You are on page 1of 3

ቀን ………………………… ዓ.

ያህዌ ንሲ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ኩባንያ


የኮንትራት ሥራ ውል ስምምነት

ውል ሰጪ ያህዌ ንሲ ኮንሰትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ኩባንያ


አድራሻው
ውል ተቀባይ
አድራሻው
የፕሮጀክቱ ስም
አድራሻው
አሠሪው መሥሪያ ቤት

የኮንትራቱ ዓይነት፤ በኛንጋቶም ወረዳ በካኩታ ቀበሌ የሚገነባው የእንስሳት ህክምና ክሊኒክ እና በሾንኮራ ቀበሌ የሚገነባው የዓሳ
መጋዘን ግንባታና ተያያዥ ሥራዎች ግንባታ ጠቅላላ የእጅ ዋጋ ብር 180,916.22 (አንድ መቶ ሰማኒያ ሺህ ዘጠኝ መቶ አሥራ
ስድስት ብር ከሀያ ሁለት ሳንቲም ብቻ) ሲሆን፤ ሁሉ ጸንቶ የሚቆየው ከዛሬው ዕለት ጀምሮ ለአንድ ወር ከ 10 ቀን ሲሆን አስፈላጊ
ሆኖ ሲገኝ በሁለቱ ተዋዋዮች ስምምነት የሚራዘም ይሆናል፡፡ይህ ውል በህግ ፊት የጸና ነው፡፡
Y^¨< ¯Ã’ƒ ´`´` SKŸ=Á w³ƒ
1. የእንስሳት ክሊኒክ ግንባታ ጥቅል ___1___
2. የደረቅ ሽንት ቤት ግንባታ ጥቅል ___1___
3. የቆሻሻ ማቃጠያ ግንባታ ጥቅል ___1___
4. የእንስሳት መከተቢያ ጥቅል ___1___
5. የቅጥር ግቢ አጥር ሥራ ጥቅል ___1___
6. የዓሳ ምርት መጋዘን ግንባታ ሥራ ጥቅል ___1___

ሀ) የውል ሰጪ መብትና ግዴታ

1. የሚሠራው ሥራ የእጅ ዋጋን ብቻ የሚያስከፍል ከሆነ ውል ሰጪ አስፈላጊውን ማቴሪያል ያቀርባል፡፡


2. የሚሠራው ሥራ የእጅ ዋጋን የሚያጠቃልል ከሆነ ውል ሰጪ የቁጥጥር ሥራ ብቻ ያከናውናል፡፡
3. በውሉ መሠረት በትክክል ለተከናወኑ ሥራዎች አስፈላጊውን ክፍያ ይፈፅማል፡፡
4. ክፍያው የሚፈጸመው በሥራ ዝርዝሩ መሠረት ለተከናወኑ ሥራዎች ብቻይሆናል፡፡
5. የሚሠራው ሥራ ሙሉ በሙሉ ያልተጠናቀቀ ሆኖ ክፍያ እንዲከፈለው ውል ተቀባይ ከጠየቀ የውል ሰጪ ተወካይ ወይም
ኃላፊ በሚወስነው መሠረት ክፍያው ከተሠራው ሥራ በከፊል ወይም በ 1/3 ኛው ይፈፀማል፡፡
6. ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ወይም ሥራው እንዲቋረጥ የሚያስገድድ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ በተዋዋዮች ስምምነት
ውሉን ሊያቋርጥ ይችላል፡፡
7. ሁሉም የፕሮጀክቱ ግንባታ ሥራዎች በሁለቱም ቀበሌዎች ጎን ለጎን መሠራት አለባቸው፡፡
8. ቅድሚያ ክፍያ የውሉ ሀያ (20) ፐርሰንት ብቻ ሆኖ በሁለት ዙር ክፍያ በሁለቱ ተዋዋዮች ስምምነት በተሰራው ሥራ
መሠረት የሚወሰን ይሆናል፡፡
9. ሁለተኛ ዙር ክፍያ የውሉ ሠላሳ (30) ፐርሰንት ሆኖ በተሰራው ሥራ መሠረት በሦስት ዙር በሁለቱ ተዋዋዮች ስምምነት
የሚከፈል ሆኖ የሚፈጸመውም ውል ተቀባዩ በተቀበለው ቅድመ ክፍያ የሚከተሉትን ሥራዎችን በአግባቡ ማከናወኑ
ሲረጋገጥ ይሆናል፡፡
1)የአፈር ቁፋሮና ተያያዥ ሥራ 2)የግንብ ሥራ 3)የአርማታና ብረት ሥራ 4)የብሎከት ሥራ
10. ሦስተኛ ክፍያ የውሉ ሰላሳ(30) ፐርሰንት ሆኖ በተሰራው ሥራ መሠረት በሁለቱ ተዋዋዮች ስምምነት በሦስት ዙር ክፍያ
የሚፈጸም ሲሆን ክፍያው የሚጀመረው የሚከተሉት ሥራዎች በተገቢ ሁኔታ መፈጸማቸው ሲረጋገጥ ይሆናል፡፡1)የአናጺ
ሥራና 2)የጣሪያ ሥራ 3)የብረታብረት፤የስቲል፤የበርና መስኮት ሥራዎች 4)የወለልና የድንጋይ ንጣፍ ሥራ
11. አራተኛ(የመጨረሻ ዙር) ክፍያ የውሉ ሀያ(20) ፐርሰንት ሆኖ በተሰራው ሥራ መሠረት በሁለቱ ተዋዋዮች ስምምነት
በሁለት ዙር ክፍያ የሚፈጸም ሲሆን ክፍያው የሚጀመረው የሚከተሉት ሥራዎች በተገቢ ሁኔታ መፈጸማቸው ሲረጋገጥ
ይሆናል፡፡1)የመስተዋት ሥራ 2)የአጥር ሥራ 3)የእንስሳት መከተቢያና የእንስሳት ማረፍያ ጥላ ሥራ
12. ከመጨረሻው ዙር ክፍያ 1/2 ኛው እጅ የሚከፈለው የማጠቃለያ ሥራ፤የልስን ሥራ፤የቶክስ ሥራ፤የቀለም
ሥራ፤የኤሌክትሪክ ሥራዎች ሲጠናቀቁና በአጠቃላይ የፕሮጀክቱ ጊዜያዊ ርክክብ ሲፈጸም ይሆናል፡፡
13. ከጠቅላላው ሥራ የመልካም ሥራ አፈጻጸም ዋስትና 5 ፐርሰንት የሚያዝ ሲሆን ጊዜያዊ የፕሮጀክት ርክክብ ከተፈጸመ
በኋላ ውል ሰጪው/ተቋራጩ ከሚቀበለው የመጨረሻ ዙር ክፍያ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡

ለ) የውል ተቀባይ መብትና ግዴታ

1. ውል ተቀባዩ የፕሮጀክቱን ግንባታ ሥራ በንድፍ (በዲሮዊንጉ)ና በሥራ ዝርዝሩ በተቀመጠው ስፔስፊኬሽን መሠረት
የመሥራትና ግልጽ ያልሆነ ነገር በሚያጋጥም ጊዜ የሳይት መሐንዲሱንም ሆነ ሌላ የሚመለከተውን አካል የማማከር
ግዴታ አለበት፡፡

2. የሚሠራው ሥራ የእጅ ዋጋን ብቻ የሚያስከፍል ከሆነ ውል ሰጪ አስፈላጊውን የሰው ኃይልና የእጅ መሣሪያዎችን
የማቅረብ ግዴታ የለበትም፡፡

3. የሚሰራው ሥራ የእጅ ዋጋን ብቻ የሚያጠቃልል ከሆነ ውል ተቀባዩ አስፈላጊውን የሰው ሀይል ያቀርባል፡፡

4. በሥራ ላይ በሠራተኞች ላይ ለሚደርሰው የአካል ጉዳት ውል ተቀባይ የማሣከም ግዴታ አለበት፡፡

5. በውሉ መሠረት ተሠርተው ለተጠናቀቁ ሥራዎች በትክክል መሠራታቸው በውል ሰጪ ሲረጋገጥ ክፍያ መጠየቅ
ይቻላል፡፡ ሆኖም ግን የክፍያው ጥያቄ ቢንያንስ ከሶስት ቀናት በፊት መታወቅ አለበት፡፡

6. ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ወይም በበሽታ ካልሆነ በቀር በምንም ዓይነት ሁኔታ ሥራውን ማቋረጥ ወይም
ማዘግየት አይቻልም፡፡

7. ውሉን ለማቋረጥ ውል ተቀባይ ሲፈልግ በቂ ምክንያት በማቅረብ ውሉን ከሚያቋርጥበት አንድ ሣምንት ቀደም ብሎ
ማሣወቅ አለበት፡፡

8. ካለምንም ማስጠንቀቂያ ውሉን ቢያቋርጥ ወይም ሥራውን አቁሞ ከ 3 ቀን በላይ ከጠፋ የሠራቸው ሥራዎች ክፍያ
ሙሉ ለውል ሰጪ ገቢ ይሆናል፡፡
9. ውል ተቀባይ ለሠራው የሥራ መጠን ከሚከፈለው የክፍያ መጠን ለመልም ሥራ ዋስትና 10% በመያዣነት ይዞ
ሥራው ሲጠቃለል ውል ሰጪ ለውል ተቀባይ ይከፍላል፡፡

ማጠቃለያ፡-
ውል ሰጪና ውል ተቀባይ ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን ሃሳቦች በሙሉ አውቀንና አምነንበት ተስማምተን በዛሬው ቀን ተፈራርመናል፡፡
የውል ሰጪ ህጋዊ ተወካይ ስምና ፊርማ የውል ተቀባይ ስምና ፊርማ

ማሳሰቢያ፡- ይህ ውል በ 3 ኮፒ ተዘጋጅቶ አንድ ለውል ተቀባይ አንድ ለአስተዳደርና ፋይናንስ አንድ ለምሕንድስና አገልግሎት ክፍል
ይሰጣል፡፡
ምስክሮች (ስምና ፊርማ)
1. ………………………………………………. ቀን………………………….
2. ……………………………………………….ቀን………………………….
3. ……………………………………………….ቀን………………………….

You might also like