች
በጣም ወደዱት። "ይህን ተውኔት የፃፍኩት ያለምንም የድራማ አጻጻፍ እውቀት፣ስሜቴን ብቻ
ተከትዬ ነው"ይላል። በዚህ ተውኔት ላይ አልተወነም፤ ነገር ግን ገና ወደ አዲስ አበባ ሳይመጣ
ጎንደር እያለ የትምህርት ቤቱ ርእሰ መምህር በፃፉት የአማርኛ ተውኔት ላይ ረዳት ተዋናይ ሆኖ
ተውኗል።ከዚህ በተጨማሪ የክፍል ጓደኞቹ ለፍቅረኞቻቸው የፍቅር ግጥም ያስጽፉትና፣እጅ
መንሻ፣ለእያንዳንዱ ግጥም የእንቁላል ጥብስ ይጋበዛል።
ብርሀኑ ከቴክኒክ ትምህርት ቤቱ በ1948 ዓ.ም ተመረቀ። በመጀመሪያ ስራው በዛው የቴክኒክ
ትምህርት ቤት የሰርቶ ማሳያ ክፍል ረዳት ኃላፊ ሆኖ ሰራ።የተመረቀው ከክፍሉ ተማሪዎች አንደኛ
ወጥቶ ስለነበር፣ ነፃ የትምህርት እድል እንደሚያገኝ ጠብቆ ነበር። ነገር ግን እድሉ እሱን ተላልፎ
ከክፍሉ አራተኛ ለወጣው ልጅ ተሰጠ።ብርሀኑ በዚህ በጣም ስለተናደደ፣በትምህርት ቤቱ
የጀመረውን ስራ ጥሎ ወጣ።በወቅቱ ምክትል የትምህርት ሚኒስትር የነበሩት ከበደ ሚካኤል
እንደነበሩ ብርሀኑ ያስታውሳል።ዋና ሚኒስትሩም ለስሙ ያህል ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ይሁኑ እንጂ፣
በተግባር ግን ያው ከበደ ሚካኤል ናቸው። ከበደ ሚካኤል ካቶሊክ ስለነበሩ ነፃ የትምህርት እድሉን
አግኝቶ ወደ ውጭ ሀገር የሄደው ልጅ የተመረጠው ካቶሊክ ስለሆነ መሆን አለበት ብሎ ብርሀኑ
ይጠረጥራል።
251
ጥቋቁር አናብስት
ትምህርት ቤቱን ከለቀቀም በኋላም ቢሆን ለአዲስ ዘመን እና ለየዛሬይቱ ኢትዮጵያ መፃፉን
አላቋረጠም።መጣጥፎቹን የሚልከው በፖስታ ቤት ነበር።ይሁን እንጂ ለጽሑፎቹ ተከፍሎት
ስለማያውቅ የራሱን አድራሻ ማስቀመጥ አስፈላጊ ሆኖ አልታየውም።አንድ ቀን ግን ጽሑፉን ይዞ
በአካል ተገኝቶ ለማስረከብ ወደ የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ቢሮ ሲሄድ ዋና አዘጋጁን አቶ አሃዱ ሳቡሬን
አገኛቸው። በጊዜው አሃዱ ሳቡሬ በጣም ታዋቂ ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ ነበሩ። በወቅቱ በተባበሩት
መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ECA) ዋና ጽህፈት ቤቱ በአዲስ አበባ እየተቋቋመ
ስለነበር፣አዲስ ዘመንን እና ኢትዮጵያን ሔራልድ እለታዊ ጋዜጣዎች ለማድረግ ተፍ ተፍ እየተባለ
ነበር። ስለዚህ አዘጋጆቹ ተሰጥኦ ያላቸውን ጸሐፍትን በማፈላለግ ላይ ናቸው። በዚህ መሰረት አሃዱ
ሳቡሬ1ብርሀኑን እያፈላለጉት የነበረ ቢሆንም፣አድራሻውን ጽፎ ስለማያውቅ፣ እሱን
ለማግኘትአዳጋች ሆኖባቸው እንደነበር ነገሩት። በመጨረሻ ተገኝቶ በማስታወቂያ ሚኒስቴር
ከፍተኛ ሪፖርተር ሆኖ እንዲሰራ ጥያቄ ሲቀርብለት ያለምንም ማወላወል ተቀበለ። በ1952 ዓ.ም
ስራውን ሲጀመር የቅጥር ደብዳቤ ወይም የቅጥር ውል እንኳን አልነበረውም።ብርሀኑ በመጀመሪያ
በሁሉም የሐገሪቱ ጋዜጦች ላይ ቢጽፍም በኋላ ጽሑፎቹ በየዛሬይቱ ኢትዮጵያ ላይ ብቻ ተወሰኑ።
በዚህ መሰረት "መሞነጫጨር የሙሉ ጊዜው ስራው" ሆነ።የስራው ሃላፊነት በሚጠይቀው መልኩ
ነፃ አስተያየቶችን፣ትርጉሞችን እና ሪፖርታዥ መስራት ቀጠለ።ወርሃዊ ደሞዙ 347 ብር ሲሆን
በካርታ ስራና ጂኦግራፊ ተቋም ያንኑ ያህልነበር የሚያገኘው።ብርሀኑ የሙሉ ጊዜጸሐፊ ሲሆን ደርቦ
ጠገግ ያሉ የሥነ ጽሑፍስራዎችንም መፃፍ ጀመረ።በደቡብ አፍሪካው የሻርፕቪል እልቂት አነሳሽነት
የከተባቸው ተከታታይ መጣጥፎች በኋላ በሁለተኛው መጽሀፉ "ድል ከሞት በኋላ" በሚል ርዕስ
ሁለተኛ መጽሐፉ ታተመ።ነገር ግን ይህ ተከታታይ ታሪክ ተጽፎ ከማለቁ በፊት ብርሀኑ "የእንባ
ደብዳቤዎች" የሚል መጽሀፍ ጽፏል።ርእሱ የተገኘው መጽሀፉ ውስጥ ከተካተቱ ሁለት ደብዳቤዎች
ነው። ይህ አሳዛኝ ታሪክ ስለ አንዲት ሴት ያወራል። ሴቲቱ ባለትዳርና የልጆች እናት ስትሆን፣
ትዳሯን በትና አንዱን "ሽቅርቅር" ተከትላ አዲስአበባ ትመጣለች። ፍቅራቸው ካለቀ በኋላ ጥሏት
እብስ ሲል ርካሽ ሴተኛ አዳሪ ሆና በስቃይ ኖራ በስቃይ ትሞታለች።ይህ መጽሀፍ በ3,000
ቅጂዎች ታትሞ ቀስ በቀስ ተሽጦ አለቀ። በጊዜው የመጽሀፍት ቅኝት የሚሰራ አልነበረም፤ስለዚህ
ብርሀኑ አንባብያን ስለ መጽሀፉ ያላቸውን አስተያየት የሚያውቅበት መንገድ አልነበረውም። ነገር
252
ጥቋቁር አናብስት
ቀጣይ መጽሀፉ "የበደል ፍፃሜ" በ1956 ዓ.ም ታተመ። ይህም መጽሐፍ እንደ "የእንባ
ደብዳቤዎች" ሁሉ መነሻው "አስደንጋጩ የሽርሙጥና ሕይወት" ነው።ብርሀኑ በተማሪነት ዘመኑ
በቀይ መብራት ወደተንቆጠቆጠችው ውቤ በረሀ ብቅ ይል ነበር። ሴቶቹ ወጣት እና ቆንጆ እያሉ
ፈላጊያቸው ብዙ ቢሆንም ካረጁ በኋላ ምን ይውጣቸው ይሆን ብሎ ይጨነቃል።እራሱም
በወጣትነታቸው ቢደሰትባቸውም፣የሕይወታቸው መጨረሻ ያሳዝነዋል።በቃለመጠይቃችን ወቅት
እንኳን አንዳንዶቹን በመንገድ ላይ ያያቸው ነበር፤ከመሃከላቸው ተጠቅመው እንደጣሉት እቃ
ያለቁ፣የጨረጨሱ ብሎም “ነካ ያደረጋቸው” የሚመስሉ ነበሩባቸው።
"አማኑኤል ደርሶ መልስ" የሚለው ቀጣይ መጽሐፉም በተመሳሳይ የታሪክ ጭብጥ፣ በተመሳሳይ
ዓመት ታተመ።የሴተኛአዳሪነት ሕይወት2 በሁለት ምክንያቶች በብርቱ ያሳስበዋል፦ አንድም በዚህ
የሕይወት መስመር የሚጓዙ ሴቶች ያሳዝኑታል፤ሁለትም ከለመደውና ከሚወደው የቤተሰብ
ሕይወት ጋር ሲያወዳድረው አፉን በእጁ ያስጭነዋል። እድገቱ በጎንደር በተለመደው ዐይነት
የቤተሰብ ስርአት ውስጥ ሲሆን ከዘመዶቹ መሀል በፍቺ የተለያየ አንድ እንኳን አያስታውስም። እሱ
ራሱ ጥሩ የትዳር ሕይወት ተደግሶ እየጠበቀው ነው። ብርሀኑ እና የሺ ፍስሐ የተገናኙት ሁለቱም
ለ"Voice of Ethiopia" በሚሰሩበት ወቅት ሲሆን ፤እሷ ለእንግሊዝኛው ዴስክ ስትሰራ
ተጫጩና በ1958 ዓ.ም ተጋቡ። ጥንዶቹ ሁለት ወንድና አንድ ሴት ልጅ ሲያፈሩ፣ ብርሀኑም
በትዳሩ ደስተኛ ነበር።
የአዲስ ዘመን አዘጋጅነቱን “በ1957 ዓ.ም አካባቢ” እንደተረከበ ሐገር አቀፍ የኢትዮጵያ ቁንጅና
ውድድር እየተዘጋጀ ነበር። በተመሳሳይ ወቅት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የተማሪዎች እንቅስቃሴ
እየተቀጣጠለ ነው። ብርሀኑ እና ያዕቆብ ወልደማርያምን የመሳሰሉ ሌሎች ጋዜጠኞች የቁንጅናው
ውድድር የሀገሪቱ አንገብጋቢ ጉዳይ እንዳልሆነ ይልቁንም ትኩረት የሚሹ ሌሎች ችግሮች እንዳሉ
በማስተጋባት ውድድሩን ተቃወሙ።ቢሆንም "ብሔራዊ አነሳሽ ኮሚቴ" ተቋቁሞ የንጉሱን ድጋፍ
አግኝቶ ሁሉም ጋዜጦች ለሁሉም እጩ ተወዳዳሪዎች እናለውድድሩ ድጋፍ ለሚያደርጉ ድርጅቶች
የፊት ገጽ ሽፋን እንዲሰጧቸው ታዘዙ። ብርሀኑ ይህንን ትእዛዝ ተላልፎየቁንጅና ውድድሩን
የሚመለከት ዘገባ በገጽ 3 ላይ አሰፈረ። የአነሳሽ ኮሚቴው ሊቀመንበር አቶ ተገኝ ይህንን ይዘው
ለማስታወቂያ ሚኒስትሩ ዶክተር ምናሴ ሐይሌ ስሞታ አቀረቡ።በዚሁ ወቅት ብርሀኑ በደቡብ
አፍሪካ ስለሚደረገው የእንቁራሪቶች የቁንጅና ውድድር (የዝላይ ሳይሆን) ዜና ደረሰው። ይህ ዜና
በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የፊት ገጽ ላይ ወጣ ( ብርሀኑ ይህንን ተንኮል ቢጤ አሁን ድረስ በፈገግታ
ያስታውሰዋል)። ይህ ጥፋት የመጨረሻውነበር። በማግስቱ ብርሀኑ ከጋዜጣው አዘጋጅነት መነሳቱን
የሚገልጽ ደብዳቤ ደረሰው፤ይሁን እንጂ ደሞዙን አልተከለከለም። የቁንጅና ውድድሩ እስኪጠናቀቅ
ለአራት ወር ያህል፣ ስራፈት ሆነ ቆየ።
ብርሀኑ ዳግም ከስራ የታገደው በ1959 ዓ.ም ነበር። እገዳው አሁንም ደሞዙን ባይጨምርም
ለስምንት ዓመትያለ ስራ ቆይቷል። አሁን ደግሞ ምክንያታቸው ለአቤ ጉበኛ የረዥም ልብወለድ
መጽሀፍ "አንድ ለናቱ" የሰራው የመጽሀፍ ቅኝት ነበር። አቤ በመጽሀፉ ዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስ
ዘራቸው ከንጉሥ ሰለሞን እና ከንግስት ሳባ እንደሚመዘዝ፣ እውነትም የይሁዳ አንበሳ እና የንጉስ
ዘር መሆናቸውን በማጋነን አቀንቅኗል።መጽሐፉን የቃኘው ሰው ቴዎድሮስ ለእንደዚህ ዐይነት ርካሽ
ነገር እንደማይጨነቅ በመግለጽ አቤን ያብጠለጥላል፤ዋናው ጉዳይ የንጉስ ዘር አለው ወይስ የለውም
የሚለው ሳይሆን ጥሩ ንጉሰ ነገስት መሆን አለመሆኑ ነው ብሎ ይጨምራል። አጼ ኃይለሥላሴ
ይህንን ባነበቡ ጊዜ በጣም ተቆጡ። ብርሃኑ ይህንን ቅኝት አይቶታል፤ነገር ግን ሕገመንግሥታዊ
አንደምታውን በቅጡ አልተረዳውም።እንደ ህገመንግስቱ ከሆነ አንድ ንጉሰነገስት ዝርያውን ከንጉሥ
ሰለሞን እና ከንግስት ሳባ መምዘዝ አለበት።ወዲያውኑ ይህንን ጉዳይ የሚመረምር ኮሚቴ
ተቋቋመ።አንዳንድ የኮሚቴው አባላት ብርሀኑ ፍርድ ቤት ቀርቦ ሊፈረድበት ይገባል እስከማለት
254
ጥቋቁር አናብስት
255
ጥቋቁር አናብስት
"የቴዎድሮስ እምባ" በ1958 ዓ.ም ታትሞ ጥሩ ተቀባይነት አገኘ። መጽሀፉ በሶስት ጋዜጣዎች
(አዲስ ዘመን፣ የዛሬይቱ ኢትዮጵያ፣ የኢትዮጵያ ድምጽ) ቅኝት እንደተሰራለት ደራሲው
ያስታውሳል።ኢትዮጵያውያን ሀገራዊ ጀግና በጠማቸው ወቅት ነበር ይህ መጽሐፍ የወጣው።
ቴዎድሮስ ይህንን ጥማት ለማርካት ይቻለዋል። ቴዎድሮስ ወደሞተበት መቅደላ ዘመቻ ለማድረግ
30 ሰዎች ያሉት ቡድን መንቀሳቀስ ጀመረ። አቤ ጉበኛ ስለ ቴዎድሮስ የፃፈው ትልቅ መጽሐፍም
በዚሁ ጊዜ ወጣ።4 የወቅቱ አየርም የብርሀኑ መጽሀፍ ጥሩ ምላሽ እንዲያገኝ ረድቷል።የመጽሐፉ
5,000 ቅጂዎች ወዲያውኑ ተሸጡ። በሃያስያን ዘንድም ጥሩ ተቀባይነት አግኝቷል። ከልጅነቱ
ጀምሮ የቴዎድሮስ ታሪክ እንደሚማርከው፣ አሁንም ድረስ ጀግናው እንደሆነ ብርሀኑ ነግሮኛል።
“ከጎንደር እንደመምጣቴ፣ ጀግናው የኔም ነው” የሚለው ብርሀኑ ይህንን ልቦለድ የፃፈው ስለ
ቴዎድሮስ የነበረውን የተጣመሙ አመለካከቶች ለማቃናት ነው። መኮንን እንዳልካቸው "ጣይቱ
ብጡል" በተሰኘ ተውኔታቸው፣ ቴዎድሮስን የሳሉበት መንገድ አናዶት ነበር።ታዋቂው የታሪክ
ጸሐፊ ተክለፃድቅ መኩሪያ ራሳቸው፣ ቴዎድሮስን ጨካኝ እና ቁጡ አድርገው ቀርፀውታል ይላል።
የደራሲ ስራ ቀላል አይደለም ይላል ብርሀኑ። የሳንሱር ክፍሉ እንዲቀበለው ስራውን ማመቻቸት፣
አሳታሚ መፈለግ እንዲሁም ለህትመቱ በቅድሚያ መክፈል ይጠበቅበታል። ከዚያ ቅጂዎቹን ይዞ
በየመጽሐፍት መደብሩ እየዞሩ ማከፋፈል፣ ሲሸጡም በሽያጩ ልክ ገንዘቡን መሰብሰብ የራሱ ስራ
ነው።
256
ጥቋቁር አናብስት
ስራ ከለቀቀ በኋላ ራሱን በተለያዩ ጉዳዮች ለመጥመድ ሞክሮ ከ1960–61 አፄ ዮሐንስ አራተኛ
የተሰዉበትን መተማን፣ ሱዳን ድንበር ድረስ ሄዶ ጎበኘ። ወንድሞቹ በዚያ ትልቅ የእርሻ መሬት
ስለነበራቸው ከፍለው ሰጥተውት እርሻ ቢጤ ቢሞክርም የግብርና ዝንባሌ ስለሌለው፣ ከአራት
ወራት በኋላ ወደ አዲስአበባ ተመለሰ።
በዚህ "ረዥም እረፍት" የከወነው ጥቂት ነበር።ብዙ ጊዜውን እንዲሁ በዋዛ በፈዛዛ አባክኗል፤
የፃፈው በጣም ጥቂት ከመሆኑም በላይ፣ አብዝቶ መጠጣት ጀመረ (ይህ ልምድ እስከ እለተሞቱ
ቀጥሏል)። ነገር ግን ምሬት አልተሰማውም፤እንዲያውም ምንም ሳይሰራ ሙሉ ደሞዙ
ስለሚከፈለው ቅሬታ አልነበረውም።ብዙ መፃፍ በቻለ ነበር፤ነገር ግን “ግራ ሳይገባው አልቀረም”፤
ስለዚህ ምንም መፃፍ አልቻለም።
****
በነዚህ ስራ በፈታባቸው ዓመታት መጨረሻ አካባቢ አንድ ክስተት ትኩረቱን ሳበውና፣ ዳግም
ሀገሪቱ ውስጥ በዋነኛነት ምን እየተካሄደ እንደሆነ እንዲያጤን አሳሰበው። ይህ ክስተት የ1965–
66 ቱ ድርቅ እና ረሀብ ነው።የረሀቡ ሰለባዎች መናገሻ እና ለገዳዲ ላይ ቢኮለኮሉም ወደ አዲስ
አበባ እንዲገቡ ግን አልተፈቀደላቸውም። ስለዚህ እሱ ሊጎበኛቸው ሄደ፤ ከጎበኛቸው በኋላ ብዕሩን
አንስቶ ድህረ–አብዮት ለጻፋቸው ሶስት ጥንድ ልብወለዶች ማስታወሻ መውሰድ ጀመረ። በጊዜው
መጽሀፉ የጎላ ፖለቲካዊ አንደምታ ይኖረዋል ብሎ አላቀደም ወይም አላሰበም።በ1965 ዓ.ም
ለመጽሀፉ ማስታወሻ እየወሰደ ቅርፁን ቢያወጣም፣ገና በስርአቱ ዝርዝሩን ቁጭ ብሎ መፃፉን
አልጀመረም። በመጀመሪያ መጽሐፉን ሲያዋቅር ያሰበው ስለ ረሀቡ ብቻ እንደነበር ይናገራል።
ስለዚህ ስለ መሬት ባለቤትነት ስርአት፣ስለ መደብ ልዩነት እና ለረሀቡ እንደ መንስኤ ሊሆኑ
ስለሚችሉ ማህበራዊ ቀውሶች የመሳሰሉ ጉዶዮችን ጭራሽ አላሰበም።ቢያስብ እንኳን ያን መሰል
ጉዳዮችን የያዘ መጽሐፍ በድሮው ስርአት ሊታተም አይችልም ነበር።በጊዜው አንድ ደራሲ የፃፈው
ነገር መታተም እንዲችል፣ ሳንሱሩን ማለፍ እንደሚችል የግድ መጨነቅ ነበረበት። ነገር ግን ስለ
ማህበራዊ ችግሮች ያውቃል፤በ1959 ዓ.ም ልክ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዋና አዘጋጅነቱ ከመነሳቱ
በፊት፣ ወደ ሞስኮ5 በተጓዘበት ወቅት የካርል ማርክስን "ካፒታል" ስላነበበ ስለ መደብ ልዩነት
በጥቂቱ ያውቃል፤ ቢሆንም ከአብዮቱ በፊት ይህንን አንስቶ መፃፍ አይችልም።
በሰኔ 1966 ብርሀኑ ወደ ወሎ ለመጓዝ ሲነሳ፣ አብዮቱ መፋፋም ጀምሯል። ወሎ በተለይ በድርቅና
በረሐብ ክፉኛ ተመቶ ነበር፤ሐይቅ እና ዙሪያውን ከጎበኘ በኋላ ከሐይቅ የአንድ ቀን መንገድ በኋላ
ወደምትገኘው ወርጠያ ተጉዞ በገበሬዎች መንደር ለሁለት ወራት ቆየ።በቆይታው ከአካባቢው
257
ጥቋቁር አናብስት
ብርሀኑ በጊዜው በኢትዮጵያ 40 ዐይነት የጭሰኛ ስርአቶች ነበሩ ይላል። ነገር ግን በወሎ የነበረው
ስርአት ከተቀረው የሀገሩ ስርአት ይለያል።ከአልጋወራሹ ጀምሮ፣ የወሎ ገዢ እና ሌሎች ሹመኞች፣
ከትንሽ እስከ ትልቅ፣ የገበሬውን ምርት በመቀራመት በክፉ የሚታወቁ ናቸው። ለሁሉም ገበሬዎች
ስርአቱ ክፉ ቢሆንም፣ "ከደቡብ ኢትዮጵያ ይልቅ ወሎዎች ላይ ይብሳል"።በደቡብ ጭሰኛው
"የሚከፍለው ቁርጥ ብሎ" ይታወቃል፤በወሎ ግን ልክ የቤተሰብ ንብረት ይመስል ሁሉም እየመጣ
የአቅሙን ያነሳል።መሬቱ ሁሉ በአልጋወራሹ፣በሌሎች የንጉሳዊ ቤተሰቡ አባላት ወይም በአካባቢው
ሹመኞች እጅ ነው።ብርሀኑ ሁሌም የንጉሡ ተቃዋሚ ቢሆንም የንጉሡ ቤተሰቦቻቸው ግን ግድ
አይሰጡትም ነበር።ስለ ኢትዮጵያ የመሬት ይዞታ ከተለያዩ መጽሀፍት የቃረመው እውቀት አለው።
ለምሳሌ በጽህፈት ሚኒስትሩ ወልደጊዮርጊስ ወልደዮሐንስ ተጽፎ በ1935 ዓ.ም የታተመው
"የመሬት ስሪት በኢትዮጵያ" እና በማህተመሥላሴ ወልደመስቀል ተጽፎበ1942 ዓ.ም የታተመው
"ዝክረ–ነገር"ይገኙበታል። ወሎ ሄዶ የነበረውን ሁኔታ በአይኑ ሲመለከት፤የገበሬዎቹን የጭሰኞቹን
ችግር ከአፋቸው ሲሰማ፣ያነበበው ሁሉ ግልጽ እና ልዩ ሆኖ ታየው። ከሁሉም የበለጠውን ጉዳት
ያደረሱት የመንደሩ ተራ ሹመኞች (የዋና ሹመኞቹ እንደራሴዎች እና የመንደሩ መሪዎች)ናቸው
ብሎ ያምናል።ገበሬዎቹ የመከላከል አቅም የላቸውም።በጊዜው ምንም የፖለቲካ ንቃትም
አልነበራቸውም።
በዚህ ወቅት ብርሀኑ የሰበሰበውን መረጃና ጭብጥ በምን ዐይነት መንፈስ መጠቀም እንዳለበት
እያወጣ እና እያወረደ በራሱ በራሱ ጭንቅላት ውስጥ መጽሐፉ ኋላ ላይ የሚኖረው ቅርጽ አልቆ
ሳይታየው በፊት አብዮቱ አዲስ የአመለካከት ፈር አመላከተው። በህዳር 1966 ዓ.ምየአዲስ ዘመን
ጋዜጣ ዋና አዘጋጅነቱ ተመልሶለት ዳግም ተቆናጠጠው። አሁን በቢሮው እስከ ምሽቱ 5 ሰአት
ድረስ እየቆየ ስለሚሰራ ለመፃፍ ምንም ጊዜ አልነበረውም። ለጊዜው የመጽሐፉን ነገር ወደ ጎን
አድርጎ ቢተወውም፣ ስለመጽሀፉ ማሰላሰሉን ግን አላቋረጠም። ነገር ግን በ1970 ዓ.ም ብርሀኑ
ለሶስተኛ ጊዜ ከአዲስ ዘመን አዘጋጅነቱ ተነሳ። “ምክንያቱ ፖለቲካ ሳይሆን አይቀርም።” ብርሀኑ እና
ጌታቸው አብዲ( በቃለመጠይቃችን ወቅት የብሔራዊ ቲያትር ዋና ስራ አስኪያጅ የነበረ)
258
ጥቋቁር አናብስት
259
ጥቋቁር አናብስት
ገሠሠ አዘጋጅነት በዚያው ዓመት መጨረሻ በብሔራዊ ቲያትር ቀረበ። በጣም ስኬታማ እና ጥሩ
ተቀባይነት አግኝቶ ለሁለት ወር ያህል ታየ።
በተመሳሳይ ወቅት፣ የ"ማዕበል"ን ሁለተኛ ቅጽ እየፃፈ ነበር። ይህንን መጽሐፍ በሚጽፍበት ወቅት
ስለ ማህበራዊ እና አብዮታዊ ችግሮች የነበረው ንቃተ ህሊና እየጎለበተ መጣ። ነገር ግን፣ ይላል
ብርሀኑ “አቢዮት እንዴት መካሄድ እንዳለበት ወይም እንደሚኖርበት የራሴ አመለካከት ነበረኝ።
በሶሻሊዝም አምናለሁ ግን ኢትዮጵያዊ ሶሻሊዝም ማዳበር አለብን። እዚህም፣ እዚያም ስህተቶች
ተሰርተዋል። ነገር ግን ሶሻሊዝም ብቸኛው መንገድ ነው። ያለ ምንም ምክንያት ቢሆንም ዘጠኝ ወር
መታሰሬ ፀረ–አብዮተኛ ሊያደርገኝ አይችልም።” ለሱ ሶሻሊዝም “ሀይማኖት” ሳይሆን ለማህበራዊ
እድገት መፍትሔ ነው።8
ብርሀኑ በ1975 ዓ.ም "ጣጠኛው ተዋናይ" የሚል ተውኔት ጽፎ በሐገር ፍቅር ቲያትር ቤት
ለመድረክ አበቃ።9 “ከምርጥ ስራዎቼ አንዱ ነው” ይላል በኩራት። በዚህ ተውኔት አዳዲስ የአጻጻፍ
ስልቶችን ሞክሯል። ይህ ስራ በተውኔት ውስጥ ሌላ ተውኔት የያዘ ሲሆን ጭብጡ አንድ ተውኔት
ለማዘጋጀት ያለውን ጣጣ ይዳስሳል።ይህ ደግሞ ልምምዶችን እና ዋናው ተውኔቱን፣ ሁለቱንም
260
ጥቋቁር አናብስት
በቀጣዩ 1977 ዓ.ም ዝነኛውን ተውኔት "አባ ነፍሶ"ንደረሰ። "አባ ነፍሶ" የዝነኛው ጦረኛ
የደጃዝማች ባልቻ የፈረስ ስም ነው። ተውኔቱ በተፃፈበት ዓመት ለመድረክ በቅቶ ለረዥም ጊዜ
ታይቷል(እስከ 1980 ዓ.ም ድረስ መታየቱን ቀጥሎ ነበር)። ከብርሀኑ ተውኔቶች ሁሉ የበለጠ ሆነ።
10
ተውኔቱ ሶስት ሰአት የሚፈጅ ሲሆን ።ሰዎች ወደ ቲያትር ቤቱ ገብተው ተውኔቱን ለመመልከት
ረዥም ሰአት ተሰልፈው ይጠብቁ ነበር። እኔ ግን ብርሀኑ ዘርይሁን እና የተውኔቱ አዘጋጅ በነፃ
ስለጋበዙኝ ከመሰለፍ ድኜአለሁ።
****
በዚህ ወቅት ብርሀኑ አዲስ ልብወለድ ለመፃፍ እየተዘጋጀ ነው። ልብወለዱ የዘመኑን “ማህበራዊ
ችግሮች” ይዳስሳል። መጽሐፉን ገና መፃፍ እየጀመረ ነበር፣ ነገር ግን ወደ ጎጃም ሄዶ ለሶስት ወር
ያህል የልብወለዱን ዳራ እና የማህበረሰቡን ዘዬ ማጥናት ያስፈልገዋል።
****
261
ጥቋቁር አናብስት
ከሆስፒታል ወጥቶ ብዙም ሳይቆይ ድጋሚ ታመመና ተመልሶ ገባ። አርብ ሚያዝያ 16 1979
ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑትን ዶክተር ብርሀኑ አበበን አግኝቼያቸው ብርሀኑን
ከአንድ ቀን በፊት እንደጠየቁት ነገሩኝ። በጊዜው በጣም ከመዳከሙ የተነሳ መናገር እንኳን
ስለማይችልና ብዙ ቀን ይቆያል ብለው አልገመቱም።በቅርቡ እጠይቀዋለሁ ብዬ ባስብም፣ ብርሀኑ
በዚያው ምሽት(ምናልባትም በጉበት ካንሰር) ከዚህ አለም በሞት ተለየ።በማግስቱ ቅዳሜ ሚያዝያ
17 ቀን 1979 ዓም በሥላሴ ቤተክርስቲያን ተቀበረ።በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ የፖለቲካ
ባለሥልጣኖች፣ ደራሲዎች(ሊቀመንበር ሆኖ ባገለገለበት የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ማህበር እና ዋና
ጸሐፊ ሆኖ ባገለገለበት የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር አባል የሆኑ)፣ቤተሰቦቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹን
ጨምሮ ብዙ ህዝብ ተገኝቷል። "The Ethiopian Herald" በሚያዝያ 18 ቀን 1979 ዓ.ም
እትሙ በጎንደር ከተማ በ1926 ዓ.ም ተወልዶ በ55 ዓመቱ መሞቱን ጽፏል።እነኚህ ቁጥሮች
ብርሀኑ ከነገረኝ ጋር አይጣጣሙም። እሱ በነገረኝ መሰረት ሲሞት 53 ወይም 54 ዓመት ቢሆነው
ነው።
***
ማስታወሻዎች
262
ጥቋቁር አናብስት
3) ሌላው ደራሲና በኃይለሥላሴ ዘመን ሚኒስትር የነበሩት ሐዲስ አለማየሁ ኃይለሥላሴ ተራው
ህዝብ የፖለቲካ ፍላጎት እንዲያድርበት አይፈልጉ እንደነበር እና ይህንን የሚቆጣጠሩላቸው
የራሳቸው ፖለቲከኞች እንደነበሯቸው አጫውተውኛል። ይህ ሁኔታ የ66ቱ አብዮተኞች በቀላሉ
ሊሞሉት ያስቻላቸውን ክፍተት መፍጠሩን ጨምረው ነግረውኛል።
5) ወደዚያ የሄደው የአፍሮ–እስያዊ ደራሲዎች ማህበርን ስብሰባ ለመካፈል ነው። ከዚያ ቀደም
ብሎ ለመንግስት የስራ ጉዳይ ወደ ግሪክ፣ ዩጎስላቪያ፣ ጀርመን እናአሜሪካ ተጉዟል ፤ በዚያውም
መጠነኛ የዘገባ ስራ ሰርቷል።
6) ሳንሱረኞቹ ብዙ ለውጥ ማድረግ ፈልገው ነበር ፤ ነገር ግን ከዚያ በፊት ረቂቁ ለማስታወቂያ
ሚኒስትሩ ግርማ ይልማ ቀረበ። እርሳቸው ግን ሳንሱረኞቹ መለወጥ ወይም ማስወገድ የፈለጉትን
አብዛኛውን ነገር እንዳለ አሳለፉት። የተደረገው ንዑስ የቃላት ለውጥ ብቻ ነው።
7)ቃሉ የመጣው ከግሪኩ "Moreshi" ሲሆን ትርጉሙም “የሚስጥር ቃል” ማለት ነው።
በኢትዮጵያ ገጠራማ አካባቢዎች አንድ ሰው ከቤቱ ወጥቶ ካመሸ፣ ዘመድ ወዳጆቹ ሲፈልጉት
ወይም ምን እንደደረሰበት ለማወቅ ሲሞክሩ፣ በእውነተኛ ስሙ አይጠሩትም። ምክንያቱም ጠላቶቹ
አውቀው ጉዳት እንዳያደርሱበት በሚስጥር ስሙወይም "ሞረሽ" ይጠሩታል።
10) " ሀብታም አላደረገኝም። ነገር ግን ለረጅም ጊዜ ሕክምና ወደ እንግሊዝ ሀገር የምትሄደውን
ሚስቴን ወጪ ለመሸፈን ረድቶኛል" ይላል።
264
ጥቋቁር አናብስት
ስብሐትገብረእግዚአብሔር
"ሊታተም የማይችለው" የደራሲዎች "ደራሲ" የበአሉ ግርማ
መጽሐፍትን ካወቅኳቸውና ካነበብኳቸው በኋላ ብዙ ዘግይቼ፣
ከነዚህ መጽሐፍቱ መሐል"ደራሲው" በተሰኘው ውስጥ፣ በአሉ
በሌሎች ልብወለዶቹ ላይ ከተለመደው በላይ አብዝቶ በሕይወት ያለ
አንድን ሰው መሰረት አድርጎ መሳሉን ተረዳሁ። ለደራሲው ሞዴል
የሆነው ሰው፣ በአሉ ምን እየሰራ እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል ፤
በአሉም መጽሐፉን ከማሳተሙ በፊት "ለሞዴሉ" ረቂቁን ደጋግሞ አንብቦለታል። ይህንን ሰው
ማግኘት ፈለግኩ ፤ ቀጥሎ የምታነቡት የዚህ ሰው ምስል ነው። ምንም እንኳን ይህንን ሰው ማግኘት
የፈለግኩት በበአሉ ታሪክ ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የነበረ ቢሆንም፣ ስለሕይወቱ ብዙ
ሲነግረኝ ግን፣ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር በራሱ አስገራሚ ሰው መሆኑን ተረዳሁ። የፃፋቸው
ጥቂት መጽሐፍት እኔ ቃለ መጠይቅ እስካደረግኩለት ጊዜ ባለመታተማቸው፣ እዚህ ለማካተት
የሚያበቃ ጠንካራ መሰረት አልነበረውም።ሆኖም ይህ ቃለ መጠይቅ ከተደረገ በኋላ የአጭር
ልብወለዶች ስብስብ የሆነውን የመጀመሪያ መጽሐፉን "አምስት ስድስት ሰባት"ን አሳተመ። እ.ኤ.አ
በ19901 ወደ ኢትዮጵያ ስመለስ፣ በመጽሐፍት መደብሮች ለሽያጭ የቀረበው ይህ መጽሐፉ ብቻ
ነበር። በዚህ መጽሐፍ ከቀረበው የበአሉ ግርማ የሕይወት ታሪክ ጋር ሲነፃፀር ይህ የስብሀት ምስል
ስብሀት ስለራሱ ባለው አመለካከት፣በአሉ ግርማ ለ"ደራሲው" የተጠቀመበት ህያው ሞዴል እና
የበአሉን መጽሐፍ ያነበቡት ሰዎች በምናባቸው በሚቀርፁት ምስል መሐል ያለውን ልዩነት ፍንትው
አድርጎ ያሳያል።
በኋላ ስብሀት ዘጠኝ ዓመት ሲሆነው፣ በአባቱ መምህርነት "የቄስ ትምህርት ቤት" ገብቶ ግእዝን
መናገር ሳይሆን ማንበብ ብቻተማረ። በተረፈ ግእዝን የሚረዳው፣ አፉን ለፈታበት ትግርኛ ባለው
ቅርበት ነው። እናቱ "ጠንካራ ሠራተኛ"፣ "ረጋ ያሉ" እና "ፍቅር የማይሰስቱ" ናቸው።
በ10 ዓመቱ፣ በታላቅ ወንድሙ እርዳታ፣ ስብሐት ወደ አዲስ አበባ መጣ። ስዊዲሽ ሚስዮን
ትምህርት ቤት ስቬን ሩቢንሰን ርእሰ መምህር እያሉ፣ አንድ ዓመት ጥሩ የአዳሪ ተማሪነት ጊዜ
አሳለፈ። ከዚያም አጎቱ ወደ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት በአዳሪነት እንዲገባ ረድተውት፣ 2ተኛ
ክፍልን መማር ሳያስፈልገው፣ ከ3ተኛ ክፍል ጀምሮ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ድረስ
ተማረ።ይህ ጀዝዊቶች የሚያስተዳድሩት "በጣም ጥሩ የሚባል ትምህርት ቤት" ነበረ።
አስተማሪዎቹ "ቅጥ ያጣ የሥነ ስርአት ቁጥጥር የሚያበዙ " ከመሆኑም በላይ፣ "ፍልስፍናቸው
በፍልስፍና ቃላት የተለወሰ ሥነ ―መለኮት" ሲሆን፣ "ይህንንም ፍልስፍና ብለን እንድንጠራው
ቢያስገድዱንም"፣እንዲሁም "ከተማሪዎች መሀል ሰላዮችን መልምለው የሚሰልሉን መሆኑ
ቢደብረንም" ጎበዝ አስተማሪዎች ነበሩ። ስብሐት አብዛኞቹ የትምህርት ዐይነቶችን ቢወዳቸውም፣
ለጂኦሜትሪ ልዩ ፍቅር ነበረው፤ የአብዛኛዎቹ ትምህርቶች ውጤቱም ጥሩ ናቸው ። “ትምህርት
በጣም ቀላል ነበር” ይላል ስብሐት። ከ10ኛ ክፍል ጀምሮ ሎንግማን በቀላል እንግሊዝኛ
የሚያሳትማቸውን መጽሐፍት እያነበበ ይደሰት ነበር። በትምህርት ቤትቲያትሮች ማዘጋጀት
የተለመደ ሲሆን፣ ስብሐትም 11ደኛ ክፍል ላይ በአንድ ቲያትር ላይ ተሳትፏል። በዛው ዓመት
የትምህርት ቤቱ መጽሔት አዘጋጅ እንዲሆን በእንግሊዝኛ መምህሩ ተመረጠ። በትምህርት ቤቱ
የአማርኛ ትምህርት በሚገባ ካለመሰጠቱም በላይ፣ ስብሐት በግሉ የግርማቸው ተክለሐዋርያትን
"አርአያ" ከ30 ገጽ በላይ አላነበበም ፤ በእርግጥ የከበደ ሚካኤልን "ታሪክና ምሳሌ" አንድ ዙር
ሳይሄድበት አልቀረም። በተጨማሪም ራሳቸው ከበደ ሚካኤል የተረጎሙትን "Beyond
Pardon" (ከይቅርታ በላይ) የተሰኘ ተውኔት ተመልክቷል ። በትምህርት ቤቱ ውስጥ ለአማርኛ
ቋንቋ ከሚሰጠው ዝቅተኛ ግምት የተነሳ፣ ስብሀት በመንገዱ የገጠሙት የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ
ፍሬዎች ብዙም አልማረኩትም ፤ የከበደ ሚካኤል ስራም ቀልቡን አልያዘውም። በአማርኛ ክፍለ
ጊዜ በክፍሉ ከሚነበብ ምንባብ የበለጠ ቦታ ሰጥቶት አያውቅም ነበር። ተማሪዎቹ ጭራሽ ከበደ
ሚካኤልን እንደ ደራሲ እንኳን አይቆጥሯቸውም። በጊዜ ሂደት በእርግጥ የስብሐት አመለካከት
ይቀየራል። በኋላ ላይ ከበደ ሚካኤል በኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ ውስጥ "ጉልህ የታሪክ ድርሻ"
እንዳላቸው ቢገነዘብም “እኔን ግን አሁንም አይማርኩኝም” ይላል። “አንዳንድ ሥራዎቻቸውን
266
ጥቋቁር አናብስት
የአስራ ሁለተኛ ክፍል ፈተናን "ደህና" በሚባል ውጤት ካለፈ በኋላ፣ እዚህም ጀዝዊቶች
በሚያስተዳድሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ገባ። እንደ ስብሐት ግምት ከሆነ፣ በጊዜው 19
ዓመት ይሆነዋል። ያጠናው የመምህርነት ሞያን ሲሆን፣ በተለይ የሰለጠነው "የሁለተኛ ደረጃ
የእንግሊዝኛ ቋንቋ መምህር" ለመሆን ነው። ከአራት ዓመት በኋላ ተመረቀ። በኮሌጅ ቆይታው
ብዙም የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ አላነበበም፤ ያነበባት ትንሿም ብትሆን ማራኪ ሆና አላገኛትም።
የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እያለ፣ የሚወዳቸው ደራሲዎች ሪደር ሀጋርድ፣ ሉዊስ ስቴቨንሰን እና አንቶኒ
ሆፕ የመሳሰሉት ነበሩ። በኮሌጅ ውስጥ "ዶስቶቭስኪ መስኮት ከፈተለት" ― " አለምን፣
ሕይወትን" የሚያሳይ መስኮት! ከዶስቶቭስኪ ሌላ ሶመርሴት ሞም፣ ዞላ፣ ሞፓሳ፣ ቼኮቭ እንዲሁም
ከሁሉ የሚያስበልጠው፣ ይህንን ቃለ መጠይቅ እስካደረግኩለት ጊዜ ድረስ የሚያደንቀው ሌዊስ
ካሮል ምርጫዎቹ ነበሩ። ረዥም እና አጭር ልብወለድ ከሌሎች የሥነ ጽሑፍ ዘውጎች ይልቅ
ይማርኩታል። በኮሌጅ እያለ ኋላራሳቸው ታዋቂ ደራሲያን ከሚሆኑት ተስፋዬ ገሰሰ እና ሰለሞን
ደሬሳ ጋር ሞቅ ያለ ጓደኝነት መስርቷል። ሁሉም "አንድ ባች" ተማሪዎች ከመሆናቸው ባሻገር፣
"ተመሳሳይ መጽሀፍ ማንበብ የሚያዘወትሩ"፣ "ውቤ በረሀ ወረድ ብለው በሕብረት የሚዝናኑ"፣
ደግሞ ስለ "ህዋ፣ እግዚአብሔር፣ እጣ ፈንታ፣ ደግነት፣ ክፋት " ሳያቋርጡ፣ ሳይሰለቹ የሚወያዩ
ነበሩ።
267
ጥቋቁር አናብስት
ኮሌጅ ላይ ሌላ ቀልቡን የሳበው በሩስያዊው ሚስተር ሶሎዱሂን " ህያው እየሆነ" በማራኪ
አቀራረብ ይማሩት የነበረው ጥንታዊ ታሪክ ነበር። በተረፈ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት
ስለማያምንና ስለማይፈልግ፣ኮሌጅ ለሱ "በጣም ቀላል" ሆኖለት አልፏል።
ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ በአስፋ ወሰን ትምህርት ቤት ለሁለት ዓመት እንግሊዝኛ ካስተማረ በኋላ
ተሰላቸ። እንደ እድል ሆኖ በዩኔስኮ በኩል የፍልስፍና እና የሶሲዮሎጂ ትምህርት ነጻ እድል አግኝቶ
ወደ ፈረንሳይ አመራ። በኤክስ―ኤን―ፕሮቫንስ ለ22 ወራት ቆየ። ስብሐት ከፈረንሳይ ተመልሶ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ የዶክተር ክላውድ ሰምነር ረዳት ሆኖ ሊሰራ ተስማምቷል።
ሰምነርሲልኩትም ይህንኑ አስበው ነበር። ሰምነር እነ ስብሀትን በኮሌጅ ለአራት ዓመት ፍልስፍና
ወይም "ፍልስፍና ነው ብለው ያሰቡትን" አስተምረዋል። በስብሀት አስተሳሰብ ግን "ያ ፍልስፍና
አልነበረም"! "በፍልስፍና መመራመር፣ መጠየቅ ትጀምራለህ። ምን ዐይነት መልስ እንደምታገኝ ግን
አታውቅም። ነገሩ የሀሳብ ጉዞ ነው። ነገር ግን እኛ በተማርነው ፍልስፍና የጥያቄዎቹ መልሶች
አስቀድመው ይታወቃሉ፤ ክርክሮቹም ቀድሞ የሚታወቀውን ውጤት እንዲያስገኙ ተብለው
የሚቀናበሩ ናቸው። ልክ የማርክሲዝም ፍልስፍና ከሚሉት ጋር አንድ ነው። መልሶቹን አስቀድመህ
ታውቃለህ ፤ አመክንዮውም ከአንተ መልስ ጋር እንዲገጥም ታረገዋለህ።እንደዚያ አድርገህ ነው
የምታወናብደው።"
268
ጥቋቁር አናብስት
ስብሐት ከሁለት ሳምንት በኋላ ፍልስፍና እና ሶሲዮሎጂን አይናችሁ ላፈር ብሎ፣ልብወለድ መፃፉን
ተያያዘው። ይህ "ሌቱም ዐይነጋልኝ" የተሰኘ ልብወለዱ፣ በአዲስ አበባ የውቤ በረሀ፣ በቀይ
መብራት ቀጠናን፣ የማታ ሕይወት ይዳስሳል። ርእሱም ከአንድ የአማርኛመጽሀፍ የተወሰደነው።
ይህንን ልብወለዱን በእንግሊዝኛ 65 ገጽ ያህል የፃፈው በሰሜን አሜሪካ እያለ ነበር። ነገር ግን
"በባእድ ቋንቋ የትርጓሜዎችን ረቂቅ ልዩነት ማጉላትና፣ ለዛውን ጠብቆ መፃፍ ስለማይቻል"
ፈረንሳይ ውስጥ እንደ አዲስ በአማርኛ ይጽፈው ጀመረ። የውቤ በረሀን ሕይወት
"እንደወረደ―ሳያሞግስም፣ ሳይነቅፍም" ፃፈ። "በአዲስ አበባ በጊዜው የነበረውን የማታ ሕይወት
እውነተኛ ምስል አቀረበ"። ይህ መጽሀፍ እስከአሁን አልታተመም፤“በዚህ የንቃት ደረጃችን
ሊታተምም አይችልም ” ይላል ስብሐት ጨምሮ። በፈረንሳይ ትምህርቱን ባይከታተልም፣ በነፃ
የትምህርት እድሉ ሁለት ዓመት ቆየ።
269
ጥቋቁር አናብስት
መነን ላይ ለሁለት ዓመት ከሰራ በኋላ የንግድ ችሎታ ከነበረው ደረጄ ደሬሳ ጋር በመሆን የህዝብ
ግንኙነት ድርጅት አቋቋሙ። ደረጀ ከድርጅቱ የንግድ ስራ ጉዳይ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን
ሲቆጣጠርስብሐት ደግሞ የድርጅቱን ሁለት የሕትመት ውጤቶች ይከታተላል። የመጀመሪያው
መጽሔት ከኢጣሊያዊው ኦስካር ራምፕተን የተረከቡትና በየሶስት ወሩ የሚታተመው
እንግሊዝኛው "ኢትዮጵያ ሚረር" ሲሆን ሁለተኛው በየወሩ የሚታተመው የአማርኛው መነን
ነበር። ደረጄ የሰለሞን ደሬሳ ታናሽ ወንድም ሲሆን ፣ በሐይለስላሴ ጊዜ የገንዘብ ሚኒስትር የነበሩት
ይልማ ደሬሳ ደግሞ አጎታቸው ናቸው። ስብሀት በዚህ ድርጅት ውስጥ ለስድስት ወይም ሰባት
ዓመታት (ቀኖችን በጉልህ አያስታውስም)ከሰራ በኋላ ድርጀቱበአብዮታዊው መንግሥት ትእዛዝ
ተዘጋ።3
የህዝብ ግንኙነት ድርጅቱን ከመሰረቱ ከሁለት ዓመት በኋላ፣ ስብሐት በደረጄ ደሬሳ በኩል ግብዣ
ላይ የተዋወቃትን የአቶ ይልማ ደሬሳን ልጅ፣ ሐና ይልማን አገባ። “በጣም ቆንጆ ነበረች” ይላል
ስብሐት “ገና እንዳየኋት ነው የወደድኳት”። ቤተሰቦቿ ስብሐትን ለመቀበል ብዙ ዓመታት
ወስዶባቸዋል። አማችነቱን በመጨረሻ ሲቀበሉ፣ስብሐትና ሐና ተጋቡ። ከሁለት ዓመት በኋላ
ብቸኛ ልጃቸውን እያሱን ወለዱ።
ጎልማሳ ጉዳዩ የተለየ ነው፤ በግለሰቡና በማህበረሰቡ መካከል ያለው ግንኙነት ነው ይበልጥ
የሚያስጨንቅህ "ከዚህም ባሻገር ልጆች፣ሥነ ጥበብና ምንነቱ― "በተለይ በቃላት የሚገለጽ
ጥበብ" ያስደስቱታል። በሕይወቱ ውበትን ተመልክቷል ፤ “መኖር የሚያስደስት ነገር ነው” ይላል፤
“መኖር አይጠገብም ” ይላል ጨምሮ። "በጣም እድለኛ ነኝ" ብሎ ከማሰቡም በላይ “
በእግዚአብሔር ባምን ኖሮ ነገሮችን ሁሉ በምክንያት ሰራው ብዬ አስብ ነበር።”―ነገር ግን በተለይ
ዶስቶቭስኪን ካነበበ በኋላ በፈጣሪ እምነቱን እያጣ መጣ፤ የዶስቶቭስኪ በእግዚአብሔር የማያምኑ
ገፀ ባህሪያት ከሚያምኑት ይልቅ አሳማኝ ነበሩ። በሕይወቱ ወደኋላ ተመልክቶ፣ ሊለውጠው
የሚፈልገው አንዳች ነገር የለም። በወላጆቹ፣ በትምህርቱ፣ በስራው፣ በሀና፣ በሁሉም ደስተኛ ነው።
ሐና “ውበትን፣ ደግነትን፣ ሩህሩህነትን፣ መልካምነትን ” አጣምራ የያዘች ሴት ነበረች። “የሷን ያህል
ጥሩ ሰው መፈለግም እችላለሁ ብዬ አላስብም ” ካለ በኋላ “በሳል ያደረገችኝ እሷ ነበረች” ብሎ
ይጨምራል። ኢያሱ ገና የሶስት ዓመት ተኩል ልጅ እያለ፣ሐና እና ደረጄ ተከታትለው ሀገር ጥለው
በመሰደዳቸው እንኳን ምንም ቅያሜ የተሰማው አይመስልም። ቆየት ብሎ ስብሐት ከሌላ ሴት ጋር
ግንኙነት ጀመረ።
የህዝብ ግንኙነት ድርጅቱ ከመዘጋቱ በፊት፣ ታዋቂው ተዋናይ ደበበ እሸቱ ለሚያዘጋጀውና በየወሩ
ለሚታተመው ቁምነገር መጽሔት በትርፍ ሰአት እንዲያግዘው ሲጠይቀው ስብሐት ደስተኛ ነበር።
ስለዚህ የደረጄ እና የስብሐት ድርጅት ሲዘጋ፣ ምንም እንኳንየሙሉ ጊዜ ስራ ባይሆንም ከደበበ ጋር
ከአንድ ዓመት በላይ ሰራ። ደበበ እሸቱ ጋር መስራቱን ወዶት ነበር፤"ምርጥ አለቃና" ፤“የሚሰጡትን
ገንቢ አስተያየቶች ሁሉ የሚቀበል ነው”ይላል። ስብሀት በየወሩ ለቁምነገር መጽሔት የሚሆን አንድ
አጭር ልብወለድ እና "ሌሎች ነገሮችንም " ይጽፍ ነበር። በተለይ"ሞትን ፈርተው ዘወትር
ስለሚሸሹ ባላባት " የፃፈው አንድ ታሪክ በተከታታይ መቅረብ ጀመረ ፤ ነገር ግን ይህ አስቂኝ ታሪክ
ከመጠናቀቁ በፊት ሳንሱር ክፍሉ "የሠራተኛውን መደብ ልእልና የሚያሳይ ካልሆነ በቀር ቀልድ
ማቅረብ አይቻልም" በማለቱ ስብሐት ስራውን ለቀቀ። ነገር ግን በዚህ ቃለመጠይቅ ወቅት የዚህን
ባላባት ታሪክ (በግምት 150 ገጽ) ያህል በሚስጥር መፃፉን አጧጡፎታል። እኚህ ገፀ ባህሪ፣
በበአሉ ግርማ "ደራሲው" ልብወለድ ላይ አጋፋሪ እንደሻው ተብለው በመጽሀፉ ውስጥ
ለተጠቀሰው "ደራሲ" ምጥ ሆነው ሲያስጨንቁት እናነባለን።
ስብሐት እንደሚለው " በአሉ ሲጽፍ ፈጣን ነው ።""በቀይ ኮከብ ጥሪ" ልብወለዱ ውስጥ
እማእላፍ (ከሺህ አንድ ማለት ነው) የሚባል ገፀ ባህሪ አለ ፤ ይኼም ገፀ ባህሪ ከስብሐት
ከራሱየተቀዳ እንደሆነነግሮኛል። በአሉ ለስብሐት ይህንን ገፀ ባህሪ በተመለከተ የፃፈውን ካነበበለት
በኋላ"ገፀባህሪው ሁለቱንም እያዝናናቸው ይስቁ ነበር።" ከዚያ በኋላ በአሉ ስለ ደራሲ ሕይወት
የሚያወራ ሙሉ መጽሀፍ ለመፃፍ አስቦ "ደራሲውን" ፃፈ። “በአሉ ሁሌም በሕይወት ያሉ ሰዎችን
ለገፀ ባህሪነት ይጠቀማል፤ ስለዚህ በቅርቡ የነበርኩትን እኔን ለልብወለዱ መጠቀሙ ተፈጥሮአዊና
የማያስገርም ነው።”
ከዚህ በኋላ ስብሐት በኢትዮጵያ መጽሐፍት ድርጅት ስራ አገኘ፤ ቢሆንም ስራው የጽሑፍ ረቂቅ
አርታኢነት በመሆኑ፣ ስራውን እንደጠበቀው አስደሳች ሆኖ አላገኘውም። ስለዚህ ከአንድ ዓመት
ትንሽ በለጥ ከሚል ጊዜ በኋላ የቱሪዝም ኮሚሽንን ተቀላቅሎ “የህትመት ውጤቶቻቸውን
እናአጠቃላይ የቱሪዝም ማስታወቂያዎቻቸው” ላይ መስራቱን ተያያዘ። ከአንድ ዓመት በኋላ የካርል
ማርክስን "ዳስ ካፒታል" ወደ አማርኛ ከሚተረጉመው ቡድን ጋር እንዲሰራ ተመርጦ ለአንድ
ዓመት አካባቢ ሰራ። በ1985 አጋማሽ ላይ ወደ ኩራዝ አሳታሚዎች ድርጅት ተዘዋውሮ እኔ
እስካነጋገርኩት ጊዜ ድረስ አርታኢ ሆኖ ሰርቷል ።
272
ጥቋቁር አናብስት
ስብሐት ለአማርኛውም፣ ለእንግሊዝኛውም “የካቲት” እስከ 1985 መጨረሻ ድረስ ይጽፍ ነበር።
በእንግሊዝኛው እትም ላይ "የደጋ ጨዋታዎች" የሚል ቋሚ አምድ ነበረው። እነኚህ ጨዋታዎች፣
የኢትዮጵያ ተረቶችን ስለሚያካትቱ፣ “ሥነ ቃላችን ደግሞ ከሥነ ጽሑፋችን ይበልጥ ስለሚጥም”
መጣጥፎቹን ማራኪ ሆነው ላገኛቸው እንደምችል ነገረኝ።
273
ጥቋቁር አናብስት
****
ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያን ከመልቀቄ በፊት፣ ስብሐትን ለጥቂት ጊዜያት በተደጋጋሚ አግኝቼዋለሁ።
ሁሌም በእጁ መጽሐፍ ይዞ የሚታየው ስብሐት ፈገግታ ከፊቱ አይለየውም። በኢትዮጵያ ሊታተም
የሚችል መጽሐፍ ቢጽፍ የሚል ምኞት ነበረኝ ፤ በ1981 ጥቅምት የመጀመሪያው መጽሐፉ
ታትሞ በአዲስአበባ የመጽሐፍት መደብሮች ለገበያ በቃ። ይህም መጽሀፉ"አምስት ስድስት ሰባት"
የተሰኘው የአጫጭር ታሪኮች ስብስብ ነበር።
የተርጓሚ ማስታወሻ
ማስታወሻዎች
1) ሐገሪቱን በ1989 ለቅቄ የሄድኩት የነበረኝ ሁለተኛው ረዥም ቆይታ ሲያበቃ ነበር። አሁን
የቆየሁት ለ4 ዓመት ሲሆን ይህ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የነበረኝን ቆይታ ወደ 14 ዓመት
ያደርሰዋል። በኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ ላይ ፍላጎት ማሳደር የጀመርኩት ከ20 ዓመት በፊት ሀገሪቷ
ውስጥ በ1965 ታህሳስ ላይ ከደረስኩኝ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ነው።
3) ደረጀ ደሬሳ አብዮቱ ፈንድቶ በኋላ ሁለት ዓመት ሳይሞላው ሀገር ጥሎ ኮብልሏል።
274
ጥቋቁር አናብስት
አሰፋገብረማርያም ተሰማ
የአብዮታዊት ኢትዮጵያ የህዝብ መዝሙር ደራሲ
አሰፋ ገብረማርያም የሚባሉ ሁለት ደራሲዎች አሉ ፤ ስለዚህ ራሱን አሰፋ
ገ/ማ/ተ ብሎ የሚጠራው ደራሲ፣ ለመለየት በስሙ ላይ የአያቱን ስም ተሰማን
ጨምሯል። ከቃለመጠይቃችን ጥቂት ዓመታት ቀደም ብሎ በባህል ሚኒስቴር
ውስጥ ነበር የሚሰራው፤ በ1980 ቃለምልልስ ከማድረጋችን በፊት
ለመጀመሪያ ጊዜ ያገኘሁትም እዚያ ነው። በጊዜው በተረት ጥናት ላይ ተጠምዶ
ነበር። በዚህ መስክ ላዘጋጃቸው ብዙ ስብስቦች የተጠናቀረ ወፍራም ጥራዝም
ደርሶኛል።የዚያኑ ያህል ስለ ኢትዮጵያ ቋንቋዎች አካዳሚ የማወቅ ፍላጎት
ነበረኝ።ይህ አካዳሚ በኃይለሥላሴ ዘመን በሌላ ቅርጽ የነበረ ቢሆንም ብዙም ተግባር
አላከናወነም። አሁን ግን ወደ ስራ የገቡ ይመስላሉ፤አሰፋም በአካዳሚው ውስጥ ቁልፍ ሰው ነበር።
ይህ አካዳሚ የአማርኛ ቋንቋ ፊደላት ተመሳሳይ አፃፃፍ እንዲኖራቸው በመስራት በዛውም
ለአጠቃቀም ቀላል እንዲሆኑየሚያስችል ስራ ሰርቷል1፤ በ1980 የሳይንሳዊ መዛግብተ ቃላትን
በተከታታይ አሳትመዋል፣ በተመሳሳይ ዓመት የግዕዝ ቅኔ ስብስብ፣ ከነአማርኛ ፍቺያቸው፣
ከምስጢርና ትርጉማቸው ጋር እንዲሁም ከቅኔው ዳራ ጋር አብሮ ታትሟል።መንግስቱ ለማ ለቅኔ
መጽሐፋቸው ብዙ ዓመት የፈጀ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል፤መጽሐፉም የወጣውበ1980 በጠና
ታሞ ሆስፒታል ከመግባቱ ጥቂት ጊዜ በፊት ነው።
***
በቤተክርስቲያን ትምህርት ቤት ሁለት ዓመት ከቆየ በኋላ፣ የስዊድን ሚስዮን ትምህርት ቤት ገባ።
የትምህርት ቤቱ ስም ቢ.ቪ. ይባላል( ይህም በሰዊድንኛ የመጽሀፍ ቅዱስ ታማኝ ጓደኞች የሚለው
በአጭሩ ሲፃፍ ነው)። ትምህርት ቤቱ ራስ ደስታ ሆስፒታል አካባቢ ከተከፈተ ብዙም አልቆየም።
ከአስተማሪዎቹ መሀል አንዱ፣ የደራሲ በእምነት ገብረአምላክ አባት የሆኑት፣ ቄስ ገብረአምላክ
ሩፋኤል ነበሩ።4
አሰፋ በዚህ የስዊድን ቢ ቪ ሚስዮን ትምህርት ቤት ለሁለት ዓመታት ቆየ። አብዛኛዎቹ መምህራን
ወጣት ስዊድናውያን ሲሆኑ በትንሿ ቤተክርስቲያናቸው ውስጥ ፒያኖ እየተጫወቱ ይዘምሩላቸው
ነበር።አስተማሪዎቹ ጥሩናቸው፤ ነገር ግን በንጽህና ጉዳይ ላይ ጥብቅ ነበሩ። ይሁን እንጂ አሰፋ
በድህነቱ ምክንያት ንጽህናውን ሁሌ ለመጠበቅ አልቻለም።ስለዚህ ከሁለት ዓመት በኋላ
የመንግስት ትምህርት ቤት ገባ። የገባበት ትምህርት ቤት የአርበኞች ትምህርት ቤት ሲባል ሰፈሩ
ውስጥ የሚያውቃቸውወንድ ልጆች ሁሉ የሚማሩት እዚህ ነው።የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን
በዚያ ጨረሰ።እዚያ ተማሪ እያለ በማዘጋጃቤት የቲያትር አዳራሽ ተውኔቶችን ይመለከት ነበር ፤
ቲያትር ቤቱ ያኔ ይገኝ የነበረው አሁን የዳግማዊ ምኒልክ ፈረሰኛ ሐውልት አጠገብ የፍርድ ቤቱ
ህንፃ ላይ ነው። ዘወትር እሁድም ሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት ይሄዳል፤ ልጆች በነፃ እንዲገቡና ማእዘን
ላይ ወይም ግድግዳውን ተደግፈው እንዲታደሙ ይፈቀድላቸው ነበር። ሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት
ተውኔት ከመቅረቡ በፊት፣ ከመስራቾቹ አንዱ የሆኑት መኮንን ሀብተወልድ ንግግር ያደርጋሉ።
አሰፋ አንዳንዶቹን ተውኔቶች በደንብ ቢያስታውሳቸውም፣ ርዕሳቸውን ወይም ደራሲያቸውን
276
ጥቋቁር አናብስት
ረስቶአቸዋል። ብዙዎቹ ተውኔቶች ቧልታይ ናቸው ፤ በብዛት የባልና ሚስትን ግጭት የሚመለከቱ
ናቸው። የአሰፋ እናት ደሀ ናቸው። ቢሆንም ጠላ ጠምቀው፣ ልብስ ሸምነው በሚያገኙት ገንዘብ
ልጆቻቸውን ያስተምራሉ። በተለይ ሴት ልጃቸውን በደንብ ይንከባከቧት ነበር።
ከስዊድን ትምህርት ቤት ከለቀቀ በኋላ፣አሰፋ ሠፈራቸው ከሚኖሩ አንድ አሮጊት ጋር መኖር
ጀመረ። አሮጊቷ የአቶ ድንቁ ልጅ ናቸው (አቶ ድንቁ ከድሬዳዋ የመጡ በደንብ የሚታወቁ ካቶሊክ
ናቸው።) አሮጊቷ ለአሰፋ ደግ ሴት ነበሩ። አሰፋ በትምህርቱ ጎበዝ ነበር። ከስድስተኛ ክፍል በኋላ
አባ ዲና ኮሌጅ መግባትፈለገ። አባ ዲና የፖሊስ መኮንኖች ማሰልጠኛ ነው። ስልጠናው ሁለት
ወይም ሶስት ዓመት ይወስዳል። አሰፋን ያማለለው 150 ብር (75$) ወርሃዊ ክፍያው ነበር።
አብረውት የተማሩት አብዛኛዎቹ የክፍል ጓደኞቹ ኮሌጁን ተቀላቀሉ። በአርበኞች ትምህርት ቤት
ያሉ መምህራኖችም የቃል ፈተናውን እንዲያልፉ ይረዷቸው ነበር። እንዲሸመድዱ ካደረጓቸው
መልሶች ውስጥ "ሀገሬንና ንጉሴን መጠበቅ እፈልጋለሁ፣ወንጀልን መዋጋት እፈልጋለሁ"
የመሳሰሉት ይገኙበታል። አሰፋ የመግቢያ እና የቃል ፈተናውን ቢያልፍም የሰውነት አቋምህ ጥሩ
አይደለም ብለው መለሱት።( እኔ ሳገኘው ግን በተቃራኒው ጥሩ ቁመና ነበረው)። ከሶስት ዓመት
በኋላ እንዲያመለክትና ያለምንም ፈተና እንደሚቀበሉት ተነግሮት ነበር። ይሁን እንጂ ተመልሶ
ወደዚያ አልሄደም። ይልቁንም ጀነራል ዊንጌት ትምህርት ቤት ገባ። ዊንጌት ብዙዎች ለመግባት
የሚንሰፈሰፉለት “የልሂቃን ትምህርት ቤት” ነው። ትምህርት ቤቱ ከሰባተኛ እስከ አስራ ሁለተኛ
ክፍል የሚያስተምር ነፃ የአዳሪ ትምህርት ቤት ነው(አሰፋ እዚህ የተማረው ለአምስት ዓመታት
ከመስከረም 1943 እስከ ሐምሌ 1948 ነው)። እንደዚያ ከሆነ አንድ ክፍል ሳይዘልል አልቀረም።
በቆይታው ጎበዝ የሚባል ተማሪ ነበር፤“በክፍሉ ውስጥ ከፍተኛ ውጤት ካመጡት ተማሪዎች
መሀል አንዱ” ሲሆን ትምህርት ቤቱ “በጥብቅ የእንግሊዝ ስርአት የተቃኘ” ነበር። ስርአቱ አሰፋ
ላይ ተጽዕኖ አድርጎበታል―ተጽእኖው“ድብልቅ ጥቅም ነበረው”ይላል። “ሥነ ስርአቱ ለተማሪዎች
ጠቃሚ ነበር”፤በጠዋት እንዲነሱ፣እንዲተጣጠቡ፣ንጽህናቸውን እንዲጠብቁ እንዲሁም ራሳቸውን
እንዲችሉ ያደርጋል ይላል። አስተማሪዎቹን በደንብ ያስታውሳል ፤ ይሁን እንጂ በሥነ ጽሑፋዊ
ሰውነቱ ላይ የተለየ ተጽዕኖ ያሳረፈበት የለም። የመጀመሪያ ርዕሰ መምህሩ ሚስተር ሄሪንግ ይባላሉ
፤"ጥብቅ እና ወግ አጥባቂ" ነበሩ። በቃለምልልሱ ወቅት የብሪቲሽ ካውንስል ሀላፊ የነበረው
ሚስተር ሀድሰን በትምህርት ቤቱ ውስጥ የሥነ ጽሑፍ አስተማሪ የነበረ ሲሆን ተማሪዎቹ ትምህርት
ቤቱ ውስጥ የሚገኘውን የተደራጀ ቤተ መጽሀፍት እንዲጠቀሙ ያበረታታ ነበር። በጊዜው ዊንጌት
ውስጥ “ልብወለድ ማንበብ ፋሽን ስለነበር” አሰፋም “እነ ዲክንስን፣አሌክሳንደር ዱማን” አነበበ።
የሚስተር ሀድሰን ባለቤት ታሪክ አስተማሪ ነበረች። ጂም ማርሻል (አሁን የአዲሳባ ዩኒቨርስቲ
መምህር) ደግሞ ሒሳብ ያስተምር ነበር። ሚስተር ሮበርትስ(በኋላ የሚንሊክ ትምህርት ቤት
277
ጥቋቁር አናብስት
278
ጥቋቁር አናብስት
አሰፋ በጄኔራል ዊንጌት ትምህርቱን ሲጨርስ ለሁለት ፈተናዎች ተቀመጠ ፤ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ
መልቀቂያ ፈተና እና የብሪቲሽ GCE ፈተና ተፈትኖ በሰባት ትምህርቶች፡በእንግሊዝኛ፣ በሥነ
ጽሑፍ፣ በሂሳብ፣ በአማርኛ፣ በፊዚክስ፣ በኬሚስትሪ እና በጠቅላላ ሳይንስ አልፏል።
አሰፋ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ከጨረሰ በኋላ፣ ደሀ እናቱን መርዳት ስለነበረበት ወዲያውኑ ወደ
ዩኒቨርስቲ አልገባም። ዊንጌት እያለ ቤተሰቡ ውስጥ የተከሰተ አንድ ነገር ጥቁር ጠባሳ ጥሎበት
አልፏል፦ትንሽ ወንድሙ ሞገስ ይታመምና፣ምናልባትም በድህነታቸው የተነሳ ሆስፒታል ሊወስዱት
ስላልቻሉ፣ ሞተ። ዝነኛው የራስ ደስታ ሆስፒታል በአቅራቢያቸው መኖሩ ሁኔታውን የበለጠ
መራር ያደርገዋል። በነዚህ ዓመታት አሰፋ ስለ ማህበራዊ ችግሮች ያለው ግንዛቤ እየጨመረ መጣ ፤
ስለዚህ አሰፋ ስለ ሶሻሊዝም “በጽንሰ ሀሳብ ደረጃ የተቀመጠ እውቀት ሳይኖረው”፣ ከራሱ ሁኔታ
በመነሳት ሶሻሊስታዊ ዝንባሌ እያሳደረ፣ ብዙዎችን ለአላስፈላጊ ስቃይና ለድህነት እየዳረገ ስላለው
የፊውዳል ስርአት እየተረዳ ነበር።
በ1949ዓም በትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ በትምህርት ስርአት ክፍል ውስጥ መስራት ጀመረ።
በእዚያ በጊዜው ተራማጅ ዲሞክራቶች ብሎ የሚጠራቸውን ብዙ ሰዎች አገኘ። ለይቶ ከጠቀሳቸው
መሐል የትምህርት ስርአት ክፍል ዋና ሐላፊና የአሰፋ አለቃ 6የነበረው ሚሊዮን ነቅንቅ፣ ከሲዳሞ
ድረስ እነ ሚሊዮንን ለመጠየቅ የሚመጣው የ1953ቱ የመፈንቅለ መንግስት የርዕዮተ አለም መሪ
የነበረው ግርማሜ ነዋይ ይገኙበታል። በወቅቱ ከበደ ሚካኤል የትምህርት ሚኒስትር ዋና
ዳይሬክተር እና የሚሊዮን አለቃ ሲሆኑ፣ አሰፋ “በቅርብም ባይሆን” ያውቃቸው ነበር። ሚሊዮን
ነቅንቅ ራሱ ገጣሚ ነበር፤እንደውም "ሮሚዮ እና ዡልየት"ን ከከበደ ሚካኤል በፊት "ካለቁ ታረቁ"
በሚል ርዕስ ተርጉሟል። አሰፋንም ያበረታታው ነበር ፤ በዚህ መሰረት የአሰፋን የ"ጁሊየስ ቄሳር"
ትርጉም ስህተቱን አርሞ ለማተሚያ ቤት ዝግጁ አድርጎለታል።7 ሚሊዮን አማርኛን በመላው
ኢትዮጵያ በሚገኙ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የመማሪያ ቋንቋ እንዲሆን በማድረግ
የመጀመሪያው የትምህርት ስርአት ሀላፊ ነበር(ከዛ በፊት አውሮፓዊ ቋንቋዎች በተለይ እንግሊዝኛ
ጊዜው ኢትዮጵያ በታላቅ ተስፋ የተሞላችበት ጊዜ ነበር። ንጉሱ የብር ኢዮቤልዩ በአላቸውን
በ1948 ሲያከብሩ አዲስ ህገ መንግስት አስረቅቀዋል(የ1923 ህገ መንግስት ማሻሻያ ተደርጎበት)።
ይህ አዲስ ህገ መንግስት የፕሬስ ነፃነት፣ የንግግር ነፃነት እና ሌሎችም ደስ ደስ የሚሉ ሀሳቦችን
ይዟል። “ሁሉም ሰው የሚያወራው ስለዚህ ነበር”፤እነሆ በመጨረሻ “ያለ ሳንሱር” መናገር፣ መፃፍ
እና ማተም ሊችሉ ነው። ስለዚህ አሰፋ "የጁልየስ ቄሳር" ትርጉሙን ለህትመት አዘጋጀና ወደ ተስፋ
ገብረስላሴ ማተሚያ ቤት ይዞት ሄደ።ተስፋ ገብረሥላሴ ማተሚያ ቤት በግእዝና በአማርኛ
የሐይማኖት መጽሀፍትን፣ የፀሎት መጽሐፍትን፣የቅዱሳን ገድሎችን፣የመሳሰሉትን እያተመ እስካሁን
ያለ ማተሚያ ቤት ነው።የግእዝ እና የአማርኛ ምንባቦችን በትይዩ የሚያቀርቡበት መንገድ በተለይ
ለግእዝ ተማሪዎች በጣም ጠቃሚ ነው። በጊዜው በኢትዮጵያ የሚታተሙ መጽሀፍት በፊት ገፃቸው
የንጉሱን ምስል መያዛቸው ደንብ ነበር።አሰፋ ግን ከዚህ ደንብ ወጥቶ፣ የንጉሱን ተወዳጅ ልጅ
የሀረሩን መስፍን የልኡል መኮንንን ምስል በምትኩ አስገባ። ልዑሉም የሞቱት በዚሁ ዓመት ነበር።
አሰፋ መጽሀፉ በሙሉ ከመታተሙ በፊት ነበርይህን ያደረገው።በተጨማሪ መኳንንቱ ላይ በምፀት
የሚያፌዝ ግጥም ጣል አድርጎ ነበር ፤ ነገር ግን ድብቅ ስለሆነ ማንም አይደርስበትም። (አሁን ላይ
ይህንን ድርጊቱን ሲያስበው የሞኝ ስራ እንደነበር ተረድቷል)።አሳታሚዎች ጋር እየሄደ
የተስተካከሉትን ቅጂዎች ያነብ ነበር።የመጨረሻው ትእይንት ሲታተም ሳንሱር አድራጊዎቹ
እየፈለጉት እንደነበርሰማ። የንጉሱን ፎቶ ሳያስገባ መጽሀፍ ለማተምመሞከር “ከደንብ ውጪ”
መሆኑን ሳንሱረኞቹ ነገሩት። (በየቦታው “ሰላዮችና”ጆሮ ጠቢዎች ስለነበሯቸው፣ በማተሚያ ቤት
ውስጥ የሚሰራ አንድ ሰው “የንጉሱ ፎቶ መቅረቱን” ነግሯቸው መሆን አለበት)። ኢትዮጵያ ግዛት
ስለሆነች፣ንጉሠ ነገሥቷ በዚህ ዐይነት መንገድ"መሞት" እንደሌለበት ተነገረው። ስለዚህ መጽሀፉ
ከታተመ በኋላ ሳይከፋፈል እንዲወረስ ተደረገ። አሰፋ ጥቂት ቅጂዎች ብቻ ደርሰውታል። በጊዜው
ደራሲዎች ለአታሚዎች በቅድሚያ መክፈላቸው እንደ ህግ ነበር። ነገር ግን የአሰፋ ጓደኞች በጊዜው
ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ተማሪ የነበረውን የአታሚውን ልጅ ያውቁት ነበር። አሰፋ እና ልጁ ከተዋወቁ
በኋላ በሱ በኩል ለህትመት በቅድሚያ ሳይከፍል መጽሀፉ መታተም ቻለ። ስለዚህ አሰፋ ሰባራ
ሳንቲም አልከሰረም። የሀይለስላሴ “የፕሬስ ነፃነት” እዚህ ድረስ ነበር ይላል አሰፋ። ( ሰዎች ግን
እስከ 1953ቱ መፈንቅለ መንግስት ድረስ ሳንሱሩ የላላ ነበር ፤ ከመፈንቅለ መንግስቱ በኋላ ግን
ዳግም ጠበቀ ይላሉ።)
280
ጥቋቁር አናብስት
በዚህ መጥፎ አጋጣሚ የተነሳ፣ ይህ መጽሀፍ የስራ መስኩን ሙሉ ለሙሉ እንዳስለወጠው አሰፋ
ይናገራል።ተስፋ መቁረጥ ስለወረሰው፣ ብዙም ሳይቆይ ስራውን ለቀቀ። በመጽሀፉ መግቢያ ላይ
እሳቸውን ሳያማክራቸው ከከበደ ሚካኤል ስራዎች ላይ ቀንጭቦየጠቀሰው ጥቅስ ስለነበረ፣
ስማቸውን በመጥቀሱ ብቻ ለሳቸውም ችግር ፈጠረባቸው። ምናልባትም ሳንሱረኞቹ ከበደ
ሚካኤል ስለጉዳዩ ቅድሚያ ሳያውቁአይቀርም የሚል ጥርጣሬ ሳያድርባቸው አልቀረም። አሰፋ የA
ደረጃ ፈተናውን ካለፈ ከበደ ወደ ለንደን ዩኒቨርስቲ እንደሚልኩት ቃል ገብተው ነበር። አሁን ግን
ቃላቸውን በማጠፋቸው፣አሰፋን ለተጨማሪ ብስጭት ዳረገው።
አሰፋ ከትምህርት ሚኒስቴር ከለቀቀ በኋላ፣ወደ ጅማ ሄዶ በጅማ ሁለተኛ ደረጃ የእርሻ ትምህርት
ቤት ማስተማር ጀመረ። ትምህርት ቤቱ የሚተዳደረው በአሜሪካኖችና በእርሻ ሚኒስቴር ትብብር
ነው። ይህ አጋጣሚ አሰፋ ከአዲስ አበባ ውጪ ለረዥም ጊዜየቆየበት የመጀመሪያው አጋጣሚ
ነበር። በ1949 መጨረሻ አካባቢ ወደ ጅማ የሄደ፣ የመፈንቅለ መንግስቱ ሙከራ ሊደረግ ትንሽ
ጊዜእስኪቀረው ድረስ ቆይቷል። በመስከረም/ጥቅምት 1953 በዴሞክራት ጓደኞቹ ሚሊዮን
ነቅንቅ እና ታደሰ ተፈራ እርዳታ፣ ዳግመኛ ትምህርት ሚኒስቴርን ተቀላቀለ (በቃለምልልሱ ወቅት
ታደሰ የጀርመን አምባሳደር ነበር)።
በዚህ ወቅት በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መሀል የመጀመሪያው የባህል ስምምነት ተፈረመ። አሰፋ እና
ሌሎች ስድስት ኢትዮጵያውያን ተመርጠው ሩስያ ውስጥ የተለያየ ስራ ተሰጣቸው። የአሰፋ ስራ
በሌኒንግራድ ዩኒቨርስቲ አማርኛ ማስተማር ነበር።
***
ሌኒንግራድ ውስጥ አሰፋ ራሱን ሙሉ ለሙሉ ለሥነ ጽሑፍ ሰጠ። የሩስያን ቋንቋ እና ሥነ ጽሑፍ
ለማጥናት በማታ የትምህርት ክፍለ ጊዜ ተመዘገበ፤በዚያ የነበረውን አብዛኛውን ጊዜ ለዚሁ
አውሎት ነበር። ወደ ሩስያ የሄደው ታህሳስ 1953 ሲሆን የቆየው እስከ ሐምሌ 1957 ድረስ
ነበር። በቆይታው የሩስኪ ቋንቋን አቀላጥፎ መናገር ችሏል። በቃለምልልሱ ወቅት የሩስያን ሥነ
ጽሑፍ ቢወድም አሁን አሁን ብዙም እያነበበውአልነበረም። ሌኒንግራድን ወዶት ነበር፤
ምክንያቱም በባህል የበለፀገ ቦታ ነው። የአሮጌውንና የአዲሱን ስልጣኔ ህብር በሥነ ህንፃውና፣
በየሙዚየሙ ማየት ይቻል ነበር። ከኢትዮጵያ ውጭ የባእድ ባህል ሲያይ ይህ የመጀመሪያ ጊዜው
ነው ( በኋላ ወደ 20 የሚደርሱ የውጪ ሃገራትን መጎብኘት ችሏል)።
ችሏል። በተጨማሪ ሌኒንግራድ ውስጥ የሩስያ ታላላቅ ዘመን ተሻጋሪ የሥነ ጽሑፍ ስራዎችን
አንብቧል። በእርግጥ የሚማረው ትምህርት እንዲያነባቸው ያስገድደዋል። ከነዚህ መሀል ቶልስቶይ፣
ፑሽኪን እና ዶስቶቭስኪ በተለይ ስበውት ነበር።ነገር ግን ከዚህም በላይ ብዙ አንብቧል ፤ከጎርኪ
ጀምሮ ያሉትን የሶቪየት ደራሲዎች ሌሎችንም አንብቧል።
282
ጥቋቁር አናብስት
አሰፋ ገብረማርያም ሶሻሊስታዊ ዝንባሌዎችን ማሳደር የጀመረው ከልጅነት ገጠመኞቹ ተነስቶ እንጂ
በጽንሰ–ሀሳብ ደረጃ ወይም መጽሐፍ በማንበብ አይደለም። ድህነት ምን እንደሆነ በሚገባ
ያውቃል፤የሚፈልገው እናቱን እና ቤተሰቡን ለመርዳት የሚበቃውን ያህል ሰርቶ ለማግኘት
የሚችልበት አጋጣሚ እንዲመቻችለት ነው። ሀብታም ለመሆን ተመኝቶ አያውቅም። ሌኒንግራድ
እያለ ሶሻሊስታዊ ስርአት እንዴት እንደሚሰራ አስተውሏል። ወደ ሀገሩ ሲመለስ ኢትዮጵያ “የተሻለ
ዲሞክራሲያዊ ስርአት” ያስፈልጋታል የሚለውን “ጽኑ እምነት” እንደያዘ ነበር ፤ ነገር ግን ኋላ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (የዛኔ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርስቲ)ተማሪ ሲሆን፣ “የተማሪዎች
እንቅስቃሴ ግንባር ቀዳሚ ተሳታፊ የሚሆንበት ሁኔታ ላይ አልነበረም።” ነገር ግን “ፖለቲካዊ ንቃተ
ሕሊናው ከፍ ያለ” ነበር። “የፊውዳል ስርአት በጅማ እና ሌሎች ቦታዎች እንዴት እንደሚሰራ”
አስተውሏል ፤ “ስርአቱን” በተመለከተም ከብዙ ምሁራን ጋር ተወያይቷል።
አሰፋ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሰ በኋላ አሰፋ ዳግመኛ ትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ መስራት ጀመሮ
እስከ 1967 ድረስ በዚያ ቆየ። በ1967 የባህል ሚኒስቴር ሲቋቋም በዛ መስራት ጀመረ በመሐል
ለአጫጭር ጊዜ ውጪ ከመሄዱ በቀር እስከ ቃለምልልሳችን ጊዜ ድረስ እዚያውነበር የሚሰራው።
በትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ በሥነ ጥበብ ክፍል ይሰራ ነበር። የክፍሉ ሀላፊ የነበረችው ሜሪ
ታደሰ ለአጭር ጊዜ ነበርበዚህ ሃላፊነት የቆየችው። ይህ ክፍል በ1967 ከአብዮቱ በኋላ 10ወደ
ባህል ሚኒስቴር ሲዘዋወር “ወይ በጡረታወይ በሌላመንገድከስራ ተገልላለች።” በዚህ ጊዜ አሰፋ
“ወጣቶች የሚበዙባቸውን ቦታዎች ይጎበኝ” ነበር ፤ ለምሳሌ አሮጌው አየር ማረፊያ አጠገብ ያለው
አባዲና ኮሌጅ(በአብዮቱ ጊዜየደህንነት ክፍሉ እዚህ ነበር)፣ ደብረዘይት የሚገኘው አየር ሀይል
የመሳሰሉት። በዚያ ከወጣቶች ጋር እየተገናኘ በብዙ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። ሥነ ልሳንእና ሥነ
ጽሑፍ ሲያስተምር ከቋንቋ እና ባህል ጉዳይ ተነስቶ እንደ እኩልነት፣ ፍትህ፣ ፖለቲካንም ጨምሮ
ወደ ሌሎችም ጉዳዮች መሄዱን ቀላል ሆኖ አግኝቶታል። ሌኒንግራድ እያለ ያዳበረውን ልምድ
ለተማሪዎቹ በክፍል ውስጥም ሆነ ከክፍል ውጪ ያካፍል ነበር።
ሜሪ ታደሰ ከባህል ሚኒስቴር ስትለቅ፣ አሰፋ እሷን ተክቶ የሥነ ጥበብ ክፍሉን መምራት ጀመረ ፤
የሾመው ወታደራዊው መንግስት ደርግ ነበር። በጊዜው የባህል ሚኒስቴር የነበሩት ዶክተር አክሊሉ
283
ጥቋቁር አናብስት
በባህል ሚኒስቴር የሥነ ጥበብ ክፍል ውስጥ ከነበረው ቆይታ በኋላ በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት
ቤትና በአዲስአበባ የሥነ ጥበብ ትምህርት ቤት አማርኛን እና "ባህልን ማክበር"ን ከ1968–70
አስተምሯል። ከዚህ ቀደም ብሎ በ1967/68 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች አካዳሚ ምክር ቤት አባል
ሆኖ ተመርጧል። በ1970 የአካዳሚውን ጽህፈት ቤት ተቀላቅሎ የሥነ ቃል ክፍል ዋና ሀላፊ ሆኖ
ለሁለት ዓመት ሰርቷል። በዚሁ ወቅት ትልቅ የሥነ ቃል አውደጥናት አዘጋጅቶ ብዙ የጥናት
ወረቀቶች ቀርበዋል። በ1973 የአካዳሚው ጊዜያዊ ዋና ጸሐፊ ሆነ ፤ በ1977 ሐላፊነቱ ቋሚ
ሆኖለት እስከ ከቃለምልልሳችን ጊዜ ድረስ ይሰራ ነበር። አሰፋ በሐላፊነት እያለ የኢትዮጵያ
ቋንቋዎች አካዳሚ ያከናወናቸው ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፡(1)የአማርኛ እና ሌሎች
ኢትዮጵያዊ ቋንቋዎች ፊደላት አንድ ወጥ የሆሄ ስርአት እንዲኖራቸው መደረጉ (2) የአማርኛ
ቅኔዎች ተሰብስበው በመቶ የሚቆጠሩት ምሳሌዎች ተመርጠው በ1980 በመጽሀፍ መልክ
መታተማቸው(3)ተከታታይ የቴክኒካዊ እና ሳይንሳዊ መዛግብተ ቃላት በዚያው ዓመት በ1980
መታተማቸው።
የኢትዮጵያ ቋንቋዎች አካዳሚ የጥቂት አስርት ዓመታት ታሪክ ያለው ቢሆንም፣ እስከ 66ቱ
አብዮት ድረስ ግን ብዙም ተግባር አላከናወነም። አካዳሚው እንዲቋቋም የታዘዘው በ1934 ነበር፤
ነገር ግን እስከ 1964 ድረስ ትእዛዙ ተፈፃሚነት ካለማግኘቱም በላይ፣ ለብዙ ዓመታትምጥቂት
ተጨባጭስራዎችን ነበር ያከናወነው። የቀድሞው የአማርኛ ቋንቋ ብሔራዊ አካዳሚ፣ በአማርኛ
ሥነ ጽሑፍወይም በቋንቋው ጥናትና አጠቃቀም ከፍተኛ ዝና ያተረፉ አባላት ነበሩት፤ ( ሁሉም
አባላት በቀዳማዊ ኃይለስላሴ የተሾሙ ናቸው) ከነዚህ መሀል ከበደ ሚካኤል፣ ግርማቸው
ተክለሀዋርያት፣ ወልደጊዮርጊስ ወልደዮሐንስ፣ ገብረክርስቶስ ደስታ፣ ማህተመሥላሴ
ወልደመስቀል፣ መርስዔሀዘን ወልደቂርቆስ፣ ተክለፃድቅ መኩሪያ፣ ዶክተር አብርሃም ደሞዝ፣
ዶክተር አክሊሉ ሀብቴ፣ ዶክተር ጌታቸው ኃይሌ፣ ዶክተር ኃይሉ ፉላስ፣ ዶክተር ስርግው
ሀብለሥላሴ ወዘተ ይገኙበታል። በ1967 አካዳሚው ስሙን ወደ “የኢትዮጵያ ቋንቋዎች አካዳሚ”
ሲቀይር የቀድሞ አባላቱ አዲሶቹን አባላት መረጡ።እነዚህም ሐዲስ አለማየሁ፣መንግሥቱ ለማ፣
ዳኛቸው ወርቁ፣ ወልደጊዮርጊስ ወልደዮሐንስ፣ ተክለፃድቅ መኩሪያ (የታሪክ ሊቅ) ፣ አፈወርቅ
285
ጥቋቁር አናብስት
ተክሌ (ሰአሊ)፣ አሰፋ ገብረማርያም ተሰማ፣ ዶክተር ብርሀኑ አበበ (የታሪክ ሊቅ) ፣ ዶክተር
አክሊሉ ሀብቴ (የአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት)፣ ዶክተር አምሳሉ አክሊሉ (የቋንቋ ሊቅ)፣
ዶክተር ፈቃዱ ገዳሙ (የሥነ ሰብዕ ተመራማሪ)፣ ዶክተር ጌታቸው ኃይሌ ( የቋንቋ ሊቅ)፣ ዶክተር
ኃይሉ ፉላስ (የቋንቋ ሊቅ) ፣ ዶክተር ኃይሉ አርአያ (የቋንቋ ሊቅ) ፣ ዶክተር መርእድ ወልደአረጋይ
( የታሪክ ሊቅ)፣ ዶክተር ታደሰ በየነ (የቋንቋ ሊቅ)፣ ዶክተር ታደሰ ታምራት ( የታሪክ ሊቅ)፣
ዶክተር ስርግው ሀብለሥላሴ ( የታሪክ ሊቅ) እና ሌሎችም ይገኙበታል።16 በኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ
ላይ ፍላጎት ያላቸው ሰዎች በ1980 አካዳሚው ያሳተመው የአማርኛ ቅኔዎች ስብስብ
ሳይማርካቸው አይቀርም። ይህን ስብስብ በማዘጋጀት ብዙ ጸሐፊዎችና ምሁራን ተሳትፈዋል፤
ለምሳሌ መንግስቱ ለማ (አርታኢ)፣ ተክለፃዲቅ መኩሪያ፣ ዶክተር አምሳሉ አክሊሉ እና ዶክተር
ኃይሉ አርአያ ይገኙበታል።የመጽሐፉ ርዕሰ "የግዕዝ ቅኔያት" ሲባል 337 ያህል ቅኔዎችን ይዟል።
ቅኔዎቹ ቀድሞ ከነበሩ ስብስቦች የተወሰዱ ሲሆን በዚህ መጽሀፍ ላይ ግን ወደ አማርኛ ቋንቋ
ተተርጉመው ከጠቃሚ ማብራሪያዎች ጋር ቀርበዋል።በዚህ ወቅት ሌላው ይህ አካዳሚ ያከናወነው
ታላቅ ተግባር የሳይንሳዊ እና ቴክኒካዊመዛግብተ ቃላት በተመሳሳይ ዓመት ማሳተሙ ነው።
ከተዳሰሱት የእውቀት ዘርፎች መሀል ህክምና፣ሥነ –እንስሳት፣ሥነ –እጽዋት፣ እርሻ፣ ጂኦግራፊ፣ሥነ
–ምድር፣ ሂሳብ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዚክስ እና ኤሌክትሮመካኒክስ ይገኙበታል። የሥነ ምግብ፣
ስታትስቲክስ እና የህንፃ ግንባታ መስኮችን የሚመለከትመዛግብተ ቃላት በኋላ ተከትለው
ወጥተዋል። አሰፋ ገብረማርያም ተሰማ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ቃላት ትርጉም ፕሮጀክት (መዛግብተ
ቃላቱን ያዘጋጀው አካል)ዳይሬክተር ነበር። ዝግጅቱ የጀመረው በ1973 ከአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ
እና ከኢትዮጵያ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ሲሆን የተባበሩት መንግስታት
የልማት ፕሮግራም የገንዘብ ድጋፍ አድርጎላቸዋል።
አሰፋ ገብረማርያም ተሰማ በተጨማሪም፣ ለብዙ ዓመታት የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር አባል
የነበረ ሲሆን የማህበሩ ዋና ፀሐፊም ሆኖ ሰርቷል። በቃለምልልሳችን ወቅት የማህበሩን ስራ
አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ነበር።በማህበሩ ውስጥ“ጥሩ የመተባበር መንፈስ” ነበር ይላል።አብረውት
ከሰሩ ደራሲዎች መሀል ብርሀኑ ዘርይሁን፣መንግስቱ ለማ፣ ተስፋዬ ገሰሰ፣አማረ ማሞ እና ሌሎችም
ይገኙበታል።ከላይ ከተጠቀሱት ስራዎች ባሻገር አሰፋ የአማርኛ ቋንቋ እና ሥነ ጽሑፍን
በሚመለከት በተለያዩ መድረኮች ላይ ብዙ ጥናታዊ ጽሑፎችን አቅርቧል። በመላው አለም በሰፊው
ተዘዋውሯል። በ1979 በሌኒንግራድ ዩኒቨርስቲ የዶክትሬት ዲግሪውን ለመከታተል የውጪ ተማሪ
ሆኖ ተመዝግቦ ነበር። በስራው እጅግ በርካታ ሽልማትን ተቀብሏል። የተመረጡ ግጥሞቹ ወደ
አረብኛ፣ እንግሊዝኛ ፣ ፈረንሳይኛ፣ ጣሊያንኛ፣ ስፓኒሽኛ፣ ሩስያኛ እና ቡልጋሪያኛ ተተርጉመው
286
ጥቋቁር አናብስት
ታትመዋል ብሏል። ምንም እንኳን የግጥም ስብስቦቹ ትልልቅ ቅጽ ባይሞሉም፣ በኢትዮጵያ ውስጥ
በደንብ የሚታወቅ ገጣሚ ነው። በግንባር ቀደምትነት የሚታወቅበት ነገር ግን በአብዮቱ ዘመን
የብሔራዊ መዝሙሩን ግጥም በመድረሱ ነው።
የተርጓሚ ማስታወሻ አሰፋ ገብረማርያም ተሰማ እሚኖርበት አሜሪካ ላስቬጋስ ውስጥ በቅርቡ
ህይወቱ አልፋለች፡፡
ማስታወሻዎች
5) ዊንጌት ውስጥ ከአሰፋ ጋር መማር ከጀመሩ ተማሪዎች መሀል በኋላ ታላቅ ጸሐፊ ተውኔት
ለመሆን የበቃው ፀጋዬ ገብረመድህን አንዱ ነው። ነገር ግን ሁለተኛው ዓመት ላይ ከዊንጌት ወጥቶ
287
ጥቋቁር አናብስት
6) በኋላ የጃፓን አምባሳደር ሲሆን በዚህ ቃለመጠይቅ ወቅት በሰሜን አሜሪካ ውስጥ “ስደተኛ”
ነበር።
7) ሚሊየን ነቅንቅ ዊንጌት ውስጥ ከነአሰፋ ዘመን በፊት አማርኛ አስተምሯል። ከዚያም ወደ
ዩናይትድ ኪንግደም ሄዶ በሥነ ትምህርት የመጀመሪያ ዲግሪውን ይዞ ተመልሷል። ሚሊየን ዌልስ
ውስጥ እየተማረ በነበረበት በዚህ ሰአት ሚካኤል እምሩ ኦክስፎርድ ውስጥ፣ መንግሥቱ ለማ ደግሞ
ለንደንየኢኮኖሚክስና የፖለቲካ ሳይንስ ትምህርት ቤት ውስጥ ይማሩ ነበር። ሶስቱ በደንብ
ይተዋወቁ እንደነበር አሰፋ ይመሰክራል።
8) ገብረክርስቶስ ደስታ በዋነኛነት የሚታወቀው በሰአሊነቱ ነው። ነገር ግን አሰፋ ገማተ፣ ሚካኤል
እምሩ እና ሌሎችም እንደ ገጣሚም ትልቅ ቦታ ይሰጡታል። ገብረክርስቶስ ደስታ በሰሜን አሜሪካ
በ1972 አርፏል። በአሳሳል ስልቱ ተማሪዎቹ ላይ ብርቱ ተጽእኖ አሳድሮባቸዋል። ኢትዮጵያ
በቆየሁባቸው ዓመታት ስሙ ገኖ የወጣና፣ ስእሎቹም በተደጋጋሚ የሚጎበኙለትሰአሊገብረክርስቶስ
ደስታ ነበር።
9)ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሱ በኋላ በ1949፣ 1951፣ 1957 ሶስት ሴት ልጆችን ወልደዋል።
10) ሜሪ ታደሰ “በኢትዮጵያ ውስጥ ከመጀመሪያዎቹ የተማሩ ሴቶች መሀል አንዷ ነች።”
“ፈረንሳዊት ሴት ያገባው” ወንድሟ ማሞ ታደሰ፣ በአንድ ወቅት የገንዘብ ሚኒስትር ነበር። "በጠራ
ጨረቃ" የሚለው የመንግስቱ ለማ ግጥም ለእሷ እንደተፃፈ “ሰዎች እንደሚያወሩ” አሰፋ ይናገራል
፤ “እርግጠኛ ግን አይደለም” ( እኔም ብሆን ለመንግስቱ ጉዳዩን አላነሳሁበትም)። ጨምሮ “ቆንጆ
ሳትሆን እንደማትቀር” ይናገራል ፤ አብረዋት የሚማሩ ወንዶች ያደንቋት ነበር ፤ በእጃቸው
ለማስገባትም “ብዙ መላ” ሞክረዋል።(መንግስቱ ለማን የሚያውቅ አንድ ሌላ ሰው ከሜሪ ጋር
ስለነበረ ግንኙነት ምንም ባያውቅም፣ ነገር ግን አልማዝ ከምትባል አንዲት ሴት ጋር ድብን ያለ
ፍቅር ውስጥ እንደነበር ፤ እርሷ ግን ሐይለማሪያም ከበደን በማግባቷ መንግስቱ በጠና እንደታመመ
“በእርግጠኝነት” ያውቃል። ሐይለማሪያም ከበደ የግርማሜ ነዋይ ዘመድ በመሆኑ ይህ ጋብቻ
በመንግስቱናበግርማሜ መሀል ያለውን ፍጭት ጨመረው። በኮተቤ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት
ቤትም ሁለቱ አብረው ተምረዋል ፤ ከ1953ቱ መፈንቅለ መንግስት ሙከራ በፊት ኋላ የስዊዲሽ
288
ጥቋቁር አናብስት
ትምህርት ቤት በሆነው በራስ እምሩ ቤት ውስጥ ስለ ለውጥ ይከራከሩ ነበር ፤ “ስለ አብዮት ግን
በፍጹም አውርተው አያውቁም”፤ አንድ ምሽት ከሞቀ ክርክር በኋላ መንግስቱ በግርማሜ እና
በአጃቢዎቻቸው ከመደብደብ ለጥቂት ነው የዳኑት)
11) ዶክተር አክሊሉ ሀብቴ የቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ነበሩ። በቃለመጠይቁ
ወቅት ከዩኒቨርስቲው ተሰናብተው አለም ባንክ ውስጥ በመስራት ላይ ይገኛሉ። ዶክተር ደምሴ
ሀብቴ የተባሉ ታናሽ ወንድማቸው የህክምና ፕሮፌሰር እና ታዋቂ የህፃናት ሀኪም ነበሩ። ሌላ ታናሽ
እህታቸው ፈረንሳይ ውስጥ ሥነ ልቦና ያጠናች፣ ቁንጅናዋ የተመሰከረለት ሲሆን አንድ ናይጄሪያዊ
አግብታለች ፤ ይህ ድርጊት በዛሬይቱ ኢትዮጵያ እንደ “ተራማጅነት” ይቆጠራል።
12) ብርሀኑ ዘርይሁን የመንግስት ደጋፊ ለነበረው የመኢሶን ፓርቲ ቅርብ ወይም አባል እንደነበር
አሰፋ ይናገራል። ብርሀኑ ዘርይሁን ከስራ በኋላ እንደ ልማዱ ለመጠጣት ወደ መጠጥ ቤት ጎራ ሲል
ኢሕአፓዎች አዲስ ዘመን ላይ ለሚጽፈው ፕሮፓጋንዳ እንደ “ቅጣት” ጣቶቹን ሊቆርጡለት ይችሉ
እንደነበር ነገር ግን “ለሥነ ጽሑፍ ሲሉ” እጆቹን እንደማይነኳቸው ይነግሩት ነበር። የብርሃኑን
መጽሀፍ የማያደንቅ የለም፤ እነሱን ጨምሮ።
13) የሞተው አዲስአበባ ውስጥ ካሉ የቀበሌ እስር ቤቶች በአንደኛው ሳይሆን አይቀርም።
15) በሱ አቅም ማድረግ የሚችለው “የመልቀቂያ ፍቃድ” መጠየቅ ነው። ነገር ግን መልቀቂያው
ተቀባይነት ካላገኘ በ"ዲሞራሲያዊቷ" ኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ማድረግ የሚችለው ነገር
አልነበረም።
289
ጥቋቁር አናብስት
16) በ1978 ከእነዚህ ውስጥ አብዛኛዎቹ አባል ነበሩ፦ አፈወርቅ፣ መንግስቱ፣ ብርሃኑ፣ ዳኛቸው፣
ፍቃዱ፣ ሐይሉ አርአያ፣ መርዕድ፣ ታደሰ ታምራት፣ ተክለፃድቅ ወዘተ። አሰፋ፣ መንግስቱ፣ ብርሃኑ፣
ሐይሉ አርአያ እና ሌሎችም የአካዳሚው የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ጭምር ነበሩ።
290
ጥቋቁር አናብስት
ፀጋዬ ገብረመድህን
"ባለቅኔ፣ ጸሐፌ–ተውኔት፣ አዘጋጅ፣ የታሪክ ሥነ –ጽሑፍ
ተመራማሪ፣የጥቁር ኢትዮ–ግብፃውያን ጥንታዊየኪነጥበብ እሴት
የሥነ –ሰብዕ ባለሙያ"ፀጋዬ ገብረመድህንን ለመጀመሪያ ጊዜ
ያገኘሁትበ1965ዓም፣ በአዲስ አበባ "የፓን–አፍሪካኒስቶች"
ጉባኤ ላይ ጥናታዊ ጽሑፍ ሲያቀርብ ነው።በጊዜው፣ ከዚያ
በኋላም በተደጋጋሚም ረጅም ሰአት የፈጀ ቆይታ ኖሮን
ቢያውቅም፣ ሁሌም ሲያናግረኝ ገና ለመጀመሪያ ጊዜ እንደተገናኘን አድርጎ ነው።ለዚህ መጽሐፍ
ቃለ መጠይቅ ላደርግለት ቢሮው ስገኝም የገጠመኝ ይኼው ነው። ለቃለ–መጠይቁ ፍላጎት
ያደረበት ይመስላል፤ እኔም እቅዴን በሚገባ ከዘረዘርኩኝ በኋላ ሥነ –ጽሑፋዊ እንጂ ፖለቲካዊ
ዝንባሌ እንደሌለኝ ግልጽ አደረግኩኝ (በዛሬይቱ ኢትዮጵያ በነበሩት"ከሌሎች የበለጡ አንዳንድ
ሰዎች" ዘንድ ይህንን ማድረጉን ጠቃሚ ሆኖ አግኝቼዋለሁ)።"ፕሮጀክቴን" በተመለከተ ከሚገባው
በላይ ገለፃ በአንክሮ የሚሰማኝ ለመሰለኝ አድማጭ(በአትኩሮት ይመለከተኝ ስለነበር) ሳደርግ
ከቆየሁ በኋላ ከጨዋታችን ጋር ምንም በማይገናኝ መልኩ፣ "ግንኮ ስካንዲኔቪያዊ አትመስልም!"
የሚል አስተያየት ሰነዘረ። የጥበባዊ ሰብእናው መገለጥ ሳይሆን አይቀርም ብዬ ካሰብኩ በኋላ
የሕዝቦችን ብሔራዊ ባህርያት በተመለከተ ሚስጢራዊ በሚመስሉ ቃላት ተነጋገርን። ከተውኔቶቹ
በአንደኛው ውስጥ፣ ገፀ–ባህሪ ሆኜ ብቅ ሳልል አልቀርም የሚል ስጋት ስላደረብኝ፣ በሕይወቱ
ታሪክ ላይ ያሳደርኩትን ፍላጎት ያህል በስካንዲኔቪያዊ ነፍስያም ላይ እንዳሳደርኩ መስዬ ለመታየት
ጣርኩ። ነገር ግን ስለራሱ ከማውራት ይልቅ ስለ ኢብሰን ማውራት አሰኘው።ዋናውን ጉዳይ ትተን
ብዙ ስናንዣብብ ከቆየን በኋላ፣ የትምህርት መረጃውን በአግባቡ በዝርዝርመዝግቦ እንደሚያቆየኝና
ያ ጥሬ መረጃ ("እውነታ")፣ስለሱ አንዳች ምስል ለመቅረጽ እንደሚረዳኝ ቃል ገባ።በአማርኛ
የታተሙ ከእሱ ጋር የተደረጉ ሁለት ቃለ–መጠይቆችንም ጠቆመኝ።ካሁን በፊት ስለ ሕይወቱ እና
ሥነ–ጽሑፋዊ ሰውነቱ "ጉዞ" ለሌሎች ሰዎች ያጫወተውን ለእኔ እንዳይደግም፣"ስራ በጣም
ይበዛበታል"።
ሲጠየቅ ቋንቋን ማስፋትና ማበልጸግ የአንድ ደራሲ ሙያዊ ግዴታ እና ሐላፊነት መሆኑን
እንደሚያምን፣ ይህም ለዘመኑና ለዘመናዊው ሥነ ጽሑፍ የሚሆን ቋንቋ መፍጠርን እንደሚጨምር
ተናግሯል። ፀጋዬ ገብረመድህን በቀላሉ የሚያነቡት ወይም ሊለው የፈለገው በቀላሉ የሚገባ ደራሲ
አይደለም። ፀጋዬ እንደሌሎቹ የኢትዮጵያ ደራሲያን፣ ከግዕዝ ቋንቋ በመነሳት አዳዲስ ሀሳቦችን
ለማጎልበት፤ ሀገር በቀል ትርጉሞችን ለማመንጨት፣ ወይም ቃላት አቀናጅቶ አዲስ ሀሳብ
ለመፍጠርአይሞክርም ፤ ይልቁንም አዳዲስ የፈጠራቸውን ቃላት እየሰነጣጠቅኩ ወደ
እንግሊዝኛስመልሳቸው ትርጉማቸውን ለመገመት አስችሎኛል፦ ፀጋዬ አብዛኛውን ጊዜ፣
በእንግሊዝኛ እያሰበ ወይም ቃል በቃል ትርጉም እየፈለገ (ሀሳቡን በመተርጎም ፈንታ ቃሉን ቀጥታ
እየተረጎመ)የፈጠራቸው ይመስላል። እንግሊዝኛ "በፈሊጣዊ አነጋገሮች" የበለፀገ እንደመሆኑ
መጠን፣ በቀላሉ "በቀጥታ" ሊተረጎሙ የማይችሉ ቃላቱና ሀሳቦቹ ብዙ በመሆናቸው፣ እነዚህ
ቃላትና ሃሳቦች በአማርኛ ቋንቋ እንደገና ሲፈጠሩለጆሮ እንግዳ ሊሆኑ ይችላሉ። ይሁን እንጂ፣
በነዚህ ጉዳዮች ላይ ያለኝ ግንዛቤ አነስተኛ በመሆኑ፣ የኔን "አስተያየቶች" ማንም ከቁምነገር
ሊጥፋቸው አይገባም። ያም ሆነ ይህ ብዙ ኢትዮጵያውያን ፀጋዬ የፈጠራቸውን ቃላቶቹን ትርጉም
ለመረዳት ይታገላሉ። አንዳንዶች እንደሚሉት የፀጋዬ ተውኔቶች በመድረክ ተመልክተዋቸው
ካልሆነ አንብበዋቸው አይገቡም። ይሄ የግጥሞቹም ባህሪ ነው፦ አንባቢው ለብቻው ሆኖ
ከሚያነባቸው ይልቅ ፀጋዬ ራሱ ሲያነባቸው ህያው ይሆናሉ።
292
ጥቋቁር አናብስት
እናቱ ቤታቸው ሲቃጠል ከእሳቱ ስላዳናቸው ለቦዳ አቦ ፀጋዬን ተሳሉ። በዚህ ስለት መሰረት ፀጋዬ
ቄስ ወይም መነኩሴ መሆን ነበረበት።2 ነገር ግን አባቱ ከዘመቻው ተመልሰው ቤተሰቦቻቸውን
ሲቀላቀሉ፣ ፀጋዬን በተመለከተ ሌላ እቅድ ነበራቸው፦ፀጋዬ ተምሮ የመንግሥት ሠራተኛ እንዲሆን
ፈለጉ።
አንደኛ ደረጃን በ16 ዓመቱ በጥሩ ውጤት ካጠናቀቀ በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ "በዝነኛው"
ዊንጌት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገባ። ነገር ግን የፀጋዬ ምኞት "የቲያትር ጥበባት" ማጥናት
ነበር፤ይሁን እንጂ እንደዚህ ዐይነት ትምህርት ቤት ባለመኖሩ የንግድ ስራ ትምህርት ቤት ገብቶ፣
ቲያትር ቤት ለማስተዳደር የሚያበቃውን የአስተዳደር ትምህርት ለመማር ፈለገ። ርእሰ መምህሩን
"ጨቅጭቆ" አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኝ፣ ሁለተኛ ደረጃ የንግድ ትምህርት ቤት ገባ። ከዚያ
ከተመረቀ ከአንድ ዓመት በኋላ በ1948 ዓ.ም "በልግ" የተሰኘውን ተውኔት በቀዳማዊ ኃይለ
ሥላሴ ትያትር ቤት (ኋላ ብሔራዊ ቲያትር) አቀረበ። በተመሳሳይ ዓመት "የሾህ አክሊል" የተሰኘ
ሌላ ተውኔት ጽፎ ከአንድ ዓመት በኋላ በዚሁ ትያትር ቤት አቀረበ ፤በ1951ዓም ደግሞ ታተመ።
293
ጥቋቁር አናብስት
በ1951 ዓ.ም ፀጋዬ በቺካጎ ከሚገኘው ብላክስቶን የህግ ትምህርት ቤት የመጀመሪያ ዲግሪውን
ተቀብሏል።ከዚህ በቀደመ ወቅት በኢትዮጵያ አለመኖሩን ወይም ጉዞ ማድረጉን ባለመጥቀሱ
ትምህርቱን የተከታተለው በርቀት ሳይሆን አይቀርም፤የሚያውቁት ሰዎችም ይህንን ሀሳብ
ያጠናክራሉ።ከዚያ የዩኔስኮን ነፃ የትምህርት እድል በማግኘቱ ከ1951–1952 ዓ.ም የለንደን
ሮያል ቲያትርና የፓሪስ ኮሜዲ ፍራንሴን ጎብኝቷል፤ወደ ዊንድሶር ሮያል ቲያትርና የሮም ኦፔራ
አዳርሽም አጭር ጉብኝት አድርጓል። የዚህ ሁሉ ጉዞ አላማ "ኤክስፐርመንታል" ቲያትር ለመማር
ነው።
ፀጋዬ ብዙ ትልልቅ የሚባሉ ስራዎች ነበሩት። ከ1953–1963ዓም ድረስ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ
ቲያትር (ኋላ ብሔራዊ ቲያትር) ዳይሬክተር የነበረ ሲሆን፣ ከ1959–1966ዓም (የአብዮቱ ፍንዳታ
ድረስ) ደግሞ የዚሁ ቲያትር ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ሆኖ ሰርቷል። ከ1967–1968 ድረስ
294
ጥቋቁር አናብስት
በባህልና ስፖርት ሚኒስትር ቋሚ ፀሐፊ ነበር። በ1969 በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የትምህርት ክፍል
ተባባሪ ፕሮፌሰር ነበር። በዚህ ውይይታችን ወቅት (1980 ዓ.ም)የባህል ሚኒስቴር አማካሪ ነበር።
በፀጋዬ ተውኔት ድርሰቶቹ፣ በግጥም ጽሑፎቹ፣ በአፍሪካ ባህል ጥናትና ምርምሩ ሙሉ ለሙሉ
የተዋጠ ይመስላል።የሚያውቁት ሰዎች ሲናገሩ፣ በጨዋታ ወቅት "ከመስኩ" ውጪ ያሉ አርእስቶች
ሲነሱ የመጫወት ፍላጎቱ ይጠፋል።የሥነ ጽሑፍ ውጤቶቹ ብዛት አስደናቂ ነው፤ ይሁን እንጂ
የአፍሪካ ቅድመታሪክ ጥናቶቹ ግምታዊ ስለሚሆኑብኝየማያሳምኑ ሆነው ባገኛቸውም፣
የሚያነሳሱትን ርእሰ ጉዳይ በተመለከተ፣ የእሱን አመለካከት መስማት ግን ደስ ይላል።
ፀጋዬ ገብረመድህን ባለትዳርና የሶስት ልጆች አባት ነው። ረዥም፣ በራው ከፊቱ ገለጥ ያለ፣ ቀጭንና
የስኳር ህመም ታማሚ ነው። ብዙ የሥነ ጽሑፍ ስብስቦችወይም የደራሲያን ማኅበሮች አባል ነው።
በብዛት የፃፈ፣በእጅጉ የተጓዘ ደራሲ ሲሆን ለሥነ ጽሑፋዊ አስተዋጽኦው ተመጣጣኝ የሆኑ ዳጎስ፣
ዳጎስ ያሉ በርካታ ሽልማቶችን ተቀብሏል።ከአውራ ኢትዮጵያዊ ደራሲያን አንዱ ነው።
295
ጥቋቁር አናብስት
ማስታወሻ(የደራሲው)
የተርጓሚ ማስታወሻ የብላቴንጌታ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን (1929-93) ዓ.ም የተላያዩ ስራዎቹ
ደጋግመው የታተሙ ሲሆን የተላያዩ ጸሐፍት ግለታሪኩን ጽፈውታል፡፡
ማስታወሻዎች
1) ቀኑን የነገረኝ ፀጋዬ ራሱ ነው። ነገር ግን በሌላ አጋጣሚ የተወለደው በ1929 ዓ.ም እንደሆነ
ተናግሯል፣ ጽፏልም። ይህ ግን እንግዳ ነገር ነው። በአውሮፓውያን አቆጣጠር ከተቀመጠው ቀን
ጋር ይጋጫል። አንድ ምንጭ ፀጋዬ የተወለደው ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ከወረረች ከስድስት ወር በኋላ
መሆኑን ገልፆ ነበር።
2) ፀጋዬ ይህን ታሪኩን ሲናገር ቃልኪዳኑ በሀዲስ አለማየሁ "ፍቅር እስከ መቃብር" ውስጥ ዋና ገፀ
ባህሪው ላይ ከሚደርስበት ነገር ጋር ተመሳሳይ መሆኑን አስተውሏል።
296
ጥቋቁር አናብስት
መንግስቱለማ
የቧልታይ ተውኔት ፋና ወጊ፣ ፀሐፌ–ተውኔት እና
ገጣሚ በንጉሱ ዘመን ተማሪዎች በተደጋጋሚ የአቤ ጉበኛን
ስራዎች ማንበቤን ይጠይቁኝ ነበር። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን
የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ እንደምከታተል የሚያውቁ
ኢትዮጵያውያን የሚጠይቁኝ የመንግሥቱ ለማ ስራዎችን
ማንበቤን ነው። መንግስቱ ከ1966ቱ አብዮት በፊትም ሆነ በኋላ በግጥምም ሆነ በተውኔት በደንብ
ከሚታወቁ ኢትዮጵያዊ ደራሲያን መሀል አንዱ ነው። ብዙዎች ቅኔን ለማብራራትና ለማሳተም
ያደረገውን ጥረት ያደንቃሉ።
የመንግሥቱ ለማ ሁለት ቀደምት ተውኔቶች ቧልታይ ነበሩ። ይህ የሥነ ጽሑፍ ዘውግ በኢትዮጵያ
የተለመደ አይደለም ። እነዚህ ሁለት ተውኔቶች “ላይ ላዩን” ሲታዩ ስለ ጋብቻ ይመስላሉ።
ርእሳቸውም (“ጠልፎ በኪሴ” እና “ያላቻ ጋብቻ”) ይህንን አመላካች ነው። ነገር ግን ተውኔቶቹ
ከጋብቻ ባሻገር ጥልቅ ጉዳዮችንም ይዳስሳሉ። ሁለተኛው ተውኔት በመደብ ልዩነት ውስጥ
የሚፈጠር ጋብቻን የሚያሳይ ነው፦ ከተለያየ መደብ የመጡ ጥንዶች ጋብቻ “ተቀባይነት” አለው?
እነሱስ ደስተኛ ይሆናሉ? ስለ“መደብ ልዩነት” በግልጽና በቀጥታ ማውራት በማይቻልበት ወቅት
መንግስቱ ለማ ቧልትን ተጠቅመው ጥያቄውን በተዘዋዋሪ መንገድ አንስተዋል።በነፃነት
የማይነገረውን፣ የማይተቸውንና ማህበረሰቡን ውስጥ ውስጡን ያኘከውን እውነታ የሳቅና የመዝናኛ
ምንጭ አድርጎታል። መንግስቱ ይህንን ለማድረግ ባህላዊውን የኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ አብጠርጥሮ
ማወቁ እጅጉን ጠቅሞታል። ተውኔቱ ብዙ ትርጉም እንዲሰጥ አድርጎ መፃፉን ተክኖበታል። ፍፁም
ቀልድ መስሎ የሚታየው የተሰወረ “ጥልቅ” ትርጉም ነበረው። ቀጥተኛውም ትርጉምም ቢሆን ያንኑ
ያህል አስፈላጊ ነው። የዘመኑ ወጣቶች ማንን፣ እንዴት ባለ ሁኔታ ማግባት እንዳለባቸው ሞቅ ያለ
ክርክር አካሂደዋል ።ተምረናል የሚሉት አንዳንዶች “ዘመናዊ” ሚስቶችን ሲመርጡ፣ መንግስቱ
ለማን ጨምሮ ሌሎቹ፣ ከ“ባእድ ባህል” ይልቅ ኢትዮጵያዊ ስርአትን ያስበለጡትን ይመርጡ ነበር።
ለነገሩ “ባእድ ባህል” የተባለውም ቢሆን፣ ያን ያህል ሥልጣኔ የዘለቀው አልነበረም።
መንግስቱ“ለማህበረሰቡ ታይታ” ሲባል የሚደረገውን የተንቀላጠጠውን የኢትዮጵያ የሰርግ ሥነ
ስርዓት፣ ከሚቃወሙት መሀል አንዱ ነበር።
297
ጥቋቁር አናብስት
****
በትርፍ ጊዜው በሸክላ አፈር የተለያዩ እንስሳትን፣የአእዋፍን እና የሰዎችን ምስል መቅረጽ፣ በውሃ
ቀለምም ሆነ በባለቀለም እርሳሶች ምስሎችን የመንደፍ ሥነ ጥበባዊ ዝንባሌዎች ነበሩት።
በሐረር የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን ከጨረሰ በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ኮተቤ በሚገኘው
የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ የለንደን ኮሌጅ
መግቢያ ፈተና ተፈትኖ አለፈ። ከዚያ ወደ እንግሊዝ ተሻግሮ የሥነ ማህበረሰብ፣ የፖለቲካ ሳይንስ
እና ኢኮኖሚክስ ትምህርቱን በለንደን ዩኒቨርስቲ የኢኮኖሚክስና የፖለቲካ ሳይንስ ትምህርት ቤት
ተከታተለ። መንግስቱ ዩኒቨርስቲው በጊዜው “የስርነቀል ምሁራን ማፍሪያ” ነበር ይላል። ለአንድ
ዓመት ያህል በለንደን ኢኮኖሚክስ ትምህርት ቤት የታዋቂው ፖለቲካል ሳይንቲስት እና የሶሻሊስት
ሀሮልድ ላስኪ ተማሪ ነበር። ላስኪ ተማሪዎቹ ላይ ጉልህ ተጽእኖ በማሳረፍ ይታወቃል።
መንግስቱም ስርነቀል ዝንባሌዎችን የወሰደው ከዚህ አስተማሪው እንደሆነ ይናገራል።
መንግስቱ ከተማሪነቱ ባሻገር በታላቋ ብሪታንያ፣ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር ውስጥ ንቁ አባል
እና የማኅበሩ ጋዜጣ The Lion Cub አዘጋጅ ነበር። ኋላ የማህበሩ ፀሐፊ ብሎም ፕሬዚዳንት
እስከመሆን ደርሷል። የውጪ ሀገር ቆይታው እና ተሞክሮዎቹ በ1955 የግጥም ጉባኤ በሚል ርእስ
በታተመው መጽሐፉ በሥነ ግጥም መልክ ተከስተዋል።ከስድስት ዓመት የውጪ ሀገር ቆይታው
በኋላ መንግስቱ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ ሀገሩን ለማገልገል ተዘጋጀ።
****
የመጀመሪያ ስራው በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን፣ የስታትስቲክስ ክፍል ሐላፊነት ነበር። ከዚያ
በኋላ ለብዙ ዓመታት የሰራው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር ሲሆን፣ በመጀመሪያ ስራው ሕንድ፣
299
ጥቋቁር አናብስት
ከዚያ ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ተዛወረና የአማርኛ ቋንቋ አካዳሚ ዋና ፀሐፊ ሆነ። ከ1966
አብዮት በኋላ የባህል ሚኒስቴር ሲቋቋም የአማርኛ ቋንቋ አካዳሚ ወደ ኢትዮጵያ ቋንቋዎች
አካዳሚ እንደገና በዚሁ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ስር ሆነ። መንግስቱም የዚሁ አካዳሚ ዋና ፀሐፊ
ሆነ። ከዚህ ባሻገር ጊዜያዊ ወታደራዊ የደርግ አስተዳደር ባቋቋመው ጊዜያዊ የመማክርት ሸንጎ
ውስጥ እንዲያገለግል በባህል ሚኒስቴር ሰራተኞች ተመርጦ ለአንድ ዓመት ከስምንት ወር አገለገለ።
በኋላ በሥነ ጽሑፍ ጉዳዮች ኤክስፐርትነት ወደ ባህል ሚኒስቴር ተመለሰ።
300
ጥቋቁር አናብስት
ከዚህ በፊት እንደተቀመጠው የመንግሥቱ ቀደምት ተውኔቶች ቧልት ቀመስ ናቸው።ሆኖም “ቁም
ነገር አዘል” ቀልዶች እንጂ ስላቅ/ሽሙጥ አልነበሩም።ምፀትን ወይም ግነትን ሳይጠቀም የኑሮን
እውነተኛ ገጽታ ለማሳየት እንደሞከረ ይናገራል። እንዲያውም ራሱን በህልም ሳይሆን በማህበራዊ
ሂስ እንደተጠመደ “ሪያሊስት” አድርጎ ይቆጥራል። በቴክኒክ ረገድ ተጽእኖ ያሳረፋበት ሞሊየር፣
ጎጎል፣ ኢብሰን እና ጆርጅ በርናርድ ሾው ናቸው ይላል። ቧልታይ ተውኔቶቹ ማህበራዊ እንከኖችን
ነቅሶ ለማውጣት የሚታትሩ ተራማጅና ለውጥ ናፋቂ ናቸው። የተውኔቶቹ ነገረ–ጉዳይ ጋብቻ
ቢሆንም፣ ጭብጣቸው ግን ከዚያም ላቅ ያለ መሆኑን ከአብዮቱ በኋላ ተናግሯል።
ከውጪ እንደተመለሰ፣ የጋብቻ ጉዳይ ችግር ሆኖ ጠበቀው። አንዳንዶች ለፍቅር ብለው ቢያገቡም፣
አብዛኛዎቹ ወንዶች ግን ሃብትና የኑሮ ደረጃን ለጋብቻ እንደ ቅድመሁኔታ ያስቀምጣሉ። መንግስቱ
በሁለቱ ተውኔቶቹ የኑሮ ደረጃን ወደጎን ብለው ለፍቅር ያገቡትን ያገናቸዋል።በወቅቱ ይህ እንደ
“አብዮታዊ” የሚባል አቋም ነበር ይላል። በመንግስቱ አመለካከት እነዚህ ሰዎች በኢትዮጵያ ውስጥ
የእውነተኛ ጋብቻፋና ወጊዎች ነበሩ። ከእንደዚህ ዐይነት ሰዎች መሀል አንዱ ባህሩ ነው። ባህሩ
ከመኳንንት ወገን የተወለደ፣ "ያላቻ ጋብቻ" የተሰኘ ተውኔቱ ዋና ገፀባህሪ ነው። ባህሩ በሚስጥር
የቤት ሰራተኛውን ማግባቱን ተከትሎ የሚመጣውን ማህበራዊ ጣጣ በጀግንነት ሲታገል ይታያል።
ደራሲው እንደሚለው በተውኔቱ ለማስተላለፍ የተፈለገው “ጥልቅ” መልእክት “በነባሩና በአዲሱ፣
በልማዳዊውናአዲስ በሚፈጠረው እሳቤ መሀል ያለው የማያቋርጥ ግጭት የሚወልደውን
ማህበረሰብ አቀፍ ለውጥ አስፈላጊነት ማሳየት ነው”ይላሉ፡፡
301
ጥቋቁር አናብስት
"ጠልፎ በኪሴ" የተሰኘው ተውኔት ያልተለመደ ባይሆንም፣ ትንሽ ወጣ በማለት ሚስት ለማግኘት
በሚደረግ ድርጊት፣ ማለትም በጠለፋ ዙሪያ የሚያተኩር ነው። ጠለፋ በኢትዮጵያ ባህል አዲስ ነገር
ባይሆንም ተውኔቱ ግን አዳዲስ ነገሮችን አካቷል። ጠላፊው፣ ጓደኞቹና ተጠላፊዋ ሁሉም ከተማ
ያደጉ፣ የተማሩ ወጣቶች ናቸው። ደራሲው በተውኔቱ “ተምረው ከወሬ ያለፈ ጠብ የማይል፣
ስርነቀል ለውጥ ሊያመጡ ያልቻሉ ወጣቶችን” ይተቻል። የተውኔቱ ዋና ገፀባህሪ በዛብህ ለማሳካት
ያለመው ነገር መና ሆኖ ቢቀርም “ሙከራው መደነቅ አለበት ፤ ቢወድቅም ለተከበረ አላማ ነው”
ጨምሮም መንግስቱ “ ዋና ገፀባህሪዬ ሁሌም ማህበራዊ ለውጥ ለማምጣት የሚታትር ነው”
ይላል። ስለ ሁለቱ ተውኔቶቹ ደግሞ እንዲህ ይላል፦ "በዛብህ እና ባህሩ ( የሁለቱ ተውኔቶች ዋና
ገፀባህሪያት)ፍፁም እኔነቴን የሚገልጡ ናቸው፤መሰረታዊ አመለካከቴ በነሱ አማካይነት ስጋ ለብሶ
ይታያል። ሁለቱም ተውኔቶች በአንድ ጭብጥ ዙሪያ/ይሽከረከራሉ//ላይ/ያተኩራሉ፦ በነባር እና
መጤ መሀል ስላለው የማያቋርጥ ግጭት።"
የአጻጻፍ ዘዬውን በተመለከተ ሁለቱን ዋና ተነጻጻሪ የቅኔ ዘውጎችን ካወዳደረ በኋላ የበለጠ የሳበውን
መንገድ እንደመረጠ ይናገራል። የዋድላ ቅኔ አስተምህሮ በቀላሉ ሊረዱት የሚችሉት ቅኔ ብዙም
ረብ የለውም ይላል። የዚህ ዐይነቱ ቅኔ ወዳጅ ፍልሱፋን"የቅኔ ውበቱ ስውርነቱ" መሆኑን
በመግለጽ ሽንጣቸውን ገትረው ይከራከራሉ። ሌላኛው የቅኔ ዘውግ (የጎንደሩ)የዚህ ፍፁም ተቃራኒ
ነው። ለነሱ ጥሩ ቅኔ የሚባለው “ቀላል ሆኖ ረቂቅ፣ ግልጽ ሆኖ ድንቅ ሲሆን ነው። በዚያው ልክ
ጥልቅና ቁምነገር ያዘለ መሆን አለበት ባይ ናቸው።” መንግስቱም ሆነ አባቱ ይህንን የጎንደር ዘውግ
ተከትለዋል፤ለዚህም ግጥሞቹ እና ተውኔቶቹ ምስክር ናቸው። የአባቱን የንግግር ለዛ “ግልጽና
የአድማጮቻቸውን ቀልብ በቀላሉ የሚገዛ በመሆኑ” ይወደዋል። “ቀላልና የነጠረ ሃሳብ እና ቋንቋ
ማዳበር መቼም ጠንክሮ መስራትን ይፈልጋል፤ የተሰወረ ሁሉ በቀላሉ እንዲታይ አልተለፋበትም”
ስለዚህ መንግስቱ የግዕዝ ቃላትን በአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ውስጥ አለቅጥ በመጠቀም እዩኝ እዩኝ
የማለት አባዜ አይዋጥላቸውም። የአንድ ፀሐፌተውኔት ቀዳሚ አላማ ተደራሲያኑ በቀላሉ
እንዲረዱት ማድረግ ነው። ተውኔት እንደ ሥነ ጥበብ ዘርፍ ለሽሽግነት አይመችም። ስለዚህ
የተውኔት ቋንቋ ረቂቅ፣ ግን ለመረዳት ቀላልመሆን አለበት።” በተውኔት ውስጥ ሴራው እና
ቀልዳቀልዱ“የተሰጥኦ ጉዳይ” ቢሆንም መንግስቱ ይህንን ተሰጥኦ የታላላቆቹን ከያኒያን ስራ
በማጥናት ማበልፀግ ይቻላል ብሎ ያምናል። በቴክኒኩ ውስጥ ስሌት፣በኪነጥበብ ውስጥ ደግሞ
ሙያ አለ። ( መንግስቱ ይህንን አመለካከቱን የገለፀው ከ1966ቱ አብዮት በኋላ በጣም ቆይቶ
በመሆኑ፣ እነዚያ ቅድመ–አብዮት ሁለት ቧልታይ ተውኔቶቹን በፃፈበት ወቅት እነዚህ ሀሳቦች ምን
302
ጥቋቁር አናብስት
ያህል ጥርት ብለው አእምሮው ውስጥ እንደነበሩ አላውቅም። እነኚህ አመለካከቶች ለ"አዲሱ
ዘመን" በልኩ የተሰፉ በመሆናቸው፣ የሰዎች ሕይወት በፃፉት ነገር ምክንያት አደጋ ላይ
በሚወድቅበት ዘመን ጠቅመውታል)
303
ጥቋቁር አናብስት
***
መንግስቱ “ተውኔትና ግጥም በተፈጥሮ የተቆራኙ ስለሆኑ ሁለቱ የሥነ ጽሑፍ ዘርፎች አብረው
ይሄዳሉ፤ድራማ የሚጽፍ ደራሲ ግጥምንም ሆነ ተውኔትን በስንኝ መሰደር ይችላል” ብሎ ያምናል።
***
304
ጥቋቁር አናብስት
***
መንግስቱ ለማ ሐምሌ 27 1980 ዓ.ም ልክ ከቀኑ 12:00 ሰአት ላይ ሞተ። እንደወዳጆቹ ከሆነ
ላለፉት 15 ዓመታት በሪህ በሽታ ተሰቃይቷል፤ለዚህ ህመሙ ማስታገሻ ከባድ መድሀኒቶችን
ይወስድ እንደነበርም ጨምረው ይናገራሉ።ስለዚህ እነኚህ ህመም ማስታገሻዎች ጉበቱንና ኩላሊቱን
ሳይነኩት እንዳልቀረ ይገምታሉ።እስከ ሕይወቱ መጨረሻ ድረስ የቤት ሠራተኛ እንኳን
አልነበረውም፤ ስለምግቡ እና ጤንነቱ መጨነቅም አቁሞ ነበር። በተጨማሪም ከመሞቱ ከሶስት
ዓመት በፊት አቆመው እንጂ በጣም ይጠጣ እንደነበርም ሰምቻለሁ።መንግስቱ እያገገመ እያለ
ኬንያ ነበርኩ ፤ ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ህመሙ አገረሸበትና ስመለስ መሞቱ ተነገረኝ። በሞተበት
305
ጥቋቁር አናብስት
ቀን በአስር ሰአት አካባቢ ጠያቂዎች አነጋግረውታል፤ነገር ግን ከሁለት ሰአት በኋላ ሐኪሙ ሁሉም
ነገር እንዳበቃለት ተናገረ። እንደ ኤድዋርድ ኡለንዶርፍ እና ሪቻርድ ፓንክረስት ያሉ ጓደኞቹ ወደ
እንግሊዝ ሄዶ ኩላሊቱ የሚቀየርበትን ሁኔታ ቢያመቻቹለትም፤በጥቁር አንበሳ በቂ የኩላሊት
እጥበት ባለመኖሩና ኩላሊት የሚሰጥ ሰው ባለመገኘቱ ሳይሳካ ቀረ።
***
የነበሯት "የነቁ" ማርክሲስቶች በጣም ጥቂት ነበሩ። በጊዜው የተሳካ መፈንቅለ መንግስት ወይም
አብዮት ቢካሄድ፣ ስልጣን ላይ የሚወጡት ሰዎች ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ ያላቸው ብቸኛ
አማራጭ የኮሚኒስታዊ ሀገሮችን እርዳታ መሻት ነው ፤ በወቅቱ ይህንን ዐይነት ድጋፍ ማድረግ
የምትችለው ብቸኛ ሀገር ደግሞ ሩስያ ወይም አንዳንድ ኢትዮጵያውያን እንደሚጠሯት "መስኮብ"
ነበረች። መንግስቱ የሶሻሊስት ርእዮተ አለምን ሳይቃወም፣ እንደ አንድ ሀገር ወዳድ ብኄርተኛ፣
ትንሽ የሶሻሊስቶች ጥርቅም፣ ከውጪ ትእዛዝ እየተቀበሉ ሀገሪቱን ማስተዳደራቸው ላይዋጥለት
ይችላል። ይሄ ሁሉ የራሴ ግምት ብቻ ባይሆን በወረቀት ሳላሰፍረው አልቀርም ነበር። ይህንን
ለመንግስቱ ስገልጥለት፣ “በትክክል!” ብሎ ስለመለሰለኝ የኔን ትርጓሜ መቀበሉን አረጋገጠልኝ።ይህ
ታዲያ መጽሀፌ ላይ የፃፍኩትን ከመደገፉም በላይ በወቅቱ መንግስቱጋዜጣው ላይ ይህ ተራ የፍቅር
ግጥም ከመሆኑ የዘለለ ሚና የለውም ብሎ የፃፈውን ያፈርሳል።7 ስለዚህ እሱ የፃፈውን ከቁምነገር
እንዳልቆጥረውና በዛሬይቱ ኢትዮጵያ8 በነበረው ሁኔታ ምክንያት ሕይወቱንና ደህንነቱን
ለማስጠበቅ ሲል የፃፈው መሆኑን ገለፀልኝ። አሁን ሳያምነኝ አልቀረም፤አለበለዚያ ይህንን ሁሉ
ባልነገረኝ ነበር። መንግስቱ ጠንቃቃ እና ተጠራጣሪ ሰው ነበር።ከእኔ ጋር ቃለመጠይቅ ለማድረግ
ከመስማማቱ በፊት በስልክ ብዙ አውርተናል። ልጠይቀው ያሰብኩትን ጥያቄዎች በወረቀት ላይ
እንድጽፋቸው አደረገና በሌላ ሰው አማካኝነት ላኩለት። በኋላ በኢትዮጵያ እንደ ትልቅ የወዳጅነት
መግለጫ የሚቆጠረውን አብሮ ማዕድ የመቁረስ ሥነ ስርዓት ስንካፈል አሁን በመተማመን በጋራ
ጉዳዮች ላይ ከልብ እንደምናወራ እርግጠኛ ሆንኩ። ነገር ግን ጥርጣሬውን ዳግም ሊያነሳሱ
የሚችሉ "ስሜትን የሚነኩ" ጥያቄዎችን ማንሳት አስፈራኝ። የግል ጉዳዮችን የሚመለከቱ ብዙ
ጥያቄዎችን ብጠይቀው ደስ ባለኝ ነበር፤ ለምሳሌ ስለ አስተሳሰብ ለውጡ፣ የሚወዳቸውና
የሚጠላቸው ነገሮች፣ በተለያየ ጉዳዮች ላይ ስላለው አመለካከት ወዘተ። ነገር ግን ይህ የሚሆን
አልነበረም።
307
ጥቋቁር አናብስት
አማረ ማሞም መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ዘመናዊ አማርኛ የሚተረጉመው የዚህ ኮሚቴ አባል ነበር።
ለረጅም ጊዜ መንግስቱ ጀምሮት የነበረውን የግል ግለ ታሪኩን መጽሀፍ እንዲጨርስ ጎትጉቶታል ።
ለመጨረሻ ጊዜ ሆስፒታል ከመግባቱ ሁለት ወር ቀደም ብሎ መንግስቱ አማረን ቤቱ ምሳ
ይጋብዘውና ያለቀውን ረቂቅ ያሳየዋል።አማረ ይህ ረቂቅ በግምት ከ300–400 ገጽ ይሆናል ይላል።
(የአማረ ማሞን የሕይወት ታሪክ በዚሁ መጽሀፍ ታገኙታላችሁ) መንግስቱ መጽሐፉ አልቋል ነገር
ግን አንዳንድ ነገሮችን መከለስና ማስዋብ ይቀረኛል ብሎ ነበር። ይህ ረቂቅ መንግስቱ ከሞተ በኋላ
ቤተሰቦቹ ( ልጆቹን እና የጥንት ሚስቱን ጨምሮ) ከሚጣሉበት ነገሮች መሐል ጠፍቶ እንደማይቀር
ተስፋ አደርጋለሁ።10ስለ ኢትዮጵያ ባህል እና ሥነ ጽሑፍ ብዙ የሚያስደስቱ ጨዋታዎች አካቶ
ሊሆን የሚችል ይመስለኛል። በሌላ በኩል በሌላ ቦታ እንደነገሩ የተገለፁ ነገሮች ተደባብሰው
ይቀራሉ። መንግስቱ ከዳግማዊ ሚኒልክ ጋር ዝምድና እንዳላቸው ጠቀስ አድርጓል፤ሌሎች ሰዎች
ይህንኑ ቢያረጋግጡልኝም መረጃው ግን አስተማማኝ አልነበረም። የጉራጌ ዘር እንዳለበት ተናግሮ
ካለማወቁም በላይ ስለዚህ የነገረኝ ዘመዱ ጭራሽ እንዳላነሳበት አሳሳበኝ። አለበለዚያ ሊከፋና ይህ
ዘመዱ ሆን ብሎ እሱን ለመጉዳት አስቦ እንደነገረኝ ሊያስብ ይችላል። ነገር ግን ለጓደኛው ሚካኤል
እምሩ ይህን ጉዳይ ሳነሳበት፣ መንግስቱ የዘር ጉዳይ ብዙም እንደማያስጨንቀው አረጋገጠልኝ ፤
እኔም በዚህ ሀሳብ እስማማለሁ። ስለዚህ ዘመዱ የነገሩኝን ነገር መንግስቱን ለመጉዳት ሳልሞክር
እንደሚከተለው አቀርባለሁ።
***
የመንግሥቱ ቅድመ አያቶች ወሎ ውስጥ በላስታ ሸደሆ፣ አቡነ አሮን ቤተክርስቲያን አካባቢ
በምትገኝ መቄት11 በምትባል ትንሽ መንደር ገበሬዎች ነበሩ። አያቱ አቶ ሐይሉ ወልደታሪክ እዚህ
ቤተክርስቲያን አካባቢ ሲኖሩ በቤተክርስቲያን ትምህርት ቤት ፊደል ቢቆጥሩም ገፍተው
ሳይሄዱበት ገበሬ ሆነው ቀሩ። ከሀይሉ ልጆች መሀል አንዱ ለማ ከሀይሉ በቤተክርስቲያን ትምህርት
308
ጥቋቁር አናብስት
መጀመሪያ በአቡነ አሮን፣ ቀጥሎ በጎንደርና በጎጃም ዲማ ተማረ (የሀይሉ ዝርያ ከጎጃም ሁሉ
ይመዘዛል) ቀጥሎ ለማ የአንኮበሩ አለቃ ሀይለማርያም ዘንድ ይማራል። ከዚያ ሐይለማሪያም
የአንጎለላ ኪዳነምህረት አለቃ ሆነው ሲሾሙ እርሳቸውን ተከትሎ ሄደ።12 ለማ ትምህርታቸውን
ከጨረሱ በኋላ ወይዘሪት አበበችን አገቡ። የአበበች አባት ተጉለቴ ሲሆኑ፣ እናቷ የባሻ ተጎዳ ልጅ
ናቸው። ባሻ ተጎዳ ጉራጌ ሲሆኑ ስራቸው ኮርቻ ማበጀት ኋላም ለዳግማዊ ምኒልክ ኮርቻ የሚሰሩ
ሰዎችን መቆጣጠር ነበር። ለማ እና አበበች ስምንት ልጆች ሲያፈሩ ከነዚህ መሀል ስድስቱ ወንድ
ሁለቱ ደግሞ ሴቶች ነበሩ። ነገር ግን ሁሉም መንግስቱን ቀድመው ሞተዋል። ወንዶች ልጆቹ
የሚከተሉት ናቸው፦ መአዛ–ክርስቶስ የተባለው ብልህ እና ዝምተኛ ሲሆን በጽሕፈት ሚኒስቴር
ይሰራ ነበር ፤ ጥቂት መጽሐፍትንም ጽፏል ፤ ሁለት ጊዜ አግብቷል ( ከመጀመሪያዋ ሚስቱ ጋር
በፍቺ ሲለያዩ ሁለተኛዋ እስከ 1980 ድረስ በሕይወት ነበረች)፤የሞተው በስኳር በሽታ ነበር ፤
ከሁለቱም ሚስቶቹ ልጆች ወልዷል። ልሳነ–ክርስቶስ እስከለተ ሞቱ በሐረር ኖሯል።መርሐ–
ክርስቶስ በአዲስ አበባ የተማረ የሥነ ህንጻ ባለሙያ ሲሆን፤አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ፈረንሳይኛ፣
ጣልያንኛ እና እንግሊዝኛ ይናገራል ፤ የሞተው ከአብዮቱ በፊት በመጠጥ ጠንቅ ነው።13 ገብረ–
ክርስቶስ ከአብዮቱ በፊት ሞቷል። ቀጥሎ የተወለደው መንግስቱ ሲሆን ትክክለኛ ስሙ መንግስተ–
ክርስቶስ ነበር። የቀረውን አንድ ወንድ ልጅና የሴቶቹን ስም ለማወቅ አልቻልኩም። ከሁሉም
ረዥም እድሜ የኖረው መንግስቱ ነው።
የመንግስቱ ዘመድ አባቱ አለቃ ለማ ሀይሉ ስለፃፉት አንድ ግጥም አጫውቶኝ ነበር። በአንድ
አጋጣሚ አለቃ ሀይሉ አዳልጧቸው ይዘውት የነበረው ባለ እንጨት ክርታስ ዳዊትላይ ይወድቁና
ጎድናቸውን ክፉኛ ይጎዳሉ። ከዚያም የሚቀጥለውን ስንኝ ደረደሩ፦
መንግስቱ ለማ ዝነኛ ሰው ቢሆንም፣ ጓደኞቹ በጣት የሚቆጠሩ ናቸው ። እነዚህ ጥቂት ጓደኞቹ፣
ለጓደኝነታቸው ትልቅ ግምት የሚሰጡ ነበሩ።
309
ጥቋቁር አናብስት
ማስታወሻዎች
2) በጽሑፍ ካገኘኋቸው መረጃዎች ጠብሰቅ ያለው መንግስቱ ለአካሉ ጌታነህ ሰጥተውት በማባዣ
የተዘጋጀቃለመጠይቅ ነው( ይህንን ቃለምልልስ ከመንግስቱ ጋር በማደርግበት ወቅት አካሉ በአዲስ
አበባ ዩኒቨርስቲ መምህር ነበር) ሆኖም ከዚህ ምንጭ አንዳንድ ማስታወሻዎችን ከወሰድኩ በኋላ
መንግስቱ የኔን ማስታወሻ ማየት ፈለገ። ከዚያም አንዳንዶቹን ሲያርም፣ ሌሎችን ደግሞ በአዳዲስ
ቃላት ተክቶፃፋቸው። ስለዚህ ከአካሉ ጌታነህ ከተዋስኳቸው ላይ ጭምር ከማስታወሻዎቼ ላይ
ትእምርተ ጥቅሶችን አስወግጄያለሁ። (የኔን ማስታወሻ ተመልክቶ ካፀደቀልኝ በኋላ ትእምርተ
ጥቅሶቹን እንዳስወግዳቸው ሐሳብ ያቀረበልኝ ራሱ መንግስቱ ነው፤ ምክንያቱም አካሉ የእርሱን
ሀሳብ ቃል በቃል እንዳሰፈረ ተደርጎ እንዳይወሰድ ስለፈለገነበር።እንደ እውነቱ ከሆነ ሃሳቦቹ እንደ
አዲስ ተጽፈዋል ባይ ነው።ነገር ግን የመንግስቱ ከአካሉን ጽሑፍም ሆነ የኔን ማስታወሻ ሲያርም
እንዳሉ እንዲተዉ የፈለጋቸው አንዳንድ ገለፃዎች በትእምርተ ጥቅስ መካከል እንዳሉ
ትቼያቸዋለሁ። ስለዚህ አንዳንዶቹ አስተያየቶች የመንግሥቱ የራሱ እንጂ የእኔ አለመሆናቸውን
ግልጽ ማድረግ እፈልጋለሁ)። ሌሎች የመረጃ ምንጮችም ተጠቅሜያለሁ፤ በይበልጥ ከራሱ ከአብዬ
መንግስቱ ጋር ያደረግኳቸው ጨዋታዎች በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ።
310
ጥቋቁር አናብስት
5) እንደ የብርሀኑ ዘርይሁን "ባልቻ አባ ነፍሶ" እና የማሞ ውድነህ "አሉላ አባነጋ" የመሳሰሉ
ተውኔቶች ብዙ ተመልካች ሲስቡና ለረዥም ጊዜ ሲታዩ ማህበራዊ ሂስ ያዘሉ ታሪካዊ ተውኔቶች
በ1980ዎቹ መጨረሻላይ እንደገና ዝነኛ ሆኑ።
7) መንግሥቱ ስለ ስጋዊ ፍቅር ጽፏል ነገር ግን በስሜ ስለሚገለጽ ፍቅር ለመፃፍ ብእሩን አንስቶ
ስንኝ አልደረደረም።ስለንጹህ ፍቅር ብቻየተጻፈግጥም እኔ ራሴበእጄ ጽፌያለሁ ቢለኝ እንኳን፣
እውን የእሱ አይመስለኝም ነበር፤ ከባህሪው ጋር አይገጥምምና። "መኖር መላ አገኘ"ም ሙሉ
በሙሉ የፍቅር ግጥም ነው ብዬ አላስብም። ከዚህ ቀደም ለዚህ ግጥም የሰጠሁትን ፀረ ማርክሲሳዊ
ትርጓሜ በይፋ እንዳነሳለት ይፈልግ እንደሆን ስጠይቀው፣ ያን እንዳደርግ እንደማይፈልግ በግልጽ
ነግሮኛል።
ወይም ቄሶችና መነኩሴዎች ከቤተክርስቲያን ወይም ገዳም የወርቅ ዋንጫ ወይም ሌላ ጠቃሚ
ንብረት መስረቅ ካልከበዳቸው፣ የቀበሌው ሰራተኞች ንብረቶቹን ለግል ጥቅም ለማዋል መስረቅ
የበለጠ አይከብዳቸውም። ከአብዮቱ በኋላ ብዙ ረቂቆች አዲስአበባ ላይ በሕገወጥ መንገድ
ሲቸበቸቡ ነበር። የራስ ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው የፀሎት መጽሀፍ እንድገዛ ቀርቦልኝ ነበር
፤ ነገር ግን ይሄ የተሰረቀ ሳይሆን መኮንን ሊሞቱ ሲሉ ለቀድሞው ሾፌራቸው እንደ ስጦታ
ሰጥተውት አሁን ችግር ውስጥ በመውደቁ ለሽያጭ ሰላቀረበው ነው።
11) ጎጃም ውስጥም መቄት የሚባል ቦታ አለ። በዛ ስም የሚጠሩ ከአንድ በላይ ቦታዎች ሊኖሩ
ይችላሉ።
12) አለቃ ኃይለማርያም በ“እብድ አይጥ” ተነክሰው በኋላ ሞቱ። አንድ ደብተራ እንዲገድላቸው
አይጡን የላከው ጠንቋይ ነው ብሏል።
312
ጥቋቁር አናብስት
ታደለ ገብረሕይወት
አብዮተኛና የድሆች አፈቀላጤ
ታደለን ያሳደጉት ጥንዶች በዚያን ጊዜ በጣም አርጅተዋል። ባልየው ጡረታ የወጡ የመንግስት
ባለሥልጣን ሲሆኑ፣ በስራቸው ምክንያት ብዙ ተጉዘዋል ፤ አሁንም ቤተሰቡ አልፎ አልፎ
ስለሚጓዝ አንዳንዴ ታደለን ይዘውት ይሄዳሉ።በቤታቸው "ባሪያዎችና አገልጋዮች" ስለነበሯቸው፣
ለታደለ የድሮ ስርአትን እንዲረዳ አድርጎታል። ሀብታምና ባህላቸውን የሚያውቁ “የሰለጠኑ” ሰዎች
ነበሩ። ልጆቹም እንዲሁ የተማሩና ለታደለም ደግ ናቸው፤በተለይ ከልጆቹ አንደኛው በኢትዮጵያ
አውራጎዳና መስሪያ ቤት የሚሰራ እና በስራው ምክንያት ከሀገር ሀገር የሚዞረው የበለጠ ደግ ነበር።
ለታደለ ይህ ቤተሰብ ተስማምቶታል፤አንዳች ችግር ገጥሞት አያውቅም። ለቤተሰቡ ልብስ እያጠበና
እየተኮሰ፣ ትምህርቱንም አብሮ በጎን ያስኬዳል። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ጨርሶ ስራ
እስከሚያገኝ ድረስ እዚሁ ቆየ።
ማቀላጠፍ ስለቻለ፤ ከዚያ በኋላ ትምህርት አስደሳች ሆነ። በዚሁ ትምህርት ቤት እስከ ስምንተኛ
ክፍል ተምሮ አጠናቀቀ። በመጨረሻዎቹ ሁለት ዓመታት እሱና ሌሎች ከአንድ ደርዘን የሚበልጡ
ተማሪዎች የጥናት ቡድን አቋቁመው ስለወደፊት እቅዳቸው ይነጋገራሉ። በዚህ ውይይት ወቅት
ታደለ ደራሲ መሆን እንደሚፈልግ ይገልፃል። የመጀመሪያ የፈጠራ ጽሑፉን በመፃፍ እጁን
ያፍታታውም ይሄኔ ነው። የሼክስፒርን "የቬኒሱ ነጋዴ"ለተማሪዎች በሚገባ ቀላል እንግሊዘኛ
እንደገና ፃፈው። ተውኔቱን ለመድረክ ከማብቃቱም በላይ፣ እራሱም ተውኖበታል። ተውኔቱ
ትምህርት ቤት ውስጥ በሚገኘው ትልቅ አዳራሽ ታየ፤“እስከ10,0002የሚደርሱ ሰዎች
ተመልክተውታል” ይላል ታደለ። "ይህ አጋጣሚ ነው ቃጭሎ) ወደ ሥነ ጽሑፍ ጎዳና የመራኝ"
ይላል።
ከኮከበ ጽባህ በኋላ፣ታደለ አዲስ አበባ የንግድ ስራ ትምህርት ቤት ገብቶ የሁለተኛ ደረጃ
ትምህርቱን አጠናቀቀ። ዘጠነኛ ክፍል ላይ ቀለል አድርጎ የተረጎመውን "የቬኒሱ ነጋዴ " ዳግም
ለመድረክ አበቃው። ትምህርት ቤቱ ውስጥ ከብዙ ደራሲያን ጋር የመገናኘቱን እድል አገኘ፤ እነሱም
ደራሲ መሆን እንዳለበት መከሩት። መምህራኑም አበረታቱት። ከዝነኛው ገጣሚ እና ፀሐፊ
ተውኔት ከጸጋዬ ገብረ መድህን እና በሙያው ኢኮኖሚስት ሆኖ ለሥነ ጽሑፍ ከፍተኛ ዝንባሌ
ካለው ከአስፋው ዳምጤ ጋር ተዋወቀ።ብሪትሽ ካውንስል ውስጥ ከሚከናወኑ ተግባራትም ጋር
ለመተዋወቅ ቻለ። ታደለ እየበሰለ የመጣበት ጊዜ ነበር። በሳምንቱ መጨረሻ ላይ ግጥሞችን
በእንግሊዝኛ ይጽፍና ሰኞ ለአስተማሪዎቹ አሳይቶ አስተያየት እንዲሰጡት ይጠይቃል። ብዙዎች
ሙከራውን ሲያደንቁለት፣ ግጥም የመፃፍ ተሰጥኦ እንዳለው እያመነ መጣ። ከዚያም ስፖርትና
ሌሎች መዝናኛዎችን ቀነስ አድርጎ ብዙ ጊዜውን መጽሐፍት ቤት ያሳልፍ ጀመር። በጊዜው
የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ቲያትር ቤት ምክትል ዳይሬክተር የነበሩት እና በቲያትር ቤት ውስጥ
የሚታዩትን አብዛኛዎቹን ተውኔቶች የደረሱት ፀጋዬ ገብረመድህን ያበረታቱት ነበር ፤ ዘወትር
በየሁለት ሳምንቱም ፊልም እንዲመለከት ነፃ ትኬት ይሰጡታል፤ በጊዜው በቲያትር ቤቱ ውስጥ
ከተውኔቶች ይልቅ ፊልሞች በብዛት ይታዩ ነበር። ታደለ አሁን በተውኔቶች ውስጥ መሳተፍ
ጀምሯል ፤ ለምሳሌ በትምህርት ቤቱ ውስጥ በእንግሊዝኛው "ኦቴሎ" ውሰጥ እንዲሁም በቀዳማዊ
ኃይለ ሥላሴ ቲያትር ቤት በቀረበው የፀጋዬ ገብረ መድህን "ሀምሌት" ትርጉም ውስጥ ተውኗል።
ይሁን እንጂ በጊዜው የቲያትር ተመልካቾች በጣም ጥቂት ነበሩ፤ አንዳንዴ በአዳራሹ ውስጥ
የሚገኙ ሰዎች ቁጥር ከ50 ላይበልጥ ይችላል።
314
ጥቋቁር አናብስት
በ1959 ዓ.ም የአስራ ሁለተኛ ክፍል ትምህርቱን በንግድ ስራ ትምህርት ቤት ጨረሰ። ጽሑፉን
በተመለከተ እርዳታና ማበረታቻ የሰጡትን የእንሊዝኛ ቋንቋ መምህራኑን፣ በተለይ እንግሊዛዊው
ኪይዝ ጆንስን እና ስኮትላንዳዊቷ ሚስ ብራይድን፣ ይወዳቸዋል።በተለይ ኪይዝ ጆንስ በሥነ ጽሑፍ
ረገድ ለታደለ “እንደ አባት ያለ” ሲሆን፤በንግድ ስራ ትምህርት ቤት ውስጥ በቆየበት አራቱም
ዓመታት ያስተማረው ሰው ነው። ታደለ እዛ በነበረበት ወቅት ከፃፋቸው ግጥሞች መሀል
የተወሰኑት በማባዣ ወረቀት ተባዝቶ በሚዘጋጀው በትምህርት ቤቱ ጋዜጣ ላይ ታትመዋል፤ ነገር
ግን የትኞቹም በሌላመንገድ ታትመው አያውቁም።
ከንግድ ስራ ትምህርት ቤት ከወጣ በኋላ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ውስጥ ተቀጥሮ መስራት
ጀመረ። በዚህ የመጀመሪያ ስራው በማህበረሰባዊ ስራዎች የትምህርት ክፍል ውስጥ፣ ለዲኑ ጸሐፊ
ሆኖ ለሶስት ዓመት ሰራ። ነገር ግን "ማነው ኢትዮጲያዊው" የሚለው መጽሐፉ በ1963 ታትሞ
ሲወጣ የዩኒቨርስቲ ኮሌጁ ፕሬዚዳንት አክሊሉ ሀብቴ በመጽሐፉ የተነሳ የእርሳቸው ጸሐፊ
እንዲሆን ጠየቁት፤ታደለም በሐሳቡ ተስማምቶ እስከ 1967 ድረስ በዚሁ ስራ ቆየ።
ታደለ ገብረሕይወት ከንግድ ስራ ትምህርት ቤት ከተመረቀ ከአንድ ዓመት በኋላ ጸሐይ ተገኝን
አገባ።በመጀመሪያ እይታ የተፈጠረ ፍቅር ሲሆን፣ ከሦስት ወራት በኋላ ተጫጩ። ከአንድ ዓመት
በኋላ ሕጋዊ ጋብቻ ሳይፈጽሙ አብረው መኖር ጀመሩ። ጸሐይ የትምህርት ቤት ፎቶዎችን፣
የምስክር ወረቀቶችን ስታይ የፃፋቸውን ነገሮች ስታነብ ተማረከችና ጨምሮ እና አስፍቶ እንዲጽፍ
ትጨቀጭቀው ጀመር። "ማነው ኢትዮጲያዊው" የተፃፈው እና የታተመው በዚህ ዐይነት ሁኔታ
ነበር። ከሚስቱ ማበረታቻ ባሻገርም ዩኒቨርስቲው ገና እያበበ ላለ ጀማሪ ደራሲ አመቺ ቦታ ሆኖ
አገኘው።በዚያም ከጨዋና፣ ከትላልቅ ሰዎች ጋር መዋል ጀመረ፤አንዳንዶቹ ኢትዮጵያዊ ሲሆኑ፣
ሌሎቹ ደግሞ የውጭ ሀገር ሰዎች ነበሩ።ከነዚህ መሀል የፖለቲካ ሳይንቲስቱ ፕሮፌሰር ንጉሴ አየለ፣
የሥነ ትምህርት ባለሙያው ፕሮፌሰር አባይነህ ወርቄ፣የታሪክ ተመራማሪዎቹ ፕሮፌሰር ስቬን
ሩቤንሰንና ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት፣የኪነጥበብ ታሪክ አጥኚው ፕሮፌሰር ቾጅናኪ፣ የአማርኛ
ቋንቋው ሊቅ ዶክተር ሐይሉ ፉላሰ፣ ዶክተር ስዩም ገብረስላሴ (ጥልቅ መረዳት እና ሰብአዊነት
ያለው ሶሺዮሎጂስት) እና ሌሎችም ብዙ ይገኙበታል።እነኚህ የተማሩ ሰዎች ታደለ የተሻለ ሰው
እንዲሆን ያነሳሱትና ሞራል ይሰጡት ነበር።
ታደለ ዩኒቨርስቲ በሚሰራበት ወቅት የማህበራዊ ሳይንስ ትምህርቶችን ጨምሮ ተምሮ አንድ
የፖለቲካ ሳይንስና፣ አንድየማህበራዊ ስራ፣ ሁለት ዲፕሎማዎችን ተቀብሏል።
315
ጥቋቁር አናብስት
በ1967 ዓ.ም ማስታወቂያ ሚኒስቴርን ተቀላቅሎ፣ የዛሬይቱ ጋዜጣ አዘጋጅ፣ ረዳት ሆኖ መስራት
ጀመረ። በዚህ ዐይነት ስራ ውስጥ፣ በየቀኑ የመፃፍ ባህል ስለሚዳብር፣ በታደለ ገብረሕይወት
ውስጥ ወሳኝ የሆነ ጊዜ ነበር። በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወረ የተለያዩ የሕይወት ገጽታዎችን
እንደተገነዘበው፣ ራሱ ያየውንና ከሌሎች የሰማውን ጽፏል፤ በጋዜጣው ላይ ያልተፃፈለት እና ርዕስ
ያልሆነ የሀገሪቱ አካባቢ የለም። ይህ አጋጣሚ ስለራሱ ህዝቦች በደንብ የማወቅ እድል ሰጠው።
በጣም ራቅ ወዳሉ የሀገሪቱ ክፍሎች ተጉዞ ብዙ ነገር ስለተማረ፤ለሀገሩ ህዝብና በጊዜው ለፈነዳው
አብዮት ፍቅርና ወገንተኝነት ይሰማው ጀመር። በዚህ የተነሳ "የኢትዮጵያን ሀብትና ድህነት"
መረዳት ቻለ። ያየውንና ሁሉ መዝግቦ ጋዜጣው ላይ፣ ብሎም ወደኋላ በሚጽፋቸው መጽሐፍት
ላይ ያንፀባርቃል።
ታደለ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተቀጣጠለ የመጣውን አብዮት ድምጽ ገና በጊዜ ሲሰማ እና ሲያጠና
ነበር። ወዲያውኑ ስለ አብዮቱ መፃፍ ጀመረ። ስለዚህ የሁለተኛ መጽሐፉን ርዕስ በዘመኑ ከሚሰሙ
መፈክሮች3መሀል መርጦ "ኢትዮጵያ ትቅደም" አለው። ይህንን መጽሐፍ በየካቲት 1966 ጀምሮት
በዛው ዓመት ሐምሌ ላይ ታተመ። ሲታተም “እንደጋዜጣ ነበር የተቸበቸበው”፤በአንድ ሳምንት
ጊዜ4 ብቻ 5,000 ቅጂዎች ተሸጠ። በመጀመሪያ ላይ ደርግ ይህንን መጽሐፍ በዐይነቁራኛ ነበር
የሚከታተለው።መጽሐፉን የሚያጠና ኮሚቴ ከተቋቀመ በኋላ መንግስት ለታደለ ምስጋና
አቀረበለት። መጽሐፉ የወጣው የአሮጌውም፣ የአዲሱም ስርአት ወኪሎች ገና ስልጣን ላይ እንዳሉ
ነበር፤ ገና ኃይለ ሥላሴንጉሥ እንዳሉ፤ እንዳልካቸው መኮንንም ጠቅላይ ሚኒስትር እንደነበሩ፤
የዚያኑ ያህል ወታደሮቹም (አዲሶቹ) የስልጣኑን ልጓም እንደጨበጡ። የታደለ ገብረሕይወት
መጽሐፍ ተቀባይነት ያገኘው ግን እንደ አብዮታዊ ስራ ነው።
316
ጥቋቁር አናብስት
አብዮቱ በታደለ የስራ ጠባይም ላይ ለውጥ አምጥቷል። ከየካቲት 19665 ዓ.ም ጀምሮ፣ታደለ
ዘወትር ከሌሊቱ 8 ሰአት ይነቃና እስከ ሌሊቱ 11 ሰአት ድረስ መጻፍና ማንበብ ልምዱ ሆነ።
ያቋረጠውን እንቅልፉን ከሌሊቱ 11 ሰአት ላይይቀጥላል።ይህ ልምድ እስከአሁንም ድረስ
ቀጥሏል። እነኚህን የማታ ማታ የስራ ሰዓታት ዋጋ ይሰጣቸዋል፤ ይደሰትባቸዋልም።
ከ1967 ጀምሮ እስከ ጥር 1971 ድረሰ ታደለ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ውስጥ ሰርቷል። የለቀቀው
ደግሞ ደሞዙ አነስተኛ ስለሆነ ነበር፤ታደለ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች የሚከፈላቸው በቂ አይደለም
ይላል። በዛ ላይ የቤተሰቡ ቁጥር በጣም እየጨመረ ነበር፤አራት ልጆች አሉት፤በቃለምልልሳችን
ወቅት ደግሞ አምስተኛው በመንገድ ላይ ነበረ። ስለዚህ የመንግስት ድርጅት በነበረው የኢትዮጵያ
ችርቻሮ ንግድ ኮርፖሬሽን ተቀጠረ። እስከ 1978 ዓ.ም እዚሁ ሰርቷል። ስራ መቀያየሩ “ለመፃፍ
ብዙ ጊዜ ሰጥቶታል”፤ጊዜ ብቻ ሳይሆን “የፈጠራ ነፃነትም” አግኝቷል። ማስታወቂያ ሚኒስቴር
ውስጥ በሚሰራበት ወቅት "የዛሬይቱ ኢትዮጵያ"አብዛኛውን ጊዜ እና ጉልበቱን ይጨርስበት ነበር።
ከጋዜጣው ስራው ጎን ለጎን እንደምንም ብሎ የሊቀመንበር ማኦን"ትንሿን ቀይ መጽሐፍ"
ተርጉሟል። ነገር ግን ማስታወቂያ ሚኒስቴር ብዙ በቆየ ቁጥር፣ ጊዜ ይበልጥ እያጠረው መጣ።
አሁን አዲሱን ስራ ከጀመረ ወዲህ ግን፣ መጻፍ የሚፈልገውን ለመጻፍ ብዙ ጊዜ አገኘ።
***
በአሉ ግርማ፣ ብርሀኑ ዘርይሁን እና ታደለ ገብረሕይወት በኢትዮጵያ ውስጥ ፈር ቀዳጅ አብዮታዊ
ደራሲያን ሆነው ይቆጠራሉ። የመጀመሪያዎቹ ሁለት ልምድ ያላቸው፣ የታወቁ እና በስራቸው
የተከበሩ ጸሐፊዎች ነበሩ። ስለዚህ በ1972 ዓ.ም የታደለ "ለቀይ አበባ"፣ ከበአሉ "የቀይ ኮከብ
ጥሪ"፣ እንዲሁም ከብርሃኑ "ማዕበል" ጋር በተመሳሳይ ጊዜ በመውጣቱ እና ልብወለዱ ከነሱ
ልብወለዶች ጋር ፈር ቀዳጅ ተብሎ መጠራቱ የራስ መተማመኑን ጨመረለት።እነኚህ ሶስት
መጽሐፍት እውነተኛ ፋናወጊ አብዮታዊ ልብወለዶች ተደርገው ይወሰዳሉ። ይሁን እንጂ
317
ጥቋቁር አናብስት
"ኢትዮጵያ ትቅደም" የተሰኘው ቀደምት መጽሐፉ ከዚህ በኋላ እንደ አብዮታዊ ልብወለድ
መወሰዱ ቀረ።
ከዚህ መጽሐፍ በኋላ ታደለ፣ ለብዛት ሳይሆን ለጥራት ዋጋ ለመስጠት ወሰነ። ይህንን የፈጠራ ስራ
እንደ ቁምነገር ወስዶ በጥልቀት መጻፍና ማንበብ ጀመረ። ይህ ሰባት ዓመታት የወሰደው የጽሞና
ጊዜ አዲስ ልብወለድ ወለደ።ልቦለዱ "1996" የሚል ስያሜ ሲኖረው በ1977 የተጠናቀቀውን
ረቂቅ በእጁ ይዞ ነበር። ይህ በእንዲህ እንዳለ "1996" ከተባለው የሳይንሳዊ ልብወለድእረፍት
ለመውሰድ የሜሪ ኮሬሊን "Vendetta"6 ወደ አማርኝ "ብቀላ" ብሎ ተረጎመ። ለማሰብ እና
ለማንበብ ስለፈለገ ወደ ስምጥ ሸለቆ ወረደ። ረቂቁን ደግሞ ደጋግሞ ይጽፋል፤አንብበው አስተያየት
እንዲሰጡት ለብዙ ሰዎች ይሰጣል፤የፃፈውን ቀዳዶ ይጥለውና እንደገ "ሀ" ብሎ መፃፍ ይጀምራል።
“ከፃፍኳቸው ልብወለዶች ሁሉ የበለጠ ምርጥ መጽሀፍ ነው፤እንደውም ዘመን ተሻጋሪ ሊሆን
ይችላል” ብሎ ያስባል። ሀሳቡ ትልቅ፣ገፀ ባህሪያቱ ሰው ሰው የሚሸቱ፣ ታሪኩ ደግሞኢትዮጵያን እና
ህዝቦቿን የሚገልጽ ጥሩ የሚባል ነው፤ልብወለዱ በአጭሩ የሚገልፀው ታደለ የወደፊቱ ኢትዮጵያዊ
ሰው ምን ሊመስል እንደሚችል ያለውን ምኞት ነው።ምኞቱ አብዮቱ ፍሬ አፍርቶ፣ በጎዳናው ላይ
ቁስላቸውን እያሳዩ የሚለምኑ የኔብጤዎች ጠፍተው ንፁህ ሰዎች፣ንፁህ ቤቶችብቻ ማየት ነበር።
ይህም ደራሲው፣ ኢትዮጵያ ነፃ ሆና ህዝቦቿም ደስተኛ ሆነው―ክብራቸው ተጠብቆ―ለማየት
ያለውን ተስፋ ያንፀባርቃል።
318
ጥቋቁር አናብስት
“ፀጉሬን ያሸበተው ይህ መጽሐፍ ነው” ይላል። ልብወለዱን ለመጨረስ ቤት ውስጥ ለረዥም ሰአት
መቀመጥ ስለነበረበት፣ ከወዳጅ ዘመዶቹ ጋር ተቆራርጧል። ነገር ግን “ካገኘሁበት እርካታ አንፃር
ይበል የሚያሰኝ ነው” ብሏል።8
***
***
ማስታወሻዎች
1) ታደለ ወደ ዋና ከተማዋ ሲያመራ ቤተሰቡ ለስራ “ወደ ክፍለሀገር” ሄደው ነበር። ነገር ግን “12
ወይም 14 ዓመት ሲሞላው” ወደ ታደለ የትውልድ ቦታ ተመለሱ።ለበአል እየሄደ ይጠይቃቸዋል።
እናቱ አማርኛ ስለማይናገሩ ከእርሳቸው ጋር ለመነጋገር ሲሞክር ኦሮምኛመለማመድ ጀመረ።
ቃለምልልሳችን እስከተደረገበት ጊዜ ድረስ፣ እናቱ በሕይወት ነበሩ።
319
ጥቋቁር አናብስት
6)ይህ የትርጉም ስራ እስከ 1985 ድረስ አራት ጊዜታትሞ በአጠቃላይ 50,000 ቅጂዎች
ተሸጧል።
320
ጥቋቁር አናብስት
አለቃ ገብረሃና
ቀልድአዋቂ፣ ሊቅ እና ዝነኛ
አንዳንድ ኢትዮጵያውያን በጣም ከመታወቃቸው የተነሳ በመጀመሪያ
ስማቸው ብቻ ይጠራሉ። ኢትዮጵያውያን የመጀመሪያ ስማቸው፣
እውነተኛ የግል መጠሪያቸው ሲሆን የአባት ስምና ማዕረግ አብሮ
ይጠቀሳል። በመጀመሪያ ስማቸው ብቻ እጅግ ከሚታወቁ
ኢትዮጵያውያን መሀል ብላቴን ጌታ ኅሩይ፣ ራስ እምሩ እና አለቃ
ገብረሃና ተጠቃሽ ናቸው። ሕሩይ በሁሉም ዘንድ እንደ ቅዱስ
የሚቆጠሩ ናቸው። የገብረሃና ግን የዚህ ተቃራኒ ነው ፤ገብረሃና
በስማቸው ስድ የሆኑ ወሲብ ነክ ታሪኮች1 እና ሌላም ብዙ
ቀልዳቀልዶች ይነገራሉ። ከሞቱ ከብዙ ዓመት በኋላ እንኳን በስማቸው ትኩስ ቀልዶች
ይፈበረካሉ። ታሪኮቹ ምንም እንኳን ሙሉ ለሙሉ ፈጠራ ቢሆኑም፣ሰዎች ስለእሳቸው ካላቸው
አመለካከት―በትዳራቸው ደስተኛ አለመሆናቸው፣ሴት አውል እንደሆኑ፣በአማርኛ ሊቅ
መሆናቸው፣ከመሳሰሉት―ጋር መግጠማቸው ብቻ ሳይሆን ይህንን አመለካከት ጠብቀውም
አቆይተዋል። የኢትዮጵያ የቤተክርስቲያን ሊቆች ቅኔ በመናገር የተካኑ ናቸው፤እናም አለቃ
ገብረሃናም እንዲህ ካሉ፣ ብዙ ቅኔ ጠገብ ታሪኮች ጋር ስማቸው አብሮ ይነሳል።
አለቃ ገብረሃናን ከኢትዮጵያ ስመጥር ደራሲዎች የሕይወት ታሪክ ጋር እዚህ ያካተትኳቸው በቋንቋ
አጠቃቀማቸው ጥበበኛ ስለሆኑ ነው።በኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ ውስጥ ሌሎች ደራሲዎች ጽሑፍ
ውስጥም እንደ ተረታዊ ገፀባህሪ ብቅ ብቅ ይላሉ።በተጨማሪ ራሳቸው የፃፏቸው የሃይማኖት
መጽሐፍትም አሉ፤ይሁን እንጂ ሳይታተሙ ቀርተዋል። እዚህ መጽሀፍ ውስጥ የተካተቱት
ደራሲዎች የተቀመጡበት ቅደም ተከተል በኖሩበት ዘመን መሰረት ቢሆን፣አለቃ ገብረሃና የመጽሐፉ
መጀመሪያ ላይ መቀመጥ ነበረባቸው። ነገር ግን ስለሳቸው ለመፃፍ ያነሳሳኝ ከሰዎች እና ደራሲዎች
321
ጥቋቁር አናብስት
***
አለቃ፣እቴጌ መነንን አስጠንተው ከጨረሱ በኋላ በእቴጌይቱ ትዕዛዝ ከፍተኛ ትምህርት ለመማር
ወደ ጎንደር ሄዱ። በአታ ላይ ሀዲስ እና ብሉይ ኪዳንን ተማሩ።እቴጌ መነን ለአለቃ መምህር ክፍያ
ምግብና ልብስ ይልኩላቸው ነበር።ይህንን ትምርታቸውን ከጨረሱ በኋላ እቴጌ መነን “አለቃ”
የሚለውን ማዕረግ ሰጧቸው። "አለቃ" የሚለው ማዕረግ የቤተክርስቲያን/ገዳም ሃላፊ ወይም
ደግሞ በአንድ የቤተክርስቲያን የእውቀት መስክ አዋቂ/ሊቅ ወይም መምህር የሆነ ማለት ሊሆን
ይችላል። ከዚህ በኋላ በጎንደር ያሉ አብያተክርስቲያንን በብቃት ማስተዳደር ጀመሩ።ሊቅነታቸው
በሁሉም ዘንድ የተመሰከረለት ሲሆን በተለይ ፍትሃ ነገስትን በመተርጎም “የሚወዳደራቸው
አልነበረም”። ፍትሐ ነገሥት አለማዊ እንዲሁም መንፈሳዊ ጉዳዮች ባንድ ተጣምረው የሚገኙበት
የህግ መጽሐፍ ሲሆን እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ኢትዮጵያ የምትዳኘውም በዚሁ መጽሐፍ ነበር።
የቋራው ካሳ የእቴጌ መነንን የልጅ ልጅ ቢያገባም፣ የሚስቱን አባት ራስ አሊን ካሸነፈ በኋላ፣ እቴጌ
መነንን ራሳቸውን ማርኮ አሰራቸው። በኢትዮጵያ ትልቁን ስልጣን ከያዘ በኋላ ዳግማዊ ቴዎድሮስ
ተብሎ ተቀብቶ ነገሰ። ከዛ በኋላ አለቃ ገብረሃና ከቴዎድሮስ ጎን ተለይተው አያውቁም። በፍጹም
አይለያዩም ነበር ይባላል። በተለይ በፍትሐ ነገሥት(መጽሐፍ ቅዱሳዊ ህግጋትን ተመርኩዞ የተፃፈ
ነው)እየተመሩ ፍትህን ለማድረስ ደክመዋል።በጊዜው በኢትዮጵያ የፍትሓ ብሄርም ሆነየወንጀለኞች
322
ጥቋቁር አናብስት
ወይም የሃይማኖት መቅጫ ህግ ስላልነበረ ሁሉም የሚዳኘው በፍትሐ ነገሥት ነበር። አለቃ በተለይ
በዘመነ መሳፍንት ፍትህ አጥቶ ለነበረው ደሃው ህዝብ ህግና ስርአትን ለማስከበር፣ ጓግተውም፣
ቆርጠውም ነበር። ቴዎድሮስ ተናዶ በሚቆጣበት ጊዜ፣ ማረጋጋቱ የአለቃ ስራ ነበር።
አለቃ ገብረሃና ዝናቸው የናኘው በዳግማዊ ምኒልክ ችሎት ነው። ዮሐንስ አራተኛ በ1881 ዓ.ም
መተማ ላይ በተደረገው ጦርነት ከተሰዉ በኋላ አለቃ ወደ ትውልድ መንደራቸው ናበጋ ተመለሱ።
ነገር ግን አለቃ በጊዜው ሊቆች በተለይ በአለቃ ገብረማርያም እና በጸሐፌ ትእዛዝ ገብረሥላሴ (ኋላ
የምኒልክ ጸሐፌ ዜና መዋዕል) በደንብ ስለሚታወቁ ወደ ምኒልክ ችሎት እንዲቀርቡ ተጠሩ።
ከምኒልክ እና ከጣይቱ ጋር በመወዳጀታቸው ዝናቸው በፍጥነት ተስፋፋ። በመጀመሪያ አለቃ
እንጦጦ ላይ በሚገኘው ቤተመንግስት፤በኋላ ደግሞ በኡራኤል እና ራጉኤል ቤተክርስቲያን፣
እንዲሰነብቱ ምርጫ ተሰጣቸው። ነገር ግን አለቃ የሚናፍቃቸው የትውልድ መንደራቸው ናበጋ
ጊዮርጊስ ነበር። ስለዚህ መናገሻው ወደ አዲስ አበባ ሲዘዋወርእስከመጨረሻው በዚያ ለመቆየት
አሻፈረኝ ብለው ወደ ትውልድ መንደራቸው ተመለሱ። ነገር ግን የአዲሳባ ቆይታቸው፣ የጎንደር እና
የአክሱምን ያህል አለቃን “አይረሴ” ለማድረግ የሚያበቃ ነበር። አፄ ምኒልክና አለቃ ገብረሃና
በአንድ ላይ ፎቶ ተነስተው ነበር ይባላል። ፎቶውም ብላቴንጌታ ሕሩይ ቤት ተቀምጦ እያለ ሌባ
ገብቶ ስለዘረፈው ጠፍቶ ቀረ። ካርዲናል ማስጃ እና ሌሎች 12 የውጭ ሀገር ሰዎች፣ እንደሚሉት
መነኩሴ ሳይሆኑ ሰላይ መሆናቸውን በቅኔ ለምኒልክ ነግረው ያሳወቁት ራሳቸው አለቃ ነበሩ ፤
አለቃ ለሃገራቸው ያላቸውን ተቆርቋሪነት እና ፍቅር በዚህ አጋጣሚ አስመስክረዋል።
324
ጥቋቁር አናብስት
በአንድ ወቅት "ትላልቅ ሰዎች" ሱረት የመማግ፣ ትምባሆ የማጨስ፟ ልምድ ነበራቸው።
ቤተክርስቲያን ግን ይህንን ልምድ በጽኑ ታወግዘው ነበር። አንድ ቀን አለቃ ሱረት ሲምጉ፣ አንድ
ቄስ አያቸውና ለምን ይሄንን እንደሚያደርጉ ጠየቃቸው። አለቃም "ለምን አላጨስም?" አሉ።
"ምክንያቱም" አለ ቄሱ "ምክንያቱም ሲጋራ የሰይጣን ንብረት ነው"
ይህ ላይ ላዩን ሲታይ ትርጉም የለሽ የሚመስል መልስ በጣም ትልቅ ትርጉም አለው። አለቃ ይህን
ቄስ የሰይጣን ንብረት የሆነውን "ሲጋራ" ለምን ተጠቀምክ ብሎ ለመጠየቅ የሴይጣን ዘመድ/ወራሽ
መሆን አለብህ እያሉት ነው።እንዲህ ያለ መልስ የባለጋራን አፍ የሚያስዘጋ ነው።አለቃም
የሚታወቁበት "ፈጣን ምላሽ" እንዲህ ያለ ነው።
አለቃ አንዲት በቅሎ ነበረቻቸው፤ይቺ በቅሎ በአንድ በኩል ያሉትን እግሮቿን በትይዩ፣በቅንጅት
በማንቀሳቀስ፣ ያለመንገጫገጭ እንድትራመድ የሰለጠነች ናት።ስለዚህ እንደውሃ የምትፈስ ነች
ማለት ይቻላል።6 ታዲያ ባለቤታቸው ወይዘሮ ማዘንጊያ ይህቺ በቅሎ በተደጋጋሚ አንዲት ሴት
ከምትኖርበት ራቅ ያለ ቤት ታስራ ይመለከታሉ። ስለዚህ ወደባለቤታቸው አንድ ሽማግሌ ልከው
እሳቸውን ችላ ብለው ለምን ሌላ ሴቶችን እንደሚያማግጡ⁷ እንዲጠይቁላቸው ያረጋሉ። በቅሎዋን
ሴትየዋ ቤት ታስራ ስላዩ “ምስክሬ”ነችአሉ (በቃል አቀባያቸው በኩል)። አለቃም ለምስክርነት እንደ
በሬ እና ላም ያሉ ሰላማዊ እንስሳት ይቅረቡብኝ እንጂ ይቺ በቅሎ እኔን በጥላቻ ስለምትመለከተኝ
ምስክር ልትሆን አይገባትም።በቅሎዋን በዳገት በቁልቁለት ስለምነዳት ቂም ሳትይዝብኝ አይቀርም።
ስለዚህ የእሷ ምስክርነት ተቀባይነት አይኖረውም።ኢትዮጵያውያን ሙግት እንደ መውደዳቸው ስለ
ችሎት ደንብ ስለሚያውቁ የአለቃን ብልሃት የሚያስደንቅ ሆነው እንደሚያገኙት አይጠረጠርም።
በህዝቡ ዘንድ ብዙ የጫወታ ለዛዎች በብዛት እና በስህተት የአለቃ ገብረሃና እንደሆኑ ይቆጠራሉ።
የሆነው ሆኖ አለቃ ፈጣን መልስ በመስጠት፣ ቃላትን በመሰንጠቅ፣ ቅኔ በመናገር፣ በቃላት
በመጫወት፣ላይ ላዩን ሲታዩ ከሚሰጡት ትርጉም የጠለቀ ሌላ ትርጉም ያለው፤ ትርጉሙን ፈልጎ
ለማግኘትም ቃላቱ ላይ ብዙ ማሰብና መመራመር የሚያስፈልገው ዐይነት ንግግር በመናገር የተካኑ
ናቸው ይባላል።አለቃ፣ በኢትዮጵያ የልሂቃን ሰማይ ላይ እንደ "ደማቅ የማለዳ/የአጥቢያ ኮከብ"
የፈለቁ ናቸው ይሏቸዋል። በብዙ ታላላቅ ነገሥታት ዘመን ኖረው፣ ሁሉንም በቅርብ ማወቅ
325
ጥቋቁር አናብስት
አለቃ ገብረሃና ከሚስታቸው ወይዘሮ ማዘንጊያ ጋር ተክሌ የተባለ ወንድ ልጅ፣ ጥሩወርቅ እና
ሲኔ/ሥነ ?? የሚባሉ ሁለት ሴት ልጆች ነበሯቸው።
የተርጓሚ ማስታወሻ
ስለ አለቃ ህይወት የሚተርኩ መጻህፍት የወጡ ሲሆን የሙሴ ሜርኖስን ፎቶ በጉልህ ባይታይም
ማስቀመጣችንን ልብ ይሏል ስለ ጥራቱም ይቅርታን እንጠይቃለን
፟በእንግሊዝ አፉ smoke tobacco ቢልም እንደ ሃገራችን የወቅቱ ባህል ከማጨስ ይልቅ
ማመንዠክ ወደ ሚለው የሚቀርብ ይመስለናል፡፡
ማስታወሻዎች
1) መጨረሻ የሰማሁት ታሪክ ይህን ይመስላል። አንድ ምሽት አለቃ ከሰራተኛቸው ጋር ፍቅር
ይሰራሉ (ኢትዮጵያውያን ይህ ዓይነቱ ድርጊት የተለመደ እንደሆነ ነግረውኛል) በኋላ ሌሊት ላይ
በራሳቸው አልጋ ከሚስታቸው ጋር ተኝተው ከሰራተኛቸው ጋር ሌላ የፍቅር ጨዋታ ማድረግ
ያምራቸዋል። ከአልጋቸው ተነስተው ወደ ሰራተኛቸው ጋር ሊሄዱ ሲሉ ሚስታቸው "አለቃ ወዴት
ነው?" ሲሏቸው "ልደግም ነዋ" ብለው መለሱ። አለቃ ፀሎት ሊደግሙ ያሉ ያስመስሉ እንጂ
እሳቸውስ ከሰራተኛቸው ጋር የፍቅር ጨዋታ ሊደግሙ ነበር።
326
ጥቋቁር አናብስት
4) ውስጠ ወይራ እስከ ስምንት የሚሆኑ አገባቦች ያሉት የሥነ ግጥም ዐይነት ነው። ከነዚህ ሁሉ
ድንገቴነቱ ዋናው ባህሪው ነው። (መጠሪያውን ያገኘውጋቢ ውስጥ በተደበቀ የወይራ ሽመል
በድንገት ከመመታት ይመስላል)
327
ጥቋቁር አናብስት
አበራ ለማ
በርካታ የአጻጻፍ ቅርጾችን የሞከረ ደራሲ አበራ ለማ በሸዋ ክፍለሀገር፣
ሰላሌ አውራጃ፣ ፍቼ በምትባል ከተማ ግንቦት 1ቀን 1943 ዓ.ም ተወለደ።
አባቱ ለማ ደግፌ1 ከሰላሌ ሲሆኑ፣ በኢትዮጵያ አውራ ጎዳና ባለሥልጣን
በመጀመሪያ በጥበቃ ኋላ ደግሞ በፀሐፊነት ሰርተዋል። እናቱ ወይዘሮ
ማጫሽወርቅ ተከተል ከመርሃቤቴ የመጡ "ንፁህ የሸዋ አማራ" ናቸው።
አበራ በአማራም፣በኦሮሞም ባህል ውስጥ ሁለቱንም ቋንቋዎች እያቀላጠፈ
አደገ። በጊዜ ከሁለት ቋንቋዎች ጋር መተዋወቁ የምናብ ነፃነት እንደሰጠው ይናገራል።ሁለቱን
ባህሎች መረዳት ብሎም ልዩነታቸውን ማወቅ በመቻሉ ደስተኛ ነው።አሁን ድረስ ሁለቱንም
ቋንቋዎች መናገር ይችላል።ልጅ እያለ በሁለቱ ባህሎች መሃል አንዳንድ “ባህላዊ ግጭቶች” ይፈጠሩ
ነበር፤ብዙውን ጊዜ አማራዎች "የበለጡ" እንደሆኑ ተደርጎ በራሳቸውም፣በሌሎች ሰዎችም
ይቆጠራሉ። አበራ ከአማራ ልጆች ይልቅ አብረውት ከብት ከሚያግዱት ከኦሮሞዎቹ ጋርይውል
ነበር። የልጅነት ጓደኞቹ አሁን ድረስ ገበሬ ሆነው ቀርተዋል።
አበራ በልጅነቱ ከቤተሰቦቹ ጋር አደገ። ትምህርት የጀመረው በ1952 ዓ.ም ሲሆን ከዚያ በፊት
ለሁለት ዓመት የቄስ ትምህርት ተከታትሏል። በአበራ እና በአስፋ ወሰን አንደኛ ደረጃ ትምህርት
ቤት ከአንደኛ ክፍል እስከ ስምንተኛ ለሰባት ዓመትተማረ። ስምንት ክፍል ለመጨረስ ሰባት ዓመት
ብቻ የወሰደበት ከሁለተኛ ክፍል ወደ አራተኛ ክፍል በአንድ ዓመት በመዘዋወር ሶስተኛ ክፍልን
በመዝለሉ ነው።በገንዘብ ችግርናበትምህርቱ መክበድ ምክንያት፣በአንደኛ ደረጃም ሆነ በሁለተኛ
ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ደስተኛ አልነበረም።ቤተሰቦቹ የሚኖሩት ገርበ ጉራቻ2 ሲሆን፤ እሱ
ደግሞ ለትምህርት ቤቱ እንዲመቸው ከአጎቱና ሌሎች ዘመዶቹ ጋር ፍቼ ይኖራል። አጎቱ ደግሞ
ንግድና ገንዘብ እንጂ ትምህርት እና የትምህርት ጉዳይ ብዙም አያስጨንቀውም። አበራ ከአጎቱ ይህ
ነው የሚባል እርዳታ ካለማግኘቱም ባሻገር፣ብዙ ብዙ ስራዎችን እንዲያከናውን ይጠበቅበት ነበር።
ለምሳሌ በጎችን እና ፍየሎችን በየቀኑ ማገድ እና አመሻሽ ላይ ወደማደሪያቸው መመለስ ነበረበት።
አበራ ከአጎቱ ልጆች ጋር ጥሩ ግንኙነት ስለነበረው አብሯቸው ማዕድ የመቅረብና ትምህርት ቤት
የመሄድ እድል አግኝቷል። አንድ ጊዜ ፈተና እያለው አጎቱ አብሮት መጥቶ ስራ እንዲያግዘው
አዘዘው። አበራ ግን ይህንን ለማድረግ ፍቃደኛ ስላልሆነ ከአጎቱ ቤት ጠፍቶ፣ለሶስት ወር ያህል
በየሱቁ በረንዳ እያደረ ፈተናውን እስኪፈተን ድረስ ቆየ።
አበራ አምስተኛ ክፍል እያለ ለአስተማሪዎቹ “ስለ ሕይወት የሚሰማውን” በተመለከተ ግጥሞች
ይጽፍላቸው ነበር፤ግጥሞቹን የሚጽፈው ደብተር ላይ ሲሆን እያንዳንዳቸው ሁለት ገጽ ያህል
328
ጥቋቁር አናብስት
አበራ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ለመከታተል ወደ ወሊሶ ( ግዮን ወሊሶ ተብሎም ይጠራል) ሄዶ
ጎበና ዳጨ (በእርሱ አጠራር ጎበና ዳጨው) አባ ጥጉ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ገብቶ
9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማረ። የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ትምህርቱን ደግሞ ደጃዝማች ገረሱ ዱኪ
ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታተለ። በዚያም ጥሩ ጊዜ አሳልፏል፤በተለይ ከተለያዩ ክበቦች እና
ሥነ ጽሑፍ ጋር የተገናኙ እንቅስቃሴዎቹ ያስደስቱት ነበር።በየወሩ መጽሔት የሚያሳትመው፣
የመጽሄት ክበብም ወስጥንቁ ተሳትፎ ያደርጋል። ክበቡን በገንዘብ የሚደግፈው አንድ መምህር
ሲሆን፣አበራም በሁለተኛ ደረጃ ተማሪነቱ የመጨረሻ ሁለት ዓመታት የክበቡ ፕሬዚዳንት ነበር።
አበራ ገና ፍቼ እያለ፣ አጫጭር ታሪኮች፣ ተረቶች እና ግጥሞች ያነብ ነበር። ከነዚህ መሀል ዋናው
በተለይ ለትምህርት ቤቶች የተዘጋጀው የከበደ ሚካኤል"ተረትና ምሳሌ"ነው።በተጨማሪ
የማህተመሥላሴ ወልደመስቀል እና የመኮንን እንዳልካቸውን መጽሐፍት አንብቧል።ስሜት የሚነኩ
ሆነው ስላገኛቸው ደራሲ እንድሆን ገፋፍተውኛል ይላል።ከነዚህ መጽሀፍት የጨዋታ ለዛ ተምሯል፤
ነገር ግን በነዚህ ሳይወሰን የወንጀል እና ልብ አንጠልጣይ ታሪኮችንም አንብቧል። በእንግሊዝኛ
እንደ"Arabian Nights"("አንድ ሺህ አንድ ሌሊት")ያሉ መጽሀፍትን ሲያነብ፣በአማርኛ ደግሞ
ለቁጥር የሚያታክቱ ቤሳ–ልብወለዶችን አንብቧል፤ርዕሳቸውን ግን አያስታውስም። የሁለተኛ ደረጃ
ትምህርቱን ለመከታተል ወደ ወሊሶ ከመጣም ወዲህ በብዛት ያነብ ነበር።በዚያ ሶስት ወይም አራት
ልጆች በአንድነት ሆነው የጥናት ወይም የንባብ ቡድን ይፈጥሩና ሰለ መጽሀፍት ይወያያሉ። የከበደ
ሚካኤል መጽሐፍት በተለይ ግጥሞቹ ይማርኩት ነበር። የአቤ ጉበኛን መጽሀፍትም አንብቧል።
ወሊሶ እያለ የአማርኛ መምህሩ አቶ ወንድሙ ተጫኔ እና የእንግሊዝኛ መምህሩ ህንዳዊው ሚስተር
ቭሬንድራ ኩማር ባሲል፣ በዝርውም ሆነ በግጥም እንዲጽፍ ያበረታቱት ነበር።እነኚህ ሁለት
መምህራን በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቆይታው ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ አስተምረውታል
፤በተለይ ህንዳዊው የእንግሊዝኛ መምህሩ ግሩም እና ልዩ ሰው ነበር። አበራ የ11ኛ ክፍል ተማሪ
እያለ በደብተር ላይ የጻፈውን 200 ገጽ ያለው የልብ-ወለድ ታሪክ ጨምሮ የፈጠራ ስራዎቹን
እርማት የሰሩለት እነኚህ መምህራን ናቸው።ምንም እንኳን መጽሐፉ ከነጭራሹ ባይታተምም፣
አበራ ግን ጥሩ ጅማሮ መሆኑ ተሰምቶት ነበር።ወንድሙ ተጫኔ ይህንን ረቂቅ ሙከራ ተመለከቱና
ለአበራ አፃፃፍን በተመለከተ አንዳንድ ምክሮች ለገሱት፤የተለያየ የአጻጻፍ ዘዬ ያላቸውን መጽሐፍት
329
ጥቋቁር አናብስት
ከዚህ አጋጣሚ በኋላ፣ አበራ ሳያቋርጥ ግጥም መጻፉን ገፋበት።አስራ ሁለተኛ ክፍልን ከጨረሰ
በኋላ፣ አዲስ አበባ ኮተቤ በሚገኘው የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ የመምህራን ማሰልጠኛ ተቋም ገብቶ
ለአንድ ዓመት ተማረ።ትምህርቱን በከፍተኛ ውጤት አንደኛ ሆኖ ካጠናቀቀ በኋላ እዛው
በተማረበት ትምህርት ቤት እንዲያስተምር ይቀጠራል ተብሎ ይጠበቅ ነበር። ነገር ግን አበራ
ግጥሞቹን ማሳተም ፈለገ፤ይህንን ለማድረግ ደግሞ ከኪሱ ገንዘብ አውጥቶ ለአታሚዎቹ በቅድሚያ
መክፈል ይጠበቅበታል።ስለዚህ የተሻለ ክፍያ አግኝቶ ተርፎት የሚቆጥብበት ቦታ እንዲመደብ
ጠየቀ።በዚህ መሰረት ጎንደር በሚገኘው የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
መምህር ሆኖ ተመደበ። ከጎንደር ከተማ ትንሽ ወጣ ብሎ በወር ሁለት ብርቤት ተከራየ። ከጓደኛው
ጋር በተከራየው በዚህ ቤት ውስጥ፣ ቤቱን ለምትጠብቅላቸው፣ ለምታፀዳላቸው እና ምግብ
ለምታበስልላቸው የቤት ሰራተኛ በወር አምስት ብር ይከፍሏታል። ለምግብ በየወሩ ከ25–30 ብር
ወጪ እያደረገ በወር ከሚያገኘው የ230 ብር ደሞዝ ላይ በዓመት 1500 ብር አካባቢ መቆጠብ
ቻለ። ይህንን ቋጥሮ ክረምት ላይ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰና 76 ግጥሞችን አሰባሰበ፤ ሁሉም
የሳንሱር ክፍሉን ይሁንታ አግኝተው ማለፍ ቻሉ። እነኚህ ግጥሞች በ1967 ዓ.ም ቀዳማዊ
ኃይለሥላሴ ከሥልጣን በተወገዱበት የመስከረም ወር "ኩል ወይስ ጥላሸት" በሚል ርዕስ ስር
ታተመ። ግጥሞቹ “ድብልቅ” ናቸው፤ስለ ፍቅር፣ ተፈጥሮ፣ ፖለቲካ፣ የሕይወት ፍልስፍና፣ የሰው
ልጅ ሥነ-ልቦና የመሳሰሉትን ከማካተታቸውም በላይ “አብዛኛዎቹ ሕይወትን ከተለያየ አቅጣጫ
ለማየት የሚሞክሩ ናቸው።” የታተሙት 2,000 ቅጂዎች በስድስት ወር ተሽጠው አለቁ።
አበራንየሚያውቁት ሰዎች ግጥሞቹን እንደወደዷቸው ነግረውታል።የአብዛኛዎቹ ግጥሞች
ማስታወሻነታቸው ለጓደኞቹ፣ ዘመዶቹ እና መምህሮቹ ነበር።አገሪቷ እረፍት አጥታ በማያቋርጥ
ለውጥ ውስጥ ስለነበረች ጊዜው የሚፈልገው የተለዩ ግጥሞችን እንደሆነ ሰዎች ይነግሩት ነበር።
ግጥሞቹ ዘመናዊውንም ልማዳዊውንም የአማርኛ አፃፃፍ የተከተሉናቸው።አንዳንድ ቦታ ቤት
የማይመቱ ስንኞችን መጠቀሙን ጥቂት ሰዎችአልወደዱለትም፤ስንኞቹ ሁሉ ቤት እንዲመቱ
ፈልገው ነበር።አበራ ይህ ልቅ ግጥም የተለመደው ባህር ማዶ እንደሆነ፣በኢትዮጵያ ውስጥ ድግሞ
ሰለሞን ደሬሳ ራሱ ይህንን ልማድ እንደጣሰው ያስታውሳል።የሆነው ሆኖ፣የተሰነዘረበት ትችት
እምብዛም እንዳልነበረ አበራ ይናገራል።
330
ጥቋቁር አናብስት
ከመጽሀፉ ህትመት በኋላ፣ አበራ ወደ ጎንደር ተመልሶ ለአንድ ዓመት ያህል አስተማረ። ከዚያ ወደ
አዲስ አበባ መጥቶ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ገባ።መጀመሪያ ሬዲዮ ላይ ለአምስት ዓመት ከሰራ በኋላ
ወደ ህትመት ክፍል ተዛውሮ ለሁለት ዓመት ሰራ።በዚያም የእለታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ
የዝግጅት ቦርድ አባል ሆኖ ርዕሰ አንቀጽ እና ሌሎች አስተያየቶችንም መፃፍ ጀመረ። የበአሉ ግርማ፣
ብርሀኑ ዘርይሁን እና ታደለ ገብረሕይወት ዝነኛ አብዮታዊ መጽሀፍት ታትመው ሲወጡ፣ አበራ
የጋዜጣው "የባህል መድረክ" የተሰኘ ገጽ አዘጋጅ ነበር። በዚሁ ወቅት አበራ እና አለቃው ትልቅ
ግጭት ውስጥ ገቡ።4አበራ በባህል ገፁ ላይ የበአሉ ግርማን "የቀይ ኮከብ ጥሪ"ን የተመለከቱ
የተለያዩ አመለካከቶችን ያንፀባርቃል። አለቃው ይህንን አልወደዱትም ፤ “ሰውዬው ደራሲዎች ላይ
ችግር በመፍጠር የሚታወቁ አደገኛ በመሆናቸው” የበአሉ ጎላ ብሎ መታየት አላስደሰታቸውም ፤
"በአሉ ለአብዮቱ የማይበጅ አደገኛ ሰው ነው" ብለው ማስወራትም ጀመሩ።አበራ ግን መጽሀፉ
ከመታተሙ በፊት በሳንሱር ክፍል ስላለፈ ጣልቃ እንዳይገቡ ነገራቸው።አለቃውም ለአበራ
"የመጀመሪያ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ" ፃፉለት። አበራ ምላሽ ሰጠ፤ ነገር ግን በሚቀጥለው ሳምንት
አለቃው ዳግም የባህል ገፁን ለማየት ጠየቁ። ግጥሞቹን ካዩ በኋላ አሁንም ለአብዮቱ እንደማይበጅ
በመግለጽ ለአበራ ሌላ ደብዳቤ ጻፉለት።አሁንም ምላሽ ሰጠ። ግጥሞቹ ግን የእነተስፋዬ ገሰሰ፣
የአለማየሁ ሞገስና የዮፍታሔ ንጉሴስሜትን የሚገልፁ ዐይነት ግጥሞች ነበሩ።አለቃው እነዚህ ፀረ–
አብዮት ግጥሞች ናቸው በማለት “ሁለተኛ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ” ጻፉለት።በወር ውስጥአበራ
ሶስተኛ “ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ” ሲደርሰው፣ስራውን ለቆ፣ ቀይ መስቀል ማህበርን ተቀላቀለ። ይህ
የሆነው በ1974 ዓ.ም ነበር። በተፈጠረው ነገር የተነሳ በጋዜጠኞች መሀል ትልቅ ግጭት ሆነ።
አበራ ለማ ከኤርትራ ተገንጣዮች ጋር የሚካሄደውን ጦርነት ለመዘገብ በፍቃደኝነት ወደ ጦር ሜዳ
ከዘመቱ ጋዜጠኞች የመጀመሪያው ነበር። ነገር ግን “ድምፁን አጥፍቶ”፣ “ያለምንም ተቃውሞ
በታዛዥነት” የማይሰራ ከሆነ፣ እነሱ ፀጥ እንደሚያሰኙት (ወደ እስር ቤት በመወርወር ወይም በባሰ
መንገድ) በመግለጽ አስጠነቀቁት።ሶስት የአበራ ረቂቆች(አንድ የልብወለዶች ስብስብ፣ አንድ
የግጥሞች ስብስብ እና በቲያትር ቤት ውስጥ ሊቀርብ እየተጠና ያለ አንድ አጭር ተውኔት) ሳንሱር
ክፍል በሚሰሩት በዚሁ አለቃው ታገዱ።አበራ በ1977 ዓ.ም"ሕይወት ለደራሲዎች ከባድ እና
አስጨናቂ ነው" ብሎኝ ነበር (አለቃው ያን ጊዜ ድረስ የሳንሱር ክፍሉ ሃላፊ ነበሩ።)
331
ጥቋቁር አናብስት
አበራ "ሽበት"ን ራሱ በ2,000 ቅጂ አሳትሞት፣ በአንድ ዓመት ውስጥ ከገበያ ጠፋ። "ሕይወት እና
ሞት" በ5,000 ቅጂዎች ታተመ። ሁለተኛው ህትመት ከቃለመጠይቃችን በኋላ ለገበያ ይቀርባል
ተብሎ ይጠበቃል።በ1975 አበራ ሌላ ሽልማት ተሸለመ።የግጥም ውድድሩን ያዘጋጀው ኢሠፓአኮ
(የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ አደራጅ? ኮሚቴ)ሲሆን አበራ፣ሽልማቱ ደግሞ 800 ብር፣ ሜዳሊያ
እና የምስክር ወረቀት ነበር።
አበራ ከሳንሱር ክፍሉ ጋር ሁሌም ችግር እንደገጠመው ነው፤በተለይ ኋላፊው ጠምደው ይዘውት
የሚጽፈውን ነገር ሁሉ ውድቅ ሊያደርጉበት የተዘጋጁ እንደነበሩ ይሰማዋል። በአንፃራዊነት ኩራዞች
332
ጥቋቁር አናብስት
በኢትዮጵያ የሳንሱር ጉዳይ ለደራሲያን የሚዋጋ እሾህ ሆኖባቸው ስለነበር፣ በተገናኙበት መድረክ
ሁሉ የሚያነሱት ጉዳይ ነው። ደራሲዎች መጽሀፉቸውን ወደ ኩራዝ ይወስዱ ዘንድ“ይገደዱ”ነበር፤
ይሁን እንጂ ኩራዝ ራሱ ብዙ ረቂቆችን አይታተሙም ብሎ መመለሱ አልቀረም።አበራ “የሳንሱር
ክፍሉ ውድቅ ያደረገበትን” ሶስት ረቂቆች ይታተሙለት እንደሆን ወደ ኩራዝ ለመውሰድ እያሰበ
ነበር። በተለይ አራት መለስተኛ ልብወለዶቹን የያዘውን ስብስቡን ለማሳተምጓጉቷል። አንደኛው
ልብወለድ ስለ የመን ሲሆን ወደዛ ጉዞ አድርጎ ሲመለስ የፃፈው ነው።ሁለተኛው ማህበረሰቡ ውስጥ
ስላለው ንቅዘት ነው። ሦስተኛው ሽፍታዎችን ለማጥፋት ቆርጦ የተነሳ አንድ የጥበቃ ቡድን፣
ከአንድ ሽፍታ ጋር ሲፋጠጡ ስለሚያጋጥማቸው አሳዛኝ አደጋ ነው። የመጨረሻው ስለ ፍትህ ጥያቄ
ነው። የመድብሉ ርዕሰ "ነፍስ ይማር" ሲሰኝ የተፃፈው በ1975 ነበር።
ሁለተኛው የታገደው ተውኔት የተፃፈው በ1976 ዓ.ም ነው።ይህ ተውኔት በትውልዶች መካከል
ስላለ ግጭት ነው። የድሮው ትውልድ ያደገው አብሽ ጠጥቶ ሲሆን አዲሱ ትውልድ ደግሞ
በዘመናዊው እና የተሟላ ምግብ ፋፋ ነው።የተውኔቱ ስም "አብሽና ፋፋ" ይሰኛል።
ሶስተኛው የታገደው መጽሀፍ "ጸሐይቱ" የግጥሞች ስብስብ ሲሆን ከ1976–77 ዓ.ም በኢትዮጵያ
የነበረውን ድርቅ እና ረሀብ ይዳስሳል። የታገደው በርዕሱ ምክንያት ነው። "ሳንሱር ክፍሉ
ኃይለሥላሴ ‘ፀሐዩ ንጉሥ’ በመባል ስለሚታወቁ ጸሐይ የሚል ቃል ለርዕሱ መጠቀም
እንደማልችል ነግሮኝ ውድቅ አደረገብኝ" ይላል አበራ።
በዚህ ዐይነት አበራ በሥነ ጽሑፍ እንቅስቃሴዎቹ ተስፋ ቢቆርጥ ምንም አያስደንቅም፤ እርግፍ
አድርጎ ሊተወው ግን አልቻለም። ከቃለመጠይቃችን በኋላም ቢሆን አበራን ዘወትር አገኘው ነበር።
መፃፉን ባያቋርጥም፣ በሕይወት ታሪኩ ላይ ሊጨምር የሚፈልገው ምንም ነገር አልነበረም።
333
ጥቋቁር አናብስት
በ1977 አበራ አብዮቱ እንደጠበቀው ባለመሆኑ ተስፋ ቆርጦ ነበር።ጀርባ መስጠቱ ከ1977 ዓ.ም
ወዲህ በየዓመቱ እየጎላ መጣ እንጂ አልቀነሰም። ነገር ግን በጊዜው ከዚህ በላይ በይፋ መናገር
“አደገኛ” ስለነበረ ተጨማሪ ዝርዝር ውስጥ ላስገባው አልፈለግኩም።
አንዳንድ አንባቢዎች አበራ ገና ለጋ ጸሐፊ በነበረበት ወቅት እንኳን ኢትዮጵያ በጊዜው ከነበሯት
ታላላቅ ጸሐፊዎች አንዱ አድርገው ይቆጥሩት ነበር።
ማስታወሻዎች
2) ገብረ ጉራቻ ማለት "የጥቁሩ ባህር አገልጋይ" ማለት ሲሆን ስያሜውን ያገኘው ጉራቻ
ከሚባለው ወንዝ መሆኑን አበራ ለማ ይናገራል።
4) አለቃው የፕሬስ ክፍል ሐላፊ ነበሩ። እስከ 1978 ድረስም የሳንሱር ክፍል ዋና ሀላፊ ነበሩ።
አበራ ሥነ ጥበባዊ ውበት ያልገባቸውና ሁሉም ደራስያን ላይ ችግር በመፍጠር የሚታወቁ ነበሩ
ይላል። እንደውም ይላል “ችግር የሚፈጥሩት ሆን ብለው ነው ፤ የኢሕአፓ ደጋፊ ስለነበሩ
መንግስትን ማስጠላት ስራዬ ብለው ተያይዘውት ነበር ይባላል።”
334
ጥቋቁር አናብስት
ተስፋዬ ገሠሠ
ለቴአትር የተሰጠ ህይወት ተስፋዬን ለመጀመርያ ጊዜ ያገኘሁት የግል
ችግሮች ተጋርጠውበት ነበር፡፡በመጀመርያ ትዳሩ፤ በስራው፤በገንዘብ…
የአብዮቱ መሳፍንት ይኖሩበታል ተብሎ በሚወራለት በቦሌ መንገድ
ላሰራው ቤት እዳውን ለመክፈል ተስኖት ነበር፡፡ ስለ ኢትዮጵያውያን
ብእረኞች የመጻፍ ሃሳቤን ሲሰማ ደስተኛ ሆኖ ለቃለመጠይቅ መጣ፡፡
ተረጋግቶ ቃለመጠይቁን ለመስጠት ግን ጥቂት ጊዜ ፈጅቶበታል፡፡
በስተመጨረሻ ለነዚህ ቃለመጠይቆች ስንገናኝ አዲስ ህይወት ጀምሮ በአዲስ ሚስት በአዲስ
ኑሮ…..ቤቱንም የማስቀረት እድል ገጥሞት ነበር፡፡(ፔጆውን ሽጦና መስዋእትነትን ከፍሎ ቢሆንም)
አዲስ አበባ ተስፋዬ የእናቱ ታላቅ እህት ጋር አረፈ፡፡ጉሮ ጉቱ ባለው ቤትዋ ነበር ባለቤቷ
የአካባቢው አስተዳዳሪ እያለ ተስፋዬ የተወለደው፡፡ አዲስ አበባ ላይ ተስፋዬ ማህበራዊ ቀውስ
ገጠመው፡፡ይህንንም ክልስ እንደሆነ በጠየቅሁት ጊዜ ባሳየኝ አጸግብሮት ይታይ ነበር፡፡ከአግራሞቱ
መለስ ካለ በኋላ “የሚስማሩን አናት የሚመታ”ጥየቄ እንደ ጠየኩት ለሙሉ ህይወቱና ስራው እርሾ
የሆነው ይሄ ነገር እንደሆነ ነገረኝ፡፡ሰዎች በአዲስ አበባና በትምህርት ቤት ዘመዶቹ መሃል ሲሆኑ
ስለ ተስፋዬ ገጽታው አስተያየት ይሰጣሉ፡፡ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ነጣ ያለ መልክና ሉጫ ጸጉር
335
ጥቋቁር አናብስት
የነበረው ሲሆን ሌሎች ሰዎች ባይነግሩኝ እኔ ልዩነቱን አላስተውለውም ነበር፡፡ይህ አዲስ አትኩሮት
ተስፋዬን ረብሾት ታሞ ሆስፒታል ሊገባ በቅቶ ነበር፡፡ተስፋዬ ሰዎች እንደሚጠቁሙት አክስቱን
ትክክለኛ አባቱ ጣልያናዊ እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ እስከጠየቀበት ጊዜ ድረስ የአእምሮ እረፍት
ማግኘት አልቻለም፡፡ክልሶች በኢትዮጵያ ብዙም የሉም ነበር በዚያ ወቅት1፡፡ጣልያኖችም ጠላት
ስለነበሩ ከጣልያን ወታደር አባት መወለዱ ለሱ አሳፋሪ ነበር፡፡ሌላው ቀርቶ የተስፋዬ አባት
ዘመዶች እንኳን የዘመዳቸው ልጅ እንዳልሆነ ይናገሩ ነበር፡፡"ይቺ እንኳን አባቴ ያወረሰኝን መሬት
ስለፈለጉ የተናገሯት ነች" ይላል ተስፋዬ፡ጥያቄው ለተስፋዬ አንገብጋቢ ሆነበት፡፡በአካል
በሚያስብል ደረጃም ራስ ምታት ይታመምየነበረ ሲሆን በኋላ ነበር የተወገደለት፡፡
ተስፋዬ በአባቱ ገሠሠ ቆለጭነት ተማመነ2 እናቱ ከተጉለት የተገኘችው በለጠች ያየህይራድ
የሚኒሊክ ቅርብ የነበሩት የደጃዝማች ግርማሜ ነዋይም ዘመድ ነበረች3፡፡ተስፋዬ በእናቴ በኩል
ከግርማሜ አራተኛ ትውልድ ነኝ ይላል፡፡ገሠሠ ቆለጭ የፊትአውራሪ ቆለጭ ልጅ ነው፡፡(ፊት
336
ጥቋቁር አናብስት
አውራሪ ቆለጭ እንደ ጓደኛቸው ደጃች በንቲ ሁሉ የኃይለሥላሴ አባት የራስ መኮንን ጦር አዛዥ
ነበሩ) ፊትአውራሪ ቆለጭ ከጉራጌ አንዲት ሴት አግብተው ገሠሠን ወለዱ፡፡4 ራስ መኮንን የሃረርጌን
ግዛት በአስተዳዳሪነት ሲሾሙ ቆለጭና በንቲ አብረዋቸው ነበር የሄዱት፡፡በአካባቢው የነበሩትን
የሃረር ሙስሊም ገዢዎች አሸንፈው አካባቢውን በጠንካራ የመንግስት ቁጥጥር ስር አዋሉት፡፡
ገሠሠ ቆለጭ በቃፊርነት ከጣልያኖች ጋር የተዋጉ ሲሆን ዋነኛውን የሽምቅ ተዋጊ ቡድን
አልተቀላቀሉም፡፡ጣልያኖቹ ገሠሠንና ሌሎችን ገበሬዎች ይቅርታ ለማድረግ ቃል ስለገቡላቸው
በይቅርታ ገብተው በገበሬነት መኖር ቀጠሉ፡፡ነገር ግን ኢትዮጵያ ከወረራው ነጻ ከመውጣቷ በፊት
ነው የሞቱ፡፡ፊትአውራሪ ቆለጭና ደጃች በንቲ ግን ለረዥም ጊዜ በህይወት ቆይተዋል፡፡ለተፈሪም
በሃረር ግዛት አስተዳዳሪ ሳሉ አማካሪ ሆነዋል፡፡
ተስፋዬ የወረሰውን መሬት ልጅነት ይዞት አልያም በትምህርቱ መንስኤነት ብዙም ሊቆጣጠረው
አልቻለም፡፡አክስቱም መሬቱን ብታስተዳድረውም ርቀት ባለው ስፍራ ስለምትኖር በሌለችበት
ስለምትቆጣጠር መሬቱን በስነ ስርአቱ መያዝ አልተቻለም፡፡ ተስፋዬ ውጪ ትምህርቱን ጨርሶ
ሲመጣ ነው መሬቱን ማቅናት የተቻለው፡፡
***
በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የአርበኞች ልጆች በአዳሪነት ሲማሩ ተስፋዬ ከነሱ አንዱ ነበር፡፡ነገር
ግን እንደ ሌሎች ልጆች ዐይነት ስሜት ሳይሰማው (እንደ ሙሉ ኢትዮጵያዊ ሳይቆጠር)እንደ
ባይተዋር እራሱን እያየ ነበር ለበርካታ አመታት የዘለቀው ፡፡እግር ኳስና ሌሎች ጨዋታዎችን እንጂ
ማንበብን አይወድም፡፡እስከ 9ኛ ክፍል መጨረሻ ድረስ በትምህርቱ ጥሩ ውጤት ሳያመጣ ነበር
የቀጠለው፡፡ ከዛ በኋላ ግን እየተሻሻለ መጣ፡፡በወቅቱ የትምህርት ጠቀሜታ አልታየውም፡፡በአንድ
ወቅት በትያትር ውስጥ ሚና ተሰጠው ሚናውም እንደ ህጻን ልጅ መጮህ ነበር፡፡ይህቺ ጥቂት
የቴአትር ክፍል ልቡን ለትያትር ሳታነሳሳው አትቀርም፡፡አንደኛ ደረጃ ሳለ የትንቢት ቀጠሮን
337
ጥቋቁር አናብስት
ሌሎቹ መሆኑን ለማስገንዘብ በመጣር ሁሌም ይሳተፋል፡፡ሁሌም ባይሆን ወደ ሃገር ፍቅር ቴአትር
ቤት ገንዘብ ባለው ወቅት ጎራ ማለትን ያዘወትራል፡፡ራዲዮንም በብዛት ይከታተላል፡፡
በ1948 ዓ.ም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኋላ ቀጥታ ወደ ዩንቨርሲቲ ኮሌጅ ገባ፡፡
ለአራት አመታትም ዋነኛ ትምህርቱን ህግ በማድረግ ተማረ፡፡ኮሌጅ እያለ ነበር ተዋናይ የመሆን
ፍላጎት ያደረበት፡፡በፊልሙም ሆነ በመድረክ…በተጨማሪ ደግሞ (ወይም) በተወሰነ መልኩ ለሱ
እንደትወና ስለሚቆጠር በተጓዳኝ ጠበቃ የመሆን ፍላጎትን አሳደረ ምንም እንኳን እነዚህ ሃሳቦች
ከውጥኑ ቅርጽ ባይዙለትም ቅሉ፡፡ለሱ ኮሌጅ ከጨረሰ በኋላ (የሆነ መልካም ነገር ብቻ
እንደሚመጣ) እርግጠኛ እየሆነ መጣ፡፡“መዝናናትንና ትፍስህት ያለው ህይወትን እፈልግ ነበር
ትርጉሙ ባይገባኝም ምንአልባት ስራ ማለት ይሆናል፤ ሚስት ፡ መኪና÷ ብቻ ከፖለቲካ ጋር
አይነካካ”
ሁለተኛ ደረጃ እያለ ልጃገረዶች መቃኘት ጀመረ፡፡በፍቅር ወደቀ (እንበለ ጾታዊ እሳቤ ወይም
ፍትወት ነበር፡፡አቅም ሳላበጅ ምንም ነገርን ከሴት ጋር አልፈጸምኩም) ይላል ባለ ረጅም ፀጉሯ
ፍዮሬላ ግን ሁሉንም በፍቅር ለማንበርከክ ጉልበት የነበራት “እንደኔው ክልስ” ነበረች ይላል፡፡
ቀጨኔ መድሃኒያለም አካባቢ ሄዶ እየሰረቀ ቆነጃጅቶቹን ይመለከታል፡፡ምንአልባት ከነሱ መሃል
አንዷ ሚስቴ ብትሆን እያለ ይከጅላል፡፡ገና ብቅ ሳይሉ ግን እየተቀለቡ ተቸግሮ በትምህርት ቤትም
ሆነ በኮሌጅ ትክክለኛ የሴት ጓደኛ ሳይኖረው ነበር ግዜውን የገፋው፡፡ሲበዛ አይናፋር ነበር፡፡በኋላ
ወደ በቀይ መብራት ወዳበደው የውቤ በርሐ ለዳንስና እንዳንዴም እጁ ከረጠበ አቅፎ ለማደር ጎራ
ማለቱን ተያያዘው፡፡ይህም የሴት ጓደኛ ከመያዝ ይቀላል፡፡ስለዚህ ሲመሻሽ ስብሃት ገብረ
እግዚአብሔርን ጨምሮ ከሌሎች ጓደኞቹ ጋር ለመዝናናት ወደዚያ ይሄዳሉ፡፡
ኮሌጅ ውስጥ በስነ ጽሁፍና ክርክር ክበቦችም ይሳተፋል፡፡ ይህም ለሰዎች በአንድ በማንኛውም
አርእስት ላይ ማውራት መጻፍ እንደሚችል ለማሳየት ያህል ነው እንጂ ትወና ነበር ዐይነተኛ
ፍላጎቱ፡፡በተጨማሪም ቅርጫት ኳስ የጠረጴዛና የሜዳ ቴኒስ እና ሶፍትቦል የሚዝናናባቸውና
339
ጥቋቁር አናብስት
***
ከዩንቨርሲቲ ኮሌጅ በ1951 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ አጠናቆ ወጣ፡፡በ1952 ወደ አሜሪካ በነጻ
የትምህርት እድል ተጓዘ፡፡እዚያ ለሁለት አመታት ያህል እስከ 1953 መጨረሻ ድረስ ቆየ፡፡ይህም
በአይዘንሃወር እና በኬኔዲ የስልጣን ዘመን ነበር፡፡በቺካጎው ኖርዝ ዌስተርን ዩንቨርስቲ ነበር
ያጠናው፡፡በሰሜኑ መሆን ከ ደቡቡ የሃገሪቱ ግዛቶች ይልቅ ለአፍርቃውያን ተማሪዎች ይሻላል፡፡
በአሜሪካ ውስጥ እያለ የቀረው አለም ምን ያህል እንደሰለጠነ አይቶ የማህበራዊ ቀውስ ተጽእኖ
አድሮበታል፡፡አሜሪካንን ከሃገሩ ጋር ማነጻጸር ወደ ጥልቅ መሬት የመስመጥ ያህል ሆነበት፡፡
ዘረኝነትንም በዚያ አየው፡፡ጥቁሮች በሚገባ አይስተናገዱም፡፡የመኝታ አገልግሎት በፈለገባቸው
አንዳንድ ቡና ቤቶች እንዳይገለገል ጥቁር በመሆኑ ብቻ ተከልክሏል፡፡ይህን ከነሱ ቁሳዊ ሃብት ጋር
በማናጸር (ትናንሽ አእምሮዎች ታላላቅ ህንጻዎችን ገነቡ)ሲል ደምድሟል፡፡“ለዚህ ይሆናል
ኢትዮጵያ መዘመን ስትፈልግ ፊቷን ወደ ምስራቅ የመለሰችው”ይላል፡፡ተስፋዬ በትምህርቱ በኩል
“የምፈልገውን አግኝቻለሁ” ስለሚል በአሜሪካን ያሳለፈው ጊዜ መልካም እንደሆነ ያስባል፡፡
በአሜሪካ በነበረው ቆይታ ለሃገሩ አንድ ነገር ማድረግ እንዳለበት በመወሰን በቴአትሩ ዘርፍ
እውቀቱን ለማበርከት ተነሳ፡፡
የመጀመርያው አመት የመሰናድኦ ሲሆን የሚቀጥለውን አመት በቴአትር ጥበብ የማስትሬት ዲግሪ
የምረቃ ስራዎችን በመስራት ነበር ያሳለፈው፡፡ለመድረክ የበቃ ተውኔት ጻፈ፡፡ በአንድ የጣልያን
340
ጥቋቁር አናብስት
***
ተስፋዬ በዚህ ዘርፍ መሰረቱ ደካማ ሆኖ ሳለ ለምን የቴአትር ጥበብን ለማጥናት ፈለገ ?በተወነበት
"እዮብ" በተባለው ተውኔት የተነሳ እንደሆነ ይናገራል፡፡ስለ መጸሐፍ ቅዱሱ እዮብ የተጻፈ ነው፡፡
ይህም የተፈጸመው ኮሌጅ አራተኛ አመት እያለ አዲስ አበባ ሆኖ ነበር ፡፡ሚናው እርሱ ራሱን እንደ
እዮብ የተበደልኩ ነኝ ብሎ አስቦ ተጫወተው፡፡ከገጸ ባኅርይው ጋር ተዋወቀ፡፡ ህመሙ ለማንነቱና
ለክብሩ ባለው ትግል ተስማማው፡፡ እግዚአብሔርም ለእዮብ “እንግዲህ እንደ ሰው ወገብህን
ታጠቅ እጠይቅሃለሁ አንተም ተናገረኝ”አለው፡፡ተስፋዬ ራሱ የተውኔቱን ጠቃሚ ነጥቦች ማሰባሰብ
ጀመረ፡፡በግል አስተሳሰቡን ሁሉ ተገዳደረው፡፡እሱ እንዳለው ከሆነ ሰዎች “በተሰጥኦ የተተወነ”
ተውኔት ነው ይላሉ፡፡“ይህ የሆነው እዮብን ስላወቅሁት ነው ለመኖር የሚደረግ ፍትግያን
እንድጋፈጥ አደፋፈረኝ፡፡የመጀመርያው ምሽት ውብ እንደነበር ተሰምቶኛል፡፡ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ
ሁለተኛውን ምሽት ተከታትሉት”ተስፋዬም በዚህ ወቅት“ትንሽ ትወናውን ስላጋነንሁት ድምጼ
ቢሰልም ንጉሱ ግን በተውኔቱ ተመስጠው ነበር ጠንካራ ስራ በመስራቴ በተውኔቱ ላይ የነበሩ
ግድፈቶችን እንዳጠራ ረድቶኛል ስለዚህም ጭምር ነው የተውኔቱ ´እንከኖች´ ሳይቀሩ መልካም
የነበሩት” ይላል፡፡
***
እነዚህ ከእሾህ አክሊል ተውኔት በኋላ በአዝማሪነት የመመደብ ፤የጨዋ ቤተሰብ ልጆችን እንዳለ
ማግኘት ያሉ ችግሮች በተጨማሪም ከጸጥታ ሃይሎች ጋር በቀጣዩ ተውኔት የገባው እሰጥ አገባ
አስጨናቂ ነበሩ፡፡11ጥንቃቄን መውሰድ ቢጀምርም ወጣትና ስሜታዊ ነበር፡፡ከጸጥታው ክፍል ጋር
ያለውም ልምድ መጥፎ ነበር፡፡12 ነገሩም የስራ ባልደረቦቹ መወያያ በመሆኑ“ያው ታውቀዋለህ ይሄ
እኮ አቢሲንያ ነው” በማለት እንደዚህ ያለ ነገር እንደሚጠበቅ ነገሩት፡፡
***
ተስፋዬ የሺን በመጻፉ ተጨማሪ 1500 ብር ገደማ አገኘ፡፡ በዚሁ ተጠቃሎ እንደ ተዋናይነትና
ዳይሬክተርነቱ ግን የተጨመረለት ነገር የለም፡፡ብዙ ጊዜ የሚተውነው በወቅቱ የሰለጠነ የሰው
ሃይል እጥረት ስለነበር ነው፡፡
በቀዳማዊ ኃይለሥላሤ ቴአትር ተስፋዬ ከስራ አስኪያጁና ከጸጋዬ ገብረመድህን ስር ሲሆን ጸጋዬ
እሱ ከመግባቱ ከጥቂት ወራት በፊት እንደ ቋሚ ጸሃፊና በትያትር ክፍሉ ሃላፊ በመሆን ነበር
የተቀጠረው፡፡ተስፋዬ እንደሚለው ጸጋዬ ገንዘብ ያስፈልገው ስለነበረ ጽሁፉ ላይ አድምቶ
ይሰራል፡፡ጭምትና ከሰው የማይግባባ ሲሆን ቁጭ ብሎ መጻፍ ብቻ ነበር ስራው፡፡በአንጻሩ
ተስፋዬ ግን (ከመሬቱ በሚያገኛት ገቢ) እየታገዘ ከጽህፈቱ ቀንሶ ከተግባቦቱ አብዝቶ ችሮታል፡፡
ሁለቱ ግን የማይነጣጠሉ ሲሆኑ ለቴአትሩ እድገት አብረው አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡ ጸጋዬ
ተስፋዬን ለተውኔትና ዳይሬክተርነት ስራው ሲፈልገው ተስፋዬ ደግሞ የጸጋዬ ቃለ ተውኔቶች
ያስፈልጉታል፡፡ አብረው በደስታ ሰሩ፡፡ቴአትሩ እመርታን እንዲያሳይ በመግፋትም በጥራቱ ረገድ
ሊያሻሽሉት በቅተዋል፡፡“እርስ በራሳችን የምንፈላለግና አንዳችን የሌላችን ጥገኛ ነበርን ”ሲል
አስተያየቱን ይሰጣል ተስፋዬ|፡፡
344
ጥቋቁር አናብስት
በሃምሌ 1955 ዓ.ም ተስፋዬ በረዳት ዳይሬክተርነትና በትወናም ጭምር የጸጋዬ "ቴዎድሮስ
"የተሰኘው ተውኔት በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ራስ መኮንን አዳራሽ ሲቀርብ ለመሳተፍ
በቃ፡፡ወቅቱ የትምህርት አመቱ መዝጊያ ሲሆን ንጉሱም ታድመዋል፡፡ተስፋዬ መልእከተኛ ሆኖ
የተራኪውን ገጸ ባህርይ ወክሎ ተጫወተ፡፡በተጨማሪም ከቀዳማይ ኃይለሥላሴ ቴአትር የተገኙ
ተዋንያን ከዩንቨርስቲውም ከውጪም የመጡ አማተርና ፕሮፌሽናል የሃገር ውስጥና የውጪ
ተዋንያን ተሳትፈውበታል፡፡
***
ከዚሀ በኋላ ነበር ተስፋዬ በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የባህል ማዕከልን በ1955 ዓ.ም መስከረም
ወይም ጥቅምት ወር ላይ የተቀላቀለው፡፡እዚያም እስከ ኢትዮጵያውኑ 1960 ቆየ፡፡ በመጀመርያ
ከአሜሪካዊው ዶክተር ፊሊፕ ካፕላን ጋር በቅርበት ሰራ፡፡የጸጋዬ ገብረመድህን ቴዎድሮስ ግሩም
አፈጻጸም ነበር ዩንቨርሲቲውን የባህል ማዕከል እንዲከፍት የገፋፋው ፡፡ባህል ማዕከሉ
በሚቀጥለው የትምህርት አመት 1956 ዓ.ም ተከፈተ፡፡ካፕላን ዳይሬክተር ሲሆኑ በአሜሪካ የብዙ
አመት የስራ ልምድ ያላቸውና ኢትዮጵያ ውስጥ በምርምር ላይ የነበሩ ሰው ነበሩ ፡፡ተስፋዬ
የአማርኛ ቴአትር ዳይሬክተር ሲሆን ለካፕላን ረዳትም ነበር፡፡ካፕላን በነሃሴ 1956 ዓ.ም ለቀው
ሲሄዱ ተስፋዬ የባህል ማእከሉ ዳይሬክተር ሆነ፡፡በማዕከሉ የመጀመርያ አመት ኦርኬስትራ
ኢትዮጵያ ሊመሰረት በቃ፡፡ የመጀመርያው ዳይሬክተሩም ሐኪም ኤል-ዳብ ዋነኛ የሙዚቃ
ዳይሬክተርና የውዝዋዜ አስተባባሪ (ኬሮግራፈር) ሆኑ፡፡14ከኦርኬስትራው ምስረታ ብዙም ሳይቆይ
ተስፋዬ ለማ በተስፋዬ ገሠሠ ተቀጥሮ ተቀላቀለ፡፡በኋላም ከሐኪም ኤል-ዳብ ተከትሎ ዳይሬክተር
ሆኗል፡፡
345
ጥቋቁር አናብስት
ተስፋዬ ገሠሠ ካስተማራቸውና በኋላ ታዋቂ ከሆኑት ተዋንያን መሃል ወንድወሰን ገብረኢየሱስ
ቆይቶ የራስ ቴአትር ስራ አስኪያጅ በኋላም የብሔራዊ ቴአትር የኪነጥበብ ዳይሬከተር የሆነ ተስፋዬ
እራሱ ዳይሬክት ባደረገው የብርሃኑ ዘርይሁን "ሞረሽ" ትያትር ላይ እየተወነ እዚያው መድረክ ላይ
ህይወቱ ያለፈች፤ወጋየሁ ንጋቱ ፤ደበበ እሸቱ ሃገር ፍቀር ትያትር ቤት እ.ኤ.አ በ1987 ለመድረክ
በዋለው በሼክስፒር የቬንሱ ነጋዴ ላይ እንደ ሻይሎክ የተጫወተ እና ሌሎችም ስራዎችን የሰራ፤
አባተ መኩርያ፤ተፈሪ ብዙአየሁ ይገኙባቸዋል፡፡ከተስፋዬ ታዋቂ ፕሮዳክሽኖች መሃል የመንግስቱ
ለማ "ያላቻ ጋብቻ" ፤የከበደ ሚካኤል "ሮምዮና ዡልየት"፤የራሱ የተስፋዬ አባትና ልጆች፡"oda
oak oracle" በጸጋዬ በእንግሊዘኛ የተደረሰ የመሳሰሉ ይገኙባቸዋል፡፡እነዚህ ሁሉ ተውኔቶች
በተስፋዬ ዳይሬክተርነት በባህል ማዕከል የቀረቡ ነበሩ፡፡“ቦታው በወቅቱ የተጨናነቀ ሲሆን
አማርኛም ሆነ እንግሊዘኛ ተውኔቶች ለእይታ ይበቁ ነበር ”ይላል ተስፋዬ፡፡ ከውጪዎቹ ተስፋዬ
የኢዮንስኮን rhinoceroes,who´s afraid of virginia wolf በኤድዋርድ አልቢ
waiting for godot የሳሙኤል ቤኬት ይገኙባቸዋል፡፡አብዛኞቹ አዲስ ዐይነት ለሙከራ
የሚሰሩ ቴአትሮች በኢትዮጵውያንና በውጪ ዜጎች የቀረቡ አውደ ርእዮችና የኦርኬስትራው
የሙዚቃ ድግሶችም ነበሩ፡፡
***
ከስራው በተጨማሪ ተስፋዬ በዚህ ወቅት የተጣበበ የቤተሰብ ህይወትም ነበረው፡፡ሁለት ልጆችንም
አፍርቷል፡፡መለስ ብሎ ያን ጊዜ ሲያስታውስ “ ጥሩ ይመስላል አስከፊ ጊዜ አልነበረም” ሲል
ይገልጸዋል፡፡የደሞዝ ጭማሪ ባይደረግለትም ንቁ ነበር፡፡ከመሬቱም ገቢ ነበረው፡፡የሚያከራያቸው
ቤቶችም ነበሩት፡፡የልጅነት ጉልበትም ሀይለኛ ስሜትም ነበረው፡፡ይህን የህይወቱን ጊዜ
“ኤልዛቤታዊ ዘመን”እና “አስደሳቹ ወቅት” ሲል ይጠራዋል፡፡ከትእይንቶች በኋላ ያመሻሻል፡፡
“ገንዘብ በኪሴ ሞልቼ ከተማዋን አስስ ነበር” ልጆቹ ተረሱ፡፡ምንም እንኳን ቁሳዊ ፍላጎታቸው
ቢሟላም የሱን በቂ ትኩረትን ማግኘት አልቻሉም፡፡ “ደንበኛ አባት ለመሆን አልተዘጋጀሁም እኔ
እራሴ ተገቢውን አስተዳደግ ስላላደገሁ” ይላል፡፡ሚስቱ ገጠሬ ናት ታጋሽና ቅር የማይላት፡፡
የተስፋዬ ወጣት ደስተኝነት አሞኛት፡፡ የተስፋዬ ቤተሰቡን ቸል የማለት ባህርይው ግን ጎልቶ
የወጣው ከአብዮቱ በኋላ ነበር፡፡ባይሰክርም ቀን በቀን መጠጣት ጀመረ፡፡አራት አምስት ቢራ አንድ
መለኪያ ውስኪ ከዚያ ያቆማል፡፡ ሞቅ ብሎት ነበር በወደ ቤት የሚመጣው፡፡ነገር ግን አይሰክርም፡
ከስምንት እስከ አስር ሰአት ባለው ጊዜ መሓል ነበር ቤቱ የሚመጣው፡፡በወቅቱ ባል የሚስቱ የበላይ
ነው የሚል ፊውዳላዊ ግንዛቤ ነበር፡፡ከአብዮቱ በኋላ ግን ይሄ ሊቀየር ችሏል፡፡የተስፋዬ አጠጣጥ
እየፈጠነ ይህም ከሚስቱ ጋር ችግሮቹን እያባባሳቸው መጣ፡፡በፊት ብዙ የምትችለው አሁን መታገስ
346
ጥቋቁር አናብስት
ሶስተኛው በተስፋዬ ተጽፎ ለመድረክ የበቃው ተውኔት (መጀመርያ በባህል ማእከል በ1959
አካባቢ በኋላ ከአመት በኋላ ደግሞ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ቴአትር የቀረበው)" አባትና ልጆች"
ይሰኛል፡፡የቱርጌኔቭ ታዋቂ ርእስ በሃሳቤ ነበር መሰል ርእሱን ሳወጣ የተውኔቱ ሃሳብ ግን
“በስነጽሁፍ ትውልድ መሃል ያለው ክፍተት መጽሐፍ” ብሎ ከሚያስቀምጠው ከዲ.ኤች ላውረንስ
sons and lovers ጋር ቅርርብ ነበረው ሲል ያስቀምጣል፡፡ምንም እንኳን የውጪ ተጽእኖዎች
ቢኖሩም ሙሉ በሙሉ ኢትዮጵያዊ እንዲሆን አስቦ ነበር የጻፈው፡፡ስለ አንድ አባትና ሁለት ልጆቹ
የሚያወሳ ነበር፡፡ታላቅየው (ሃላፊና ሁሉ በእጁ የሚባል ) አይነት ባህርይ ሲኖረው የክብር ዘበኛ
አባልም ነበር፡፡ታናሽየው ደግሞ ራሱን የሚያዳምጥ ሃሳቡን የሚያመናትል አይነት ባህርይ ያለው
የኮሌጅ ተማሪ ነበር፡፡ታናሹ ማንነቱን የህይወትን ትርጉም በመፈለግ ወዘተ በመሳሰሉት ሲጠመድ
እነዚህ ዐይነት ጥያቄዎች ግን በታላቅየው ጭርሱኑ አይታሰቡም፡፡ተስፋዬ በዚህ ለማመልከት
የሞከረው ወጣቱ ትውልድ የራሱን እሴት በመፈለግ ስራ መጠመዱን ይህን ሲያደርግ ግን ከታላቆቹ
ምንም እርዳታ አለማግኘቱን ማሳየት ነው፡፡ባህላዊ እሴቶች (እንደ ሃይማኖት፤ባህል ወዘተ)ከይዘቱ
አንጻር በሂደት ለፈተና ይቀርባሉ፡፡ትያትሩ በተጋጋለ ፍላጎት የተሞላ በተወሰነ መልኩ ቁምነገራም
ስለመጻኤ አመላካች ግን ለስነምግባር አስተምህሮ እምብዛም የሆነ ነው ይለዋል፡፡
በ1957 ዓ.ም ተስፋዬ ከአመት እስከ አመት የሚሄድ በጥበባት ላይ ያተኮረ (ምንአልባትም ለ52
ክፍል የሄደ)ሳምንታዊ የሬድዮ ፕሮግራም ጀመረ፡፡የኪነጥበባት ጉዞ የተሰኘ ፕሮግራሙ ለ30
ደቂቃ የሚደመጥ ሲሆን ይህ መርሐግብር በአዲስ አርእስትና በሌሎች ፕሮዲውሰሮች
በጭውውታችን ወቅትም አየር ላይ ይውል ነበር፡፡ተስፋዬ እንደሚለው ከሆነ ይህ ፕሮግራም
ከመድረክ በላይ ብዙ ህዝብ ጋር የመድረስ አቅም ነበረው፡፡“በጊዜው ኪነጥበባቱን ለህዝቡ
አስተዋውቋል አላማውም ለጥበብ ያለንን ንቃተ ህሊና ማዳበር” ነው፡፡ለተስፋዬ ይህ የትርፍ ጊዜ
ስራው ሲሆን በፕሮግራም 60 ብር ብቻ ነበር የሚያገኝበት፡፡በሱ እግር የተተካው ወንድወሰን
ገብረኢየሱስ ግን እንደ ሙሉ ጊዜ ስራ ለበርካታ አመታት ይዞታል፡፡
ቀጣይ የተስፋዬ ተውኔት ለአባትና ልጆች እንደ´ተቀጥላ´ ተውኔት ተደርጎ የተጻፈ ነው፡፡"ኡኡኡኡ"
ወይም "በገላጋይ"ስለ ገበሬ ባልና ሚስት የተደረሰ አጭር ተውኔት ሲሆን መጀመርያ በባህል
ማዕከል ቀጥሎ በራድዮ ነበር የቀረበው፡፡በአባትና ልጆች ላይ ያለው አባት በዚህኛው ትአትር ላይ
347
ጥቋቁር አናብስት
መጥቶ በተጣሉት ሁለቱ ባለትዳሮች መሃል እርቀ ሰላምን ያወርዳል፡፡ የገጠሩን ህይወት ለማሳየት
የጻፍኩት ተውኔት ሲሆን “በቀላል ህይወት ውስጥ ያውን የፍቅር ገጽታ ያሳያል” ይላል፡፡16
የመጨረሻው በባህል ማዕከል ሳለ የጻፈው ቴአትር "ሲዳዳን" ነው፡፡“ባለአንድ ገቢር ህልም አስተኔ”
ተውኔት ሲል ይጠራዋል፡፡ በ1959ዓ.ም ነው የተጻፈው ሲል ያስባል፡ በሬድዮ ብቻ ነበር
የተላለፈው፡፡ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ምንአልባት በ1960ዓ.ም አካባቢ ተስፋዬ መልሶ አነሳው ይህም
የሆነበት መክንያት የገጸ ባህርያቱ ወለፈንዴነት ነው፡፡ከባሻገር ነው የሚመጡ፡፡የሚያወሩት
የሚጨዋወቱት ሁሉ ግራ በሚያጋባ የድምጽ ቅላጼ ሲሆን ይነጋገሩና ተነው ይጠፋሉ፡፡ታሪኩ
በህልም አለም የሚታይ ዐይነት በተመሳሳይ ወቅትም እውን የሆነ ነው፡፡ “ሁሌም ጥላ ስለሆነው
ሞት፤ስላቅ፣ስስት” ነበር ተውኔቱ፡፡ ተስፋዬ የሬድዮ አድማጩ እንዴት እንደተቀበለው
የሚያውቀው ነገር የለም፡፡በዚያ ላይ ደግሞ ስለ ሰዎች አስተያየት በማመንታት የሚሰነዘር ስለሆኑ
በማለት ብዙም ጠቀሜታ እነደሌላቸው በማሰብ አይጨነቅም፡፡ነገር ግን የራሱን ተውኔቶች ከሞላ
ጎደል በተጻፉበት ሁኔታ ሲተወኑ ማየት ለሱ ያሳፍረዋል፡፡እሱ የሚፈልገው ተውኔቱን ከተዋንያኑ
ጋር ተጫውቶ እዚያው እያለ የክለሳ ማሻሻያዎችን ማድረግ ነበር፡፡በገሃዱ አለም ግን የዚህ ዐይነት
ለውጥን ለማድረግ ትንሽ እድል ብቻ ነው ያለው፡፡
ተስፋዬ ገሠሠ በ1960 ዓ.ም መጨረሻ የባህል መዕከልን ለቀቀ፡፡ ለማዕከሉ የሚመደቡ በጀቶች
መቆራረጥና የሱ በተለይ ለኦርኬስትራው ይህን ለሟሟላት መዳከር አሰለቸው፡፡አንዳንድ
ሙዚቀኞች ከገንዘብ ጋር በተያያዘ ለቀቁ፡፡በመጨረሻ ተስፋዬ እራሱ ለቅቆ እጥፍ ደሞዝ ወዳገኘበት
የኢትዮጵያ ቴሌኮሚዩኒኬሽንን በህዝብ ግንኙነት ሰራተኛነት ተቀላቀለ፡፡ ከ1961 መጀመርያ
አንስቶ እስከ 1965 ድረስ በዚህ ስራ ቆየ፡፡ ከስራዎቹ መሃል አንዱ የድርጅቱን መጽሄት ቴሌ
ነጋሪት ላይ በአርትኦት መሳተፍ ነበር፡፡እሱ ነበር ለእውቅና ያበቃውና እስከ ቃለመጠይቃችን
ወቅት እንዲዘልቅ ያስቻለው፡፡በዚህ ስራ ላይ እያለ ኢትዮጵያን በደምብ እንዲያውቅ ያስቻለውን
ጉዞ ተጉዟል፡፡በትርፍ ግዜው ደግሞ በተለያዩ ተውኔቶች ላይ ይሳተፋል፡፡ ለምሳሌ ግራዝያኒን
በመወከል በጸጋዬ ገብረ መድህን ጴጥሮስ ላይ፤እንደ ሃምሌት በመሆን በጸጋዬ ገብረ መድህን
የሼክስፒር ትርጉም ስራ ላይ፤እንዲሁም እራሱ ዳይሬክት ባደረገው የነጋሽ ገብረ ማርያም የድል
አጥቢያ አርበኛ ላይ የጣልያን ወታደር በመሆን፤ወደ አልጄርያ በማቅናትም የአፍሪካውያን የጥበብ
ፌስቲቫል ላይ ጴጥሮስን ደግሞ ተጫውቷል፡፡
ቴሌኮሚዩንኬሽን በገባ በመጀመርያው አመት እስካሁን ድረስ የታተመለት ብቸኛ የተውኔት ስራው
የሆነውን "እቃው" የተሰኘው ተውኔት ደረሠ፡፡እንደ እቃ ለአገልግሎት ስለሚውሉና እንደ እቃ
ስለሚቆጠሩ ሰዎች ነው፡፡ከዚህች መጽሐፍ ህትመት በኋላ እንዲህ ያሉ ልግመኞችን “እቃው”ብሎ
348
ጥቋቁር አናብስት
እዚህ እንደ ህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ሆኖ ነበር የሚሰራው፡፡የመጀመርያው የላይኛው ቢሮን ጣእም
ማጣጣም ጀመረ፡፡ጠቃሚ ስብሰባዎችን ከጠቃሚ ሰዎች ጋር አካሄደ፡፡ በሆቴሎች ከስብሰባ በኋላ
ከነዚህ ጠቃሚ ሰዎች ጋር ይጠጣል፡፡ደሞዙም ጥሩ ሆነለት፡፡ቆንጆ ቆንጆ ሴቶችን አግኝቶ
ተቃበጠ፡፡ከተወሰኑት ጋር ወሲብ ቢፈጽምም እንደ ጓደኞቹ ግን ለሊቱን ሙሉ አይቆይም፡፡ከግዜ
349
ጥቋቁር አናብስት
ተስፋዬ መጻፉን ቀጥሎ በርካታ አጫጭር ታሪኮችን ጨረሰ፡፡በባህል ማዕከል ጊዜው ሲያደርገው
እንደነበር ሁሉ በጥበብ ዙርያ ለተለያዩ ጋዜጦች መጻፍ ጀመረ፡፡በወቅቱ ለጥበብ እንደ አስተዋዋቂዋ
ነበር፡፡የአጫጭር ታሪኮቹ ስብስብና የግጥሞቹ መድበል "መተከዣ" ተብላ በ1967 ዓ.ም
ለህትመት በቃች፡፡ንጉሱ ከስልጣን ከመወገዳቸው በፊት ለአታሚዎቹ ተልኮ የነበር ቢሆንም ያለ
ምንም ስራ ለ6 ወር ተቀመጧል፡፡ከአብዮቱ በኋላ ነበር ብቅ ያለችው፡፡ከእቃው ውጪ የታተመች
ብቸኛ ስራው ነች፡፡ሁለቱ ታሪኮች ከትምህርት ቤት ዘመኑ ሲሆኑ ጓደኞቹን ሞዴል በማድረግ
ተጠቅሞባቸዋል፡፡እነዚህ ታሪኮች ስለተማሪ ህይወት የሚያነሱ እንጂ ፖለቲካዊ ይዘት
አልነበራቸውም፡፡አንዱ ታሪክ ስለ አንዲት አማራ ሴተኛ አዳሪና ስለሚያዘወትራት ጋናዊ ደንበኛዋ
ነው፡፡“በቀደመውም አሁን በምንኖርበት ዘመን እንደሚታየው ሁሉ የተወሰነ ዘረኝነት
ተንጸባርቆበታል”18ተስፋዬ የሚወደው ሌላው ታሪክ ሽልንጌ (የ ኦ .ሄንሪ ዐይነት ታሪክ ነው)በባቡር
ወደ ሃረር ሲሄድ ያገኘውን ልምድ የሚያካፍልበት ታሪክ አንዳንዶች “ይሄ ምርጡ ስራው ነው”
ይላሉ፡፡ተስፋዬ“የሆነ ዐይነት የቼኾቭ ነጸብራቅ በታሪኮቹ ውስጥ አለ፡፡አብዮተኛ ባይሆኑም
ያለመርካት ስሜት ግን ይነበብባቸዋል ቆስቋሽ የምባል ዐይነት ሰው አይደለሁም፡፡ ወሬኛ እንጂ
አሳቢ ዐይነትም አይደለሁም” ይላል፡፡ስለግጥሞቹ (አንዱ ለእናቴ የሚለው ለእናቱ መታሰብያ
የተደረገ ነበር ከንግግራችን ጥቂት ጊዜ በፊት በሬድዮ ሄዷል) ሲናገርም ግጥሞቹ የግል ልምዱ
ነጸብራቆች የሆኑ ማህበራዊ ትችቶች ያዘሉ በሞትና ህይወት ግንዛቤዎች ላይ የተንተራሱ ናቸው
ይላል፡፡የበሰሉ ሌሎች ተጨማሪ ስራዎችን ማሳተም ቢፈልግም ሳይቻል ቀርቷል፡፡
***
በአብዮቱ አመት በሚያዝያ 1966 ተስፋዬ የሃገር ፍቅር ቴአትር ስራ አስኪያጅ ሆነ፡፡19 ቀጣዩ
ሙዚቃዊ ተውኔቱ "ማነው ኢትዮጵያዊው?" በ1966 ዓ.ም የተጻፈውም ሆነ ለመድረክ የበቃው
የሃገር ፍቅር ስራ አስኪያጅ በነበረበት ወቅት በመስከረም 67 ነው፡፡"ማነው ኢትዮጵያዊው?"
የሚለው ርእስ ከታደለ ገብረ ህይወት መጽሐፍ የተወሰደ ሲሆን ተስፋዬ ገጸባህርያቱን ቢጠቀምም
የታሪኩ ፍሰት ግን የተለየ ነበር፡፡“ከፕርል ኤስ በክ the good earth ከሚለው መጽሀፍ በርካታ
ክፍሎችን ተከትሎ ወደ ሀገርኛ በመመለስ ራስን ለማወቅ የተደረገ ጠንካራ ሙከራ ነው” ይላል
ተስፋዬ፡፡በተውኔቱ ላይ ያሉት ግጥሞች በሙዚቃ መልክ የቀረቡ እንጂ ራሳቸውን ችለው
በግጥምነት መልክ ሊቀርቡ የሚችሉ ዐይነት አልነበሩም፡፡“እንደ ኦክሎሃማ ሙዚቃዊ ትእይነት
350
ጥቋቁር አናብስት
351
ጥቋቁር አናብስት
***
ከሶስት ወራት በኋላ በሬድዮ ሞስኮ የስራ እድል ቢሰጠውም መንግስት የመውጫ ቪዛ ከለከለው፡፡
በምትኩ ወደ ትምህርት መገናኛ ማእከል ተልኮ ለወራት ቆየ፡፡
ተስፋዬ በእስር ቤት ሳለሁ “በብሄራዊ ቴአትር የነበሩ ተዋንያን በጸጋዬ ገ/መድህን ላይ አመጹ”
ይላል፡ጸጋዬ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ይሰራ በነበረው በካሳዬ ዳመና ተተካ፡፡ከትምህርት መገናኛ
የተወሰነ ቆይታው በኋላ ተስፋዬ ገሠሠ ደግሞ የብሄራዊ ቴአትር ስራ አስኪያጅ ሆነ፡፡ካሳዬ ደግሞ
ወደ ትምህርት መገናኛ ከሄደ በኋላ ኬንያ ዋና መስርያ ቤቱን ወደአደረገው አለም አቀፉ የስርጭት
አገልግሎት URTNA ያመራው፡፡22
ሁለተኛው የብሄራዊ ትያትር ቆይታው እስከ 1976 ዓ.ም ለስምንት አመታት የዘለቀ ሲሆን
ለተስፋዬ አስደሳች አልነበረም፡፡ግፊት የበዛበት ወቅት ነበር፡፡“ለጥበብ ለመቆም የጥበብን ዋጋ ፊት
ለፊት ለማስገንዘብ” አዳጋች የነበረበት ፤ምንም እንኳን ከፖለቲከኞቹ ጋር መወዳደር ቢከብድም23
በአንጻሩ በሌላ በኩል ደግሞ ታላቅ ወቅትም ነበር፡፡እራሱ የተወነበትን የመንግስቱ ለማን "ጸረ-
ኮሎንያሊስት" ለመድረክ አበቃ፡፡ cherchez la femme የተሰኘ ተውኔቱንም ጽፎ በ1972
ዓ.ም ቢጨርስም በብሔራዊ ቴአትር ሳይታይ በሃገር ፍቅርና ራስ ቴአትር ለመድረክ በቃ፡፡የተውኔቱ
ርእስ ምጸታዊ ሲሆን ዋናው አላማው በወቅቱ የነበሩትን ነጭና ቀይ ሽብር ለመንካት ነበር፡፡24
በአለቆቹ ግን አልታወቀም፡፡ተውኔቱ ለዚህ ሁሉ ሽብርና ተያያዥ ክፋቶች ማን ሃላፊነቱን
እንደሚወስድ ይጠይቃል፡፡ ድርጊቱ የሴተኛ አዳሪነት ንግድ በሚካሄድበትና መጠጥ
በሚሸጥበትበሴቶች ቡና ቤት ውስጥ የሚፈጸም ሲሆን (ይህ ደግሞ በቁምነገር እንዳይወሰድ
አድርጎታል) በምሽት አንድ የታክሲ ነጂ ከቤቱ ተወስዶ እንደ ሽብሩ አካል ይገደላል፡፡ይህ ሰውዬ
352
ጥቋቁር አናብስት
በተመሳሳይ አመት 1972 ዓ.ም "ተሃድሶ" የተሰኘውን ባለ ሁለት ገቢር ተውኔት ለአምስተኛ
የአብዮቱ ክብረ በአል ጻፈ፡፡ይህ ፖለቲካዊ ተውኔት ሲሆን ተስፋዬ በወቅቱ “ከመንግስት ጋር አብሮ
ነበር ”ምንም እንኳን በግለኝነት እራሱን ከምንም በአብዮቱ መነሾ ከነበሩ ፓርቲዎች ጋር
ባያቆራኝም ተስፋዬ ለወደፊቱ ተስፋን የሰነቀበት ጊዜ ነበር፡፡ዋነኛ የተውኔቱ ገጸ ባህርይ የደርግ
አባል የሆነ ሰው ሲሆን የመጀመርያው ገቢር (ብሬችቲያን ከአንዱ ቦታ ወደ ሌላው ሲዘዋወር
ያሳያል) ሁለተኛው የህዝቡን ሸንጎ ያሳያል፡፡ህዝቡ የተያዙ ካሃዲዎችን ዝርዝር ያሳያል፡፡የአብዮቱ
መነሾ በፍቅር ግለት የተሞላና በዲሞክራሲ ስም የተፈጸመ ነበር፡፡ነገር ግን ከመሃል አንድ ሰው
ተነስቶ በስመ ዴሞክራሲ ፓርቲ ልመስርት ቢል እስር ቤት ይወረወራል፡፡ይሄ ደግሞ በአብዮቱ
እንደሚፈጸሙ ቃል የተገቡ ነገሮች ላይ ጥርጣሬን ያጭራል፡፡ተስፋዬ ተውኔቱ በቅርጽ ደካማ
ቢሆንም የድራማ ተጽእኖዎችን ተጠቅሟል ይላል፡፡ለምሳሌ ተፈጽመው የሚያውቁና
ላለመደገማቸው ምንም ዋስትና የሌላቸው የሆኑ ድርጊቶችን በማስመሰል ተዋንያኑ ከህዝቡ መሃል
ገብተው መሳርያ በመደገን እጅ ወደ ላይ! ብለው ህዝቡን የሚያስደነግጡበት ትእይንቶች የመሳሰሉ
ሲሆን ከእውነታዊ ተውኔት ጋር ተቀራርቦ ነበር፡፡
በዚህ የብሔራዊ ትአትር ቆይታው ትአትርን ወደ ህዝቡ ማድረስ የሚወደው ተስፋዬ ቴአትር
ቤቶችን በክፍለሃገራት ለመጀመር ቅርንጫፍ ለመክፈት አስቦ በ1971 ዓ.ም የላሊበላ ትአትር
ቡድንን በወሎ ቴአትር አዳራሽ ከደሴ ማዘጋጃ ቤት ጋር በመተባበር መሰረተ፡፡26 ተውኔቶቻቸውን
ሲያቀርቡ ሲዘፍኑና ሲወዛወዙ እንደ ሃገር ፍቅር ቴአትር ነበር፡፡ነገር ግን ይህ የማስፋፋት ሃሳብ
ከባህል ሚንስትር ችግር ይዞ መጣ ፡፡ በወቅቱ ሚንስትሩ በአሉ ግርማ ነበር፡፡ ቢሆንም ተስፋዬ
በሃሳቡ ገፍቶበት በባህር ዳርና በጎንደር ተመሳሳይ ቡድኖችን አቋቋመ፡፡ጅማም ሄዶ ተመሳሳይ ስራ
ሊጀምር በነበረበት ወቅት ነበር ካራቸውን የሻጡበት፡፡ከቁጥጥር ውጪ እየወጣ ነው በሚል ስሜት
አርፎ እንዲቀመጥ በማሰብ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን አማካሪ እንዲሆን አደረጉት፡፡እንደዚህ ዐይነት
ስራዎች ለብርሃኑ ዘርይሁንና ለጸጋዬ ገብረ መድህንም የተሰጡ ማግለያዎች ነበሩ፡፡
353
ጥቋቁር አናብስት
ተስፋዬ እንዲህ ባለ ሁናቴ በኢትዮጵያ ትያትር ተጽእኖ ፈጣሪ ከነበረበት ስልጣን ዳግም ተወገደ፡፡
ነገር ግን በርካታ ባለሙያዎችን በዩንቨርሲቲ ባህል ማእከልም ሆነ በብሄራዊ ቴአትር አሰልጥኖ
የሱን አላማ አንግበው ተልእኮውን እስከዳር የሚያደርሱ ሰዎችን አፍርቷል፡፡በግሉ ለኢትዮጵያ
ቴአትር የበኩሉን ማበርከቱን ከዚህ በኋላም እራሱን ችሎ እንደሚቀጥልም ያምናል፡፡
ከብሄራዊ ቴአትር በለቀቀበት ተመሳሳይ አመት 1976 አንድ "ፍርዱን ለእናንተ" የምትል ተውኔት
ጽፏል፡፡night of January 19th በተሰኘ የአንዲት አሜሪካዊት ሴት ድርሰት ላይ የተመረኮዘ
ነው፡፡ወጥ ስራውን በቅርበት ተከታትሎ እንደውም አንዳንድ ክፍሎች ቃል በቃል መልሶ ያቀረበው
ቢሆንም ነገር ግን አጨራረሱን ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል፡፡የተስፋዬ ተውኔት የሚያጠነጥነው
በአንድ የሞተ ኢትዮጵያዊ ላይ ሲሆን ሌላ የሞተ ገጸ ባህርይም ከመካከለኛው ምስራቅ ያመጣል፡፡
ተስፋዬ ተውኔቱ በጥሩ ሁናቴ እንደተዋቀረ ያስባል፡፡በተውኔቱ መሃል ሰዎች በሚፈጠሩት ክስተቶች
ላይ ፍርድ እንዲሰጡ ይጠየቁ ነበር፡፡ያ ነበር የተውኔቱ ርእስ መነሾ፡፡27 ተስፋዬን ብዙዎች ስለ
ፈጠራው አሞገሱት፡፡ ለመጀመርያ ደራሲዋ እውቅናን አልሰጠሁም ስሟንም አላነሳሁም ይላል
በአሁን(በንግግራችን ወቅት)ስሟንም ረስቶታል፡፡
መጀመርያ በብሄራዊ ቴአትር ታይቶ ከወር በኋላ እንዲቆም ተደረገ፡፡ተስፋዬ ለባለስልጣኖች አቤት
ካለ በኋላ በብሄራዊ ቴአትር መታየት ቢጀምርም ተመልሶ በባህል ሚንስትር ትእዛዝ ከሶስት
ትርኢት ቆይታ በኋላ እንዲታገድ ሆነ፡፡ ሳንሱሩ ቢያሳልፈውም ደርጎቹ በእነሱ ላይ እንደተሰነዘረ
ሽሙጥ ቆጠሩት፡፡በ1979 ዓ. ም አንድ ጊዜ በድጋሚ በባህል ማዕከል ለመታየት ግን ችሏል፡፡
***
ተስፋዬ ይህን ግዜ በድጋሚ ብሄራዊ ቴአትር ስባረር ሚስቴ የህይወታችን አለመቀየርና ድግግሞሽ
አታክቷት ከቤት አባረረችኝ ሲል ታሪኩን ያስታውሳል፡፡28ይህ የሆነው በ1976 ዓ.ም ነበር፡፡
በ1977 ተለያይተው በ1979 ፍቺ ፈጸሙ፡፡በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ነበር ከተስፋዬ ጋር ልገናኝ
የቻልኩት፡፡ አንድ ነገር እየረበሸው እንደሆነም ግልጽ ነበር፡፡ከቤተሰቡ ችግር ውጪ እሱና ባለቤቱ
ለከፈቷት የሃገር ባህል ምግብ ቤትም ሃላፊነት ነበረበት፡፡ነገር ግን በፍቺያቸው ወቅት ይህን ምግብ
ቤት እንድትወስደው በፍቺ ስምምነቱ ለሚስቱ ተፈረደላት፡፡በተመሳሳይ ወቅትም በቦሌ መንገድ
ለሚገኘው ቤቱ ወጪ ለመሸፈን መቻሉ እያጠራጠረው ነበር፡፡በአማካሪነትም የሚሰራው ስራ
(እሱም አለቃውም እንደነገሩኝ)ከምንም የማይሻል ሲሆን፡እንደ እድል ሆኖለት በ1979 ዓ.ም
በባህል ማእከል ዳይሬክተርነት አዲስ ስራ አገኘ፡፡አዲስ ሚስትም አገባ፡፡ቤቱንም ይዞ መቀጠል
የሚችል ይመስል ነበር፡፡እኔ እስከማውቀው ጊዜ ድረስ ቢጠጣም ከመጠጡ ቀንሷል፡፡“እንዴት
354
ጥቋቁር አናብስት
መጠጥ ማቆም እችላለሁ? አዲሷን ሚስቴን ጤነኛ ብሆን ኖሮኮ አግቢኝ ብዬ ደፍሬ ባልጠየቅኋት
ነበር!”ቢሆንም ከጊዜ ወደ ጊዜ ሃኪሙ መጠጥ ቢቻል ለ 6 ወራት እንዲያቆም ካልሆነ እንደሚሞት
ነግሮታል፡፡ አሁን ውሃ ብቻ ነው የሚጠጣው፡፡
ምን አልባት ቦዝኖ ከመዋል በችግሩ ወቅትም ቢሆን መጻፉን ቢቀጥልም ወይም ችግር የሚያነሳሳው
እንደሆነ ቢገምትም በ1979 "መንገደኞች" የተባለውን ኮመድያ ጻፈ፡፡“በጥሩ ሁኔታ የተዋቀረው
ድርሰቴ” ሲል ይናገርለታል፡፡በገብርኤል ንግስ ወደ ሐረር ቁልቢ ገብርኤል ልጅ ለማግኘት ለበረከት
ለመልካም እድል ለጥምቀት ወዘተ ስለሚሄዱ ሰዎች ነው የተጻፈው፡፡ የክርስትያኖች ቤተ
ክርስትያን ቢሆንም ሙስሊሞችም በገብርኤል “ስለሚያምኑ” ይሄዳሉ፡፡ዋናው የተውኔቱ ገጸ
ባህርይም አንድ ሙስሊም ሽማግሌና ያስኮበለላት ሴት እንዲሁም ስለነሱ በቀድሞ ውሽማዋ በኩል
ስለሰማች “እውነተኛ ሚስቱ” ነው፡፡ኮመዲው የሚመነጨው ከተከታታይ ትንቅንቆቹ ነው፡፡
በምንነጋገርበት ወቅትም ለመድረክ አልበቃም፡፡
ከጥቂት አመታት በኋላ "ሰኔና ሰኞ" የተሰኘ ተውኔት ደረሰ፡፡በሰኔና ሰኞ ግጥምጥሞሽ መጥፎ ገድ
ላይ የተመሰረተ ነው፡፡አስደሳች ነው የሚለው ታሪክ መቼቱ ከአብዮቱ በፊት በነበረችው አስመራ
ውስጥ ሰኔ 1 ቀን ነው፡፡አንድ ሰው ከኢትዮጵያ ለመገንጠል ከሚዋጉት ነጻ አውጪዎች 10000
ብር የሚጠይቅ ደብዳቤ ይደርሰዋል፡፡ ይህ ካልሆነም እንደሚገድሉት ይነግሩታል፡፡ወደ ፖሊስ
ጣብያ ደብዳቤውን ይዞ ሄዶ ለመኮንኑ እያሳየው ሳለ ሌላ ተመሳሳይ ደብዳቤ የደረሰው ሰው መጣ፡
፡በተውኔቱ የተሳለው መጥፎ ገድ ታድያ ይሄ ከመክፈል ውጪ አማራጭ የሌለው ችግር ነው፡፡
ለተገንጣዮቹ ገንዘቡ ተሰጣቸው፡፡ገጸባኅርያቱ ኤርትራዊ ሲሆኑ በባህል ማእከል ለመድረክ በቅቷል፡
፡
355
ጥቋቁር አናብስት
***
ተስፋዬን ከዚህ ቆይታችን በኋላ በተደጋጋሚ አግኝቼዋለሁ፡፡ ከሌሎች ሃላፊነቶቹ በተጨማሪ በኤ.አ
1988 በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የድራማ ክፍሉ የበላይ እንደተደረገ ነግሮኛል፡፡ ኢትዮጵያን በ
1989 እ.ኤ.አ ከመልቀቄ በፊት አንዴ ለአጭር ቆይታ ተገናኝተን በእንግሊዘኛ የጻፈው ረቂቅ
እንዳለውና አንብቤ አስተያየት እንድሰጠው ጠይቆኝ የነበር ቢሆንምበኢትዮጵያ የምሰራውን ስራ
ለመቋጨት በጥድፊያ ላይ ስለነበርኩ ልቀበለው አልቻልኩም ፡፡ለእነዚህ ገጾች መጻፍ መክንያት
ከሆኑ ንግግሮቻችን በኋላ የመጻፍ ጉጉት እንዳደረበት ነግሮኛል፡፡አንድ ሰው በሱ ስራዎች ከተደሰተ
በተሻለ ለመጻፍ ግዴታ ውስጥ እንደሚገባና በፊት ከሰራው ሳይቀር በተሻለ ለመስራት ጊዜውንና
ተሰጥኦውን መጠቀም እንዳለበት አጫወተኝ ፡፡ከሁለተኛው የኢትዮጵያ ጉብኝቴ እ.ኤ.አ 1989
በኋላ ዳግመኛ ላገኘው ባልችልም ለኢትዮጵያ ቴአትር አንድ ጉልህ መዳረሻ ማስቀመጡን
አምናለሁ፡፡
የደራሲው ማስታወሻ
በቅርቡ የኦማር ኻያምን ሩባያቶች ተርጉሞ ማሳተሙ ተነግሮኛል፡፡
የተርጓሚው ማስታወሻ
ተስፋዬ ገሠሠ ከዚህ ጽሁፍ ጥንቅር በኋላ የተለያዩ ስራዎችን አሳትሞ ለገበያ አቅርቧል፡፡
ማስታወሻ
356
ጥቋቁር አናብስት
2)ቆለጭ በጎንደር አካባቢ የታወቀ ስም ሲሆን በጣና ሃይቅ ካለ ብርማ አንጸባራቂ መልክ ያለው
አሳ መጠርያ ነው፡፡ከሌላው መጠርያ ስም ቁልጭልጭ ጋር ተመሳሳይነት አመጣጥ ሊኖረው
ይችላል፡፡
ደጃዝማች ግርማሜ የየ53ቱ መፈንቅለ መንግስት ርእዮተ አለማዊ መሪ ግርማሜ ንዋይም አያት
ናቸው፡፡
5)ተስፋዬ በዚያን ወቅት ´ግራጫ´ በሚል ግራጫ ቀለም ባላቸው የአህያና የበቅሎ ለመጠርያ
በሚያገለግል ስም እንደሚጠራ ያስታውሳል፡፡ይህ ስምም ለክልሶች እንደ ቅጽል በመሆን ያገለግል
ነበር፡፡
9)ቆይቶ በተመሳሳይ ቴአትር ቤት በስራ አስኪያጅነት በተሾመው ሰይፉ እነሱ የቀረበለት ሲሆን
በወቅቱ በዳይሬክተርነት መአረግ ያለ ሰው እንዳልነበረ ተስፋዬ ይናገራል፡፡
11)ከአብዮቱ በኋላ ምንም ያህል መጥፎ ጊዜም ቢመጣ ወደ ኋላ የሚነገርም ቢሆን ወታደራዊው
መንግስት ገና ስልጣን ላይ ሳለ ነበር ተስፋዬ በድፍረት ያጫወተኝ፡፡
358
ጥቋቁር አናብስት
12)ኋላ ከኢምፔሪያሊዝም ውድቀት በኋላ ማድረግ እንደ ጀመሩት ሳይሆን ባለስልጣኖቹ በዛን
ወቅት መግደል አይፈልጉም ነበር፡፡
14)ተስፋዬ የባህል ማእከሉን ከለቀቀ በርካታ አመታት በኋላ አንድ አሜሪካዊ ኦርኬስትራ
ኢትዮጵያን ተቀላቀለ፡፡ቻርለስ ሳተን የተባለው ይህ አሜሪካዊ ባህላዊውን የሙዚቃ መሳርያ
መሰንቆን በዝቅተኛ ደረጃ ከሚጫወቱ ሰዎች ተምሮ የመጣ ሲሆን ከዛ በኋላ በኦርኬስትራው
ዝግጅቶች ላይ መሳተፍ ጀመረ፡፡ከውጪ ዜጎች ጥቂቶቹ ናቸው የኢትዮጵያን ሙዚቃ ለምደው
ለመጫወት የሚበቁት፡፡
21)በቃለመጠይቃችን ወቅት በሳምንት ሶስት ጊዜ ይታይ የነበረ ሲሆን ሁሉም የሚታዩት ከሰአት
በኋላ ነበር፡፡በኢትዮጵያ የምሽት መርሐግብራት ብዙም አልተለመዱም፡፡
359
ጥቋቁር አናብስት
22)ትምህርት በሬድዮ ቢቆይ ኖሮ ተስፋዬ የተሻለ ክፍያ ያለውን በዝና ከፍም ያለውን የURTNA
ስራ እንደሚያገኝ አይገምትም፡፡ እዛው በነበረበት ስራ ላይም ይቆይ ነበር፡፡
27)ወጡ የአሜሪካው ስራ ሸንጎ የነበረው ሲሆን በኢትዮጵያ ግን ፍርድ ሸንጎ ስለሌለ ዳኞቹን
መጠቀም ግድ ሆኖበታል፡፡
360
ጥቋቁር አናብስት
ሳህለሥላሴ ብርሃነማርያም
በሶስት ቋንቋ የሚጽፉ ሁለገብ ደራሲሳህለሥላሴ ብርሃነማርያም
የተወለዱት በቀድሞው ሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ ጨቦ እና ጉራጌ ወረዳ፣
ሲስ በተባለች መንደርነው።ትውልዳቸው ከሰባት ቤት ጉራጌ ውስጥ
አንዱ በሆነው ቸሃ ነው።የሚኖሩት ከአርሶአደር እና አርብቶአደር
አባታቸው፣ ከቤት እመቤት እናታቸው እንዲሁም ከወንድምና
እህቶቻቸው ጋር ነበር። በጉራጌ ባህል "ሴቶች ብዙም ቦታ
አይሰጣቸውም"፤ስለዚህ ገና የአስረኛ ክፍል ተማሪ ሳሉ አባታቸው ሲሞቱ፣ ምንም እንኳን
እናታቸው ያኔም ሆነ አሁን ይህንን ቃለመጠይቅ ባደረግንበት 1977 ዓ.ም በሕይወት የነበሩ
ቢሆንም፣ታላላቅ እህቶች ቢኖራቸውም፣የቤተሰብ ሃላፊነቱን ተቀብለው እርሻውንና ቤተሰቡን
የማስተዳደር ኃላፊነቱን ተረክበዋል።ይህ አዲስ ሃላፊነት ሳህለሥላሴ ትምህርታቸውን አቋርጠው
ጊዜያቸውን ሁሉ ቤተሰቡንና እርሻውን መንከባከብ ላይ እንዲያውሉ አስገደዳቸው።ነገር ግን
የአባታቸው ጓደኛ የነበሩት በሳቸውም ሕይወት ውስጥ ሚና የነበራቸው አባ ፍራንሷ ማርቆስ
የተባሉ የካቶሊክ ቄስ፣ ትምህርታቸውን እንዳያቋርጡ እና ቤተሰቡንና እርሻውን በትርፍ ሰአታቸው
እንዲንከባከባቸው አሳመኗቸው።ትምህርት ቤት በሚሆኑባቸው ወቅት አጎታቸው ተክተው በስራ
እያገዟቸውት፣ ምክራቸውን ተቀብለው ተግባራዊ አደረጉ።
361
ጥቋቁር አናብስት
ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት እያሉ ሳህለሥላሴ በክርክር ክበብ ውስጥ ሆነውየንግግር ጥበብ
ይማርካቸው ነበር፡፡ምንም እንኳን "አንደበተ ርቱእ" ባይሆኑም አድማጮቻቸውን በንግግራቸው
ይዘው ለመንጎድ ያኔም ሆነ በኋላ ይመኙ ነበር―ያ ምኞት ግን አሁን ሞቷል።በሕይወታቸው
ለመጀመሪያ የፃፉት መጣጥፍ ለትምህርት ቤታቸው መጽሔት ሲሆን ስለ ምኞት መሆኑን
ከማስታወሳቸው በስተቀር ዝርዝሩን ረስተውታል።2
ከዚያ በኋላ ዘመድ ቤት ለአንድ ዓመት ኖሩ።ነገር ግን መጀመሪያ ሊያገኟቸው ስላዳገታቸው ተፈሪ
መኮንንን ለቀው የሐረር መምህራን ማሰልጠኛን ለመቀላቀል አስበው ነበር።ነገር ግን ሳህለሥላሴ
ከትምህርት ቤቱ ምርጥ አምስት ተማሪዎች አንዱ በመሆናቸው የትምህርት ቤቱ ርእሰ መምህር
በተፈሪ መኮንን እንዲቆዩ ፈለጉ፤ከብዙ ጥረት በኋላ ሳህለሥላሴ ዘመዶቻቸውን ማግኘት ቻሉ።
ሳህለሥላሴ በላዛሪስት ሚስዮን ቆይታቸው ለበዛ የካቶሊክ ቀኖና ቢጋለጡም ከልባቸው ሊቀበሉት
ግን አልቻሉም።በጣም ጥብቅ እና ከሰብአዊ ባህሪ የራቀ ሆኖ ይሰማቸው ነበር።ሕይወት እና
ቀኖናው የሚጣጣሙ አልሆኑም።ስለዚህ አመፁ፤ይሁን እንጂ ስለቄሶቹ ብዙ ጥሩ ትዝታዎች
አሏቸው።በሚስዮኑ ለነበሩት ተማሪዎች እንደ ወላጅ አባቶች ነበሩ።በቆይታቸው መጨረሻ ከነበሩት
አለመስማማቶች መሐል ሀጢያትን በተለይ ደግሞ የፆታ ግንኙነትን በተመለከተ ያላቸው ሕግጋት
ነበሩ።ቤተክርስቲያን መሄዳቸውን ባያቋርጡም በውስጣቸው ግን አመፁ።ቀኖናቸው የሰውን
ምክንያታዊነት ይቃረናል።በቃለ መጠይቃችን ወቅት ቤተክርስቲያን መሄዳቸውን አቁመዋል፤
እንደውም ረዥም ጊዜ ሆኗቸዋል።ይሁን እንጂ ኢአማኒ አይደለሁም― “ነፃ አሳቢ” እንጂ ይላሉ።
ሳህለሥላሴ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው ዩኒቨርስቲ
ኮሌጅ ገቡ።ይህ እንግዲህ የቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የአሁኑ አዲስአበባ
ዩኒቨርስቲ ከመቋቋሙ በፊት ነበር። በዩኒቨርስቲ ኮሌጁ ለአራት ዓመት ማለትም ከመስከረም
1948 እስከ ሐምሌ 1951 ዓ.ም ድረስ ቆይተው በሥነ ጥበብ ፋካልቲ ውስጥዲግሪያቸውን
362
ጥቋቁር አናብስት
363
ጥቋቁር አናብስት
ከኮሌጅ ጊዜያቸው "የግል" ትዝታዎቻቸው መሐል የክርክር ክበብ አባል መሆናቸው፣ የቅርጫት
ኳስ መጫወታቸው(በረዥም ቁመታቸው ምክንያት እና ምንም እንኳን "ሶፍትቦል" መጫወት
የበለጠ ቢወዱም፤የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እያሉ እግር ኳስ መጫወታቸው ይገኝበታል)።
ከልጅነታቸው ጀምሮ ዋና በጣም ይወዱ ነበር።ኮሌጅ እያሉ በጣም ይመገባሉ፤ጓደኞቻቸው
ከሚበሉት እጥፍ ያሻምዱ ነበር። ዳንስም ይወዳሉ“በዳንስ አብጃለሁ ―ነፃነትን ይሰጠኝ ነበር
መሰለኝ”ይላሉ።ደግሞም ከጓደኞቻቸው ጋር "ሁሉንም ዐይነት መጥፎ የሚባሉ ድርጊቶች"
ይፈጽሙ ነበር፤ምሳሌ በአዲስ አበባ ዝነኛው የቀይ መብራት ሰፈር፣ውቤ በረሀ ወርደው ሴተኛ
አዳሪዎችንመጎብኘት የመሳሰሉት፤ከነዚህ ሴተኛ አዳሪዎች ጋር ጥሩ ትዝታዎች አሏቸው ምክንያቱም
መልካም ሰዎች ነበሩ፤ደግሞም “በጣም ይወዱን ብሎም ያፈቅሩን ነበር” ብለዋል፤ታዲያ ይህ
አመለካከታቸው ከአውሮፓ እና አሜሪካ ሴተኛ አዳሪዎች ጋር ኋላ ከነበራቸው ልምድ ጋር
ተጣርሶባቸዋል። ደግሞ በሌላ ጊዜ ለተማሪዎች ህብረት ፀሐፊነት ቢወዳደሩም፣ኋላ ላይ በካናዳ
ፕሮፌሰር በሆኑትና "አክራሪ" የፖለቲካ አመለካከት በነበራቸው ሐጎስ ገብረእየሱስ ተሸንፈዋል።
ሳህለሥላሴ አላገቡም፤ነገር ግን ፍቅር ይዟቸው ያውቃል። ኮሌጅ እያሉ ገና ስምንተኛ ክፍል
በነበረች ልጅ ፍቅር ከንፈው ነበር።ገና እንዳይዋትት ነበር የወደዷት፤ጠንካራ ዱካ ጥሎ ያለፈ
364
ጥቋቁር አናብስት
***
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ዲግሪያቸውን ከተቀበሉ ከሁለት ወር በኋላ ወደ ፈረንሳይ አቀኑ።
ማጥናት የፈለጉት የፖለቲካ ሳይንስን ቢሆንም ይሄ ምርጫ የኢትዮጵያን መንግስት የሚያስደስት
አልነበረም፤ስለዚህ ኮሌጅ አብረዋቸው የነበሩት አብዛኛዎቹ ጓደኞቻቸው በውጪ ሀገራት ነፃ
የትምህርት እድል ሲያገኙ እሳቸው ምንም ሳያገኙ ቀሩ። ምክትል የትምህርት ሚኒስትር የነበሩት
እንዳልካቸው መኮንን (የደራሲውና ፖለቲከኛው ራስ ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው ልጅ)
በሣህለሥላሴ ምርጫ ተሳለቁ። "ከዚህ ሁሉ ለፓርላማ ለምን አትወዳደርም?" ብለው
ስላላገጡባቸው ሳህለሥላሴ በፖለቲካ ሳይንስ ምንም ነፃ የትምህርት እድል ሳያገኙ ቀሩ። ይሁን
እንጂ ከዚያ በኋላ አንድ ፈረንሳያዊ መምህር አዲስ አበባ በሚገኘው የፈረንሳይ ኢምባሲ
ተሯርጠው በፈረንሳይ ህግ ማጥናት የሚያስችላቸውን ነፃ የትምህርት እድል አገኙላቸው።ስለዚህ
በመስከረም 1952 ዓ.ም እርሳቸው እና ሌሎች ጥቂት ተማሪዎች እድሉን በመጠቀም ወደ ፈረንሳይ
አቀኑ። በዚህ ወቅት በሳህለሥላሴ ሕይወት አንድ ለውጥ ተከሰተ።እንዳልካቸው መኮንን
ጥያቄያቸውን አጣጥለው ስለሳቁባቸው የመኳንንትን ዘር አምርረው ጠሉ፤የገዢው መደብ አባል
ቢሆኑ ኖሮ እንደዚያ እንደማይሳቅባቸው እርግጠኛ ነበሩ።
ሳህለሥላሴ በዚህ ወቅት ዝንባሌያቸው ስራ መስራትና ያሻቸውን ማንበብ እንጂ የክፍል ፈተናዎችን
ማለፍ አልነበረም፦ የዩኒቨርስቲ የመማሪያ መጽሐፍትን አሁን ድረስ ይጠላሉ። ይህ የማንበብ
ፍላጎት ሳይቀንስ ባይቀርም አሁን በቃለ መጠይቃችን ወቅትራሱ በሰፊው ያነባሉ፤ አሁን በእድሜ
እንደመግፋታቸው፣የበሰሉ፣ዘመን ተሻጋሪ መጽሐፍትን ይመርጣሉ―ደግሞ ተወዳጅ ዘመናዊ
መጽሐፍትን(አጥረው የሚዘጋጁትን ማንበብ ትተዋል)፣እናም "ሁሉንም አቀፍ" መጽሐፍትን፣
ማለትም ሀሳብ፣ ፍልስፍና፣ የራሳቸው ሥነ ጽሑፋዊ ዘዬ እና የአጻጻፍ ተውህቦ ባንድነት ያሏቸው
መጽሐፍት ምርጫዎቻቸው ናቸው። አሁን የመጀመሪያ ምርጫቸው ረዥም ልብወለድ ቢሆንም
366
ጥቋቁር አናብስት
ሳህለሥላሴ ወደ ፈረንሳይ የሄዱት በዚያው ወደ አሜሪካ የመሻገር ምኞት ስለነበራቸው ነው። በዚህ
ወቅት ዝነኛው የኢትዮጵያ ቋንቋ አጥኚ ዎልፍ ሌስላው ረዷቸው።ሳህለሥላሴ ሌስላውን
የሚያውቋቸው ገና እምድብር እያሉ እሳቸው እና የክፍል ጓደኞቻቸው እያንዳንዳቸው
አስርየጉራግኛ ቋንቋ ምሳሌያዊ አነጋገሮችንእንዲሰበስቡ በጠየቋቸው ጊዜ ነው―ለዚህ ጥረታቸው
ልጆቹ የየራሳቸውን ፎቶግራፍ ተሸልመዋል።በኋላም ሌስላው ሳህለሥላሴን በዩኒቨርስቲ ኮሌጅ
ሲያገኟቸው ስለ ጉራግኛ ቋንቋ "ያልጠየቋቸው ጥያቄ" አልነበረም። በኋላ እዚያው በአዲስአበባ
ኮሌጅ ውስጥ እያሉ ሳህለሥላሴ ለሌስላው በፖለቲካ ሳይንስ የነፃ ትምህርት እድል ያገኙ ዘንድ
እንዲረዷቸው ሲጽፉላቸው፣ ሌስላው ይህ በስድስት ወር ሊሳካ ይችላል ብለው
መለሱላቸው―ይህንን በልባቸው ይዘው ወደ ፈረንሳይ ተሻገሩ።ፈረንሳይ እያሉ በደብዳቤ
መገናኘታቸውን ቀጥለው፣ በመጨረሻ በቆይታቸው ማብቂያ ሌስላው ነፃ የትምህርት እድሉን
እንዳገኙላቸው ነገሯቸው። ከዚያም ፓሪስ ወደሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በመሄድ
ፓስፖርታቸው የአሜሪካ ቪዛ ለማስመታት እንዲቻል ተደርጎ እንዲስተካከል ቢጠይቁ አምባሳደሩ
አካለወርቅ ሀብተወልድ ወደ ውጪ የመጣኸው ህግ እንጂ ፖለቲካ ሳይንስ ለማጥናት አይደለም
በማለት ከለከሏቸው።ይህ የሆነው ከ1953ቱ ያልተሳካው መፈንቅለ መንግስት ሙከራ በፊት
ነበር። በዚህ ሙከራ ወቅት፣የአምባሳደሩ ወንድም መኮንን ሀብተወልድ በመሞታቸው፣ አምባሳደሩ
ለቀብር ወደ አዲስአበባ ሄዱ። ሳህለሥላሴ ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም፣ ዳግመኛ ወደ ፓሪስ
አቅንተው (ይህንን ጉዞ ለማድረግ ገንዘብ መበደር ጭምር አስፈልጓቸው ነበር)ሁለተኛ ጸሐፊውን
ቢያገኙት በትህትና ከማስተናገዱም በላይ ወደ አንደኛ ፀሐፊው ሄዶ ፓስፖርቱ ተስተካከለላቸው፡፡
―ነገር ግን ከአምባሳደሩ ፍቃድ ውጪ በመሆኑ በሚስጥር እንዲይዙት ተነገራቸው። ሳህለሥላሴ
367
ጥቋቁር አናብስት
***
368
ጥቋቁር አናብስት
369
ጥቋቁር አናብስት
በዚህ ወቅት ሳህለሥላሴ ሶስት መጽሐፍትን በሶስት ቋንቋዎች ጽፈዋል፦ "የሺነጋ መንደር" በአፍ
መፍቻቸው በጉራግኛ (ኋላ በእንግሊዝኛ ተተርጉሞ የታተመ)፣ "ወጣት ይፍረደው" በአማርኛ
እንዲሁም "አፈርሳታ" በእንግሊዝኛ። እነዚህን ሶስት መጽሀፍት "እንደሙከራ" ይቆጥሯቸዋል።
ከዚህ ሁሉ በኋላም እንደ ደራሲእንዴት መቀጠል እንዳለባቸው አያውቁም። "የመጻፍ ዝንባሌ"
በውስጣቸው እንዳለ በደመነፍስ ቢያውቁም በአፃፃፍ ዘዴና ቋንቋ ገና ሙከራ እያደረጉ ነበር።
ከመጀመሪያ መጽሐፋቸው በኋላ በጉራግኛ ለመፃፍ አልሞከሩም ፤ ለዚህም በቂ ምክንያት አለኝ
ብለው ያስባሉ ፦አንደኛ አንባቢዎቹ በጣም ጥቂት ናቸው (ምንም እንኳን በመላ ሐገሪቱ ከ1.5
ሚሊዮን ጉራጌዎች በላይ ቢኖሩም)፣ ይሸጣል ብሎ ስለማይገምት የትኛውም አሳታሚ በጉራግኛ
ለማተም አይደፍርም፣ ከ1966 አብዮት በፊት አማርኛ ብቸኛው የመፃፊያ ቋንቋ ተደርጎ
ስለሚወሰድ ሳንሱር ክፍሎች የጉራግኛ መጽሀፍ ሐሳቡራሱ ሳያስቃቸው አይቀርም።በነዚህ
370
ጥቋቁር አናብስት
ችግራቸው ለመፃፊያ የሚሆን ርእስ ማግኘት ነው።መጽሐፍ ሲያነቡ አንድ ሐሳብ ካገኙ ማስታወሻ
ይይዛሉ። ከሚያዘወትሩበት መጠጥ ቤት ፊትለፊት መኪናቸው ውስጥ ብቻቸውን ቁጭ ብለው
ሲጠጡ ብዙ ጊዜ ሐሳብ ይመጣላቸዋል።9 በዚህ መንገድ ሁለት መጽሐፍት "በሃሳባቸው"
ጽፈዋል፤—የሁለት መጽሐፍት ሴራ፣ ቅርጽና አርእስት በዚህ በሚወዱት መጠጥ ቤት ፊት ለፊት
መኪናቸው ውስጥ ቁጭ ብለው ተከስተውላቸዋል።በሌላ በኩል፣ምንም እንኳን ባህላዊውን
የምርመራ መንገድ "አፈርሳታን" በተመለከተ በመጽሐፉ ከአንድ አንቀጽ በላይ ባይጠቀስም፣
ለ"አፈርሳታ" የሚሆነውን መነሻ ሀሳብ እና ርእስ ያገኙት በማህተመሥላሴ ወልደመስቀል በተፃፈው
"ዝክረ ነገር" ከተሰኘ ዝነኛ መጽሐፍ ነው።ሐሳቡ በአእምሮአቸው ስር ከሰደደ በኋላ በጉዳዩላይ ገፀ
ባህሪያቱንና ሴራውን ለማበልፀግ የሚያስችላቸውን ሰፊ ምርምር እና ጥናት አደረጉ።ያኔ ነው ቁጭ
ብለው ለልብወለዱ ቅርጽ ለመስጠትዝግጁ የሆኑት።
ቀጥለው የፃፉት መጽሀፍ Warrior Kingን ሲሆን ይህንን መፃፍ የጀመሩት The Afersataን
ከጨረሱ በግምት ከአንድ ዓመት በኋላ ነው።በመሀሉ አጫጭር መጣጥፎችንና የመጽሐፍት
ቅኝቶችን ጽፈዋል።“ምንም እንኳን በኋላ ወርውሬ ብጥለውም፣ ብቀዳድደውም፣ ሁሌም የሆነ ነገር
መፃፍ አለብኝ” ይላሉ። በዚህ መሰረት የሐዲስ አለማየሁ10 "ፍቅር እስከ መቃብር" ላይ ሰፋ ያለ
ቅኝት አደረጉ―ይህንን በማድረግም የመጀመሪያው ናቸው። ከዚያ በኋላ ደግሞ በአፈወርቅ
ገብረእየሱስ "ጦቢያ"11 ላይDialogue ለተሰኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ህትመት ሂስ አዘጋጁ።
ገና ወንጂ እያሉ ለአማርኛው እለታዊ ህትመት “አዲስ ዘመን” የፈጠራ ጽሑፍን በተመለከተ አንድ
መጣጥፍ ጽፈዋል።
372
ጥቋቁር አናብስት
ስላሉት ተጽእኖ አላሳደረብኝም ይላሉ። ስለዚህ "Warrior King"ን ሲጽፉ ከዚያ በፊት ማንም
ያልተጠቀመውን ሴማ በመምረጥ፣ ወጥ የሆነ ነገር እንደፈጠሩ ነው የሚሰማቸው።
Warrior King ቀደም ብለው እሳቸው ከፃፏቸው መጽሐፍት ሁሉ የላቀ እንደሆነ ይሰማቸዋል።
በሃያሲያን ዘንድም ከፍተኛ ተቀባይነት ከማግኘቱም በላይ "በአንድ ዩኒቨርስቲ የወሩ ምርጥ
መጽሐፍ ተብሎ ተመርጧል" የአጻጻፍ ዘዴዎችን የሚመለከቱ መጽሐፍትን ጎንለጎን ማንበባቸው
ተጨምሮ በዚህ መጽሐፍ እንደ ደራሲ መመንደጋቸው ቢሰማቸውም መጽሐፉ እንደ "The
Afersata" በደንብ አልተሸጠም።በእርግጥ በቃለ መጠይቃችን ወቅት አንዴ በድጋሚ ታትሞ
ነበር።ሁለተኛውን የቴዎድሮስ መጽሐፍ በተመለከተ ስለ አወዳደቃቸው "አጭርመጣጥፍ" ጽፈው
ነበር።ነገር ግን ይህ የኢትዮጵያ የታሪክ ወቅት ብዙ የተጠናና የተፃፈበት በመሆኑ፣ወጥ የሆነ ነገር
ማበርከት እንደማይል ተሰምቷቸዋል።በዚህ የተነሳ ለመፃፍ የታቀደው ሁለተኛ መጽሐፍ በጭራሽ
ላይሳካ ይችላል። "Warrior King"ን ከፃፉበኋላ በሳል ደራሲ እየሆኑ መምጣታቸው
ተሰምቷቸው ነበር፤በራስ መተማመናቸውም ጨምሯል።ነገር ግን ያኔም ሆነ አሁንበ1985
"ጥንቅቅያሉደራሲ" እንደሆኑ አይሰማቸውም።
መጽሐፉ የወጣው በ1966ቱ የኢትዮጵያ አብዮት ወቅት ነበር፤ይሄም በመጀመሪያ ከተፃፈ ከአንድ
ሁለት ዓመት በኋላ መሆኑ ነው―ይህ የሆነበት ምክንያት አሳታሚው ሔይንማን መጽሐፉን
በአፍሪካ ፀሐፊዎች ተከታታይ መጽሐፍት የሚካተቱት አንዳንድ ነገሮች ከተስተካከሉ በኋላ ነው
በማለታቸው ነበር።በዚህ መሰረት በከፊል በድጋሚ ከተፃፈ በኋላ ተቀባይነትን አግኝቷል።በ1971
ሳህለሥላሴ የሚሼል ኮትስ ኮርፖሬሽንን ለቀው ወጡ። "Warrior King" የተፃፈው በብሔራዊ
ሀብቶች ልማት ኩባንያ ውስጥ የአስተዳደር መኮንን ሆነው እስከ 1974 በሰሩበት ወቅት ሲሆን
በዛው ዓመት በአዲስአበባ የእንግሊዝ ኢምባሲ በአስተርጓሚነት ተቀጠሩ።እስከ 1988
ድረስምሰርተዋል ።ከ1966 ወዲህ ድርሰትን የሙሉ ጊዜ ሥራቸው አድርገው በዚሁ ለመተዳደር
ያልሙ ነበር።በኢትዮጵያ እስከቆየሁበት እ.ኤ.አ 1989 ድረስ ግን ይህ ህልም እውን አልሆነም።
ነገር ግን የእንግሊዝ ኢምባሲን ከተቀላቀሉ በኋላ ጊዜያቸውን ለፈጠራ በአግባቡ ከመጠቀማቸውም
በላይ "አራት እጥፍ ውጤታማ" ሆነዋል።በእንግሊዝ ኤምባሲ ውስጥ የነበራቸውን ስራ
ወደውታል፤ምክንያቱም ነፃነት ሰጥቷቸዋል፤በተጨማሪ የትርጉሙ ስራ―ከአማርኛ ወደ እንግሊዝኛ
እና በተገላቢጦሹ―ከመፃፍ ጋር የተያያዘ በመሆኑ የሚያስደስት ልምድ ሆኖላቸዋል።የመፃፍን
አካላዊም ሆነ የፈጠራ ገጽታውን እንደሚወዱት ይናገራሉ።እስከማውቃቸው ድረስ አላገቡም።
373
ጥቋቁር አናብስት
----
ቀጣዩ ስራቸው አጠር ብላ የተዘጋጀችው የቻርልስ ድክንስ A tale of two cities የሁለት
ከተሞች ወግ በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ መመለስ ነው፡፡በአጭሩ የተዘጋጀውን የመጽሐፉን ቅጽ
በትምህርት ቤት ቆይታቸው ያነበቡት ሲሆን ያላጠረውን ሙሉውን ክፍል የኋላኋላ በተደጋጋሚ
አንብበውታል፡፡ ዋናው ገጸባህርይም በአእምሮአቸው ተቀርጾ ቀርቷል፡፡ሃገራቸውም በተመሳሳይ
የአብዮት ጉዞ ላይ በመሆኗ በወቅቱ በአስተርጓሚነት ይሰሩት ከነበረው ስራ በላይ ይሄንን የሚስብ
ሆኖ አግኝተውታል፡፡ ነገር ግን ያለ ጥሩ አሳታሚም እንደማይሰሩት ወሰነው የነበር ቢሆንም
የኢትዮጵያ መጻሕፍት ድርጅት (ኋላ ወደ ኩራዝ በሄዱት አስፋው ዳምጤ በኩል)ዘላቂነት ያላቸው
የውጪ ስራዎችን የማሳተም ፍላጎቱ እንዳለ ስለተነገራቸው የትርጉም ስራውን መስራት ጀመሩ፡፡
375
ጥቋቁር አናብስት
የተዘጋጀውን አዲስ የአማርኛ መዝገበ ቃላትን ገዙ፡፡The tale of two cities መተርጎምም
ጀመሩ፡፡ ጥሩ ተቀባይነትንም አገኘ፡፡ በthe Ethiopian herald ላይም ጥሩ ዳሰሳ ተደረገለት፡፡
ድጋሚ በሌላ ሃገራዊ ዳሰሳ ቢቃኝም ያን ያህል ጥሩ የሚባል ግን አልነበረም፡፡አንድ ጓደኛቸው
ደውሎ በትርጉሙ እንደተደሰተና ጨምረው እንዲሰሩ አንደሚፈልግ ነገራቸው፡፡በኢትዮጵያ
የትርጉም ስራ ውስጥ በብዛት በማቅረብ የሚታወቁት ደራሲ የሚባሉት ማሞ ወድነህ ደውለው
እንኳን ደስ ያለህ አሏቸው፡፡ የኢትዮጵያ መጻሕፍት ድርጅት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ዳባ ከቢቢሲ
ጋር በነበራቸው ቆይታ ስለስራው መልካም ጎን እያነሱ አወደሱት፡፡ሌሎችም በበጎ አወሱት፡፡ሳንሱር
አድራጊዎቹም ያለ ምንም ማስተካከያስለተቀበሉላቸው ደስተኛ ሆነዋል፡፡
376
ጥቋቁር አናብስት
ሳህለሥላሴ የፈጠራ ጽሑፍ በሚያነቡ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ለውጥ ያመጣል ብለው ያምናሉ።
የለውጥ መሳሪያ ነው ብለው ያምናሉ። አብዮቱም የተቀሰቀሰው በኋላ "ሰለባ" በሆኑት ምሁራን
እንጂ ሌሎች እንደሚሉት በሌሎች ሀይለኞች እንዳልሆነም ያስባሉ። ያለ ምሁራን ተሳትፎ ለሀገሪቱ
"መጪው ጊዜ" ብሩህ ይሆናል ብለው አያስቡም ፤ ምክንያቱም "ማህበረሰቡ መሀል ንቃት ያላቸው
እነሱ ናቸው"። ስለዚህ የህዝቡን ባህል፣ሥነ ጽሑፍና አስተሳሰብ ለማበልፀግ የሚችሉትን
አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን መቀጠል ይፈልጋሉ።
የተርጓሚው ማስታወሻ
ደራሲና ተርጓሚ ሳህለሥላሴ ብርሀነማርያም ከዚህች መድብል ጥንቅር በኋላ እንደ ሹክታ፤
መከረኞች፤እምቢ ባዮች፡ዕጣ ፈንታ፡እምዩ(የተጠቀሰው)የእየሱስ ህይወት፡ፍኖተ ህይወት(ግለ
ታሪክ) መሳሰሉትን መጻሕፍት ያሳተሙ ሲሆን በስነጽሁፍ ዘርፍ የ1994 ዓ.ም የህይወት ዘመን
ሽልማትና፤ በወልቂጤ ዩንቨርሲቲ በስነ-ጽሑፍ ዘርፍ የክብር ዶክትሬት ተሸላሚም ሆነዋል፡፡
የግርጌ ማስታወሻዎች
377
ጥቋቁር አናብስት
2) ለዚህ መጣጥፍ የሚሆን ስዕል የሰራው ቴዎድሮስ ጽጌ ስራዎቹን በአዲስ አበባና በናይሮቢ
ማሳየት የቻለ አማተር ሰአሊ ለመሆን በቅቷል። የአዲስ አበባው ኤግዚቢሽን "የቀለም ቋንቋ"
ተብሎ መሰየሙ ተገቢ ነው ምክንያቱም የቀረቡት ስእሎች በቀለም የተንቆጠቆጡ ነበር ይላሉ
ሳህለሥላሴ። ሰአሊውን በትርፍ ጊዜያቸው ያሰለጠኑት ዝነኛው አርቲስት እስክንድር ቦጎሲያን
ናቸው።
378
ጥቋቁር አናብስት
10) ይህ መጽሐፍ ለረዥም ጊዜ ምናልባት እስከ አሁንም ድረስ በኢትዮጵያ በብዛት የተሸጠ
መጽሀፍ ነው።
12) በዚህ መሰረት በመጽሐፉ መቼት ውስጥ የተካተተው የአብዮቱ የመጀመሪያ ዓመት አማን
አንዶምና ስልሳዎቹ በህዳር 1967 ከመገደላቸው በፊት ያበቃል።
13) ብሔር ብሔረሰቦች በራሳቸው ቋንቋ መጻፍ አለባቸው የሚለው አቋም ኢትዮጵያ ውስጥ
በሚገባ ድጋፍ አላገኘም። ብሔራዊ ቋንቋ ሲባል የምንረዳው የጎሳዎች ቋንቋ ሳይሆን የመንግስት
ይፋዊ ቋንቋ መሆኑን ነው።
14)ያልተለቀቁት የ"ባሻ ቅጣው" ቅጂዎች መንግስት ከቆለፈበት መጋዘን ተሰርቀው ለገበያ ውለው፣
በመጋቢት 1978 መርካቶ ውስጥ ለእኔም እንድገዛቸው ቀርበውልኝ ነበር። በኋላ መጽሀፉ ብዙ
ማስተካከያ ተደርጎበት በሰኔ 1978 ከመለቀቁ በፊት አሳታሚውን የኢትዮጵያ መጽሐፍት
ማእከልን ብዙ ወጪ አስወጥቶታል። ይህንን የተከለሰ ቅጂ እኔም ለመግዛት ችያለሁ።
15) "ባሻ ቅጣው" ከታተመ በኋላ ሌሎቹንም መጽሐፍት ማውጣት ጀመረ ፤ በዚህ መሰረት
"እምዩ" በ1979 ታትሟል። የታተመውም ከሌሎች አሳታሚዎች ይልቅ የሳንሱር ሂደቱ ለዘብ
በሚለው የመንግስት ኣሳታሚ፣ ኩራዝ ዘንድ ነው።
379
ጥቋቁር አናብስት
ታደሰ ሊበን
የአማርኛ አጭር ልብወለድ ፋናወጊ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው
ምርጥ የአጭር ልብወለድ ጥበበኞች ውስጥ ታደሰ ሊበን
አንዱ ነው፤ነገር ግን ስራዎቹ ጥቂት ናቸው። እስካገኘሁት ጊዜ
ድረስ ያሳተማቸው መጽሐፍት ሁለት ቀጫጭን ቅፆችን ብቻ
ነው። እነዚህ ቅፆች ግን በአገር ውስጥም በውጪም ያሉ
አንባቢዎችን ( ከነዚህ መሀል መንግስቱ ለማ እና ላንፍራንኮ
ሪቺ ይገኙበታል) አድናቆት ለማግኘት በቂ ነበሩ። ላገኘው
ስሞክር የሚያውቁት ደራሲዎች ወይም ከመጻሕፍቱ ባሻገር ስለእሱ የሚያውቁ ሰዎች በጣም ጥቂት
ነበሩ። የደራሲያን ማህበርም ሆነ ሌሎች ደራሲዎችን ማዕከል ያደረጉ ስብስቦች አባል አልነበረም።
ደራሲ ጓደኞችም አልነበሩትም። ቀደም ብዬ የሚሰራው ባንክ ውስጥ እንደሆነ አውቄያለሁ። አንድ
ጊዜ ኬንያ እያለሁ፣ ለትልቅ ስብሰባ ወደ ሀገሪቱ ከሚመጡ ከፍተኛ የባንክና የገንዘብ ባለሙያዎች
መሀል ስሙበጋዜጣ ላይ ተጠቅሶ አይቼዋለሁ።የኢትዮጵያ ንግድ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት መሆኑን
በኋላ ላይ ለመረዳት ችያለሁ።ነገር ግን ከተወሰነ ዓመት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ስመለስ፣
ከጠየቅኳቸው መሀል የት እንደማገኘው ሊነግረኝ የሚችል አንድምሰው አልነበረም። ነግር ግን
በአፍሪካ አዳራሽ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ሰራተኞች በሚጠቀሙበት ባንክ ቼኬን
ለሚመነዝርልኝ ባለሙያ ስሙን ስጠቅስለት ወዲያውኑ ቢሮው የት እንደሚገኝ ነገረኝ። ቢሮው
በቸርችል ጎዳና ከራስ ሆቴል ተሻግሮ በሚገኘው በአዲሱ የንግድ ባንክ ህንፃ ላይ፣ነው። በተነገረኝ
አድራሻ መሰረት ቢሮው ስሄድ ታደሰ ሊበንን አገኘሁት።ታደሰ የብድር ክፍል ሀላፊ ነበር። በትህትና
ከተቀበለኝ በኋላ የመጣሁበትን ጉዳይ ነገርኩት። እሱም በሌላ ቀን ስለ ሕይወቱና ስራው
እንደሚያጫውተኝ ቃል ገባ። እኔም "Tradition and Change in Ethiopia" የሚለውን
መጽሐፌን ሰጠሁት። በመጽሐፉ ውስጥ ስለሱ ስራዎችም ስለጠቀስኩ ለቃለመጠይቁ ዝግጅት
ይረዳዋል።
ታደሰ እድሜው እየገፋ ነው። ቢሆንም ከእድሜው አንፃር ቢሸብትም ገና ወጣት ይመስላል።
በአግባቡ ለመተዋወቅ ያህል ጥቂት ካወራንና ስልክ ቁጥር ከተለዋወጥን በኋላ፣ አሮጌው አየር
ማረፊያ አካባቢ በሚገኘው ቤቴ ገና ባልወሰንነው ቀን ለመገናኘት ተቀጣጥረን ተለያየን።
***
የታደሰ ወላጆች ሁለቱም ወሎዬዎች ነበሩ። አባቱ ሊበን ጣፈጠ በመጀመሪያ ገበሬ ኋላ ደግሞ ነጋዴ
ነበሩ። የተወለዱት ከኮምቦልቻ አቅራቢያ ጎሴ ውስጥ በጀቢል ነው። በሰገሌ ጦርነትላይ በንጉሥ
ሚካኤል በኩል ሆነው ልጃቸውን አቤቶ (ልጅ) እያሱን ከሥልጣን ያስወገደውን አዲሱን መንግስት
380
ጥቋቁር አናብስት
ተዋግተዋል። ንጉስ ሚካኤል በተፈሪ መኮንን (ኋላ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ) ሲሸነፉ፣ አቶ ሊበን
በግዞት ወደ ወለጋ ተልከው ደምቢዶሎ ላይ ሰፈሩ። ከዚያ ከደምቢዶሎ ተነስተው፣ በጭነት
እንስሳት አዲሳባን እያቋረጡ እስከ ወሎ፣ደሴ ድረስ መነገድ ጀመሩ።አቶ ሊበን የታደሰን እናት
ጀማነሽ ወልደሚካኤልን ሲያገቡ ጎልማሳ ነበሩ። ወይዘሮ ጀማነሽ ከወሎ፣ አምባሰል ቢሆኑም
ቤተሰቦቻቸው ቡኖ በደሌ፣ ወለጋ ላይ የሰፈሩ ነፍጠኞች ነበሩ። ሊበን እና ጀማነሽ የተገናኙት
ደምቢ ዶሎ ሲሆን፣ ብቸኛው ልጃቸው ታደሰ ንግስት ዘውዲቱ ከሞተች ከጥቂት ቀናት
በኋላበ1923 ዓ.ም እዚያው ተወለደ። ታደሰ ሰድስት ዓመት ሲሆነው አባቱ ሞቱ፤እናቱ ከዚህ
በኋላ ሁለት ጊዜ አግብተው፣ ከሁለቱም ትዳር ልጆች አፍርተዋል። ነገር ግን ታደሰ ገና የሁለት
ዓመት ልጅ እያለ፣ ቤተሰቡ ወደ አዲስአበባ መጥቶነበር።ታደሰ ሲወለድ ሽማግሌ ስለነበሩት አባቱ
ምንም አያስታውስም፤እናቱ ግን ገና ወጣት ነበረች።ወለጋ እያሉ ከታደሰ ቤተሰብ ተጠግተው
የሚኖሩ ሁለት ዘመዶች ነበሩ ፤ አቶ ሊበን በንግዳቸው ምክንያት ሲከብሩ ሁለት ወንድሞቻቸው
ወደ ቤታቸው መጡ። ደምቢ ዶሎውስጥ አንደኛው የአሜሪካ ሚስዮን ትምህርት ቤት ሌላኛው
ደግሞ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ትምህርት ቤት ገቡ።ቤተሰቡ ወደ አዲስአበባ ሲመጣ
ወንድማማቾቹ እዚያው ቀሩ።
ከታደሰ አባት ሞት ጥቂት ጊዜ በኋላ፣ በአሜሪካ ሚስዮን ትምህርት ቤት የነበረው ጎበዜ ጣፈጠ
የተሰኘ አጎቱ፣ ታደሰን ከእናቱ እቅፍ ወስዶ፣ ከአዲስአበባ በቅርብ ርቀት አቃቂ ላይ በሚገኘው
አድቬንቲስት ሚስዮን ትምህርት ቤት አስገባው። ታደሰ እዚህ ትምህርት ቤት ሲገባ 10 ዓመቱ
ሲሆን አንደኛ ደረጃ ትምህርቱን እስኪጨርስ በዚያው ቆይቷል።በጣም የሚወዳት እናቱ
ትናፍቀዋለች፤፣ እሷም አቃቂ እየመጣች ትጠይቀው ነበር። ጥሩ ታሪክ ተራኪ ነበረች ፤ ታደሰም
ልብወለድ የመፃፍ ተሰጥኦውን ከእሷ እንዳገኘ ያምናል። ቤት ውስጥ ብዙ ታሪክ ታወራላቸዋለች ፤
ከነዚህ መሀል ታደሰ ሁለቱን መርጦ ነግሮኛል ፤ እኔም ባጭሩ መልሼ እነግራችኋለሁ፤(በአጭሩ
የምነግራችሁ ታደሰ ወደፊት እንደገና መፃፍ ሲጀምር ሊጠቀማቸው ስለሚፈልግ እንዳልሰርቀው
በሚል ነው)።1
381
ጥቋቁር አናብስት
እውነተኛ ጓደኞች የስጋ ዘመዶቹ መሆናቸውን በዚህ ዘዴ አወቀ። ታደሰም በዚህ ታሪክ የተነሳ
ከእናቱ ትምህርት ተማረ።
እናቱ ለታደሰ የነገረችው ሌላኛው ታሪክ፣ ለሞት ካላት ቋሚ ፍርሀት የመነጨ ነው። ከነሕይወቷ
እንዳትቀበር ስለምትሰጋ ( ተመሳሳይ ታሪኮችን ሰምታስለምታውቅ) የሬሳ ሳጥን ውስጥ ከመግባቷ
በፊት ለአንድ ሙሉ ቀን በድኗ እንዲሁ እንዲቀመጥ ትሻለች።2 በዚህ የተነሳ የታደሰ እናት በ83
ዓመታቸው በ19877/78 አ.ም በእርግጥ ሲሞቱ የተቀበሩት ዘግይተው ነበር። ኢትዮጵያ ውስጥ
ለቀብር የሚመጡ ሰዎች ብዛት ትልቅ ግምት ስለሚሰጠው፣ የታደሰ እናት ለቀብራቸው
የሚመጣው የሰው ብዛት እና ማን ማን ይመጣ ይሆን የሚለው ያስጨንቃቸው ነበር። ታደሰ ገና
ልጅ እያለ ይህ ጉዳይ ምንኛ እንደሚያሳስባቸው የሚገልጥ ታሪክ ነግረውታል። ታሪኩ እንዲህ
ነው፦
አንዲት መሀን ሴት፣ብዙ ልጆች ካሏት ሴት ጋር ተጎራብታ ትኖራለች። እናትየው በእርጅናዋ ወራት
በልጆቿ እየተጦረች ደስተኛ ሕይወት እንደምታሳልፍ ተስፋ ስታደርግ፣ መሀኗ ግን “ቀባሪ በፈጣሪ”
እያለች ተስፋዋን በእግዚአብሔር ላይ አድርጋለች። እናታቸው ስታረጅ፣ በማያልቀው ፍላጎቷ
የተሰላቹት ልጆች በጅብ እንድትበላ ገላጣ ቦታ ላይ ከጣሏት በኋላ ጥርጣሬ ለማዳፈን መሀኗን ሴት
እንደ እናታቸው አድርገው ተቀበሏት። አንዳንድ ጥርጣሬዎች ሲፈጠሩ፣ በሰፈሩ
አውጫጪኝ/አፈርሳታ ላይ ተገኝተው እናታቸው እንደሆነች አስረግጠው ተናገሩ። መሀኗም
ሚስጥራቸውን ጠበቀች፤እነሱም በአግባቡ ተንከባከቧት።እስከ ሕይወቷ ፍፃሜ ድረስ በደስታ ኖረች
፤የተቀበረችውም በታላቅ ክብር ነበር። የእውነተኛ እናታቸው ፍፃሜ ግን በጅቦች በመበላቷ
አላማረም ።የተገኘው ቀሪ አካሏ እጆቿና እግሮቿ ብቻ ናቸው፤ኢትዮጵያውያን ጅቦች እነኚህን
የሰውነት ክፍሎች አይበሉም ብለው ያምናሉ።
በ1949 በታተመው የመጀመሪያ መጽሐፉ "መስከረም" መግቢያ ላይ፣ ታደሰ ሊበን በአጭር
ልብወለድ ጥበብ ችሎታቸውን ማሻሸል የሚፈልጉ እንዲያነቧቸው ብዙ ታዋቂ የአጭር ልብወለድ
ጸሐፍትን ይጠቁማል። በመስኩ በሚገባ እንዳነበበ ግልጽ ነው። ነገር ግን ራሱን በተመለከተ
ችሎታውን ለማዳበር ከነዚህ ደራሲዎች ይልቅ የእናቱ አስተዋጽኦ እንደሚበልጥ ይናገራል። ገና ልጅ
እያለ ከእናቱ ጋር ስለሚተኛ ብዙ ታሪኮች ይነግሩት ነበር። እናቱ ጥብቅ የሥነ ስርዓት ቁጥጥር
የሚያደርጉ ቢሆኑም ለልጆቻቸው ደግ ነበሩ። በባህሪያቸው ያሰቡትን ሳይደብቁ ለሁሉም
ይናገራሉ። “በአካል ግዙፍ እና መልከመልካም” ሲሆኑ ። አባቱ ከሞተ በኋላ ታደሰ ከእርሳቸው ጋር
ይኖር ነበር። ሁለተኛ ባል ካገቡም በኋላ ለተወሰነ ጊዜ አብሯቸው ኖሯል ። በኋላ ቤቱን ጥሎ ሄደ።
በጣም ብቸኛ ልጅ እንደነበር ይናገራል። ምናልባት እንደልቡ ጓደኞችን ለመምረጥ አልቻለም
ይሆናል። አንዴ ሶስተኛ ሀብታም ባላባት ባል ያገቡትን እናቱን ለመጠየቅ ከአዲስአበባ 75 ኪሜ
382
ጥቋቁር አናብስት
***
ገና የስድስት ዓመት ልጅ እያለ ለጋነቱ ታይቶ የቀበና የልጃገረዶች አድቬንቲስት ሚስዮን ትምህርት
ቤት እንዲገባ ተፈቀደለት። ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ስትወር፣ የሚያሳድገው አጎቱ አሁንም ድረስ ከደሴ
ወጣ ብለው የሚኖሩ ሁለት የአባቱ ወንድሞች ጋር ሊያስተዋውቀው ወደ ወሎ ይዞት ሄደ።
አጎትየው ወደ ወሎ የሄደው፣ እንግሊዝኛ ስለሚችል በጣሊያኖች እየታደነ ስለነበር ነው። ለአራት
ዓመት ያህል ወሎ ውስጥ ተደብቆ ቆየ። ታደሰ ግን ከአንድ ዓመት በኋላ ወደ አዲስአበባ ተመለሰ።
ሌላኛው አጎቱ ደምቢዶሎ ውስጥ ሲሞት፣ አብሮት የነበረው አጎቱ ለቀብር ወደዚያው ሄደ። የታደሰ
እናት ግን አዲስ አበባ እንዲቆይ አልፈለጉም ምክንያቱም ባሊላ(ታደሰ ስያሜውን ያገኙት ባሊላ
ከሚባሉ የኢጣሊያ መኪናዎች ነው ይላል―በሕሩይ የሕይወት ታሪክ ስር የግርጌ ማስታወሻውን
ይመልከቱ) ስለሚባሉ ዩኒፎርም ተሰጥቷቸው ሙሶሎኒን የሚያሞግሱ መዝሙሮችን ስለሚዘምሩ
ልጆች ሰምተው ስለነበር ታደሰም እንደነሱ ለመሆን ይገፋፋል ብለው በመፍራታቸው ነበር።
ስለዚህ ከነበረበት ጃንሜዳ ( ጣሊያኖች አዘውትረው ኳስ የሚጫወቱበት አካባቢ ነበር)
አስወጥተው ከአዲስአበባ 40 ኪሜ በምትርቀው ሰንዳፋ ውስጥ አንድ ባለ ጠጅ ቤት የሩቅ
ዝምድና ካላቸውና ጓደኛቸው ከሆኑ ወይዘሮ ዘንድወስደው “ሰጡት”። እንደዚህ ርቆ ከተቀመጠ
"ባሊላዎችን" ለመሆን አይጎመዥም። ሂሳብ መቀበል ላይ ጎበዝ ስለነበር ጠጅ በማሳለፍ ያግዛቸው
ነበር። በጣም ብዙ የኢጣሊያ ጦር ሰራዊት በቤቱ በኩል ሲያልፍ እንዴት እንደነበረ እስከ አሁን
ድረስ ያስታውሳል።
አጎቱ ጎበዜ ከደምቢዶሎ ሲመለስ የሰባት ዓመቱን ታደሰን ሊያገኘው አልቻለም ፤እናቱም ወዴት
እንዳለ አልናገር አለች። ስለዚህ በታደሰ እናት እነደተናደደ ወደ ደሴ ሄደ። ታደሰ መጠጥ ቤት
ውስጥ ለሁለት ዓመት ከሰራ በኋላ ወደ አዲስአበባ መጣ። ከጦርነቱ በኋላ አቃቂ አድቬንቲስት
ሚስዮን ማስተማር የጀመረው አጎቱ፣3 ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጣና የአስር ዓመቱን
ታደሰ እዛው አቃቂ ሚስዮን ወስዶ አስገባው። ይህ አጎቱ በአቃቂ ለትንሽ ጊዜ ካስተማረ በኋላ ወደ
ደሴ አድቬንቲስት ትምህርት ቤት ተዛወረ ፤ በመጨረሻም የመንግሥት ትምህርት ቤት ገባ። ይህ
አጎቱ በአድቬንቲስት ሚስዮኑ በነበረው ቦታ ምክንያት ታደሰ ለትምህርት ቤት ወይም ለምግብና
383
ጥቋቁር አናብስት
ለመኝታ መክፈል አይጠበቅበትም ።ነገር ግን በክፍያ ፋንታ በየቀኑ ለአራት ሰአታት በአትክልት
ስፍራው መስራት ይጠበቅበት ነበር፤ክፍያ የሚከፍሉት ተማሪዎች ለሁለት ሰአታት ብቻ ይሰራሉ።
ሁለተኛ ደረጃን እ.ኤ.አ 1949 ካጠናቀቀ በኋላ፣ ልክ ፈተናውን እንደጨረሰ ደሴ የሚገኙ አጎቱ ጋር
ተደብቆ ቆየ። ምክንያቱም በግድ የአየር ኃይል አባል እንዲሆን ተመልምሎ ስለነበር ነው፤ እሱ
ደግሞ እዚያ መስራት አልፈለገም።5ጠፍተው የተደበቁ ልጆችን መፈለጉ ሲያበቃ፣ታደሰ ወደ
አዲስአበባ ተመለሰ። ከዚያም የግል የሙስሊም ትምህርት ቤት በሆነውና ከአንዋር መስጊድ ቀጥሎ
በሚገኘው ደጃዝማች ኡመር ሰመተር ትምህርት ሂሳብ እና እንግሊዝኛ ለሁለት ዓመት አስተማረ።
ጥሩ አስተማሪ ሳይሆን አይቀርም፤ ምክንያቱምተማሪዎቹ ስምንተኛ ክፍልን (የመለስተኛ ሁለተኛ
ደረጃ ትምህርት ቤት ማጠናቀቂያ)በጥሩ ውጤት አልፈዋል።
384
ጥቋቁር አናብስት
የባንክ ተቀጣሪ ከሆነ በኋላ ለዚህ አዲስ የስራ ዘርፍ የሚሆን ትምህርት ለማግኘት ሞከረ።
መጀመሪያ ቢሮው ካይሮ ከሚገኘው የብሪቲሽ ትምህርት ቤት በርቀት የሒሳብ ስራ፣የቢዝነስ
እንግሊዝኛእና የቢዝነስ አርቲሜቲክ መማር ጀመረ። ከሁለት ዓመት በኋላ ቢያቋርጠውም፣
እስከተማረበት ድረስ ላለው የምስክር ወረቀት ተቀብሏል ፤ በስራውም ረገድ ትምህርቱ በጣም
እንደረዳው ይናገራል።ትምህርቱን ቢጨርሰው ኖሮ፣የተመዘገበ/የተመሰከረለት የሒሳብ ሰራተኛ
መሆን ይችል ነበር። ነገር ግን ርቆ ከመሄዱ በፊት በሥነ ጽሑፉ ተሳበ። በግሉ ብዙ ካነበበ በኋላ፣
የፃፋቸው ታሪኮች በኋላ "መስከረም" በሚል የአጭር ታሪኮች መድብል ታተሙ። መስከረም
የዓመቱ የመጀመሪያ ወር ከመሆኑ ባሻገር፣አዲስ ጅማሬ፣ አዲስ ተስፋ እና አዲስ ቃልኪዳንን
ያመለክታል።
ይህ መጽሐፍ ዝግጁ ከመሆኑ በፊት እ.ኤ.አ 1948 አገባ፤ቀኑን እርግጠኛ ለመሆን ቀለበቱን
አውልቆ የታተመውን ቀን ማየት አስፈልጎት ነበር―26/6/48 ይላል (ኢትዮጵያውያን የደስታ
ቀኖችን እንደ ምእራብያውያን በየዓመቱ አያከብሩም፤ይልቁንም ሙት አመቶችን እስከ ሰባት ዓመት
ድረስ ያከብራሉ) ሚስቱ የአዲስ አበባ ንግድ ስራ ትምህርት ቤት ምሩቅ ስትሆን የተገናኙት ባንክ
ቤት ውስጥ በፀሐፊነት ስትሰራ ነው። የአዲስአበባ ልጅ ስትሆን ሁለት ልጆቻቸውንም የወለዱት
እዚሁ ነው።የመጀመሪያዋ ሴት ልጅ ስትሆን አግብታና ሁለት ልጅ ወልዳ በሰሜን አሜሪካ
ትኖራለች፤ሁለተኛው ወንድ ልጅ ቆይቶ በ1966/67 ዓ.ም የተወለደ ሲሆን ከእህቱ ጋር ይኖራል።
የታደሰ ሚስት ጤናዋ አስተማማኝ ስላልነበረ፣የወለዱት እነዚህን ሁለት ልጆች ብቻ ነው።
ከጋብቻው በኋላ ብዙም ሳይቆይ በ1949/50 ዓ.ም ታደሰ በ"መስከረም" ውስጥ የተካተቱ
አብዛኛዎቹ ታሪኮችን ፃፈ፤ነገር ግን አንዳንዶቹን የፃፋቸው ከዛ በፊት ሳያገባ በፊት ብቸኛ እያለ
ሲሆን፣ ታሪኮቹ በጊዜው የነበረውን ልምድ እና አስተውሎት ያንፀባርቃሉ። የባንክ ቤቱንም ሆነ
የመምህራንነት ስራውን ለማግኘት ተቸግሮ ነበር።
ከማግባቱ በፊት ባሳለፈው የብቸኝነት ሕይወት ምክንያት ሳይሆን አይቀርም ከልጅነቱ አንድ
አጋጣሚ አስታወሰ። በአጋጣሚው ታደሰ የገና ጨዋታ ከአንዲት ቆንጆ ልጅ ደጅ ላይ ሲጫወት
እናቱ ቡዳ ናት ወላጆቿም ቆማጣ ናቸው ብለው ያስጠነቅቁታል። (በኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ
በኦሮሞ ባህል ውስጥ የወንድና ሴት ልጅ የቅርብ ግንኙነት በጊዜ ሊጀምር ይችላል)።
እንደተጠቀሰው ታደሰ ከዚህ አጋጣሚ ተነስቶ የፃፈውን "ጅብ ነች" የተሰኘ ታሪክ ለመጀመሪያ
መድብሉ"መስከረም" የመክፈቻ ታሪክ አድርጎታል። ስለዚህ የግል ገጠመኞችና በአካባቢው
የሚያስተውላቸው ነገሮች የታሪኮቹን ጭብጦች የሚያገኝባቸው ቦታዎች ናቸው።ሁለቱም
መጽሐፍቶቹ በ5,000 ቅጂዎች የታተሙ ሲሆን በጊዜው እንደተለመደው ራሱ ሳንሱር ጋር
መውሰድ፣ ለማተሚያ ቤት ቅድሚያ ክፍያ መክፈል ነበረበት። ቅጂዎቹን እንዲሸጡለት ለጓደኞቹ
ካከፋፈለ በኋላ “እንደ ትኩስ ኬክ” ወዲያውኑ ተሸጡ ይላል።ይሁን እንጂ እስካሁን ድረስ በድጋሚ
አልታተመም።እስካሁን ባያደርገውም በተደጋጋሚ ለሚያሳትመው ይችል እንደነበር ፤አሁን ቢሆን
ወደፊት ሊያደርገው እንደሚችል ይናገራል።
ወደፊት ታደሰ "በአላማ" ይጽፋል። እንደሚናገረው፣ መፃፉን ማቋረጡ ስህተት ሊሆን ይችላል፤
ነገር ግን ይህንን የተረዳው ከጥልቅ ማሰላሰል በኋላ ሲሆን እዚህ ድምዳሜ ላይ የደረሰው
የነበረበትን ግብረገባዊ ግራ መጋባትን ካጠራ በኋላ ነው። ያኔ “አልበሰለም” ነበር ከአሁን በኋላ ግን
የትኛውም ያሳተማቸውም ሆኑ ሌሎች ታሪኮቹ አያሳፍሩም። ነገር ግን የተሻሉ
ታሪኮችን―የእግዚአብሔርን ክብር የሚገልጡ እና የኑሮውንም መንገድ የሚያሳዩ
ታሪኮችን―የሚጽፍበትን ችሎታ እንዲሰጠው ይፀልያል።“ስብከት መሰል” ወይም ግብረገባዊ
ታሪኮችን መጻፍ ከጀመረ አንባቢዎች ይበረክቱልኛል ብሎ በማመን ይሆን ?“አንባቢዎች እንዴት
መኖር እንዳለባቸው የመምከር ፍላጎት”እንደሌlው፣ነገር ግን “ሰዎችን በመንፈስ ከፍ የሚያደርግ
ነገር”እጽፋለሁ ብሏል። ይሁን እንጂ ይህንንም ራሱ ቢሆን በግልጽ አያደርግም። ከድሮም ቢሆን
ታሪኮቹ ከዋናው የታሪክ መስመር ወጣ ብለው የተደበቁ ጥልቅ ትርጉሞች አሉት። በዚህ መሰረት
አንደኛው የታተመው ታሪኩ "ትንሽ ልጅ" ስለ አንድ ልጅ ያወራል። ይህ ልጅ አንድ እንግዳ
ቤታቸው መጥቶ ለሚጠይቃቸውእንደ―ስምህ ማነው? ወላጆችህን ትወዳቸዋለህ? ለመሳሰሉት
ጥያቄዎች―መልስ መስጠት ይፈራል። "ትንሹ ልጅ" በኢትዮጵያ ውስጥ ስለነበረው፣ የመናገር እና
ሀሳብን የመግለጽ ነፃነት እጦት መሆኑን አሁን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ራሱ ገና አሁን ነው የተረዱት።
በኢትዮጵያ ውስጥ የነበረው ባህል እንዲህ ያለ ነበር ይላል ታደሰ። በታሪኩ ውስጥ ልጁ እናቱንና
አባቱን ስለመውደዱ የተጠየቀው "አገርህንና ንጉስህን ትወዳለህ ወይ?" ለማለት ነው።ሰዎች
አገራቸውን እና ገዢዎቿን እንደሚወዱ በግልጽ ለመናገር እንኳን ይፈራሉ። ነገር ግን በሚስጥር
ያወሩታል።ይሄም ልክ ልጁ እንግዳው ከቤት እስኪርቅ ጠብቆ፣ ከአባቱ እና ከእናቱ አይን ተሰውሮ
የእንግዳውን ጥያቄዎች ሁሉ እንደሚመልስለት ማለት ነው።6
ታደሰ ንጉሡን ሁሌም ቢወዳቸውም ነገር ግን ይህን ለመናገር የሚያመነታበት ጊዜ ነበር። “የእሱ
ትውልድ ሰዎች ንጉሱንም ንግስቷንም ስለሚወዱ ስለነሱ አንዳች መጥፎ ነገር አይተነፍሱም ነበር”
ይላል።
ኃይለሥላሴ በቤተመንግሥቱ ኩሽና የተዘጋጀ ምግብ ራሳቸው ይዘው ኮተቤ ወደሚገኘው ቀዳማዊ
ኃይለሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይዘው ዘወትር ሃሙስ እንደሚመጡ በተለይ
ያስታውሳል ፤በሁዳዴ ደግሞ ዘወትር አርብ የፆም ምግብ ይዘው ይመጣሉ።በገበታ ወቅት ንጉሡም
ከተማሪዎቹ ጋር ተቀምጠው ይበላሉ።ምግቡይጣፍጥ እንደሆነም ተማሪዎቹን ይጠይቃሉ―አዎን!
387
ጥቋቁር አናብስት
ተማሪዎቹ ስለ ንጉሳቸው ያላቸው ትዝታ እንዲህ ያለ ነበር፤ስለዚህ በዚያው በንጉሱ ዘመን የንጉሱን
ስም በፍቅር መጥራት “የሚያስጠረጥርበት” ዘመን ላይ መድረስ ያሳዝናል። ነገር ግን ታደሰ ለንጉሱ
ያለው ፍቅር አልቀነሰም። በመንግሥቱ ሐይለማሪያም አምባገነናዊ ማርክሳዊ አገዛዝ ወቅት እንኳን
ለኃይለሥላሴ ያለውን ውዴታ ለመግለጽ አያፍርም ወይም አይፈራም።
***
ታደሰ በኢትዮጵያ መንግስት ባንክ በ1951 ዓ.ም የዴስክ ጸሐፊ ሆኖ ስራ ጀመረ። ከአንድ ዓመት
በኋላ መዝገብ ያዥ ሆነ። በዚህ ስራ ለሁለት ዓመት ከቆየ በኋላ ምክትል መርማሪ ሆነ። ከአንድ
ዓመት በኋላ መዝገብ ያዥ ሆኖ በመጀመሪያው የባንኩ ቅርንጫፍ በአዲስ ከተማ (የዛኔ ቁጨራ
ተብሎ ይጠራ ነበር) ከአንዋር መስጊድ በቅርብ ርቀት ይሰራ ነበር። በኋላ የባንኩ ረዳት ስራ
አስኪያጅ ሆኖ ለሶስት ዓመት ሰራ። ከዚህ በኋላ ስለ ባንክ ስራ እንዲማር ወደ ጣሊያን፣ ሮም
እ.ኤ.አ በ19647ተልኮ በክሬዲቶ ኢታሊያኖ ለዘጠኝ ወራት ትምህርት ተከታተለ። ይህንን በውጪ
ሀገር ያደረገውን የመጀመሪያ ቆይታ ወዶት ነበር።
ታደሰ የተሰጠው ስራ የንግድ ባንክን (በ1965 ባንኩ ለሁለት ከተሰነጠቀ በኋላ እነሱን ተቀላቅሏል)
የአራዳ ቅርንጫፍ ማደራጀት ነበር። ይህ ስራ የተሰጠው ባንኩ ውስጥ ሁሉን ስራ በሚመለከት
ልምድ ስለነበረው ነው። ለስድስት ወር የሰራበት ይህ ቅርንጫፍ በጊዜው ትልቁ ቅርንጫፍ ነበር።
ከዚያ መከላከያ ሚኒስትር ፊትለፊት ወደሚገኘው ዋና ቅርንጫፍ ተዛወረና የብድር ክፍል ዋና ሀላፊ
ሆነ።ከዚህ በኃላ ኒውዮርክ ወደሚገኘው ቼዝ ማንሃተን ባንክ ተልኮ ስለ "ብድር ጉዳዮች" እያጠና
ለአምስት ወራት ቆየ። በጊዜው የብድር ክፍል ሃላፊነቱን እንደያዘ ነው። ከዚህ በተጨማሪ በቼዝ
388
ጥቋቁር አናብስት
ማንሀተን ባንክ ምክር መሰረት የብድር ትንተና ትምህርት በርቀት ወስዶ በ1960 ዓ.ም የምስክር
ወረቀት ተቀበለ። ከኒውዮርክ እንደተመለሰ የብድር ክፍል ረዳት ስራ አስኪያጅ ሆኖ ከ1961–
1966 ዓ.ም አብዮቱ እስከሚፈነዳ ሰራ።እስከዚህ ወቅት ድረስ በንግድ ባንክ ለስምንት ዓመት
ሰርቷል።
አብዮቱ በ1966 ከፈነዳ በኋላ፣ ታደሰ አድሃሪ ተብሎ፣ ከነበረው ደረጃ ዝቅ ተደርጎ ከዘጠኝ ዓመት
በፊት ራሱ ባደራጀው የንግድ ባንክ የአራዳ ቅርንጫፍ እንደገና ስራ አስኪያጅ ሆነ። በዚያ ለሁለት
ዓመት ከሰራ በኋላ፣ የአዲስ ከተማ ቅርንጫፍ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነ። ይሄ ቅርንጫፍ ከአራዳው
ቅርንጫፍ ስለሚተልቅ እንደ እድገት የሚቆጠር ነበር።
በ1976/77 ዓ.ም ወደ አዲስአበባ ተመልሶ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር ክፍል ሐላፊ ሆነ።
በቃለመጠይቃችን ወቅት በዚሁ የስራ መደብ ላይ ነበር። ታደሰ ሊበን የጡረታ መብቱ ተከብሮለት
በ1978 ዓ.ም መጨረሻ ጡረታ እንደሚወጣ ተስፋ ያደረገ ቢሆንም፤ለተጨማሪ ሶስት ዓመታት
ስራውን እንዲቀጥል ጥያቄ ቀርቦለታል።
389
ጥቋቁር አናብስት
በአንድ ወቅት ብርሀኑ ዘርይሁን በሬዲዮ ቀርቦ ታደሰ ሊበን ሥነ ጽሑፍን የከዳው ለገንዘብ ብሎ
ነው ፤ ስለዚህ ባንክ ቤት መስራት ጀመረ ማለቱን ያስታውሳል፤ "ብዙዎች ባለመፃፌ ይወቅሱኛል"።
አንዳንድ ታሪኮቹ ከአብዮቱ በፊት ወደ ሩስኪ ተተርጉመዋል።አሁን ድረስ እንኳን ታደሰ ሊበን
መኖሩን ወይም መሞቱን ለማወቅ የሚፈልጉ ሩስያውያን አሉ። በ1964 ጣሊያን ውስጥ ፕሮፌሰር
ላንፍራኖ ሪቺ ስለሚተማመኑበት ወደ ኔፕልስ ወስደውት በጋዜጣቸው ላይ ስለ ታደሰ እና አፃፃፉ
ማስፈራቸውን ያስታውሳል።
በታደሰ ሊበን የቀደመ አፃፃፍ የሚደነቁ ሞልተዋል ፤ የመፃፍ ሀይሉ ከመዳከሙ ወይም ተሟጦ
ከማለቁ በፊት ዳግመኛ ብእሩን አንስቶ እንዲጽፍ የሚመኙም ብዙ ናቸው።
***
የሕይወት ታሪኩን ከላይ እንደተጠቀሰው ከነገረኝ ከብዙ ወራት በኋላ ለመፃፍ የበለጠ ጥድፊያ
እንዳደረበት ገለፀ። ስለ ሕይወቱና አላማው ከነገረኝ በኋላ ለመፃፍ የበለጠ ሳይነሳሳ፣ እንዲሁም
ህሊናው ይበልጥ ሳይቆረቁረው አልቀረም።
የተርጓሚው ማስታወሻ
ታደሰ ሊበን “መስከረምና፤ ሌላው መንገድ” በቅርቡ በድጋሚ የታተሙ ሲሆን የአጭር ልብወለድ
በመጻፍ ግን የተመስገን ገብሬ የጉለሌው ሰካራም ይቀድማል የሚሉ ሰዎች አሉ፡፡
ማስታወሻዎች
390
ጥቋቁር አናብስት
5) በንጉሡ ዘመን ጎበዝ ተማሪዎችን ለአየር ኃይል መመልመል የተለመደ ነበር። የሁለተኛ ደረጃ
ተማሪዎች የአየር ሀይልን ሊቀላቀሉም፣ ላይቀላቀሉም እንደሚችሉ ቃል ይገባላቸውና በፈቃደኝነት
የመግቢያ ፈተና እንዲወስዱ ይደረጋል። ነገር ግን ያለፉትን እንዲቀላቀሉ ያስገድዷቸው ነበር።
7) የገለፀላቸው የስራ ቆይታዎች ተደማምረው ከ1951 እስከ 1964 መሀል ካሉት ዓመታት
ጋርልክ አይመጡም። አንዳንድ ስራዎች ላይ ከተባለው ጊዜ በላይ ቆይቶ ይሆናል። ይሁን እንጂ
ቀኖቹን እንደተነገረኝ አስፍሬያቸዋለሁ።
391
ጥቋቁር አናብስት
ሲራክ ኅሩይወልደሥላሴ
የአባቱ ልጅ እና አንድ መጽሐፍ ብቻተርጓሚ ብላታ ሲራክ በኢትዮጵያ
ወግና ደንብ መሰረት በአባቱ ስም በ“ኅሩይ” ብቻመጠራት ይበቃው ነበር።
ነገር ግን በራሱ ስም ላይየአባቱንና የአያቱን ስም ጨምሮ ሲራክ ኅሩይ
ወልደሥላሴ ተብሎ መጠራቱን መረጠ። ስመጥር አባት ሲኖሩህ ፣ደንብ
መሻር ይፈቀድልሃል። ከሲራክ መገለጽ የሚያሻው አስፈላጊ ነገር የአባቱ
ልጅ መሆኑ ነው። ሲራክ ከአባቱ የወረሳቸውን የሥነጽሑፍ ስራዎች ቅርስ
ጠብቆ በማቆየት፣ ከዳር በማድረስና በማሳተም፣ የአባቱ “የጽሁፍስራአስፈጻሚ” ሆኗል። የአባቱን
የኅሩይ ወልደሥላሴን ታሪክ ስጽፍ አብዛኛዎቹን መረጃዎች ያገኘሁት ሲራክ በጥንቃቄ
ካስቀመጠው ካልታተመው የአባቱ የቀን ውሎ ዘገባዎችና ማስታወሻዎች ሲሆን ሌሎች
ማስታወሻዎቹ በአደባባይ ቢታወቁም፣ ይሄኛው ግን ከሕዝብ አይን ተሰውሮ የተቀመጠነበር።1
ከአለቃገብረሃና ወዲህ እንደ ሲራክ በቀልደኝነቱ የሚታወቅ አንድም ኢትዮጵያዊ ደራሲ የለም።
ሁለት ቀልዶቹን ለአብነት ያህል እነሆ፦
392
ጥቋቁር አናብስት
ሲራክ ከወጣትነቱ ጀምሮ በተለይ ደግሞ ኦክስፎርድ ተምሮ ከመጣ ወዲህ አፈንጋጭ ነበር። ከዛ
በፊት በግብጽ፣አሌክሳንድሪያ ተምሯል።
ከሁለተኛው የአለም ጦርነት በኋላ ኢትዮጵያን ጎብኝቶ ሲራክን ያገኘው ስዊድናዊ ጸሐፊ “ሲራክ
በራሱ ህዝብ ኋላቀርነት ላይ የሚሳለቅ ግብዝ ነው” ሲል ትንሽ ቆይቶ ባሳተመው መጽሐፉ
አስፍሯል።ይኸው ጸሐፊ ሲራክ በራሱ ህዝብ መሳለቁና መዘባበቱ ልክ እንዳይደለና፣ ይህን
አመለካከቱን እስካልቀየረ ድረስ፣ ለቁምነገር አይበቃም የሚል አስተያየት ጨምሯል።
ብላቴንጌታ ኅሩይ ሁለት ወንድ ልጆች ነበሯቸው፤ ፈቃደስላሴ እና ሲራክ። ሲራክ በመጀመሪያ
ግዕዝ ለመማር ወደ ታላቁ የደብረሊባኖስ ገዳም ሄደ። ከዚያ በኋላ ወደ አዲስአበባ ተመልሶ
ሚስዮን ትምህርት ቤት ገባ። ቀጥሎ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ለመከታተል ከወንድሙ ጋር
አሌክሳንድሪያ ወደሚገኘው ቪክቶሪያ ኮሌጅ ሄደ።ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ስትወር ኅሩይ ወደ
እንግሊዝ ተሰደዱ። ሁለቱም ልጆቻቸው ወደ እንግሊዝ ቢከተሏቸውም የነሱ ምክንያት ግን
ለትምህርት ነበር።የሄዱትበ1928 ዓ.ም በሱዳን በኩል ሲሆን፣ ፈቃደስላሴ በካምብሪጅ ምህንድስና
ሲማር፣ ሲራክ ደግሞ በኦክስፎርድ ፍልስፍናን አጥንቷል።
ኃይለሥላሴ በ1933 ዓ.ም ከእንግሊዝ እንደተመለሱ፣ ሲራክ በሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ዋና
ጸሐፊ ሆኖ ተሾመ። በሹመኝነቱ ወቅት፣ ከብዙ ሚኒስትሮች በተለይም ደግሞ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ
ከራስ ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው ጋር አይጣጣምም ነበር። ጉቦ መብላታቸውን፣ ጉዳዮችን
በቀጠሮ እያሳደሩ ሰው ማጉላላታቸውን፣ ለሰዎች ቀጥተኛ ውሳኔ እና መልስ በመስጠት ፋንታ
በኢትዮጵያ አሁን ድረስ እንደተለመደው “ነገ፣ተመለስ!” እያሉ የሰዎችን ጊዜ ማቃጠላቸውን ፣ሁሉ
ይጠላል።
ከጊዜ በኋላ ሲራክ ከመንግስት ስራ እንዲሰናበት በጠየቀው መሰረት ተፈቀደለት። ከዚያ በኋላ
ይተዳደር የነበረው እሱም፣ ሚስቱም ከወላጆቻቸው በወረሱት መሬት እና ከሚያከራያቸው ቤቶች
በሚገኘው ገቢ ነበር።
393
ጥቋቁር አናብስት
ከኢትዮጵያ ድንበር ባሻገር ሁለተኛው የአለም ጦርነት አሁንም ገና እየተቀጣጠለ በነበረበት ወቅት
ሲራክ የእንግሊዝ ኢምባሲ የፕሬስ መኮንን ከነበሩት ሚስተር ዱልፍስ ሞልስዎርዝ ጋር ተዋወቀ።
ይህ ቢሮ በኢትዮጵያ“ ወደ ድል ጎዳና” የሚል ህትመት ማዘጋጀት ጀመረ። ሲራክ በሚስተር
ሞልስዎርዝ3 ስር ሆኖ፣ መጣጥፎችን ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ ይተረጉም ነበር። ሌላው
ኢትዮጵያዊ አቶ በዕደማርያም ደግሞ ለሲራክ ጸሐፊ ወይም ረዳት፣ ለሚስተር ሞልስዎርዝ ደግሞ
አስተርጓሚ እንዲሆን ተቀጠረ። አቶ በእደማርያም የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የአስረኛ ክፍል
ምሩቅ እና ብዙ የቤተክርስቲያን ትምህርት የነበራቸው ሰው ነበሩ። አቶ በእደማርያም የሲራክን
ግርድፍ ረቂቆች በእጅ ገልብጠው፣ ቋንቋውን አቃንተው ወደ ማተሚያ ቤት ይልካሉ። የሳሙኤል
ጆንሰንን ራሴላስ ወደ አማርኛ ቋንቋ እንዲተረጉም ሲራክን የገፋፉት ራሳቸው ሚስተርሞልስዎርዝ
ሲሆኑ፣ በዚህ መሰረትትርጉሙ በመፃፍ መልክ ከመውጣቱ በፊት፣ በዚሁ መጽሔት ላይ
በተከታታይ ይወጣ ጀመር። እንደተለመደው ሲራክ በግርድፉ ተርጉሞ ረቂቁን ካዘጋጀ በኋላ አቶ
በዕደማርያም ለህትመት እንደሚሆን አድርገው ያስውቡታል። መጽሐፉ ጀርመንና ኢጣሊያ
ከተሸነፉ በኋላም ተተርጉሞ በጋዜጣው መቅረቡ አልቀረም፤ ብቻ የጋዜጣው ስም ተቀይሮ “ጊዜ
የወለደው” ተባለ።ጋዜጣው የሚታተመው ከተቀረው ኤርትራ ጋር በእንግሊዝ ስር በነበረችው
አስመራ ነበር።
ሲሆን ሲራክም ዘወትር እንዲህ እያለ ይመክረው ነበር፦“አፍህን ያዝ፤ሁለተኛ ፖለቲካ ውስጥ
እንዳትገባ!” በኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ ውስጥ ሲራክ የሚታወቀው የሳሙኤል ጆንሰንን "ራሴላስ"
ወደ አማርኛ ቋንቋ በመተርጎሙ እና የአባቱን አንዳንድ ስራዎች በማሳተሙ ነው። በነገራችን ላይ
ሳሙኤል ጆንሰን "ራሴላስ"ን በ1751 ዓ.ም በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ የፃፈው የእናቱን ቀብር
ወጪ ለመሸፈን ነበር።አንዳንዶች ሲራክን እንደ ፈላስፋ ይቆጥሩታል። ነገር ግን በሀገሩ ባህል እና
ፖለቲካ ላይ ይህ ነው የሚባል ተጽእኖ አልፈጠረም።
ማስታወሻዎች
1) የኅሩይን ታሪክ ከፃፍኩ በኋላ የሕይወት ታሪካቸው ታትሞ ወጣ። ደራሲው ይህንን ማስታወሻ
አግኝቶት ሊሆን ይችላል። ይሁን እንጂ እኔ መጽሀፉን አላነበብኩትም።
3) የተወለደው ተጉለት ውስጥ በወደራና ሞጆ ወረዳ ነው። አባቱ አለቃ ሲሆኑ ያሳደጉት አጉቱ
ተጉለት ውስጥ ኤጲስ ቆጶስ በኋላ ደግሞ የወለጋ ጳጳስ ሆነዋል። ምሁር፣ጸሐፊ እና ሰአሊ የነበሩ
ሲሆን አንዳንዶች ደግሞ እንደ ቅዱስ ሰው ይቆጥሯቸዋል።
395
ጥቋቁር አናብስት
396
ጥቋቁር አናብስት
በዓሉ ግርማ
"የሥነ –ጽሑፍ አድባር" "ለመፃፍ የተወለደ" እና "ለፃፈው
የተሰዋ" ደራሲ፣ ጋዜጠኛ እና ሰማዕት
በብዙዎች አስተያየት በአሉ ግርማየኢትዮጵያ ቁንጮ ደራሲ ነው። ሌሎች ደራሲዎች የትኛውንም
የበአሉን "ነጠላ ስራ" የሚያስከነዳ አንድ "ነጠላ ስራ" ደርሰው ይሆናል ፤ ነገር ግን በአጠቃላይ
ሲታይ ኢትዮጵያ እንደ በአሉ በተከታታይ አቅሙን ያስመሰከረ ድንቅ ደራሲ አላፈራችም። ሌሎች
ደግሞ በአሉን ከሌሎች ጸሐፊዎች ጋር ያስተካክሉታልወይም አንድ ወይም ሁለት ከእሱ የተሻሉ
ደራሲዎች እንደሚኖሩ ያስባሉ። የሆነው ሆኖ የኔ አላማ ስራዎቹን መመዘን ሳይሆን የምችለውን
ያህል ስለ ሕይወቱ መረጃ መስጠት ነው።
***
በአሉ ግርማ በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ፣ በኢሉባቡር ክፍለሀገር ውስጥ በምትገኝ ሱጴ የተባለች
ትንሽ ከተማ ተወለደ ( ሱጴ የበአሉ ሁለተኛ ልብወለድ መቼት ነች።) የበአሉ እናት "የአካባቢው
ተወላጅ፣ ምናልባት ኦሮሞ" ሳይሆኑ አይቀርም። አባቱ በሕንድ የጉጂራት ተወላጅ ሲሆኑ፣ ወደ
397
ጥቋቁር አናብስት
ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው በፊት እዚያው ሕንድ አግብተው የወለዱ አናፂ ነበሩ። አባትየው
የሒንዱ እምነት ተከታይ እንደመሆናቸው ከጋብቻውጪ ልጅ መውለዳቸው"በሃይማኖቱ
የሚፈቀድ" አልነበረም፤የበአሉ መወለድም እንደ "ክፉ አጋጣሚ" ይቆጠር ጀመር። የአባቱ ስም ባቡ
ይሰኛል። ከቤተሰቡ ተለይቶ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ ገና ወጣት የነበረ ሲሆን በአሉ ነፍስ ሳያውቅ
ወደ ህንድ ተመልሷል።
በአሉ ስሙን እንዴት እንዳገኘ በውል ባይታወቅም፣ ከአባቱ ስያሜ ጋር ተዛምዶ ሳይኖረው
አይቀርም። ከብዙ ዓመታት በኋላ በአሉ ለስራ ሕንድን ሲረግጥ፣ አባቱን ለማግኘት ወይም ስለአባቱ
ለማወቅ ቢሞክርም አልተሳካለትም።
በአሉ ለእናቱና አባቱ ብቸኛ ልጅ ነው። በኢትዮጵያ ባህል መሰረት በአሉ ግርማ ሳይሆን በአሉ ባቡ
ተብሎ መጠራት ነበረበት። ግርማ ያሳደጉት አያቱ፣ የቅርብ ዘመዱ ወይም እንጀራ አባቱ ሊሆኑ
ይችላሉ። እንደዚህ ዐይነት ነገሮች ያልተለመዱ አይደሉም። በአሉ በእናቱ በኩል ብዙ ወንድሞች
ስላሉት (እነ መሰለ ግርማ) አቶ ግርማ የእናቱ ሁለተኛ ባል፣ የእንጀራ አባቱ መሆናቸው ብዙም
አያጠራጥርም። ስለዚህ በአሉ በእንጀራ አባቱ እጅ አድጓል።
በ1960 ዓ.ም በአሉ ግርማ ከኃይለሥላሴ መንግሥት ጋር ግጭት ውስጥ ገብቶ ነበር። በዚህ
ምክንያትለስድስት ወራት ያህል ከስራ "ታገደ"። በጋዜጠኝነት ሙያው ግን ብርቱ በመሆኑ
ከአብዮቱ ፍንዳታ2 ከ1966 በፊት የመነን፣ የአዲስ ሪፖርተር፣ እንዲሁም የአማርኛው አዲስ ዘመን
አዘጋጅ ሆኖሰርቷል። በአሉ በሶስቱም ጋዜጦች ቅርጽ እና ይዘት ላይ ስር ነቀል ለውጥ ማምጣቱ
ይነገርለታል።
በአሉ ሁለት ዝነኛ ልብወለዶቹ “ከአድማስ ባሻገር” እና “የሕሊና ደወል” የፃፈው ገና ከአብዮቱ
በፊት የአዲስ ዘመን ጋዜጣ አዘጋጅ እያለ፣ነው።ሁለተኛው ልብወለድ "ተራማጅ" እና "አብዮት
ናፋቂ" ሴማዎች ስላሉት ከ1966 የአብዮት ነፋስ ጋር በደንብ እንዲነፍስ አስችሎታል። በእርግጥ
ከአብዮቱ በፊት የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ እያለ፣ በጋዜጣው የሚወጡ መንግስትን
398
ጥቋቁር አናብስት
የሚደግፉ ርእሰ አንቀፆች ፀሐፊ እርሱ ነው ተብሎ በመታመኑ፣ "አፍቃሪ አፄ" ነው ተብሎ ይታማ
ነበር። ነገር ግን እንደሚባለው፣ በአሉ እንደዚህ ዐይነት ርእሰ አንቀጾችን አልፃፈም ፤ እንደውም
አፄውንና አስተዳደራቸውን በግልጽ በመቃወሙ ከላይ እንደተገለፀው ከስራ ታግዷል። ይሁን
እንጂብዙዎች ስለ ፖለቲካ ዝንባሌዎቹ ያላቸው "ጥርጣሬዎች" በዩኒሸርስቲም ሆነ ሌሎች
አካባቢዎች በጥርጣሬ እንዲታይ ምክንያት ሆነውበታል። በሌላ በኩል ደግሞበአሉ ሥልጣን
ያላቸው ጓደኞችና ወዳጆች ነበሩት።
ከዚህ በፊት በአሉ በስራው የላቀ ደረጃ ላይ ደርሷል። በ1974 እ.ኤ.አ አዲስ ዘመንን ለቆ
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነ። በ1969 ዓ.ም የወቅቱ ርእሰ–ብሔር
ተፈሪ በንቲ ከተወገዱ በኋላ፣በማስታወቂያ ሚኒስቴር ቋሚ ፀሐፊ/ተጠሪ?/ሆኖ፤ነበር።ተፈሪ በንቲ
በተወገዱ ጊዜ ቋሚ ፀሐፊ/ተጠሪ/ የነበረው ሰው ለብዙ ዓመታት እስር ተዳረገ።4 ከእሱ በኋላበዓሉ
የኃላፊነቱን ስፍራ ተረከበ።በወቅቱ የማስታወቂያ ሚኒስትር ባለመኖሩም፣ በዓሉ ሥልጣኑንም፣
ተግባሩንም በመረከብ የማስታወቂያ ሚኒስቴርን የአስተዳደርና የፖለቲካውን ስራ ደርቦ መስራት
ያዘ።ትልቅ ስልጣንና ሐላፊነት ስለነበረው በዚያው ልክ ብዙ ጠላት አፈራ፤ከነዚህ መሐል ጎሹ ሞገስ
(እስከ 1986 የሳንሱር ሀላፊ የነበረ)፣ እምሩ ወርቁ ( በኋላ የአዲስ ዘመን ዋና አዘጋጅ የሆነ)፣ ፀሐይ
ደባልቀው (በኋላ የኢሠፓአኮ ዋና ፀሐፊ የሆነና ቀጥሎ ም "እስር ቤት የተወረወረ")፣ ገዳሙ
አብርሃ ( የማስታወቂያ ሚኒስትር አማካሪየሆነ፣ ስልጣኑን ውጭ ሀገር ሄዶ እንኳን ያስጠበቀ፤
የበአሉ ጠላቶች "አስተባባሪ" እንደሆነ የሚወራለት፤የበአሉ ተቃዋሚዎች "ፊታውራሪ")5 ገዳሙ
አብርሃ በግልጽም፣ በስውርም የኤርትራ ነፃነት ግንባርን በመደገፍም ይታማል፤በአሉም ይህን
ያውቃል። የሳንሱር ክፍል ኃላፊነቱን ገዳሙ አብርሃ የተሾመው ጎሹ ሞገስ የኢሕአፓ አባል መሆኑ
ይወራል። እምሩ ወርቁ በሌላው ህቡ ዕቡድን በ"ኢጭአት" አባልነት ይጠረጠራል። በአሉ "ከነዚህ
399
ጥቋቁር አናብስት
ሰዎች ጋር ከባድ ግጭት ውስጥ ነበር" በአሉ እንደ ሊቀመንበሩ የሰደድ አባል ሲሆን ( በደርግ ጊዜ
ሚኒስትር የነበሩ ሰው እንደነገሩኝ ሊቀመንበሩ ሰደድን ሲመሰርቱ በአሉ ተባባሪ ነበር)። ከላይ
የተጠቀሱት የበአሉ ጠላቶች ኋላ ሰደድን ቢቀላቀሉም፣ "በአሉ እንደ እውነተኛ የሰደድ አባላት
ስላልተቀበላቸው"፣ እርስ በእርስ ይጣሉ ጀመር። በአሉ ብዙ ጠላቶች ለማፍራት እስከመድፈር
ያደረሰው ከሊቀመንበሩ ጋር ያለውን ቅርበት ተማምኖ፣ እሳቸው ይጠብቁኛል ብሎ ገምቶ ነው
ተብሎ ይታመናል። ከላይ የጠቀስኳቸው ሚኒስትር ጨምረው እንደነገሩኝ፣ በአሉ በፖለቲካ
ሰውነቱ ይበልጥ የማደግ ብርቱ ምኞት ነበረው።
በአሉ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ውስጥ እያለ፣ግርማ ይልማ ሚኒስትር ሆነው በመሾማቸው፣ ጠላቶቹ
ከሳቸው ጀርባ ተሰባሰቡ፤ስለዚህ በዚህ መስሪያ ቤት በአሉ ብቻውን ጠላቶቹን ለመጋፈጥ ተገደደ።
6
በዚህ ወቅት ነበር በአሉ ስልጣኑን እና ክብሩን ለማስጠበቅ፣ በልብወለዶቹ አማካይነት መታገል
የጀመረው። በ"የቀይ ኮከብ ጥሪ" ልብወለዱ በማስታወቂያ ሚኒስትር የሚገኙ "የቤቱ ውስጥ
ጠላቶቹን"ታግሏል፤የመጽሐፉ አብዛኛዎቹ ገፀ ባህሪያትምበማስታወቂያ ሚኒስቴር ከሚገኙ ሰዎች
የተቀዱ ናቸው። ከዚህ በኋላ በቀጣይ"ሐዲስ"፣በኃላ "የሕሊና ደወል" የተሰኘ ልብወለዱን
አስፋፍቶና አሳድጎ መጣ። ብዙዎች እንደሚስማሙበት"ሐዲስ" የበአሉ ግርማ ቁንጮ ስራ ነው።
በመጀመሪያው ስድስት ወር ብቻ 10,000 ቅጂዎች ሲሸጥ፣ይሄም በኢትዮጵያ ገበያ ትልቅ የሚባል
ነው።
***
ኦሮማይ የተፃፈው በቀይ ኮከብ ጥሪ ዘመቻ ወቅት በአሉ ከሊቀመንበሩ ጋር በቅርበት እየሰራና
በተደጋጋሚ እያገኛቸው ኤርትራ ውስጥ በቆየባቸው ሶስት ወራትነው። ስለዚህ ሊቀመንበሩ ስለ
መጽሐፉ መነሻ ይዘት በጥቂቱ ከማወቃቸው ባሻገር እንዲያውም የመጽሐፉን ሀሳብ ተቀብለውትም
401
ጥቋቁር አናብስት
በአሉ ግርማ ካሁን ቀደም መጽሐፍቱን የግል አሳታሚ በሆነው በኢትዮጵያ የኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ
ፕሬስ ይዞታን በወረሰው የኢትዮጵያ መጽሐፍት ማእከል አሳትሟል። የኦሮማይን ረቂቅ መጀመሪያ
የሰጠው ለነሱ ነበር። ነገር ግን በአሉ እንደሚለው ረቂቁን የሰጠው አንድ አርታኢ ከነሱ ይልቅ
የመንግሥት ንብረት ለሆነው ኩራዝ አሳታሚዎች11 እንዲያሳይ መከረው ፤ በአሉም ምክሩን
ተግባራዊ አደረገ። የኩራዝ ስራ አስኪያጅ ረቂቁን ገና በለጋነቱ አስመራ ላይ አንብቦታል። ኩራዞች
ረቂቁን እንዳገኙ፣ ቦርዳቸውን እንኳን ሳያማክሩ በችኮላ ወደ ማተሚያ ቤት ወሰዱት። በተለመደው
አሰራር መሰረት አንድ መጽሐፍ ከመታተሙ በፊት የቦርዱን ይሁንታ ማግኘት አለበት።12 ከቦርድ
አባላቱ መሐል፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አስተማሪ የነበሩት አቶ ደበበ ሰይፉ መጽሐፉ እየታተመ
መሆኑን ሰምተው፣ ስርአቱን ያልተከተለውን አካሄድ ተቃውሙ።ስለዚህ እኚሁ የቦርድ አባል፣
መጽሐፉን አንብበው፣ አስተያየታቸውን እንዲሰጡና፣ መጽሐፉም ለቦርዱ እንዲቀርብ ተወሰነ። አቶ
ደበበ ረቂቁን ካነበቡ በኋላ በተለይ ይዘቱ ላይ መሰረታዊ "ስህተቶች" እንዳሉበት በመግለጽ፣ ኩራዝ
መጽሐፉን ከማሳተሙ በፊት ስህተቶቹ መስተካከል እንዳለባቸው ገልፀው አስተያየታቸውን ለቦርዱ
ፃፉ።የቦርዱ ሊቀመንበር አቶ ዳኛቸው ወርቁ በዚህ አስተያየት ከመናደዳቸውም በላይ(
እንደተነገረኝ ከሆነ) እነዚህ አስተያየቶች ግምት ውስጥ ከገቡ፣የበዓሉ መጽሐፍ እንዳይታተም
ውድቅ ሊያስደርጉት ይችላሉ ብለው ተናገሩ።13ከዚያም ቦርዱ፣ ሊቀመንበሩ ረቂቁን እንዲያነቡ
ጥያቄ አቀረበ፤ሊቀመንበሩም አንብበው አስራ አምስት ገጽ ሪፖርትፃፉ። ከበአሉ ጋር ከተነጋገሩበት
በኋላ በአሉ አንዳንድ ለውጦችን ለማድረግ ተስማማ ፤ ሌሎች ማሸሻያዎችን ውድቅ ያደረገበት
ምክንያት ግን የፃፋቸው ፍሬ ነገሮች "በአደባባይ የሚታወቁ" ናቸው ብሎ በመገመቱ ነበር።
ከአሉባልታ ጋር ሲወዳደር ተጽፎ የታተመን ነገር የላቀ ኃይል አሳንሶ በማየት ስህተት ሳይሰራ
አልቀረም።
ከዚያ በኋላ መጽሐፉ ታትሞ ተሰራጨ ፤ በአንድ ሳምንት ብቻ 5,000 ቅጂዎች ተሸጡ። ነገር ግን
ብዙም ሳይቆይ መጽሐፉ ከገበያ እንዲወጣ ተደረገ።የደኅንነት አባላትም፣መጽሐፉን ከያለበት
ማደንና ከሰው እጅ ሳይቀር መቀማቱን ተያያዙት።14መጽሐፉ የታገደበት ምክንያት በይፋ
402
ጥቋቁር አናብስት
ቀድሞውኑም ብዙ ጠላቶች የነበሩት በአሉ ግርማ፣ አሁን ደግሞ ይበልጥ ሀይለኛ የሆኑ ጠላቶችን
ጨምሮ አፈራ። አንዳንድ ሰዎችወደ መጨረሻው አካባቢ በአሉ ትእቢተኛ፣ ኩራተኛና ጉረኛ እየሆነ
መጥቶ ነበር ይላሉ። በሊቀመንበር መንግሥቱ ያለቅጥ ተመክቶ ይሆናል፤16የነበረችው ስልጣን
እንደጠበቀው አስተማማኝ አለመሆኗን አልተገነዘበም። ወይንም ደግሞ በቀደምት መጽሐፍቱ
“በህዝብ” ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነት በማግኘቱ፣ ስለሚጽፈው ነገር ብዙ መጨነቅ ሳያቆም
አልቀረም። በሌላ በኩል ደግሞ የሚገጥመውን ፈተና ከወዲሁ ጠንቅቆ አውቆትም ሊሆን ይችላል
የጻፈው።ወይም በቀደመ መጻሐፍቱ ዝና ተመምኖ ሊሆን ይችላል፡፡17ለፖለቲካዊ መሻቱ
መረማመጃ እንዲሆነው፣ እንዲሁ በድፍረት የፃፈው ሊሆንም ይችላል። ወይም አብዮቱ እየሄደበት
ያለበትን ጎዳና ወደ መቃወም ደርሶም ሊሆን ይችላል።በአንድ ወቅት ለጥቂት ጓደኞቹ
እንደነገራቸው ከሁሉም በላይ የሚፈልገው በህዝብ ዘንድ ተቀባይነትን ማግኘትና ህዝብ ልብና
አእምሮውስጥ መግባቱን ነው፤እንደምኞቱ መጻሕፍቱ እሱ ከጠፋ ከረጅም ጊዜ በኋላ ራሱ፣ ከሊቅ
እስከ ደቂቅ በህዝብ ዘንድ ተወዳጅ ሆነዋል። ስለዚህ በአሉ ላመነበት ዓላማ ሲል ሕይወቱን ጭምር
አደጋ ላይ ለመጣል እስከመድፈር ሳይደርስ አይቀርም።18
በአሉ ግርማ ኦሮማይን በሚጽፍበት ወቅት የማስታወቂያ ሚኒስቴር ዋና ፀሐፊ ሲሆን የሀገሪቱ
ፕሮፖጋንዳ ክፍል በሱ ቁጥጥር ስር ነበር።ነገር ግን መጽሐፉ ከወጣ ከጥቂት ጊዜ በኋላ በመጽሐፉ
ምክንያት ከስራ ታገደ። ይህየሆነው በነሐሴ 1975 ዓ.ም ነበር። ለ6 ወይም7 ወራት ያህል ሳይሰራ
እንዲሁ“ተንሳፍፎ” ከረመ። ከፊት ለፊቱ ምን እንደሚገጥመው ያላወቀው በአሉ በ1976 የካቲት
ድንገት "ጠፋ"። በአሉ ከስራ በታገደበት ወቅት ምኞቱ "የህዝብ ተቀባይነት እና የሌሎች ደራሲያን
አክብሮት ማግኘት ብቻ እንደሆነ" ተናግሮ ነበር።
በአሉ ግርማ ከጠፋ በኋላ መንግስት በአሉ የኛ ወገን ነበረ፤አሁን ግን በአድሃሪነት ከድቶን ተሰወረ
የሚል ወረቀት በመላ ሐገሪቱ በተነ። ያለበትን የሚያውቅ ለመንግስት ማሳወቅ እንዳለበት ተገለፀ።
ይህ ሁሉ ሽርጉድ መንግሥት በአሉ የት እንዳለ እንደማያውቅ ወይም እጁ እንደሌለበት
"ለማስመሰል" የተደረገ ነበር።
***
ስለበአሉ ግርማ ሰብዕና ለማውራት የሚያስችል ቀረቤታ የለኝም።ባገኘሁት ወቅት ተግባቢ ቢሆንም
የተጨናነቀ ይመስል ነበር። ብዙ ውዝግብ ማሥነ ሳቱ የጠንካራ አመለካከቶች ባለቤት መሆኑን
ይመሰክራል። የስራዎቹ ውጤታማነት ብቃቱን ያስረዳሉ። ብዙም መልከመልካም ባይሆንም ሴቶች
በቀላሉ ይረቱለታል።ለአንድ ዓመት ያህል ከኢትዮጵያ ቁንጮ ዘፋኞች መሐል የአንዷ "ፍቅረኛ"
ነበር።ነገር ግን ትዳር የመሰረተው ከሌላ ሴት ጋር ነው።ደብዛው ድንገት በጠፋበት ወቅት
ከኢትዮጵያ ቆነጃጅት መሐል ግንባር ቀደም ከሆኑት ወይዘሮ አልማዝ ጋር ሐያ ዓመት በጋብቻ
ተሳስሮ አንድ ሴትና ሁለት ወንድ ልጆች አፍርቷል።የበአሉ ሚስት እሱን ከማግባቷ በፊት
ባለትዳርና የአምስት ወይ ስድስት ልጆች እናት ነበረች።20 ባሏ አቶ ከበደ ሐይሌ በአዲስ አበባ
ማዘጋጃ ቤት ከፍተኛ ባለሥልጣን ሲሆን አባቱ ሐይሌ አባ መርሳ ስመጥር አርበኛ ነበሩ። አልማዝ
በውበቷ ምክንያት በአርሲ ገዢ ዳንኤል አበበ (የራስ አበበ ዳምጤ ልጅ)21 እስከመጠለፍ ሁሉ
ደርሳለች።ባሏ አቶ ከበደ ለግርማዊነታቸው አቤት ብሎ ነበር ሚስቱን ለማስመለስ የቻለው።
የአልማዝ ወንድም ከበአሉ ጋር በማስታወቂያ ሚኒስቴር ሰርቷል። በወንድሟ ምክንያት በዓሉና
አልማዝ ተዋወቁና "ከባሏ አለያይቶ የራሱ አደረጋት"። ከባሏ ጋር ከተፋታች በኋላ በልጃገረድ ወግ
አገባት።ቅልጥ ያለ ሰርግ ተደግሶ በወግ ማእረግ ተዳሩ። እስከመጨረሻው ድረስ እጅግ የሚቀራረቡ
ጥንዶች ነበሩ።
በአሉ እንደ ጸሐፊስ እንዴት ያለ ነበር? በኦሮማይ ምክንያት ዝናው ጫፍ ደርሷል፤ነገር ግን ስለዚህ
መጽሐፍ እርስ በእርስ የሚቃረኑ አስተያየቶች ተደምጠዋል።ብዙዎች ከዚህ የተሻሉ መጽሐፍት
ቀደም ብሎ እንደፃፈ ያምናሉ። ሌሎች ደግሞ ኦሮማይ ከሁሉም የበለጠ ታላቅ ስራው ነው፤የመፃፍ
404
ጥቋቁር አናብስት
ችሎታው ጣራ የነካበት "እንደ ደራሲ ራሱን ያገኘበት ስራው" ነው ይላሉ።በአፃፃፍ ይሁን በጭብጥ
ቁንጮ ስራው ነው ብለው ይጨምራሉ፦ በመጽሐፉ"ሙሉ ለሙሉ ራሱን ለእውነት አስገዝቷል፤
አላማውንም አሳክቷል"ይላሉ"በገፀ ባህሪይ አሳሳል፣ በልብ ሰቀላ፣ በአፃፃፍ ዘዬ፣ በጭብጥ፣ በጥሩ
አጀማመር እና አጨራረስ"―በአጠቃላይ በሁሉም መስክ ኦሮማይ ታላቅ ስራ ነው። አንድ ጎላ
ብሎ የሚሰማ አስተያየት "በአፃፃፍ ዘዬ፣ በሥነ ጽሑፍ ውበት እና በጭብጦቹ ትልቅነት በአሉን
የሚተካከል አንድም ደራሲ የለም" ይላል። አንዳንድ ሰዎች ከሌሎች የኢትዮጵያ ደራሲዎች ጋር
እንዲህ ያወዳድሩታል፦ ከበደ ሚካኤል ጥሩ ገጣሚ፣ በሳል ተርጓሚ በመሆን የበለጡ ናቸው ፤
ሀዲስ አለማየሁ የበለጡ ነጠላ መጻሕፍትን ጽፈው ሊሆን ይችላል፤ነገር ግን በአጠቃላይ ሲታይ
በአሉ ግርማ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ደራሲዎች ሁሉ ምርጡ ነው፤በአሉ ከአንድ መጽሐፍ ወደ ሌላ
መጽሐፍ እየተካነ የመጣ፣ በመጽሐፉ ላመነበት ነገር ራሱን ያስገዛ፣ በመጨረሻም ለእውነትና
ለመርሁ ሲል ራሱን እስከ ሰማዕትነት ድረስ የሰጠ ነበር።
***
ከዚህ በታች ከሌሎች የቃረምኩትን አንዳንድ መረጃዎች እጨምራለሁ። አንዳንዴ ከሰዎች ወይም
ከጽሑፍ ያገኘኋቸውን መረጃዎች ሲያጎሉ ሌላ ጊዜ ደግሞ በከፊል ይቃረናሉ ወይም ያርማሉ።
በአሉ ግርማ የተወለደው በ1930 ወይም 1931 ዓ.ም ነው። አፉን የፈታው በኦሮምኛ ቋንቋ
ነበር። አስር ዓመት ሲሞላው ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ልእልት ዘነበወርቅ ትምህርት ቤት ገባ።
በዚህ ትምህርት ቤት የአማርኛ መምህሩ የነበሩትን አለቃ ዳዊትን ያደንቅ ነበር።ወንዶችና ሴቶች
ተቀላቅለው የሚማሩበት ትምህርት ቤት ስለነበር ልጃገረዶችን በቀላሉ እና በነፃነት ይግባባል።
የወንዶች ብቻ ወደሆነው ዊንጌት ሲገባ ጥሩ ቤተ መጽሐፍት እና ብቃት ያላቸው መምህራን
ስለገጠሙት በማንበብ ተጠመደ። በዊንጌት አራት ዓመት ከቆየ በኋላ፣ በ1950 አዲስ አበባ
ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ገብቶ ለአራት ዓመታት ማህበራዊ ሳይንስና ጋዜጠኝነት አጥንቶ የመጀመሪያ
ዲግሪውን ተቀበለ።መፃፍ የጀመረው በተማሪነት ዘመኑ ሲሆን፣ ለዩኒቨርስቲ ኮሌጁ መጽሔት
(News and Views) ጽሑፎች ያዋጣ ነበር።ኋላም የመጽሔቱ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሰርቷል።
አብዛኞቹ መጣጥፎቹ ዘመናዊ ሕይወትን ( ለስራ ያለን ግድየለሽነት የመሳሰሉትን ) ይተቻል።
ይህንን ጭብጥ በመጀመሪያ ልብወለዱም ዳስሶታል።
ከዩኒቨርስቲ ኮሌጅ በኋላ በኢትዮጵያ ሬድዮ ሪፖርተር ሆነ። በሰሜን አሜሪካ የፖለቲካ ሳይንስ እና
ጋዜጠኝነት አጥንቷል። ከተመለሰ በኋላ ብዙም ሳይቆይ የመነን ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ እና፤ቀጥሎ
ደግሞ በጊዜው ዝነኛ የነበረው አዲስ ሪፖርተር ዋና አዘጋጅ ሆነ። ነገር ግን በመጽሔቱብዙ "ለውጥ
405
ጥቋቁር አናብስት
በአሉ ግርማ ከሚወዳቸውና ተጽእኖ ካሳረፉበት ደራሲያን መሐል ሄሚንግዌይ፣ ግራሃም ግሪን፣
ዶስቶቭስኪ ሲገኙበት የዳኒሽ ተወላጁን እና ፈላስፋውን ሶረን ኪርክጋርድንም ያደንቀው ነበር።
የተርጓሚው ማስታወሻ
ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ “በዓሉ ግርማ ሕይወቱና ስራዎቹ ”መሰለ የእንጀራ አባቱ ልጅ እንደሆነ፤
እሱ ብቻም ሳይሆን ሌሎች የእንጀራ አባት ልጆች እንደነበሩ፤ በግርማ ስም መጠቀሳቸውን ፤ግርማ
የያኔ ሁለተኛ ባል ስለመሆኑ የተጻፈውን ፈጽሞ ሐሰትና የተሳሳተ መረጃ ነው ሲሉን በአሉ ከእናቱ
የሚወለዱ ወንድምም እህትም እንደሌለው እናቱም ከህንዳዊ ባላቸው ሲለያዩ ያገቡት አበበን እንጂ
ግርማን ያለመሆኑን ጽፈዋል፡፡(ገጽ23)
ማስታወሻዎች
1) አንዱ ምንጭ ወደ አዲስ አበባ በአስር ዓመቱ መጥቶ የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በዘነበወርቅ
ተከታትሎ እንደጨረሰ ይናገራል።
4) ይሁን እንጂ ስለ በአሉ ግርማ መረጃ በማሰባስብበት ወቅት በዓሉ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ፓርቲ
ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ነበር።
406
ጥቋቁር አናብስት
5) "የቀይ ኮከብ ጥሪ" የተሰኘው የበአሉ መጽሀፍ ውስጥ ከማስታወቂያ ሚኒስትር ባልደረቦቹ ጋር
ጌታቸው የሸዋሉል በሚል ስም ሰካራም እና የነቀዘ “ብልሹ ገፀባህሪ” ሆኖ ተቀርፇል። በአሉ
ለልብወለዶቹ ሰዎችን፣ ቦታዎችን እና ድርጊቶችን ከሕይወት ልምዱና ከአካባቢው መውሰዱ
የሚታወቅበት ባህሪ ነው።
6) ይህን መረጃ ያገኘሁት ለበአሉ ቅርብ ከነበሩ ሰዎች ነው። ይሁን እንጂ፣ ግርማ ይልማ ሀቀኛ እና
እንደተፈለገ የሚጠመዘዝ ሰው እንዳልሆነ ሁሉም ይስማማሉ።
8) ሁሌም ሳየው ሰማያዊውን የኢትዮጵያ ሰራተኞች ፓርቲ ካኪ ዩኒፎርም ለብሶ ነው። አብዛኛዎቹ
ፓርቲውን የተቀላቀሉት ከስራ እንዳይባረሩ “ተገድደው” ነው። የፓርቲው ዩኒፎርም የተስማማው
ይመስላል።
407
ጥቋቁር አናብስት
መቅረብ የሚችለው። አንዳንዴ ረቂቁ ተቀባይነት አግኝቶ መጽሀፉ ከታተመ በኋላ ሳንሱረኞቹ
ሀሳባቸውን በመለወጣቸውመጽሐፉ ለገበያእንዳይቀርብ የሚታገድበት ጊዜ አለ ፤ ኪሳራው ሙሉ
በሙሉ የአሳታሚዎች ነው።
13) ከዚህ በኋላ ብዙም ሳይቆይ፣ ተቃውሞ ያነሳው አባል በ"ኦሮማይ" ጉዳይ በተፈጠረው
አለመግባባት ከቦርድ አባልነቱ ራሱን አግልሏል።
14) የቀሩት የ"ኦሮማይ" ቅጂዎች በወንጂ ስኳር ፋብሪካ ተቆራርጠውተፈጩ። እነዚህን ቅጂዎች
ማሰባሰቡና ወደ ወንጂ የመላኩ ሂደት የቀሩ ወይም የተደበቁ ቅጂዎች እንዳይኖሩጥብቅ የደህንነት
ቁጥጥር ተደርጎበታ ይሁን እንጂ መርካቶ አካባቢ መጽሀፉን ማግኘት ችዬ ነበር ፤ በእርግጥ ውድ
ዋጋ (50 ብር) መክፈል ነበረብኝ። ከዚያ በፊትናይሮቢእያለሁፎቶኮፒውን አግኝቼ እኔም ለራሴ
ፎቶኮፒ ለማድረግ ችዬ ነበር። መጽሀፉን ከልባቸው ማንበብ ለፈለጉ፣ ቅጂዎችን ማግኘት ያን ያህል
ከባድ አልነበረም።
16) በ"ኦሮማይ" ውስጥ መንግስቱ የተፃፈላቸውን ከሚያነቡ ይልቅ በራሳቸው ንግግር ሲያደርጉ
እንደሚሻሉ የጠቀሰው ሳያስቆጣቸው እንዳልቀረ አንዳንዶች ይናገራሉ። ይሄ መንግሥቱ ማንበብ
አይችልም ወይም በደንብ አልተማረም የሚል ድብቅ ስድብ የያዘ ነው ይላሉ። ይህ እውነት ከሆነ
መንግስቱ ለበአሉ የሚያደርጉለትን ጥበቃ ለማቆም በቂ ምክንያት ይሆናቸዋል።
18) አብዮቱ በ66 ከፈነዳ በኋላ ሁሌም አደጋ ውስጥ እንደነበር ሳያውቅ አይቀርም። ለምሳሌ
በአብዮቱ የመጀመሪያ ዓመታት መኢሶን “ስልጣን በነበረው” ወቅት በማስታወቂያ ሚኒስትር
ውስጥ ሊያጠፋቸው ከሚፈልጋቸው ከ30 ከሚበልጡ ሰዎች መሐከል በ3ተኛ ተራ ቁጥር ላይ
ስሙ ሰፍሮ እንደነበር በቂ መረጃየነበራቸው ሰዎች ይናገራሉ።
408
ጥቋቁር አናብስት
19) በ1979 አንድ የቀበሌ ታጣቂ በአሉ በእነሱ ቀበሌ ውስጥ እንደተገደለ ማውራቱን የሰማ ሰው
ነገረኝ( በ1987 በደርግ ባለስልጣኖች ላይ የቀረበ ክስ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ይመስላል።)
21) የተነገረኝ እንደዛ ነው። ነገር ግን ዳንኤል አበበ የራስ አበበ አረጋይ ልጅ ሳይሆን አይቀርም።(
ደጃዝማች አበበ ዳምጠው የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ የመጀመሪያ ልጅ የነበሩት የልዕልት ተናኘወርቅ
የመጀመሪያ ባል የራስ ደስታ ዳምጠው ወንድም ነበሩ)
409
ጥቋቁር አናብስት
ከበደሚካኤል
የአማርኛ ስነፅሁፍ ታላቁ ሰው ከበደሚካኤልን ለበርካታ ጊዜ
ባገኛቸውም በዚያ ላይ ብቻ ተመስርቼ ግን ታሪካቸውን ማስቀመጥ
አልወደድኩም፡፡ጓደኞቼን ቃለመጠይቅ ላደርግላቸው እፈልጋለሁ
ስላቸው ተስፋ አስቆርጠውኝ ነበር፡፡“አእምሯቸው በጥሩ ሁኔታ ላይ
አይደለም የማያውቁትን ጠያቂ እንኳን በጥሩ መንፈስ አይቀበሉም ፤
ነገር ግን ለውጭ ሃገር እንግዶችያላቸው ጥርጣሬ እንደሃበሾቹ
አይደለም”ሲሉ ትንሽ የተስፋ ጭላንጭል ፈነጠቁልኝ፡፡ አማረ ማሞ የግጥም መድበል ማዘጋጀት
ፈልጎ የሳቸውን ግጥም ለማካተት ሊጠይቃቸው ቤታቸው በሄደበት (የደርግ ሰላይ ነህ)ብለው በሩን
ፊቱ ላይ ደርግመውበታል፡፡
በ1978 መባቻ አንድ እሁድ ጠዋት ነው ከበደን ለማየት የሄድኩት፡፡እስኪገርመኝ ድረስ በሞቀ
አቀባበል አውራሪስ ሆቴል ወደነበረው ክፍላቸው እንድገባ በመጋበዝ ነበር የተቀበሉኝ፡፡የሚኖሩት
በዋናው ህንጻ ሆኖ በላይኛው ፎቅ አንድ ሰፊ ክፍል ውስጥ እንደማረፊያና እንደ እንግዳ ቤት
ይገለገሉበት ነበር፡፡ የግል መጸዳጃና መታጠቢያ የሆኑ ከጎን የተያያዙ አንድ ወይም ሁለት ክፍሎች
አሉ፡ ዋናው ክፍል በመጻሕፍትና በሻንጣዎች የተጨናነቀ ነበር፡፡ከበደ በጋወን ሲሆኑ ግዜው ቀትር
አካባቢ ቢደርስም አልጋው አልተነጠፈም፡፡ትኩስ ፍራፍሬ በትሪ ሆኖ ከአልጋው አጠገብ
ተቀምጦላቸዋል፡፡አንድ ያልተማረ የሚመስል ትንሽ ሰው ብቅ እያለ ትእዛዛቸውን ይቀበላል፡፡ከዚያ
410
ጥቋቁር አናብስት
በአንድ የግንኙነታችን ወቅት ግጥም በልጅነታቸው ለሳቸው በጣም ጠቃሚ እንደነበር አሁን ግን
በተውኔት ላይ የበለጠ ፍቅር እያሳደሩ መምጣታቸውን ነገሩኝ፡፡ኢትዮጵያውያን አንባቢዎች
የከበደን “ግጥሞች” “አቻ የለሽ” ሲሉ ያወድሷቸዋል፡፡ግጥምን በትምህርተ ጥቅስ ያስቀመጥኩበት
መክንያት ሁሉም ሰዎች ተውኔቶቻውን እንደ ግጥሞቻው አካል ስለሚቆጥሩት ነው፡፡ሁሉም
412
ጥቋቁር አናብስት
***
የማውቃቸው በድርሰቱ አለም ውስጥ ያሉም የሌሉም ኢትዮጵያውያን የከበደን የፈጠራ ስራዎች
ልቅም አድርገው ያውቋቸዋል፡፡በርካታ ጸኃፍት የሳቸው ተጽዕኖ እንዳደረባቸው ይናገራሉ፡፡ሁሉም
ወደ ትምህርት ቤት ከጣልያን ወረራ በኋላ የገቡ ልጆች ከስራዎቻቸው አንዱን ሳያነቡ አይቀሩም፡፡
የከበደን ግጥሞች በቃላቸው ተወጥተው እርስ በእርስ ይደጋገሙ እንደነበር ያጫወቱኝ ሰዎች አሉ፡፡
ወደ ኋላ ዘመናቸው አብዮታዊ የነበሩ አንዳንዶች ሳይቀሩ በከበደ ግጥሞች ውስጥ ባሉ ሃገራዊ
413
ጥቋቁር አናብስት
በ1970ቹ ሁለተኛ አጋማሽ ከበደ ሚካኤል በአዲስ አበባ መንገዶች ላይ ሲዘዋወሩ ይታዩ ነበር፡፡
በተለይ በፒያሳ አካባቢ ሁሌም እንደባላባት በደንብ ለብሰው ጥቁር መለዮና ካፖርት ደርበው ትንሽ
ሳምሶናይት ይዘው ነበር የሚወጡት፡፡አጭርና በዝግታ የሚጓዙ ቢሆንም ቀጥ ብለው በኩራት ነበር
የሚያዘግሙት ፡፡ፈገግ ሲሉ አይቻቸው አላውቅም::ቢሉ እንኳ ከሳቸው የማይጠበቅ እንግዳ ነገር
ይመስለኛል፡፡ እንደ እደሜያቸው ሳይሆን ገና ይመስላሉ፡፡መጀመርያ ያየሁዋቸው ጊዜ ከልጅነት
ፎቶዋቸው ጋር ያላቸው መመሳሰል ያስገርም ነበር፡፡በራሳቸው የሚተማመኑ ስለእራሳቸው ብቻ
የሚያስቡና አንዳንዴም ግትር ሰው እንደ ሆኑ ነው የኋላ ኋላ የተሰማኝ፡፡አንድ የካቶሊክ ቄስ
አዘወትሮ እንደሚጎበኛቸው ተነግሮኛል፡፡
ከበደ ሚካኤል በርካታ ሰዎችን በህይወት አጋጣሚ አስከፍተዋል፡፡ስለወታደራዊው መንግስት
በግልጽ የተቃውሞ ንግግር በማድረጋቸው ለ6 ወራትም ታስረው ነበር፡፡በተቃራኒው በብዙዎች
የሚከበሩ ብዙዎችም ሊያግዟቸው የሚፈልጉ ሲሆን ከብዶ የሚታያቸው ግን ተቀራርቦ ግላዊ
ግንኙነት መፍጠሩ ነው፡፡አንዳንድ ደራሲዎች ልዩው ደራሲያችን ለሚሏቸው ለእኚህ ሰው (የተለየ
ነገርን ለማድረግ )እየተነጋገሩ ይገኛሉ፡፡
***
የከበደን ምስል ክሱት ለማድረግ የሚያስችል በቂ መረጃ ባለማግኘቴ ከሌሎች ጥናት ያገኘሁትን
ጨምሬ አቀርባለሁ፡፡
በመስከረም 1973 ዓ.ም ለየካቲት መጽሄት የተጻፈ አንድ መጣጥፍ ከበደ 65 አመታቸው
መሆኑን ይናገራል፡፡ይሄ ትክክል ከሆነ የተወለዱት በ1908 ነው ማለት ነው፡፡ቅዳሴን ለመማር ወደ
ቤተክህነት ትምህርት ቤት ነው በመጀመርያ ያቀኑት፡፡ቆይተው ፈረንሳይኛ ጣልያንኛና እንግሊዘኛን
ያጠኑ ሲሆን በስነ ግጥምና በተውኔት ድርሰት አጻጻፍ ላይ ግን ዘመናዊ ትምህርትን አልቀሰሙም፡፡
የቅኔ ትምህርቱ ግን ያለጥርጥር ተጽእኖ አሳድሮባቸዋል፡፡ዋነኛ መምህሮቼ የሚሏቸው ደጋግመው
ያነበቧቸው ከ3000 በላይ መጻሕፍት ናቸው ይላሉ፡፡
አብዛኛው ህብረተሰብ ስለ ከበደ ሚካኤል የግል ህይወት የሚያውቀው ነገር ውሱን ነው፡፡
በጽሁፎቻቸው መቅድም ላይ ባሉት ጥቂት ቃላትም ተንተርሶ፡ ብዙሃኑ ከጽሁፎቻቸው ሌላ
ስለሳቸው የሚያወቀው ቁንጽል ነው፡፡ሆኖም በ1975 ወይም 76 አስፋው አጽማት የተባለ ተማሪ
414
ጥቋቁር አናብስት
----
ከበደ ሚካኤል ለአስፋው እንደነገሩት ከሆነ የተወለዱት በ1907 ህዳር ነው፡፡አንኮበር ከተማ፡፡
የአባታቸው ስም አይታገድ ሲሆን የእናታቸው ደግሞ አጸደ ሚካኤል ነው፡፡በጽድአምባ ግዮርጊስ
ክርስትና የተነሱ ሲሆን ስመ ክርስትናቸው ቀጸላ ግዮርጊስ ነው፡፡ከበደ ተወልደው ብዙም ሳይቆዩ
አባታቸው እናታቸውን ጥለው ስለሄዱ ከበደ አባታቸውን አይተው አያውቁም ፡፡ለዛም ነው
በተለመደው መልክ ሳይሆን የእናታቸውን አባት ስም ለመጠርያነት የወሰዱት፡፡ከበደ
ትምህርታቸውን በአራት አመታቸው ሲጀምሩ ከሴት አያታቸው ጋር ነበር የሚኖሩት፡፡አያታቸው
የጣራውዷ ወይዘሮ ወለተ ገብርኤል ይሰኛሉ ፡፡ከአለቃ ተክለ ግዮርጊስ ስር በወንድ ሃያታቸው
ደጃች መኩርያ በተተከለው ገርብ ገብርኤል ነበር ዳዊት የደገሙት፡፡ግዕዝንም በደንብ
አስተምረውኛል ይላሉ፡፡
415
ጥቋቁር አናብስት
በጣልያን ወረራ ወቅት ለጣልያኖቹ የስርጭት ሰራተኛ የነበሩ መሆኑን ግን አንስተው አያውቁም፡፡
ተገደው ይሁን ወደው ያደረጉት እንደሆንም አይታወቅም፡፡
416
ጥቋቁር አናብስት
የተርጓሚ ማስታወሻ -ክቡር ዶክተር ከበደ ሚካኤል በጥቅምት 26 ቀን 1990 የክብር ዶክትሬት
ማዕረግ ሲበረከትላቸው ህዳር 3 1991 አርፈዋል፡፡ከመጻሕፍቶቻቸው መሃል የእውቀት
ብልጭታ፤ የመጀመርያ እርምጃ፤ታሪክና ምሳሌ፤ታላላቅ ሰዎች፤የኣለም ታሪክ፤ብርሃነ ሕሊና፤የቅኔ
አዝመራ፤ የቅኔ ውበት፤ጃፓን እንዴት ሰለጠነች፤የትንቢት ቀጠሮ፤አኒባል፤በላይነህ(የቅጣት
ማእበል)፤ ካሌብ፤ አክዐብ፤ቅዱስ ገብርኤል በምድረ ገነት እና የመሳሰሉት ሲገኙ ከእረፍታቸው
በኋላም ለህትመት የበቁ በርካታ ስራዎች አሉ፡፡
ማስታወሻ
4)በሆቴሉ የሚሰሩ ሰዎች እንደነገሩኝ ከሆነ አንዳንዴ በንዴት ብው የሚሉበት ወቅቶች አሉ፡፡
ይህንን ለመመስከር ባልበቃም አንዳንዴ ባህርያቸው ላይ አንድ ጥላ ሲያጠላ ይታየኝ ነበር፡፡
417
ጥቋቁር አናብስት
7.አንድ ጠቃሚ የምእራባውያን ነጥብ ክስተቶችን በተውኔት መሃል መፍጠር ሲሆን ቀደምት
የኢትዮጵያና የአፍሪካ ስራዎች ግን ይህ ያጥራቸው ነበር፡፡ኢትዮጵያውያን ምንአልባትም ህይወትን
እንደማትለወጥ ድንገቴ ክስተት የሌላት አድርገው ያዩዋት ይሆናል፡፡በዚህ ማህበረሰብ ውስጥ
ታድያ እንዴት ነው የምእራባውያን ተጽእኖ ሊያርፍ የሚችለው?የኢትዮጵያና የተቀረው የአፍሪካ
ጸሃፊዎችም ችግራቸውን በራሳቸው እንዲፈቱት መተዉ የተሻለ ነው፡፡
418