You are on page 1of 2

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግሰት በደቡብ ኦሞ ዞን የጂንካ ከተማ አስተዳደር ፋ/ኢ/ል ጽ/ቤት የ 2002 በጀት ዓመት ኦዲት

ሪፖርት
1 መግቢያ
የክልሉ ዋናው ኦዲተር መ/ቤት” እንደገና ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 83/1996 በተሰጠው ስልጣንና
ተግባር መሰረት በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግሰት በደቡብ ኦሞ ዞን የጂንካ ከተማ አስተዳደር ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት የ 2002 በጀት
ዓመት ሂሣብ ኦዲት አድርገናል፡፡
2 የሥራ አመራሩና የዋና ኦዲተር መ/ቤት ኃላፊነት
ወቅታዊ የሆኑ የሂሣብ መግለጫዎችን አዘጋጅቶ ማቅረብ የኦዲት ተደራጊው መ/ቤት የሥራ አመራር ኃላፊነት
ሲሆን፣ ¾H>dw SÓKÝ‹” ኦዲት uTÉ[Ó S<Á© ¾*Ç=ƒ አስተያየት መስጠት ደግሞ የክልሉ ዋናው
ኦዲተር መ/ቤት ኃላፊነት ነው፡፡
3 የኦዲቱ ወሰንና ኃላፊነት
ኦዲቱ የተከናወነው ዓለም አቀፍ የኦዲት ደረጃዎችን መሰረት ያደረገው የኢትዮጵያን የመንግስት ሂሳብ የኦዲት ደረጃዎች
በመከተል ነው፡፡ እነዚህን የኦዲት ደረጃዎች መከተል ኦዲቱን በሚገባ አቅደን በመስራት በተዘጋጁት የሂሳብ መግለጫዎች
ላይ አጥጋቢ የሆነ ማረጋገጫ / የኦዲት አስተያት / ለመስጠት ያስችለናል፡፡
ኦዲታችን የሚያካትተው፡-

 በሂሳብ መግጫዎች/ሪፖርቶች/ ላይ የሰፈሩት አሀዞችና መግለጫዎችን የሚደግፉ ማስረጃዎችን በናሙና


በመመርመር ጉልህ ከሆኑ መዛባቶች የጸዱ መሆናቸውን ማረጋገጥን፣
 ዝርዝር የፋይናንስ እንቅስቃሴዎች በክልሉ መንግስት በወጡት አዋጆች፤ ደንቦችና መመሪያዎች መሰረት
መከናወናቸውን በናሙና መመርመርን፤
 የተዘጋጁት የሂሳብ መግለጫዎች የክልሉ መንግስት የሂሳብ አያያዝ ሥርዓት በመከተል የተዘጋጁ መሆኑን
በናሙና መመርመርን፤
 የመንግስት ንብረት አስተዳደር በክልሉ መንግስት በወጡ ህጎች፤ ደንቦችና መመሪያዎች መሰረት መከናወኑን
በናሙና መመርመርን ያጠቃልላል፡፡
ዝርዝር የፋይናንስ እንቅስቃሴዎች ተገቢ የሆኑ አዋጆችን፤ ደንቦችንና መመሪያዎችን በመከተል የተፈጸሙ መሆኑን
እንዲሁም የሂሳብ መግለጫዎች ጉልህ ከሆኑ መዛባቶች የፀዱ ለመሆኑ በቂ ማስረጃና አጥጋቢ ማረጋገጫ የሚሰጥ መረጃና
ማብራሪያ ሊያስገኝ በሚችል መልኩ ኦዲቱን አቅደን አከናውነናል፡፡ ይሁን እንጂ በጽ/ቤቱ የሚታዩትን የውስጥ ቁጥጥርና
ሌሎች ድክመቶችን ሙሉ ለሙሉ ሊያሳይ አይችልም፡፡ የውስጥ ቁጥጥርና ሌሎች ከዚህ ጋር የተያያዙ ግድፈቶችና
ስህተቶች ሁሉ ሊታወቁ የሚችሉት ይህን አስመልክቶ ሰፊ ጊዜ በመውሰድ ልዩ የዝርዝር ኦዲት በጥልቀት ሲከናወን መሆኑን
እንገልጻለን፡፡
¾T>Ÿ}K<ƒ ¾*Ç=ƒ }Å^Ñ>¨< S/u?ƒ ¾H>dw SÓKÝ‹ Ÿ²=I ¾*Ç=ƒ ]þ`ƒ Ò` }Áò¨< k`uªM::
 ¾Ñu= H>dw ]þ`ƒ'
 ¾´¨<¨<` ]þ`ƒ
 የ¨Ü H>dw ሪ þ`ƒ'
 ¾}cwdu= H>dw ]þ`ƒ'
 ¾}ŸóÃ H>dw ]þ`ƒ'
 ¾H>dw TS³²—
 ¾u˃ TS³²—

4 የኦዲት ግኝት፣
1 በሂሳብ እንቅስቃሴ መዝገብ ያልተመዘገበ ብር 171,648.29 በሌጀር ያልተመዘገበ ብር 446.56 የገቢ
ሂሳብ ተገኝቷል፤
2 በማነስ ወደ ገቢ ሂሳብ ሪፖርት የተላለፈ የገቢ ሂሳብ ብር 318,278.92 ተገኝቷል፤
3 በታጠፈ የወጪ ማስመስከሪያ የተመዘገበ በወጪ ሂሳብ ሪፖርት የተላለፈ የወጪ ሂሳብ ብር 3849.00
ተገኝቷል፤
4 ትክክለኛ ባልሆነ የሂሳብ መደብ የተመዘገበና ሪፖርት የተደረገ የወጪ ሂሳብ ብር 993.60 ተገኝቷል፤
5 በሂሳብ እንቅስቃሴ በወጪ ከተመዘገበው ሂሳብ በማነስ ብር 126,684.35 እና በመብለጥ ብር
123,689.35 በወጪ ሂሳብ ሪፖርት የተላለፈ መሆኑ ታውቋል፤
6 ወደ ተሰብሳቢ ሂሳብ መቀየር ሲገባው ያልተቀየረ የሠነድ ሂሳብ ብር 9,532.84 የበጀት ዓመቱ እና ብር
742,749.20 ውዝፍ ተገኝቷል፤
7 ያለአግባብ የተከፈለ የውሎ አበል ሂሳብ ብር 164.50 ተገኝቷል፤
8 የወጪ ማስረጃ ያልቀረበለት የወጪ ሂሳብ ብር 5012.00 ተገኝቷል፤
9 አግባብ ያለው የወጪ ማስረጃ ያልቀረበለት ወጪ ብር 27,322.70 ተገኝቷል፤
10 የንብረት መዝገብ ያልተቋቋመ እና ምዝገባ የማይከናወን መሆኑ ታውቋል፤
11 የንብረት ቆጠራ እየተደረገ ከመዝገብ ከወጪ ቀሪ ጋር የማይመሳከር መሆኑ ታውቋል፤፤

5 አስተያያት
ከላይ በዝርዝር በተገለጹት ምክንያቶች በሂሳብ ሪፖርቶች ላይ የሰፈሩት አሀዞች ጉልህ ከሆኑ መዛባቶች የጸዱ
መሆናቸውን፣ ዝርዝር የፋይናንስ እንቅስቃሴዎች በክልሉ መንግስት በወጡት አዋጆች፤ ደንቦችና መመሪያዎች መሰረት
መከናወናቸውን፤ የተዘጋጁት የሂሳብ መግለጫዎች የክልሉን መንግስት የሂሳብ አያያዝ ሥርዓት በመከተል የተዘጋጁ
መሆኑን፤ የመንግስት ንብረት አስተዳደር በክልሉ መንግስት በወጡ ህጎች፤ ደንቦችና መመሪያዎች መሰረት መከናወኑን
በአጥጋቢ ሁኔታ አያሳይም፡፡

You might also like