You are on page 1of 23

የደቡብ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት

የዋናው ኦዲተር መስሪያ ቤት

The Southern Nations, Nationalities & People Regional State

Office of The Auditor General

የዜጎች ቻርተር

Citizen Charter

2005 ዓም
2013

0
ማውጫ
መግቢያ፣............................................................................................................................................2
የቻርተሩ ዓላማ፡-.................................................................................................................................2
የመ/ቤቱ ተልዕኮ፤ ራዕይ፤ እሴቶች..........................................................................................................3
የመ/ቤቱ ተገልጋዮችና ባለድርሻ አካላት..................................................................................................3
የዋናው ኦዲተር መ/ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ድንጋጌዎች...........................................................................4
የዋናው ኦዲተር መ/ቤት ሥልጣንና ተግባር፤............................................................................................4
ስለኦዲት ሥርዓት ወሰንና የጊዜ ገደብ....................................................................................................6
የኦዲት ተደራጊዎች ግዴታ...................................................................................................................6
የመተባበር ግዴታ.................................................................................................................................6
የማስታወቅ ግዴታ...............................................................................................................................7
ዋናው ኦዲተር መ/ቤት የሚያከናውናቸው የኦዲት ዓይነቶች....................................................................7
ዋናው ኦዲተር መ/ቤት የሚከተለው አሰራር-..........................................................................................8
ኦዲቱን ለማከናወን የተቀመጠ ስታንደርድ............................................................................................10
የሙያ ስነ ምግባር ስታንዳርድ.............................................................................................................10
የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፤የሚከናወኑበት ቦታ፤ክንውኑ የሚወስደው ጊዜ........................................11
የፋይናንሻል ኦዲት ዋና እና ዝርዝር ተግባራት የሚከናወኑበት የጥራት ስታንዳርድ.......................................13
ለክዋኔ ኦዲት ዋና ዋና ተግባራት የተቀመጠላቸው የጥራት ስታንዳርድ.....................................................20
የተገልጋዮች መብት...........................................................................................................................20
ከኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች የሚጠበቁ ቅድመ ሁኔታዎች........................................................................20
አገልግሎቱ በቀጥታ የሚመለከታቸው አካላት.......................................................................................21
አስተያየት የሚሰጥባቸውና ተሳትፎ የሚደረግባቸው ሁኔታዎች..............................................................22
የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ስነ ሥርዓት..............................................................................................22
ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ ችግሮችን አስመልክቶ ካሣና የተለያዩ ማካካሻዎችን ለማድረግ
የሚወሰዱ ኃላፊነቶች........................................................................................................................23
የክትትልና ግምገማ ሥርዓት...............................................................................................................23
የመረጃ ሥርጭትና ግብረ መልስ..........................................................................................................24

1
1 መግቢያ፣
የደቡብ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት ዋናው ኦዲተር መስሪያ ቤት የሚሰጠውን የኦዲት
አገልግሎት ቀልጣፋና የተገልጋዮችንና የባለድርሻ አካላትን ፍላጎት የሚያረካ ለማድረግ፤ በዋናው ኦዲተር
መ/ቤት እና በኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች መካከል ያሉትን የሥራ ግንኙነት ለማሻሻል እንዲሁም ኦዲት ተደራጊ
መ/ቤቶች ስለ ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ተግባር፣ሥልጣንና ኃላፊነት ያላቸው ግንዛቤ ለማሳደግና ለኦዲት ሥራ
ተባባሪ እንዲሆኑ ይረዳ ዘንድ ይህ የዜጎች ቻርተር ተዘጋጅቷል፡፡
በመሆኑም ቻርተሩ የደቡብ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት ዋናው ኦዲተር መስሪያ ቤት
ከኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች ጋር የሚያደርገውን የሥራ ግንኙነት ግልጽ ቀልጣፋና ስኬታማ እንዲሆን
ለሚያደርገው ጥረት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ይታመናል፡፡ በተጨማሪም ቻርተሩ የደቡብ
ብሔሮች፤ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት ዋናው ኦዲተር መስሪያ ቤት ለሚያከናውናቸው ልዩ ልዩ
ኦዲቶች፤ ስለኦዲቶቹ ደረጃና የኦዲት ስልቶች /Auditing Procedures/ ለኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች
ለማስታዋወቅ፤ እንዲሁም ከመ/ቤቶቹ የሚጠበቁትን ትብብሮች ለማሳወቅ እንደሚረዳ ይታመናል፡፡

2 የቻርተሩ ዓላማ፡-
2.1 ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው አሰራር ለማስፈን፤
2.2 ተገልጋዮች ከዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የሚያገኙትን አገልግሎት አውቀውና የሚጠበቅባቸውን
ቅድመ ሁኔታ ተረድተው የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ለማስቻል፤
2.3 የዋናው ኦዲተር መ/ቤት ተልዕኮውን እንዳይወጣ ማነቆ የሆኑ ተግዳሮቶችን ከተገልጋዮች ጋር
በመመካከርና በመተባበር በጋራ ለመቅረፍ፤
2.4 በኦዲት ሥራ ላይ ተገልጋዮችና አገልግሎት ሰጪዎች የባለቤትነት ስሜት እንዲፈጥሩ ለማስቻል፤
2.5 የፋይናንሻል /ሕጋዊነት/ እና የክዋኔ ኦዲት ዋና ዋና የአሠራር ሂደቶችን ግልጽ ለማድረግ እና
2.6 ዋናው ኦዲተር መ/ቤት የልዩ ኦዲት ወይም ምርመራ ሥራ እንዲሠራ በሚጠየቅበት ጊዜ ጥያቄዎችን
ለማስተናገድ የሚጠቀምባቸውን መመዘኛዎችንና የአሠራር ስልቶችን ለመግለጽ ነው፡፡

3 የመ/ቤቱ ተልዕኮ፤ ራዕይ፤ እሴቶች

3.1 ተልዕኮ
በክልሉ የኦዲት ስርዓትን በማጠናከር የክልሉ መንግስት መ/ቤቶች ተግባራቸዉን በወጡ ህጎች፤ ደንቦችና
መመሪያዎች መሰረት ስለማከናወናቸዉ እንዲሁም የሚጠበቅባቸዉን ግብ ለሟሟላት በቅልጥፍናና
ኢኮኖሚያዊ በሆነ መንገድ ስለመፈጸማቸዉ ተቀባይነት ያላቸዉን የኦዲት ደረጃዎች በመጠቀም ቀልጣፋ
የኦዲት አገልግሎት በመስጠት ለክልሉ ም/ቤትና ለሚመለከታቸዉ አካላት ነጻና አስተማማኝ መረጃ
ማቅረብ፡፡
3.2 የመ/ቤቱ ራዕይ

2
በ 2017 ዓ.ም ለክልሉ ኢኮኖሚ ዕድገትና መልካም አስተዳደር መስፈን አስተዋጽኦ የሚያደርግ የኦዲት
አገልግሎት የሚሠጥ ሞዴል ተቋም ሆኖ ማየት፡፡
3.3 የመ/ቤቱ እሴቶች
የመ/ቤቱ የአሠራር ባህል የሚገልጹ እሴቶች
 ግልጸኝነትና ተጠያቂነት ማስፈን መሠረታዊ የተልዕኮአችን መገለጫ ነው፡፡
 ሙያዊ ነፃነትና ብቃት ማጐልበት የሥራዎቻችን ጥራት ማረጋገጫ ነው፡፡
 በመማማርና በመደጋገፍ መልካም የሥራ ግንኙነት መመስረት መሠረታዊ የጋራ አመለካከታችን ነው
 መልካም የሙያ ሥነ-ምግባር እሴቶች መላበስ የሥራዎቻችን አፈፃፀም ጥራት መለኪያችን ነው፡፡
 ደንበኞቻችንን በቅንነት፤ በትህትናና በታማኝነት ማገልገል ልዩ መለያችን ነው፡፡

3.4 የመ/ቤቱ ተገልጋዮችና ባለድርሻ አካላት


3.4.1 የመ/ቤቱ ተገልጋዮች
 የክልሉ ምክር ቤት
 ኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች
3.4.2 ባለድርሻ አካላት
 የክልሉ ምክር ቤት
 የክልሉ ህዝብ
 መስተዳደር ምክር ቤት
 የፌደራልና የክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤቶች
 የፍትህ አከላት
 ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ
 ዕርዳታና ብድር ሰጪ የልማት አጋሮች

4 የዋናው ኦዲተር መ/ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ድንጋጌዎች

4.1 የዋናው ኦዲተር መ/ቤት ሥልጣንና ተግባር፤


4.1.1 የክልል ምክር ቤት ጽ/ቤትን ጨምሮ በክልሉ የሚገኙ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች እና ድርጅቶችን
ሂሣብ ዕርዳታዎችንና ስጦታዎችን አካቶ ኦዲት ያደርጋል፣ያስደርጋል፤
4.1.2 የክልል ምክር ቤት ጽ/ቤትን ጨምሮ በክልሉ የሚገኙ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች እና ድርጅቶችን
አጠቃላይ የቁጥጥር ሥርዓት በበቂ ሁኔታ መነደፉንና በትክክለኛ መንገድና በብቃት ተግባራዊ መሆኑን
ለማረጋገጥ የቁጥጥር ምርመራ ያደርጋል፤ያስደርጋል፤

3
4.1.3 የክልል ምክር ቤት ጽ/ቤትን ጨምሮ በክልሉ የሚገኙ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች እና ድርጅቶች
ያስገኙት ውጤት ሕጉን የተከተለ፣ ኢኮኖሚያዊ በሆነ አሠራር የተፈጸመ መሆኑንና ተፈላጊውን ግብ
መምታቱን ለማረጋገጥ እንደ አስፈላጊነቱ የክዋኔ ኦዲት ያደርጋል፤ ያስደርጋል፤
4.1.4 የክልል መንግሥት ከብር 5 ዐዐ,ዐዐዐ /አምስት መቶ ሺህ ብር/ በላይ የሚጠይቅ ሥራ የግል ሥራ
ተቋራጮች እንዲሠሩ በውል የሰጠ እንደሆነ ይህንኑ መንግሥት ነክ የሆነ የግል ሥራ ተቋራጮች ሂሣብ
ይመረምራል፡፡ ሆኖም የማጭበርበር ድርጊት ለመፈጸሙ ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ፍንጭ ያገኘ እንደሆነ
ሥራው የሚጠይቀው ገንዘብ ከብር 500000/አምስት መቶ ሺህ ብር/ በታች ቢሆንም የመንግስት
ሥራ ነክ የሆነ የተቋራጮች ሂሳብን ይመረምራል፤ያስመረምራል፤
4.1.5 በክልል ምክር ቤት ጥያቄ፤በመደበኛ የኦዲት ሥራ ጊዜ የዋናው ኦዲተር መ/ቤት በሂሳቡ ላይ ተንኮል
ለመሰራቱ ፍንጭ ከታየ፤ በፍርድ ቤቶች አግባብ ያለው ትዕዛዝ ሲቀርብና እንዲሁም በጉዳዩ ክብደት
ላይ ተመስርቶ ከመንግስት መ/ቤቶች፤ ከድርጅቶችና ከህብረተሰቡ በሚቀርበው ጥያቄና ጥቆማ
በመነሳት ከመደበኛ ኦዲት ውጭ የልዩ ኦዲት ያከናውናል፤ እንዲከናወን ያስደርጋል፤
4.1.6 ከዚህ በላይ በሰፈሩት ድንጋጌዎች መሰረት ያከናወነውን የኦዲት ሥራ ውጤት አግባብ ላለው
የመንግስት መ/ቤት ወይም ለድርጅቱ የበላይ ኃላፊ ያሳውቃል፡፡ የኦዲት ውጤቱ ወንጀል መፈጸሙን
የሚያሳይ ሆኖ ሲገኝ ለሚመለከተው አካል ወዲያውኑ ሪፖርት ያደርጋል፣
4.1.7 ጉዳዩ ከሚመለከታቸው መሥሪያ ቤቶች እና ድርጅቶች እንዲሁም ከፌደራልና ከሌሎች ክልል የኦዲት
መ/ቤቶች ጋር በመመካከር የኦዲት ደረጃ /ስታንዳርድ/ እና የአሰራር ሥርዓት መወሰኛ መመሪያዎችን
ያወጣል፤
4.1.8 አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ከሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶችና ድርጅቶች ጋር በመተባበር ለውስጥ
ኦዲተሮች ተገቢውን ስልጠናና የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምስክርነት ይሰጣል፤ እንደ አስፈላጊነቱም
የውስጥ ኦዲት ሪፖርት እንዲቀርብለት ሊያደርግ ይችላል፤
4.1.9 አንድ ሂሣብ ወንጀል ባለበት ሁኔታና ታማኝነት በጎደለው አኳኋን መያዙን ለማመን ምክንያት ያለው
እንደሆነ ይህንኑ ሂሣብ የሚመለከቱ ጽሑፎች፣ መዘክሮች፣ መዝገቦች፣ ሰነዶችና ሌሎች ተያያዥነት
ያላቸው መረጃዎች ላይ ያሽጋል፤
4.1.10 የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ስለገንዘብና የሂሣብ አጠባበቅ በሚያዘጋጀው ህግና ደንብ
ረቂቆች ላይ አስፈላጊውን ምክርና አስተያየት ይሰጣል፣
4.1.11 ከሚመለከታቸው የፌዴራልና የክልል መንግስታት መሥሪያ ቤቶች ጋር በመተባበር የሂሣብ አያያዝ እና
የኦዲት ሙያ ትክክለኛውን ፈር ይዞ እንዲዳብር ጥረት ያደርጋል፤
4.1.12 በክልሉ ውስጥ በኦዲት ሙያ ለሚሰማሩ ኦዲተሮችና የሂሳብ አያያዝ ሥራ ለሚያከናውኑ የሂሳብ
አዋቂዎች በስራው መስክ ለመሰማራት የሚያስችላቸውን የምስክር ወረቀት ይሰጣል፤ያድሳል፤
ያግዳል፤ ይሰርዛል፤

4
4.1.13 ከፌደራል መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት ጋር በመተባበር የኦዲተሮችንና የሂሳብ አያያዝ
ባለሙያዎችን የብቃት ማረጋገጫ የምስክርነት ወረቀት ለመስጠት፤ ለማደስ፤ለማገድ እና ለመሰረዝ
የሚያስችል ወጥነት ያለው ደረጃ ያወጣል፤
4.1.14 የምሥክር ወረቀት በሚሰጥበትና በሚያድስበት ጊዜ በሚያወጣው መመሪያ መሠረት ተገቢውን ዋጋ
ያስከፍላል፤
4.2 ዋናው ኦዲተር ያከናወነውን የምርመራ ውጤት ለተመርማሪው መስሪያ ቤት/ድርጅት/ኃላፊ ያሳውቃል፡፡
የተመርማሪ መ/ቤትና ድርጅት የበላይ ኃላፊ በምርመራ ውጤት ላይ የሚሰጠውን
አስተያየት፤የሚያቀርበው ተቃውሞ አጥጋቢ ያለመሆኑን ዋና ኦዲተሩ የገመተ እንደሆነ የተሰጠውን
አስተያየትና የቀረበውን ተቃውሞ መ/ቤቱ በሚያቀርበው ዓመታዊ ሪፖርት ውስጥ ማስገባት አለበት፡፡

4.3 ስለኦዲት ሥርዓት ወሰንና የጊዜ ገደብ


4.3.1 መ/ቤቱ አንድን ሂሳብ ኦዲት ሲያደርግ የኦዲት ተደራጊ መ/ቤትን የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓት
በመገምገም አንድ በአንድ/በዝርዝር/ ወይም በአልፎ አልፎ የኦዲት ዘዴ ሊመረምር ይችላል፡፡ ሂሳቦችን
ኦዲት አድርጎ በሚያቀርበው ዘገባ ውስጥ ለእያንዳንዱ ሂሳብ የኦዲት ዘዴውን ሁኔታና ጥልቀት
መግለጽ አለበት፡፡
4.3.2 መ/ቤቱ በሚያከናውናቸው የኦዲት ሥራዎች ኦዲት ከሚደረግበት የበጀት ዓመት ወደኋላ ከሁለት
በጀት ዓመታት ማለፍ የለበትም፡፡ ነገር ግን ወንጀል ተፈጽሟል ብሎ ያመነ እንደሆነ ከተባሉት ሁለት
የበጀት ዓመታት አልፎም ቢሆን ኦዲት ሊያደርግ ይችላል፡፡

4.4 የኦዲት ተደራጊዎች ግዴታ


4.4.1 ማንኛውም ሰው ኦዲተሩ ለኦዲት ሥራ አስፈላጊ ናቸው ያላቸውን ሰነዶች፤ የቃል ማስረጃዎች እና
ወይም ሌሎች መረጃዎችን እንዲያቀርብ በተጠየቀ ጊዜ የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡
4.4.2 መ/ቤቱ እንዲቆጣጠራቸው ስልጣን የተሰጠውን አካላት ገንዘብ ወይም ንብረት የተረከበ፤ ወጪ
ያደረገ፤የከፈለ ወይም ለሂሳብ ኃላፊ የሆነ ማንኛውም ሰው ሲጠየቅ ሂሳቡን ኦዲት የማስደረግ ግዴታ
አለበት፡፡
4.4.3 ኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች በመ/ቤቱ በተላኩ ሪፖርቶች ውስጥ የተገለጹ ግኝቶችን አስመልክቶ
ተገቢውን የእርምት እርምጃ እንዲወስዱ በተሰጠው የማሻሻያ ሀሳቦችና አስተያየቶች መሰረት
በተሰጠው ቀነ ገደብ ጊዜ ውስጥ እርምጃ የመውሰድና ውጤቱን የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው፡፡

5
4.4.4 የኦዲት ተደራጊ መ/ቤትን ሂሳብ ኦዲት ለማድረግ እንዲቻል በሕግ ጥላ ሥር የሚገኝ ጉዳዩ
የሚመለከተው ግለሰብ በሚጠይቅበት ጊዜ ለማስመርመር ግዴታ አለበት፡፡

4.5 የመተባበር ግዴታ


4.5.1 መ/ቤቱ ሥልጣኑንና ተግባሩን ሥራ ላይ ለማዋል እንዲችል ማንኛውም ሰው አስፈላጊውን ድጋፍ
መስጠት ይኖርበታል፡፡

4.6 የማስታወቅ ግዴታ


4.6.1 የመ/ቤቱ
4.6.1.1 የክልሉ ዋናው ኦዲተር መ/ቤት የኦዲት ሥራ በሚያከናውንበት ጊዜ ወንጀል መፈጸሙን
የሚያሳምን በቂ ምክንያት ያገኘ እንደሆነ ይህንኑ ለክልል ፍትህ ቢሮና ለሚመለከታቸው አካላት
የማስታወቅ ግዴታ አለበት፡፡
4.6.2 ሌሎች አካላት
4.6.2.1 መ/ቤቱ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባር በአግባቡ ለመወጣት ያስችለው ዘንድ በክልሉ ውስጥ
ተፈጻሚነት ያላቸው መመሪያዎች እንዲወጡ ሲደረግ የሚመለከተው አካል መ/ቤቱን የማሳወቅ
ግዴታ አለበት፡፡

5 ዋናው ኦዲተር መ/ቤት የሚያከናውናቸው የኦዲት ዓይነቶች


5.1 የፋይናንሻል ኦዲት፡-
የፋይናንሻል /ሕጋዊነት/ ኦዲት የክልሉ መንግሥት ገንዘብና ንብረት አግባብ ባላቸው ሕጎች ደንቦችና
መመሪያዎች መሠረት መጠበቁንና በአግባቡ ሥራ ላይ መዋሉን፤የመንግሥት ገቢ በትክክል መሰብሰቡን
እንዲሁም ኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች የሚያዘጋጇቸው የሂሳብ መግለጫዎች(Financial Statements) ጎላ ያለ
ስህተት (material misstatement) የሌለባቸው መሆኑን ለማረጋገጥ የሚከናወን የኦዲት ዓይነት ነው፡፡ ኦዲቱ
ሶስት ዋና ዋና ምዕራፎች(Stages) አሉት፡፡ ምዕራፎቹም፤
 የቅድመ ዕቅድና ስትራቴጂክ ዕቅድ (pre-engagement activities & strategic planning)
 የዝርዝር ዕቅድና ኦዲት( Detail planning & field work)
 የሪፖርቲንግ (Reporting) ናቸው፡፡
ኦዲቱ የዋና ኦዲተር መ/ቤት በሚያዘጋጀው ዓመታዊ የኦዲት ሥራ ዕቅድ መሰረት ይከናወናል፡፡
5.2 የክዋኔ ኦዲት፡-

6
የክዋኔ ኦዲት የክልሉ መንግስት መ/ቤቶች ዕቅዶች፣ ፕሮጀክቶችና ፕሮግራሞች ኢኮኖሚያዊ፤ ውጤታማና
ብቃት ያለው አፈጻጸም እንዲኖራቸው የሚያስችል ግብዓት ለመስጠት የሚከናወን የኦዲት ዓይነት ነው፡፡
ኦዲቱ አራት ደረጃዎች ያሉት ሲሆን ደረጃዎቹም፤
 የቅድመ ኦዲት ሥራዎች( pre-engagement activities)
 የዳሰሳ እና የአዋጭነት ጥናት (Overview & Feasibility study)
 ዝርዝር የኦዲት ዕቅድ ማዘጋጀትና ኦዲት ማድረግ (Detail Planning & execution)
 ሪፖርቲንግ (reporting) ናቸው፡፡
ኦዲቱ የዋና ኦዲተር መ/ቤት በሚያዘጋጀው ዓመታዊ የኦዲት ሥራ ዕቅድ ወይም በክልል ም/ቤት ጥያቄ
መሰረት በማንኛውም ጊዜ ተጀምሮ ሊከናወን ይችላል፡፡
5.3 ልዩ ኦዲት (Investigation)፡-
ከክልል ምክር ቤት፤ ከስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን፤ ከፍርድ ቤቶች፤ ከኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች እና
ክህብረተሱ በሚቀርብ ኦዲት ይደረግልን ጥያቄና ጥቆማ መሰረት የሚከናወን ኦዲት ሲሆን የኦዲት ሥራውም
እንደጉዳዩ ዓይነት የሚለያይ ነው፡፡
የዋና ኦዲተር መ/ቤት የሚቀርብለትን የልዩ ኦዲት ጥያቄ ለመቀበል ወይም ላለመቀበል ውሣኔ ላይ ከመድረሱ
በፊት ጥያቄው አምሰት መመዘኛዎችን ማሟላቱን ያረጋግጣል፡፡
መመዘኛዎቹም የሚከተሉት ናቸው
5.3.1 ጥያቄው ለዋናው ኦዲተር መ/ቤት በአዋጅ ከተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት ጋር የሚጣጣም መሆኑን፤
5.3.2 ሥራውን ለመሥራት የሚያስችል ብቃትና ግብዓት መኖሩን፤
5.3.3 ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ጥያቄውን ቢቀበል በበጀት ዓመቱ ያቀዳቸው መደበኛ የኦዲት ሥራዎችንም
ማጠናቀቅ መቻል አለመቻሉን፤
5.3.4 እንዲሠራ የተጠየቀው ኦዲት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ መሥራት የሚቻል መሆን
አለመሆኑን፤
5.3.5 የዋናው ኦዲተር መ/ቤት የሙያ ነፃነትን የማይነካ እንዲሁም የዋናው ኦዲተር መ/ቤት የኦዲት
ደረጃዎችን ለመተግበር ማስቻል አለማስቻሉ የሚሉ ናቸው፡፡
በተጨማሪም ከመ/ቤቶቹ የተጠየቁት የኦዲት/የምርመራ ይደረግልን ጥያቄዎች፣ መመዘኛዎቹን ቢያሟሉም
እንኳ በአንድ ጊዜ ከተለያዩ አካላት በርካታ ጥያቄዎች ከቀረቡ ሁሉንም መቀበል ስለማይቻል የቀረበው ጥያቄ
ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ ወይም የንብረት ምዝበራን የሚመለከት ከሆነ ቅድሚያ ሊሰጠው ይችላል፡፡

7
6 ዋናው ኦዲተር መ/ቤት የሚከተለው አሰራር-
6.1 የኦዲት ሪፖርቶች በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሰረቱ፤ ሚዛናዊና የኢትዮጵያ መንግስት የኦዲት
ደረጃዎችን (Ethiopian government auditing standards) እና ዓለም አቀፍ የመንግስት ኦዲት
ደረጃዎችን (International government auditing standards) ያሟሉ ይሆናሉ፡፡
6.2 ኦዲቶች ሲካሄዱና ሲጠናቀቁ የኢትዮጵያ መንግስት የኦዲት ደረጃዎችን (Ethiopian government
auditing standards) እና ዓለም አቀፍ የመንግስት ኦዲት ደረጃዎችን (International government
auditing standards) ያሟሉ እንዲሆኑ በየደረጃው ተገቢውን የጥራት ቁጥጥር (quality control)
ያደርጋል፡፡
6.3 ኦዲት ከመጀመሩ በፊት የትብብር ደብዳቤ ለክዋኔና ለፋይናንሻል ኦዲት፤ በተጨማሪም
የኢንጌጅመንት ደብዳቤ(engagement letter) ለፋይናንሻል ኦዲት ይልካል፡፡
6.4 የኦዲት ቡድን ኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች እንደደረሰ የትብብርና የኢንጌጅመንት ደብዳቤ
ይሰጣል፤የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት የመግቢያ (entrance) ስብሰባዎችን በማድረግ ስለኦዲቱ
አጠቃላይ ሁኔታ ማብራሪያ ይሰጣል፤
6.5 ከላይ በተራ ቁጥር 6.4 የተገለጸው ቢኖርም ለማከናወን የታሰበው ልዩ ኦዲት ከሆነና ስለ ኦዲቱ
መጀመር በቅድሚያ ማሳወቅ በሥራው ሂደትና ውጤት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ሊኖረው ይችላል ተብሎ
ከታሰበ ስለኦዲቱ መጀመር በቅድሚያ ላይገለጽ ይችላል፡፡
6.6 የፋይናንሻል /ሕጋዊነት/ ተከታታይ ኦዲት የመጀመሪያ ዙር እንደተጠናቀቀ ረቂቅ የማኔጅመንት
ደብዳቤ (draft management letter) ተዘጋጅቶ ለኦዲት ተደራጊው ይሰጣል፡፡
6.7 የሚከናወኑ ኦዲቶች /ምርመራዎች/ በኢንጌጅመንት ደብዳቤው በተቀመጠው የጊዜ ገደብ
እንዲጠናቀቁ ያደርጋል፤
6.8 የተከታታይ ኦዲቱ 2 ኛ ዙር የኦዲት ሥራ ሲጠናቀቅ፤ የክዋኔ እና በተከታታይ ኦዲት የማይሸፈኑ
መ/ቤቶች የፋይናንሻል ኦዲት እንደተጠናቀቀ የመውጫ ስብሰባ ይደረጋል፡፡ የስብሰባው ዓላማ ኦዲቱ
በተከናወነበት ጊዜ የተገኙት ግኝቶችና ግኝቶቹም በተሟላ ማስረጃ የተደገፉ መሆኑን የኦዲት ተደራጊ
መ/ቤቶች እንዲያውቁት ለማድረግ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በኦዲቱ ወቅት የተገኙትን ችግሮች
/ግኝቶች/ ለመፍታት ያስችላሉ ተብለው በቀረቡት የማሻሻያ ሀሣቦችና የተደረሰባቸው
መደምደሚያዎች በስብሰባው ውይይት ይደረግባቸዋል፡፡ በስብሰባው ላይ ጉዳዩ የሚመለከታቸው
የኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች እና ሥራው የሚመለከታቸው የዋናው ኦዲተር መ/ቤት ኃላፊዎች
ይገኛሉ፡፡ በስብሰባው ወቅት ኃላፊዎቹ የሚሰጡት አስተያየት በቃለ ጉባኤ ከተያዘ በኋላ ተፈርሞበት
አስተያየቱ በመጨረሻው ሪፖርት ውስጥ እንዲካተት ይደረጋል፡፡

8
6.9 በክልል ምክር ቤት፣ በፍርድ ቤቶች፣ በሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ተጠይቆ ለሚካሄዱ የልዩ
ኦዲት ሥራዎች የመውጫ ስብሰባ ላይደረግ ይችላል፡፡ ኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች በተገኙ ግኝቶችና
በተደረሰባቸው ድምዳሜዎች ላይ አስተያየት አንዲሰጡ ላይጠየቁ ይችላሉ፡፡
6.10 የፋይናንሻልና ክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ለኦዲት ተደራጊ መ/ቤት ይላካል፣ የልዩ ኦዲት ሪፖርት ለጠየቀው
አካል ይላካል፣ እንደአስፈላጊነቱ ግልባጭ ለሚደረግላቸው አካላት ይልካል፡፡
6.11 ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ለሥራው የሰበሰባቸውን መረጃዎች በተለይም በከፍተኛ ጥንቃቄ መጠበቅ
የሚገባቸውን በጥንቃቄ የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ መረጃውን የሰጠው መ/ቤት የሚጠይቀውን
የመረጃ አጠባበቅ ሥርዓት ለማሟላትም ዋናው ኦዲተር መ/ቤት የተቻለውን ጥረት ያደርጋል፡፡ ሆኖም
ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ጥንቃቄ የሚያስፈልገውን መረጃ ለማግኘት የመፈረም ወይም ከኦዲት
ተደራጊው መ/ቤት ጋር የተለየ ስምምነት የማድረግ ግዴታ የለበትም፡፡
6.12 ከተለያዩ አካላት የሚቀርብ የልዩ ኦዲት ጥያቄ ተቀባይነት ካገኘ ሥራው መቼ እንደሚጀመር
ተቀባይነት ካላገኘ ደግሞ ምክንያቱን በ 1 ዐ የሥራ ቀናት ውሰጥ ጥያቄውን ላቀረበው መ/ቤት
ይገልጻል፡፡
6.13 ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ከክልል ምክር ቤት በጽሁፍ ከተጠየቀ ሪፖርታቸው ለህዝብ ይፋ ለሆኑ
ኦዲቶች ደጋፊ የሆኑ ኦዲቱ በተከናወነበት ወቅት የተዘጋጁ ሰነዶችንና መረጃዎችን ለምክር ቤቱ
ሊሰጥ ይችላል፡፡ ሥራው በሂደት ላይ ያለ ኦዲት ወይም ምርመራ በሚከናወንበት ወቅት የተያዙ
የኦዲት መረጃዎች ለማንኛውም አካል አይሰጥም፡፡

7 ኦዲቱን ለማከናወን የተቀመጠ ስታንደርድ

7.1 የሙያ ስነ ምግባር ስታንዳርድ


7.1.1 *Ç=}` ¾*Ç=ƒ ›e}Á¾ƒ” u’é’ƒ እ”ÇÃcØ Ý“ ¾T>ðØ` T”—¨<”U Ñ<x' eÙ ታና Ów¹
Ÿ*Ç=ƒ }Å^Ñ>‹ SkuM ¾KuƒU'
7.1.2 *Ç=}` Ÿ*Ç=ƒ }Å^Ñ> ¾Se]Á u?ƒ ኃላፊ' W^}— ¨ÃU K?KA‹ u*Ç=~ Là }ê°• K=ÁXÉ\
ŸT>‹K<“ ¾*Ç=~” Y^ ’é’ƒ ØÁo ¨<eØ ŸT>Ÿ~ ›"Lƒ Ò` ¾ÓM Ó”–<’ƒ K=ÁÅ`Ó
›ÃÑvU::
7.1.3 *Ç=}` ¾Y^¨<” ኃ Lò’ƒ KÓM ØpU TªM ¾KuƒU' ›”Ç=G<U ¾S<e“ YÒ„‹” ŸT>ðØ`“
¾*Ç=~” Y^ Ø`×_ ¨<eØ ŸT>Ÿ~ Ó”–<’„‹ SqÖw ›Kuƒ::
7.1.4 *Ç=}` ¾*Ç=ƒ Y^ uT>ÁŸ“¨<”uƒ Ñ>²? Ÿ*Ç=ƒ }Å^Ñ>¨< S/u?ƒ W^}™‹“ ኃላፊዎች Ò`
Y^” T°ŸM vÅ[Ñ SÓvvƒ“ SŸvu` SY^ƒ ›Kuƒ ¨ÃU Y^” T°ŸM "Å[Ñ Ó”–<’ƒ vhÑ` Ó”–
<’ƒ SõÖ` ¾KuƒU::

9
7.1.5 *Ç=}` Y^¨<” uT>ÁŸ“¨<”uƒ Ñ>²? ¾Y^ ኃ Lò’~” uSÖkU u*Ç=ƒ }Å^Ñ>‹ Là }Ñu= ÁMJ’
Ý“ SõÖ` ¾KuƒU'
7.1.6 *Ç=}` *Ç=ƒ ŸT>ÁÅ`Ѩ< S/u?ƒ wÉ` SÖ¾pU J’ S¨<cÉ ¾KuƒU::
7.1.7 *Ç=}` *Ç=ƒ ¾T>ÁÅ`Óuƒ ¾H>Xw c’Ê‹“ Ÿ*Ç=ƒ }Å^Ñ>‹ ¾}cÖ<ƒ” ¾Y^ SX]Á‹
በታማ˜’ƒ Öwq Y^¨<” እ”ÇÖ“kk SSKc Õ`u ታ M::
7.1.8 *Ç=}` ¾S”ÓYƒ” Y^ c¯ƒ u›Óvu< KS”ÓYƒ Y^ TªM ›Kuƒ :
7.1.9 ¾*Ç=}` ª“ ƒŸ<[ƒ uÓ˜„‡ Là єu=“ ¾Te}"ŸÁ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ›e}Á¾ƒ KSeÖƒ
እ”Í= eI}ƒ ðLÑ> w‰ SJ” ¾KuƒU::
7.1.10 *Ç=}` ¾Se]Á u?~” SM"U eU ¾T>Öwp“ ¾›c^` vIM እንዲዳብር ¾T>Ø` SJ” ›Kuƒ::
7.1.11 *Ç=}` uY^ ›Ò×T> ¾Á³†¨<” T”—¨<U óÃM T>eÖ=^©’ƒ SÖup ›Kuƒ::
7.1.12 *Ç=}` *Ç=ƒ eKT>Å[Ѩ< Se]Á u?ƒU J’ W^}— Ÿ›ÉKA©’ƒ ’é J• S[Í uTcvcw ƒ¡¡K—
ÉUÇT@ LÃ K=Å`e ÃÑvM::

7.2 የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፤የሚከናወኑበት ቦታ፤ክንውኑ የሚወስደው ጊዜ


7.2.1 ፋይናንሻል ኦዲት
  ዋና እና ዝርዝር ተግባራት ሥራው ሥራው አንድ ክንውን የሚወስደው ጊዜ
 ተ   የሚከናወንበት የሚከናወንበት በሰዓት
ራ ቦታ ጊዜ
ቁ     አነስተኛ መካከለኛ ከፍተኛ
1 የቅድመ ዕቅድና በኦዲት ዋና ከየካቲት- 106.00 241 275.00
ስትራቴጂክ ዕቅድ (pre- ሥራ ሂደት ታህሳስ
engagement activities ቢሮ ውስጥና
& strategic planning) በመስክ

2 የዝርዝር ዕቅድና ከየካቲት- 116.00 363.00 499.0


ታህሳስ 0
ኦዲት(Detail በመስክ
planning&field work)
3 የሪፖርት (Reporting) በኦዲት ዋና ከየካቲት- 52.00 91.20 97.00
ሥ/ሂ/ ታህሳስ
  ድምር 274.00 697.00 871.0
0

7.2.2 የክዋኔ ኦዲት ዋና ዋና ተግባራትና የጊዜ ስታንዳርድ

10
ተ.ቁ ዋና እና ዝርዝር ተግባራት አንድ ክንውን የሚወስደው ጊዜ በሰዓት
ስራዎች ስራዎች
የሚሰሩበት የሚሰሩበት
ቦታ ወቅት ዝቅተኛ መካከለኛ ከፍተኛ
ስጋት ስጋት ስጋት
1 የቅድመ ኦዲት ሥራዎች ( pre- በኦዲት ዋናሥ/ሂ ከነሐሴ-ሰኔ 24 30 30
engagement activities) ቢሮ ውስጥ
2 የዳሰሳ እና የአዋጭነት ጥናት ከነሐሴ-ሰኔ 859 998 1343
(Overview & Feasibility መስክ ላይ
study)
3 ዝርዝር የኦዲት ዕቅድ ማዘጋጀትና ከሐምሌ-ሰኔ 1334 1508 1794
ኦዲት ማድረግ (Detail መስክ ላይ
Planning& ececution)
4 ሪፖርቲንግ (reporting) በኦዲት ከሐምሌ-ሰኔ 314 358 392
ዋና/ሥ/ሂ/ ቢሮ
ውስጥ
ድምር 2531 2894 3559

7.3 የፋይናንሻል ኦዲት ዋና እና ዝርዝር ተግባራት የሚከናወኑበት የጥራት ስታንዳርድ


7.3.1 (ለከፍተኛና መካከለኛ ስጋት ኦዲት)
መለያ ዋናና ዝርዝር ተግባራት ማጠናቀቅ መከለስ
Completed by Reviewed
by
PE የቅድመ ኦዲት ሥራዎች ማጠናቀቅ PRE-
ENGAGEMENT ACTIVITIES
 PE1 የሙያ ስነ-ምግባር መግለጫ ማስሞላት CODE OF ኦዲት ማናጀርና ዳይሬክተር
ETHICS የኦዲት ቡድን (director)
አባላት(each team
member)
 PE2 የኦዲት ቲም ብቃት ማጣሪያ ማስሞላት ማናጀር/manager/ ዳይሬክተር
COMPENTENCY MATRIX OF AUDIT TEAM (director)
 PE3 የኦዲት ቲም ስምምነት ማስሞላት TEAM ቡድን መሪ ማናጀር/ma
AGREEMENT (Team leader) nager/
 PE4 የታቀደውና በስራ ላይ የዋለው ሰአት ማስሞላት ቡድን መሪ ማናጀር/ma
BUDGETED vs ACTUAL HOURS (Team leader) nager/
 PE5 የኦዲት ስራ ስምምነት ደብዳቤ /Engagement letter ማናጀር ዳይሬክተር
ማዘጋጀት እና መፈረም /manager/ (director)
ለኦዲት ተደራጊው መ/ቤት የትብብር ደብዳቤ ማዘጋጀትና ማናጀር ዳይሬክተር
መፈረም /manager/ (director)
PE6 Quality control questionnaire (የጥራት ቁጥጥር ማናጀር ዳይሬክተር
መጠይቅ መሙላት) /manager/ (director)

11
መለያ ዋናና ዝርዝር ተግባራት ማጠናቀቅ መከለስ
Completed by Reviewed
by

P የኦዲት ዕቅድ ማዘጋጀት


 P1 የጉልህነት መጠን መወሰን/planning matariality/ ቡድን መሪ ማናጀር/ma
(Team leader) nager/
P2 በባለፈው አመት ጉዳዮች ላይ ክትትል ማድረግ FOLLOW ቡድን መሪ
UP PRIOR YEAR’S MATTERS ኦዲተር (Team
(Auditor) leader)

 P3 ቡድን መሪ ማናጀር/ma


ግምገማ የሚደረግባቸው ሂሳቦች መለየት/lead schedule/ (Team leader) nager/
 P4 የመጀመሪያ የትንተና ክለሳ ማድረግ PRELIMINARY ቡድን መሪ ማናጀር/ma
ANALYTICAL REVIEW (Team leader) nager/
 P5 የውስጥ ኦዲት ግምገማ ማድረግ REVIEW OF ኦዲተር ቡድን መሪ
INTERNAL AUDIT (Auditor) (Team
leader)

 P7 የማጭበርበር ማጣሪያ ሊስት መሙላት FRAUD ኦዲተር ቡድን መሪ


CHECKLIST (Auditor) (Team
leader)

 P8 የቁጥጥር አካባቢ ማጣሪያ ሊስት መሙላት CONTROL ኦዲተር ቡድን መሪ


ENVIRONMENT CHECKLIST (MANUAL) (Auditor) (Team
leader)

 P12 የባለሙያ የስራ ውጤት መጠቀም USING THE WORK


እንደ አስፈላጊነቱ As required
OF AN EXPERT
 P13 የባህሪያዊ ስጋት በፋይናንሽያል መግለጫ ደረጃ መረዳት
ማናጀር ዳይሬክተር
INHERENT RISK ON A FINANCIAL
/manager/ (director)
STATEMENT LEVEL
 P14 አጠቃላይ የኦዲት ስትራቴጂ ማዘጋጀት OVERALL ቡድን መሪ ማናጀር/ma
AUDIT STRATEGY (Team leader) nager/
 P16 የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት መግለጫ /system description for ኦዲተር ቡድን መሪ
audit components/ ማዘጋጀት (Auditor) (Team
leader)

 P17 በውስጥ ቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ መተማመን ስለመቻሉ ኦዲተር ቡድን መሪ


መወሰን reliance on key controls for components (Auditor) (Team
leader)

 P19 የኦዲት ፕሮግራሞች ማዘጋጀት(substantive audit


procedures to be performed) ቡድን መሪ ማናጀር/ma
(Team leader) nager/

12
መለያ ዋናና ዝርዝር ተግባራት ማጠናቀቅ መከለስ
Completed by Reviewed
by
 P20 ለእያንዳንዱ ኦዲት ፕሮግራም የኦዲት ናሙና ኦዲተር ቡድን መሪ
መወሰን( determine the sample size for each audit (Auditor) (Team
procedure and sample source leader)

P21 Reviewer work sheet ማናጀር ዳይሬክተር


/manager/ (director)
በጥልቀትኦዲት የሚደረጉ ማስረጃዎች መከታተያ ማዘጋጀት ቡድን መሪ
evidence tracking sheet ኦዲተር (Team
(Auditor) leader)

Quality control questionnaire ማናጀር ዳይሬክተር


/manager/ (director)
3 ዝርዝር ኦዲት ማከናወን audit field work

 E1 ለኦዲት ያለቀረቡ ማስረጃዎች መጠየቂያ(Evidence ኦዲተር ቡድን መሪ


tracking sheet) (Auditor) (Team
leader)

 E2 በጥልቀት ኦዲት የሚደረጉ ሂሳቦች በዓይነት መለየት lead


schedule on component level ቡድን መሪ ማናጀር/ma
(Team leader) nager/
 E3 ዝርዝር ኦዲት ማከናወን(perform substantive audit ቡድን መሪ
procedure) ኦዲተር (Team
(Auditor) leader)

Test of controls ኦዲተር ቡድን መሪ


(Auditor) (Team
leader)

 E4 የተከናወነ ዝርዝር ኦዲት መከለስ(perform substantive ኦዲተር ቡድን መሪ


analytical procedures (Auditor) (Team
leader)

 E9 የኦዲት ማስታወሻ (audit query) ኦዲተር ቡድን መሪ


(Auditor) (Team
leader)

 E11 የኦዲት ማጠቃለያ (audit summary memorandum) ኦዲተር ቡድን መሪ


(Auditor) (Team
leader)

13
መለያ ዋናና ዝርዝር ተግባራት ማጠናቀቅ መከለስ
Completed by Reviewed
by
የሂሳብ መግለጫዎች ማዘጋጀት ቡድን መሪ ማናጀር/ma
(Team leader) nager/
በጀት ማመዛዘን /budget analysis ኦዲተር ቡድን መሪ
(Auditor) (Team
leader)

የቋሚና አላቂ ዕቃዎች የውስጥ ቁጥጥር ግምገማ እና ኦዲተር ቡድን መሪ


ምልከታ ማከናወን (Auditor) (Team
leader)

ተያዥ ማቅረብ የሚገባቸው ሠራተኞች ፋይል ማጣራት ኦዲተር ቡድን መሪ


(Auditor) (Team
leader)

E10 Complete reviewer worksheet ማናጀር ዳይሬክተር


/manager/ (director)
Quality control questionnaire for fieldwork ማናጀር ዳይሬክተር
/manager/ (director)
4 ሪፖርት

የስራ አመራር ማረጋገጫ ደብዳቤ መቀበል(management ቡድን መሪ ማናጀር/ma


representation letter (Team leader) nager/
 R1 የስራ አመራር ሪፖረት(final management letter) ቡድን መሪ ማናጀር/ma
(Team leader) nager/
 R2 yåÄþT GŸèC(audit difference) ማናጀር ዳይሬክተር
/manager/ (director)
Code of Ethics compliance ማናጀር ዳይሬክተር
/manager/ (director)
 R3 በሚቀጥለው ኦዲት ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች (matters
for attention during next year's audit) ቡድን መሪ ማናጀር/ma
(Team leader) nager/
R4 Complete reviewer worksheet ማናጀር ዳይሬክተር
/manager/ (director)
 R6 ዝርዝር የጥራት ቁጥጥር መጠይቅ quality control
questionaire for components) ማናጀር ዳይሬክተር
/manager/ (director)
የመውጫ ውይይት Closing meeting Team leader & team
Members and manager/ director
ረቂቅ የኦዲት ሪፖርት(specimen audit report) ማናጀር ዳይሬክተር
/manager/ (director)
7.3.2 ( ለአነስተኛ ስጋት ኦዲት)
14
መለ ዋናና ዝርዝር ተግባራት ማጠናቀቅ መከለስ
ያ Completed by Reviewed by
PE የቅድመ ኦዲት ሥራዎች ማጠናቀቅ PRE-  
ENGAGEMENT ACTIVITIES  
 PE1 የሙያ ስነ-ምግባር መግለጫ ማስሞላት CODE OF ETHICS ኦዲት ማናጀርና ዳይሬክተር
የኦዲት ቡድን (director)
አባላት(each team
member)
 PE2 የኦዲት ቲም ብቃት ማጣሪያ ማስሞላት COMPENTENCY ማናጀር ዳይሬክተር
MATRIX OF AUDIT TEAM /manager/ (director)
 PE3 የኦዲት ቲም ስምምነት ማስሞላት TEAM AGREEMENT ቡድን መሪ ማናጀር/man
(Team leader) ager/
 PE4 የታቀደውና በስራ ላይ የዋለው ሰአት ማስሞላት BUDGETED ቡድን መሪ ማናጀር/man
vs ACTUAL HOURS (Team leader) ager/
 PE5 የኦዲት ስራ ስምምነት ደብዳቤ /Engagement letter ማናጀር ዳይሬክተር
ማዘጋጀትና መፈረም /manager/ (director)
ለኦዲት ተደራጊው መ/ቤት የትብብር ደብዳቤ ማዘጋጀትና መፈረም ማናጀር ዳይሬክተር
/manager/ (director)
የጥራት ቁጥጥር መጠይቅ Quality control ዳይሬክተር
ማናጀር
questionnaire
/manager/ (director)
P የኦዲት ዕቅድ ማዘጋጀት
 P1 የጉልህነት መጠን መወሰን/planning matariality/ ቡድን መሪ ማናጀር/man
(Team leader) ager/
P2 በባለፈው አመት ጉዳዮች ላይ ክትትል ማድረግ FOLLOW UP ቡድን መሪ
PRIOR YEAR’S MATTERS ኦዲተር (Team
(Auditor) leader)

 P3 ቡድን መሪ ማናጀር/man


ግምገማ የሚደረግባቸው ሂሳቦች መለየት/lead schedule/ (Team leader) ager/
 P5 የውስጥ ኦዲት ግምገማ ማድረግ REVIEW OF INTERNAL ኦዲተር ቡድን መሪ
AUDIT (Auditor) (Team
leader)

 P7 የማጭበርበር ማጣሪያ ሊስት መሙላት FRAUD ኦዲተር ቡድን መሪ


CHECKLIST (Auditor) (Team
leader)

 P8 የቁጥጥር አካባቢ ማጣሪያ ሊስት መሙላት CONTROL ኦዲተር ቡድን መሪ


ENVIRONMENT CHECKLIST (MANUAL) (Auditor) (Team
leader)

 P13 የባህሪያዊ ስጋት በፋይናንሽያል መግለጫ ደረጃ መረዳት ቡድን መሪ ማናጀር/man


INHERENT RISK ON A FINANCIAL STATEMENT (Team leader) ager/

15
መለ ዋናና ዝርዝር ተግባራት ማጠናቀቅ መከለስ
ያ Completed by Reviewed by
LEVEL
 P14 አጠቃላይ የኦዲት ስትራቴጂ ማዘጋጀት OVERALL AUDIT ቡድን መሪ ማናጀር/man
STRATEGY (Team leader) ager/
 P16 የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት መግለጫ /system description for ኦዲተር ቡድን መሪ
audit components/ ማዘጋጀት (Auditor) (Team
leader)

 P17 በውስጥ ቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ መተማመን ስለመቻሉ መወሰን ኦዲተር ቡድን መሪ


reliance on key controls for components (Auditor) (Team
leader)

 P19 የኦዲት ፕሮግራሞች ማዘጋጀት(substantive audit ቡድን መሪ


procedures to be performed) ኦዲተር (Team
(Auditor) leader)

 P20 ለእያንዳንዱ ኦዲት ፕሮግራም የኦዲት ናሙና ኦዲተር ቡድን መሪ


መወሰን( determine the sample size for each audit (Auditor) (Team
procedure and sample source leader)

P21 Reviewer work sheet ማናጀር ዳይሬክተር


/manager/ (director)
በጥልቀትኦዲት የሚደረጉ ማስረጃዎች መከታተያ ማዘጋጀት ኦዲተር ቡድን መሪ
evidence tracking sheet (Auditor) (Team
leader)

የጥራት ቁጥጥር መጠይቅ መሙላት Quality control


ማናጀር ዳይሬክተር
questionnaire
/manager/ (director)
3 ዝርዝር ኦዲት ማከናወን audit field work

Test of control ኦዲተር ቡድን መሪ


(Auditor) (Team
leader)

 E3 ዝርዝር ኦዲት ማከናወን(perform substantive audit ኦዲተር ቡድን መሪ


procedure) (Auditor) (Team
leader)

 E4 የተከናወነ ዝርዝር ኦዲት መከለስ(perform substantive ኦዲተር ቡድን መሪ


analytical procedures (Auditor) (Team
leader)

16
መለ ዋናና ዝርዝር ተግባራት ማጠናቀቅ መከለስ
ያ Completed by Reviewed by
 E9 የኦዲት ማስታወሻ (audit query) ኦዲተር ቡድን መሪ
(Auditor) (Team
leader)

 E11 የኦዲት ማጠቃለያ (audit summary memorandum) ኦዲተር ቡድን መሪ


(Auditor) (Team
leader)

የሂሳብ መግለጫዎች ማዘጋጀት ቡድን መሪ ማናጀር/man


(Team leader) ager/
በጀት ማመዛዘን/budget analysis ቡድን መሪ ማናጀር/man
(Team leader) ager/
የቋሚና አላቂ ዕቃዎች የውስጥ ቁጥጥር ግምገማ እና ምልከታ ቡድን መሪ ማናጀር/man
ማከናወን (Team leader) ager/
ተያዥ ማቅረብ የሚገባቸው ሠራተኞች ፋይል ማጣራት ቡድን መሪ ማናጀር/man
(Team leader) ager/
E10 Complete reviewer worksheet ማናጀር ዳይሬክተር
/manager/ (director)
የጥራት ቁጥጥር መጠይቅ መሙላት Quality control ማናጀር ዳይሬክተር
questionnaire for fieldwork /manager/ (director)
4 ሪፖርት

የስራ አመራር ማረጋገጫ ደብዳቤ መቀበል(management ቡድን መሪ ማናጀር/man


representation letter (Team leader) ager/
 R1 የስራ አመራር ሪፖረት(final management letter) ቡድን መሪ ማናጀር/man
(Team leader) ager/
Code of Ethics compliance
ማናጀር ዳይሬክተር
/manager/ (director)
 R2 yåÄþT GŸèC(audit difference)
ማናጀር ዳይሬክተር
/manager/ (director)
 R3 በሚቀጥለው ኦዲት ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች (matters
for attention during next year's audit) ቡድን መሪ ማናጀር/man
(Team leader) ager/
R4 Complete reviewer worksheet ማናጀር ዳይሬክተር
/manager/ (director)
 R6 ዝርዝር የጥራት ቁጥጥር መጠይቅ quality control ማናጀር ዳይሬክተር
questionaire for components) /manager/ (director)
የመውጫ ውይይት Team leader
Members and Manager /Director

17
መለ ዋናና ዝርዝር ተግባራት ማጠናቀቅ መከለስ
ያ Completed by Reviewed by
ረቂቅ የኦዲት ሪፖርት(specimen audit report) ማናጀር ዳይሬክተር
/manager/ (director)

7.3.3 ለክዋኔ ኦዲት ዋና ዋና ተግባራት የተቀመጠላቸው የጥራት ስታንዳርድ


ተ.ቁ ማጠናቀቅ መከለስ/መገምገም
ዋና ዋና ተግባራት Completed by Reviewed by
1 የቅድመ ኦዲት ሥራዎች የቡድን መሪ እና ማናጀር እና
ኦዲተሮች ዳይሬክተር
2 የዳሰሳና አዋጭነት ጥናት የቡድን መሪ እና ማናጀርና
ኦዲተሮች ዳይሬክተር
3 ዝርዝር ኦዲት
3.1 ዝርዝር የኦዲት እቅድ የቡድን መሪ እና ማናጀርና
ኦዲተሮች ዳይሬክተር
3.2 ዝርዝር ኦዲት የቡድን መሪና ማናጀርና
ኦዲተሮች ዳይሬክተር
4 የኦዲት ሪፖርት ማናጀርና
የቡድን መሪ ዳይሬክተር

8 የተገልጋዮች መብት
8.1 ተገልጋይ በሃይማኖት፤ በፖለቲካ፤በፆታ፤ በብሔር፤ በቋንቋና በመሳሰሉት ጉዳዮች ልዩነት ሳይደረግ
አገልግሎት ማግኘት
8.2 ቅሬታ የማቅረብና ምላሽ የማግኘት

9 ከኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች የሚጠበቁ ቅድመ ሁኔታዎች


9.1 ሂሣብ በህግ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ዘግቶ ለኦዲት ማቅረብ፤
9.2 ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ለኦዲት ሥራ የሚፈልጋቸው ማስረጃዎች፤
9.2.1 ፊዚካል (Physical) ማስረጃ በአካል ተገኝቶ ሁኔታዎችን በመረዳት ወይም በመመልከት
እንዲሁም የፎቶግራፍ እና የቪዲዮ ካሜራ በመጠቀም የሚሰበሰብ ማስረጃ፣
9.2.2 የሰነድ (Documentary) ማስረጃ ደብዳቤዎች ቃለ-ጉባኤዎች መዝገቦች የኤሌክትሮኒክስ
መረጃዎችንና ከመሣሰሉት የሚሰበሰብ ማስረጃን ያካትታል፡፡
9.2.3 ቴስቲሞናያል (Testimonial) ማስረጃ ፊት ለፊት በመገኘት ወይንም በስልክ በሚደረግ ቃለ
መጠይቅ የሚሰበሰብ ማስረጃ እና በጽሁፍ ተዘጋጅቶ በኦዲት ተደራጊ መ/ቤት ኃላፊዎች
እንዲሞሉ ከሚላኩ መጠየቆች (questionnaires) መልስ የተሰበሰበ ማስረጃን ያካትታል፡፡

18
9.2.4 አናሊቲካል (Analytical) ማስረጃ በኦዲት ተደራጊው መ/ቤት ወይንም በዋና ኦዲተር
መ/ቤት ኦዲተሮች የተዘጋጁ መረጃዎችን በመተንተን የሚገኙ ማስረጃዎች ናቸው፡፡ ኦዲት
ተደራጊ መ/ቤቶች አራቱንም ዓይነት ማስረጃዎች በተፈለገው ጊዜ በተጠየቀ በ 3 ቀን ውስጥ
መስጠት፡፡ በተለይም ከመ/ቤቶቹ የሥራ አመራር አባላት ብቻ ሊገኝ የሚችል ማስረጃ
በሚፈለግበት ጊዜ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ኃላፊዎች በተገቢው ጊዜ የመስጠት ኃላፊነት
አለባቸው፡፡
9.3 ለኦዲተሮች ሥራ ተስማሚ የሆነ ቢሮ የሥራ ጊዜ ሳይባክን አዘጋጅቶ መስጠት፤
9.4 የኦዲት መግቢያና መውጫ ስብሰባዎች በኢንጌጅመንት ደብዳቤ (engagement letter) ውስጥ በተመለከቱት
ቀነ ገደቦች ለማካሄድ እንዲቻል ሁኔታዎች ማመቻቸት እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ኃላፊዎች በተጠቀሱት
ስብሰባዎች መገኘት፤
9.5 ለኦዲት ሥራ የሚያስፈልጉትን መረጃዎች የሚያውቅና ለኦዲት ሥራ የሚያስፈልጉትን ስብሰባዎችን
የሚያመቻች እንዲሁም ልዩ ልዩ ከኦዲቱ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ለማስፈፀም የሚችል ኃላፊ ( focal person)
መመደብ፡፡
9.6 በረቂቅ የፋይናንሻል (የሕጋዊነት) እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርቶች ላይ ያላቸውን አስተያየት በመውጫ ስብሰባ
ወቅት መግለጽ ይኖርባቸዋል፤
9.7 በፋይናንሻል ኦዲት ረቂቅ የማኔጅመንት ደብዳቤ መሰረት በግኝቶቹና በተሰጡ የማሻሻያ ሀሳቦች ላይ እርምጃ
መወሰዱን ወይም የሚወሰድ ስለመሆኑ ለሥራ አመራር ደብዳቤ (management letter) የጽሁፍ ምላሽ ከ 1
እስከ 3 ቀናት ጊዜ ውስጥ መስጠት፤
9.8 ኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች በተሰጣቸው ረቂቅ የሥራ አመራር ደብዳቤና በመውጫ ስብሰባ ወቅት መግባባት
በተደረሰባቸው ግኝቶች ላይ ዋናውን ሪፖርት እስከሚደርስ ሳይጠብቁ የማስተካከያ እርምጃ መወሰድ
ይጠበቅባቸዋል፡፡

10 አገልግሎቱ በቀጥታ የሚመለከታቸው አካላት


የዋናው ኦዲተር መ/ቤት አገልግሎት ተጠቃሚዎች በማቋቋሚያ አዋጁ የተገለጹ ከላይ በተራ ቁጥር 4.1 ሥር
የተዘረዘሩት ናቸው፡፡

11 አስተያየት የሚሰጥባቸውና ተሳትፎ የሚደረግባቸው ሁኔታዎች


 እያንዳንዱ ኦዲት እንደተጠናቀቀ በሚደረጉ የመውጫ ስብሰባዎች
 በዋና ኦዲተር መ/ቤት በሚገኙ አስተያየት መስጫ ሳጥኖች
 በአካል መ/ቤቱ በመገኘት
 በደብዳቤ፤በኢሜይል

19
11.2 የመ/ቤቱና ኃላፊዎች አድራሻ
11.2.1 የመ/ቤቱ ስም የደቡብ ብሄሮች፤ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ሲሆን
አድራሻው፤ ሀዋሳ ከተማ ፤ ሐይቅዳር ክፍለ ከተማ፤ ጉዱማሌ ቀበሌ ፖስታ ሳጥን ቁጥር 66 E-mail
auditorgeneralsouth@yahoo.com
11.2.2 የመ/ቤቱ ኃላፊዎች አድራሻ፤
ተቁ የሥራ አድራሻ
ስልክ ፋክስ ኢሜይል
የኃላፊ ስም ኃላፊነት
1 አቶ ሣህሌ ገብሬ ዋና ኦዲተር 0462201525 0462206138 Gebre_40@yahoo.com
2 አቶ ሲንቦ ሽብሩ ም/ዋና 0462201860 0462204600 ssinbo@yahoo.com
ኦዲተር

12 የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ስነ ሥርዓት


 ቅሬታ የተሰማው ተገልጋይ ቅሬታውን በቀጥታ አገልግሎት ለሰጠው ፈጻሚ በቃል፤ በጽሁፍ ወይም
በስልክ ያቀርባል፡፡
 ቅሬታው የቀረበለት ፈጻሚም የቀረበለትን ቅሬታ አጣርቶ እስከ ግማሽ ቀን ባለ ጊዜ ለቅሬታ
አቅራቢው ምላሽ በጽሁፍ ይሰጣል፡፡
 በተሰጠው ምላሽ ያልረካ ተገልጋይ ለሥራ ሂደት ባለቤት ቅሬታውን ያቀርባል፡፡
 ቅሬታ የቀረበለት የሥራ ሂደት ባለቤትም ቅሬታውን አጣርቶ እስከ 3 ቀናት ባለ ጊዜ ውስጥ በጽሁፍ
ምላሽ ይሰጣል፤
 በተሰጠው ምላሽ ያልረካ ተገልጋይ ጉዳዩ ለተቋሙ የበላይ ኃላፊ ያቀርባል፤ የበላይ ኃላፊውም
ቅሬታው እንዲጣራ በማድረግ ለቅሬታ አቅራቢው በ 2 ቀን በጽሁፍ መልስ ይሰጣል፤
 ጉዳዩ ተጣርቶ የተሰጠው ውሳኔ ወይም የተወሰደው እርምጃ በተቋሙ ማስታወቂያ ሰሌዳ፤ ድረገጽ
ላይ እንዲወጣ ይደረጋል፤
 ተገልጋዩ ከዚህ በላይ በተመለከተው አግባብ በተሰጠው ውሳኔ ካልረካ ቅሬታውን ለክልል ምክር ቤት፤
ለሚመለከተው ፍርድ ቤት፤እንባ ጠባቂ ተቋም፤ለሰባዊ መብት ኮሚሽን፤ ለሚዲያ ማቅረብ ይችላል፡፡

13 ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ ችግሮችን አስመልክቶ ካሣና የተለያዩ


ማካካሻዎችን ለማድረግ የሚወሰዱ ኃላፊነቶች
የዋናው ኦዲተር መ/ቤት ለአገልግሎት ተቀባዮች የገባቸውን ቃሎች ባለመጠበቁ አገልግሎት ተቀባዩ
የደረሰበትን ኪሳራ እንዲተካለት ወይም እንዲካካስለት የመጠየቅና የማግኘት መብት ይኖረዋል፡፡ በሌላ በኩል
 ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ለምርመራ እንዲቀርብለት የሚጠይቃቸውን ተገቢነት ያላቸውን ሰነዶች፤
የቃል ማስረጃዎችና ወይም ሌሎች መረጃዎችን ያላቀረበ፤

20
 ሀሰተኛ መሆኑን እያወቀ ወይም እውነተኛ መሆኑን ለማመን ምክንያት ሳይኖረው ማንኛውንም
መረጃ ለዋናው ኦዲተር መ/ቤት ወይም ኦዲተሮች ወይም ለወኪሎች የሰጠ፤
 የዋናው ኦዲተር መ/ቤት ሥራውን በሚገባ እንዳያከናውን ያሰናከለ፤
 በቂ ህጋዊ ምክንያት ሳይኖረው ከዋናው ኦዲተር መ/ቤት በቀረቡ ኦዲት ሪፖርቶች ላይ በተሰጡ
የማሻሻያ አስተያየቶችና ሀሳቦች መሰረት ወቅታዊና አጥጋቢ እርምጃ ያልወሰደ፤
 ማንኛውም አገልግሎት ተቀባይ የዋናው ኦዲተር መ/ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ እና የዚህ ቻርተር
ድንጋጌዎችን እንዲፈጽም በተጠየቀ ጊዜ ፈቃደኛ ሆኖ ያልተገኘ እንደሆነ ከአምስት እስከ ሰባት ዓመት
ሊደርስ በሚችል እስራት ወይም እስከ ብር 10000.00 /አስር ሺህ ብር/የገንዘብ መቀጫ ወይም
በሁለቱም ይቀጣል፡፡

14 የክትትልና ግምገማ ሥርዓት


14.1 ፈጻሚዎች፤ አስተባባሪዎች፤ የሥራ ሂደት ባለቤቶች በቻርተሩ መሰረት ስለመፈጸማቸው
በለውጥ ሠራዊት የአሰራር ሥርዓት መሰረት በየሳምንቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ሁኔታ እየተገመገመ
ለተቋሙ የበላይ አመራር ሪፖርት እንዲቀርብ ይደረጋል፡፡
14.2 የተቋሙ የበላይ አመራርም በየወቅቱ በቀረቡት የክትትልና የግምገማ ሪፖርቶች ላይ በመመስረት
የእርምትና የማስተካከያ እርምጃ ይወስዳል፡፡
14.3 የዋናው ኦዲተር መ/ቤትና ኦዲት ተደራጊ መ/ቤቶች በቻርተሩ በተቀመጠው መሰረት ግዴታቸውን
ያሟሉ ስለመሆኑ እንደአስፈላጊነቱ ኦዲቱ እየተካሄደ እና እያንዳንዱ ኦዲት እንደተጠናቀቀ
በመውጫ ስብሰባ ወቅት ይገመገማል፤ ውጤቱ በሪፖርት ለመ/ቤቱ ይቀርባል፤
14.4 ተገልጋዮች በየጊዜው የሚሰጡት አስተያየት እየተሰበሰበና እየተተነተነ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ
ማሻሻያ የሚደረግበት አሰራር ይዘረጋል፤
14.5 በዓመት አንድ ጊዜ የተገልጋዮችና ባለድርሻ አካላት ዕርካታ የዳሰሳ ጥናት ይደረጋል፤
14.6 በዓመት አንድ ጊዜ የዋናው ኦዲተር መ/ቤት የሚመለከታቸው ፈጻሚዎች፤ አስተባባሪዎች፤ የሥራ
ሂደት ባለቤቶች፤ የኦዲት ተደራጊ መ/ቤት ኃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የቻርተሩ
አፈጻጸም ግምገማ ይደረጋል፤
14.7 በየጊዜው ከሚደረግ ክትትልና ግምገማ በመነሳት በቻርተሩ ላይ አስፈላጊ የሆኑ ማሻሻያዎች
ይደረጋሉ፡፡

15 የመረጃ ሥርጭትና ግብረ መልስ


በዜጎች ቻርተር ውስጥ የተካተቱ ስታንዳርዶችንና ልዩ ልዩ መረጃዎችን ዜጎች እንዲያውቋቸው
ቡክሌቶችን፤ በራሪ ጽሁፎችን፤ ድረ ገጽን፤ ዜና መጽሄቶችንና ሌሎች የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም

21
የማስተዋወቅ ተግባር ይከናወናል፡፡ የዜጎች ቻርተርን ክትትልና ግምገማ በማድረግ የተገኙ ውጤቶችን፤
የታዩ ችግሮችን፤ የተወሰዱ እርምጃዎችንና የተደረጉ ማሻሻያዎችን በተመለከተ ግብረ መልስ በጽሁፍ
ይሰጣል፡፡

22

You might also like