You are on page 1of 11

አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለመከበር ምክንያቱ ምንድን ነው ?

በፌደራል ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ የህዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ


ለአለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8) መከበር ምክንያት የተጠነሰሰው በ 18 ተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ እንደነበር
የተለያዩ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ በ 1857 እ.ኤ.አ. በአሜሪካ ኒውዮርክ ከተማ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ሴት ሰራተኞች
የአነስተኛ የደሞዝ ክፍያንና ለጤና ምቹ ያልሆኑ የሥራ ሁኔታዎችን በመቃወም በከተማዋ ዋና ዋና ጐዳናዎች ሠላማዊ
ሠልፍ አካሄዱ፡፡
በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን ሴቶች ሰብአዊ መብቶቻቸውን ለማስከበር ተቃውሞ የጀመሩበት ወቅት ነበር፡፡ በኢንዱስትሪ
በበለፀጉ አገሮች ዘንድ የሠራተኛው ቁጥር ሥርአተ ጾታዊ ስብጥር በከፍተኛ ደረጃ ሚዛናዊ ያልነበረ ከመሆኑ የተነሣ
በአብዛኛው በጣም ትንሽ የሚሆኑት የየኢንዱስትሪው ሴት ሰራተኞች ለ 191 ዐሩ ታሪካዊ ኮንፈረንሰ ቅድመ ሁኔታ
መሟላት ምክንያት ነበሩ፡፡ በተለይም በጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎችና በማምረቻ ቦታዎች የሚሰሩ ሴት ስራተኞች ለጤና
በማይስማማ የሥራ ቦታ ይመደቡ የነበር ከመሆኑም በላይ እጅግ አነስተኛና የዕለት የኑሮ ሕይወታቸውን ለመምራት
በማያስችል ክፍያ ይሠቃዩ ነበር፡፡
በዚህም የተነሣ የሴት ሠራተኞቹና ተባባሪ ወንድ አጋሮቻቸው በሚያደርጉት አመጽ በኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ ላይ
ተደጋጋሚ የሆነ ኪሣራ መድረሱ እየተባባሰ ሄደ፡፡ የሠራተኛው ማህበራት እየተጠናከረ መምጣት በሌላ በኩል ለሴቶች
እንቅስቃሴ አጋዥነቱን እያጐላው መጣ፡፡ በአውሮፖ፣ በታላቋ ብሪታንያ፣ በአሜሪካና በትንሹም ቢሆን በአውስትራሊያ
ሴቶች የመምረጥና መመረጥ መብታቸው እንዲከበር የሚመለከታቸውን ሁሉ ማግባባት የጀመሩት በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን
ነበር፡፡ ይህ ትግላቸው በሴቶች ዙሪያ ይታዩ የነበሩ ማንኛውም ጭቆናዎች እንዲወገዱ አመላካች ከመሆኑም ሌላ ተጨባጭ
ለውጥ እንዲከሰት በር ከፋች ሆነ፡፡
በ 19 ዐ 3 በአሜሪካ የሠራተኞች ማህበራትንና ነፃ የሴቶች ማህበራት የሴቶችን በምርጫ የመሣተፍ መብት በመደገፍ
የሴቶችን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬ እንዲመጣ ለመርዳት የሚያስችል የሴት ሠራተኞች ማህበራት ሊግ ተመሠረተ፡፡
በ 19 ዐ 8 አሜሪካ ውስጥ በየካቲት ወር የመጨረሻው ሳምንት ዕሁድ ቀን የአሜሪካ ሶሻሊስት ሴቶች ሰላማዊ ሠልፍ
በማደራጀት ለመጀመሪያ ጊዜ “የሴቶች ቀን” በሚል አከበሩ፡፡ የሠላማዊ ሠልፉ ጥያቄ የምርጫ መብትን የሚመለከት ብቻ
ሣይሆን ፖለቲካዊና ኢኰኖሚያዊ መብቶቻቸውንም የማረጋገጥ ጭምር ነበር፡፡ በ 19 ዐ 9 እንደዚሁ በአሜሪካ ወደ
3 ዐ,ዐዐዐ የሚጠጉ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ ሴት ሠራተኞች ሠላማዊ ሠልፍ በማደራጀት ለ 13 ሣምንታት የቀጠለ
የሥራ ማቆም አድማ መቱ፡፡ የዚህ ሠላማዊ ሠልፍ አመጽ የተሻለ ክፍያና ምቹ የሥራ ሁኔታ ጥየቃ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ
የተቋቋመው የሴት ሠራተኞች ማህበራት ሊግ አመጹን ለማስተባበርና በአመጹ ምክንያት ለታሠሩ ሴቶች የገንዘብ ድጋፍ
በማድረግ እንቅስቀሴውን አግዟል፡፡
በ 191 ዐ የሴቶች ቀን እንዲከበር በመላዋ የአሜሪካ ግዛቶች በሚኖሩ የሴት ሶሻሊስቶችና ፌሚኒስቶች ዘንድ ተቀባይነትን
አገኘ፡፡ በ 191 ዐ እንደዚሁ በዴኒማርክ ኮፐን ሃገን ከተማ በተደረገው 2 ኛው አለም አቀፍ የሴቶች ሶሻሊስት ኮንፈረንሰ
ላይ የሴቶች ቀን አለም አቀፍ ተቀባይነት ኖሮት እንዲከበር ከሴት ሠራተኞች ማህበራት ሊግ ተወካዮች ሃሳቡ ቀረበ፡፡
አሜሪካ በሴት ሠራተኞች የትግል እንቅስቃሴ በመመሰጥና የራሷን ድርሻ ለመወጣት በማሰብ በአመት አንድ ቀን የሴቶች
ዓለም አቀፍ ቀን ሆኖ በ 2 ኛው አለም አቀፍ የሶሻሊት የሴቶች ኮንፈረንስ ቀርቦ ከ 17 ሀገሮች በመጡ የሠራተኞች
ማህበራት፣ የሶሻሊስት ፓርቲዎች፣ የሴት ሠራተኞች ክበብ ተወካዮች ዘንድ ያለምንም ድምጽ ልዩነት ሀሳቡ ተቀባይነት
አገኘ፡፡ በኮንፈረንሱ የሴቶች በምርጫ የመሣተፍ መብት ጠቀሜታው ከፍተኛ እንደሆነ እንደገና ተረጋገጠ፡፡
የጀርመኗ ክላራ ዜተኪን እና የሩሲያዋ አሌክሳንድራ ኰሎንታይ የሴቶች በምርጫ የመሣተፍ መብት አስገዳጅና ለብቻው
ራሱን ችሎ የሶሻሊስት ፕሮግራም አካል ሆኖ መታየትና መረጋገጥ እንደሚገባ ታግለዋል፡፡ በኮፐን ሀገን ኮንፈረንስ ውሳኔ
መሠረት ማርች 19/1911 የሴቶች ቀን ሆኖ በኦስትሪያ፣ በዴኒማርክ፣ በጀርመን እና በሲውዘርላንድ መከበር ጀመረ፡፡
በዚሁ ቀን ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሴቶችና ወንዶች በአሉን ያከበሩት ሲሆን መሠረታዊ ጥያቄአቸው በሴቶች የመምረጥ
መመረጥ መብት ብቻ ሣይሆን፣ የሙያ ክህሎቶቻቸውን የማጐልበትና ፆታን መሠረት ያደረገ መድልኦና ልዩነት
እንዲወገድም መታገል እንዳለባቸው በማመላከት ጭምር ነበር፡፡
በመጀመሪያው የአለም ጦርነት ዋዜማ ወቅት ከ 1913-1914 የፖስፊስት እንቅስቃሴ ተግባሩን ማከናወን እንደጀመረ
የሩሲያ ሴቶች ለመጀመሪያ ጊዜ በ 1913 የካቲት ወር የመጨረሻው ዕሁድ ዕለት የሴቶች ቀንን አከበሩ፡፡ ከዚያን ጊዜ
ጀምሮ በአውሮፖ በማንኛውም ቦታ በየአመቱ የማርች 8 ዕለት ወይም በዚሁ ዕለት አካባቢ ጦርነትን በመቃወምም ሆነ
ሰላምን በሚሰብክ መንገድ ሲከበር ቆይቷል፡፡
በ 1917 ቱ የሩሲያ አብዮትና በአንደኛው የዓለም ጦርነት ሳቢያ ከ 2 ሚሊዮን በላይ ወታደሮች ከማለቃቸው ጋር ተያይዞ
የሩሲያ ሴቶች ጦርነቱ እንዲያበቃ በመቃዎም ጥያቄያቸው “ዳቦና ሰላም” መሆኑን በሰላማዊ ሰልፍ አስተጋቡ፡፡ በጊዜው
የሩሲያ ከፍተኛ የፖለቲካ አካል አመጹን ቢቃወምም ሴቶች በአመጹ ከመቀጠል ወደኋላ አላሉም፡፡ ከዚህ አጋጣሚ 4
ቀናት በኋላ የሩሲያ ዛር /መንግስት/ ሥልጣኑን እንዲለቅ አስገዳጅ ሁኔታ በመፈጠሩ ሥልጣኑን ለቀቀ፡፡ በምትኩ ጊዜያዊ
ስልጣን የተረከበው አዲሱ መንግስት የሴቶችን የመምረጥ መብት ተቀበለ፡፡ የሴቶች ትግል ሥር እየሰደደና በመላው ዓለም
በመስፋፋቱ ለጥያቄአቸው ተገቢ ምላሽ ለማግኘት እልህ አስጨራሽ እንቅስቃሴያቸው ተፋፍሞ ቀጠለ፡፡
አለም አቀፍ የሴቶች ቀን እ.ኤ.አ. ከ 1910 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ሐገራት መከበር ቢጀምርም በሩሲያ የ 1917 አብዮት
ወቅት በሴቶች አመጽ አስገዳጅነት መንግስት የሴቶችን መብት የተቀበለበትና በዓሉ የተከበረበት ታሪካዊ የመጨረሻ ቀን
የካቲት ዕሁድ የነበረው በ 1917 የካቲት 23 እንደ ጁሊያን አቆጣጠር ወይም እንደ ጐርጐሪያን አቆጣጠር ማርች 8
ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ከ 3 ዓመታት በኋላ በ 1921 ማርች 8 አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ይፋ ሆኖ መከበር ጀመረ፡፡
የተጋጋለው የሴቶች ቀን ተፋፍሞ ባለበት በመቀጠል በ 1977 እ.ኤ.አ. የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም ማርች 8 አለም
አቀፍ የሴቶች ቀን ሆኖ እንዲከበር መወሰኑን የተለያዩ የታሪክ ድርሳናት ይጠቁማሉ።
St. Peter's Specialized Hospital ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
8. März 2018 ·
አለም አቀፍ የሴቶች ቀን በየዓመቱ የካቲት 29 ቀን በመላው ዓለም ይከበራል:: በዓሉ በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን የተደረገ ትግልን
አስመልክቶ የተጀመረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን በተለያዩ ሀገት በተለያዩ ሁኔታ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ የተለያዩ ሀገራት
በተለያየ ሁኔታ ቢያከብሩትም በዋነኛነት ግን ሴቶች በኢኮኖሚያዊ በፖለቲካዊ እና በማህበራዊ እኩል ተሳትፎዋቸውንና
ተጠቃሚነታቸውን እውቅና በመስጠት ይከበራል፡፡ የህግና የሰብዓዊ መብታቸውንና ነፃነታቸውን ለማስከበር ጾታዊ ጥቃትን
ለማስቆም የሚደረግ ትግልን ይዘክራል እንዲሁም የሴቶችን ሁለንተናዊ እኩልነትና ሰላምን ለማምጣት ትግል ያደረጉ ሴቶችን
በማሰብ በትግል ታሪክ ያላቸውን ቦታና የከፈሉትን መስዋትነት ዕውቅና የሚሰጥ ቀን ነው፡፡
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ ታሪካዊ ቀን ሆኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ መከበር የጀመረው በአውስትራሊያ፣
ዴንማርክ፣ ስዊድንና ጀርመን እ.ኤ.አ በ 1911 ነበር፡፡ ዘንድሮ በአለም ደረጃ ለ 107 ኛ በአገራችን ደግሞ ለ 42 ኛ ጊዜ
ይከበራል፡፡ የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዓል ‹‹በተደራጀ የሴቶች ተሳትፎና ንቅናቄ የሴቶችን ሁለንተናዊ
ተጠቃሚነት እናረጋግጥ›› በሚል መሪ ቃል ይከበራል፡፡ በአለም ላይ የሚገኙ ሴቶች ዘር ቀለም ቋንቋ ሃይማኖት እና መልካ-
ምዕድራዊ ድንበር ሳይወስናቸው ለነጻነታቸው፣ ለሰብዓዊ እኩልነታቸው፣ ለፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው
መረጋገጥ በአንድ ድምጽ ይጮኻሉ፡፡
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ታሪካዊ አመጣጥ
1909 እ.ኤ.አ
አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ የተከበረው በሰሜን አሜሪካ እና በአውሮፓ ሀገሮች ነው፡፡ እ.ኤ.አ 1909 በአንድ
የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች የነበረውን አነስተኛ ክፍያና ረጅም የስራ ሰአት በመቃወም የተደረገውን
ትግል ለማሰብ ነበር፡፡
1910 እ.ኤ.አ
ሶሻሊስት ኢንተርናሽናል የተባለው ድርጅት በዴንማርክ ሁለተኛው የሴቶች ኮንፍረንስ በኮፐንሀገን ሲያካሄድ ስብሰባውን
ትመራ የነበረችው ክላራዜትኪን ትባል የነበረች ጀርመናዊት ሴት የአለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ሃሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ ስታቀርብ
ቀኑ በአለም አቀፍ ደረጃ በተመሳሳይ ቀን እንዲከበር ቀኑም የሴቶች ቀን እንዲባል ሃሳብ አቀረበች ፡፡ ሃሳቡንም ከ 17 ሃገራት
የተውጣጡ 100 የሚሆኑ የስብሰባው ተካፋዮች ተቀበለው ቀኑን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን አሉት ፡፡ የኮምፐንሃገኑ ውሳኔ
የሴቶች መምረጥና የመመረጥ መብትን እንዲረጋገጥ በሁሉም ሃገሮች ተቀባይነት እንዲኖረው አጥብቆ አስተጋብቷል፡፡
1911 እ.ኤ.አ
የኮፐንሀገን ሰብሰባ መነሻ አድርጎ በኦስትሪያ፣ በዴንማርክ፣ ሲውዘርላንድና ጀርመን አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ
ማርች 19 ተከብሮ ዋለ በእለቱ ከ 1,000,000 በላይ የሚሆኑ ሴቶች የተገኙ ሲሆን የመምረጥና የመመረጥ መብት ጨምሮ
የመስራትና የሙያ ስልጠና መብት እንዲረጋገጥላቸውና በስራ ገበታ ላይ በሴቶች ላይ የሚፈጻሙ አድልዎች እንዲቆሙ
ጠየቁ፡፡ እስከ አሁን ድረስ በዚሁ ቀን እየተከበረ ይገኛል፡፡
1913-14 እ.ኤ.አ
የሩሲያ ሴቶች አለም አቀፉን የሴቶች ቀን የመጀመሪያው የአለም ጦርነት ከመጀመሩ ቀደም ብሎ በየካቲት ወር መጨረሻ
እሁድ የሰላም ስብሰባ አድርገው ነበር፡፡ በዚሁ አመት በተደረገ ስብሰባ ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ ማርች 8
እንዲሆን ተስማሙ፡፡ በሀገራችን የሴቶች እኩልነት እንቅስቃሴዎች በይፋ መታየት ከጀመሩ አያሌ አመታት ተቆጠረዋል
ለዚህም የተለያዩ ፖሊሲዎች ፣ሕጎችና ደንቦች ተቀርጻዋል በአሁኑ ጊዜም ተግባራዊ የሆነው የቤተሰብ ህግ ለዚህ ማሳያ
ቢሆንም በየቤቱና በየማዕዘናቱ ለሴቶች መብት ያለው ግንዛቤ እዚህ ደረሰ የሚያሰኝ አይደለም በብዙ ሀገራት እንደታየው
የሴቶች መብት እድገት አዝጋሚና እና በግማሹ የህብረተሰብ ክፍል ዘንድ እንኳን በቂ ግንዛቤ ያላገኘ ነው፡፡ ለዚህም የተለያዩ
ምክንያቶችን መጥቀስ ቢቻልም የግንዛቤ ማነስና የአመለካከት አቅጣጫዎቹ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ብዙዎቹ የሴቶችን የመብት
እኩልነት የማስከበር እንቅስቃሴን የሚያዩት እንደ ጥቅም ፍላጎትና እንደፈለጉ ወጥቶ የመግባት፣ ያለመስራት ወይንም የወንዱን
ክብር እንደመጣስ አድርገው ያዩታል፡፡ ሀቁ ግን የሴቶች እኩልነት ማለት እኩል የትምህርት ፣የጤና እና የስራ እድል አግኝቶ
የበኩሉን በማበርከት ወንዱን የማገዝ እና ሀገርን የማልማት ጉዳይ ነው፡፡ ግማሽ የህብረተሰብ ክፍል መስራትና ማበርከት
የሚችለውን ሳያቀርብ ልማትን መጠበቅ አይቻልም፡፡
33333333333333333333333333333

ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን
አጋሩ




አስተያየቶችን ይዩ
Print
በሴቶች ጉዳዮች በኩል የታዩ መሻሻሎች የሚንጸባረቁበት፣ አስፋላጊ ለውጦች እንዲደረጉ ጥሪ የሚቀርብበት፣
በዓለም ደረጃ ለጾታ እኩልነት ለሚሰሩ ሴቶች ብርታትና ቁርጠኝነት እውቅና የሚሰጥበት እለት ነው።
ዋሽንግተን ዲሲ —
ዛሬ እ.አ.አ. አቆጣጠር ማርች ስምንት ማለት መጋቢት ስምንት በዓለምአቀፍ ደረጃ የሚከበር የሴቶች ቀን
ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እ.አ.አ. በ 1975 ዓ.ም. ዕለቱን የሴቶች መብትና የዓለምአቀፍ ሰላም
የሚታሰብበት እንዲሆን ሰየመው። በ 1977 ዓ.ም. ደግሞ በመንግስታቱ ድርጅት በውሳኔነት ጸደቀ።

በሴቶች ጉዳዮች በኩል የታዩ መሻሻሎች የሚንጸባረቁበት፣ አስፋላጊ ለውጦች እንዲደረጉ ጥሪ የሚቀርብበት፣
በዓለም ደረጃ ለጾታ እኩልነት ለሚሰሩ ሴቶች ብርታትና ቁርጠኝነት እውቅና የሚሰጥበት እለት ነው።
ሴቶችና ልጃገረዶች በዓለም ደረጃ የትምህርት እድል ለማግኘት፣ እኩልነታቸው በህግ ፊት እንዲከበር፣ ሴቶች
በባንክ ገንዘብ የማስቀመጥንና የማውጣትን፣ ስልጠናን የጎልማሶች ትምህርትን ለመሳሰሉት ወንዶች
ለሚያገኙት መሰረታዊ አገልግሎትም ተደራሽነት እንዲኖራቸው ስለሚያደርጉት ትግል እንዲታወቅ
የሚያስችልበት እለትም ነው። ሴቶች መሰረታዊ የሆነው ሰብአዊ መብታቸው እንዲከበርና የማንም ንብረት
ሳይሆኑ ነጻ ስዎች ተደርገው እንዲታዩ ሲታገሉ ኖረዋል።

ሴቶችና ልጃገረዶች ካለፉት 41 ዓመታት ወዲህ በተሻለ ሁኔታ ይገኛሉ። ግን አሁንም ቢሆን ብዙ የሚቀር ነገር
አለ። በዓለም ደረጃ በድህነት ከሚፈረጁት ሰዎች አብዛኞቹ ሴቶች ናቸው። በማንኛውም የዓለም ክፍል
የወንዶችን ያህል መብትና እድል አለን ሊሉ የሚችሉ ሴቶች የሉም። ስራቸው ተገቢ ዋጋ አያገኝም።
ከወንዶች ጋር በአንድ አይነት ስራ ላይ ተሰማርተው ወንዶች ከሚያገኙት ክፍያ በ 30 እና በ 40 ከመቶ ያነሰ
ነው የሚከፈላቸው። በኢኮኖሚ ራሳቸውን አለመቻላቸው ራሱ በሌላውም ህይወታቸው ሃይል
እንዳይኖራቸው ያደርጋል። በጾታ ላይ ለተመሰረተ ጥቃት ይጋለጣሉ።

EMBED SHARE
ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን አከባበር በዓለም ዙርያ
EMBED SHARE
The code has been copied to your clipboard.

640 360
width px height px
 Share on Facebook
 Share on Twitter

The URL has been copied to your clipboard


https://amha

No media source currently available

0:533:332:51
እ.አ.አ. እስከ 2030 ዓ.ም. በሚኖረው ጊዜ ውስጥ (በ 15 ዓመታት ጊዜ ውስጥ ማለት ነው) የሴቶች እኩልነት
የሚረጋገጥበት ጊዜ እንዲሆን፣ በያዝነው ዓመት ትኩረት ተሰጥቶበታል።
ይህም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በ 15 ዓመታት ውስጥ ዘላቂ የልማት አጀንዳ እንዲኖር ያወጣው እቅድ
አካል ነው። ድርጅቱ የጾታ እኩልነትና ሰብአዊ መብት እንዲከበር እንዲሁም ሴቶች ራሳቸውን እንዲችሉ
ለማደረግ ካለው ቁርጠኛነት ጋር የተያያዘ ነው።

ይህም በሴቶች ላይ የሚደረግ ማንኛውም አይነት አድልዎና ማንኛውም አይነት በሴቶች ላይ የሚፈጸም
ጥቃት እንዲቆም፣ ከእድሜ በታች የሆኑ ልጃገረዶችን በግዴታ መዳርና ግርዘት ማቆም የመሳሰሉትን
ያካትታል። ልጃገረዶችና ወንዶች ጥራቱ የተጠበቀ የትምህርት እድል እንዲያገኙ ማድረግም በድረጅቱ ግብ
ውስጥ ተካቷል።

ማንኛውም እድገት የሚፈልግ ማህበረሰብ ሴቶች ራሳቸው እንዲችሉ ከወንዶች ጋር እኩል መብት
እንዲኖራቸው ለማድረግ መጀመር ይኖርበታል።

ዛሬ ተከብሮ በዋለው ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን ለሴቶችና ልጃገረዶች ክብር በመስጠት ዓለም ሴቶችና
ልጃገረዶች የሚጨቆኑበት ሳይሆን መላ የብቃት መሰረታቸውን የሚተገበሩበት እንዲሆን ቆርጠን የምንነሳበት
እለት ነው ሲል የዛሬው ርእሰ-አነቀጽ ሀተታውን አብቅቷል።

የሴቶች ቀን ድሮና ዘንድሮ


22 March 2015

በጋዜጣዉ ሪፓርተር

የዓለም ሴቶች ቀን በየዓመቱ በውጮቹ አቆጣጠር ማርች 8፣ በኢትዮጵያ የካቲት 29 እየተከበረ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከ 1967
ዓ.ም. ወዲህ በየዓመቱ እያከበረችው ሲሆን፣ እንደወቅቱ ርዕዮተ ዓለም ፖስተሮች ሲዘጋጁለት ኖሯል፡፡ ከ 36 ዓመት በፊት
(1971 ዓ.ም.) በኅብረተሰብአዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ዘመን፣ በአዲስ አበባ የዓለም ሴቶች ቀንን
ለማክበር የተሠራጨውን (በግራ) እና ዘንድሮ የኢትዮጵያ ሴቶች ማኅበራት ቅንጅት በፖስተርና በፖስት ካርድ መልክ
ያሳተመውንና ያሠራጨው እዚህ ላይ ይመለከቷል፡፡ (ሔኖክ መደብር)
ሴቶች 'ፌሚኒስት' መባልን ለምን ይጠላሉ?
18 የካቲት 2019

የፎቶው ባለመብት,GETTY IMAGES


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የጾታ እኩልነት ጥያቄዎች ገፍተው ወደ አደባባይ እየመጡ ነው። በተለይም በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ ጉዳዩ ሰፊ ትኩረትና ሽፋን
አግኝቷል። ያም ኾኖ ብዙ ሴቶች 'ፌሚኒስት' መባልን አይሹም።
በአሜሪካና በእንግሊዝ በተደረጉ ተከታታይ የዳሰሳ ጥናቶች እንኳ ብንመለከት ከአምስት ሴቶች አንዷ ብቻ 'ፌሚኒስት' መባልን ትሻለች።
ያም ሆኖ በጾታ እኩልነት የሚያምኑ ሴቶች ቁጥር እጅግ ከፍተኛ ነው።
ሴቶችን አንድ ያደረጉ ንቅናቄዎች
በቅርብ ዓመታት ውስጥ ጾታዊ ንቅናቄዎች ዓለምን ከዳር እስከ ዳር አነቃንቀዋል። ዶናልድ ትራምፕ በ 2017 ሥልጣን ሲይዙ ሚሊዮኖች አደባባይ ወጥተው
ተቃውመዋቸዋል። የሰልፉ ዓላማ አደጋ ላይ ወድቆ የነበረውን የሴቶች መብትን መከላከል ነበር።
• ታሪክ እየቀየሩ ያሉት ሴቶች
በሆሊውድ የሃርቬይ ዌንስን ቅሌት 80 ሴቶች ድምጻቸውን ካሰሙ በኋላ ዓለም 'ሚ ቱ' በሚለው ንቅናቄ ተናውጦ ነበር። ተዋናይት አሊሳ ሚላኖ ጥቃት
የደረሰባችሁ ሁሉ 'እኔም ተጠቅቻለሁ" በሉ ካለች ወዲህ በ 24 ሰዓታት ብቻ ግማሽ ሚሊዮን ሴቶች ምላሽ ሰጥተዋል።
ይህ ቁልፍ ቃል በ 80 አገራት መጠነ ሰፊ ንቅናቄን ፈጥሯል።
ከዚህ ክስተት በኋላ በርካታ ሴት ተዋንያን ፌሚኒስት መሆናቸውን ይፋ አደረጉ። ያም ሆኖ ጥናቶች አሁንም የሚበዙ ሴቶች 'ፌሚኒስት' የሚለው ቃል
እንደሚጎረብጣቸው ነው።
አሐዞች ምን ይናገራሉ?
በ 2018 በተደረገ አንድ ጥናት 34 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች ፌሚኒስት ነን ሲሉ ተናግረዋል። ይህ አሐዝ በ 2013፣ 27 በመቶ ብቻ ነበር። በቅርብ ዓመታት
ወደ አደባባይ የወጡ የጾታ እኩልነት ንቅናቄዎች ያመጡት ለውጥ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
አሐዙ በአውሮፓ አገራት መካከል እንኳ ሰፊ ልዩነት እንዳለ ያሳያል። መጠይቅ ከተደረገላቸው የጀርመን ሴቶች 8 ከመቶ ብቻ 'ፌሚኒስት' ነን ሲሉ በአንጻሩ
40 እጅ የሚሆኑት የስዊድን ሴቶች 'ፌሚኒስት' ስለመሆናቸው በኩራት ተናግረዋል።
• ሴቶችን ከመንቀሳቀስ የሚያግደው መተግበሪያ ሊመረመር ነው
ዋናው የጥናቱ ጭብጥ ስለምን ሴቶች 'ፌሚኒስት' መባልን ጠሉ የሚለው ነው። የጥናቱ አስገራሚ ገጽታ ደግሞ ራሳቸውን ፌሚኒስት ብለው መጥራት
የማይወዱ ሴቶች ብዙዎቹ በጾታ እኩልነት የማያወላዳ አቋም ያላቸው መሆኑ ነው።
43 በመቶ እንግሊዛዊያን፡ "ሴቶች ቤት መዋል አለባቸው"
27 ሺህ ሰዎች የተሳተፉበትና በ 2016 በአሜሪካ የተደረገ ሌላ ጥናት ከተጠያቂዎች ሁለት እጅ የሚሆኑ በጾታ እኩልነት የሚያምኑ ሆነው ተገኝተዋል።
በ 1977 ይህ አሐዝ አንድ አራተኛ ብቻ ነበር።
በተመሳሳይ በ 2017 በእንግሊዝ በተደረገ ሌላ ጥናት ከመቶ ስምንት እጅ የሚሆኑት ብቻ የሴቶች ሚና በቤት ውስጥ መወሰን ይኖርበታል ብለው
እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
• የተነጠቀ ልጅነት
ሴቶች ልጅ በማሳደግና ምግብ በማብሰል መወሰን አለባቸው ብለው የሚያምኑ ዜጎች ቁጥር በ 1984 ዓ.ም 43 ከመቶ ደርሶ እንደነበር ማስታወስ ያሻል።
ይህ አሐዝ የሚነግረን በዓመታት ውስጥ ትልቅ የአመለካከት ለውጥ መምጣቱን ነው።
ጥያቄው አሁንም በዚህ ሰፊ የአስተሳብ ሽግግር በተደረገበት ዘመን እንኳ 'ፌሚኒስት' መባል የማይወዱ ሴቶች ቁጥር ለምን ከፍተኛ ሆነ የሚለው ነው።

የፎቶው ባለመብት,GETTY IMAGES


ቃሉ አሉታዊ ገጽታን ተላብሷል
በ 2018 በተሠራ ሌላ የዳሰሳ ጥናት ከፍ ባለ የቢሮ ሥራ ላይ ያሉት ራሳቸውን 'ፌሚኒስት' ብለው ለመጥራት አያፈገፍጉም። ነገር ግን ዝቅተኛ ሥራ ላይ
በተሠማሩት መሀል ቃሉ እምብዛምም አይወደድም።
ሌላ ጥናት እንዳሳየው ደግሞ ፌኒዝም በነጮች ዘንድ ካልሆነ በሂስፓኒክ፣ በእሲያና በጥቁሮች ዘንድ ጥሩ ስም የለውም።
ሦስት እጅ የሚሆኑ ጥናቱ ላይ የተሳተፉ ሴቶች ፌሚኒዝም የነጭ ሴቶችን ሕይወት ያሻሻለ ነገር አድርገው ነው የሚወስዱት።
ሌላው ለቃሉ አለመወደድ ምክንያት ተደርጎ በጥናት የተወሰደው ነባር አስተሳሰቦች ለውጥ አለማሳየታቸው ነው።
ስካርሌት ከርቲስ በቅርብ ባሳተመችው ''Feminists Do not Wear Pink and Other Lies" በተሰኘው መጽሐፏ እንዳሰፈረችው ፌሚኒስቶች
በ 1920 ዎቹ ትዳር ያልቀናቸው፣ ወንድ ጠል፣ በወሲብ ምርጫቸውም አፈንጋጭ፣ እንዲሁም ወንዳወንድ ተደርገው ይታሰቡ እንደነበረና ይህ አስተሳሰብ
ከመቶ ዓመት በኋላም እንዳልተቀረፈ ታስረዳለች።
በዳሰሳ ጥናቱ ላይ የተሳተፉ ብዙዎቹ ሴቶችም ራሳቸውን 'ፌሚኒስት' ከሚል ቃል ማራቅ የሚሹት ሰዎች ከላይ በተጠቀሱት አሉታዊ መገለጫዎች የተነሳ
ነው።
ማርች 8፡ የዓለም የሴቶች ቀንን ማንና የት ጀመረው?
8 መጋቢት 2020
የፎቶው ባለመብት,AFP
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በተመለከተ ከመገናኛ ብዙኃን አለያም ከወዳጅ ሰምተው ይሆናል። ፅንሰ ሐሳቡ ምን ይሆን? መቼ ይከበራል? በዓል ወይስ
የተቃውሞ ቀን?
በተመሳሳይስ ዓለማቀፍ የወንዶች ቀንስ ይኖር ይሆን ? ዓለም አቀፋ የሴቶች ቀን በየዓመቱ መጋቢት ስምንት መከበር ከጀመረ ዘመናትን አስቆጥሯል፤
ለተጨማሪ መረጃዎች አብረውን ይዝለቁ፦
ታሪካዊ ዳራ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን የአመፅ እንቅስቃሴን መነሻ በማድረግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዘንድ እውቅናን ለማግኘት የበቃ በዓል ነው::
ወቅቱ እንደ አውሮፓውያኑ 1908 ነበር በኒውዮርክ ከተማ ነዋሪ የሆኑ 15,000 ሴቶች የተሻሻለ የሥራ ሰዓትና የደመወዝ ክፍያን እንዲሁም የመምረጥ
መብታቸው እንዲከበር አደባባይ የወጡት።
ከአንድ ዓመት በኋላም የአሜሪካ ማኅበራዊ ፓርቲ ዕለቱን የሴቶች ብሔራዊ ቀን በማለት አውጆታል።
ክላራ ዚክተን በተባለች ሴት አማካኝነት ደግሞ በዓሉ ዓለማቀፋዊ ቅርፅን እንዲይዝ በ 1910 ላይ በዴንማርክ ዋና ከተማ ኮፐንሀገን በተካሔደው ዓለማቀፋዊ
የሠራተኛ ሴቶች ኮንፍረስ ላይ ሐሳቡ ቀረበ።
ከአስራ ሰባት ሀገራት የተውጣጡ መቶ ተሳታፊ ሴቶች ሀሳቡን በጄ አሉት። ይህንንም ተከትሎ ኦስትርያ ዴንማርክ ጀርመንና ስዊዘርላንድ በዓሉን በ 1911
በማክበር ፈር ቀዳጅ ሆኑ።
ባለፈው የፈረንጆች 2011 ይሄው በዓል ለመቶኛ ጊዜ የተከበረ ሲሆን በዚህ ዓመት ሲታሰብ ደግሞ ለ 109 ኛ ጊዜ ነው ማለት ይሆናል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሴቶች ቀንን በ 1975 በይፋ ሲያከብር በዓሉ ዓለማቀፋዊ ይዘት ሊኖረው ችሏል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞም በ 1996 ተ.መ.ድ "ያለፈውን በማሰብ የወደፊቱን እናቅድ " የሚል መሪ ቃል ይዞ ተከብሯል።
በዚህ ዓመት ደግሞ " እኩልነት የሰፈነባት ዓለም ሁሉን ማድረግ ትችላለች " በሚል የሚከበር ሲሆን ለፆታዊ እኩልነት ህዝቦች በጋራ ተሳስበው እንዲሰሩ
የሚያሳስብ ነው።
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ሴቶች በማኅበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነትን ለማግኘት የተጓዙትን ጉዞም ያስታውሳል።
መቼ ይከበራል? ዛሬ ላይ በዓሉ መጋቢት በባጀ በ 8 ኛው ቀን ይከበራል። ይሁን እንጂ ክላራ በተባለቺው ሴት አማካኝነት ሐሳቡ ሲጠነሰስ የተቀመጠለት
ቋሚ ቀን አልነበረም።
የሩሲያ ሴቶች በ 1917 "ዳቦና ሰላም " በማለት ያነሱት የተቃውሞ እንቅስቃሴ የበለጠ ቅርፅ እንዲይዝ አድርጎታል።
ይሄው ለአራት ቀናት የዘለቀው አመፅ በጁላዊያኑ የዘመን አቆጣጠር ዕሑድ የካቲት 23 የሩሲያውን ቄሳር የሴቶችን የመምረጥ መብት እንዲፈቅድ ያስገደደ
ሲሆን በመንግሥት አስተዳደር ደግሞ እውቅና እንዲሰጥ ሆኗል ይህ እንግዲህ በጎርጎሳውያኑ የዘመን አቆጣጠር መጋቢት 8 መሆኑ ነው።

የፎቶው ባለመብት,GETTY IMAGES


ዓለማቀፍ የወንዶች ቀን በ 1990 ዎቹ እውቅናን ካገኘበት ዕለት ጀምሮ በየዓመቱ ህዳር 19 ይከበራል፤ ምንም እንኳን እስካሁን ድረስ በተመድ እውቅናን
ያላገኘ ቢሆንም ታላቋን ብሪታኒያ ጨምሮ ከ 60 አገሮች በላይ የሚያከብሩት ሲሆን አላማውም "የጎልማሶችና የህፃናት ወንዶች ጤንነት" ላይ በማተኮር ፃታዊ
ተግባቦትን ለማሻሻል ፆታዊ እኩልነትን ለማስፈንና አርአያ ለሚሆኑ ወንዶች እውቅና መስጠት" ላይ ያተኮረ ነው።
"ጎልማሶችና ህፃናት ወንዶች ላይ ተፅእኖ መፍጠር" የ 2019 ዓለም አቀፍ የወንዶች ቀን መሪ ቃል ነበር።
የሴቶች ቀን ዓለም አቀፍዊ አከባበር እንግዲህ የሴቶች ቀን በብዙ አገሮች ማለት ይቻላል ብሔራዊ በዓል ሲሆን በተለይ በሩሲያ ከዕለቱ ሦስት አራት ቀን
ቀደም ብሎ የአበባው ገበያ ይደራል።
በቻይና ደግሞ በመንግሥት አስተዳደር በመፈቀዱ አብዛኛው ሴቶች የግማሽ ቀን ዕረፍት የሚሰጣቸው ቢሆንም በአንፃሩ ደግሞ ይህንን የማያከብሩ
ቀጣሪዎችም ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።
ወደ ጣሊያን ስንመጣ ደግሞ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክቶ ሴቶች ምሞሳ የተሰኘውን በቢጫና ሮዝ ቀለማት ያሸበረቀ አበባ በገፀ በረከትነት ያገኛሉ።
ምክንያቱ በውል ባይታወቅም ይሔው ልማድ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በሮማ እንደተጀመረ ይታመናል።
በአሜሪካ ደግሞ መጋቢት ወር የሴቶች ታሪካዊ ወር ነው፤ የፕሬዝዳንቱ ቢሮም ለሴቶች ስኬትና ድል በየዓመቱ እውቅና ይሰጣል።
የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን "እያንዳንዳችን ለእኩልነት" የሚለውን መሪ ቃል ከፊት በማድረግ ይከበራል። የአብሮነት ህብርን እሳቤ በመመርኮዝ
የተመረጠ ነው የበዓሉ ዘመቻም " ሁላችንም ባለ አሻራዎች ነን" ይላል። የእያንዳንዳችን የተናጥል እንቅስቃሴ ባህሪና ሥነ ልቦና በማኅበረሰቡ ዘንድ
የሚኖረው ተፅእኖ ቀላል አይደለም።
በዚህ ህብረ ቀለምም ለውጥ ማምጣት እንችላለን፤ በአብሮነት ህብርም ፆታዊ እኩልነት እንዲሰፍን መረዳዳት እንችላለን " በማለት ያትታል።
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ይሔው ዓለም አቀፋዊ በዓል ታላቅ የሚባል እምርታ ላይ ደርሷል። ለአብነት በጥቅምት ወር 2017 #እኔም [#metoo] በማለት
የሴቶችን ፆታዊ ጥቃትና ትንኮሳ ለመቃወምና ለማውገዝ ሚሊዮኖች በማህበራዊ መገናኛ ገፆች ድምፃቸውን አሰምተዋል።
ይሔው #እኔም እንቅስቃሴ በ 2018 አድጎ አለማቀፍዊ ቅርፅ በመያዝ እንደ ህንድ ፈረንሳይና ደቡብ ኮሪያ ያሉ ሀገራት ይህንንኑ ዘመቻ ለለውጥ
ተቀላቅለዋል።
በአሜሪካ በሚደረገው የኘሬዝዳንቱ ሥልጣን ዘመን አጋማሽ ምርጫ ላይ የሴቶች ቁጥር ብልጫ የታየበት ነው። በሰሜን አየርላንድም የፅንስ ማቋረጥ
ኢህጋዊነት ሲሻር የሱዳን ሴቶች እንዴት መልበስና መንቀሳቀስ እንዳለባቸው የሚደነግገው ህግ ምሊቀየር ችሏል።

ወጣቶች
የዓለም የሴቶች ቀን በኢትዮጵያ
ኢትዮጵያው ውስጥ በሚመጣው እሁድ ማለትም የካቲት 29 ቀን የዓለም የሴቶች ቀን ይከበራል። የኢትዮጵያ ሴቶች
ህፃናት እና ወጣቶች ሚኒስቴር የዘንድሮው መሪ ቃል ደግሞ «የሴቶች ደህንነትና መብት መከበር ለሰላማችንና
ለህልውናችን መሠረት ነው » የሚል ነው።

Volume 90%

አውዲዮውን ያዳምጡ።10:14

የዓለም የሴቶች ቀን
በየዓመቱ በጎርጎሪዮሳዊው መጋቢት 8 ቀን የዓለም የሴቶች ቀን ይከበራል። ከዚህ የሴቶች ቀን ጋር በተያያዘ የመብት እና የእኩልነት
ጥያቄዎች አብረው ይነሳሉ። አንድ የዓለም ባንክ ጥናት እንደሚያመላክተው በዓለም ላይ 143 ሃገራት የሴቶች እና ወንዶች እኩልነትን
በሕገ መንግሥታቸው ላይ ያሰፈሩ ቢሆንም ስምንት ሃገራት ማለትም ቤልጄም፣ ካናዳ፣ ዴንማርክ፣ ሲውዲን፣ አይስላንድ፣
ሉክስንበርግ፤ ፈረንሳይ እና ሊትዌኒያ ብቻ ናቸው የሴቶች እና የወንዶች እኩልነት መብትን የሚያረጋግጡት። ጥናቱ ትኩረቱን
ያደረገውም ሥራን፣ የቤተሰብ፣ የንብረት ባለቤትነት፣ የጡረታን እና የመሳሰሉ ጥያቄዎች ላይ ተመርኩዞ ነው። የሚያሳዝነው ነገር
ግን እስካሁን በየትኛውም ሀገር የወንድ እና የሴቶች እኩልነት ሙሉ በሙሉ አለመረጋገጡን ነው የግሎባል ጀንደር ጋፕ መዘርዝር
የሚጠቁመው።
የዘንድሮው የተባበሩት መንግሥታት የዓለም የሴቶች ቀን መሪ ቃል "I am Generation Equality" ወይም «የእኩልነት ትውልድ ነኝ»
የሚል ነው። በርግጥ አዲሱ ወይም የአሁኑ የኢትዮጵያ ትውልድ እኩልነቱ ተረጋግጧል ብሎ ያምናል? DW ያነጋገራቸው ወጣቶች
እንደሚሉት በፊት ከነበረው ሁኔታ አሁን ላይ የተሻለ ነገር ነው ያለው። ኢትዮጵያ ውስጥ ከግንዛቤ ሁኔታ ጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያለው
የሚለው አንድ ወጣት ወደ ተግባር ሲመጣ ብዙ ተግዳሮቾች አሉ ይላል። « በተለይ ባለሁበት ባህር ዳር አካባቢ ገጠር የሚገኙ ሴቶች
ላይ የወንዶች ተፅዕኖ ከፍ ያለ ነው።» ይላል። ወንዶ ገነት የምትኖረው ወጣትም ይህን ትጋራለች « አንዳንድ አካባቢ ሴት ወጣቶች
ሰርተው እንዲለወጡ አያደርጓቸውም የቤት እመቤት ብቻ ሆነው እንዲቀሩ ነው የሚፈልጉት»
ወይዘሮ ስመኝ ውቤ በኢትዮጵያ ሴቶች ህፃናት እና ወጣቶች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴታ ናቸው። የሚሰሩበት መሥሪያ ቤት
የዘንድሮውን የዓለም የሴቶች ቀንን ያከበረው በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚከበርበት ዕለት አራት ቀን ቀደም ብሎ ነበር። « በዓሉን
በሁለት መልክ ነው ያከበርነው አንዱ ጥቃት ደርሶባቸው በተለያዩ ማዕከል ውስጥ ላሉ ሁለት ተቋማት ድጋፍ እንዲሰጡ በማድረግ
ሲሆን ሌላው ደግሞ የመድረክ ውይይት በማካሄድ ነበር። » ይላሉ የአለም የሴቶች ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ 109 ኛ ጊዜ
በኢትዮጵያ ደግሞ ለ 44 ኛ ጊዜ እየተከበረ እንደሆነ የሚናገሩት ሚኒስትር ዴታ። የተለያዩ የሃገሪቱ ባለድርሻ አካላት በተሳተፉበት
ይኸው ውይይት ላይ አሁንም ለሴቶች ፈተና ናቸው ተብለው የተነሱት ጉዳዮች ወይዘሮ ስመኝ እንደሚሉት ሴቶች ላይ
የሚፈፀመውት የተለያዩ ጥቃቶች ናቸው።
የዘንድሮው የሴቶች ቀን መሪ ቃል «የሴቶች ደህንነትና መብት መከበር ለሰላማችንና ለህልውናችን መሠረት ነው» የሚል ነው።
ሚኒስቴሩ ይህንን ርዕስ የመረጠበትንም ምክንያት በሀገሪቱ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ ነው ። « በሀገራችን በተለያዩ ምክንያት ግጭቶች
አሉ። በዚህ ደግሞ ዋንኛ ተጠቂ እየሆኑ ያሉት ሴቶች እና ህፃናት ናቸው» ይላሉ ወይዘሮ ስመኝ። መሥሪያ ቤታቸው ጥቃት
ከሚለው አንዱም የታገቱት ሴት ተማሪዎችን ጉዳይ ነው። « በሴቶች ላይ እንደዚህ አይነት ጥቃቶች የሚደርሱ ከሆነ የሚጎዳው
አጠቃላይ ማህበረሰቡ ነው። »
ሌላው የዘንድሮውን የዓለም የሴቶች ቀንን በሚመለከት የሴቶች ህፃናት እና ወጣቶች ሚኒስቴር ትኩረት እንዲሰጥበት ያለው ጉዳይ
የሴቶች የፖለቲካ ተሳትፎን በሚመለከት ነው።
« የሴቶች የፖለቲካ ለውጥን በሚመለከት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ለውጥ ነው ያለው» የሚሉት ወይዘሮ ስመኝ
«በመጪው ምርጫ ምን ያህሉ ፓርቲ ሴቶችን ወደ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ለማምጣት ጥረት ያደርጋል» የሚለው እንደሚያሳስባቸው
ተናግረዋል።

You might also like