Professional Documents
Culture Documents
የቁርኣኑ_ዒሳ_የመጽሐፍ_ቅዱሱ_ኢየሱስ_አይደለም
የቁርኣኑ_ዒሳ_የመጽሐፍ_ቅዱሱ_ኢየሱስ_አይደለም
1
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
2
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ማውጫ
ርእስ፤ ገጽ
መግቢያ፤ 3
የመንደርደሪያ ጥቂት ነጥቦች፤ 5
ቃሉ ተበረዘ? ተከለሰ? ተለወጠ? 7
ኢየሱስ ፍጡር ነው ወይ? 13
ኢየሱስ ከሥላሴ አካላት በሥጋ የመጣው ነው፤ 20
‘ሰውየው ብቻ ዒሳ’ እና ሰው የሆነው ኢየሱስ አሥራ ሁለት ነጥቦች፤ 32
የመስቀል ሞቱ፤ 73
የመስቀል ሞት ምንድር ነው? 91
ጌትነት፥ ሞና ትንሣኤ፤ 92
የትንሣኤው ምስክሮች፤ 93
የመስቀሉ ሞት ምንነት፤ 104
የእርግጠኛነታችን መሠረት፤ 105
መስቀሉ ከአራት ማዕዘናት ሲታይ፤ 107
መደምደሚያ፤ 124
ዋቢ መጻሕፍት፤ 127
3
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
መግቢያ
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም፤ ከቶም አይደለም። የቁርኣኑ ዒሳ
ከስሙ ጀምሮ፥ ሥራውም፥ ማንነቱም የመጽሐፍ ቅዱሱ ክርስቶስ አይደለም።
በመጽሐፉ ገጾች ውስጥ ይህንን በዝርዝር እንመለከተዋለን።
ከጥቂት ዓመታት በፊት ሳዲቅ መሐመድ፥ ‘ዒሳ በቁርኣንና በወንጌል’ በሚል ርእስ ስር
29 ክፍሎች ያሉት የስሕተት ትምህርት አሰራጭቶ ነበር። ጠቅላላው ስርጭት ከ6
ሰዓት በላይ የሆነ፥ የቁርኣኑ ዒሳ ትክክለኛው ኢየሱስ፥ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ
ደግሞ የሰዎች ፈጠራ መሆኑን ለማሳየት አስልቶ ያቀረበው የማደናገርና የስሕተት
ትምህርት ነው። እንደ ሌሎቹ የእስልምና ምካቴ እምነት ሰዎች ግቡ ሁለት ነው።
አንዱ፥ ሙስሊሞችን በአለማወቅ ጭጋግ ውስጥ ማቆየት ሲሁን ሁለተኛው
ክርስቲያኖችን ደግሞ ማደናገርና ስለ እምነታቸው ጥያቄ እንዲፈጠርባቸው ማድረግ
ነው። አንዳንድ ሰዎች ከቃሉ ያልተማሩትን ነገር ያስተምራሉ፤ ሲያስተምሩም
በድፍረት ነው። ስለማያውቁት ነገር ይናገራሉ፤ ሲናገሩም በግለት ነው። የሳዲቅ
መሐመድ መሠረታዊው ስሕተት እርሱ ዒሳ የሚለው ሰው፥ ያ ሰው የአዲስ ኪዳኑ
ኢየሱስ አለመሆኑን አለማወቁ ነው። ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ በሥጋ መጥቶ
አገልግሎ፥ ሞቶ፥ ከሙታን ተነሥቶ ወደ አብ ካረገ ከ600 በላይ ዓመታት ቆይቶ
የተፈጠረ ፍጡር ነው።
1
በቪድዮ የተሰራጩት ስምንት ክፍሎች እዚህ ይገኛሉ።
ክፍል አንድ፥ https://www.youtube.com/watch?v=twW-MZuZeNI
ክፍል ሁለት፥ https://www.youtube.com/watch?v=HZgjZ_s3fXc&t=1349s
ክፍል ሦስት፥ https://www.youtube.com/watch?v=hTKfnwfi3DI&t=337s
ክፍል አራት፥ https://www.youtube.com/watch?v=_GvH_2c-BXA&t=1502s
ክፍል አምስት፥ https://www.youtube.com/watch?v=snTkz5u4fn0&t=970s
ክፍል ስድስት፥ https://www.youtube.com/watch?v=FZkJcxHaY2A&t=1s
ክፍል ሰባት፥ https://www.youtube.com/watch?v=5bZbVbTADr0&t=2599s
ክፍል ስምንት፥ https://www.youtube.com/watch?v=cyRcEYwhrsE&t=483s
4
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
በንባቡ ውስጥ ስለ መጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ ያለን መረዳት ይበልጥ ግልጽ እንደሚሆን
እና ሙስሊሞችም ይህንን በሥጋ የተገለጠውን ኢየሱስ በእውነት ይረዱትና ያውቁት፥
ይቀበሉትና ይድኑበትም ዘንድ በመመኘት አበረክታለሁ።
ዘላለም መንግሥቱ።
5
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
6
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
7
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
መጽሐፍ ቅዱስ ተበርዟል፥ ተከልሷል የሚሉ ሰዎች ይህንን የሚሉት የነሱ መጽሐፍ
ከዚህ መጽሐፍ ጋር ሲጋጭ፥ እሱን ትክክል፥ ይህንን ስሕተት ለማድረግ ከመፈለግ
የተነሣ ብቻ ነው እንጂ የተበረዘ መሆኑን ለማሳየት፥ ‘ይኸው ኦርጅናሌው የሚለው
እንዲህ ነው፤ እናንተ እጅ ያለው መጽሐፍ የሚለው ደግሞ እንዲህ ነው።’ በማለት
አይደለም። እንዲህ ማለት የጀመሩት መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ሳይሆን ቁርኣንም ጭምር
ተጽፎ ከተጠናቀቀ በብዙ መቶ ዓመታት በኋላ፥ ለትልልቅ ጥያቄዎች፥ ለትልልቅ
የመጽሐፍ ቅዱስ እና የቁርኣን ልዩነቶች፥ መጽሐፍ ቅዱስ በሚናገርባቸው ጉልህና
ግልጽ ጠያቂ ጉዳዮች መልስ ሲያጡ፥ ‘ይህ በእጃችሁ ያለው የተበረዘው ነው።
የቀድሞው ኦርጅናሌው ቢኖር ኖሮ የሚለው እንደዚህ፥ ልክ እንደ ቁርኣኑ ነው፤’
ይሉናል።
8
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
3፥3-4 ከርሱ በፊት ያሉትን መጻሕፍት የሚያረጋግጥ ሲኾን መጽሐፉን (ቁርአንን) ባንተ ላይ
ከፋፍሎ በውነት አወረደ። ተውራትንና ኢንጂልንም አውርዷል።
ለመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ ከመጽሐፍ ቅዱስ ይልቅ ከራሱ ከቁርኣኑ መጥቀስ የተገባ
ስለሆነ ነው ከቁርኣኑ የጠቀስኩት። አንድ ሁለት ልጨምር፤ በሱረቱ ዩኑስ (ሱራ
ወይም ምዕራፍ 10) ቁጥር 94-95 የተጻፈው በዚያን ጊዜ በእጃቸው የነበረው ወይም
አይሁድና ክርስቲያኖች ያነብቡት የነበረው መጽሐፍ የጥርጣሬያቸው ማስወገጃ
መጽሐፍ መሆኑን የሚናገር ክፍል ነው።
9
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ይህን በተመለከተ አንድ ሁለት የመጨረሻ ላክል፤ እነዚህ እንዲያውም ሰዎቹ መጽሐፍ
የተሰጡ ወይም የተሰጣቸው መሆናቸውን ብቻ ሳይሆን፥ ቃላቶቹ የማይለወጡና
ለዋጭ የሌላቸው መሆናቸውን የሚመሰክሩ ናቸው፤
10
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
አንድ ጽሑፍ ተበረዘ ወይም ተቀየጠ ለማለት ዋናው ማረጋገጫ ከጽሑፉ በኋላ
የተፈጠረ ጥያቄ፥ ወይም ጥርጥር፥ ወይም ለሙግት መልስ ማጣት፥ ወይም ስሕተትን
ለመሸፈን መሞከር፥ ወይም ሌላ የግምትና የመላ ምት ድኩም ማጣጣያ ሳይሆን ወደ
ኋላ የተጓዘና፥ ‘አልተበረዘም’ የሚሉትን ሰዎች አፍ ማስያዝ የሚችል የምንጭ ሰነድ
በማቅረብ ነው መሆን ያለበት። መጽሐፍ ቅዱስ ተበረዘ የሚሉ ሰዎች የተበረዘ
መሆኑን ለማሳየት እጅግ ብዙ መልፋት የሚጠበቅባቸው መሆኑን ባለማወቅ ነው
2 Plummer p. 48.
11
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
12
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
እውነት ኢየሱስ ሰው የሆነ ወይም በሥጋ የመጣ አምላክ ነው ወይስ ሰው ብቻ? እርሱ
ፍጡር ነው ወይስ ፈጣሪ? ሳዲቅ ኢየሱስን ደጋግሞ ፍጡር እና ፍጥረት በማለት
ተናግሯል። ሌሎችም የሚሉት ያንኑ ነው። ይህ ስሕተት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ
ኢየሱስ ፍጡር ወይም ፍጥረት መሆኑን አንዴም አይጠቅስም። ፍጡር ማለት
ያልነበረና ወደ መኖር በሌላው፥ በፈጠረው አማካይነት የመጣ ማለት ነው። አንድም
ቦታ እርሱ የተፈጠረ ፍጡር ወይም ካለመኖር ወደ መኖር የመጣ መሆኑን መጽሐፍ
ቅዱስ አይናገርም። ኢየሱስ ፍጡር መሆኑ በቃሉ፥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከቶም
አይገኝም። ፈጣሪ መሆኑ ደግሞ በግልጽ እና በተደጋጋሚ ተጽፏል። ስለዚህ ኢየሱስ
ፈጣሪ እንጂ ፍጡር አይደለም። ፈጣሪ ደግሞ ፍጡር መሆን አይችልም። ምክንያቱም
እርሱ እራሱን መፍጠር አይችልምና። አንዳንድ የስሕተት አስተማሪዎች እግዚአብሔር
መጀመሪያ ኢየሱስን ፈጥሮ ከዚያ ኢየሱስ ሌሎቹን ነገሮች ሁሉ ፈጠረ የሚሉ አሉ።
ይህም የጨለመበት ስሕተት ነው።
13
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ቀደም ሲል ካነሳኋቸው ነጥቦች አንዱ መጽሐፍ ቅዱስ ከቁርኣን ቀድሞ የተጻፈ ሰነድ
ብቻ ሳይሆን ወንጌላት ኢየሱስን በቅርብ በሚያውቁ አብረውት በነበሩ እና፥
አብረውት ከነበሩት ሰዎች ጋር አብረው በነበሩ ሰዎች የተጻፉ ታሪኮች፥ የተጻፉ ዜና
ሕይወቶች ናቸው። ስለ ኢየሱስ ማወቅ የሚፈልግ ማንም ሰው መሄድ ያለበት በግልጽ
እንደሚታወቀው የሚያውቁት ሰዎች ወደ ጻፉት እንጂ ከብዙ መቶ ዓመታት በኋላ
እርሱን የማያውቀው፥ የስሚ ስሚ ስለ እርሱ ያወቀ ሰው ወደ ተናገረውና ያንን
የተናገረውን ሰምተው ሌሎች ወደጻፉት መጽሐፍ አይደለም።
ዕብ. 1፥1-3 ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን
በነቢያት ተናግሮ፥ ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ
በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፤ እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ
4 https://www.youtube.com/watch?v=0gOcq-Mh0bo
14
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
እነዚህ ከብዙ ጥቂት ጥቅሶች ናቸው። እነዚህ የሚያሳዩን ኢየሱስ ፈጣሪ እንጂ ፍጡር
አለመሆኑን ነው። ኢየሱስ ሰው ነው፤ ሰው ከሆነ ታዲያ እንዴት ነው ፍጡር
የማይሆነው? ሊባል ይችላል። ይህን በሌላ ክፍል እናነሣዋለን። በአጭሩ ግን ኢየሱስ
ሰው ብቻ ሳይሆን ሥጋ የለበሰ አምላክ ነው። አምላክ ነው፤ በአምላክነቱ ላይ ሥጋን
ወሰደ ወይም በሥጋ መጣ። የመጣው ደግሞ ለአንድ ዓላማ ነው። ያንንም
እንመለከታለን። እዚህ ግን ፍጡር አለመሆኑን ለማመልከት መጽሐፍ ቅዱስ አንድም
ስፍራ ኢየሱስን ፍጡር አለማለቱንና ደጋግሞ ግን ፈጣሪ መሆኑን መግለጡን ማየቱ
በቂ ነው።
15
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
16
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
የቃል ማንነት ወይም መለኮትነት የሚታየው በሥላሴ ማንነት ውስጥ ነው። እዚህ ላይ
ነገረ ሥላሴን በሌላ ስፍራ የምናየው ቢሆንም ሳዲቅ ራሱም፥ ዮሐ. 1፥1-2ን በመጥቀስ
ሁለት እግዚአብሔር ነው ወይ? የሚል ጥያቄ አቅርቧል። ‘ቃል እግዚአብሔር ዘንድ
ነበረ ብሎ ቃልም እግዚአብሔር ነው ካለ እግዚአብሔር ዘንድ ሌላ እግዚአብሔር አለ
ማለት ነው?’ ብሎአል። በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት፥ እግዚአብሔር ሥላሴ ነው።
እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ሆኖ ሦስት አካላት የሆነ እግዚአብሔር ነው። አብ፥
ወልድ፥ መንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ።
17
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
(የሁን) የሚለው በቅንፍ ውስጥ መሆኑ የተጨመረ መሆኑ ገላጭ ነው። እዚያ
ዘፍጥረት ውስጥ ይሁን የተባለውና የሆነው ብርሃን ነው። ይሁን ተባለና ሆነ። እዚህ
ግን ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው እና እግዚአብሔር የሆነው ቃል ራሱ ነው ሥጋ
የሆነውና በሥጋ የመጣው።
18
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ይህንን የቃልን ሥጋነት ክፍል ስደመድም አንድ ጥያቄ ልጠይቅ። ይህ ጥያቄ የውይይት
ጥያቄም ሊሆን ይችላል። ጥያቄውም፥ እግዚአብሔር ቢፈልግ የፈለገውን፥ የወደደውን
መሆን ይችላል ወይስ አይችልም? የወደደውን ሊያደርግ ብቻ ሳይሆን የፈለገውን
ሊሆንም ሥልጣን አለው ወይስ የለውም? እርሱ ያሻውን መሆን ይችላል? ወይስ እኛ
የገደብንለትን ሥልጣን ማለፍ የማይችል አምላክ ነው? ለምሳሌ፥ እግዚአብሔር ሰው
ልሁን ቢል፥ ሥጋ ልልበስ ቢል ይችላል ወይስ አይችልም?
19
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
20
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
5፥73 እነዚያ አላህ የሦስት ሦስተኛ ነው (1) ያሉ በእርግጥ ካዱ፤ ከአምላክም አንድ
አምላክ እንጅ ሌላ የለም፤ ከሚሉትም ነገር ባይከለከሉ፣ ከነሱ እነዚያን የካዱትን አሳማሚ
ቅጣት በእርግጥ ይነካቸዋል። [የግርጌ ማስታወሻ 1፥ ከሦስት አማልክት አንዱ ነው ያሉ፤
በሥላሴ የሚያምኑ።]
21
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
የሚለው ይህንን ጥቃት አመልካች ነው። በነገራችን ላይ፥ ቁርኣን ሁለት ምድቦች
አሉት፤ አንዱ መኪያ ይባላል እንደዚህ የሚባሉት የመካ ሱራዎች ናቸው። ሁለተኛው
መዲኒያ ይባላል በመዲና የተነገሩ ናቸው። መኪያዎች የኢስላም ነቢይ ሙሐመድ
በመጀመሪያዎቹ ዓመታት በመካ ሲኖር የተናገራቸው ሱራዎች ናቸው። ቁርኣን እንደ
መጽሐፍ ቅዱስ በጊዜ ቅደም ተከተል የተጻፉ ሱራዎች ወይም ምዕራፎች ስብስብ
ስላልሆ ሱራዎቹ ተሰባጥረው ነው የሚገኙት። ስብጥሩ ከትልልቅ ሱራዎች ወደ
ትንንሽ ነው። ከጠቅላላው 114 ሱራዎች 75% መኪያዎች ወይም የመካ ሱራዎች
ሆነው 25% መዲኒያዎች ወይም የመዲና ሱራዎች ናቸው። የመዲና ሱራዎች ከሂጅራ
ወይም ከመካው ስደት በኋላ በመዲና የተነገሩ ናቸው። እነዚህ የመዲና ሱራዎች
አጥላይነትና አግላይነት፥ እንዲሁም የአጥቂነትና የወራሪነት ስሜት የሚገለጥባቸው
ወይም የተገለጠባቸው ናቸው። ለምሳሌ ከመጀመሪያዎቹ 9 ሱራዎች ውስጥ 6ቱ
የመዲና ሱራዎች ናቸው። በነዚህ በስድስቱ ውስጥ ብቻ 110 በላይ የአጥቂነት ወይም
የጂሃድ ጥቅሶች ወይም አያዎች ይገኛሉ። ከሱራዎቹ ሁሉ በቅደም ተከተል
የመጨረሻው ሱራ ሱረቱል-ተውባህ የተባለው (ምዕራፍ 9) ሲሆን ይህ ሱራ
አጋሪዎችን ሁሉ ባገኛችሁባቸው ስፍራ ግደሏቸው የሚለው ያለበት ነው።
22
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
በዚህ አካሄድ የመካ ሱራዎች በቀላሉ የመዲና ሱራዎችን ይተካሉ ማለት ነው።
ለምሳሌ፥ የቀደመውን በመካው ሱራ፥ ‘በሃይማኖት ማስገደድ የለም።’ የሚለውን (2፥
256) ወይም በ109፥6 ‘ለናንተ ሃይማኖታችሁ አላችሁ፤ ለኔም ሃይማኖቴ አለኝ።’
የሚለውን ምንም ማስፈራሪያ የሌለበትን የመካ ስብከት ይህኛው ከላይ ያየነው የሱራ
9 ቃል ይሽረዋል ማለት ነው። ይህ የመሻር ድንጋጌ የኋለኞቹን ትክክለኛ
ያደርጋቸዋል። አንቀጽን በአንቀጽ መለወጥ ይባላል፤ (2፥106፤ 16፥101)። ይህ የመሻር
ሕግ ራሱን ቁርኣንን ራሱን ያስተካከለ ወይም ያሻሻለ አድርጎ ስለሚያቀርበው
ዘላለማዊ የአለመሆኑ አንድ ውስጣዊ አስረጅ ነው።
23
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
24
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ኢየሱስ ከአብ ጋር እኩልና ያልተናነሰ አምላክ ነው። መንፈስ ቅዱስም ከአብና ወልድ
ጋር እኩልና ያልተናነሰ አምላክ ነው። ሥላሴ የአኀዝ ብዝኀነት ሳይሆን የአሐድ ማንነት
መግለጫ ቃል ነው። ቁጥርን ብቻ ሳይሆን፥ የአካል ቁጥር እንደተጠበቀ ሆኖ፥ ከቁጥር
በላይና ከቁጥር ይልቅ ማንነትን ገላጭ አሳብ ነው።
25
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ነቢል ይህ እርስ በራስ የሚጣረስ ስለመሆኑ ለማሳየት ከአላህ ስሞች ሁለቱን ለምሳሌ
ያወሳል፤ አርራሕማን እና አርራሂም የተባሉት ስሞች፥ ሌላ አካል ካልኖረበት ፍጹም
አሐድ ጋር የማይሄዱ ስሞች ናቸው። አንድ አካል ብቻውን ከሆነ ለራሱ አይራራም
ወይም ራሱን አይምርም። ራሱንም አይወድድም። ራሱን ካልወደደ ወይም
የሚወድደው ሌላ እስኪመጣ ድረስ አል-ዉዱድ መሆን አይችልም ማለት ነው። ከላይ
በስነ መለኮት monad ወይም monadism ከሚባለው አስተምህሮ ጋር አንድ ነው
ያልኩት ነው ይህ ‘ፍጹም አሐድ።’ የመጽሐፍ ቅዱሱ እግዚአብሔር ፍጹም አሐድ
ሳይሆን ሥሉስ አሐድ፥ ወይም በስነ መለኮቱ ቃል Triune ነው። እኔ አንድ ሰው ነኝ
አንድ አካል አለኝ። አንድ ሰው ሆኜ ሁለት አካል ሊኖረኝ አይችልም። እግዚአብሔር
ግን አንድ እግዚአብሔር ነው፤ አንድ እግዚአብሔር ሆኖ ሳለ ሦስት አካል ነው። ይህ
አንድ ሆኖ ከአንድ በላይ አካል መሆን ዲበ አእምሮአዊ ጉዳይ ነው። ሆኖም ግን
የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ነው።
26
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
27
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ዘፍ. 11፥6-7 እግዚአብሔርም አለ፦ እነሆ፥ እነርሱ አንድ ወገን ናቸው፥ ለሁሉም አንድ
ቋንቋ አላቸው፤ ይህንም ለማድረግ ጀመሩ፤ አሁንም ያሰቡትን ሁሉ ለመሥራት
አይከለከሉም። ኑ፥ እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ
እንደባልቀው። እዚህ ደግሞ ነጠላ ባለቤትና የብዙ ግስ እናገኛለን።
ח ֽד׃ ְ 4
ָ ֶשׁמַע יִשְׂרָ אֵל י ְהו ָה אֱלֹהֵינו ּ י ְהו ָה ׀ א
28
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ከላይ ሁለት ነጥቦችን እንመለከታለን ካልኩት አንዱ እስካሁን ያየነው ነገረ ሥላሴ
ነው። ሁለተኛው ነጥብ፥ ከሥላሴ አካላት በሥጋ የመጣው ወልድ መሆኑ ነው። አብ
አልመጣም፥ መንፈስ ቅዱስ አልመጣም። ወልድ ግን መጥቷል። ስለዚህ መምጣት
1ዮሐ. 4፥2-3 ይህንን ይለናል፤ የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ ታውቃላችሁ፤ ኢየሱስ
ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የሚታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፥ ኢየሱስ
ክርስቶስም በሥጋ እንደ መጣ የማይታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፤
ይህም የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፤ ይህም እንዲመጣ ሰምታችኋል፥ አሁንም
እንኳ በዓለም አለ።
በሥጋ መምጣት ማለት ቀድሞ ከነበሩበት ስፍራና ሁኔታ በዚህኛው ሁኔታ፥ ማለትም
በሥጋ ሁኔታ መምጣት ነው። ይህንን መምጣት የማይታመን መንፈስ፥ ይህንን
የማያምን፥ የማይቀበል መንፈስ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ ኢየሱስ በሥጋ አልመጣም
የሚል መንፈስ ሁሉ የእግዚአብሔር መንፈስ አይደለም። ከላይ ባየነው በ1ዮሐ. 4፥2-3
ይህ የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው ተብሏል።
29
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ዕብ. 2፥14-15፤ እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ
ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ
ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም
30
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
31
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
32
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ኢየሱስ ለምን ወንድ ሆነ? ወንድ የሆነው በዔድን ገነት የተሰጠው ተስፋ ይፈጸም
ዘንድ ነው። ያ የዘፍ. 3፥15 ተስፋ መቅድመ ወንጌል ይባላል። ያ ተስፋ ሲሰጥ በተባእት
ወይም በወንድ ጾታ ነው የተነገረው፤ በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም
መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን
ትቀጠቅጣለህ። እርሷ ሳይሆን እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል ነው የተባለውና ‘እርሱ’ ሆኖ
ነው የመጣው። ሰኮናውን እንጂ ሰኮናዋን አልተባለም። ይቀጠቅጣል እንጂ
ትቀጠቅጣለች አልተባለም። ያ የተስፋ ቃል የተፈጸመበትን ሁኔታ ጳውሎስ በገላ. 4፥4
ሲናገር እንዲህ አለ፤ ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት
የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤ የተወለደውን እንጂ
የተወለደችውን አላለም፤ የተወለደውን ልጁን ላከ።
33
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
34
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
57፥3 እርሱ ፊትም ያለ ኋላም ቀሪ፣ ግልፅም ስውርም ነው፤ እርሱም ነገርን ሁሉ ዐዋቂ
ነው።
35
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
36
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
(The Messiah, Jesus, the son of Mary, was but a messenger of Allah and
His word which He directed to Mary and a soul [created at a command]
37
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
7
Quran: English Translation: Saheeh International; http://tanzil.net/
Pdf: http://quranpdf.net/
38
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
39
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ምግብ መብላትና ውኃ መጠጣት አንዱ የሰው መሆን ባህርይ ነው። ምግብ መብላቱን
ሳዲቅ እንዳለው ቁርኣኑ ብቻ ሳይሆን ወንጌላቱም አሳምረው ገልጠውልናል፤
እንዲያውም፥ ማቴ. 11፥9 በላተኛ እንዳሉት በመጥቀስ እንዲህ ይላል፤ የሰው ልጅ
እየበላና እየጠጣ መጣ፥ እነርሱም፦ እነሆ፥ በላተኛና የወይን ጠጅ ጠጭ፥ የቀራጮችና
የኃጢአተኞች ወዳጅ ይሉታል። ጥበብም በልጆችዋ ጸደቀች። እግዚአብሔር ምግብ
መመገብ አያስፈልገውም። እውነት ነው፤ አያስፈልገውም። ኢየሱስ ግን ሰው በመሆኑ፥
ሰው ደግሞ ምግብ ስለሚመገብ፥ ምግብ ተመግቧል። ምግብ መብላቱ፥ ተመጋቢ
መሆኑ አምላክ አለመሆኑን ሳይሆን ሰው መሆኑን ያሳያል። መተኛቱም እንዲሁ።
40
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
4ኛ ወደ ፊት ሟች ኢየሱስ
41
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
42
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ይህ፥ ኢየሱስ እናቱንና እርሱን ከአላህ ጋር ሦስት አማልክት አድርጎ እንደሆነ ተጠይቆ
አልወጣኝም ያለበት ቃል። በኢስላም ሥላሴ ምን እንደሆነ ያለውን መረዳት
የሚገልጥልን ጥቅስም ይህ ነው። በሚሰጠው መልስ አምላክ አለመሆኑን መግለጡ
ነው። ግን ይህ ጥያቄ ቀድሞውኑ የተጠየቀ ጥያቄ ነው? ወይስ ገና ወደፊት የሚጠየቅና
የሚመለስ ጥያቄ ነው? ወደ ፊት የሚጠየቅ ከሆነ፥ እርሱ ገና ወደ ፊት የሚጠየቀውንና
የሚመልሰውን መልስ እኛ አሁን ማወቃችን ገራሚ ነው። ጥያቄውንም መልሱንም እኛ
አውቀነዋል። ዒሳ ግን ገና አላወቀም ማለት ነው? ይመስላል። ወይስ እርሱም አውቆ
መልስ እያዘጋጀ ነው? ወይስ መልሱ ይህ እኛም ያወቅነው ነው?
43
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
መቼም፥ ‘ወደ አምላኬ’ ያለውን ቃል ዋቢ አድርጎ ከጠቀሰ ሳዲቅ ጥቅሱን፥ ዮሐ. 20፥
17ን ይቀበለዋል ማለት ነው። የሚደንቀኝ ነገር ሙስሊሞች ከመጽሐፍ ቅዱስ ሲጠቅሱ
ልክ ያንን ቃል እንደሚቀበሉት አድርገው ሲሆን፥ ‘ይህንን ቃል እውነት እንደሆነ
እስክትጠቅሱት ድረስ ከተቀበላችሁት፥ በእውነት የጌታ ቃል ነው ብላችሁ
ትቀበሉታላችሁ?’ ሲባሉ የሚሠሩት ድራማ የሚደንቅ ነው። ሳዲቅ ይህንን ጥቅስ
ሲጠቅስ ጥቅሱን ስለሚቀበለው ነው የጠቀሰው? ወይስ ሳይቀበለው ግን ለመጥቀስ
ፈልጎ ነው የጠቀሰው? ወይስ ጎምዶ፥ የሚጎምድበትን ቦታ ደግሞ ራሱ መርጦ ነው
የሚቀበለው?
44
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ሳዲቅ ኢየሱስ አምላክ እንዳለው ከቁርኣን በርከት አድርጎ ጠቅሷል፤ [3፥52፤ 5፥72፤
5፥117፤ 19፥36፤ 43፥64]። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፥ እርሱ እንዳለው፥ ‘ጌታዬና
ጌታችሁ’ የሚል የለም። ኢየሱስ አብን፥ ‘አባቴ’ ብሏል፤ ይህ ግንኙነቱን ይገልጣል።
‘አምላኬ’ ብሏል፤ ይህ ሰውነቱን ይገልጣል። ጌታዬ ግን አላለም። በመጽሐፍ ቅዱስ
ይህ ጌታ አብን አባትና አምላክ ማለቱ ደግሞ ተደጋግሞ ተጽፏል። ደቀ መዛሙርቱም
ይህንን ብለዋል። ለምን? እናስታውስ ኢየሱስ በሥጋ ሲመጣ፥ ሰው ሲሆን ሰው
የሆነውን ሁሉ ሆኗል፥ ሰው የሆነውን ሁሉ አድርጓል ከኃጢአት በቀር ብያለሁ።
በሰውነቱ ወደ እግዚአብሔር ጸልዮአል፤ አባቴ ብሎ ለምኗል፤ አምላኬ ብሎ
ተናግሯል። ለምን? ሰው ስለሆነ። ጥቂት ጥቅሶች ልጨምርበት፤
45
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
46
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ከዚህ በፊት ይህን ጽሑፍ ስጀምር እንዳልኩት፥ ስለ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ አንድ የማንነት
ምስል አቅርቤ እንደነበረው ነው። ያንን አሳብ ጥቂት ሐረጎች ልጨምርበትና እንደገና
እንዲህ ልበለው፥ ‘በኋላ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ የተባሉት ተፈሪ መኮንን፥ ከአባታቸው
ከልዑል ራስ መኮንን ወልደ ሚካኤል እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺመቤት አሊ
ሐምሌ 16 ቀን 1884 ዓ. ም. በኤጄርሳ ጎሮ የተወለዱ ስድስት ዓይን እና አምስት እግር
ያላቸው፥ ቁመታቸው አሥራ አራት ሜትር ከስንዝር የሆኑ፥ ከቶም ንጉሥ ያልነበሩ፥
ከደርግ ግድያ አምልጠው ወደ ሰማይ ያረጉ፥ አሁን ጃህ ተብለው የሚመለኩ አምላክ
ናቸው።’ ብል ከዚህ ውስጥ ከማን መወለዳቸው፥ የት መወለዳቸው እና መቼ
መወለዳቸው፥ ከእውነተኛው ታሪካቸው ጋር የሚመሳሰል ነው። በከፊል ተመሳሰለ
ማለት ግን አንቀጹ እውነት ነው ማለት አይደለም። የቁርኣኑን ዒሳ ስናስብም ቢበዛ
ጉዳዩ ይኸው ነው። ስለ ወንጌል ስርጭት ስልጠና የሚሰጡን ሰዎች ሊያመሳስሉ
የሚችሏቸው ከመጽሐፍ ቅዱስ የተወሰዱ ነገሮች መኖራቸውን ብቻ በማየት መሳት
የለብንም።
47
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
በዚህ ጉዳይ ላይ ወረራውና ተኩሱ ከቁርኣን አቅጣጫ ሲሆን ምካቴዬና ምላሼ ከቃሉ፥
ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ነው። እውነተኛውን ክርስቶስ፥ ሌላ ያልሆነውን ክርስቶስ፥
የመጽሐፍ ቅዱሱን ክርስቶስ ማወቅ ሕይወት ነው። ዮሐ. 17፥1-3 ይህን ይነግረናል፤
ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ወደ ሰማይ ዓይኖቹን አነሣና እንዲህ አለ፦ አባት ሆይ፥ ሰዓቱ
ደርሶአል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ፥ በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥
ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው። እውነተኛ
አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች
የዘላለም ሕይወት ናት። አብን እና የተላከውን ወልድን ማወቅ የዘላለም ሕይወት
ነው። ወልድ የተላከ ስለመሆኑ ወደ ፊት ለብቻው አናየዋለን። ግን እሱን ማወቅ
የዘላለም ሕይወት ምንጭ መሆኑን እናስተውል። ይኸው ዮሐንስ በመልእክቱ ደግሞ፥
በወልድ የሚታመን አብ አለው፤ ወልድን የሚክድ አብ የለውም ይላል። 1ዮሐ. 2፥22-
23 ክርስቶስ አይደለም ብሎ ኢየሱስን ከሚክድ በቀር ውሸተኛው ማን ነው? አብንና
ወልድን የሚክድ ይህ የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው። ወልድን የሚክድ ሁሉ አብ እንኳ
የለውም፤ በወልድ የሚታመን አብ ደግሞ አለው። ኢየሱስን ማወቅና በእርሱ መታመን
የሕይወት ምንጭነቱን አመልካች ትምህርቶች ናቸው።
48
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ማር. 6፥3 እንዲህ ይላል፤ ይህስ ጸራቢው የማርያም ልጅ የያቆብም የዮሳም የይሁዳም
የስምዖንም ወንድም አይደለምን? እኅቶቹስ በዚህ በእኛ ዘንድ አይደሉምን? አሉ፤
ይሰናከሉበትም ነበር።
የዮሴፍ ልጅ ያሉትም አሉ፤ ሉቃ. 4፥22፤ ዮሐ. 1፥46 እና 6፥12። ነገር ግን ኢየሱስ
የዮሴፍ ልጅ አለመሆኑ የታወቀ ስለሆነና ይህ ጥያቄ እንደ ሙግት መቅረብም
ስለማይችል ይህን እንለፈው። ከነዚህ የናዝሬት ሰዎች ብቻ በቀር ኢየሱስን፥ ‘የማርያም
ልጅ ወይም የዮሴፍ ልጅ ብሎ የጠራው’ በአዲስ ኪዳን ማንም የለም። ሳዲቅ
እንዳለው ሐዋርያቱ ኢየሱስን፥ ‘የማርያም ልጅ’ እያሉ አልጠሩትም። አንዴም
አልጠሩትም። እንደዚያ ብለው ጠርተውት ቢሆኑ ኖሮ ሐዋርያቱ የጻፉት ወንጌልና
መልእክቶች ብዙ ናቸውና በዚያ ውስጥ አንዴ እንኳን፥ አንዴ ብቻ እንኳን ባገኘን
ነበር። አንዴ ብቻ እንኳ። ግን አንድም የለም።
ሀ. እግዚአብሔር አብ መስክሯል፤
ለ. ኢየሱስ ራሱ መስክሯል፤
51
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ሐ. መልአክ መስክሯል፤
52
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ዮሐ. 11፥27 እርስዋም፦ [የአልዓዛር እኅት ማርያም] አዎን ጌታ ሆይ፤ አንተ ወደ ዓለም
የሚመጣው ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆንህ እኔ አምናለሁ አለችው።
ዮሐ. 5፥17-18 ኢየሱስ ግን፦ አባቴ እስከ ዛሬ ይሠራል እኔም ደግሞ እሠራለሁ ብሎ
መለሰላቸው። እንግዲህ ሰንበትን ስለ ሻረ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ደግሞ ራሱን
ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሎ፦ እግዚአብሔር አባቴ ነው ስላለ፥ ስለዚህ አይሁድ
ሊገድሉት አብዝተው ይፈልጉት ነበር። ይህንን ጥቅስ ቀድሜ ጠቅሼዋለሁ። እነዚህ
ሰዎች ማለቱን መናገራቸው ቢሆንም ማለቱን ማረጋገጣቸውም ነው።
53
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ሰ. አሕዛብ መስክረዋል፤
ማር. 15፥39 በዚያም በአንጻሩ የቆመ የመቶ አለቃ እንደዚህ ጮኾ ነፍሱን እንደ ሰጠ
ባየ ጊዜ፦ ይህ ሰው በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ አለ።
54
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ሮሜ. 1፥1-4 ሐዋርያ ሊሆን የተጠራ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ጳውሎስ በነቢያቱ አፍ
በቅዱሳን መጻሕፍት አስቀድሞ ተስፋ ለሰጠው ለእግዚአብሔር ወንጌል ተለየ። ይህም
ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት
የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ዕብ. 7፥3 አባትና እናት የትውልድም ቍጥር የሉትም፥ ለዘመኑም ጥንት ለሕይወቱም
ፍጻሜ የለውም፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ልጅ ተመስሎ ለዘላለም ካህን ሆኖ
ይኖራል።
55
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
56
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ሉቃ. 22፥42፤ ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን
የአንተ እንጂ እያለ ይጸልይ ነበር።
58
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ይህ ማለት ኢየሱስ በራሱ ፈቃድ ምንም አያደርግም ማለት እንጂ ከቶም ምንም
ማድረግ አይችልም፤ ፈጣሪ ሳይሆን ፍጡር ነው፤ አቅም የለውም፥ ፈቃድም የለውም
ማለት አይደለም። እዚሁ ምዕራፍ ቁጥር 21 ላይ፥ አብ ሙታንን እንደሚያነሣ
ሕይወትም እንደሚሰጣቸው፥ እንዲሁ ወልድ ደግሞ ለሚወዳቸው ሕይወትን
ይሰጣቸዋል። ይላል። ይህ ለአብነት ያህል ነው። በሌሎች ብዙ ቦታዎች ሲፈውስ፥
ተአምራት ሲያደርግ፥ ይቅርታ ሲያደርግ በፈቃዱ ነው ያደረገው። የግል ፈቃዱን
አለማድረጉ፥ ማድረግ አለመቻሉ ሳይሆን፥ ፈቃዱን ማስገዛቱና ፈቃዱ ከአብ ፈቃድ
ጋር አንድ ፈቃድ መሆኑ አረጋጋጭ ነው። ስለዚህ፥ ‘በራሱ ኃይልና ፈቃድ ምንም
ሊያደርግ አለመቻሉ ፍጡር ብቻ የመሆኑ አረጋጋጭ ነው፤’ የተባለው ማጣጣያ ክስ
መሠረተቢስ ክስ ነው።
59
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ማር. 11፥13-14 እና 20-24 ቅጠልም ያላት በለስ ከሩቅ አይቶ ምናልባት አንዳች
ይገኝባት እንደ ሆነ ብሎ መጣ፥ ነገር ግን የበለስ ወራት አልነበረምና መጥቶ ከቅጠል
በቀር ምንም አላገኘባትም። መልሶም፦ ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም ማንም ከአንቺ ፍሬ
አይብላ አላት። ደቀ መዛሙርቱም ሰሙ። . . . ማለዳም ሲያልፉ በለሲቱን ከሥርዋ
ደርቃ አዩአት። ጴጥሮስም ትዝ ብሎት፦ መምህር ሆይ፥ እነሆ፥ የረገምሃት በለስ
ደርቃለች አለው። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ በእግዚአብሔር እመኑ።
እውነት እላችኋለሁ፥ ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥
ይህን ተራራ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል። ስለዚህ እላችኋለሁ፥
የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፥ ይሆንላችሁማል።
60
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
61
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
የመጽሐፍ ቅዱሱን ኢየሱስ እንደ ጌታ የማይቀበሉት እንደ ሳዲቅ ያሉት ሰዎች ግዙፍ
ችግር ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጥቅስ ሲጠቅሱ የምትመቻቸው የሚመስላቸውን
አንዲት ቃል ወይም አንድ ሐረግ ብቻ ይወስዱና አጠገቡ ያለውን ወይም ያ ቃል
እውስጡ ያለበትን አሳብም አለመውሰዳቸው ነው። ለምሳሌ፥ ቀደም ሲል እንዳየነው፥
ሳዲቅ ኢየሱስ የተላከው መሆኑን ሲናገር ትኩረቱ የተላከ መሆኑ ላይ ብቻ ነበር።
‘ከተላከ፥ ማን ላከህ? ነው የምንለው’ ብሏል። ግን የስፍራው፥ የክፍለ ምንባቡ አሳብ፥
የዘላለም ሕይወት ምንጭ እርሱንና የላከውን አብን ማወቅ መሆኑን ወይም የሚለውን
ቃል አላወሳም። የተላከ መሆኑን ብቻ እንጂ የተላከው እርሱ ማን መሆኑን፥ ወይም
በክፍሉ ውስጥ፡ማን ተብሎ እንደተጠቀሰ እንኳ አላወሳም። ለምን? አሳቡ፥ ጥረቱ፥
ኢየሱስ የበታች መሆኑን፥ የላኪው ተላኪ ወይም ተላላኪ መሆኑን፥ ፍጡር መሆኑን፥
ለማሳየት ነው። ለዚህ ነው የተላከው የዘላለም ሕይወት ምንጭ መሆኑን ያላወሳው።
ይህ የሳዲቅ እና የብጤዎቹ ትልቁ ችግር ነው። ሌላ ምሳሌ ብናይ፥ በዮሐ. 12፥44 በእኔ
የሚያምን በላከኝ ማመኑ ነው እንጂ በእኔ አይደለም፤ ያለውን ሲወስድ፥ በላከኝ
ማመኑ ነው የሚለው ላይ ያተኩራል እንጂ፥ የኢየሱስና የአብ አንድ መሆን ላይ
አያተኩርም። ‘በእኔ የሚያምን’ ነው እኮ ያለው! በእኔ የሚያምን ካለ ኢየሱስ
የሚታመን ወይም የሚታመነው ነው ማለት ነው። ከአብ ጋር የሚታመነው ነው
ማለት ነው። በኢስላም ብዙ ሺህ ነቢያትና መልእክተኞች አሉ ይባላል፤ (ከ120ሺህ
በላይ) ከነዚህ ማንም፥ ‘በእኔ እመኑ!’ ያለ ረሱል ወይም መልእክተኛ የለም። ኢየሱስ
ግን ይህንን ብሏል። ይህንን የመታመን ነገር ወደ ጎን ገፍቶ የተላከ መሆኑ ላይ ብቻ
ማተኮር ማሳት ነው። ለቅሞ የሚፈልጉትን ብቻ ወስዶ የቀረው እስከመኖሩም መርሳት
ለማሳት ማደናገር ነው።
62
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
63
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ምሳሌ ደግሞ ሰጠ። ምሳሌ የሰጠው የኖኅን ዘመን ነው። የኖኅ ዘመን እንደ ነበረ የሰው
ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና። በዚያች ወራት ከጥፋት ውኃ በፊት፥ ኖኅ ወደ
መርከብ እስከገባበት ቀን ድረስ፥ ሲበሉና ሲጠጡ ሲያገቡና ሲጋቡም እንደ ነበሩ፥
የጥፋት ውኃም መጥቶ ሁሉን እስከ ወሰደ ድረስ እንዳላወቁ፥ የሰው ልጅ መምጣት
ደግሞ እንዲሁ ይሆናል። ማቴ. 24፥37-39።
ከትንሣኤው በኋላም ይህንኑ ጥያቄ ጌታን ጠይቀውት ነበር፤ የሐዋ. 1፥6-7 እነርሱም
በተሰበሰቡ ጊዜ፦ ጌታ ሆይ፥ በዚህ ወራት ለእስራኤል መንግሥትን ትመልሳለህን?
ብለው ጠየቁት። እርሱም፦ አብ በገዛ ሥልጣኑ ያደረገውን ወራትንና ዘመናትን
ታውቁ ዘንድ ለእናንተ አልተሰጣችሁም፤ አላቸው። ይህ ከትንሣኤው በኋላ ነው፤ ያኔ
በሥጋው ወራት ስለሆነ ነው ያልተናገረው ቢባል፥ ‘ይህኛው ከትንሣኤው በኋላ ነውና
መናገር ይችል ነበር፤’ ማለት ይቻላል። ነገር ግን እዚህም አልተናገረም፤ ለምን? መልሱ
ግልጽ ነው፤ ታውቁ ዘንድ ለእናንተ አልተሰጣችሁም፤ ልናውቀው አልተሰጠንም።
መቼ እንደሚመጣ ማወቅ ቢያስፈልገን ኖሮ ጌታ በግልጽ ይነግረን ነበር። ቀኒቱን ብቻ
አይደለም፤ ሰዓቲቱንም በተናገረ ነበር፤ ግን ይህን ማወቅ ለእነርሱም፥ ለአኛም
አልተሰጠንም፤ አያስፈልገንም።
64
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ኢየሱስ ነቢይ ነው? በእርግጥ ነው። አስቀድሞ ትንቢት የተነገረለት ነቢይ ነው። በዘዳ.
18፥15-18 አምላክህን እግዚአብሔርን በኮሬብ ስብሰባ ተደርጎ በነበረበት ቀን፦
እንዳልሞት የአምላኬን የእግዚአብሔርን ድምፅ ደግሞ አልስማ፥ ይህችን ታላቅ እሳት
ደግሞ አልይ ብለህ እንደ ለመንኸው ሁሉ፥ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ መካከል
ከወንድሞችህ እንደ እኔ ያለ ነቢይ ያስነሣልሃል፤ እርሱንም ታደምጣለህ።
እግዚአብሔርም አለኝ፦ የተናገሩት መልካም ነው፤ ከወንድሞቻቸው መካከል እንደ
አንተ ያለ ነቢይ አስነሣላቸዋለሁ ቃሌንም በአፉ አደርጋለሁ፥ ያዘዝሁትንም ቃል ሁሉ
ይነግራቸዋል፤ በስሜም የሚናገረውን ቃሌን የማይሰማውን ሰው እኔ እበቀልለታለሁ።
ለነዚያ ያንን እነሱ ዘንድ በተውራትና በኢንጂል ተጽፎ የሚያገኙትን የማይጽፍና የማያነብ
ነብይ የሆነውን መልክተኛ የሚከተሉ ለሆኑት (በእርግጥ እጽፋታለሁ)፤ . . .
ይህን የዘዳ. 18፥18ን ትንቢት ለኢስላም ነቢይ ማድረግ በሦስት ምክንያቶች ስሕተት
መሆኑን ላሳይ፤
65
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
66
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ጌታ ነቢይ መሆኑም ተደጋግሞ ተጽፎአል። ማቴ. 13፥57 ኢየሱስ ግን፦ ነቢይ ከገዛ
አገሩና ከገዛ ቤቱ በቀር ሳይከበር አይቀርም አላቸው። ይላል። ይህን ጌታ ነው
በናዝሬት የተናገረው። የተናገረው የተለመደ አባባልን ቢሆንም ራሱን እንደ ነቢይ
በማድረግ አቅርቧል። በሉቃ. 13፥33ም ተቀራራቢ ነገር ተናግሯል፤ ዳሩ ግን ነቢይ
ከኢየሩሳሌም ውጭ ይጠፋ ዘንድ አይገባውምና ዛሬና ነገ ከነገ በስቲያም ልሄድ
ያስፈልገኛል።
ሉቃ. 7፥16 ሁሉንም ፍርሃት ያዛቸውና፦ ታላቅ ነቢይ በእኛ መካከል ተነሥቶአል፥
ደግሞ፦ እግዚአብሔር ሕዝቡን ጐበኘ እያሉ እግዚአብሔርን አመሰገኑ። ይህም
የሕዝቡ መረዳትና ስሜት ነው።
67
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
69
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
70
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
71
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ባታምኑ አብ በእኔ እንደ ሆነ እኔም በአብ እንደ ሆንሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ
ሥራውን እመኑ።
72
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
የመስቀል ሞቱ
የኢየሱስ በመስቀል መሞት ዒሳ ኢየሱስ አለመሆኑን አረጋጋጭ ነው። ባለፉት ክፍሎች
ዒሳ ፍጡር ነው፤ አምላክ አይደለም በማለት መሐመድ ሳዲቅ ላቀረባቸውን 12 ነጥቦች
ምላሽ ስሰጥ የምላሼ ዋና አሳብ፥ እርሱ ዒሳ የሚለው ሰው የመጽሐፍ ቅዱሱን
ኢየሱስን አለመሆኑን ማሳየት ነው። ኢየሱስ በሥጋ የተገለጠ ወይም ሥጋ የለበሰ
አምላክ መሆኑን በስፋትና በዝርዝር አይተናል። ከላይ ካየናቸው ብዙ ገጾች አሳቦች
እነዚህ ሁለቱ፥ የቁርኣኑ ዒሳ እና የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ በቅርበት ሲፈተሹ
ፈጽሞም አንድ እንዳልሆኑ ማረጋገጥ ከባድ አይሆንም። እስካሁን ያየናቸው ነጥቦችም
ያንን አሳይተውናል። ቀጥሎ የምንመለከተው ነጥብም ይህንን ይበልጥ ያረጋግጥልናል።
73
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
አንደኛው ነጥብ፥ ሳዲቅ፥ ‘የውርስ ኃጢአት ብሎ ነገር የለም፤ የምትክ ሞትም የለም፤’
ብሏል። በቀጥታም ባይሆን ግንኙነቱ የኢየሱስ ሞት ምትካዊ ሞት በመሆኑ ነው።
ሌላው ቢቀር፥ ኢየሱስ ለኛ ሞተ የሚባለው ነገር ወደ ጎን ቢቀመጥ፥ ለኛም አልሞተም
ቢባል፥ ኢየሱስም በመስቀል ላይ አልሞተም ብንል፥ ቁርኣኑ እንደሚለው ኢየሱስ
አልተሰቀለም፤ አልሞተም ብለን ብንወስድ ያልሞተበት ምክንያት አለ አይደል? ይህንን
አንርሳ። እነሱ አልሞተም ነው የሚሉት። ለምን አልሞተም? እንዴት አልሞተም ሲባል
የሚሰጡት ምክንያት ራሱን የሚገድል ምክንያት ነው።
ሁለተኛው ነጥብ፥ ትልቅ ጉዳይ አይደለም፤ የእግረ መንገድ ነጥብ ነው። ደጋግሞ፥ እነ
አዳም ቅጠል በሉ ይላል፤ የምን ቅጠል እንደሚያወራ ግልጽ አይደለም። ጫት የቃሙ
አስመሰላቸው። መጽሐፍ ቅዱስም ቁርኣንም ላይ ጫት ቃሙ፤ ወይም ቅጠል በሉ
አይልም። አል አዕራፍ 7፥22
74
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
75
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ሱረቱ አል-ኒሳእ ከመዲና ሱራዎች አንዱ ነው። የመዲና ሱራዎች የኋለኞቹ ሱራዎች
ናቸው። ይህንን አሳብ ቀደም ባለው ክፍል እንደጠቀስኩት በቁርኣን መሻር የሚባል
ድንጋጌ አለ፤ (በእንግሊዝኛ abrogation ይሉታል፤) የኋለኞቹ የቀደመውን የሚሽሩት
ናቸውና የመዲና ሱራዎች የመካ ሱራዎችን ይሽራሉ። ይህ የመዲና ሱራ ነው።
ክርስቲያኖችንና አይሁድን ለማጥቃት ከተሰነዘሩትና እምነታቸውን ለማጠልሸትና
መጽሐፎቻቸውን ለማጥላላት የተነገሩት አያዎች (አንቀጾች) ያሉባቸው ሱራዎች ደግሞ
የመዲና ሱራዎች ናቸው። ሙስሊሞች መጽሐፎቹን አናጥላላም ሊሉ ይችላሉ፤ ግን
የሚለውን አለመቀበል እኮ ማጥላላትና ማዋደቅ ነው። ያ ብቻ አይደለም፤ መሻር እኮ
መከለስና መበረዝም ነው። ይህንን ለመቀበል አያስቡም።
76
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
77
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ለቃላቶቹ ለዋጭ የላቸውም ማለት ለዋጭ የላቸውም ነው። አራት ነጥብ። መጽሐፉን
መለወጥ የሚችል ማንም ሊኖር አይችልም። ይህ መጽሐፍ ያኔ ሙሐመድ እርሱ
የተቀበለው ከነበረ አሁን ለምን አይቀበሉትም? የዚህ አጭር መልስ ከተቀበሉ ከሁለቱ
አንዱ ብቻ ትክክል መሆኑ የሚታይ ስለሆነና ያንን መገዳደር የሚችል ማረጋገጫ
ባለመኖሩ ነው። ወይ ተሰቅሏል ሞቷል ትክክል ነው፤ ወይም አልተሰቀለም አልሞተም
ትክክል ነው። ሁለቱም ትክክል መሆን አይችልም። አንዱ ከሌላው ጋር ተቃራኒ ነውና
ሁለቱም ትክክል አለመሆንም አይችሉም። ከሁለቱ አንዱ ብቻ ትክክል ነው። መቼም
ይህ መጽሐፍ ከኢስላም ነቢይ በኋላ ተለወጠ ወይም ተበረዘ እንዳይባል ከላይ
እንዳልኩት ያኔ የነበረውና ከዚያም በፊት የነበረው አዲስ ኪዳን ከአሁኑ ጋር ፍጹም
አንድ መሆኑን የሚያረጋግጡ ብዙ ሺህ፥ ከ25 ሺህ በላይ የጽሑፍ ቁራጮች ብቻ
ሳይሆኑ በሙሉ ይዘት የተደጎሱ መጽሐፎችም አሉ። አይቶ ማረጋገጥ የሚወድ በቀላሉ
ሊያይ እስከሚችል ድረስ የነዚህ ሰነዶች የሚነበብ ጽሑፋቸውና የሚታይበ፥ አካል
በቤተ መዘክሮችም፥ በምስል በኢንተርኔትም ይገኛል።
በዚህ ጥቅስ ውስጥ ብዙ ግጭቶች አሉበት። አንድ አምስት ያህል ጉልህ ግጭቶች
አሉበት። ከዚያም ሊበዙ ይችላሉ፤ ለኔ የታዩኝ አምስቱ እነዚህ ተራና አላፊ ሳይሆኑ
መሠረታዊ ስሕተቶችና ግጭቶች ናቸው።
አይሁድ ሳይሞት በፊት፥ ‘አጋንንት አለበት፥ ሕዝቡን ያስታል፤ አሳች ነው’ ነበር
የሚሉት እንጂ መሢሕ ብለውት አያውቁም። ከሞተ በኋላም እንኳ፥ ‘ያ አሳች’ ነበር
78
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ያሉት፤ ሲኖር ሳይሆን፥ ከሞተ በኋላ እንኳ። ማቴ. 27፥63-66፤ ጌታ ሆይ፥ ያ አሳች
በሕይወቱ ገና ሳለ፦ ከሦስት ቀን በኋላ እነሣለሁ እንዳለ ትዝ አለን። እንግዲህ ደቀ
መዛሙርቱ መጥተው በሌሊት እንዳይሰርቁት ለሕዝቡም፦ ከሙታን ተነሣ እንዳይሉ፥
የኋለኛይቱ ስሕተት ከፊተኛይቱ ይልቅ የከፋች ትሆናለችና መቃብሩ እስከ ሦስተኛ ቀን
ድረስ እንዲጠበቅ እዘዝ አሉት። ጲላጦስም፦ ጠባቆች አሉአችሁ፤ ሄዳችሁ
እንዳወቃችሁ አስጠብቁ አላቸው። እነርሱም ሄደው ከጠባቆች ጋር ድንጋዩን አትመው
መቃብሩን አስጠበቁ። ይህንን አይሁድ ያሉት ለጲላጦስ ነው። ያ አሳች ነው ያሉት፤ ‘ያ
መሢሕ፤ ያ የገደልነው መሢሕ’ አላሉም።
ሁለተኛ፥ በዚህ አንቀጽ ውስጥ ያለው ሌላው ውስጣዊ ችግር እነዚህ፥ ‘እኛ የአላህን
መልክተኛ የመርየምን ልጅ አልመሲሕ ዒሳን ገደልን’ ያሉት ሰዎች መረገማቸው ነው።
ገደልን በማለታቸው (ረገምናቸው)፤ ‘ረገምናቸው’ የሚለው በቅንፍ ውስጥ ሆኖ ነው
የተጻፈው። ይህ ማለት የተጨመረ ቃል ነው ማለት ነው? ይሁን እንጂ፥ በቅንፍ
ሆኖም ግን ተጽፏል፤ ሰዎቹ ተረግመዋል ማለት ነው። ረጋሚው ማን ነው? እንደ
ጥቅሱ አሳብ አላህ ነው። አላህ ረጋሚም ነው ማለት ነው።
79
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ተመሰለ ማለት መሰለ የሌላውን መልክ ያዘ ማለት ነው። የተገደለው በዒሳ ተመሰለ
ከተባለ፥ ይህ የተመሰለው ሰው ያንን ሰው አይደለም ማለት ነው። ካልሆነ ይህ ሰው
ያንን ሰው አለመሆኑን በመናገር፥ ራሱን ለመከላከል ምንም እርምጃ አይወስድም?
ልብሱን ሲገፍፉት፥ አካሉን ሲገርፉት፥ ሲጎስሙት፥ ሲከፉበት፥ ሲተፉበት፥
ሲያላግጡበት፥ ሲዘብቱበት፥ የእሾክ አክሊል ሲያደርጉበት፥ መስቀል ሲያሸክሙት፥
ሲሰቅሉት፥ አንድ ጊዜ እንኳ፥ ‘እኔ እሱ ሰውዬ አይደለሁም!’ ማለት አይችልም ነበር?
በተለይ ጲላጦስ ፊት ቀርቦ፥ ‘የአይሁድ ንጉሥ ነህን?’ ብሎ ሲጠይቀው፥ ‘ኧረ እኔ
እሱን አይደለሁም!’ እንዴት አላለም? ‘አይደለሁም’ ብሎ በአንዲት ቃል ነጻ መውጣት
አይችልም ነበር? ወይስ መልኩ ሲቀየር ዱዳም ሆኖ ነበር? ‘እኔ ያንን ሰው አይደለሁም’
ብሎ መትረፍ እየቻለ አለማድረጉ ግዙፍ ውስጣዊ ግጭት ነው።
80
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ከቁርኣን መጽጻፍ በፊት ከእውነትና ከእውነታ የራቁ ቢሆኑም እነዚህን የመሰሉ ነገሮች
ኖረው አያውቁም ማለት አይደለም፤ ያውቃሉ። አንዳንዶቹ በአካል ሌላ ሰው ነው
ሲሉ ሌሎች አካል መሰለ እንጂ አካል አልነበረም የሚሉ ናቸው። በጉልህ
የሚታወቀው ዶሴቲዝም የሚባለው ቀደም ሲል አንዴ የጠቀስኩት በሁለተኛው ምዕት
ዓመት ብቅ ያለ ኑፋቄ ነው። ቃሉ δόκησις (ዶኬሲስ) δοκεῖν (ዶኬይን)
81
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
82
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
83
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
84
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
እነዚህ ሦስት ጥቅሶች ናሙና ብቻ ናቸው። ከማርቆስ ወንጌል ሌሎች ጥቅሶችን ወይም
ሌሎቹን ሦስቱን ወንጌላት ብንጨምር ብዙ ይህን የሚመስሉ እናቀርባለን። (ማቴ. 26-
27፤ ሉቃ. 22-23፤ ዮሐ. 18-19 ተመልከቱ።) የተሰቀለው ሌላ ሳይሆን ኢየሱስ
ለመሆኑ ይህ አስረጅ ነው። ይህ ሰው ኢየሱስን ሳይሆን ኢየሱስን እንዲመስል
የተደረገውና የመሰለው ሰው ቢሆን ከላይ የተጻፈውን አለመናገር ብቻ ሳይሆን፥
'በሐሰት ነው የምከሰሰው! እናንተ ሰዎች አይገባችሁም እንዴ?!' ይል ነበር፤ የተሰቀለው
ሰው ግን ይህንን አላለም። ዲዳ ካልሆነ በቀር መከላከያውን ማቅረብ ይችል ነበር።
ዲዳ አለመሆኑ ደግሞ ግልጽ ነው፤ በመናገሩ ይታወቃል።
የኢየሱስ እናት ማርያም እንኳ ኢየሱስ ከመስቀል ሲናገራት ያ ድምጽ የሌላ መሆኑን
አልጠረጠረችም። የተቀየረው ሰው መልኩ ብቻ ሳይሆን ድምጹም ተቀይሮ ነበር
ማለት ነው? አላህ መልኩን ከቀየረና መቀየር የሚችል አምላክ ከሆነ ድምጽ፡መቀየርም
85
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
86
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
87
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
88
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ዮሐ. 3፥14-15 ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን
ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል።
[ስቅለት]
90
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
በጣም ፈጣንና ቀልጣፋ የግድያ መንገዶች አሉ፤ ተወግቶ መገደል፥ ለአውሬ ተሰጥቶ
መበላት፥ በእሳት መቃጠል ቀላል፥ ቀልጣፋና ፈጣን ሞት ናቸው ከመስቀል ጋር
ሲነጻጸሩ። መስቀል በማሰቃየት መግደያ መሳሪያ ነው። በመስቀል ላይ የሚሰቀሉ
አንዳንዶቹ አስቀድሞ በሚቀበሉት ድብደባና ግርፋት ለሞት የቀረቡ ሆነው ነው
የሚሰቀሉት። እጃቸው ተዘርግቶ ደረታቸው ስለሚወጠር የሳቡትን አየር ለማውጣት
ወይም ወደ ውጪ ለመተንፈስ ጭንቅ ነው። አየር ለመሳብ በተቸነከረው እግራቸው
ረግጠው ከፍ ማለት አለባቸው። ይህ ደግሞ ቀላል አይደለም፤ ችንካር ነው። ከፍ ብሎ
መተንፈስ ለመቻል የችንካሩን ቁስል ስቃይ ችለው ነው የሚረግጡትና ከፍ የሚሉት።
ብቻ መተንፈስ ስላለባቸው እንደምንም ከፍ ብለው ወደ ውስጥ ይስቡና ዝቅ ሲሉ
ወደ ውጪ ይተነፍሳሉ። ጥቂት ቆይተው መተንፈስ አቅቷቸው እንደ ታፈነ ሰው
ተሰቃይተው ይሞታሉ። ካልሞቱና ቶሎ መሞት ካለባቸው ጭናቸው እንዲሰበር
ይደረጋል። ጭናቸው ከተሰበረ በእግራቸው ረግጠው ቀና ማለት አይችሉምና
መተንፈስ አቅቷቸው ይሞታሉ። የመስቀል ሞት በጥብቅ የሚሸሹት፥ ወይም
ተገድደው የሚሞቱት እንጂ ፈቅደው የሚሞቱት ሞት አይደለም። ጌታ ግን ወድዶ፥
ወድዶን ነው በመስቀል ላይ የሞተልን።
91
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ነገር፥ እውነት ላልሆነ ነገር፥ ውሸት መሆኑን ነፍስያው ለምታውቀው ነገር ነፍሱን
የሚሰጥ? ተታልሎ ሰጠ ማለት ይቻላል? ከሆነ፥ ያታለለውስ ማን ነው? ያስ ሌሎቹን
አታልሎ ያስሞተ ሰው እንዴት ሆኖ ሞተ?
92
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ሞቱን እውን ያደረገው ደግሞ ትንሣኤው እውን መሆኑ ነው። ቁርኣን እንደሚለው
አልሰቀሉትም፥ አልገደሉትም ተወሰደ እንጂ የሚለው ሐሰት መሆኑን የምናውቀው
ትንሣኤው የሐዋርያቱን ሕይወት ፈጽሞ የገለበጠው ጉዳይ በመሆኑ ነው። ኢየሱስ
ከተወሰደ በአካል ሊታይ አይችልም። ያ የተሰቀለውን በሌላ እንዲመሰል ያደረገው ሌላ
የተነሣ ሰውም አስመስሎ ካላቀረበ በቀር። ግን የተነሣው ደግሞ ራሱ ኢየሱስ መሆኑን
በተለያዩ ማስረጃዎች ሲያረጋግጥ አርባ ቀን ቆይቷል። ሐዋ. 1፥3 ደግሞ አርባ ቀን
እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ
93
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ምስክር አንድ፤
94
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
95
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ምስክር ሁለት፤
But all human efforts, all the lavish gifts of the emperor, and the
propitiations of the gods, did not banish the sinister belief that the
96
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ትርጉም፤
97
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
3. Now there was about this time Jesus, a wise man, if it be lawful to
call him a man; for he was a doer of wonderful works, a teacher of
98
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
such men as receive the truth with pleasure. He drew over to him
both many of the Jews and many of the Gentiles. He was [the] Christ.
And when Pilate, at the suggestion of the principal men amongst us,
had condemned him to the cross, those that loved him at the first did
not forsake him; for he appeared to them alive again the third day; as
the divine prophets had foretold these and ten thousand other
wonderful things concerning him. And the tribe of Christians, so
named from him, are not extinct at this day.14
ትርጉም፤ ‘እነሆ በዚህ ዘመን ኢየሱስ የተባለ ጠቢብ ሰው ነበረ፤ ሰው መባሉ ሕጋዊ
ከሆነ፤ ምክንያቱም እርሱ ተምራትን አድራጊና እውነትን የሚወድዱ ሁሉ በደስታ
የሚሰሙት ነበረ። ከአይሁድም ከአሕዛብም ብዙዎችን ወደራሱ ስቦ ነበር። እርሱ
ክርስቶስ ነበረ። ከኛ መካከል አለቆቻችን ባቀረቡለት አሳብ ተስማምቶ ጲላጦስ
እንዲሰቀል በፈረደበት ጊዜ ከቀድሞ የወደዱት አልከዱትም ነበር። ከዚያም
የእግዚአብሔር ነቢያት ይህንና ሌሎችንም እልፍ ድንቅ ነገሮች እንደተናገሩለት
በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተነሥቶ ታያቸው። በእርሱ ስም የተሰየሙትና ክርስቲያን
የተባሉት ሕዝቦች እስከ ዛሬ ድረስም አልጠፉም።’ (ትርጉም የራሴ።)
99
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
15 F. F. Bruce: The New Testament Document, IVF & Tyndale Press., London 1960, p.
113, 143.
16 Habermas, Gary R. The Verdict of History, Thomas Nelson, Nashville, 1982, pp. 100.
17 Ibid., pp. 107-108.
18 Ibid., pp. 89-90.
100
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
On the Eve of Passover they hung Yeshu the Notzarine. And the
herald went out before him for 40 days [saying]: “Yeshu the
Notzarine will go out to be stoned for sorcery and misleading and
enticing Israel [to idolatry]. Any who knows [anything] in his defence
must come and declare concerning him.” But no-one came to his
defence so they hung him on the Eve of Passover.19
ትርጉም፤ በፋሲካ ዋዜማ የናዝሬቱን የሱስ ሰቀሉት። አዋጅ ነጋሪው ከእርሱ በፊት
40 ቀናት ቀድሞ፥ ‘የሱስ የናዝሬቱ ስለ ጥንቆላ እና እስራኤልን (በጣዖት አምልኮ)
ስለማሳት በድንጋይ ተወግሮ ይገደላል። ስለ እርሱ ምንም ነገር የሚያውቅና
የሚሟገት ማንም ሰው ቀርቦ መናገር አለበት።’ እያለ ለፈፈ። ነገር ግን ሊሟገትለት
የመጣ ማንም አልነበረምና በፋሲካ ዋዜማ ሰቀሉት።
19
Sanhadrin 43a (http://www.tyndale.cam.ac.uk/Tyndale/staff/Instone-
Brewer/prepub/Sanhedrin%2043a%20censored.pdf).
20 Habermas, Gary R. The Verdict of History, Thomas Nelson, Nashville, 1982, p. 99.
101
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ምስክር ሦስት፤
102
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
የነዚህንና ከነዚህ በኋላ የኖሩትንና ከአዲስ ኪዳን ጥቅሶች እየጠቀሱ የጻፉትን የአባቶች
ጽሑፎች በመሰብሰብ ጠቅላላውን አዲስ ኪዳን በሙሉ (ከ17 ጥቅሶች በስተቀር)
እንደገና መጻፍ ይቻላል ይላል የምካቴ ክርስትናው ምሑር ጆሽ ማክደዌል።21 ጆሽ
ማክደዌል የክርስቶስን ሞትና በተለይም፥ ትንሣኤ እውነት አለመሆኑን ለማረጋገጥ
ሰፊና ጥልቅ ምርመራ ካደረገ በኋላ የትንሣኤው ማስረጃ ክብደቱና ብዛቱ ከሞት
የተነሣውን ጌታ በማመንና በመከተል ክርስቲያን ከመሆን ሌላ አማራጭ ሊሰጠው
ስላልቻለ በ1959 ክርስቲያን የሆነ ሰው ነው።
ምስክር አራት፤
21 Mc Dowell, Josh: Evidence that Demands a Verdict, Campus Crusade for Christ
International, Arrowhead, San Bernadino, CA, 1977, pp. 54-55.
103
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
የመስቀል ሞት ምንነት
መስቀሉ የክርስትና እምነት እንብርት መሆኑ የታወቀ ነው። ቀደም ሲል
እንደተመለከትነው ክርስቶስን በተመለከተ መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምራቸው ሦስት
ዐበይት ትምህርቶች አሉ። እነዚህም፥ ጌትነቱ፥ ሞቱ እና ትንሣኤው ናቸው። ብዬ
ነበር። ሥጋ መልበሱም ትልቅ ነጥብ ነው፤ ግን ሥጋዌው በሞቱ ውስጥ የሚጠቀለል
ነው። የሞተው ሥጋ ስለለበሰ ወይም በሥጋ ስለመጣ ነው በማለት እነዚህን ሦስት
ግዙፋን ትምህርቶች ጌትነት፥ ሞት፥ ትንሣኤ የሚለውን ጠቅልሎ፥ ጠፍሮ የያዘልን
አንድ ጥቅስ አይተን ነበር፤ ሮሜ. 10፥9፤ ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር
እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና።
104
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
105
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
106
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
107
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
1. የመስቀሉ አስፈላጊነት
እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ግን በብሉይ ኪዳን ዘመን፥ ከነአዳም ዘመን ጀምሮ
ለመሥዋዕት ደም ይፈስስ ነበር። ደም ሕይወት አለበት፥ ነፍስ አለበት፤ ጥቂት
ጥቅሶችን ላሳይ፤
109
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
2. የመስቀሉ ትንቢት
ማቴ. 17፥ 22-23 በገሊላም ሲመላለሱ ኢየሱስ፦ የሰው ልጅ በሰዎች እጅ አልፎ ይሰጥ
ዘንድ አለው፥ ይገድሉትማል፥ በሦስተኛውም ቀን ይነሣል አላቸው። እጅግም አዘኑ።
3. የመስቀሉ ድርጊት
112
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
113
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
114
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
115
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
116
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
117
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
መታየቱ
የአንዱ ተጠራጣሪ የቶማስ ምስክርነት ብቻውን እንኳ ትልቅ ነው። ቶማስ ጠርጣሪና
አእምሮውን የሚተማመን ሰው ነበረ። ካየው በኋላ ግን ጌታዬና አምላኬ ነበር ያለውና
የሰገደለት፤ ዮሐ. 20፥28።
የሮም ፍርድ
119
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
የተጻፈው ቃል
መጽሐፍ ቅዱስና ቁርኣን እርስ በርሳቸው ይቃረናሉ። ማናቸውም ሁለት ነገሮች እርስ
በርስ ከተቃረኑ ወይ ሁለቱም ስሕተት ሊሆኑ ይችላሉ፤ ወይም ከሁለቱ አንዱ ብቻ
ትክክል ነው እንጂ ሁለቱም እርስ በርስ የሚቃረኑ ነገሮች በአንድ ጊዜ ትክክል ሊሆኑ
አይችሉም። ቁርኣንና መጽሐፍ ቅዱስ ክርስቶስን፥ ስቅለቱን ሞቱንና ትንሣኤውን
በተመለከተ የተራራቁ ሳይሆኑ ፈጽሞ የተቃረኑ ናቸው። ተሰቅሏል፤ አልተሰቀለም።
ሞቷል፤ አልሞተም። ተነሥቷል፤ አልተነሣም ነው ልዩነቱ። ይህ ከሆነ የክርስቶስን
ሞትና ትንሣኤ በተመለከተ ከሁለቱ አንዱ ብቻ ትክክል ነው እንጂ ሁለቱም ትክክል
ሊሆኑ አይችሉም።
የአይሁድ አለማስተባበል
120
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ሰንበት
ጳውሎስ
121
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
ጳውሎስ ክርስትናን እንደፈጠረ ወይም እንደቀረጸ የሚገምቱ ሰዎች ነገር እውነት ከሆነ
ጳውሎስ ይህንን ክርስትና የተባለ ተረት ፈጥሮ፥ እርሱ ለፈጠረውና እውነት ላልሆነው
ተረት ነው እንዲያ የተንገላታውና ዋጋ የከፈለው ማለት ነው? የመጨረሻው የከፈለው
ዋጋ ደግሞ ነፍሱን መስጠቱ ነበር። ማነው ለተፈጠረ ውሸት፥ ያውም ራሱ ለፈጠረው
ውሸት የሚሞት? ራሱ ለፈጠረው ውሸት የሚሞት ሰው ካየን ዕብድ ሰው አየን ማለት
ነው። የጌታን ሐዋርያት ስናስተውላቸው ውሸት ሕያው ሆኖ እንዲቆይ ብለው ለውሸት
ነፍሳቸውን የሚሰጡና ራሳቸውን የሚሸጡ ሳይሆኑ ውሸትን የሚጸየፉ ሰዎች
ለመሆናቸው በቃሉ ውስጥ የምናያቸው ታሪካቸው ይመሰክራል።
122
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
123
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
መደምደሚያ
እንደ መደምደሚያ ቃል የኢየሱስን አንድያነት በመናገር ልጨርስ። አንድያ ልጅ
የሚለው ቃል ለክርስቶስ መግለጫ ሲሆን መሳይ ወይም ቀዳሚና ተከታይ የሌለው
መሆኑን የሚያሳይ ቃል ነው። በብሉይ ኪዳን ቋንቋ ለሰዎችም የተጠቀሰ ቃል ሆኖ
ብቸኛ ልጅን ያመለክታል፤ ለምሳሌ፥ ኤር. 6፥26፤ አሞ. 8፥10፤ ዘካ. 12፥10። ቃሉ
ּ יָחִידያኺይድ አንድና ብቸኛ መሆንን እንዲሁም የተወደዱ መሆንንም ያሳያል።
በመዝ. 22፥20 ብቻነት፥ በመዝ. 68፥6 ብቸኞች የሚለውም ቃል ከዚህ አንድ ነው።
በዘፍ. 22፥2፥12፥16 ብቸኛ ሳይሆን ልዩ ወይም የተወደደ ልጅነትን ያሳያል። ይህንኑ
ታሪክ የዕብራውያን ጸሐፊ በአዲስ ኪዳን አንድያ ልጅነት አድርጎ ያቀርበዋል፤ ዕብ. 11፥
17።
124
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ
(μονογενής) እርሱ ተረከው። ዮሐ. 1፥18
በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር
ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን (μονογενής) ወደ ዓለም ልኮታልና። 1ዮሐ. 4፥9
ሌሎች የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው የተጠሩ አሉ፤ ለምሳሌ፥ እስራኤል እንደ አንድ
ሕዝብ በዚህ ስም ተጠርተዋል፤ ዘጸ. 4፥23። እኛም የክርስቶስ ተከታዮች
የእግዚአብሔር ልጆች ነን፤ ዮሐ. 1፥12፤ 11፥52፤ ሮሜ 8፥14-21፤ ገላ. 3፥26፤ ፊል. 2፥
14-15፤ 1ዮሐ. 3፥2። ይህ ልጅነት እኛ በክርስቶስ በኩል ያገኘነው ልጅነት ሲሆን
ብቸኛና መሳይ የለሽ ልጅነት አይደለም። የክርስቶስ μονογενής ወይም አንድያ ልጅ
መሆን ብቸኛና መሳይ የለሽ ልጅነት ነው። የአብ አንድያ ልጅ ሲባል በሥላሴ ውስጥ
ያለው ዘላለማዊ ስፍራና ባህርይ እንጂ ልጅ ከአባት በኋላ እንደሚገኝ አብ ቀዳሚ
ወልድ ተቀዳሚ ማለት አይደለም። አብ አስቀድሞ የነበረ፥ ወልድ ቀድሞ ሳይኖር
ቆይቶ ኋላ መኖር የጀመረ ማለት አይደለም።
125
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
126
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
Klein, William W., Blomberg, Craig L., and Hubbard, Robert L.,
Jr. Introduction to Biblical Interpretation, Copyright © 1993,
2004, 2017 by ZONDERVAN, ePub Edition Edition ©
February 2017.
127
የቁርኣኑ ዒሳ የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ አይደለም።
128