You are on page 1of 9

ጀኔሪክ (GENERIC) አማካሪ መሀንዲሶች ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር

የመመሰረቻ ጽሑፍ

አንቀጽ አንድ

ምሥረታ

በሰነዱ ግርጌ ፊርማችንን ባሰፈርነዉ መካከል በኢትዮጵያ ንግድ ሕግ በዚህ መመሰረቻ ጽሐፍና ተያይዞ በሚገኘዉ የመተዳደሪያ ደንብ ስምምነቶች
የሚገዛና ዓላማዉም ከዚህ በታች በአንቀጽ 4 ሥር የተመለከተትን የንግድ ሥራ ተግባራት ማከናወን የሆነ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኀበር
ለመመሥረት ስምምነት ተደርጓል፡፡

አንቀጽ ሁለት

የአባላቱ ስም፣ ዜግነትና አድራሻ

አድራሻ
ዘግነት
ተ.ቁ

ሰም

ከተማ

ከተማ

የቤ.ቁ
ወረዳ
ክፍለ
አቶ አበበ ባንጃዉ ወንድምአገኘሁ
1 ኢትዮጵያዊ አ/አ ን/ስ/ ላፍቶ 12 አዲስ
(ADP in BLDG.ENG + BSc in COTM + MSc in COTM)
ወ/ሮ አፀደ አርሼ ዲዶ
2 ኢትዮጵያዊ አ/አ ን/ስ/ ላፍቶ 12 አዲስ
(ADP in BLDG.ENG)
ወ/ሪት አምሮት አንጀሎ አርሼ
3 ኢትዮጵያዊ አ/አ ን/ስ/ ላፍቶ 12 አዲስ
(BSc in CIVIL ENG. + MSc in COTM)
አቶ ደረጀ ባንጃዉ ወንድምአገኘሁ
4 ኢትዮጵያዊ አ/ም ሼቻ በሬ
(ADP in BLDG.ENG + BSc in CIVIL ENG.)
አቶ ተድላ ወርቁ አበራ
5 ኢትዮጵያዊ አ/ም ሼቻ
(BSc in ARCHITECTURE)
አቶ ዮሰፍ አሸናፊ አርሼ
6 ኢትዮጵያዊ አ/አ ን/ስ/ ላፍቶ
(BSc in CIVIL ENG.)
አቶ ክሩቤል አንጀሎ አርሼ
7 ኢትዮጵያዊ አ/ም ሼቻ
(BSc in CIVIL ENG.)
ወ/ሪት ዮኋና አምሳሉ አሰፋ
8 ኢትዮጵያዊ አ/ም ሼቻ
(BSc in CIVIL ENG.)
አቶ ዳግማዊ ነገዱ ባንጃው
9 ኢትዮጵያዊ አ/ም ሲቀላ
(BSc in MECHANICAL ENG.)
አቶ ዳኛቸው አማኑ ወንድምአገኘሁ
10 ኢትዮጵያዊ ሲቀላ
(DP in ELEC.ENG + BSc in CIVIL ENG.)
አቶ ሸበለው በድሉ ወንድምአገኘሁ
11 ኢትዮጵያዊ አ/ም ሼቻ
(ADP in Water + BSc in URM + MSc in COTM.)
አቶ በዕውቀቱ አወቀ አልቶ
12 ኢትዮጵያዊ አ/ም ሼቻ
(BSc in Wat t& Env + MSc in Hyd ENG.)
አንቀጽ ሦስት

የማኀበሩ፣ ስምና አድራሻ

1.1 የማኀበሩ ስም ጀኔሪክ (GENERIC) አማካሪ አርክቴክቶች እና መሀንዲሶች ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ነዉ፡፡
1.2 አባላቱ ወደ ፊት በሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞችም ሆነ ከኢትዮጵያ ዉጭ ቅርንጫፍ የመክፈት
መብታቸዉ አንደተጠበቀ ሆኖ የተመዘገበዉ የማኀበሩ ዋና መሥሪያ ቤት በአዲስ አበባ ከተማ
ን/ስ/ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 02 የቤት/ቁ አዲስ ዉስጥ ነዉ፡፡

አንቀጽ አራት

የማኀበሩ፣ የንግድ ሥራ ዓላማዎች

ማኀበሩ የተቋቋመበት ዓላማዎች፣

1. አርክቴክቸራል እና ኢንጂነሪንግ ዲዛይን ስራዎችን መስራት፣


2. የጤና፣ የትምህርት ተቋም፣ የኢንዱስትሪ፣ የእርሻ፣ የስፖርት እና የመዝናኛ ማዕከሎች፣ የሆቴልና ሪዞርት፣
የላንድ ስኬፕ አርክቴክቸር እና ሪል እስቴት ደቬሎፕመንት ዲዛይኖችን መስራት፣
3. የአዉሮፕላን ማረፊያ ተርሚናሎችን፣ ድልድዮችን፣ ግድቦችን የተነሎችን አጠቃላይ የዲዛይን ሰራዎችን
መሰራት፣
4. የዉሃ ስራዎችን ማጎልበት የከተማና የገጠር ዉሃ ልማትና ሳኒቴሽን፣ የአካባቢ ጥናት የዝናብ ዉሃና ፍሳሽ፣
ሃይድሮሊክ ስትራክቸር፣ የዉሃ ስራ ቁፋሮዎች እና ወ.ዘ.ተ የዲዛይን ስራዎችን መስራት፣
5. የላብራቶሪ ስራዎችና ማቴሪያል ምርመራዎችን ማካሄድ፣
6. የኮንትራት አስተዳደር ቁጥጥር እንዲሁም የዋጋ ግምቶችን መስራት፣
7. የኮንስትራክሽን ማኔጅመት የማማከር አገልግሎት መስጠት፣
8. አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራዎችን የማማከር ስራ አገልግሎት መስራት፣
9. በአገር ዉስጥ እና በዉጭ አገር በንግድ ኢንተርፕራይዞች፣ ማህበሮችና ከግለሰቦች ጋር በሽርክና መስራት፣
10. ኮሚሽን ኤጀንት በመሆን መስራት በተጨማሪም ከማህበሩ ስራና ተግባር ጋር የሚካሄድ ስራዎችን በሙሉ
መስራት፣
11. የምሕንድስና እና የማማከር ስራ ላይ መሰማራት፣
12. ከምህንድስና ጋር ተያያዥነት ያላቸዉ ስራዎችን መስራት፣
13. በምህንድስና ዘርፍ የፕሮጀክት ቀረፃ እና የፕላን ዝግጅት ማከናወንና የማማከር ስራ ማካሄድ
14. ከመንግስት በሊዝም ሆነ ከግል የሕንፃና የመኖሪያ ቤት መስሪት ቦታ በመከራየትም ሆነ በመመራት ለመኖሪያ
ለቢሮና ለተለያዩ የንግድ ስራዎች የሚሆኑ ህንፃዎችን መገንባት ማከራየት መሸጥ፣
15. ሪል እስቴት ማቋቋም እና የግንባታ፣ የመሣሪያ ኪራይ እና የሽያጭ ስራዎችን መስራት፣
16. የኮንስትራክሽን ዕቃዎች ማስመጣት፣ ማከራየት፣ መሸጥ፣
17. ለኮንስትራክሽን ኢንዳስትሪው ግብዓት የሚሆኑ ሶፍትወሮችን ማቅረብ፤ ማሰልጠን፤ መሸጥ፤
18. የህንፃ ተቋራጭ የመንገድ ስራ የኮንስትራክሽን ስራ መስራት፣
19. የኮንስትራክሽን መሳሪያዎችን ማስመጣት፣
20. ማንኛዉንም የግንባታና የኮንስትራክሽ ስራዎችን መስራት፣
21. የኮንስትራክሽን እቃዎች ኪራይ አገልግሎት መስጠት፣
22. ብሎኬት፣ ቱቦ፣ ታይልስ፣ ጡብ፣ እና የመሳሰሉት የኮንስትራክሽን እቃዎች ማምረትና መሸጥ ማናቸዉንም
ለድርጅቱ ጥቅም ሊያስገኙ የሚችሉ ስራዎች መስራት፣
23. ሲሚንቶ፣ ብረታ ብረት፣ ቆርቆሮ፣ ሚስማር እና በአጠቃላይ ለኮንስትራክሽንና ለግንባታ ስራዎች የሚዉሉ
ዕቃዎችን እንዲሁም ተገጣጣሚ የህንፃ እቃዎችን ማስመጣት፣ ማከፋፈልና መሸጥ፣
24. ሪል እስቴት የቋቋም እና የግንባታ፣ የመሣሪያ ኪራይ እና የሽያጭ ስራዎችን መሰራት፣
25. የተለያዩ ብረታ ብረቶችን ከዉጭ አገር አስመጥቶ ለአገር ዉስጥ ገበያ ማቅረብ፣
26. የተለያዩ ማምረቻ መሣሪያዎችን የጡብ ማምረቻ ቱቦ መሰሪያ፣ የፒቪሲ ፓይፕ መሰሪያ፣ የጠጠር ማምረቻ
ወይም የድንጋይ መፍጫ መሣሪያዎችን ከዉጭ ማስመጣት እና ጠጠር ማምረት፡፡

አንቀጽ አምስት

የማኀበሩ፣ ካፒታል

የማኀበሩ ካፒታል ብር 2,220,000.00 ሁለት ሚሊየን ሁለት መቶ ሃያ ሺህ ብር/ ሲሆን ይኸዉ ገንዘብ በጠቅላላ በጥሬ ገንዘብ ብር 600,000.00
/ስድስት መቶ ሺህ ብር/ እና በአይነት ብር 1,620,000.00 /አንድ ሚሊየን ስድስት መቶ ሃያ ሺህ ብር/ በሙሉ በአባላት ተከፍሏ፡፡ ጠቅላላዉ
ካፒታል እያንዳንዳቸዉ ብር 1000.00 /አንድ ሺህ ብር/ ዋጋ ባላቸዉ 2220 /ሁለት ሺ ሁለት መቶ ሃያ/ አክስዮኖች ተከፍሏል፡፡

በመስራች አባላት የተያዘዉ የአክስዮን መጠን የሚከተለዉ ነዉ፡፡


የአክስዮን

ገንዘብ በጥሬ
የአንዱ

በአይነት

መዋጮ
ጠቅላላ
ተ.ቁ

ስም
ዋጋ
መጠን

1 አቶ አበበ ባንጃዉ ወንድምአገኘሁ


650 1,000 50,000 600,000 650,000.00
(ADP in BLDG.ENG + BSc in COTM + MSc in COTM)
2 ወ/ሮ አፀደ አርሼ ዲዶ
490 1,000 50,000 440,000 490,000.00
(ADP in BLDG.ENG)
3 ወ/ሪት አምሮት አንጀሎ አርሼ
450 1,000 50,000 400,000 450,000.00
(BSc in CIVIL ENG. + MSc in COTM)
4 አቶ ደረጀ ባንጃዉ ወንድምአገኘሁ
80 1,000 60,000 20,000 80,000.00
(ADP in BLDG.ENG + BSc in CIVIL ENG.)
5 አቶ ተድላ ወርቁ አበራ
80 1,000 60,000 20,000 80,000.00
(BSc in ARCHITECTURE)
6 አቶ ዮሰፍ አሸናፊ አርሼ
70 1,000 50,000 20,000 80,000.00
(BSc in CIVIL ENG.)
7 አቶ ክሩቤል አንጀሎ አርሼ
70 1,000 50,000 20,000 70,000.00
(BSc in CIVIL ENG.)
8 ወ/ሪት ዮኋና አምሳሉ አሰፋ
50 1,000 30,000 20,000 50,000.00
(BSc in CIVIL ENG.)
9 አቶ ዳግማዊ ነገዱ ባንጃው
50 1,000 30,000 20,000 50,000.00
(BSc in MECHANICAL ENG.)
10 አቶ ዳኛቸው አማኑ ወንድምአገኘሁ
80 1,000 60,000 20,000 80,000.00
(DP in ELEC.ENG + BSc in CIVIL ENG.)
11 አቶ ሸበለው በድሉ ወንድምአገኘሁ
80 1,000 60,000 20,000 80,000.00
(ADP in Water + BSc in URM + MSc in COTM.)
12 አቶ በዕውቀቱ አወቀ አልቶ
70 1,000 50,000 20,000 70,000.00
(BSc in Wat t& Env + MSc in Hyd ENG.)
ጠቅላላ ድምር
2220 1000 600,000 1,620,000 2,220,000.00

በአይነት የተዋጣ

1. አቶ አበበ ባንጃዉ ወ/አገኘዉ ግምቱ ብር 400,000.00 /አራት መቶ ሺህ ብር/ የሚያወጣ የስሌዳ ቁጥር 2-A45719
የሻንሲ ቁጥር NZE120-3076288 የሞተር ቁጥር 2NZ-3461403 ሞዴል CBA-NZE120-AEPNK የሆነዉን
አዉቶሞቢል መኪና እና ግምቱ ብር 200,000.00 / ሁለት መቶ ሺህ ብር/ የሚያወጡ ሁለት ላፕ ቶፖች የሲሪያል
ቁጥራቸው 3424354356465 እና 4586676667 የሆኑትን ዘመናዊ ገሚንግ ላፕቶፖች ለዲዛይን ሥራ የሚያገለግሉ
በአይነት ወደ ማህበሩ ገቢ አድርገዋል፡፡
2. ወ/ሮ አፀደ አርሼ ዲዶ ግምቱ ብር 400,000.00 /አራት መቶ ሺህ ብር/ የሚያወጣ የሰሌዳ ቁጥር 2-A23449 የሻንሲ
ቁጥር JT132LNH300008390 የሞተር ቁጥር 2L-4686524 ሞዴል LN170L-CRMDXW የሆነዉን ደረቅ ጭነት ፒካፒ
መኪና እና ግምቱ ብር 40,000.00 /አርባ ሺህ ብር/ የሚያወጡ ሁለት ላፕ ቶፖች የሲሪያል ቁጥራቸው
3424354356465 እና 4586676667 የሆኑትን ላፕቶፖች ለቢሮ ሥራ የሚያገለግሉ በአይነት ወደ ማህበሩ ገቢ
አድርገዋል፡፡
3. ወ/ሮ አምሮት አርሼ ግምቱ ብር 400,000.00 /አራት መቶ ሺህ ብር/ የሚያወጣ የሰሌዳ ቁጥር 2-A23449 የሻንሲ
ቁጥር JT132LNH300008390 የሞተር ቁጥር 2L-4686524 ሞዴል LN170L-CRMDXW የሆነዉን ደረቅ ጭነት ፒካፒ
መኪና በአይነት ወደ ማህበሩ ገቢ አድርገዋል፡፡
4. አቶ ደረጀ ባንጀው ግምቱ ብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ የሚያጣ ላፕ ቶፕ የሲሪያል ቁጥሩ 3424354356465 የሆነ
ለቢሮ ሥራ እንዲያገለግል በአይነት ወደ ማህበሩ ገቢ አድርገዋል፡፡
5. አቶ ተድላ ወርቁ አበራ ግምቱ ብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ የሚያጣ ላፕ ቶፕ የሲሪያል ቁጥሩ 3424354356465
የሆነ ለቢሮ ሥራ እንዲያገለግል በአይነት ወደ ማህበሩ ገቢ አድርገዋል፡፡
6. አቶ ዮሰፍ አሸናፊ አርሼ ግምቱ ብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ የሚያጣ ላፕ ቶፕ የሲሪያል ቁጥሩ 3424354356465
የሆነ ለቢሮ ሥራ እንዲያገለግል በአይነት ወደ ማህበሩ ገቢ አድርገዋል፡፡
7. አቶ ክሩቤል አንጀሎ አርሼ ግምቱ ብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ የሚያጣ ላፕ ቶፕ የሲሪያል ቁጥሩ
3424354356465 የሆነ ለቢሮ ሥራ እንዲያገለግል በአይነት ወደ ማህበሩ ገቢ አድርገዋል፡፡
8. ወ/ሪት ዮኋና አምሳሉ አሰፋ ግምቱ ብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ የሚያጣ ላፕ ቶፕ የሲሪያል ቁጥሩ
3424354356465 የሆነ ለቢሮ ሥራ እንዲያገለግል በአይነት ወደ ማህበሩ ገቢ አድርገዋል፡፡
9. አቶ ዳግማዊ ነገዱ ባንጃው ግምቱ ብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ የሚያጣ ላፕ ቶፕ የሲሪያል ቁጥሩ
3424354356465 የሆነ ለቢሮ ሥራ እንዲያገለግል በአይነት ወደ ማህበሩ ገቢ አድርገዋል፡፡
10. አቶ ዳኛቸው አማኑ ወንድምአገኘሁ ግምቱ ብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ የሚያጣ ላፕ ቶፕ የሲሪያል ቁጥሩ
3424354356465 የሆነ ለቢሮ ሥራ እንዲያገለግል በአይነት ወደ ማህበሩ ገቢ አድርገዋል፡፡
11. አቶ ሸበለው በድሉ ወንድምአገኘሁ ግምቱ ብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ የሚያጣ ላፕ ቶፕ የሲሪያል ቁጥሩ
3424354356465 የሆነ ለቢሮ ሥራ እንዲያገለግል በአይነት ወደ ማህበሩ ገቢ አድርገዋል፡፡
12. አቶ በዕውቀቱ አወቀ አልቶ ግምቱ ብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ የሚያጣ ላፕ ቶፕ የሲሪያል ቁጥሩ
3424354356465 የሆነ ለቢሮ ሥራ እንዲያገለግል በአይነት ወደ ማህበሩ ገቢ አድርገዋል፡፡

አንቀጽ ስድስት

የአባላቱ ኃላፊነት

አባላት ከላይ የተጠቀሰዉን ካፒታል በጥሬ ገንዘብ እና በአይነት በሙሉ የተከፈለ መሆኑን በአንድነት እና በነጠላ አረጋግጠዋል፡፡ ስለሆነም የአባላቱ
ኃላፊነት በማኀበሩ ዉስጥ ባላቸዉ አክስዮን መጠን የተወሰነ ነዉ፡፡

አንቀጽ ሰባት

የትርፍና ኪሣራ ክፍፍል

አባላቱ በተለየ ሁኔታ ካልተስማሙ በስተቀር ከጠቅላላዉ ዓመታዊ ትርፍ ሕጋዊ የመጠባበቂያ ገንዘብ እና ሌሎች ጠቅላላ ወጪዎች ከተቀነሱ በኃላ
ቀሪዉ በአባላት መካከል እንደ አክስዮን ይዞታቸዉ ይከፋፈላል፡፡ ኪሳራም ካለ በተመሳሳይ ሁኔታ በአባላቱ መካከል ይከፋፈላል፡፡ ሆኖም አባላቱ
በማኀበሩ ዉስጥ ካለዉ የአክስዮን ካፒታል በላይ ተጠያቂ ሊሆኑ አይችሉም፡፡

አንቀጽ ሰምንት

ጠቅላላ ጉባዔ

8.1 የማህበሩ ከፍተኛ የስልጣን አካላት ጠቅላላ ጉባዔዉ ነዉ፡፡


8.2 የጠቅላላ ጉባዔዉ ስልጣንና ተግባር እንዲሁም የስብሰባዉ ሁኔታ በመተዳደሪያ ደንብ ላይ የተገለፀዉ ነዉ፡፡
አንቀጽ ዘጠኝ
ሥራ አመራር
የማኀበሩ ሥራ አስኪያጅ ሥልጣንና ተግባር በዚህ መመስረቻ ጽሑፍ በዝርዝር የተመለከተ ከአባላቱ መካከል ወይም ከዉጭ በአባላቱ
በሚመረጥ፣ የሥልጣን ዘመኑ ባልተወሰነ ጊዜ የሆነ አንድ ዋና ሥራ አስኪያጅ ይመራል፡፡ በዚህ መሰረት አቶ አበበ ባንጃዉ ወ/አገኘዉ
የመጀመሪያ የማኀበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ እንዲሁም ወ/ሮ አፀደ አርሼ ዲዶ የመጀመሪያዉ የማህበሩ ምክትል ሥራ
አስኪያጅ ሆነዉ ተመርጠዋል፡፡

አንቀጽ አስር
የማኀበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሥልጣን ተግባር
10.1. የማኀበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ የሥራ ዘመናቸዉ ሲያልቅ በድጋሚ ሊመረጡ ይችላሉ፡፡ ማህበሩ በዋና ዳይሬክተር
እንደ አስፈላጊነቱ የሚሾሙ የዘርፍ ሥራ አስኪያጆች ሊኖሩት ይችላል፡፡ የሥራ አስኪያጅ ስልጣንና ተግባር
የሚከተለዉ ይሆናል፡፡
10.2. የዘርፍ ሥራ አስኪያጅን ይሾማል፣ ይሽራል፣ ተግባራቸዉን ዘርዝሮ ይሰጣል፣ ይቆጣጠራል፡፡
10.3. ማኀበሩ በመወከል ይፈርማል፡፡
10.4. ለማኀበሩ ቴክኒካዊና አስተዳደራዊ ተግባሮች ኃላፊ ነዉ፡፡
10.5. የጠቅላላ ጉባዔ ዉሳኔዎችን ሥራ ላይ ያዉላል፡፡
10.6. ለማህበሩ የሚከፈል ገንዘብ መቀበል፣ የማህበሩን ዕዳዎች መክፈል፣ ማናቸዉም የሐዋላ ወረቀት የተሰፋ ሰነድ፣
የባንክ ሰነድ ማዘጋጀትና በጀርባ ላይ መፈረም፣ ማደስና መክፈል እንዲሁም የጭነት ማስታወቂያ ደረሰኞች፣ የቦንድ
ሰርተፊኬቶችን ወይም ማናቸዉንም ሰነዶች ማጽደቅና ከጀርባዉ መፈረም፡፡
10.7. የማኀበሩ ወኪል ወይም ሠራተኛ ይቀጥላል፣ ያሰናብታል፣ ክፍያዉን፣ ደሞዙን ጉርሻን ሌሎች ከመቀጠርና ከመሰናበት
ጋር የተያያዙ ሁኔታዎች ይወሰናል፡፡
10.8. በማህበሩ ስም የባንክ ሂሣቦች ከፍቶ ገንዘብ ገቢ ያደርጋል፡፡ ሂሣቦቹን በፊርማዉ ያንቀሳቅሳል፡፡
10.9. የማንኛዉም በኢትዮጵያ ዉስጥ ካለ ወይም የዉጭ አገር ባንክ ገንዘብ ድርጅት በመያዣ ወይም በማህበሩ ስም
መፈረም፣
10.10. ማናቸዉም ዉሎች ወይም ስምምነቶች መግባት መፈፀምና መፈረም፡፡
10.11. በአገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ ሀገር በሚገኙ የመንግስት መ/ቤቶች፣ ፍ/ቤቶች፣ ኮርፖሬሽኞች፣ እና ህጋዊ ተቌማት
ፊት ማህበሩን በመወከል መፈረም፣
10.12. በማህበሩ ስም በማንኛዉም የመንግስት ሆነ የግል ባንኮች ሂሳብ መከፍት እና ሒሳቡንም በፊርማዉ ማንቀሳቀስ፣
10.13. በጠቅላላ የማህበሩ ዓላማ ግብ ለማድረስ ወይም የማህነሩን ጥቅም ለመጠበቅ የሚያስፈልጉ ጉዳዮችን ይፈፅማሉ፣
10.14. ለማኀበሩ ንግድ በመልካም ሁኔታ መካሄድ የሚጠቅሙ ግዢዎች ሽያጭና የእነዚህን ማዘዣዎች ይወስናል፣ የኪራይ
ዉል ይዋዋላል፡፡
10.15. ከማኀበሩ ንግድ ጋር የተያያዙ ማናቸዉንም የንግድ ልዉዉጥ በተመለከተ ከሦስተኛ ወገኞች ጋር ዉል ይዋዋል፣
በማህበሩ ስም የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረት ይገዛል ይሸጣል በስጦታ ያስተላልፋል፣ በማህበሩ ስም
ስጦታ ይቀበላል፣
10.16. በማናቸዉም ፍርድ ቤት ማኀበሩ ከሳሽ፣ ተከላሽ ወይም ጣልቃ ገቢ በሚሆንበት ጉዳይ ሁሉ ማኀበሩን በመወከል
አስፈላጊዉን ይፈጽማል፣ እንደዚሁም የሕግ ጠበቃ ወይም አማካሪ በመወከል ይከራከራል፡፡
10.17. ማኀበርቶኞች ሲቀበሉትና ሊያፀድቁት እንዲችሉ የሂሳብ ወጪና የገቢ መዝገብ በደንቡ እንዲያዝ አስፈላጊዉን
እርምጃ ይወስዳል፡፡ የማህበሩ ዓላማ ግቡን እንዲመታ አስፈላጊ መስሎ በታየዉ ጊዜ ለዋናሥራ አስኪያጅ ከተሰጠት
ስልጣንና ተግባር መሀል ማንኛዉንም በሌላ ለሦስተኛ ሰዉ እንዲፈጸም በማኀበሩ ስም ዉክልና መስጠት ይችላል፡፡
10.18. የማኀበሩን የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረት ይሸጣል ይስዉጣል በባንክ በዋስትና በማስያዝ ገንዘብ
ይበደራል፡፡
10.19. የማኀበሩን ወይም የሌላ ሦስተኛ ወገን የሚንቀሳቀስ ወይም የማንቀሳቀስ ንብረት መያዣ በማድረግ ከግልም ሆነ
ከመንግስት ባንኮች የብድር ዉሎችን ተዋዉሎ ብድር ይበደራል፡፡
10.20. በማህበሩ ስም የተፃፋ ቼኮች ላይ ይፈርማል፣ ቼክ ያዘጋጃል፣ በፊርማዉ ያንቀሳቅሳል፡፡
10.21. የማህበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ማናቸዉም በሕግም ሆነ በዚህ የመመስረቻ ጽሁፍ የተሰጡትን ስልጣን በሙሉ
ወይም በከፊል ለተወሰነ ጊዜ ለሌላ የማህበሩ አባል በዉክልና ሊያስተላልፍ ይችላል፡፡እንደዚሁም ዋና ሥራ አስኪያጅ
መቅጠር የሚችሉ ሲሆን ለሚቀጠረዉ ስልጣኑን በሙሉ ወይም በከፊል በዉክልና ማስተላለፍ ይችላል፡፡ ዋና ሥራ
አስክያጅ ለማህበሩ ጥቅም ሲባል ለማህበሩ አባል ለሆነ ስልጣኑን ሊያስተላልፍ ይችላል፡፡ዋና ሥራ አስኪያጅ ለሌላ
አካል እና ለቀጠረዉ የተሰጠዉን ዉክልና ሳይሽሩ በዚያዉ ጊዜ ዉስጥ በዚያዉ ስልጣን በተደራቢነት ሊሰራ ይችላሉ፡፡
ዋና ሥራ አስኪያጅ ከድርጅቱ ኃላፊ ወይም ሰራተኞች የባንክ ሒሳብ እንዲያንቀሳቅሱ ወይም ዉል እንዲፈርሙ
መወከል ይችላል፡፡
10.22. የዋና ሥራ አስኪያጅ ደሞዝ በጠቅላላ ጉባዔ ይወሰናል፡፡
10.23. የማህበሩ ካፒታል ½ በላይ ሲጠፋ አስቸኳይ ልዩ ጉባዔ ይጠራል፣

አንቀጽ አሥራ አንድ


የማህበሩ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሥልጣንና ተግባር

የማህበሩ ዋና ሥራ አስክያጅ በማይኖሩበት ጊዜ ሁሉ እርሳቸዉን ተክተዉ ይሰራሉ፣ ለእሳቸዉ የተሰጣቸዉን ስልጣን በሙሉ
ያከናዉናሉ፡፡

አንቀጽ አሥራ ሁለት


ኦዲተር

ማህበሩ በአባላቱ የሚመረጡ ኦዲተር /ኦዲተሮች/ ይኖሩታል፡፡

አንቀጽ አሥራ ሶስት


ተቆጣጣሪ

ጠቅላላ ጉባዔዉ ወይም ዋና ሥራ አስኪያጅ ተቆጣጣሪዎችን ይሾማል፣ ይሽራል፣ የሚከፈላቸዉን የክፍያ መጠን ይወስናል፡፡
ተቆጣጣሪዎች የኩባንያዉን ሒሳብ በየሩብ ዓመቱ ማለትም በዓመት አራት ጊዜ ተመርምሮ በየሩብ ዓመቱ ሪፖርት
እንዲቀርብ በአራተኛዉ ሩብ ዓመት የዓመቱ መጠቃለያ ሒሳብ እንዲቀርብ ያደርጋል፡፡

አንቀጽ አሥራ አራት


ማሻሻያ

ይህ የመመስረቻ ጽሁፍ 2/3 ኛ የአክሲዮን ድርሻ ባላቸዉ አባላቱ ድምጽ ይሻሻል፡፡

አንቀጽ አሥራ አምስት


የማኀበሩ የሥራ ዘመን

አባላቱ በተለየ ሁኔታ ለመወሰን ያላቸዉ መብት እንደተጠበቀ ሆኖ ማኀበሩ የተቌቌመዉ ላልተወሰነ ጊዜ ነዉ፡፡

የመስራች አባላት ስም ፊርማ

13. አቶ አበበ ባንጃዉ ወንድምአገኘሁ


14. ወ/ሮ አፀደ አርሼ ዲዶ
15. ወ/ሪት አምሮት አንጀሎ አርሼ
16. አቶ ደረጀ ባንጃዉ ወንድምአገኘሁ
17. አቶ ተድላ ወርቁ አበራ
18. አቶ ዮሰፍ አሸናፊ አርሼ
19. አቶ ክሩቤል አንጀሎ አርሼ
20. ወ/ሪት ዮኋና አምሳሉ አሰፋ
21. አቶ ዳግማዊ ነገዱ ባንጃው
22. አቶ ዳኛቸው አማኑ ወንድምአገኘሁ
23. አቶ ሸበለው በድሉ ወንድምአገኘሁ
24. አቶ በዕውቀቱ አወቀ አልቶ
ቴምብር እና ፊርማ

You might also like