Professional Documents
Culture Documents
ፐፕረሮ
ፐፕረሮ
ነገር ግን ጥበቡ ዘመነኛ ቅርጹን የያዘው ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ከ 2500 ዓ/ዓ በፊት መጀመሪያ
በግብጽ የአባይዶስ (Abydos ) ሀይማኖታዊ ክብረ በአል ላይ ከሚቀርቡ የመስዋእት ዝማሬዎች
ሲሆን ቀጥሎም በዋናነት የድራማ ቅርጽ የያዘው ደግሞ በግሪክ አቴንስ ይከወን በነበረው የዳይኖሲያ
አመታዊ የመስዋእት ክብረ በአል ላይ ይከወኑ ከነበሩ ድራማ መሰል መዝሙር አቀፍ ሁነቶች መሆኑን
ማወቅ ይቻላል፡፡ ከዚህ ሀሳብ በመነሳት ፎክሎር የዘመናዊ ድራማ ቀደምት አባት ወይም መነሻ ምንጭ
ነው ለማለት እንችላለን፡፡
ፎክሎራዊ ጉዳዮች ከዚህ ቀጥሎ በነበሩት ወርቃማ የግሪክ ድራማ ዘመናትም ቢሆን የታሪክ ፣ የገጻ
ባህሪ ፣ የመቼት እነዲሁም የሀሳብ ምንጭ ወይም መነሻ በመሆን አገልግለዋል፡፡
በሀገራችንም ከመጀመሪያው ዘመናዊ ቴአትር ጽሁፍ ጀምሮ ፎክሎራዊ ሀሳቦች በተለያየ መልክ ኪነ ጥበባዊ ፋይዳቸውን
ገልጠው ተመልክተናል፡፡ በዚህም ግዜ የተውኔት አንድ ዘውግ በሆነው ትውፊታዊ ቴአትር ውስጥም ልዩ ልዩ የሆኑ
ፎክሎራዊ ጉዳዮች ኪናዊ ለዛን ተላብሰው ይቀርባሉ፡፡
ከዚህም በመነሳት እነዚህ ፊክሎራዊ ጉዳዮች በኢትዮጲያ ትውፊታዊ ቴአትር ውስጥ ያላቸው ጥቅል
ኪነ ጥበባዊ ፋይዳ በምን መልክ እንደሚገለጥ በሳይናሳዊ መንገድ ለመተንተን ይህን ርእሰ ጉዳይ
መርጫለው፡፡
በዚህ ርእሰ ጉዳይ ይህን ጽሁፍ ለማቅረብ ያሰብኩትም ይህንን እንደ የቃቄ ወርደወት መሰል ጀግና
ከዘመናቸው የቀደሙ ተራማጅ ሴቶችን የፈጠረውን ማህበራዊ ተቋም ለማስተዋወቅ እንዲሁም
ምናልባትም በሌሎች አካባቢዎች ባልተለመደ ሁኔታ በጉራጌ ማህበረሰብ ውስጥ ለሴቶች የሚሰጥን
ከፍተኛ አዎንታዊ ግምት እና ሴቶቹም በማህበራዊ መዋቅሩ ውስጥ ያላቸውን የላቀ ሚና ለማሳየት
በማሰብ ነው፡፡
ከዚህ መደበኛ የፍትህ ስርአት መዘርጋት እቀድሞ በሀገራችን በሚገኙ ሁሉም ማህበረሰቦች የአካባቢውን ሰላም
ለማስጠበቅ፣ ፍትህን ለማስፈን፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚአዊ መስተጋብሩን በአግባቡ ለማስቀጠል፣ በህዝቦች
መካከል መተማመንን ለመፍጠር እና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ባህላዊ የፍትህ ተቋማት ወይም
ስርአቶች ይገኛሉ፡፡
የጉራጌ ክፍለ ህዝብም ለዘመናት ሰላሙንና ውስጣዊ አንድነቱን ጠብቆ በዙሪያው ካሉ ሌሎች ማህበረሰቦችም
ጋር ተከባብሮ እና ተግባብቶ እንዲኖር፣ ጠንካራ የስራ ባህሉን ይበልጥ እንዲያዳብር እንዲሁም በተለያየ
ምክንያት የተፈጥሮም ሆነ ሰው ሰራሽ አደጋዎች ሲከሰቱ ፈጣሪን የሚለማመንበት እርቅ የሚወርድበት
ስርአቱ ነው ኬርታ፡፡
ይህ የኬርታ ስርአት የጉራጌ ክፍለ ህዝብ ለዘመናት ሲጠቀምበት የኖረ ሲሆን አሁንም ድረስ በሰባቱ የጉራጌ
ማህበረሰቦች መካከል የሚፈጠሩ ውስጣዊ ግጭቶችን እንዲሁም ከሌሎች ማህበረሰቦች ጋር ሊኖሩ የሚችሉ
ግጭቶችን በማክሰም የተጣሉ የሚታረቁበት፣ የበደሉ የሚክሱበት፣ ተራርቀው የሚኖሩ የሚገናኙበት፣ በቀደ
ዘመን የተሰራ ግፍ ጡር የሚወጣበት የማህበረሰቡ በጎ እሴቶች የሚበረታቱበት እና በውስጡ በርካታ ባህላዊ
ስርአቶች የሚከወኑበት የሰላም መድረክ ነው፡፡
እኔም በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ ይህን ጽሁፍ ለማቅረብ የተነሳሁት የባህላዊ ስርአቱን የተለየ አከዋወን ለማሳየት፣
ስርአቱ ለማህበሩ የሚሰጠውን አዎንታዊ ግልጋሎት በግልጥ ለማሳየት እንዲሁም በአሁኑ ግዜ ማህበረሰቡ
በተለያዩ አካላት እየደረሰበት ያለውን ውስጣዊ የመከፋፈል አደጋ ይህን ማህበራዊ ተቋም ተጠቅሞ እንዴት
እንደተቋቋመው ለማሳየት በማሰብ ነው፡፡