You are on page 1of 5

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክና ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ

የምርታማነት ማሻሻያ እና የልህቀት ማዕከል

የውል ስምምነት

የግንባታ ጉዳይ አስተዳደር ዉል

የክረምት በጎ አደራጎት ህንፃ ብሎክ የግንባታ ስራ

ዉል ሰጪ፡- ምርታማነት ማሻሻያና የልህቀት ማዕከል


አድራሻ፡ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልደታ ክፍለ ከተማ ልደታ ጤና ጣቢያ አጠገብ

ስልክ ቁጥር፡+251115584766/+251947377025

ፖ.ሳ.ቁ.፡5538 ከዚህ በኃላ ዉል ሰጪ/ግዥ ፈፃሜ/አሰሪ ተብሎ ሊጠራ ይችላል፡፡

እና

ዉል ተቀባይ፡_____________________

አድራሻ፡________________________

ስልክ ቁጥር፡______________________

ከዚህ በኃላ ዉል ተቀናይ/አቅራቢ/ተቌራጭ ተብሎ ሊጠራ ይችላል፡፡

ይህ ዉል በልደታ ክፍለ ከተማ የሚገኝን 9.6 ሜ በ 5.30 ሜ የሆነ ባለሁለት ክፍል ከጭቃ የተሰራ መኖሪያ ቤት አፍርሶ
በዲዛይንና ስፔስፊኬሽን በተመለከተዉ መሰረት መገንባት ሲሆን ይህም “ስራዉ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡ በመሆኑም ዉል
ተቀባይ በብር፡ _________________________________________________________________

የእጅ ዋጋ ይህ “የዉል ዋጋ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ዉል ተቀባይ ስራዉን ርክክብ ከተፈጸመበት ቀን ጀምሮ በሰላሳ (30)
ቀናት ዉስጥ ግንባታዉን አጠናቆ ለዉል ሰጭ ማስረከብ አለበት፡፡

(ሀ) ግዥ ፈፃሚው አካል የተወሰኑ የግንባታ ሥራዎች መካከል፡በጥንቃቄ የጭቃ ቤቱን የማፍረስ ስራ፤ የቁፋሮ ስራ፤
የግንብ ስራ፤የአርማታ ስራ፤ የብሎኬት ግድግዳ ስራ፤የማሳመር/የአጨራረስ ስራ፤የልስን ስራ፤ የታይሊንግ ስራ፤
የቀለም ቅብ ስራ፤ የጣሪያ ና ቆርቆሮ ማልበስ ስራ፤ የበርና መስኮት ስራ፤ የመስተዋት ገጠማ ስራ፤የቧንቧ መስመር
ገጠማ ስራ፤ የመብራት መስመር ስራ
(ከዚህ በኋላ “የግንባታ ሥራዎች” እየተባሉ የሚጠሩ) ሥራ ተቋራጩ የግንባታ ሥራዎቹን ለማከናወን ያቀረበውን ጠቅላላ
የእጅ የውል ዋጋ ብር በፊደል____________________________ በአሀዝ:____________________________
(ከዚህ በታች “የውል ዋጋ” እየተባለ የሚጠራ) ሰለተቀበለ፣

(ለ) ሥራ ተቋራጩ የግዥ ፈፃሚ አካሉን በመወከል ተፈላጊውን የሙያ ችሎታ፣ ሠራተኞችና የቴክኒክ ዕውቀት
በመጠቀም የተጠየቁት የግንባታ ሥራዎች በዚህ የውል ሁኔታዎች መሠረት ለመፈፀም ስለተስማማ፣
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክና ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ
የምርታማነት ማሻሻያ እና የልህቀት ማዕከል
ሁለቱ ወገኖች እንደሚከተለው ተዋውለዋል፡፡

1. ስምምነት

1.1 በዚህ ውል ውስጥ ቃላቶችና አገላለፆች በተጠቀሰው ውል ሁኔታዎች ውስጥ በቅደም ተከተል የተሰጣቸውን
ተመሳሳይ ትርጉሞች ይኖራቸዋል።
1.2 ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ሰነዶች በግዥ ፈፃሚው አካልና በሥራ ተቋራጩ መካከል በተደረገው ስምምነት
ውስጥ የተካተቱና የውሉ አካል ሆነው የሚነበቡ/የሚቆጠሩ ናቸው።
1. ይህ የውል ስምምነት ከአባሪዎች ጋር
2. በግዥ ፈፃሚ አካል ለሥራ ተቋራጩ የተፃፈ የአሸናፊነት ድብዳቤ
3. ልዩ የውል ሁኔታዎች
4. አጠቃላይ የውል ሁኔታዎች
5. የዋጋ ማቅረቢያ ሠንጠረዥና አባሪዎቹ
6. የቴክኒክ መወዳደሪያ ሀሳብ ከግንባታ ስራዎች ዝርዝር
7. የንድፍ ሰነዶች (Drawings)
(ለ) ለጥቅል ዋጋ ውሎች: የጥቅል ዋጋው ዝርዝር ((የስሌት ስህተቶች ከታረሙ በኋላ)
1.3 ይህ ውል በሁሉም ሰነዶች ላይ የበላይነት ይኖረዋል፡፡ በውሉ ሰነዶች ላይ ልዩነት ወይም ያለመጣጣም
በሚኖርበት ጊዜ ከላይ በተዘረዘሩት ቅደም ተከተል መሠረት የበላይነት ይኖራቸዋል፡፡
1.4 ግዥ ፈፃሚው አካል ለሥራ ተቋራጩ የሚፈጽመውን ክፍያ ግምት ውስጥ በማስገባት በዚህ ውል ውስጥ
እንደተመለከተው ሥራ ተቋራጩ የግንባታ ሥራዎቹን ለማከናወንና በውሉ ድንጋጌዎች መሠረት ግድፈቶችን
ለማረም ከግዥ ፈፃሚው አካል ጋር ግዴታ ይገባል፡፡
1.5 ግዥ ፈፃሚው አካል ሥራ ተቋራጩ ለሚተገብራቸው የግንባታ ሥራዎች፣ እንዲሁም ግድፈቶች ለማረም
ለገባው ግዴታ የውሉን ዋጋ ወይም በውሉ ድንጋጌዎች መሠረት ተከፋይ የሚሆነውን መጠን በተባለው ጊዜና
ሁኔታ ለመክፈል ግዴታ ይገባል፡፡

2. የተዋዋይ ወገኖች መብትና ግዴታዎች

2.1.የዉል ተቀባይ ግዴታዎችና መብቶች

2.1.1.የዉል ተቀባይ ግዴታዎች


2.1.1.1. በዚህ ዉል መሰረት ሊሰራዉ የፈረመበትን የግንባታ ስራ በዚህ ዉል እና በዉሉ አካል በተደረጉ ሰነዶች በተመለከተዉ
አይነት የስራዉ አሰራር ዝርዝር እና የግንባታ ስፔስፊኬሽን እና የወቅቱ የሙያ ስነምግባር እንዲሁም ቴክኖሎጂ በሚጠይቀዉ
ደረጃ በጥራት በሚገባ ይከናወናል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክና ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ
የምርታማነት ማሻሻያ እና የልህቀት ማዕከል
2.1.1.2.ይህ ዉል ሳይት ርክክብ ከተደረገበት ቀን ጀምሮ ሰላሳ(30) ተከታታይ የካላንደር ቀናት ሙሉ ግንባታ ስራዉን
ለማከናወን የእጅ ዋጋ ብር፡______________________________________________________________________
ብቻ በዉሉ አግባብ በጥራት አጠናቆ ያስረክባል፡፡
2.1.1.3.የግንባታ ስራዉ የሚከናወነዉ ዉል ሰጪ በሚመድበዉ የግንባታ ስራ ተቆጣጣሪ መሃንዲስ/አማካሪ ጋር በመመካከር
ነዉ፡፡
2.1.1.4. ዉል ተቀባይ ዉል በተፈራረመበት የግንባታ ስራ ዉስጥ አብረዉ ሊሰሩ የሚገባቸዉ የለዉጥ ስራዎች ሲያጋጥሙ
ሁኔታዉን ለዉል ሰጪ ማሳወቅ ይኖርበታል በዉል ሰጪ በኩልም የለዉጥ ስራዉን ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር በመመካከር
መሰራት እንዳለበት ሲታመንበት ስራዉ ከመሰራቱ በፊት በቅድሚያ ዉል ሊወስድ ይገባል፡፡ዉል ሳይወስድ የተሰራ ስራ ዉል
ሰጪ ክፍያ እንዲፈጽምለት አይገደድም/አይከፈልበትም፡፡

2.1.2.የዉል ተቀባይ መብቶች

2.1.2.1.የቅድሚያ ክፍያ ለዉሉ ጉዳይ ብቻ አገልግሎት ላይ የሚዉል ከጠቅላላ ዋጋ እሰከ 20% የማግኘት መብት አለዉ፡፡
2.1.2.2.የግንባታ ስራዉ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ጊዜያዊ ርክክብ እሰከ ሚደረግበት ጊዜ ባለዉ ዉስጥ ለስራዉ የተመደበዉን
የዉሉን ገንዘብ ቅድሚያ ክፍያን ሳይጨምር በ 4 ዙር እንዲከፈለዉ የመጠየቅ መብት አለዉ፡፡

2.2.የዉል ሰጪ ግዴታዎችና መብቶች

2.2.1.የዉል ሰጪ ግዴታዎች
2.2.1.1 ቅድሚያ ክፍያና ሌሎች ለተሰሩ ስራዎች ተከታታይ ክፍያዎች እንዲከፈለዉ በዉል ተቀባይ ሲጠየቅ እና በዉል ሰጪ
አማካሪ ወይም አግባብ ባለዉ ተቆጣጣሪ መሃንዲስ ተረጋግጦ ሲቀርብ ስለ ትክክለኛነቱ መርምሮ በማጽደቅ ክፍያ የመፈጸም
ግዴታ ይኖርበታል፡፡
2.2.1.2 ግንባታዉ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ በ አምስት(5)ቀናት ዉስጥ ጊዚያዊ ርክክብ ይፈጽማል፡፡

2.2.1.3. የግንባታዉን ስራ የሚያደናቅፍ እና በዉል ሰጪዉ ጥረት ወይም ጣልቃ ገብነት ሊወገዱ የሚገባቸዉን እክሎች
ስለማጋጠማቸዉ ዉል ተቀባይ በጽሁፍ አድርጎ ለዉል ሰጪ ተቌም ገቢ በማድረግ ሲገለጽለት እክሉ በዉል ሰጪ የሚወገዱ
ከሆነ ተገቢዉን ህጋዊ እገዛ ያደርጋል፡፡
2.2.1.4 ዉል ሰጪ ለግንባታዉ አስፈላጊ የሆኑ የግንባታ ጥሬ ዕቃዎችን በወቅቱ ለዉል ተቀባይ ያቀርባል፡፡

2.2.2.የዉል ሰጪ መብቶች
2.2.2.1. በዚህ ዉል ጉዳይ የዉል ሰነዶች በተለይም የስራ ስፔስፊኬሽን በተመለከተዉ ዓይነት፤ ጥራት ና በተወሰነዉ ጊዜ
የግንባታዉ ስራ ተጠናቆ የመረከብ መብት አለዉ፡፡
2.2.2.2. ለዉል ተቀባይ በዚህ ዉል የሰጠዉን የግንባታ ስራ በሚመድበዉ ተቆጣጣሪ መሀንዲስ እና እንደአስፈላጊነቱ
በሚያሰማራዉ አማካሪ አማካኝነት ይቆጣጠራል፡፡
2.2.2.3. ለዉል ተቀባይ በዚህ የግንባታ ዉል የቅድሚያ ክፍያ የሚፈጸምለት ከሆነ ይኸዉም የቅድሚያ ክፍያ ገንዘብ
ለግንባታዉ ስራ ከሚከፈለዉ ተከታታይ ክፍያዎች በመቶኛ እየተሰላ ተቀናሽ በማድረግ የማስመለስ መብት አለዉ፡፡
2.2.2.4. ተቌራጭ ግዴታ የገባበትን የግንባታ ስራ በዉሉ አግባብ በተቀመጠዉ ዓይነትና በተወሰነዉ ጊዜ ማጠናቀቅ ሳይችል
ሲቀር ስራዉን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ በሌላ ተቌራጭ የማስጨረስ ሙሉ ስልጣን አለዉ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክና ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ
የምርታማነት ማሻሻያ እና የልህቀት ማዕከል
3. ስለ ክፍያ አፈፃጸም
3.1.ዉል ሰጪ ለግንባታ ስራዉ የተስማማበትን የእጅ ዋጋ ብር፡
__________________________________________________________________
ብቻ ስራዉ ተጠናቆ ጊዜያዊ ርክክብ ሲፈጽም ለዉል ተቀባይ ይከፍላል፡፡
3.2.ከላይ በተራ ቁጥር 3.1 የተገለጸዉ ገንዘብ መጠን በ አራት(4) ተከታታይ የክፍያ ጊዜ የሚፈጸም ሆኖ የመጀመሪያዉ ዙር
ከጠቅላላ የፊዚካል ስራዉ 25% ሲከናወን፤ሁለተኛዉ ዙር ከጠቅላላ የፊዚካል ስራዉ 50% ሲከናወን፤ሶስተኛዉ ዙር ከጠቅላላ
የፊዚካል ስራዉ 75% ሲከናወን፤አራተኛዉ ዙር ከጠቅላላ የፊዚካል ስራዉ 100% ተጠናቆ ጊዚያዊ ርክክብ ሲፈጸም
የሚከፈል ይሆናል፡፡

4.አለመግባባቶች ስለሚፈቱበት ሁኔታ


4.1. ከዚህ ዉል ጋር ተያይዞ የሚነሳ ማንኛዉም አለመግባባት በቅድሚያ በተዋዋዮች ቀጥተኛ ዉይይት ወይም ሶስተኛ ወገን
ባለበት በስምምነት ሊፈታ ይችላል፡፡
4.2. በተ.ቁ 4.1 አለመግባባቱ ካልተፈታ ጉዳያቸዉ በቀጥታ ወይም ዉክልና ስልጣን ባለዉ ፍርድ ቤት ማቅረብ ይቻላል፡፡
ለማስረጃነት ይሆን ዘንድ ተዋዋዮች ከላይ በተጠቀሰው ቀን፣ ወርና ዓ.ም. በየስማቸው አንፃር በመፈረም ይህንን ውል
መስርተዋል፡፡

ተ.ቁ ዝርዝር ጠቅላላ የእጅ ዋጋ በብር ምርመራ


(Lump sum)

1. በጥንቃቄ የጭቃ ቤቱን የማፍረስ ስራ( Demolition)

2. የቁፋሮ ስራ(Excavation)

3. የግንብ ስራ(Masonry)

4. የአርማታ ስራ(Concrete Work)

5. የብሎኬት ግድግዳ ስራ(Block Work)

6. የማሳመር/የአጨራረስ ስራ (Finishing Work)

6.1 የልስን ስራ (Plastering)

6.2 የታይሊንግ ስራ (Tilling Work)

6.3 የቀለም ቅብ ስራ(Painting Work)

7. የጣሪያ ና ቆርቆሮ ማልበስ ስራ(Roofing Work)

8. የበርና መስኮት ስራ( Door & Windows)

9. የመስተዋት ገጠማ ስራ( Glazing Work)

10. የቧንቧ መስመር ገጠማ ስራ(Sanitary Work)


በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክና ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ
የምርታማነት ማሻሻያ እና የልህቀት ማዕከል
11. የመብራት መስመር ስራ(Electrical Work)

ጠቅላላ የእጅ ዋጋ (Lump sum) ቫትን ሳይጨምር 45000.00

ጠቅላላ የእጅ ዋጋ

ስለግዥ ፈፃሚው አካል/አሰሪ ስለአቅራቢው/ተቌራጭ

ምርታማነት ማሻሻያና የልህቀት ማዕከል __________________


ፊርማ፡- ___________ ፊርማ ፡- _____________
ስም ፡-______________________ ስም _________________________
ኃላፊነት፡- ___________________ ኃላፊነት፡- _______________
ቀን፡- __________________ ቀን፡- ________________ .

ምስክሮች
ምርታማነት ማሻሻያና የልህቀት ማዕከል ስም፡-_______________________
ፊርማ፡- __________________ ፊርማ ፡- __________________
ስም ፡- __________________ ስም ___________________
ኃላፊነት፡- _________________ ኃላፊነት፡- ______________
ቀን፡- _____________________ ቀን፡- ____________________

You might also like