You are on page 1of 113

የአዲስ አበባ ከተማ ጥቃቅንና አነስተኛ

ኢንተርፕራይዞች የሁኔታ ዳሰሳ ጥናት (ከ1996-2008)

አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ቢሮ

እና

በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ

በጋራ ትብብር የተዘጋጀ ጥናት

ጥቅምት 2009

አዲስ አበባ

1
ማውጫ ገጽ

ምዕራፍ አንድ፡ መግቢያ ............................................................................................................................ 7


1.1 የጥናቱ መነሻ ሁኔታዎች .................................................... 9
1.2 የችግሩ ምንነት ሐተታ ..................................................... 13
1.3 የጥናቱ ዓለማ ........................................................... 14
1.3.1 አጠቃላይ ዓላማ ........................................................ 14
1.3.2 የጥናቱ ዝርዝር ዓላማዎች ................................................. 14
1.4 የጥናቱ መሠረታዊ ጥያቄዎች ................................................ 14
1.5 የጥናቱ ፋይዳዎች ........................................................ 15
1.6 የጥናቱ ወሰን ............................................................ 15
1.7 የጥናቱ ውስንነቶችና የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎች .............................. 16
1.7.1 የጥናቱ ዉስንነቶች ...................................................... 16
1.7.2 ለጥናቱ ዉስንነቶች የተሰጡ መፍትሔዎች ..................................... 16
1.8 ማጠቃለያ .............................................................. 16
ምዕራፍ ሁለት፡ ተዛማጅ ጽሑፎች ዳሰሳ .................................................................................................... 18
2.1 መግቢያ ............................................................... 18
2.2 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ ................................... 18
2.2.1 የ1990 ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ ............................. 19
2.2.2 የማእከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ ትርጓሜ ....................................... 19
2.2.3 የተሻሻለው የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ ......................... 19
2.3 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ታሪካዊ አመጣጥ፤ ዕድገትና ፋይዳዎች ............. 20
2.4 የሌሎች አገሮች መልካም ተሞክሮ ............................................ 22
2.4.1 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ሚና .................................... 22
2.4.2 የማሌዥያ መልካም ተሞክሮ ............................................... 23
2.4.3 የጃፓን መልካም ተሞክሮ ................................................. 24
2.4.4 የታንዛንያ ተሞክሮ ...................................................... 25
2.4.5 ከሌሎችመልካምተሞክሮልምድየተገኘትምህርት .................................. 26
2.5 ጥቃቅንናአነስተኛኢንተርፕራይዞችልማትበኢትዮጵያ ................................ 26
2.5.1 የፖሊሲናስትራቴጂአቅጣጫ ................................................ 27
2.5.2 የጥቃቅንናአነስተኛኢንተርፕራይዞችየፖሊሲ ማዕቀፎች ............................. 27
2.5.3 የፖሊሲና ስትራቴጂ አፈጻጸም .............................................. 28
2.6 ማጠቃለያ .............................................................. 28
ምዕራፍ ሦስት፡ የጥናቱ ዘዴ ..................................................................................................................... 30
2
3.1 መግቢያ ............................................................... 30
3.2 የጥናቱ አቀራረብ ......................................................... 30
3.3 የጥናቱ ተሳታፊዎች ....................................................... 30
3.4 የጥናቱ መረጃ ምንጭና አሰባሰብ ዘዴ .......................................... 31
3.5 የመረጃ አደረጃጀትና ትንተና ................................................ 31
3.6 ማጠቃለያ .............................................................. 32
ምዕራፍ አራት፡ የመረጃ ትንተናና ግኝቶች ................................................................................................ 33
4.1 መግቢያ ............................................................... 33
4.2 የጥናቱ ተሳታፊዎች ሁኔታ .................................................. 33
4.2.1 ጾታ................................................................. 33
4.2.2 ዕድሜ ............................................................... 34
4.2.3 የትምህርት ደረጃ ....................................................... 35
4.3 የጥቃቅንናአነስተኛኢንተርፕራይዞችሁኔታ ....................................... 36
4.3.1 የኢንተርፕራይዞቹአመሰራረትእናአዝማሚያ (ትሬንድ) ............................. 36
4.3.2 የኢንተርፕራይዞቹ አይነት ................................................ 37
4.3.3 የኢንተርፕራይዞች ህጋዊ አደረጃጀት ......................................... 37
4.3.4 ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ..................................... 38
4.3.4.1 ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ................................................... 40
4.3.4.2 የኮንስትራክሽን ዘርፍ .................................................. 41
4.3.4.3 የአገልግሎትዘርፍ ..................................................... 41
4.3.4.4 የከተማ ግብርና ዘርፍ .................................................. 42
4.3.4.5 የንግድ ዘርፍ ........................................................ 42
4.4 የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ዕድገትና ስርጭት ................................... 42
4.5 የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የድጋፍ ማዕቀፍ አፈጻጸም ............................. 46
4.5.1 የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የብድር/ፋይናንስ ድጋፍ አገልግሎት .................... 47
4.5.2 የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የገበያ ትስስር ድጋፍ ............................... 54
4.5.3 የሰዉ ኃይል ልማትና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ ................... 56
4.5.4 የቴክኖሎጂ ዕድገት ድጋፍ አገልግሎት ........................................ 59
4.5.5 የገበያ ልማትና ግብይት ድጋፍ አገልግሎት .................................... 60
4.5.6 የፋይናንስና ብድር አገልግሎት ዉጤታማ ለማድረግ የተሰጡ ሌሎች ድጋፎች ............ 61
4.5.7 የሚሰጡ የድጋፍ ዓይነቶች ችግር ፈቺነት እና ወቅታዊነት .......................... 62
4.5.8 የመስሪያ ቦታ ድጋፍ አገልግሎት ............................................ 63
4.5.9 ኢንተርፕራይዞች የሚደረግላቸዉ ድጋፍ ግልጽነት፤ ፍትሃዊነት እና ተደራሽነት .......... 70
3
4.5.10 የሚሰጠዉ ድጋፍ እንደዘርፉ ባህርይ እና በደረሰበት ዕድገት ደረጃ መሰረት ስለመሆኑ ...... 71
4.6 የኢንተርፕራይዞቹ የልማት አስተዋዕጾ .......................................... 74
4.6.1 በኢንተርፕራይዞቹ የታቀፉ አባላት .......................................... 74
4.6.2 የተፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ................................................... 77
4.7 በተላያዩ ምክንያቶች የከሰሙ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች .................... 80
4.7.1 የከሰሙ ኢንተርፕራይዞች ስራ ያቆሙበት ዘመን ................................ 80
4.7.2 ኢንተርፕራይዞቹ አሁን ያሉበት ሁኔታ ....................................... 81
4.7.3 ኢንተርፕራይዞች ለሦስተኛ ወገን የተላለፉበት ምክንያት ........................... 82
4.7.4 የኢንተርፕራይዞችአይነት ................................................. 82
4.7.5 የኢንተርፕራይዞች ህጋዊ አደረጃጀት ......................................... 83
4.7.6 ኢንተርፕራይዞች ተሰማርተዉበት የነበረ ዋና የስራ ዘርፍ .......................... 83
4.7.7 ኢንተርፕራይዞች ተሰማርተዉበት የነበረ ንዑስ የስራ ዘርፍ ......................... 84
4.7.8 ኢንተርፕራይዞች ሲቋቋሙ እና ስራ ሲያቆሙ የነበራቸዉ የዕድገት ደረጃ ............... 86
4.7.9 ለኢንተርፕራይዞች የተሰጠ የድጋፍ አይነት .................................... 87
4.7.10 ኢንተርፕራይዞች የከሰሙበት ምክንያት ....................................... 87
4.7.11 ኢንተርፕራይዞች ሲደራጁና ስራ ሲያቆሙ የነበራቸዉ የአባላት ብዛት.................. 88
4.8 የኢንተፕራይዞች የዕድገት ማናቆዎች .......................................... 88
4.9 ማጠቃለያ................................................................ 90
ምዕራፍ አምስት፡ የጥናቱ ድምዳሜ እና የወደ ፊት የትኩረት አቅጣጫዎች ................................................. 91
5.1 መግቢያ ............................................................... 91
5.2 የጥናቱ ድምዳሜ ......................................................... 92
5.3 ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ................................................ 95
ዋቤ ማጣቀሻዎች ..................................................................................................................................... 97
አባሪሁለት፡ለአዲስ አበባ ከተማ የጥቃቅንና አነስተኛ ለከሰሙኢንተርፕራይዞችየተዘጋጀቃለ-መጠይቅ .. 108
አባሪሦስት፡ አግባብነትላላቸዉየሥራሀላፊዎችናባለሙያዎችየተዘጋጀየቃለ-መጠይቅጋይድ .......... 112

የሠንጠረዦች ዝርዝር

ሠንጠረዥ 1፡ የ1990 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ በኢትዮጵያ ............... 19


ሠንጠረዥ2፡ የተሻሻለው የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ በኢትዮጵያ ............. 20
ሠንጠረዥ3፡ የስራአስኪያጅ/ሰብሳቢ/ባለቤቶች ጾታ ...................................... 33
ሠንጠረዥ4፡ የስራአስኪያጅ/ሰብሳቢ/ ባለቤቶች የትምህርት ደረጃ ............................ 35
ሠንጠረዥ5፡ የኢንተርፕራይዞች አይነት በክፍለ ከተማ ................................... 37

4
ሠንጠረዥ6፡ የኢንተርፕራይዞች ህጋዊ አደረጃጀት ...................................... 37
ሠንጠረዥ7፡ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ ዋና የስራ ዘርፎች ........................... 38
ሠንጠረዥ8፡ የኢንተርፕራይዞች ስርጭት በክፍለ ከተማና በየተሰማሩበት የስራ ዘርፎች ............ 39
ሠንጠረዥ9፡ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ....................... 40
ሠንጠረዥ10፡ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ የኮንስትራክሽን ዘርፎች.................... 41
ሠንጠረዥ11፡ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ የአገልግሎት ዘርፎች ........................ 41
ሠንጠረዥ 12፡ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ የከተማ ግብርና ዘርፎች ..................... 42
ሠንጠረዥ 13፡ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ የንግድ ዘርፎች ........................... 42
ሠንጠረዥ 14፡ የኢንተርፕራይዞች እድገት በየክፍለ ከተማ ................................ 45
ሠንጠረዥ15፡ ኢንተርፕራይዞች ብድር ላለማግኘታቸዉ የሰጡአቸዉ የተለያዩ ምክንያቶች ......... 48
ሠንጠረዥ16፡ ኢንተርፕራይዞች የብድር አገልግሎት ድግግሞሽ/ብዛት ........................ 49
ሠንጠረዥ17፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለመጨራሻ ጊዜ ያገኙት የብድር መጠን ...... 50
ሠንጠረዥ18፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለመጨራሻ ጊዜ ብድር ያገኙበት ዓ/ም ........ 51
ሠንጠረዥ 19፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ተመላሽ ያደረጉት የብር መጠን............ 52
ሠንጠረዥ20፡ ኢንተርፕራይዞች ብድር ወይም የፋይናንስ ድጋፍ ያገኙበት ተቋም ............... 53
ሠንጠረዥ21፡ የተሰጠዉ የብድር ድጋፍ አገልግሎት በሚፈለገዉ መጠንና እና ወቅት ስለመሆኑ ..... 54
ሠንጠረዥ22፡ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተሰጡ የገበያ ትስስር ድጋፍ አገልግሎቶቸ .... 56
ሠንጠረዥ23፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ባገኙት የገበያ ትስስር የተገኘ የብር መጠን .... 56
ሠንጠረዥ 24ሀ፡ የሰዉ ኃይል ልማትና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን የሥልጠና ድጋፍ አገልግሎት ..... 57
ሠንጠረዥ 24ለ፡ የሰዉ ኃይል ልማትና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ከሥልጠና ውጭ የተሰጡ ድጋፍ
አገልግሎቶች ................................................................. 58
ሠንጠረዥ 25፡ ለኢንተርፕራይዞች የተሰጠ የመሣሪያ ሊዝ ድጋፍ ........................... 59
ሠንጠረዥ26፡ የቴክኖሎጂ ዕድገት ድጋፍ አገልግሎት .................................... 60
ሠንጠረዥ27፡ የገበያ ልማትና የግብይት ድጋፍ አገልግሎት ............................... 61
ሠንጠረዥ28፡ የፋይናንስና ብድር ድጋፍ ዉጤታማ ለማድረግ የተሰጠ ድጋፍ አገልግሎት .......... 62
ሠንጠረዥ29፡ የመስሪያ ቦታ ድጋፍ አገልግሎት........................................ 64
ሠንጠረዥ30፡ የመስሪያ ቦታ ስፋት (በካሬ ሜትር) ...................................... 65
ሠንጠረዥ31፡ ኢንተርፕራይዞች ያገኙት የመስሪያ ቦታ ዓይነት ............................. 66
ሠንጠረዥ32ሀ፡ ከመሰረተ ልማት አቅርቦት ጋር የተያያዙ የመስሪያ ቦታ ችግሮች ................ 68
ሠንጠረዥ32ለ፡ ሌሎች የመስሪያ ቦታ ችግሮች......................................... 69
ሠንጠረዥ 33፡ በሚሰጡ ድጋፋዊ አገልግሎቶች ላይ ኢንተርፕራይዞቹ ያላቸዉ አስተያየት ......... 71
ሠንጠረዥ 37 የከሰሙ ኢንተርፕራይዞች ሁኔታ ........................................ 81
ሠንጠረዥ 38፡ የከሰሙ ኢንተርፕራይዞች ሁኔታ በክፍለ ከተማ ............................ 81

5
ሠንጠረዥ 39፡ ኢንተርፕራይዞች ለሶስተኛ ወገን የተላለፉበት ሁኔታ በክ/ከተማ ................. 82
ሠንጠረዥ 40፡ የከሰሙ/ለሶስተኛ ወገን የተላለፉ ኢንተርፕራይዞች አይነት በክ/ከተማ ............. 82
ሠንጠረዥ 41፡ የከሰሙ/ለሶስተኛ ወገን የተላለፉ ኢንተርፕራይዞች ህጋዊ አደረጃጀት.............. 83
ሠንጠረዥ 42፡ ኢንተርፕራይዞቹ ተሰማርተዉበት የነበረ ዋና የስራ ዘርፍ በክ/ከተማ .............. 83
ሠንጠረዥ 43፡ የከሰሙ/የተላለፉ ኢንተርፕራይዞች በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ..................... 84
ሠንጠረዥ 44፡ የከሰሙ/የተላለፉ በኮንስትራክሽን ዘርፍ................................... 84
ሠንጠረዥ 45፡ የከሰሙ/የተላለፉ በአገልግሎት ዘርፍ .................................... 85
ሠንጠረዥ 46፡ የከሰሙ/የተላለፉ በከተማ ግብርና ዘርፍ .................................. 85
ሠንጠረዥ 47፡ የከሰሙ/የተላለፉ በንግድ ዘርፍ ........................................ 86
ሠንጠረዥ 48፡ ኢንተርፕራይዞቹ ሲቋቋሙ እና ስራ ሲያቆሙ የነበራቸዉ የዕድገት ደረጃ .......... 86
ሠንጠረዥ 49 ለኢንተርፕራይዙ የተሰጡ የድጋፍ አይነቶች ............................... 87
ሠንጠረዥ 50፡ ኢንተርፕራይዙ የከሰመባቸው/ለሦስተኛ ወገን የተላለፈባቸው ምክንያቶች .......... 87
ሠንጠረዥ 51፡ ኢንተርፕራይዞች ሲደራጁና ስራ ሲያቆሙ የነበራቸዉ የአባላት ብዛት............. 88
ሠንጠረዥ 52፡ ኢንተርፕራይዞቹ ሥራቸዉን በሚያከናዉኑበት ወቅት ያጋጠሙ ዋና ዋና ችግሮች .... 89

የግራፎች ዝርዝር

ግራፍ 1፡የጥናቱ ተሳታፊዎች ዕድሜ ................................................ 34


ግራፍ 2፡ የጥቃቅንናአነስተኛየተመሰረቱበትጊዜ ........................................ 36
ግራፍ 3፡ የኢንተርፕራይዞች ዕድገት በተሰማሩበት ዋና ዋና ዘርፎች ......................... 44
ግራፍ 4፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የብድር/ፋይናንስ ድጋፍ አገልግሎት ............. 47
ግራፍ5፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለመጨራሻ ጊዜ ብድር ያገኙበት ዓ/ም ............ 51
ግራፍ6፡ የሚሰጡ የድጋፍ ዓይነቶች ችግር ፈቺነት እና ወቅታዊነት .......................... 63
ግራፍ 7፡ ለኢንተርፕራይዞች የመስሪያ ቦታ የተሰጠበት ዓ/ም .............................. 66
ግራፍ8፡ ኢንተርፕራይዞች ያገኙት የመስሪያ ቦታ አገልግሎት .............................. 67
ግራፍ 9 ኢንተርፕራይዞች አሁን እየሰሩ ያሉበት ሁኔታ .................................. 70
ግራፍ10፡ የሚሰጡ ድጋፎች እንደዘርፉ ባህርይ እና ከደረሰበት የዕድገት ደረጃ አንፃር ስለመሆኑ...... 72
ግራፍ 11፡ በኢንተርፕራይዞች መነሻ አደረጃጀት የተመዘገቡ አባላት ብዛት በትምህርት ደረጃ ....... 75
ግራፍ 12፡ አሁን በሥራ ላይ ባሉ ኢንተርፕራይዞች የተመዘገቡ የአባላት ብዛት ................. 76
ሠንጠረዥ 35፡ ኢንተርፕራይዞች የአባላት ብዛት በትምህርት ደረጃ .......................... 77
ግራፍ 13፡ ኢንተርፕራይዞች የአባላት ብዛት በዕድሜ .................................... 77
ግራፍ 14፡ የከሰሙ ኢንተርፕራይዞች የተዘጉበት ወይም ለሶስተኛ ወገን የተለለፉበት ዘመን......... 80

6
ምዕራፍ አንድ፡ መግቢያ
የዚህ ሰነድ ዋና ይዘት በአዲስ አበባ ከተማ ከ1996 ዓ.ም ጀምረው በጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ልማት የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ስርጭት፤ እድገት እና ያሉበት ሁኔታ ዳሰሳና
ግኝት የሚያመላከት ሲሆን በመጀመሪያ ሰነዱ በቅድሚያ መግቢያና መነሻ ሃሳብ ይዟል፡፡
በመቀጠልም የጥናቱ ዓላማና፣ የጥናቱን ወሰን፣ የጥናቱን አካሄድ፤ ከጥናቱ የሚጠበቀው ውጤት፤
ተዛማጅ ጽሑፎች ዳሰሳ፤ የጥናቱን ግኝትና ማጠቃለያ ሀሳብ እንዲሁም ጥናቱ ያመላከተውን
የትኩረት አቅጣጫ ያካተተነው፡፡

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት እና ሥራ ዕድል ፈጠራ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን


ዕቅዱ ቅድሚያ የተሰጠው ዘርፍ ነው፡፡ በዚህ ዘርፍ በመጀመሪያው ከተያዙት ሥራዎች መካከልም
አንዱ የሥራ ዕድል ፈጠራና የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማትን የማስፋፋት ሥራ ነው፡፡በአዲስ አበባ
ከተማ ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ዕቅድ ተይዞ ወደ ሥራ የተገባ ሲሆን
ይህንን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችሉ በርካታ የአደረጃጀት፤ የስልጠና፤ የማምረቻና መሻጫ ቦታዎች
አቅርቦት፤ የፋይናንስና ቴክኖሎጂ ግብኣቶች አቅርቦት እንዲሁም የገበያ ትስስር የመፍጠር ሥራዎች
ትኩረት ተሰጥቷቸው ተከናውነዋል፡፡ በዚሁ መሰረት 29016ኢንተርፕራይዞች የተቋቋሙ ሲሆን
139650 ሥራ ፈላጊዎች የሥራ ዕድል መፍጥር የተቻለ ቢሆንም በሂደት ባጋጠሙ ምክንያቶች
የኢንተርፕራይዞቹም ሆነ የአባላት ቁጥር በእጅጉ የቀነሰበት ሁኔታ እንዳለ በዚህ ጥናት ታይቷል፡፡
በዚህ አፈፃፀም ዙሪያ በርካታ ችግሮች መከሰታቸው አልቀረም፡፡ በዚህም መሰረት የዚህ ጥናት ዋና
አላማ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የተደራጁት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
ከተደረገዉ ዝርዝር ቆጠራ ዉጤት መረጃ በመነሳት ጥናት ማካሄድና ያሉበትን አጠቃላይ ሁኔታ
በመዳሰስ ማነቆዎችን ለይቶ የዘርፉን የልማት አቅጣጫ በትክክለኛና በተጨባጭ መረጃ ላይ
ተሞርኩዞ መምራት የሚያስችል የመፍትሔ ሃሳብ ለመጠቆም ነው፡፡

መረጃዉ የተሰበሰበዉ በአዲስ አበባ ከሚገኙ ሁሉም ኢንተርፕራይዞች ነዉ፡፡ ቀደም ሲል መረጃ
ለመሰብሰብ የታቀደዉ 27187 ቢሆንም በመስክ መረጃ የተሰበሰበዉ ከ29016 ኢንተርፕራይዞች
ነዉ፡፡ የጥናቱ መረጃ በዋናነት ከመጀመሪያ ምንጮች የተሰበሰበ ሲሆን እንደአስፈላጊነቱ ሁለተኛ
ምንጮችም ጥቅም ላይ ዉለዋል፡፡ የመጀመሪያ ምንጭ መረጃ የተሰበሰበዉ መጠይቅ በማዘጋጃትና
ቁልፍ ለሆኑ መረጃ ሰጪዎች ቃለ-መጠይቅ ተዘጋጅቶ ጥያቄ በማቅረብ ነዉ፡፡ የመጀመሪያ መረጃ
ምንጭ በዋናነት የኢንተርፕራይዞቹ ኃላፊዎች ወይም ሥራ አስኪያጆች ሲሆኑ እነርሱ ባልተገኙበት
ሁኔታ ከኢንተርፕራይዞቹ አባላት ጋር በመነጋገር የተሰበሰበ ነዉ፡፡ በአካል በመገኘት የተደረጉ
እይታዎችና ምልከታዎችም መረጃዉን ለመሰበሰብ በጥቅም ላይ ዉለዋል፡፡ የከሰሙ
ኢንተርፕራይዞችን በሚመለከትም ስለእነርሱ በትክክል የሚያዉቁ የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ጽ/ቤት ሀላፊዎችና ባለሙያዎችን ጭምር በማነጋገር መረጃ ተሰብስቧል፡፡በዚህ
7
መልክ መረጃ ማግኘት ባልተቻለበት ሁኔታ ከሁለተኛ ምንጭ የተገኘዉን መረጃ እንደ ማካካሻ
በመጠቀም ሥራ ላይ እንዲዉል ተደርጓል፡፡

የጥናቱ ዉጤት እነደሚያመለክተዉ ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንጻር በዘርፉ በርካታ የሥራ ዕድሎች የተፈጠሩ
ቢሆንም በከተማዉ ከሚኖሩ ስራ ፈላጊ ዜጎች አንጻር ሲታይ ግን የተፈጠረዉ የሥራ እድል በቂ
ኤዶለም፡፡ የተፈጠሩት አብዛኞቹ የስራ ዕድሎችም ቢሆኑ በቋሚ ስራ ላይ በተለይም በአምራች ዘርፉ ላይ
እንዲሆን ከማድረግ አንጻር እጥረት ያለበት እንደሆነ የጥናቱ ዉጤት ያሳያል፡፡ የኢንተርፕራዞች የደረጃ
ሽግግርና እድገት አፈጻጸም ካለው ፍላጎትና ተደራሽነት አንጻር ሲታይ አፈጻፀሙ ዝቅተኛ እንደሆነ
የጥናቱ ዉጥት ያመለክታል፡፡ በአጠቃላይ የጥናቱ ዉጤት እንደሚያመለክተዉ በጥቃቅንና አነስተኛ
ተቋማት ልማት ዘርፍ እየተሰማራ ያለው የሰው ኃይልና የዘርፉን ልማት ለመደገፍ የተሰረው ሥራ የዘርፉ
የልማት ስትራተጂ የሰጠውን ትኩረት የሚመልስ ሆኖ አልተገኘም፡፡

በዘርፉ ለተመዘገበው ዝቅተኛ አፈጻፀም በኢንተርፕራይዞቹ ወይም በአንቀሳቃሾቹ የሚታየው የአመለካከት


ዝንፈት በምክንያትነት የሚገለጽቢሆንም ዘርፉን ለማጠናከር የተሰጠዉ የመንግስት ድጋፍ የተሟላ
ካለመሆኑም ባሻገር በዘርፉ የሚሰማራ የሰዉ ኃይል ከመሰረቱ በመኮትኮት ልማታዊ ዕይታ እንዲኖራው
በማድረግ ቅኝቱን በልማታዊ አስተሳሰብ ለመግራት የተሰረዉ ሥራ በቂ አለመሆኑን የጥናቱ ግኝት
ያመለክታል፡፡

በዚሁ መሰረት በዘርፉ የታዩ የአፈጻጸም ዉስንነቶች ለመቅረፍና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ጥናቱ
የትኩረት አቅጣጫዎች አመልክቷል፡፡በጥናቱ የተሸፈኑትንም ሆነ ሌሎች በዘርፉ የተስተዋሉ ተግዳሮቶችን
ለመቅረፍ በዘርፉ አመራርም ሆነ ፈጻሚ ደረጃ ወቅቱ የሚጠይቀውን ድጋፍና ክትትል በማድረግ
በሁለተኛዉ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ ዘመን ለነዚህ ጉዳዮች ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት
መተግበር ይጠይቃል፡፡በጥናቱ የተለዩ ግኝቶች በአንድ በኩል በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
ልማት ተሰማርተው የሚገኙ አንቀሳቃሾች እየገጠሟቸው የሚገኙ የፋይናንስ አቅርቦት፤ መሰረተ ልማት፣
የሥልጠና፣ መልካም አስተዳደር እና በሌሎች ምክንያቶች ዘርፉ ተገቢውን ትከረት በመስጠት ንቅናቄ
ተፈጥሮ ስላልተመራ ዘርፉ ዕመርታ ያለማስመዝገበ ሆኖ ታይቷል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ከአንቀሳቃሾቹ
የመነጩ ችግሮች በስፋት የሚታይበት በመሆኑ የዘርፉን እድገት ቀፍድዶ ይዞኣል፡፡ የዚህ ጥናት
የመፍትሔ ምክረ-ሓሰብ ማጠንጠኛም የዘርፉ ልማት እንቅስቃሴ የሚስፋፋበትና ለኢንዱስትሪ ልማቱ
ያለዉን ሚና እንዲያጎለብት ማስቻል ላይ ያጠነጥናል፡፡ በዚህ ረገድ የሚታየውን ጉድለት ለማስተካከል
በቀጣይ ኢንተርፕራይዞች የደረሱበትን የዕድገት ደረጃ መሰረት ያደረገ መንግስታዊ ድጋፎች መስጠት
የሚያስችል በህግ ማዕቀፍ የተደገፈ አሰራር ሥርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡የባለድርሻ አካላትን
በማስተባበር የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን የዕድገት ደረጃ መሰረት ያደረገ፣ መጠነ ሰፊና ሁሉን
አቀፍ ድጋፍ ቀጣይነት ባለው መልኩ መስጠት ይገባል፡፡

8
ከሌሎች ሀገሮች ተሞክሮ አንፃር ሲነጻጸር በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኢንተርፕራይዞቹ
የሚሰጠው ድጋፍ እንደ የእድገት ደረጃቸው ታይቶ የሚሰጥ ሳይሆን የጅምላ ድጋፍ ነው፡፡ ስለዚህ
የድጋፍ አሰጣጡ የዕድገት ደረጃውን መሰረት ያደረገ መሆን አለበት፡፡ በምስረታ ደረጃ ላይ ለሚገኙ
የሚሰጡ ድጋፎች የሰለጠነ የሰው ሀይል እንዲያገኙ ፣ጥሬ ዕቃ እንዲያገኙ ፤መሠረተ ልማት
እንዲሟላላቸውና የገበያ እውቀት እንዲያገኙ ማድረግ ነው፡፡ በእድገት ደረጃ ላይ ላሉ ደግሞ የብቃት
ማረጋገጫ መስጠት ፣የገበያ ልማት ፣የታክስ ተጠቃሚነትና የክህሎት ስልጠና ድጋፍ መስጠት ነው፡፡
በመስፋፋት ደረጃ ለሚገኙ ኢንተርፕራይዞች የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ ፣ የስራ አመራር ብቃት
ግንባታ ፣የንግድ ምልክት፣ የሽያጭ አውታሮች ፣ የኢንፎርሚሽንና ኮሚኒኬሽን ወዘተ መስጠትና
በማብቃት ደረጃ ለደረሱ ኢንተርፕራይዞች የዲዛይን አቅም ግንባታ ፣ የንግድ ምልክት ትውውቅ ፣
የኢንዱስትሪ ማስፋፊያና የውጭ ኢንቨስትመንት ድጋፍ መስጠት ናቸው፡፡

1.1 የጥናቱ መነሻ ሁኔታዎች

አገራችን ባለፉት አመታት ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገትን በማረጋገጥ፤ ማህበራዊ ልማትን በማፋጠንና
ዲሞክራሲያዊና ልማታዊ መንግስትን እውን በማድረግ ከፍተኛ ለውጥ አስመዝግባለች፡፡ ጥቃቅንና
አነስተኛ አንተርፕራይዞች በሀገሪቱ ለተመዘገበው እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ
አበርክተዋል፡፡የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስ ት ራተ ጂ የተመለከተዉ ዋናው
አቅጣጫ የሥራ ዕድል መፍጠር; ድህነትን መቀነስና በአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ላይ
የተመሰረተ ማኑፋክቸሪንግ ማስፋፋት እና ኢንዱስትሪያሊስት ባለሀብቶችን በብዛትና በጥራት
ማፍራት ነዉ፡፡ ይህንን ግብ ተግባራዊ ለማድረግ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በልማት
ውስጥ ካላቸው ከፍተኛ ሚና አንጻር ፈርጀ ብዙ ውጤት በሚያስመዘግቡ የእድገት ዘርፎች ላይ
ትኩረት በመስጠት በተደረገዉ ርብርብ ዘርፉ በሀገሪቱ ለተመዘገበዉ የኢኮኖሚ ዕድገት የበኩሉን
አስተዋጽኦ አድርጎኣል፡፡

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ዋና ማዕከሉ በከተሞች የሚገኘውን ስራ አጥነትንና


ድህነትን ለመቀነስ ሰፊ የስራ ዕድል መፍጠርና ለኢንዱስትሪ ልማት ሰፊ መሠረት የሚሆኑ ልማታዊ
አስተሳሰብ የተላበሱ ተቋማትን በብዛት እንዲፈጠሩ ማድረግ እንደሆነ በጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራተጂ ሰነድ ላይ ተመልክቷል፡፡ በኢንዱስትሪ ልማት ስትራተጂ
ውስጥም ወሳኝ ቦታ የተሰጠው ለጥቃቅንና አነስተኛ ተቋሞች ነው፡፡ ምክንያቱም በቅድሚያ በከተሞች
ስራ ዕድል የሚፈጥረው ዋናው ዘርፍ ይኸው በመሆኑና የኢኮኖሚ ልማትሥራዎች መሰረታዊ
ማጠንጠኛ አንዱ የሥራ እድል መፍጠር በመሆኑ ነው፡፡ እንዲሁም ተቋሞቹ በኢንዱስትሪ በተለይም
በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ዋናዎቹ አምራች ኃይሎች መሆናቸው ስለማይቀር ጠንካራና በተግባር
የተፈተኑ የልማታዊ ባለሀብት መፈልፈያ መሳሪያዎች በመሆናቸውም ጭምር ነዉ፡፡

9
በኢንዱስትሪ ልማት የላቀ ደረጃ ላይ የደረሰችውና እንደ ቶዮታና ሶኒ ያሉ ዓለም አቀፍ ግዙፍ
ኩባንያዎች ያፈለቃችው ጃፓን ሳትቀር ከ50% በላይ የሚሆነው የማኑፋክቸሪንግ ምርቷ የሚመረተው
በጥቃቅንና አነስተኛ የማኑፋክቸሪንግ ተቋሞች ነው፡፡ ስለዚህ በሀገራችንም ጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች በአምራች ኢንዱስትሪው በሀገር ልማት የሚኖራቸዉን ሚና ማጎልበት እጅግ
አስፈላጊ ነው፡፡

ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋሞች ዋነኛ የስራ እድል ፈጣሪ ኃይሎች የሚሆኑበት እንደኛ ባሉ አገሮች ብቻ
ሳይሆን እንደ አሜሪካ ባሉ የበለፀጉ አገሮችም ጭምር መሆኑን የስትራቴጂ ሰነዱ ያስረዳል፡፡
ስለሆነም ለአጭር ጊዜ ብቻ ሳይሆን ለዘለቄታውም ዋናዎቹ የስራ እድል ምንጮች እነዚህ ተቋማት
በመሆናቸው ቅድሚያ ተሰጥቶ ሊጠናከሩ እንደሚገባ የዘርፉ የልማት ስትራቲጂ በግልጽ
አስቀምጧል፡፡ ይህ ስትራቲጂ ተግባራዊ ሲሆን በከተሞቻችን የሚኖሩ ስራ ፈላጊ ዜጐች በተለያዩ
የስራ ዘርፎች ተሰማርተዉ ዕለታዊ ገቢያቸውን በማሳደግና የኑሮ ደረጃቸዉን በማሻሻል የከተሞችን
ልማት ለማፋጠን አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ከመሆኑም በላይ የኢንዱስትሪውን ልማት ለማሳደግ
መሰረት የሚሆኑ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በማብቃት ፈጣንና ቀጣይነት ያለው
የአገራችንን እድገት በማረጋገጥ ህዝቡ ከልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያስችል ነው፡፡

ከላይ እነደተመለከተዉ መንግስት በሀገራችን ላለፉት አስር አመታት ለጥቃቂንና አነስተኛ


ኢንተርፕራይዞች ልማትና ዕድገት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እየሰራ ቢገኝም፤ በአምራች ዘርፍ
ላይ ያለው ተሳትፎ ግን በቂ አለመሆኑ ታይቶዋል፡፡ ከላይ የተዘረዘሩት እንደመልካም አጋጣሚ
(Opportunity) የሚጠቀሱ ቢሆንም ለዘርፉ ልማት በቀጣይ እንደ ፈታኝ ተግዳሮት (Challenge)
የሚታዩ ጉዳዮች አሉ፡፡ዘርፉ ስኬቶችና ጥንካሬዎችም ነበሩት፡፡በዘርፉ ካሉ ተግዳሮቶች ዋነኛዉ
ከአመለካከት ጋር የተየያዘ ነዉ፡፡ በርካታ ሰው በጥቃቅንና አነስትኛ ኢንተርፕራይዞች አምራች
ዘርፎች ላለመግባት አምራች ዘርፉ ከሌሎቹ ዘርፎች ሲነጻጸር ትርፋነቱ ዝቅተኛ ነዉ ብሎ ያስባል፡፡
በዘርፉ መሰማራት ትርፍ ለማግኘት ረጂም ጊዜ የሚውስድ እንደሆነ ይታሰባል፡፡በጥቃቅንና
አነስተኛ በአምራች ዘርፍ የተሰማሩ አንቀሳቃሾች ጭምር ከአጭር ጊዜ አኳያ ከንግድና
አገልግሎት በማወዳደር በፍጥነት ሃብት የማካበት ፍላጎት ይንፀባረቅባቸዋል፡፡ ኢንተርፕራይዞቹ
ትርፋማ ቢሆኑም ገበያው በየቀኑና በየሳምንቱ የማያቋርጥ ከፍተኛ ገቢ ማስገኘት እንዳለበት የማሰብ
ሁኔታ ይታያል፡፡ ከአመለካከት ችግሮች በዘለለ መሰረታዊ የሆኑ ምክንያቶች አሉት፡፡ በገበያዉ ላይ
ያለዉ ሸማች በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ሸማች ሲሆን የተሻለ ጥራት ያለው ምርት ስለሚገዛ ጥራቱ
አስተማማኝ የሆነ የዘርፉ ምርት ገበያ ሲያገኝ በሌላ በኩል በዕውቀት ያልተመሰረተ ገዥ ከሆነ
ደግሞ ጥራት የሌለው ምርት ሲገዛ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚያመርቱት ምርት
በሙሉ ጥራት እንደሌለው ተደርጎ ስለሚወሰድ በአጠቃላይ ሸማቹ ሕብረተሰብ አመለካከት በአሉታዊ
ጎኑ ያሰፋውና አምራቾች ገበያ ያጣሉ፡፡ በተለይ የሕብረተሰቡ በሀገር ምርት የመጠቀም ንቃተ ህሊና
10
እጅግ ዝቅተኛ በሆነበት ሁኔታ በጥራት የሚከሰት እንከን ከላይ የተጠቀሰ ሁኔታ እንዲሰፋ ሰፊ ዕድል
ይሰጣል፡፡

የፋይናንስ ውስንነት እንዲሁም የማያሻማ ማነቆ መሆኑ መገንዘብ ይቻላል፡፡ አንደኛ በተግባር አሁን
ኢንተርፕራይዞቹ በብዛት እየተሰማሩበት ያሉት በብረታ ብረትና እንጨት ስራዎች ዘርፍ በመሆኑ
እነዚህ ስራዎች ደግሞ በአንጻራዊነት ከ ፍ ተኛ ካፒታል የሚጠይቁ ናቸዉ፡፡ በመሆኑም
አንተርፕራይዞች በርከት ያለ ካፒታል የማግኘት ዕድላቸው ጠባብ እንደሚያደርገው ግልፅ ነው፡
የፋይናንስ አቅርቦትና ተደራሽነት ሁለተኛ ገጽታው የመመለሻ ጊዜው አጭር መሆን ይባስ ውጤታማ
እንዳይሆን ያደርገዋል፡፡ በተለይ ለአምራች ዘርፉ የሚፈቀደው የብድር መጠኑ በተቻለ ዓቅም እያደገ
ቢሆንም የመመለሻ ጊዜው እጅግ አጭር (ከሶስት እስከ አምስት ዓመት) በመሆኑ በተለይ ጀማሪ
ኢንተርፕራይዞች ስራውን መልመድ ሲጀምሩ ገንዘቡ ስለሚመለስ ስራው እስከመቆም ያደርሳቸዋል፡፡

ሌላዉ ተግዳሮት ለእያንዳንዱ ኢንተርፕራይዝ የሚሆን መሬት ማዘጋጀት በራሱ በአቅርቦት በኩል
ፈተና ነው፡፡ በሀገራችን ከተሞች ለዚህ ተግባር ብቻ ሳይሆን ለሌሎች አገልግሎቶች የሚሆን መሬትም
በስፋት ለማቅረብ ከካሳና ተያያዥ ወጪዎች በተገናኘ ምክንያት መሬት በበቂ ሁኔታ እየቀረበ
አይደለም፡፡ ለጥቃቅንና አነስተኛ የሚሰጥ ቦታም በጊዚያዊነት በመሆኑ ኢንተርፕራይዞቹ ተረጋግተው
ለመስራት የሚያስችል አይደለም፡፡ ይሁንና በቋሚ ቦታዎችም ቢሆን በስትራቴጂው በተቀመጠ
አኳኋን የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች መንደሮች ለመገንባት ከፋይናንስ ዓቅም አንፃር
እየተቻለ አለመሆኑን በዘርፉ የተደረጉ ጥናቶች ያስረዳሉ፡ ስለሆነም ለኢንተርፕራይዞች መሬት
ማቅረብ በራሱ ፈታኝ ሆኗል፡፡ ሼዶች ለመገንባት የሚጠይቀው ወጪም እጅግ ከፍተኛ ከመሆኑ
በተጨማሪ የግንባታ ወጪ በየጊዜው እየናረ በመሆኑ የኢንተርፕራዞቹን የሼድና የመሬት ጥያቄ
መመለስ ፈታኝ እየሆነ መጥቷል፡፡ በአንዳንድ የሀገሪቱ ከተሞች በከተሞች ማስፋፍያ አከባቢ
የተቻለውን ያህል ጥረት እየተደረገ ቢሆንም የመሰረተ ልማት ችግር ያለበት ነዉ፡፡ ተጠቃሽ ከሆኑ
መሰረተ ልማቶች መብራት የመጀመርያ ጥያቄ ነው፡፡

በአምራች/ማኑፋክቸርንግ ዘርፍ ሊሰማራ የሚገባው ሀይል የመመልመል ስራም በብቃት እየተሠራ


አይዶለም፡፡ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ስራችን ኢንተርፕራይዞች ከተፈጠሩ በኋላ ብቻ የሚሰጥ
በመሆኑና ዘርፉን መቀላቀል ያለበት የሰዉ ሀይል በጥናት እየተመለመለ የሚሰራበት የኢንዱስትሪ
ኤክስቴንሽን አሰራር የለም፡፡ አንቀሳቃሾች የፈጠሯቸው ቴክኖሎጂዎች እንኳን ማባዛትና ማሻሻያ
ተደርጐባቸው እንዲሸጋገሩ የሚደረግበት ሁኔታ ባለመኖሩ ጥቃቅን አነስተኛ የኢንዱስትሪ ሰፊ
መሠረትና መፈጠሪያ ማድረግ አልተቻለም፡፡ እስካሁንም እንደ ሀገር በአምራች ዘርፍ የተሰማራው
ከ16 በመቶ በላይ እንዳልሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ በዘርፉ ያሉት ማበረታቻዎችና አስቻይ
ሁኔታዎችም ያን ያ ህል ጠንካራ አይዶለም፡፡በአጠቃላይ ዘርፉ በርካታ ችግሮት በስፋት
ይታዩበታል፡፡ አብዛኞቹ ችግሮች ዓመታት ያስቆጠሩና ለመፍታቱም ጠንካራ እ ርም ጃ
11
ያልተወሰደባቸው ናቸው፡፡ ከዚህ አንጻር በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት በተለይም
የአምራች ዘርፍ በዘርፉ ስ ት ራተ ጂ በታሰበዉ ልክ እየተመራ መዋቅራዊ ሽግግርና ዕድገት
እያስመዘገበ ነው ለማለት አያስደፍርም፡፡

ከላይ የተጠቀሱ ተግዳሮቶች ቢኖሩም በሀገራችን ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ሠፊ የስራ


እድል ፈጣሪ ኃይሎች እንዲሆኑና በአምራች ኢንዱስትሪ ሰፊ መሰረት እንዲጥሉ የሚያስችሉ
ስራዎች እየተሰሩ ናቸዉ፡፡ ይህንን ተከትሎ በአዲስ አበባ ከተማ በርካታ የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርኘራይዞች በተለያዩ ዘርፎች እንዲሰማሩ በማድረግ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላለዉ ለከተማ ነዋሪ
ህዝብ በተለይም ለሥራ አጥ ሴቶችና ወጣቶች ሠፊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡ ኢንዱስትሪው ሰፊ
መሠረት እንዲኖረውም በርካታ ኢንተርፕራይዞች በቀላል አምራችነት እንዲጀምሩና በሂደት
የምርታቸው ዓይነትና የቴክኖሎጂ አቅማቸውን መዋቅር እንዲያሳድጉ እየተደረገ ነው፡፡ በዚህ ጥረት
በኢንዱሰትሪው ውስጥ የደረጃ መዋቅር ስብጥር ለማስተካከል በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
ሰፊ ስራ በመሰራቱ በከተማዋ በርካታ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በአምራች ዘርፍ
ተሰማርተው ይገኛሉ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን ነዋሪ ህዝብ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ችግሮችን በመቅረፍና
የነዋሪዎችዋን የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ሰፊውን የህብረተሰብ ክፍል በተለይም በርካታ ሥራ ያልነበራቸዉን
ሴቶችንና ወጣቶችን በጥቃቅንና አነስተኛ አንተርፕራይዞች በማደራጀት የሥራ ዕድል በመፍጠር
ኑሮኣቸውን ለማሻሻልና ከልማቱ የተጠቃሚነት ዕድል ለማስፋት ባካሄደው ከፍተኛ ጥረት አበረታች
ውጤቶችን ማስመዝገብ ችሏል፡፡ በዚህም መሠረት የአዲስ አበባ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ
ልማት ቢሮ በሥሩ ባሉት አስር ክ/ከተሞችና 117 ወረዳዎች በሚገኙ ጽ/ቤቶች ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ
የተደራጁ 27187 ኢንተርፕራይዞች በውስጣቸው የስራ ዕ ድል መፍጠራቸውን በየጊዜው ከሚደረጉ
ሪፖርቶች የሚገለጽ ቢሆንም የተፈጠረው የስራ ዕድል ከድግግሞሽ ነጻ በሆነ አኳኋን በጠራ የመረጃ /data
base/ ስርዓት በአንድ ማዕከል አገልግሎት በአንድ ቋት እየተቀናነሰና ስራ ፈላጊው ዜጋ ከወሰደው የስራ
አጥ ካርድ አንጻር እየተረጋገጠ የስራ ስምሪት እንዲያገኝ የተኬደበት ርቀት ሰፊ ጉድለት የነበረበት ነው፡፡
ስለሆነም አንድ ስራ የተፈጠረለት ዜጋ (በተለይ በጊዜያዊ ስራ ዕድል) ከአንድ ጊዜ በላይ ሪፖርት ሊደረግ
የሚችልበት ዕድል ዝግ እንዳልነበረ መገንዘብ ይቻላል፡፡ የመረጃ ስርዓቱን በአንድ ማዕከል አገልግሎት
ላይ ማዘመን ከተቻለ የመረጃ ጥራቱና ተዓማኒነቱ በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ይቻላል፡፡

ስለሆነም በአዲስ አበባ ከተማ እስከ አሁን የተደራጁ ኢንተርፕራይዞችበስራ ላይ መኖር ያለመኖራችውን፣
አሁን ያሉበትን ደረጃ፣የስራ ስምሪታቸው ስብጥርና ምክንያት፣ ከመንግሥት እየተደረገላቸው ያለውን
የድጋፍ ማዕቀፍ እና የሥራ ዕድልን ከመፍጠር አንጻር የወጣቶችና የሴቶች ተሳትፎ ምን ያህል እንደሆነ፣
የኢንተርፕራይዞቹ ወደ ታዳጊ መካከለኛ ኢንዱስትሪ ኢንተርፕራይዝነት የመሸጋገር ሂደቱ ምን
እንደሚመስል፣ ከኢንዱስትሪ ልማት ያላቸውን ትስስርና ያሉባቸውን መሰረታዊ ተግዳሮቶች ለይቶ
12
በማወቅ ዘርፋ እንዲሰፋ የሚያስችሉ እርምጃዎች መውሰድና የተሻለ አስቻይ ሁኔታ መፍጠር
ያስፈልጋል፡፡

በአጠቃላይ የስራ ዕድል ፈጠራው የተሳካ ነዉ ማለት ይቻላል፡፡ ሆኖም ግን የኢንተርፕራይዞች ልማትን
ከማስፋፋት አንጻር የሚፈጠሩ አብዛኞቹ የስራ ዕድሎች በቋሚ ስራ ላይ በተለይም በአምራች ዘርፉ ላይ
እንዲሆን ከማድረግ አንጻርና በዚህ ዘርፍ የሚሰማሩ ዜጎች ዝርዝር መረጃ ከመያዝ አንስቶ ተከታታይ የሆነ
ግንዛቤ በመፍጠርና በማሳመን ላይ የተመሰረተ የማያቋርጥ የቁጠባ ስራ እንዲፈጠር በማድረግ በመምራት
በስትራተጂው መሰረት በርካቶችን ወደ ቋሚ ስራ ዕድል ማሸጋገር ያስፈልጋል፡፡ በዚህ ረገድ የሚታየውን
ጉድለት ለማስተካከል በቀጣይ ከጅምላ መንግስታዊ ድጋፍ በመውጣት በጥቃቅን፤ በአነስተኛና በመካከለኛ
ደረጃ የሚገኙትን እንተርፕራይዞች የደረሱበትን የዕድገት ደረጃ መሰረት ያደረገ መንግስታዊ ድጋፎች
መስጠት የሚያስችል አሰራር በመዘርጋት በመጀመሪያ ዙር የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የታየዉ
ጉድለት በቀጣዩ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዓመታት እንዳይደገም በግልጽ አሰራር እንዲታገዝ
አቅዶ መስራት ይጠይቃል፡፡ የዚህ ሰነድ ዓላማም ይህንኑ ለማጠናከር ወይም እዉን ለማድረግ
የሚያስችል ጥናት በማካሄድ ችግሮችን መለየትና የመፍትሔ ሀሳብ መስጠት ነዉ፡፡

1.2 የችግሩ ምንነት ሐተታ

አገራችን ከምትከተላቸው የእድገትና ድህነት ቅነሳ ስትራቴጃዊ አቅጣጫዎች መካከል የከተሞች


የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራቴጂ አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ስለሆነም እነዚህን
ኢንተርፕራይዞች በተደራጀና ጥራት ባለው መረጃ ላይ ተመስርቶ ማስተዳደር ኢኮኖሚያዊ፣
ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ እነዚህ ኢንተርፕራይዞች በአሁኑ ሰዓት ያሉበትን
ደረጃ በማጥናትየወደፊት አቅጣጫ መንደፍ ተገቢ ነው፡፡

በዚሁ መሰረት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያሉት ኢንተርፕራይዞች ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ
ተደራጅተው በ2006 ዓ.ም ያሉበትን ሁኔታ ለማጣራት ዳግም ምዝገባ የተካሄደ ቢሆንም ያለው መረጃ
ግን ኢንተርፕራይዞቹ ያሉበትን ሁኔታ በግልጽ የሚያሳይ ባለመሆኑ በከተማዉ የሚገኙ
ኢንተርፕራይዞች ምዝገባና ቆጠራ ተካሂዷል፡፡የዚህን ቆጠራ ዉጤት መሰረት በማድረግ በዘርፉ
ያሉትን ወሳኝ ማነቆዎች በመለየት ለዘርፉ ልማት ዘላቂነት የተሻለ አስቻይ ሁኔታ ለመፍጠር
ለከተማ አስተዳደሩም ሆነ ለኢንተርፕራይዞቹ ግብዓት ይሆን ዘንድ ይህ ጥናት ተከናውኗል፡፡ጥናቱ
በዋናነት ያተኮረዉ የዘርፉ ዕድገት ከኢንዱስትሪው ልማት ጋር ያለው ትስስርና ኢንተርፕራዞቹ
ያሉባቸውን ማነቆዎች ማየት፣ አፈጻጸማቸውን መገምገም፤ በሌላ በኩል ደግሞ በዘርፉ የሚሰማሩ
አንቀሳቃሾች በማኑፋክቸርንግ ዘርፉ በስፋት ያልተሰማሩበትን በአፈጻጸምና አሰራር ደረጃ የሚገለጹ
ምክንያቶች አጥንቶ መሰረታዊ ለውጥ ለመምጣት የሚያስችሉ የፖሊሲ የመፍትሔ ምክረ-ሐሳቦች

13
ማቅረብ ነዉ፡፡ በመሆኑም ጥናቱ ለከተማ አስተዳደሩ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ፋይዳ
አለዉ፡፡ በተጨማሪም ለኢንተርፕራይዞቹም ሆነ ለተጠቃሚው ህብረተሰብ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለዉ፡፡

1.3 የጥናቱ ዓለማ

ይህ ጥናት እንዲያሳካ የታሰበዉ አጠቃላይና ዝርዝር ዓላማዎች የሚከተሉት ናቸዉ፡፡

1.3.1 አጠቃላይ ዓላማ

የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የተደራጁት የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ዝርዝር ቆጠራ ማካሄድና ያሉበትን አጠቃላይ ሁኔታ በመዳሰስ ማነቆዎችን ለይቶ
የዘርፉን የልማት አቅጣጫ በትክክለኛና በተጨባጭ መረጃ ላይ ተሞርኩዞ መምራት የሚያስችል
የመፍትሔ ሃሳብ ለመጠቆም ነው፡፡

1.3.2 የጥናቱ ዝርዝር ዓላማዎች

 ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ቆጠራ ማካሄድና አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች
ማደራጀትና መተንተን፤
 ከ1996 ዓ.ም ጀምረው የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች የእድገት ደረጃቸውን ሁኔታ በመዳሰስ፣
የአካባቢ ስርጭታቸውን ከዕድገት ተኮር ዘርፎች አንጻር በዝርዝር መለየት፤
 በስትራቲጂው የድጋፍ ማዕቀፍ መሠረት የተሟላ ድጋፍ ያገኙና ያላገኙ ኢንተርፕራይዞችን
በዝርዝር መለየት፤
 ከህዝብ ተጠቃሚነት አንጻር በኢንተርፕራይዞቹ የታቀፉ አንቀሳቃሾች እና የፈጠሯቸው
ቋሚና ጊዜያዊ የሥ ራ ዕድሎች በጾታ፣ በዕድሜና በትምህርት ደረጃ በዝርዝር ለይቶ
ማስቀመጥ፤
 በሂደት የከሰሙ ኢንተርፕራይዞች ብዛታቸውን መለየትና የከሰሙበትን ምክንያት ማወቅ፣
 ኢንተርፕራይዞቹ ከተሰማሩበት የዕድገት ዘርፎች አንጻር የአፈጻጸም ማነቆ የሆኑትን ችግሮች
በመለየትና በመተንተን ቀጣይ ትኩረት ለሚሹ ጉዳዮች የመፍትሄ ሃሳብ ማስቀመጥ፤

1.4 የጥናቱ መሠረታዊ ጥያቄዎች

ከላይ በጥቅል ዓላማ በተቀመጠዉ መሰረት ዝርዝር ዓላማዎቹን ከግብ ለማድረስ ትኩረት በመስጠት
በዚህ ጥናት በዝርዝር መመለስ የሚገባቸው ገዥ ጥያቄዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡

 ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ የተደራጁት ኢንተርፕራይዞች በአሁን ሰዓት በተጨባጭ በሥራ ላይ


ያሉት በቁጥር ስንት ይሆናሉ?
 ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃቸው ሁኔታና የአካባቢያዊ
ስርጭታቸው ከአምስቱ የእድገት ተኮር ዘርፎች አንጻር በምን ሁኔታ ላይ ይገኛሉ?
14
 ለኢንተርፕራይዞቹ ከተደረገላቸው ስትራቴጂያዊ ድጋፍ አንጻር ድጋፉ እንዴት ይገለጻል?
የተሟላ ድጋፍ ያገኙትስ ስንት ናቸው?
 የኢንተርፕራይዞቹ አንቀሳቃሾችና በስራቸው የተፈጠሩት የሥራ ዕድሎች በፆታ፣ በዕድሜና
በትምህርት ደረጃ ሲታዩ ምን ይመስላሉ?
 በሂደት የከሰሙ ኢንተርፕራይዞች ካሉ ምን ያህል ናቸው? የከሰሙበት ምክንያትስ
ምንድነው?
 ከዘርፉ ስትራቴጂ እና ኢንተርፕራይዞቹ ከተሰማሩበት አምስቱ የዕድገት ተኮር ዘርፎች
አፈጻጸም አንጻር ማነቆዎችና መፍትሔዎች ምን ምን ናቸው?

1.5 የጥናቱ ፋይዳዎች

ይህ ጥናት የሚከተሉት ዋና ዋና ፋይዳዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡

 በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ አብዛኛውን


ህብረተሰብ በተለይም ወጣቶችና ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚሰጡ የድጋፍ ማዕቀፎች
ከአድሎአዊ አሰራር እና ከእላፊ ተጠቃሚነት ተላቀው በልማታዊ መንገድ ብቻ ማደግ
የሚችሉ ኢንተርፕራይዞችን በማፍራት እየተመዘገበ ያለውን ውጤት በተጨባጭ መረጃ ላይ
ተሞርኩዞ ለመገምገም እንዲሁም በየጊዜው እያደገ ከመጣው ፍላጎት አንጻር የማሻሻያ
እርምጃዎችን በመውሰድ ዘርፉን በእውቀት ለመምራት ያግዛል፤
 ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች በተመለከተ የጠራ፣ ግልጽ፣ ወጥነትያለው፣
ተደራሽና ተአማኒነት ያለው መረጃ በመሰብሰብ እና በማጥናት በቀጣይ የእድገት ተኮር
ዘርፎችን መሰረት ያደረገ የልማት አቅጣጫን እና ከሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን
ዕቅድ አንጻር ዘርፉን ለመምራት በጎ አስተዋዕጾ ይኖረዋል፤
 የዘርፉን እንቅስቃሴ ከስትራቴጂው ትግበራ አንጻር ለመምራት በግልጽ መረጃ ላይ የተደገፈ
ፈጣን ውሳኔ ለመስጠት ያስችላል፣
 የዚህ ጥናት ውጤት ለቀጣይ ጥናት እንደመነሻ ሆኖ ያገለግላል፡፡

1.6 የጥናቱ ወሰን

ይህ ጥናት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ1996ዓ.ም ጀምሮ በአምሰት የእድገት ተኮር ዘርፎች
ማለትም በማኑፋክቸሪንግ፣ በኮንስትራክሽን፣ በአገልግሎት፣ በንግድና በከተማ ግብርና በተደራጁ
የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተሟላ፣ ተዓማኒና ትክክለኛ መረጃ በመሰብሰብ ማጥናትን
ማዕከል ያደረገ ነው፡፡ በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በ117 ወረዳዎች ሥር ከ1996
ዓ.ም ጀምሮ በአምስቱ የዕድገት ተኮር ዘርፎች በጥቃቅና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ተደራጅተው
የከሰሙ፤ ወደ መካከለኛ ታዳጊ ኢንተርፕይዝ የተሸጋገሩ እና አሁን በከፊል ወይም

15
በሙሉከመንግስት የሚሰጡትን የተለያዩ ድጋፎች እየተጠቀሙ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች ዝርዝር
መረጃ ለይቶ በመሰብሰብ፤ በማደራጀትና በመተንተን በዘርፉ ልማት እንቅስቀሴ የሚታዩ ማነቆዎችን
ለይቶ ቀጣይ ትኩረት አቀጣጫዎች ለማሳየት ነው፡፡

1.7 የጥናቱ ውስንነቶችና የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎች

1.7.1 የጥናቱ ዉስንነቶች

በኢንተርፕራይዞች ቆጠራ እና ጥናት ወቅት በሁሉም ኢንተርፕራይዞች ዘንድ ያጋጠሙ ዋና ዋና


ችግሮች የሚከተሉት ናቸዉ፡፡

 አንዳንድ ኢንተርፕራይዞች በተለይም የከሰሙት በአድራሻቸው አለመገኘት፤

 መረጃ ሰብሳቢዎችና ሱፐርቫይዘሮች ተግባራትን ከጽ/ቤቶች ጋር ተቀራርቦ ለመፍታት


ውስንነት መታየት፤

 የተሰጠውን መረጃ ለማረጋገጥ የወረዳ ጽ/ቤቶች ዝግጁነት ማነስ

 የተሰበሰበዉ መረጃ በአግባቡ ለትንተና በሚያመች መልኩ በሶፍትዌር አለማደራጀት፤

 በኮብል ስቶን ሳይት ማግኘት የተቻለው ተደራጅተው በሥራ ላይ ያሉትን ሲሆን በተለያየ ጊዜ
ተደራጅተው የተበተኑትን በዝርዝር የማግኘት ችግር ማጋጠሙ፤

 በኮብል ስቶን ሳይት መረጃ ሰብሳቢዎችን ለማሰማራትና ለመከታተል የትራንስፖርት ድጋፍ


ውስንነት ማጋጠሙ፤

1.7.2 ለጥናቱ ዉስንነቶች የተሰጡ መፍትሔዎች

 ሱፐር ቫይዘሮች የስራ ክፍፍል አድረገው ተግባሩን እንዲደግፉ እና ዕቅድ አዘጋጅተው


እንዲያቀርቡ ተደርጓል

 የተሰበሰበዉ መረጃ በአግባቡ እንደገና እንዲደራጂ ተደርጎ የትንተና ሥራ ተሠርቷል፡፡

 ለመረጃ ሰብሳቢዎች በግል በትራንስፖርት ለመሄድ አመቺ ባልሆኑባቸዉ ክፍለ ከተሞች


መረጃው ተሰብስቦ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የተሽከርካሪ ድጋፍ ከዩኒቨርሲቲ እና ከቢሮ
በመመደብ አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጓል

1.8 ማጠቃለያ

ከላይ እንደተመለከተዉ በዚህ በመጀመሪያዉ ምዕራፍ ለዚህ ሰነድ ዝግጅት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮች
የተዳሰሱ ሲሆን ጥናቱ የተመራበት አቅጣጫ የሚያመላክቱ ዝርዝር ዓላማዎችና መሪ ጥያቄዎች

16
እንዲሁም የጥናቱ ፋይዳና በጥናቱ ሂደት ያጋጠሙ ውስንነቶችና መፍትሔዎቻቸው ተዳስሰዋል፡፡
በሚቀጥለዉ ምዕራፍ ከኢንተርፕራይዞች ልማት ጋር ተዛማጅነት ያለቸዉ የጽሁፎች ዳሰሳ ቀርቧል፡፡

17
ምዕራፍ ሁለት፡ ተዛማጅ ጽሑፎች ዳሰሳ
2.1 መግቢያ

ሀገራችን ኢትዮጵያ በዘረጋቻቸው የኢኮኖሚና ማህበራዊ መርሃ-ግብሮች በመታገዝ ባለፉት ተከታታይ


አመታት ፈጣን ልማት አስመዝግባለች፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ታምኖበታል፡፡ ስለሆነም መንግስት ለበርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች የስራ
ዕድል ለመፍጠር እና ድህነትን ለመቀነስ ብሎም ሴክተሩን የኢንዱስትሪ ዕድገት መሰረት ለማድረግ
ስትራቴጂና ፖሊሲ በአገር አቀፍ ደረጃ ቀርጾ ተግባራዊ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም ይህን ስትራቴጂና ፖሊሲ ተግባራዊ ያደረገ ሲሆን ቀደም ሲል
የተገኙ ውጤቶችን በተሻለ መንገድ ለማስቀጠልና የቀጣይ ትራንስፎርሜሽን ዕቅዶችን ለማሳካት
ባለፉት አመታት በዘርፌ ያጋጠሙ ችግሮች፤ የተገኙ ልምዶችና የውጭ ሀገር ተሞክሮዎችን መዳሰስ
አስፈላጊ ሆኗል፡፡ በመሆኑም በዚህ ምዕራፍ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ ፣ታሪካዊ
አመጣጥና ዕድገት የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ እንደዚሁም የኢትዮጵያ ጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ስትራቴጂናፖሊሲ እንዲሁም የአፈፃፀም ስልቶች ተዳሰዋል፡፡

2.2 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ

የተለያዩ ሀገራት ተሞክሮ እደሚያሳየው የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ልማት ለማፋጠንና


ቀጣይነት ያለው ድጋፍ ለማድረግ ወጥነት ያለው ሀገራዊ የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞችትርጓሜ አስፈላጊ ነው፡፡ ከውጭ ሀገር ተሞክሮ እንደተስተዋለው በአጠቃላይ ሲታይ
በዋናነት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ ሦስት መሰረታዊ መስፈርቶችን የያዘ ነው፡፡

1. የሙሉጊዜተቀጣሪየሰውኃይልብዛት
2. ጠቅላላሃብት፣የተጣራሀብትናየተከፈለካፒታልእንዲሁም
3. ጠቅላላአመታዊ ሽያጭሲሆኑ

እነዚህን መሰረቶች በጣምራ ወይም በተናጥል ይጠቀሟቸዋል፡፡ ሆኖም ግን አንዳንድ ሀገሮችና አለም
አቀፍ ተቋማት ከነዚህ ሦስት መሰረታዊ መስፈርቶች በተጨማሪ ህጋዊ ባለቤትነት፤ በኢንዱስትሪው
አይነት (ማኑፋክቸሪንግ ፣ ኮንስትራክሽን ፣ ትራንስፖርት ፣ ጅምላና ችርቻሮ ንግድ፣አገልግሎት
ወዘተ) እንዲሁም ደግሞ የዋጋ ግሽበትንና የምርታማነት እድገትን ታሳቢ በማድረግ የትርጉም
ማሻሻያ ያደርጋሉ፡፡

በሀገራችን ኢትዮጵያ ሶስት የተለያዩ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜዎች በስራ ላይ


ውለዋል፡፡ እነዚህም፡-

1. የ1990 የጥቃቅንናአነስተኛልማትኤጀንሲትርጓሜ

18
2. የማዕከላዊስታቲስቲክኤጀንሲትርጓሜ
3. የተሻሻለውየጥቃቅንናአነስተኛኢንተርፕራይዞችትርጓሜናቸው

2.2.1 የ1990 ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ

ይህ ትርጓሜ መሰረት ያደረገው የተከፈለ ካፒታልን ነው፡፡

ሠንጠረዥ 1፡ የ1990 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ በኢትዮጵያ


የሰውኃይል የተከፈለካፒታል
ዘርፍ
- <ብር 20 ሺህ
ጥቃቅንኢንተርፕራይዝ
- <ብር 500 ሺህ
አነስተኛኢንተርፕራይዝ

ምንጭ፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ኤጄንሲ (1997)

ይህ ትርጓሜ በሁለቱም ዘርፍ የተከፈለ ካፒታልን ብቻ መሰረት ያደረገ በመሆኑ የስራ ዕድል ፈጠራን
አያመለክትም፡፡ እንደዚሁም ደግሞ በአብዛኛው የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቋቋሙት
በራስ መዋጮ እና በባንክ ብድር በመሆኑ የተቋሙን ሙሉ ገጽታ አያሳይም፡፡ በነዚህ ምክንያቶች
ይህ ትርጓሜ ክፍተቶች ይታዩበታል፡፡

2.2.2 የማእከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ ትርጓሜ

የማእከላዊ ስታስቲክስኤጀንሲዘርፉን በተመለከተ የሰጠው ትርጉም ስራዎች የሚሰሩበትን የቴክኖሎጂ


ሁኔታና የሰው ኃይልን ግምት ውስጥ በማስገባት ነው (CSA 2003)፡፡ በዚህም መሰረት፡-

ሀ/ የዕድ ጥበብና የጎጆ ኢንዱስትሪ በቤተሰብ የሰው ሃይል ላይ የተመሰረቱ የሞተር ሀይልን
የማይጠቀሙ እና በእጅ የሚሰሩ ተግባራትን ያካትታል፡፡

ለ/ አነስተኛ ማኑፋክቸሪግ ኢንዱስትሪ ከ10 ያነሰ የሰው ሃይል ያላቸውና የሞተር ሃይልን የሚጠቀሙ
ናቸው፡፡

ይህ ትርጓሜ ሁሉንም ዘርፎች ያላካተተና የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ ብቻ ያተኮረ መሆኑና


የካፒታል መጠን እንደመስፈርት አለመጠቀሙ ውስንነቶች አሉበት፡፡

2.2.3 የተሻሻለው የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ

የኢትዮጵያ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ኤጀንሲ የውጭ ሀገራትን ተሞክሮ መሰረት
በማድረግና ሥራ ላይ ያለውን የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ ክፍተቶች በመገንዘብ
ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞችን ብዛትና ጠቅላላ ሀብት በመስፈርት በመጠቀምና በኢንዱስትሪና
በአገልግሎት በመክፈል የተሻለ ትርጓሜ ሰጥቷል (የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራዮዞች ኤጄንሲ፤
2005)፡፡

19
ሠንጠረዥ2፡ የተሻሻለው የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ በኢትዮጵያ
የኢንተርፕራይዝ ደረጃ ዘርፍ የሰው ኃይል ጠቅላላ ካፒታል
ጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ኢንዱስትሪ < 5 <ብር 100 ሺህ

አገልግሎት < 5 <ብር 50 ሺህ


አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ኢንዱስትሪ ከ6-30 ከብር 100,001-1.5 ሚሊዮን
አገልግሎት ከ6-30 ከብር 50,001-500 ሺህ

ምንጭ፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ኤጄንሲ (2005)

ከላይ በተገለፀው ትርጉም በሰው ሃይልና በጠቅላላ ሃብት መካከል አሻሚ ሁኔታ ሲፈጥር የጠቅላላ
ሀብት መጠን ቀዳሚ መስፈርት ሆኖ ያገለግላል፡፡ ይህ ጥናት የተሻሻለውን የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ትርጓሜ የተጠቀመ ሲሆን፡-

ጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ማለት የኢንተርፕራይዙን ባለቤት የቤተሰብ አባላትና ተቀጣሪ ሰራተኞችን


ጨምሮ እስከ 5 ሰዎች ቀጥሮ የሚያሰራና የጠቅላላ ካፒታሉ መጠን ህንፃን ሣይጨምር በአገልግሎት
ዘርፍ ከብር 50,000 (ሃምሳ ሺህ ብር) ወይም በኢንዱስትሪ ዘርፍ ከብር 100,000 (አንድ መቶ ሺህ
ብር) ያልበለጠ ኢንተርፕራይዝ ነው፡፡

አነስተኛ ኢንተርፕረይዝ ማለት ደግሞ የኢንተርፕራይዙን ባለቤት፣የቤተሰብ አባላትና ተቀጣሪ


ሰራተኞችን ጨምሮ ከ6-30 ሰዎች የሚያሰማራና የጠቅላላ ካፒታሉ መጠን ህንፃን ሣይጨምር
በአገልግሎቱ ዘርፍ ከብር 50,001 (ሃምሳ ሺህ አንድ ብር) እስከ ብር 500,000 (አምስት መቶ ሺህ
ብር) ወይም በኢንዱስሪ ዘርፍ ከብር 100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) እስከ 1.5 ሚሊዮን ያልበለጠ
ኢንተርፕራይዝ ነው፡፡

2.3 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ታሪካዊ አመጣጥ፤ ዕድገትና ፋይዳዎች

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የትና እንዴት እንደተመሰረቱ በግልፅ የሚታወቅ ነገር የለም፡፡
ነገር ግን ዛሬ በአደጉ ሀገራት የምናያቸው ትላልቅ ኩባንያዎች የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞችውጤቶች እንደሆኑ መረጃዎች ያመላክታሉ (Snodgras and Biggs: 1996) ፡፡ዛሬ
ድረስ ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለስራ ፈጠራ ብሎም ለማኑፋክቸሪንግ ዕድገት ያላቸው ሚና ከፍተኛ
እንደሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና አግኝቷል (ILO 2003, Haftu etal 2009)፡፡ እንዲሁም
ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ለማድረግ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ታምኖበታል፡፡

መረጃእንደሚያመለክተው እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከ1970 በፊት ትልልቅ የማኑፋክቸሪንግ


ኢንዱስትሪዎችን በመጠቀም ስራ አጥነትን ለመቀነስ የተደረገው ጥረት ውጤታማ አልነበረም፡፡
ምክንያቱ ደግሞ እነኝህ ትላልቅ ኢንተርፕራይዞች የሚፈልጉት ትላልቅ ማሽነሪዎችን፣ የተሻሻለ
ቴክኖሎጂ ትላልቅ፤ ኢንቨስትመንት እና ፋይናንስ እንዲሁም የተማረ የሰው ሃይል በመሆኑ ነው፡፡

20
ይህ ደግሞ ኢትዮጵያን ጨምሮ በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት አቅርቦታቸው ውስን ነው፡፡ ስለዚህም
ብዙዎቹ እንደሚስማሙበት በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት በተላይም በአፍሪካ ትላልቅ ኢንዱስትሪዎችን
ማስፋፋት ላይ ብቻ ያተኮረ ፖሊሲ ትክክል አለመሆኑን ብቻ ሳይሆን ብዙ ወጣቶችን ስራ አጥ
ማድረግም ጭምር ነው፡፡

ከ1970 ወዲህ የታዩ የሥራ አጥነት፣ የድህነትና ኢፍትሃዊ የሆነ የሃብት ክፍፍል የብዙ ሀገራት
ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች እንደገና እንዲፈተሹ ረድቷል፡፡ በተለይ ILO ያጠናው ጥናት
እንደሚያሳየው ጉልበትን በሰፊው በመጠቀም የተሻለ ገቢ ማግኘት የሚቻለው ጥቃቅንና አነስተኛ
ጥቃቅን ሴክተሩን በመጠቀም ነው (Yose Gugler: 2002):: ስለሆነም ሰፊ የሰው ጉልበትን በመጠቀም
የተሻለ ለማምረትና ስራ አጥነትን ብሎም ድህነትን በገጠርም ሆነ በከተማ ለመቀነስ በማደግ ላይ ያሉ
ሀገራት የሚከተሉት አቅጣጫ ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማትን ማስፋፋት ነው /Thorbecke: 2000/::

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ውጤታማ ለማድረግ ያደጉትም ሆነ በማደግ ላይ ያሉ


ሀገራት ለዘርፉ ድጋፍ በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ WB፣UNIDO፣ADB እና ሌሎችም አለም አቀፍ
ተቋማት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ፖሊሲዎችን ይደግፋሉ፡፡ ለምሳሌ Tlus T.
(2006) እንደገለፀው የዓለም ባንክ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ላይ ትኩረት ያደረገባቸው
ሦስት ምንያቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡ እነርሱም፡

1ኛ ውድድርንና ስራ ፈጠራን ለማበረታታት፣ 2ኛ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተሻለ


ውጤታማ በመሆናቸውና የሥራ ዕድል በመፍጠርም ከታላላቅ ኢንተርፕራይዞች ስለሚሻሉ እንዲሁም
3ተኛ ደሃውን የህብረተሰብ ክፍል በቀላሉ ለመድረስ እንዲቻል ነው፡፡

በተግባር ሲታይ ምንም እንኳን ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ለስራ ፈጠራ ወዘተ በአደጉ ሀገራት ለምሳሌ
አሜሪካ ፣ጣሊያን፤ ጃፓን እና ምስራቅ ኤሺያ ሃገራት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ትልቅ
ሚና ያላቸው ቢሆንም በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት በተላይም በአፍሪካ የሚገኙ በርካታ ቁጥር ያላቸው
ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችየድህነትና የኋላ ቀርነት ምልክት ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ ነገር
ግን OECD (2004) ባወጣው መረጃ እንደተመለከተው መጠነ ሰፊ የሆነና ጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞችን ያካተተ ዕድገት ፈጣን ከመሆኑም ባሻገር ለብዙ ድሃ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሻለ
ዕድል ከመፍጠሩም በላይ ብሎም ለድህነት ቅነሳ መሰረትይሆናል፡፡ ብዙውን ጊዜ ትላልቅ የሚባሉ
ኩባንያዎች ከማምረት ይልቅ ንግድ ላይ ያተኩራሉ፡፡ ለስራቸውም የተሻለ ቴክኖሎጂ የሰው ሀይልና
ካፒታል ይፈልጋሉ፡፡ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችግን አስፈላጊው ድጋፍ ቢደረግላቸው
በማኑፋክቸሪንግና ሌሎች የማምረት ሥራዎች ይሰማራሉ፡፡ ከህረተሰቡና ከታላላቅ ኢንተርፕራይዞች
መካከል በመሆን የማስተሳሰር ስራ ይሰራሉ፡፡ ቀስ በቀስም ወደ መካከለኛና ትልልቅ ኢንተርፕራይዝ
ያድጋሉ፡፡ በተግባር በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት የሚገኙት አብዛኞቹ ጥቃቅንና አነስተኛ

21
ኢንተርፕራይዞች ግን ብዙ ጊዜ ወደ ሚቀጥለው ደረጃ ከማደግና የተሸለ የኢኮኖሚ ዕድገት
አስተዋጽኦ ከማድረግ ይልቅ ባሉበት የመቆየት አዝማሚያ ይታይባቸዋል፡፡ እዚህ ላይ መጠየቅ
ያለበት ጥያቄ አንዳንድ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከሌሎች በተለየ ሁኔታ ለማደግ
የቻሉት ለምንድን ነው የሚለው ነው፡፡ ለምንስ ብዙዎቹ ለማደግ አልቻሉም የሚለዉ ሌላ ጥያቄ
ነው፡፡ ይህ እንደተቋሙ የስራ ዘርፍ እንዲሁም የተቋሙ የፋይናንስ አቅም፤የቴክኖሎጂ
አጠቃቀም፤ከሌሎች ጋር ተባብሮ የመስራት የተሻለ የቢዝነስ ኢንቨስትመንትና የህግ ማዕቀፍ መኖር
የተሻለ መሰረተ ልማት መኖር እንዲሁም የተሻለ የገበያ ትስስር መኖር ወዘተ ወደተሻለ ደረጃ
ለማደግም ሆነ ባሉበት ለመቀጠል እንደምክንያት ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡

ስለሆነም የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳዎችን ከግምት ውስጥ


በማስገባት ከላይ የተጠቀሱትን ምክንያቶች ማዕከል ያደረገ ድጋፍ ማድረግ የተሻለ አማራጭ ነው፡፡

2.4 የሌሎች አገሮች መልካም ተሞክሮ

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በሌሎች ሀገሮች የኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን


ተሞክሮ መዳሰሱ ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ በተለያዩ ሀገራት የሚጫወቱት ሚና እና የማሌዥያ ፣
የጃፓን እንዲሁም የታንዛንያ ተሞክሮ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

2.4.1 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ሚና

በአደጉ ሀገራትም ይ ሁን በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች


በኢኮኖሚው ውስጥ በአጠቃላይ ሀገራዊ ምርትና ከስራ ዕድል ፈጠራ አንፃር ከፍተኛ ድርሻ አላቸው፡፡
እንደ Todaro (2000) ሴክተሩ በከተማ የሥራ ዕድል በመፍጠር ትልቁን ድርሻ ይወስዳል፡፡ በኤስያ
ባሉ ሀገራት ብንመለከት በህንድ 50 በመቶ ፤ በኢንዶኔዥያ 45 በመቶ ፤ በማሊዥያ 35 በመቶ
እንዲሁም በፓኪስታን 60 በመቶ የስራ እድል በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ተፈጥሮአል፡፡
በላቲን አሜሪካ እንደዚሁ በቦሊቪያ 61 በመቶ ፤ በአርጀንቲና 55 በመቶበብራዚል 56 በመቶና
በፖሩዋጋይ 69 በመቶ ይደርሳል፡፡ በአፍሪካ ከሚገኙ ሀገራት በኬኒያ 40 በመቶ፤ በጋና 80 በመቶ
እንዲሁም በኢትዮጵያ 80 በመቶ (Omer et al 2015) ይደርሳል፡፡

ሌላ መረጃ እንደሚያሳየው ደግሞ በህንድ ዘርፉ 45 በመቶ የማኑፋክቸሪንge እንዲሁም የኤክስፖርት


ድርሻ 40 በመቶ ያለው ሲሆን ወደ 60 ሚሊዮን ለሚሆኑ ሰዎች የስራ ዕድል ፈጥሮአል፡፡ በተመሳሳይ
መልኩ በጃፓን ዘርፉ 83.3 በመቶ በማኑፋክቸሪንግ ድርሻ ያለው ሲሆን 40 ሚሊዮን ለሚሆኑ ሰዎች
የስራ ዕድል ፈጥሮአል፡፡ እንደዚሁም በቻይና 20.85 ሚሊዮን ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
የሚገኙ ሲሆን 128.2 ሚሊዮን ሰራተኞችን የቀጠሩና ከ2,720 ቢሊዮን ዶላር በላይ ለኢኮኖሚው
አስተዋፅኦ ያደርጋሉ፡፡ በያመቱም 9.12 በመቶ በአማካኝ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
ቁጥር ይጨምራል (Daniel and Mood: 1998).
22
በአፍሪካ ሀገራትም እንደዚሁ በኬኒያ 1.3 ሚሊዮን የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞቸች ለ2.4
ሚሊዮን ኬኒያዊያን ስራ የፈጠሩ ሲሆን ይህም ከአጠቃላይ የሠራተኞች ቁጥር 15 በመቶ ፣ ከሀገሪቱ
ኢኮኖሚ ደግሞ 18 በመቶ አስተዋጽኦ አላቸው (NBS 1999)፡፡ በታንዛኒያ እንደዚሁ 1 ሚሊዮን
ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞቸች ከ20-30% የኢኮኖሚ እድገትና ከ20-30% የስራ ፈጠራ
አስተዋፅኦ ያደርጋሉ (UNCTAD 2005)፡፡ በከተሞች ስንመለከት በአክራ 70 በመቶ፣ በአዲስ አበባ
61 በመቶ ፣በዳሬሰላም 56 በመቶ በካምፖላ 46 በመቶ እና በሀረሬ 17 በመቶ ለስራ ፈጠራ ድርሻ
እንዳላቸው ተመልክቷል (Tegegne and Helmsing 2005)፡፡

የታይላንድ ILO ዳይሬክተር ሆኑት ሚስተር ዷን ሰማቪያ የተባሉት ጸሐፊ እንደገለፁት በአንድ ሀገር
የኢኮኖሚና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ከሌሎች የድህነት ቅነሳና የስራ ዕድል ፈጠራ ስትራቴጂዎች
መካከል የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ከፍተኛውን ስፍራ እንደሚያዝ ይናገራሉ፡፡
ፀሐፊው እንደሚሉት በታይላንድ የአገሪቱ የተባበሩት መንግስት የድህነት ቅነሳና ልማት ፕሮጀክቶች
ኤጀንሲን በመጥቀስ ድህነትን ከመሰረቱ ለመቅረፍ ዜጎች በጥ/አ/ኢ ልማት ማደራጀትና ወደ ስራ
ማሰማራት በሁለቱም ፎርማልና ኢንፎርማል ሴክተር ውጤቱ አመርቂ መሆኑን በጥናት የተረጋገጠ
መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ ለዚህም እንደምክንያት ሲገለፁ በዘርፉ የሚሳተፉ የህብረተሰብ ክፍሎች
የሚፈጠርላቸው የስራ መስክ በመጠንም ሆነ መጥራት ለመምረጥና በርካታ ዜጎችን ካላቸው ዝንባሌ
ጋር የሚጣጣሙ የሙያ መስክ ላይ በመሳተፍ ወደ ስኬት ጎዳና የሚወስዳቸውን እጣ ፈንታ ለመወሰን
ሰፊ ዕድል እንደሚያገኙ ያረጋግጣሉ፡፡ ሲያጠቃልሉም በዚህ ጥቃቅንና አነስተኛ ልማት ፕሮጀክት
የሚከናወኑ ስራዎች በስራ ፈጠራና በድህነት ቅነሳ ላይ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ አበክረው
ያስረዳሉ (Project ILO/UNDP THA 1991:3)፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥም ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የበርካታ ህ ብረተ ሰ ብ መተዳደሪያ


እንደሆኑ መረጃዎች ያሳያሉ (GTP 2010፣ 2015)፡፡የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን በ2013 እንደ
አውሮፓውያን አቆጣጠር ባስጠናው ጥናት እንደተመለከተው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
ከ70 በመቶ በላይ ለከተማ የስራ ዕድል አስተዋፅኦ ያደርጋሉ፡፡ በሀገራችን ኢትዮጵያ ከ1 ሚሊየን
በላይ የሚሆ ኑ ጥ/አ/ኢ የሚገኙ ሲሆን ከነዚህ መካከል 99.4% ጥቃቅን ናቸው፡፡ መረጃው
እንደሚገልፀው ዘርፉ በርካታ ችግሮች ያሉበት ቢሆንም መንግስት በየጊዜው ለማሻሻል ጥረት
እያደረገ መሆኑን ይገልፃል፡፡

2.4.2 የማሌዥያ መልካም ተሞክሮ

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በማሌዥያ ኢኮኖሚ ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ ነው፡፡ የማሌዥያ
መንግስት ከ1970 እንደ አዉሮፓ አቆጣጠር ጀምሮ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልዩ
ትኩረት መስጠቱን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ በተለይ በ1ኛው፣ በ2ኛው እና በ3ኛው የኢንዱስትሪ

23
ማስተር ፕላን የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ከማኑፋክቸሪንግ ጋር ለማስተሳሰር መንግስት
ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንደተንቀሳቀሰ ያሳያል (MITI, 2005)፡፡ እንደ SMIDEC(2002)ጥቃቅንና
አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የማኑፋክቸሪንግ ሴክተሩን 93.8 በመቶ የሚይዙ ሲሆን 38.9 በመቶ
ለሚሆኑ የሀገሪቱ ዜጎች የስራ እድል ፈጥረዋል፡፡ሴክተሩ በአብዛኛው የተሰማራው በማኑፋክቸሪንግ
ዘርፍሲሆን በዋናነት በጨርቃ ጨርቅ፣ የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ምርቶች፣ የእንጨትሥራዎች፣
የምግብና መጠጥ ዝግጅትና የግንባታ ግብዓት ምርቶች የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

የተለያዩ ሀገራት ተሞክሮ እንደሚያሳየው ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚሰጡ ድጋፎች


የኢንተርፕራይዞችን የዕድገት ደረጃ መሰረት ያደረጉ ናቸው፡፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
የዕድገት ደረጃ መሰረት ያደረገ ድጋፍ መስጠት 2 ገጽታዎች ሲኖሩት አንደኛው ኢንተርፕራየዞቹ
ከጥቃቅንና አነስተኛ ወደ መካከለኛ የሚሸጋገሩበትን የዕድገት ደረጃዎች የሚያመለክት
ሲሆን፤ሁለተኛው ደግሞ በአሉበት ደረጃ ማለትም በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝነት
ተጠናክረውና ተወዳዳሪ ሆነው ለመቀጠል የሚያልፉበትን ሂደት የሚያመላክት ነው፡፡

በማሊዢያ ኢንተርፕራይዞች በአራት የተከፈለ የዕድገት ደረጃዎች ያሏቸው ሲሆን እነዚህም


የምስረታ፣ የዕድገት፣ የመስፋፋትና የማብቃት ናቸው፡፡ የድጋፍ አሰጣጡ የዕድገት ደረጃውን
መሰረት ያደረገ ነው፡፡ በማሊዢያ በምስረታ ደረጃ የሚሰጡ ድጋፎች የሰለጠነ የሰው ሀይል
እንዲያገኙ ፣ጥሬ ዕቃ እንዲያገኙ፤መሠረተ ልማት እንዲሟላላቸውና የገበያ እውቀት እንዲያገኙ
ማድረግ ነው፡፡ በእድገት ደረጃ ደግሞ የብቃት ማረጋገጫ መስጠት፣ የስታንዳርድ፣ የገበያ ልማት፣
የታክስ ተጠቃሚነትና የቴክኒክ ድጋፍ ይሰጣቸዋል፡፡ በመስፋፋት ደረጃ ለሚገኙ ኢንተርፕራይዞች
የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ፣ የስራ አመራር ብቃት ግንባታ፣ የንግድ ምልክት፣ የሽያጭ አውታሮች፣
የኢንፎርሚሽንና ኮሚኒኬሽን፣ የቬንቸር ካፒታልና የአውት ሰርቪሲንግ ይደረግላቸዋል፡፡
በመጨረሻው ማለትም በማብቃት ደረጃ ለደረሱ ኢንተርፕራይዞች የዲዛይን አቅም ግንባታ ፣ የንግድ
ምልክት ትውውቅ፣ የኢንዱስትሪ ማስፋፊያና የውጭ ኢንቨስትመንት ድጋፍ ይደረግላቸዋል
(SMIDEC 2002)፡፡

2.4.3 የጃፓን መልካም ተሞክሮ

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በጃፓንም ተመሳሳይነት አለው፡፡ የዕድገት ደረጃዎች በሶስት


ይከፈላሉ፡፡ እነሱም የምስረታ፣ የማጠናከሪያና የማብቂያ ደረጃ ናቸው፡፡በምስረታ የዕድገት ደረጃ
የሚሰጡ ድጋፎች አዲስ ጀማሪዎች የሚገጥማቸውን እንቅፋቶችና ማነቆዎችን ለመሻገር የሚያስችል
የተሟላ ድጋፍ ነው፡፡ ይህም ድጋፍ 80 በመቶ የመነሻ ካፒታል፣ ብድርና መመለሻ ጊዜ እስከ 10
አመት፤ የተቀናጀ ድጋፍ በሀገር አቀፍ፤በክልልና በከተሞች መስጠትና የስልጠናና የም ክ ር
አገልግሎትን ያካትታል፡፡ በማጠናከሪያ የእድገት ደረጃ የሚሰጡ ድጋፎች የስራ አመራር ብቃትን

24
ለማጎልበት የሚሰጡ ሙያዊ ድጋፎች ናቸው፡፡ በማብቃት እድገት ደረጃ ሚሰጡት ድጋፎች
በማንኛውም ጊዜ ከሚገጥማቸው ስጋት ለመጠበቅ የሚያስችሉ ድጋፎች ናቸው፡፡

2.4.4 የታንዛንያ ተሞክሮ


የታንዛንያ ተሞክሮ እንደሚያሳየው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በስራ ፈጠራ እና ድህነት
ቅነሳ ከፍተኛ ድርሻ አላቸው፡፡ የታንዛንያ መንግስት ለጥቃቅንና አነስተኛ የሰጠው ትርጓሜ
በመስፈርቶች ከኢትዮጵያ ጋር የሚመሳሰል ሲሆን ጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ማለት እስከ 4 ሰዎች
ቀጥሮ የሚያሰራና የጠቅላላ ካፒታሉ መጠን ከ 5 ሚሊየን የታንዛንያ ሽልንግ ያልበለጠ
ኢንተርፕራይዝ ነው፡፡ አነስተኛ ኢንተርፕረይዝ ማለት ደግሞ ከ5-49 ሰዎች ቀጥሮ የሚያሰማራና
የጠቅላላ ካፒታሉ መጠን ከ 5-200 ሚሊየን ያልበለጠ ኢንተርፕራይዝ ነው፡፡

የታንዛንያ መንግስት ከ1966 እ ንደ አውሮፓ አቆጣጠር ጀምሮ ለጥቃቅንና አነስተኛ


ኢንተርፕራይዞች ልዩ ትኩረት መስጠቱን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞችን ከማኑፋክቸሪንግ ጋር ለማስተሳሰር መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ተንቀሳቅሷል ፡፡

በአሁኑ ሰአት የታንዛንያ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ፖሊሲ ትኩረት ያደረገው
አዳዲስ ኢንተርፕራይዞችን ማቋቋም እና በስራ ላይ ያሉት ደግሞ ተወዳዳሪ እንዲሆኑና የተሻለ ገቢ
እንዲያገኙ ብሎም የሀገሪቱ የኢኮኖሚ መሰረት አንዲሆኑ እየጣረ ይገኛል(MIT, 2013). የፖሊሲ
አቅጣጫው 7 ጉዳዮች ላይ ያተኩራል፡፡

1. የህግ ማእቀፉን ማሻሻል


2. የተሸለ መሰረተ ልማት ማቅረብ
3. የስራ ፈጠራ ባህልን ማሻሻል
4. የተሸለ የፋይናንስ አገልግሎት መስጠት
5. ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ደጋፍ የሚሰጡ ባለድርሻ አካላትን አቅም ማጎልበት
6. የገጠር ኢንዱስትሪን ማስፋፋት
7. ስርአተ ፆታ እና ሌሎች ክሮስ ከቲንግ ኢሹስ ትረት መስጠት

ይህ ስትራቴጅ በተመረጡ ጉዳዮች ላይ የተኮረ አቅጣጫ የተከተለ ነው፡፡ ይህን ስትራቴጅ


ለማስፈጸም የንግድና ኢንዳስትሪ ሚኒስቴር መሪነቱን የወሰደ ሲሆን የታንዛንያ ናሽናል ቢዝነስ
ካውንስል እና ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ፎረም ትልቅ ሚና ይጫወታሉ፡፡ በንግድና
ኢንዳስትሪ ሚኒስቴር ስር ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ሴክሽን የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ልማት ፖሊሲን ለማስፈጸም እንደ ፎካል ፖይንት የተቋቋመ ሲሆን አላማውም
የፖሊሲውን አፈጻጸም መደገፍ፣ ማደራጀት ፣ መቆጣጠር እና መገምገም ነው፡፡ በተጨማሪም
የአነስተኛ ኢንዳስትሪ ልማት ኦርጋናይዜሽን አንዱ በመንግስት ሴክተሩን ለማገዝ የተቋቋመ ተቋም
25
ነው፡፡በታንዛንያ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ፖሊሲ ሴቶች ልዩ ትኩረት
ተሰጥቷቸዋል፡፡ የድጋፍ አሰጣጥ ሂደቱም ሴቶችን በየደጃው ተጠካሚ የሚያደርግ ነው፡፡ በዘርፉ
የተለያዩ ችግሮች ያሉ ቢሆንም ከኢትዮጵያ አንጻር ኢታይ የትኩረት አቅጣጫን በመለየትና ሴቶችን
የዘርፉ ተጠቃሚ ለማድረግ የሄዱት ርቀት እንደ መልካም ተሞክሮ የሚወሰድ ነው፡፡

2.4.5 ከሌሎችመልካምተሞክሮልምድየተገኘትምህርት
በኢትዮጵያ ከውጭ ተሞክሮ አንፃር ሲታይ ድጋፎች በየእድገት ደረጃቸው ታይቶ የሚሰጥ
አልነበረም፡፡ አሁንም የሚሰጠው ድጋፍ የጅምላ ድጋፍ ሲሆን የተሰጠውን ድጋፍ መሰረት ያደረገ
ግምገማና በድጋፍ ያገኙትን ለውጥ መረጃ የመያዝ ልምድና የመቀመር ሁኔታ አልነበረም ወይም
አይታይም፡፡በተሻሻለው የጥቃቅንና አነስተኛ ኤጀንሲ ባወጣው የድጋፍ ማዕቀፍ ግን ተሞክሮዎችን
እና ያለባቸውን ችግሮች ከግምት ውስጥበማስገባት የድጋፍ ማዕቀፉን በዕድገት ደረጃው ለማድረግ
አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ በዚህ መሠረት የእድገት ደረጃዎችም በሶስት ተከፍለዋል፡፡ እነርሱም
የምስረታ፣ታዳጊ እና የማብቃት ደረጃ ተብለው ተለይተዋል፡፡ የእነዚህ የእድገት ደረጃዎች አይነት
መሠረታዊ አላማ ኢንተርፕራይዞችን ቀጣይነት ያለው ዕድገት እንዲያስመዘግቡና ይህንን መሰረት
ያደረገ የተቀናጀ ግልፅ መስፈርትና የድጋፍ ማዕቀፎችን ለማዘጋጀት ጠቃሚ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡
ሆኖም ግን ፖሊሲው በአግባቡ ተግባር ላይ አልዋለም፡፡ አንዱ ምክንያት የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ያሉበትን ሁኔታ አለማወቅ ነው፡፡ይህም ጥናት ያስፈለገዉ በአዲስ አበባ ከተማ
አስተዳደር የሚገኙ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ሁኔታ፤የዕድገት ደረጃቸውን፣ያለባቸውን
ችግርና የሚያስፈልጋቸውን ድጋፍ ለማወቅነው (የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ኤጄንሲ:
2005)፡፡

ከላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረዉ የሌሎች አገሮች ተሞክሮ የሚያሳየው የተቋማትን የእድገት ደረጃ
መሰረት ያደረገ ድጋፍ ለመስጠት የእድገት ደረጃ ስታንዳርድ ማዉጣትና በስታንዳርዱ መሰረት
ደረጃቸዉን መለየት፤ ለእያንዳንዱ የእድገት ደረጃ የሚጣጣም ድጋፍ ማድረግ፤ እንዲሁም ዉጤቱን
መገምገምና መቀመር በመሆኑ ይህ ተሞክሮ ለኢትዮጵያም ጠቃሚ ነዉ፡፡

2.5 ጥቃቅንናአነስተኛኢንተርፕራይዞችልማትበኢትዮጵያ

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ሥራ ዕ ድል በመፍጠር፤ ለቴክኖሎጂ ሽግግር


አስተዋዕጾ በማድረግና የገበያ ትስስር በማሳለጥ ለድህነት ቅነሳና ለአገርቱ አጠቃላይ ልማትና ዕድገት
ያላቸዉን ፋይዳበመገንዘብ መንግስት ከማደራጀት አንስቶ የድጋፍ ማዕቀፎችን በማዘጋጀትና
አፈጻጸሙን ክትትል በማድረግ የራሱን ሚና ለመወጣት እያደረገ ያለዉ ጥረት ዋጋ ሊሰጠዉ የሚገባ
ነዉ፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ስትራቴጂ አቅጣጫ፤ ፖሊሲና
አፈጻጸም እንደሚከተለዉ ቀርቧል፡፡

26
2.5.1 የፖሊሲናስትራቴጂአቅጣጫ

በኢትዮጵያ ታሪክ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ረዘም ያለ ዕድሜ ያስቆጠሩ ቢሆንም ልዩ


ትኩረት ተሰጥቷቸው መደራጀት የጀመሩት አሁን በስልጣን ላይ ባለው መንግስት ከ1996 ዓ.ም
ጀምሮ ነው፡፡ ይህም የጥቃቅን ፋይናንስ ተቋማት ማቋቋሚያ አዋጅ (Proclamation No. 40/1996)
በ1996 ከወጣ በኋላ ማለት ነው፡፡ ይህን ተከትሎ በ1997 ደግሞ በፌዴራልና በክልል ደረጃ
የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ስትራቴጂ ወጣ፡፡ እንዲሁም እነሱን የሚያደራጁ ኤጀንሲዎች
በሚኒስቴሮች ምክር ቤት (Regulation No. 33/1998) ተቋቋሙ፡፡ እነዚህን ተቋማት ከሴክተሩ
ለማስተሳሰርና የተሻለ ድጋፍ ለመስጠት ይቻል ዘንድ ደግሞ እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ2011
ስትራቴጂው እንደገና ተከለሶ በአሁኑ ሰዓት በመስራት ላይ ይገኛል፡፡

በዚህ ስትራቴጂ ላይ የጥቃቅንና ኢንተርፕራይዞች ኢንተርፕራይዞች ዘርፍ የልማት ራዕይ


‹‹ለኢንዱስትሪው ልማት አስተማማኝና ሰፊ መሰረት ያለው ተወዳዳሪ ዘርፍ ተፈጥሮ ማየት›› ነው፡፡
ዋና ዋና አላማዎች በሶስት የሚከፈሉ ሲሆን ቀዳሚው ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር የህብረተሰቡን ገቢ
ለማሻሻል እና ድህነትን ለመቀነስ እንዲሁም ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል እንዲፈጠር ለማድረግ፤
ተወዳዳሪና ቀጣይነት ያለው ፈጣን ልማት የሚያስመዘግብና ለኢንዱስትሪው ልማት አስተማማኝ
መሰረት የሚጥል ዘርፍ እንዲሆን ለማስቻልና የመጨረሻው ደግሞ በከተሞች ሰፊ መሰረት ያለው
ልማታዊ ባለሀብት በመፍጠር የዘርፉን ልማት ለማስፋፋት ነው (የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ኤጄንሲ (እ.አ.አ 2011)፡፡

በሀገሪቱ የኢንዱስትሪ ልማት ዕቅዱ ውስጥ ወሳኝ ቦታ የተሰጠው ለጥቃቅንና አነስተኛ ተቋሞች ነው፡፡
ይህ የሆነው በቅድሚያ በከተሞች የስራ ዕድል የሚፈጥረው ዋናው ዘርፍ ይሄው በመሆኑና የኢኮኖሚ
ልማት እቅዱም አንድ መሰረታዊ ማጠንጠኛ የሥራ ዕድል መፍጠር በመሆኑ ነው፡፡ አነስተኛና
ጥቃቅን ተቋሞች ዋነኛ የስራ ዕድል ፈጣሪ ሀይሎች መሆናቸውን ደግሞ የተለያዩ ሀገራትን ተሞክሮ
አሳይቶናል፡፡

2.5.2 የጥቃቅንናአነስተኛኢንተርፕራይዞችየፖሊሲ ማዕቀፎች

የጥቃቅንና አነስተኛ ልማት ፖሊሲ ከአጭር ጊዜ አኳያ ካፒታልን ቆጥቦ ፈጣን ልማት ለማረጋገጥ
ሲሆን ከመካከለኛና ረጅም ጊዜ አኳያ የካፒታልና ቴክኖሎጂ አቅምን በማጠናከር የማያቋርጥ ፈጣን
እድገት ማስመዝገብ ነው፡፡ ፖሊሲው የሚያተኩረውበሀገራችን ውስጥ ያለውን የስራ አጥነት ችግር
በመቅረፍና የወደፊት ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ሰፊ መሰረት ያለው ልማታዊ ባለሀብት
በመፍጠርና የወጣቱን የስራ ክህሎትና የስራ ፈጣሪነት አመለካከት በማጎልበት የቁጠባ ባህሉን
ለማሻሻልና የዕድገት ደረጃን መሰረት ያደረገ ድጋፍ በመስጠት ላይ ነው፡፡ የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ልማት ኤጀንሲ በ1997 ዓ.ም በመጀመሪያውና በ2000 ዓ.ም በሁለተኛው እትሙ
27
ዝርዝር ፖሊሲዎችን አውጥቷል፡፡ እነሱም የሰው ሀብት ልማትና የቴክኖሎጂ እድገት፤የፋይናንስ
ምንጭና አቅርቦት፣የመስሪያና የመሸጫ ቦታ አቅርቦት ፣የገበያ ልማት፣ የአንድ ማዕከል አገልግሎት
፣የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት፣ የድጋፍ ሰጭ አካላትን ማጠናከርና ምቹ የስራ አካባቢን
መፍጠር ናቸው፡፡እነዚህ ፖሊሲዎች ተሻሽለው የወጡት ከባለፈው ተሞክሮ የነበሩ ድክመቶችና
መሰረታዊ ችግሮችን ከግምት ውስጥ በማስገባት ነው፡፡

2.5.3 የፖሊሲና ስትራቴጂ አፈጻጸም

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የእድገት ደረጃቸው በሚፈልገው ደረጃ የመንግስት ድጋፎችና


አገልግሎቶች በጣም አስፈላጊ ናቸው፡፡ እነዚህም ድጋፎችና አገልግሎቶች የተቀመጡ ፖሊሲዎችን
መሰረት ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ በፖሊሲው ላይ ከተቀመጡ ድጋፎች መከካከል የማምረቻና
የመሸጫ ክላስተር ማዕከላትን የማመቻቸት/ማዘጋጀት፣ ጥቅም ላይ ማዋልና ማስተዳደር፣የብድርና
ቁጠባ አገልግሎቶች ማመቻቸት፣ የብድር አመላለስና የቁጠባ አሰባሰብን ማጠናከር፣ መረጃዎችን
የማሰባሰብ፣ የማጠናከርና ለተጠቃሚዎች የመስጠት፣ ኢንተርፕራይዞችን በመንግስት የልማት
ፕሮጀክቶች በማሳተፍ የገበያ ተጠቃሚ ማድረግ፤ ኤግዚብሽኖችንና ባዛሮችን በማስተባበር ምርትና
አገልግሎቶችን በማስተዋወቅ መደገፍ፣ በኢንተርፕራይዞች መካከል የልምድ ልውውጥና የገበያ
ትስስር ማመቻቸት፣ ኢንተርፕራይዞች የጋራ መገልገያዎች፣ የጋራ ግዥና የገበያ ማፈላለግ ስራዎችን
እዲሰሩ መደገፍ ናቸው፡፡

የዘርፉ መሰረታዊ ችግሮች ተብለው በብዙ ጥናታዊ ጽሁፎች የተመለከቱት የፋይናንስ አቅርቦት
ችግሮች፣ የማምረቻና የመሸጫ ማዕከላት እጥረት፣ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እጥረት፤ የተሰማራ
የሰው ሀይል እጥረት፤ የገበያ የግብይት አቅርቦት ችግር፤ የተቀናጀና የአንድ ማዕከል አገልግሎት
እጥረት፤ የአመለካከት ችግር፤ ሙስናና ብልሹ አሰራሮች እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ችግሮች
ናቸው፡፡

ሆኖም ግን የዘርፉ መሰረታዊ ችግሮች ተብለው በብዙ ጥናታዊ ጽሁፎች የተመለከቱት የፋይናንስ
አቅርቦት ችግሮች፣ የማምረቻና የመሸጫ ማዕከላት እጥረት፣ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እጥረት፤
የሰለጠነ የሰው ሀይል እጥረት፤ የገበያና የግብይት አቅርቦት ችግር፤ የተቀናጀና የአንድ ማዕከል
አገልግሎት እጥረት፤ የአመለካከት ችግር፤ ሙስናና ብልሹ አሰራሮች እንዲሁም የመልካም
አስተዳደር ችግሮች ናቸው፡፡

2.6 ማጠቃለያ

በተዛማጅ ጽሑፎች ዳሰሳ እንደታየው የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በአደጉትም ሆነ በማደግ


ላይ ባሉ ሀገራት በስራ ፈጠራ፣ በድህነት ቅነሳ እንዲሁም ቀጣይነት ባለው ልማት ያላቸው ድርሻ

28
ከፍተኛ ነው፡፡ የተለያዩ ሀገራት ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚሰጡት ድጋፍ የእድገት
ደረጃቸውን ማእከል ያደረገ ነው፡፡

በሀገራችን ኢትዮጵያም የስራ ዕ ድል ለመፍጠር እና ድህነትን ለመቀነስ ብሎም ሴክተሩን


የኢንዱስትሪ ዕድገት መሰረት ለማድረግ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተሰጠው ትኩረት
አበረታች ነው፡፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራቴጂና ፖሊሲ በአገር አቀፍ
ደረጃ ተቀርጾ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ሆኖም ግን የድጋፍ አሰጣጡ የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞችን የእድገት ደረጃ ማእከል ያደረገ አልነበረም፡፡ ስለሆነም የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ያሉበትን የእድገት ደረጃ በጥናት ለይቶ የእድገት ደረጃቸውን ማእከል ያደረገ
ድጋፍ አሰጣጥ ስትራቴጂ መተግበር ወሳኝነት አለው፡፡

29
ምዕራፍ ሦስት፡ የጥናቱ ዘዴ
3.1 መግቢያ

ይህ ጥናት መረጃዎችን አግባብነት ካላቸዉ ምንጮች በመሰብሰብ፤ በማደራጀትና በመተንተን


የተካሄደ በመሆኑ ለፖሊሲና ለተለያዩ ዉሳኔዎች ግብዓት ሆኖ ሊያገለግል ይችላል፡፡ የመረጃ ጥራትና
ይህንን መረጃ ለመሰብሰብ ሥራ ላይ የዋለዉ የመረጃ አሰባሰብ ዘዴ የጥናት ዉጤቱን ለተፈለገዉ
ዓላማ ለመጠቀም በሚያስችል መልኩ የተቃኘ ነው፡፡ በወቅቱ የነበረዉን መረጃ መሠረት በማድረግ
የጥናቱን የመረጃ ወሰን የተደረገው በ10 ክፍለ ከተሞች ከሚገኙ 117ወረዳዎችና በወረዳዎቹ ሥር
የሚገኙትን ኢንተርፕራይዞች በሙሉ አምስቱንም የእድገት ተኮር ዘርፎች በማካተት ነው፡፡በዚሁ
መሠረት መረጃዉ የተሰበሰበዉ በ10 ክፍለ ከተሞችና 117 ወረዳዎች ውስጥ ከሚገኙ ከ29016
ኢንተርፕራይዞች ነው፡፡

ይህ ጥናት ሳይንሳዊ ይዘቱ እንደተጠበቀ ለአገርና ለከተማ አስተዳደሩ ለወደፊት የፖሊሲ አቅጣጫ
በሚጠቅም መልኩ የተቃኘ ነው፡፡ ለዚህም ዋናው ምክንያት የጥናቱ መረጃ የተሰበሰበው በአዲስ አበባ
ከተማ ካሉት እንተርፕራይዞች ላይ ብቻ በመሆኑ በጥናት ውጤቱ ላይ ተመሥርቶ የእነዚህኑ
ኢንተርፕራይዞች የወደፊት አፈጻጸምና ውጤታማነት ማሻሸል በማስፈለጉ ነው፡፡ ስለዚህ የዚህ ጥናት
ዘዴ ሳይንሳዊውን መሠረት ሳይለቅ የጥናት ዓላማዉንና ጥናቱ የተደረገበትን ቦታ እንዲሁም ሶሺዮ-
ኦኮኖሚዉን ግምት ውስጥ ያስገባ ነው፡፡

3.2 የጥናቱ አቀራረብ

በዚህ ጥናት ከ1996 ዓ/ም ጀምሮ የተደራጁ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በአምስት የዕድገት
ተኮር ዘርፎች ተካተዉ ታይተዋል፡፡ መረጃ ሰጪዎች ሀሳባቸዉንም ሆነ በአሀዝ የሚገልጹትን መረጃ
ለማሰባሰብ እንዲያመች መረጃዉን የሚሞሉበት መጠይቅ ተዘጋጅቶ ከተገቢዉ ክትትል ጋር
እንዲሞሉ ተደርጓል፡፡ የጥናቱ ዘዴ በዋናነት ከኢንተርፕራይዞቹ በጥናቱ ዓላማና ጥያቄዎች ላይ
በመመርኮዝ ሀሳባዊና አሀዛዊ መረጃ በማሰባሰብ፤ በማደራጀትና በመተንተን ከመረጃ ት ንተ ና
የሚገኘዉን ውጤት የጽሑፍ ሪፖርት በማዘጋጀት ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ላይ የተመሠረተ ነዉ፡፡

3.3 የጥናቱ ተሳታፊዎች

ጥናቱ የታለመለት ዓላማ ለማሳካት ሲባል በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚገኙትን ከ1996 ዓ.ም
እ ስከ መጋቢት 2008 ዓ.ም ድረስ የተደራጁትን 29016 ኢንተርፕራይዞች በሙሉ በጥናቱ
አካትቷል፡፡ የጥናቱ መጠይቅ የተሞላዉ በየኢንተርፕራይዙ ኃላፊ ወይም የሥራ አስኪያጅ ሆኖ
እነርሱ ባልተገኙበት ሁኔታ ግን ከኢንተርፕራይዞቹ አባላት ጋር በመነጋገር የተሰበሰበ ነው፡፡

30
በዚህ ረገድ የከሰሙ ኢንተርፕራይዞችን በሚመለከት አንቀሳቃሾችን ወይንም ሥራ አስኪያጆችን
ማግኘት አስቸጋሪ ሆኖ በተገኘበት ሁኔታ አደራጅ መስሪያ ቤቱ መረጃ እንዲሞላ የተደረገበትም
አጋጣሚ ነበር፡፡ መረጃዉን ለማግኘት ቀደም ሲል በነበረዉ አድራሻቸዉ በተለይም በስልክ
ቁጥራቸዉ፤ እስካሉበት ድረስ በአካል በመሄድ መጠይቁን ለመሙላት ጥረት ተደርጓል፡፡ ይህ ሁሉ
ተሞክሮ ባልተቻለበት ሁኔታ ግን ስለእነርሱ በትክክል ያውቃሉ ተብለዉ የሚታሰቡ የጥቃቅንና
አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ጽ/ቤት ሀላፊዎችንና ባለሙያዎችን በመጠየቅ መጠይቁ ተሞልቷል፡፡
ከሁለተኛ ምንጭ የተገኘዉንም መረጃ እንደ ማካካሻ በመጠቀም ሥራ ላይ እንዲዉል ተደርጓል፡፡

3.4 የጥናቱ መረጃ ምንጭና አሰባሰብ ዘዴ

የጥናቱ መረጃ በዋናነት ከመጀመሪያ ም ንጮ ች የተሰበሰበ ሲ ሆን እንደአስፈላጊነቱ ሁለተኛ


ምንጮችም ጥቅም ላይ ዉለዋል፡፡ የመጀመሪያ ምንጮች መረጃ በመሠረታዊነት ከኢንተርፕራይዞቹ
ከራሳቸዉ የተሰበሰበ ሲሆን በአካል በመገኘት የተደረጉ እይታዎችንና ምልከታዎችንም ይጨምራል፡፡
የመጀመሪያ ምንጭ መረጃ የተሰበሰበዉ መጠይቅ በማዘጋጃት፤ የጥናቱን ዓላማ መጠይቁን የሚሞሉ፡
የሚያስሞሉና የሚያስተባብሩ አካላት በአግባቡ እንዲረዱ ገለጻ በመስጠት ነዉ፡፡ ከዚህ ሌላ ቁልፍ
ለሆኑ መረጃ ሰጪዎች ቃለ-መጠይቅ ተዘጋጅቶ ጥያቄ በማቅረብ መረጃ ተሰብስቧል፡፡ መጠይቅ
በመሙላት መረጃ የሰጡትን አካላት በሚመለከት መረጃ ሰጪዎቹ የመጠይቁን አሞላል፡ ጥያቄዎቹን
… ወዘተ በትክክል መረዳታቸዉን ለማረጋገጥና መጠይቁ በአግባቡ ተሞልቶ የሚፈለገዉን መረጃ
የማቅረብ ብቃት እንዳለዉ ለመፈተሸና የማስተካከያ እ ርም ጃ ለመውሰድ እንዲያስችል ታስቦ
አስቀድመዉ በናሙናነት በተመረጡ ክፍለ ከተሞች፤ ወረዳዎችና ኢንተርፕራይዞች አመሳካሪ ወይም
ቅድመ-መረጃ መጠይቆች እንዲሞሉ ተደርጓል፡፡ በማመሳከሪያ መጠይቆች አሞላል ላይ የታዩት
ክፍተቶች መነሻ በማድረግ ማሰተካከያ ከተደረገ በኋለ መጠይቆቹ ተሰራጭተዉ መረጃ የማሰባሰብ
ሥራዎች ተሰርተዋል፡፡ ስለመረጃዎቹ ትክክለኛነትም መረጃ ሰጪዎቹ በጥያቄዎቹ መጨራሻ ላይ
በፊርማቸዉ እንዲያረጋግጡ ተደርጓል፡፡ ኢንተርፕራይዞቹ በአካል ስለመኖራቸዉ፤ አሁን ያሉበት
አካላዊ ሁኔታ፤ የማምረቻና መሸጫ ቦታዎች፤ ወዘተ ስለመኖራቸዉ በምልከታ ቅኝት ተደርጓል::
የሁለተኛ ምንጮች የተለያዩ ተዛማጅ ጽሑፎች፤ የከተማ አስተዳደሩን ሪፖርት፤ ከጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች አደራጅ መ/ቤትና ሌሎችን አግባብነት ያላቸዉን ምንጮች በመጠቀም መረጃ
የማሰባሰብ ሥራ ተከናዉኗል፡፡

3.5 የመረጃ አደረጃጀትና ትንተና

መረጃዉ በመስክ በሚሰበሰብበት ወቅት እንደአስፈላጊነቱ የመረጃዉን ትክክለኛነት የማረጋገጥና


ጉድለት በሚታይበት ጊዜ እስከ ምንጩ በመሄድ የማጥራት ሥራ ተሠርቷል፡፡ ከመስክ የተሰበሰበዉ
መረጃ በስስፕሮ ሶፍተዌር ከዚያም ወደ ”Excel” እና “SPSS” ተቀይሮ ትንተናዉ ወደሚሠራበት

31
ኮምፕዉተር እንዲገባ ተደርጓል፡፡ ጥሬ ሐቁ በአግባቡ ከተደራጀ በኋላ ሳይንሳዊ ስልቶችን የተለያዩ
ሠንጠራዦች፤ ግራፎችና ስታቲካዊ ዘዴዎች ሥራ ላይ በማዋል የመተንተኑ ተግባር ተከናውኗል፡፡

3.6 ማጠቃለያ

ከላይ እንደተገለጸዉ ጥናቱ በዋናነት የተፈለገዉ በቀጣይ ኢንተርፕራይዞቹ አደረጃጀታቸውን፤


አሠራራቸውንና አፈጻጸማቸውን አሻሽለውና አሳልጠው ወደተፈለገው ግብ እንዲደርሱና በአገሪቱ
ዕድገት ጉዞ ላይ የራሳቸው አሻራ እንዲያሳርፉ ለማስቻል ነው፡፡ የከተማ አስተደደሩ የጥናቱን ዉጤት
መነሻ በማድረግ እንደአስፈላጊነቱ የፖሊሲ፤ ስትራቴጂና አፈጻጸም ለውጥ ሊያደርግ ይችላል፡፡ ጥናቱ
ይህንን ከፍተኛ ዓላማ እንዲያሳካ ብቃት እንዲኖረውና ለጥናቱ በሥራ ላይ የዋለዉ መረጃም
በትክክለኛና አሳማኝ በሆነ መንገድ አግባብነት ካለዉ የመረጃ ምንጭ እንዲመጣ ጥረት ተደርጓል፡፡
በዚህ መልክ የተሰበሰበውን መረጃ በተገቢው መንገድ መንገድ በማደራጀትና በመተንተን ይህ
ሪፖርት ተዘጋጅቷል፡፡ ከዚህ በመነሳት የጥናቱ ውጤቱን እንደተገቢነቱ ማስተካከያ በማድረግ በጥናቱ
ውስጥ እንደ ጉድለት የተመለከቱ ጉዳዮችን በማረምና የወደፊት የትኩረት አቅጣጫ ሥር የተዘረዘሩ
ጉዳዮችን በማጤን ለቀጣይ አፈጻጸምን ማሻሻል ይገባል፡፡

32
ምዕራፍ አራት፡ የመረጃ ትንተናና ግኝቶች
4.1 መግቢያ

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ዘርፍ የሃገራችን ቁልፍ ችግር የሆነውን ድህነትና
ኋላቀርነት ለመቀነስ ዋነኛ መፍትሄ መሆኑ ታምኖበታል፡፡ በዚህም መሰረት የዘርፉን ልማት ለማገዝ
በሚያስችል መልኩ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራቴጂ እና ፖሊሲ ተቀርጾ
በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ በዚህም በርካታ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሮላቸው ሃብት አፍርተው
ተጠቃሚ ከመሆን አልፈው ለሌሎች የስራ ዕድል መፍጠር ችለዋል፡፡

በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት እየተመዘገበ ያለውን ውጤት በላቀ ፍጥነትና


ተከታታይነት ባለው መልኩ ለማገዝ ይቻል ዘንድ በአዲስ አበባ ከተማ የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞችን በሚመለከት ይህ ጥናት ተደርጓል፡፡ በዚህም ኢንተርፕራይዞች በእንቅስቃሴ ላይ
መኖር ያለመኖራችውን፣ አሁን ያሉበትን ደረጃ፣ ከመንግሥት እየተደረገላቸው ያለውን የድጋፍ
ማዕቀፍ እና የሥራ ዕድል ከመፍጠር አንጻር የወጣቶችና የሴቶች ተሳትፎ ምን ያህል እንደሆነ
ለማወቅ ሁሉ ን ም ኢንተርፕራይዞች ያካተተ መረጃ ተሰብስቧል፡፡ የመረጃው ትንታኔም
እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

4.2 የጥናቱ ተሳታፊዎች ሁኔታ

አብዛኛዉን ጊዜ የኢንተርፕራይዞች ስራ አስኪያጅ/ሰብሳቢ/ የሚሆኑት የኢንተርፕራይዞች ባለቤቶች


ናቸዉ፡፡ ስለዚህ ኢንተርፕራይዞችን ወክለዉ ለጥናቱ መረጀ በመስጠት የተሳተፉት እነዚህ ሥራ
አስኪያጆች/ባለቤቶች ናቸዉ፡፡ የሥራ አስኪያጆችን/ባለቤቶችን ማንነትና ያላቸዉን አቅም ማወቅ
ደግሞ የተቋሙን ዕድገትና ዉጤታማነት ይወስነዋል፡፡ ስለሆነም የጥናቱ ተሳታፊዎች (የሥራ
አስኪያጆች/ባለቤቶች) ጾታ፣ ዕድሜ እና የትምህርት ደረጃ እንደሚከተለዉ ቀርቧል፡፡

4.2.1 ጾታ

ሠንጠረዥ3፡ የስራአስኪያጅ/ሰብሳቢ/ባለቤቶች ጾታ
የኢንተርፕራይዙ አይነት ድ ምር

ጾታ ጥቃቅን አነስተኛ

ወንድ 13870 (60%) 1909 (83%) 15779 (62.12%)

ሴት 9142 (40%) 393 (17%) 9535 (37.54%)

ድ ምር 23012 2302 25314

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

33
በሰንጠረዥ 3 እንደተመለከተዉ አብዛኛዎቹ (62.12%) የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
የሚመሩት ወይም የተያዙት በወንዶቹ ሲሆን የሴቶቹ ድርሻ 37.54% ነዉ፡፡ ሆ ኖም ግን
በኢንተርፕራይዞች አይነት ሲታይ ሴቶች ከአነስተኛ(17%) ይልቅ በጥቃቅን(40%) የተሻለ ድርሻ
አላቸዉ፡፡ መረጃዉ እንደሚያመለክተዉ የሴቶች ተወዳዳሪነት እንዲያድግ የድጋፍ ማዕቀፉ ለሴቶች
ልዩ ድጋፍ መስጠት እንደሚገባ የጥናቱ ዉጤት ያሳያል፡፡

ከአራዳ ክ/ከተማ በቃለ መጠይቅ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ከዚህ በፊት ዝቅተኛ የነበረው
የሴቶችና ወጣቶች ተሳትፎ በአሁኑ ሰዓት በተሸለ መልኩ ለውጥ እያመጣ መሆኑን በመግለፅ
በተለይም ከስደት ተመላሽ ሴቶች ከምንጊዜውም በተሻለ መልኩ በስራው ላይ በመሳተፋቸው
የሴቶችን ቁጥር ከዙህ በፊት ከነበረው ከፍ እነዲል አደርጎታል፤ በአሁኑ ሰዓትም ከ50% በላይ
መሆኑን ተጠያቂዋ አስረድተዋል፡፡ ነገር ግን በሰንጠረዥ 3 እንደተመለከተው የሴቶቹ ድርሻ
37.54% ነዉ፡፡ ምንም እንኳ አሁን ያለው የሴቶች ተሳትፎ ከነበረው የተሻለ ቢሆንም ሴቶች
እንደወንዶቹ ከቤት ወጣ ብለው የመስራቱ ነገር ክፈተት አለ፡፡ በመሆኑም በኢንተርፕራይዝነትም
ቢሆን የተደራጁት ሴቶች አብዛኛው በራሳቸው ቤት መስራት ይፈልጋሉ፡፡ ይህ ደግሞ ያሉበት
የመስሪያ ቦታ የንግድ ህጉ በሚፈቅድው መሰረት ስላልሆነ አሁንም ስራውን በከፍተኛ ንቅናቄ
ለመምራት አልተቻለም፡፡ ይህ ሁኔታ የግንዛቤ ለውጥ ተፈጥሮ ካልተቀየረ ለወደፊትም ቢሆን
ለኢነተርፕራይዞቹ እደገት እንቅፋት ሆኖ መቀጠሉ አይቀርም በማለት የስራ ክፍሉ አመረር
ገልፀዋል፡፡

4.2.2 ዕድሜ

የስራ አስኪያጅ/ሰብሳቢ/ባለቤት እድሜ (%)


40.00
35.00
30.00
25.00
20.00
15.00
10.00
5.00
0.00
<= 20 21-30 31-40 41-50 51-60 >60

ግራፍ 1፡የጥናቱ ተሳታፊዎች ዕድሜ


ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

34
በግራፉ እንደሚታየዉ አብዛኛዎቹ (72.3%) የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ከ
21-40 ባለዉ የዕድሜ ክልል ዉስጥ የሚገኙ ናቸዉ፡፡የጥናት ዉጤቱ የሚያሳየዉ የወጣቶችን ይበልጥ
ተጠቃሚነት በመሆኑ ይህ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነው፡፡ ምክንያቱም ይህ የዕድሜ
ክልል አምራችና ዉጤታማ የተባለዉን የህብረተሰብ ክፍል የሚያካትት በመሆኑና የጥቃቅንና
አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን የወደፊት እድገት እና የድጋፍ አይነት የሚወስን በመሆኑ ነው፡፡

4.2.3 የትምህርት ደረጃ

ሠንጠረዥ4፡ የስራአስኪያጅ/ሰብሳቢ/ ባለቤቶች የትምህርት ደረጃ


ጾታ
የትምህርት ደረጃ
ወንድ ሴት ድ ምር
አንደኛደረጃ (1-8) 4334 2805 7139 (28.67%)
ሁለተኛደረጃ(9-10) 3407 1316 4723 (18.97%)
መሰናዶ (11-12) 1998 1618 3616 (14.52%)
ሰርተፊኬት (10+1) 350 128 478 (1.92%)
ኮሌጅዲፕሎማ (10+2) 914 361 1275 (5.12%)
ኮሌጅዲፕሎማ (10+3) 1002 306 1308 (5.25%)
ኮሌጅዲፕሎማ (12+2) 362 154 516 2.07%)
ኮሌጅዲፕሎማ (12+3) 1066 359 1425 (5.72%)
ዲግሪ 1442 391 1833 (7.36%)
ማስርስ 235 76 311 (1.25%)
ዶክትሬት 25 19 44 (0.18%)
ያልተማረ 492 1738 2231 (8.96%)
ድ ምር 15627 9271 24899
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በሰንጠረዥ 4 እንደተመለከተዉ በጾታ ሲታይ ወንዶቹ ከሴቶቹ የተሻለ የትምህርትደረጃ አላቸዉ፡፡
ነገር ግን እንደአጠቃላይ ሲታይ አብዛኛዎቹ ከመሰናዶ አላለፉም (62.16%) ወይም መደበኛ
ትምህርት አልተማሩም (8.96%). ወደ ዩኒቨርሲቲ ወይም TVET ገብተዉ ሰርተፍኬት፣ ዲግሪ እና
ከዚያ በላይ ያላቸዉ ከ 29 % አይበልጡም፡፡ ይህ የጥናት ዉጤት የሚያሳየዉ ምንም እንኳን
በመዲናችን ብዙ የተማረ ሥራ አጥ ወጣት ያለ ቢሆንም በአመለካከት ላይ በቂ ሥራ ስላልተሰራ
የጥቃቅንና አነስተኛ ሥራ የዝቅተኛ ትምህርት ያላቸዉ ተደርጎ የተወሰደ መሆኑ ግምት ዉስጥ ገብቶ
የግንዛቤ ሥራ ሊሰራ ይገባል፡፡

35
4.3 የጥቃቅንናአነስተኛኢንተርፕራይዞችሁኔታ

4.3.1 የኢንተርፕራይዞቹአመሰራረትእናአዝማሚያ (ትሬንድ)

ጥቃቅን

ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አይነት


የጥ/አ/ኢንተርፕራይዞች ብዛት

አነስተኛ
የጥ/አ/ኢንተርፕራይዞች የተመሰረቱበት ዘመን

ግራፍ 2፡ የጥቃቅንናአነስተኛየተመሰረቱበትጊዜ
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በግራፉ እንደተመለከተዉ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በመንግስት መደራጀት ከጀመሩበት
ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ ሲታይ በአነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የቁጥር ዕድገት ለዉጥ ላይ ጎላ ያለ ልዩነት
አይታይም፡፡ ነገር ግን በጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ላይ መሰረታዊ ለዉጥ ታይቷል፡፡ በ1997 ዓ.ም
ከፍተኛ መቀነስ ያሳየ ሲሆን አስከ 2003 ዓ.ም የቁጥር ዕድገቱ መጠነኛ ነበር፡፡ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ
እስከ 2007 ዓ.ም ከፍተኛ የቁጥር ዕድገት ታይቷል፡፡ ይህ የሚያሳየዉ ምንም እንኳን ጥቃቅን
ኢንተርፕራይዞች በየጊዜዉ የሚቋቋሙ ቢሆንም ወደ አነስተኛ ኢንተርፕራይዝነት አለማደጋቸዉን
ነዉ፡፡ ስለዚህ መንግስት አስፈላጊዉን ትኩረትሊሰጥ ይገባል፡፡

36
4.3.2 የኢንተርፕራይዞቹ አይነት

በጥናቱ የተካተቱት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ሲሆኑ በክፍለ ከተማ እንደሚከተለው


ተመልክቷል፡፡

ሠንጠረዥ5፡ የኢንተርፕራይዞች አይነት በክፍለ ከተማ


የኢንተርፕራይዙአይነት
ክ/ከተማ ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
አራዳ 2445 107 2552 (10.05%)
አዲስከተማ 1547 128 1675 (6.59%)
ቦሌ 2159 180 2339 (9.21%)
የካ 3408 463 3871 (15.24%)
አቃቂቃሊቲ 1512 279 1791 (7.05%)
ንፋስስልክ 2341 407 2748 (10.82%)
ጉለሌ 2458 178 2636 (10.38%)
ቂርቆስ 2606 115 2721 (10.71%)
ልደታ 1587 124 1711 (6.74%)
ኮልፌቀራንዮ 3025 330 3355 (13.21%)
ድ ምር 23088 (90.9%) 2311 (9.1%) 25399 (100%)
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በጥናቱ ከተካተቱት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች መካከል 90.9%ቱ ጥቃቅን
ኢንተርፕራይዞች ሲሆኑ 9.1% ደግሞአነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ናቸዉ፡፡ ይህም የሚያመለክተው
አብዘኛዎቹ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ወደሚቀጥለዉ የዕድገት ደረጃ ከመሸጋገር ይልቅ
በያሉበት የመቆየት ዝንባሌ ማሳየታቸዉን በመሆኑና ይህም የኢንዱስትሪ ልማቱን እንቅስቃሴ
የሚያቀጭጭ በመሆኑ እርምት ሊደረግ ይገባል፡፡ ስርጭቱን በሚመለከት በክ/ከተማ ሲታይ የካ
ክ/ከተማ ከሁለቱም የዕድገት ደረጃ የተሻለ ድርሻ አለዉ፡፡ የካ ክ/ከተማን ተከትሎ ኮልፌ ቀራንዮ
የተሻለ ስርጭት ያለዉ ቢሆንም በአነስተኛ ተቋማት ግን ንፋስ ስልክ የተሻለ ነዉ፡፡ አራዳ፣ ጉለሌ፣
ቂርቆስ፣ ቦሌ ተመሳሳይ የሚባል ስርጭት ሲኖራቸዉ በአቃቂ ቃሊቲ እና ልደታ ያነሰ ስርጭት
ታይቷል፡፡

4.3.3 የኢንተርፕራይዞች ህጋዊ አደረጃጀት

ሠንጠረዥ6፡ የኢንተርፕራይዞች ህጋዊ አደረጃጀት


ሕጋዊ አደረጃጀት ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
በግል 12789 (55.39%) 832 (36%) 13621 (53.63%)
በህብረት ሽርክና 5466 (23.67%) 1031 (44.62%) 6497 (25.58%)
ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር 504 (2.18%) 295 (12.77%) 799 (3.15%)
በአክሲዮን ማህበር 10 (0.04%) 5 (0.22%) 15 (0.06%)
በህብረት ሥራ ማህበር 4319 (6.40%) 148 (6.4%) 4467 (17.59%)
ጠ/ድምር 23088 2311 25399
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
37
በሰንጠረዥ 6 እንደተመለከተዉ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ህጋዊ አደረጃጀት ትልቁን
ድርሻ (53.63%) የሚይዙት በግል የተደራጁት ናቸዉ፡፡ በህብረት ሽርክና (25.58%) እና በህብረት
ሥራ ማህበር (17.59%) የተደራጁት ሁለተኛና ሦስተኛ ደረጃን ይይዛሉ፡፡

ከአራዳ ክ/ከተማ በቃለ መጠይቅ እንደተገለጸው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በክፍለ


ከተማው ከ1996 ዓም ጀምሮ ህጋዊ ሆነው የተደራጁ ቢሆንም አብዛኛዎቹ ኢንተርፕራይዞች
የተደራጁበት አግባብ በህብረት ስራ ነበረ፡፡ ይህ አሰራር የራሱ የሆን አሉታዊ ጎን ሰለነበረው
አብዛኛዎቹ ኢንተርፕራይዞች በ2006 ዓ.ም የንግድ ህጉ በሚያዘው መሰረት እንደገና ወደ ህብረት
ሽርክና ማህበር እንዲዞሩ ተደረገ፡፡ ኢንተርፕራይዞች በዚህ አሰራር የተካተቱ መሆኑንና ይህም
ኢንተርፕራይዞቹን በግል አስከመደራጀት ድረስ የሚያስችል መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

4.3.4 ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩበት የስራ ዘርፍ

ሠንጠረዥ7፡ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ ዋና የስራ ዘርፎች


የስራ ዘርፍ ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
ማኑፋክቸሪንግ 4863 (21.06%) 1233 (53.35%) 6096 (24%)
ኮንስትራክሽን 6324 (27.39%) 738 (31.93%) 7062 (27.8%)
አገልግሎት 3859 (16.71%) 155 (6.73%) 4014 (15.8%)
ከተማግብርና 343 (1.49%) 59 (2.55%) 402 (1.58%)
ንግድ 7699 (33.35%) 126 (5.45%) 7825 (30.81%)
ጠ/ድምር 23088 2311 25399
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በሰንጠረዥ 7 እንደተመለከተዉ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከተሰማሩባቸዉ ዋና ዋና
የስራ ዘርፎች እንዳጠቃላይ ሲታይ ትልቁን ድርሻ (30.81%) የሚይዘዉ የንግድ የስራ ዘርፍ ነዉ፡፡
ኮንስትራክሽን (27.8%) እና ማኑፋክቸሪንግ (24%) ሁለተኛና ሦስተኛ ደረጃን ይይዛሉ፡፡አገልግሎት
(15.8%) እና ከተማ ግብርና (1.58%) አራተኛና አምስተኛ ደረጃ ላይ ናቸዉ፡፡

በኢንተርፕራይዝ አይነት ሲታይ ግን በጥቃቅን የተደራጁት ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ


ዘርፎች ከላይ ለአጠቃላይ ኢንተርፕራይዞች የተቀመጠዉን ደረጃ የያዘ ነዉ፡፡ በአነስተኛ ከተደራጁት
ግን የመጀመሪያዉን ደረጃ የሚይዘዉ ማኑፋክቸሪንግ (53.35%) ሲሆን ኮንስትራክሽን (31.93%) እና
አገልግሎት(6.73%) ሁለተኛና ሦስተኛ ደረጃን ይይዛሉ፡፡

በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራቴጂ እና ፖሊሲ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ትልቁን


ድርሻ እንዲይዝ ቢፈለግም በተግባር ግን መሪነቱን የንግድ ዘርፍ የያዘ በመሆኑ ይህንን ሁኔታ
ለመቀየር መሰራት አለበት፡፡ ሆኖም ግን በአነስተኛ ከተደራጁት ማኑፋክቸሪንግ መሪነቱን መያዙ
የኢንዳስትሪዉን ሴክተር ትራንስፎርም ከማድረግ አንጻር ተስፋ ሰጭ ነዉ፡፡ የከተማ ግብርና
በሁለቱም ዘርፍ መበረታታት አለበት፡፡ ዝርዝሩ እንደሚከተለዉ ቀርቧል፡፡
38
ሠንጠረዥ8፡ የኢንተርፕራይዞች ስርጭት በክፍለ ከተማና በየተሰማሩበት የስራ ዘርፎች
ዋናዘርፎች
ተቁ ክፍለከተማ
ማኑፋክቸርንግ ኮንስቴራክሽን ንግድ አገልግሎት የከተማግብርናድምር
ቁጥር % ቁጥር % ቁጥር % ቁጥር % ቁጥር % ቁጥር %
1 አራዳ 407 6.7 245 3.5 1402 17.9 480 12.0 18 4.5 2552 10.0
2 አዲስከተማ 468 7.7 152 2.2 699 8.9 343 8.5 13 3.2 1675 6.6
3 ቦሌ 514 8.4 980 13.9 420 5.4 370 9.2 55 13.7 2339 9.2
4 የካ 674 11.1 1750 24.8 839 10.7 527 13.1 81 20.1 3871 15.2
5 አቃቂቃሊቲ 483 7.9 584 8.3 393 5.0 282 7.0 49 12.2 1791 7.1
6 ንፋስስልክ 757 12.4 1353 19.2 293 3.7 294 7.3 51 12.7 2748 10.8
7 ጉለሌ 732 12.0 313 4.4 1194 15.3 363 9.0 34 8.5 2636 10.4
8 ቂርቆስ 437 7.2 336 4.8 1279 16.3 653 16.3 16 4.0 2721 10.7
9 ልደታ 296 4.9 639 9.0 499 6.4 246 6.1 31 7.7 1711 6.7
10 ኮልፌ 1328 21.8 710 10.1 807 10.3 456 11.4 54 13.4 3355 13.2
ድ ምር 6096 100 7062 100 7825 100 4014 100 402 100 25399 100
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
የኢንተርፕራይዞቹ ስርጭት በየክፍለ ከተማ ሲታይ በተነፃፃሪ ትልቁን ድርሻ (15.2%) የያዘዉ የካ
ክፍለ ከተማ ሲሆን ኮልፌ ክፍለ ከተማ የካ ክፍለ ከተማን ቀጥሎ 13.2% ድርሻ ይዟል፡፡ ንፋስ ስልክ
10.8%፣ ቂርቆስ 10.7%፣ ጉለሌ 10. 4%፣ አረዳ 10.0%፣ እንዲሁም ቦሌ 9.2% ኢንተርፕራይዞች
ድርሻ ያላቸዉ ሲሆን አዲስ ከተማ 6.6% እና ልደታ 6.7% ድርሻ በመያዝ ዝቅተኛ
የኢንተርፕራይዞች ቁጥር የተመዘገበባቸዉ ክፍለ ከተሞች ናቸዉ፡፡ ከላይ እንደተገለጸዉ በየክፍለ
ከተማ የሚታየዉ የጥቃቂንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ስርጭት ከፍተኛ ልዩነት ይታይበታል፡፡
ለዚህም ምክንያት ይሆናል ተብሎ የሚገመተዉ ያለዉ የህዝብ ብዛት፤ የተመዘገቡ ሥራ ፈላጊዎች
ብዛት፣ ለሥራዉ የሚያስፈልገዉ ግብኣት ሥርጭት እና ሌሎች አቅምና አደረጃጀትን የሚመለከቱ
ጉዳዮች በየክፍለ ከተማዉ ልዩነት ስለሚኖራቸዉ መነሻ ምክንያቶቹን ለማወቅ በነዚህ ጉዳዮች ላይ
ተጨማሪ መረጃ በመሰብሰብ መተንተን የሚጠይቅ ነዉ፡፡

የኢንተርፕራይዞች ስርጭት በየተሰማሩበት የዕድገት ዘርፎች ሲታይ ትልቁን ድርሻ (31%) የያዘው የንግድ
ዘርፍ ሲሆን ኮንስትራክሽን፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ አገልግሎትና የከተማ ግብርና ዘርፎች ድርሻ እንደየቅደም
ተከተላቸው 28%፣ 24%፤ 16% እና 1% ድርሻ ይዘዋል፡፡ በየክፍለ ከተማ ያለው የእድገት ዘርፎች
ስርጭት ስንመለከት በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በተነፃፃሪ ከፍተኛ የኢንተርፕራይዞች ቁጥር ያስመዘገበው
ኮልፌ (21.8%) ክፍለ ከተማ ነው፡፡ በመቀጠል ንፋስ ስልክ 12.4%፣ ጉለሌ 12%፤ እንዲሁም የካ ክፍለ
ከተማ 11.1% በማስመዝገብ ተቀራራቢነት ያለው የኢንተርፕራይዞች ቁጥር ያስመዘገቡ ሲሆን ልደታ እና
አራዳ 4.9% እና 6.7% ድርሻ በመያዝ ዝቅተኛ የኢንተርፕራይዞች ቁጥር በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ
ያስመዘገቡ ከፍለ ከተሞች ናቸው፡፡ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ከፍተኛ የኢንተርፕራይዞች ቁጥር ያለው የካ
ክፍለ ከተማ (24.8%) ሲሆን ንፋስ ስልክ 19.2%፤ ቦሌ 13.9%፣ እንዲሁም ኮልፌ 10.1% ድርሻ አላቸው፡፡

39
በዚህ ዘርፍ ዝቅተኛ ድርሻ ያላቸው ክፍለ ከተሞች አዲስ ከተማ 2.2%፣ አራዳ 3.5%፣ ጉለሌ 4.4% እና
ቂርቆስ 4.8% ናቸው፡፡

በንግድ ዘርፍ ከሚንቀሳቀሱ ኢንተርፕራይዞች ትልቁን ድርሻ (17.9%) የያዘው አራዳ ክፍለ ከተማ
ሲሆን ቂርቆስ ክፍለ ከተማ (16.3%) ጉለሌ (15.3%)፣ የካ 10.7%፣ ኮልፌ 10.3% ድርሻ አላቸው፡፡
ንፋስ ስልክ፣ አቃቂ ቃሊቲ፣ ቦሌ እና ልደታ ክፍለ ከተሞች 3.7%፣5.0%፣ 5.4%፣ 6.4% ድርሻ
በቅደም ተከተል አላቸዉ፡፡ በአገልግሎት ዘርፍ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ 16.3% በመያዝ ከፍተኛው
ድርሻ ያለው ሲሆን የካ ክፍለ ከተማ በ13.1% ድርሻ በመያዝ ሁለተኛ ነው፡፡ በዘርፋ 6.1% ብቻ
በመያዝ ዝቅተኛ ድርሻ ያለው የልደታ ክፍለ ከተማ ነው፡፡ የከተማ ግብርና ዘርፍ የየካ ከፍለ ከተማ
የተሻለ ድርሻ (20.1%) ያለው ቢሆንም በዚህ ዘርፍ በአጠቃላይ በከተማው ያለው እንቅስቅሴ እጅግ
ዝቅተኛ (1%) በመሆኑ በከተማው የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥና ለከተማዋ አረንጓዴ ልማት ካለው
ፋይዳ አንጻር ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ የሚገባ ዘርፍ ነው፡፡

4.3.4.1 ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ

ሠንጠረዥ9፡ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች


ንዑስ የስራ ዘርፍ ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
ጨርቃጨርቅናስፌት 1931 152 2083 (34.21%)

ቆዳናየቆዳውጤቶች 220 37 257 (4.22%)

የምግብናመጠጥዝግጅት 721 94 815 (13.38%)

የብረታብረትናኢንጂነሪንግምርቶች 676 437 1113 (18.28%)

የእንጨትሥራዎች 569 309 878 (14.42%)

ባህላዊየዕደጥበብናጌጣጌጥሥራዎች 153 10 163 (2.68%)

አግሮፕሮሰሲንግ 17 7 24 (0.39%)

የግንባታግብዓትምርቶች 521 171 692 (11.36%)

ሌሎች የማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች 50 14 64 (1.05%)


ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በማኑፋክቸሪንግ ዘር ፍ ከተሰማሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች መካከል አብዛኛዎቹ
በጨርቃጨርቅናስፌት የተሰማሩ ሲሆን የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ምርቶች፣ የእንጨት ሥራዎች፣
የምግብና መጠጥ ዝግጅትና የግንባታ ግብዓት ምርቶች ከሁለት እስከ አምስት ደረጃ እንደቅደም
ተከተላቸዉ ይይዛሉ፡፡ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በግብርና ላይ ያተኮረ ቢሆንም በአግሮፕሮሰሲንግ የተሰማሩ
የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝች ቁጥር ግን በጣም አነስተኛ ነዉ፡፡

40
4.3.4.2 የኮንስትራክሽን ዘርፍ

ሠንጠረዥ10፡ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ የኮንስትራክሽን ዘርፎች


ንዑስ የስራ ዘርፍ ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
ሥራ ተቋራጭነት 1797 550 2347 (33.31%)
ንዑስ ሥራ ተቋራጭነት 153 18 171 (2.43%)

ባህላዊ የማዕድን ሥራዎች 14 5 19 (0.27%)

ኮብል ስቶን ሥራዎች 3981 119 4100 (58.19%)

የመሠረተ ልማት ግንባታ ንዑስ ተቋራጭነት 251 44 295 (4.19%)

የከበሩ ድንጋይ ልማት 18 1 19 (0.27%)

ሌሎች የኮንስትራክሽን ዘርፎች 93 2 95 (1.35%)


ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በኮንስትራክሽን ዘርፍ ከተሰማሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች መካከል አብዛኛዎቹ በኮብል
ስቶን ሥራዎች (58.19%)የተሰማሩ ሲሆን በሥራ ተቋራጭነት (33.31%) የተሰማሩት በሁለተኛ ደረጃ
ላይ ይገኛሉ፡፡ከሁለቱ ዉጭ ባሉ ዘርፎች የተሰማሩት ግን ቁጥራቸዉ አነስተኛ ነው፡፡

4.3.4.3 የአገልግሎትዘርፍ

ሠንጠረዥ11፡ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ የአገልግሎት ዘርፎች


ንዑስ የስራ ዘርፍ ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
የገጠርአነስተኛ ትራንስፖርትአገልግሎት 44 4 48 (1.20%)
ካፌና ሬስቶራንት 2030 80 2110 (52.88%)

የማከማቻ አገልግሎት 12 1 13 (0.33%)

የቱሪስት አገልግሎት 5 0 5 (0.13%)

የማሸጊያ አገልግሎት 18 2 20 (0.50%)

የሥራ አመራር አገልግሎት 10 0 10 (0.25%)

የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት 217 3 220 (5.51%)

የፕሮጀክት ኢንጂነሪንግ አገልግሎት 6 0 6 (0.15%)

የምርት ዲዛይንና ልማት አገልግሎት 24 2 26 (0.65%)

የግቢ ውበት፤ የጥበቃ እና ጽዳት አገልግሎት 289 7 296 (7.42%)

የጥገና አገልግሎት 235 4 239 (5.99%)

የውበት ሳሎን ሥራዎች 405 14 419 (10.50%)

የኤሌክትሮኒክስና ሶፍት ዌር ልማት 104 8 112 (2.81%)

የዲኮር ሥራ 8 1 9 (0.25%)

ኢንተርኔት ካፌ 20 0 20 (0.50%)

የጋራዥና መገጣጠም ስራዎች 26 3 29 (0.73%)

ሌሎችየአገልግሎት ዘርፎች 387 21 408 (10.23%)


ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በአገልግሎት ዘርፍ ከተሰማሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት
በካፌና ሬስቶራንት (52.88%)የተሰማሩ ናቸዉ፡፡ የውበት ሳሎን ሥራዎች፣የግቢ ውበት፤ የጥበቃ እና

41
ጽዳት አገልግሎት፣ የጥገና አገልግሎት እንዲሁም የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ንዑስ ዘርፍ ላይ
በርካታ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ተሰማርተዉ ይገኛሉ፡፡

4.3.4.4 የከተማ ግብርና ዘርፍ

ሠንጠረዥ 12፡ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ የከተማ ግብርና ዘርፎች


ንዑስ የስራ ዘርፍ ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
ዘመናዊ የእንስሳት እርባታ 155 39 194 (48.50%)

የዶሮ እርባታ 120 13 133 (33.25%)

የንብ ማንባት 8 0 8 (2.00%)

እንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ 2 0 2 (0.50%)


ዘመናዊ የደን ልማት 4 3 7 (1.75%)
አትክልትና ፍራፋሬ 39 4 43 (10.75%)
ሌሎች የከተማ ግብርና ዘርፎች 13 0 13 (3.25%)
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በከተማ ግብርና ዘርፍ ከተሰማሩ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች መካከል አብዛኛዎቹ
በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ (48.50%) እና የዶሮ እርባታ ላይ የተሰማሩ ናቸዉ፡፡ አትክልትና
ፍራፍሬ ላይም 10.75% ተሰማርተዋል፡፡

4.3.4.5 የንግድ ዘርፍ

ሠንጠረዥ 13፡ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩባቸዉ የንግድ ዘርፎች


ንዑስ የስራ ዘርፍ ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
የሀገር ውስጥ ምርቶች ጅምላ ሽያጭ 226 17 243 (3.09%)
የሀገር ውስጥ ምርቶች ችርቻሮ ንግድ 7238 106 7344 (93.27%)
የጥሬ ዕቃ አቅርቦት 78 9 87 (1.10%)
ሌሎች የንግድ ዘርፎች 200 0 200 (2.54%)
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በንግድ ንዑስ የስራ ዘርፍ ከተሰማሩ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝች መካከል ከ 93% በላይ
በሀገር ውስጥ ምርቶች ችርቻሮ ንግድ ላይ የተሰማሩ ናቸዉ፡፡

4.4 የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ዕድገትና ስርጭት

የጥቃቂንና አነስተኛ ተቋማት በሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ላይ የሚኖራቸዉ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ


ለዘርፉ ልማት ትኩረት በመስጠት መንግስት የጥቃቂንና አነስተኛ ኢንተረፕራይዞች ልማት
ስትራተጂ መንደፉ ይታወቃል፡፡ ከዚህ አንጻር በአዲስ አበባ ከተማ ፈጣንና ቀጣይነት ያለውን
ልማት ለማረጋገጥ፤ ድኅነትን ለመቀነስና የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል በተለይም በከተማዉ ሥር ሰድዶ
የቆየውን ሥራ አጥነትን ለማስወገድ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት በተደረገው
ሁሉአቀፍ ድጋፍ ሰፊ የስራ ዕድል በመፍጠርና ዘርፉ በኢንዱስትሪ ልማቱ ውስጥ የሚጠበቅበትን
ሚና ለመጫወት የሚያስችሉ ሁኔታዎችን የማመቻቸት ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡
42
የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዋናው ትኩረት የሥራ ዕድል መፍጠርና ድህነትን መቀነስ
አስፈላጊነት እንደተጠበቀ ሆኖ በአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ላይ የተመሰረተ ማኑፋክቸሪንግ
ማስፋፋት እና ኢንዱስትሪያሊስት ባለሀብቶችን በብዛትና በጥራት ማፍራት ነው፡፡ ይህንን ግብ ተግባራዊ
ለማድረግ የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች በልማት ውስጥ ካላቸው ከፍተኛ ሚና አንጻር
ፈርጀ ብዙ ውጤት በሚያስመዘግቡ የእድገት ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ ለመረባረብ አቅጣጫ
ተቀምጧል፡፡ በዚሁ መሠረት ከ1996 ዓ/ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ በተደረገዉ እንቅስቀሴ በተለየዩ
ዘርፎች ኢንተርፕራይዞቹ ያስመዘገቡት የእድገት ደረጃ በሚከተለዉ ስዕላዊ መግለጫተመልክቷል፡፡
የኢንተርፕራይዞችን የደረጃ ሽግግር በተመለከተ 3311(13%) ኢንተርፕራይዞች ከጥቃቅን ጀማሪ ወደ
ተለያዩ የዕድገት ደረጃዎች ተሸጋግረዋል፡፡ ከታች በስዕላዊ መግለጫ በግልፅ እንደሚታየዉ በተግባር ላይ
ካሉ 25399 ኢንተርፕራይዞች መካካል በጀማሪ የዕድገት ደረጃ ያሉት 22088 (87%) ሲሆኑ 2044(8%)
በታዳጊ፤ 598 (2.4%) ወደመካከለኛ ኢንዱስትሪ ለመሸጋገር እየበቁ ያሉ ሲሆን የሽግግር ሂደቱን በብቃት
አሟልተዉ ወደመካከለኛ ኢንዱስትሪ የተሸጋገሩ 669 (2.6%) አንቀሳቃሾች ናቸዉ፡፡

በማኑፋክቸርንግ ዘርፍ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች በድምር ከ24% በላይ አይደሉም፡፡ ደረጃ


ዕድገታቸውም ያን ያህል አመርቂ አይደለም፡፡ በ12 አመት ዉስጥ በዘርፉ ወደ መካከለኛ ደረጃ
የተሸጋገሩ ኢንተርፕራዞች 10.4% ብቻ ናቸዉ፡፡የሀገራችን ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ መጠንና
ውጤታማነት ከፍተኛ እ ም ርታ እንዲያስመዘግብ መሠረት የሚሆነው በጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዝ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ አንቀሳቃሾች ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ
የሚያደርጉት ሽግግር ነዉ፡፡ ከዚህ አንፃር በሀገር ደረጃ የተመዘገበዉን የዘርፉን አፈፃፀም በመቃኝት
ማነፃፀር ይጠቅማል፡፡ በዚህም መሠረት በአለፋት አራት አመታት (2003 እስከ 2006 ዓ.ም)
በሀገራችን ዘርፉን ከተቀላቀሉት ኢንተርፕራዞች በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩት ከጠቅላላው
(11.7%, 11.4%, 10.4% እና 10.5%) በተከታታይ መሆኑ የሚያሳየው ወደ ዘርፉ የሚቀላቀለው
ኢንተርፕራይዝ ከጠቅላላው 10-12% ያልበለጠ መሆኑን ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በአለፋት አራት
አመታት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ
የሚያደርጉት የዕድገት/ሽግግር/ አፈጻጸም ሲታይ በሀገር ደረጃ ያለዉ በድምር ዝቅተኛ ነው፡፡
በ2003 ዓ/ም ከጠቅላላ ኢንተርፕራይዞች 0.45 በመቶ ብቻ ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝነት
የተሸጋገሩ ሲሆን በተመሳሳይ በ2004 ዓ/ም 0.57 በመቶ፣ በ2005 ዓ/ም 1.06 በመቶ፣ እንዲሁም
በ2006 ዓ/ም 2.36 በመቶ ያህሉ ተሸጋግረዋል፡፡ የዕድገት ጉዞው ከአመት አመት እየተሻሻለ የመጣ
ቢሆንም ዘርፉን ከተቀላቀሉት ቁጥር አንፃር ግን ሲታይ በጣም አነስተኛ እና የሚፈለገውን ያህል
እንዳልተጓዝን ያሳያል፡፡በሀገር አቀፍ ከተመዘገበዉ አንጻር ሲታይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
የተመዘገበዉ ወደ መካከለኛ ደረጃ የሚደረግ ዕድገት/ሽግግር/ ያን ያህል አመርቂ ባይሆንም የተሻለ
ነዉ ብሎ መዉሰድ ይቻላል፡፡

43
30000

25000

20000

15000

10000

5000

0
ማኑፋክቸሪንግ ኮንስትራክሽን አገልግሎት ከተማ ግብርና ንግድ ድምር
ጀ ማሪ 4524 6035 3765 334 7430 22088
ታዳጊ 831 603 207 59 344 2044
የበቃ 270 298 15 2 13 598
መካከለኛ 471 126 27 7 38 669
ድምር 6096 7062 4014 402 7825 25399

ግራፍ 3፡ የኢንተርፕራይዞች ዕድገት በተሰማሩበት ዋና ዋና ዘርፎች


ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በከተማ አስተዳደሩ የተመዘገበዉ አፈጻፀም በአጠቃላይ ካለው ፍላጎትና ተደራሽነት አንጻር ሲታይ
በተለይም በርካታ ኢንዱስትራሊስቶችን ለማፍራት ከተጣለው ግብ አኳያ ሲታይ እጅግ ዝቅተኛ
በመሆኑ ለተቋማቱ የተሟላ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎቶች መስጠት ልዩ ትኩረት የሚሻ
ነዉ፡፡ በተለይም ሥልጠና መስጠት ብቻ በራሱ ግብ ባለመሆኑ የሚሰጡ ስልጠናዎች የክህሎት
ክፍተት በሚገባ ተገምግሞና የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ተሰርቶባቸዉ በተለዩ ክፍተቶች በጥልቀትና
በተግባር ላይ አተኩረዉ እንዲሰጡ ማድረግና የተሰጡ ስልጠናዎች ያመጡትን ፋይዳና ለውጥ
በመገምገም ተከታታይ ሥራ መስራት የሚጠበቅ ይሆናል፡፡ ሌላው መታየት ያለበት መሰረታዊ
ስትራተጂያዊ ጉዳይ ዘርፉን የመቀላቀል ውሳኔ ለግለሰቡ /ኢንተርፕራይዙ/ ሙሉ በሙሉ የተተወ
መሆኑ ነዉ፡፡ ነገር ግን የአገልግሎቱና የንግዱ ዘርፎች ተጨማሪ ኃይል ለማሰማራት ያላቸው ዓቅም
ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠበበ መሄዱ አይቀሬ ስለሆነና ሰፊ ገበያው የሚታየው በአምራቹ ዘርፍ በመሆኑ
በአምራች ዘር ፍ ሊሰማራ የሚገባው ሀይል በጥናት እየተመለመለና ተገቢዉ ድጋፍ እ ተ ሰጠ
የሚሰማረበት የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አሰራር ሊኖር ይገባል፡፡ ስለዚህ ኢንተርፕራይዞች በየትኛው
ዘርፍ መሰማራት እንዳለባቸው ለኢንተርፕራይዞቹ ውሳኔ ብቻ መተው በአምራች ዘርፍ ለማምጣት
ያቀድነው ግብ ለማሳካት እንቅፋት ስለሚሆን ኢንተርፕራይዞችን በአምራች ዘርፍ ሊያሰማራ የሚችል
እቅድና ማበረታቻ ማዕቀፍ ለመጥናት ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

44
ልክ እንደ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ሁሉ በከተማ ግብርና ዘርፍ የተፈጠረው የስራ ዕድሎችም ከከተማዉ
ዕምቅ ሀብት አንጻር ሲታይ ያልተነካ ነው ብሎ መውሰድ ይቻላል፡፡ የከተማ ግብርና በሥራ ዕድል
ፈጠራ እና በአትክልትና ፍራፍሬ አቅርቦት በብዙ አፍሪካ ከተሞች ከፍተኛ ሚና ያለ ቢሆንም
በአዲስ አበባ በተነጻጸር ዝቅተኛ ነዉ፡፡ በአፍሪካ 40 ከመቶ ነዋሪ በግብር የሚሳተፍ ቢሆንም በአዲስ
አበባ ከተማ ከሚኖር 662728 አባዎራ ውስጥ 18 ሺህ አባዎራ ማለትም 3 ከመቶ በታች ብቻ
በከተማ ግብርና እንደሚሳተፍ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ በዚህ ዘርፍ የሚሠራዉ ሥራ በቀላሉ መፈጸም
የሚችል ሥራ መሆኑን አጽንኦት በመስጠት በከተማዉ ለዚህ ዘርፍ የሚውል በቂ መሬት በማቅረብ
ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የስራ ዕድል መፍጠሪያ ዘርፍ እንዲሆን በማድረግ የከተማውን ማህበረሰብ
የምግብ ዋስትና እና አረንጓዴነት ለማረጋገጥ የራሱ አስተዋጽኦ የሚኖረው ይሆናል፡፡

ሠንጠረዥ 14፡ የኢንተርፕራይዞች እድገት በየክፍለ ከተማ


የኢንተርፕራ የኢንተርፕራ ክፍለ ከተሞች ድምር
ይዞች አይነት ይዞች የእድገትአራዳ አዲስ ቦሌ የካ አቃቂ ንፋስ ጉለሌ ቂርቆስ ልደታ ኮልፌ
ደረጃ ከተማ ቃሊቲ ስልክ
ጀማሪ 2159 1448 1948 3178 1360 2140 2325 2415 1478 2877 21328
ታዳጊ 236 59 143 174 121 134 89 140 86 128 1310
ጥቃቂን የበቃ 30 15 39 32 16 40 14 28 12 9 235
መካከለኛ 20 25 29 24 15 27 30 23 11 11 215
ድምር 2445 1547 2159 3408 1512 2341 2458 2606 1587 3025 23088
ጀማሪ 45 49 64 183 72 112 60 33 45 97 760
ታዳጊ 22 34 54 183 94 97 46 40 58 106 734
አነሰተኛ የበቃ 22 14 29 66 37 70 46 27 14 38 363
መካከለኛ 18 31 33 31 76 128 26 15 7 89 454
ድምር 107 128 180 463 279 407 178 115 124 330 2311
ጀማሪ 2204 1497 2012 3361 1432 2252 2385 2448 1523 2974 22088
ታዳጊ 258 93 197 357 215 231 135 180 144 234 2044
ድምር የበቃ 52 29 68 98 53 110 60 55 26 47 598
መካከለኛ 38 56 62 55 91 155 56 38 18 100 669
ድምር 2552 1675 2339 3871 1791 2748 2636 2721 1711 3355 25399
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

ከላይ በሠንጠረዥ 14 እንደተመለከተዉ ከ90% በላይ ድርሻ የያዙት ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች

ናቸዉ፡፡ በአሥራ ሁለት አመት በኢንተርፕራይዞቹ የተደረገዉ የእድገት ሽግግር በተመለከተ


በአነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተመዘገበዉ እድገት በተነጻጻር የተሻለ ሲሆን አብዘኛዎቹ
የጥቃቅንኢንተርፕራይዞች ወደሚቀጥለዉ የዕድገት ደረጃ ከመሸጋገር ይልቅ በያሉበት የመቆየት
የመረጡ ይመስላል፡፡ የእድገት ሽግግሩ በየክፍለ ከተማ ሲታይ በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ በየደረጀዉ
የተደረገዉ የእድገት ሽግግር በተነፃፃሪነት የተሻለ ሆኖ ታይቷኣል፡፡ በከፍለ ከተማዉ ወደ መካከለኛ

45
የእድገት ደረጃ የተሻገሩት ኢንተርፕራይዞች 5.6% ናቸዉ፡፡ ሌሎች ከከተማዉ አማካይ(2.6%) በላይ
ወደ መካከለኛ የእድገት ደረጃ ያሻጋገሩ ክፍለ ከተሞች አቃቂ ቃሊቲ(5%)፣ አዲስ ከተማ(3.4%)፣ እና
ኮልፌ (3%) ናቸዉ፡፡ ቦሌና ጉለሌ ክፍለ ከተሞች 2.6% እና 2.1% ወደ መካከለኛ የእድገት ደረጃ
ያሻጋገሩ ሲሆን ቂርቆስ፣ የካ እና አራዳ 1.4% ተመሳሳይ የእድገት ሽግግር ያስመዘገቡ ክፍለ ከተሞች
ናቸዉ፡፡ የልደታ ክፍለ ከተማ 1.0% ኢንተርፕራይዞች ወደ መካከለኛ የእድገት ደረጃ በማሸጋገር
ዝቅተኛዉን ድርሻ ይዞ ይገኛል፡፡

በአጠቃላይ በኢንተርፕራይዞቹ የተደረገዉ የእድገት ሽግግር እጅግ ዝቅተኛና ከተደራጁት


ኢንተርፕራይዞች ቁጥር አንጻር ገና ሰፊ ስራ የሚጠይቅ ነው፡፡ በተለይም በከፍተኛ ዕድገት ደረጃ
ላይ በሚገኙት ኢንተርፕራይዞች የተደረገው የደረጃ ሽግግር አፈጻፀም ዝቅተኛ በመሆኑ ጠንካራ
ድጋፍና ክትትል የሚያስፈልገው ነው፡፡የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንትርፕራይዞች ልማት የኢንዱስትሪ
ልማትን ለማሳካት ዋነኛ መፍትሔ መሆኑንና ልማታዊ የኢንዱስትሪ ባለሀብት የሚፈጠርበት መሆኑን
የኢንዱስትሪ ልማትና የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራቴጂዎች በግልፅ
አስቀምጠውታል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ የጥቃቅን አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዘርፍ ከገቢ ማስገኘትና
ሥራ አጥነትን ችግር ከመቅረፍ በዘለለ ያለዉ ፋይዳ የተሟላ ግንዛቤ የተያዘበት አለመሆኑን ከጥናቱ
ወጤት መገንዘብ ይቻላል፡፡ በኢንተርፕራይዞቹ ዘንድ የደረጃ ሽግግር ላለማድረግ ካፒታላቸውን
ከመደበቅ አንስቶ የሚደረጉ የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከቶች መኖራቸዉን በቃለ-መጠይቅ የተገኘዉ
መረጃ ያረጋግጣል፡፡ ኢንተርፕራይዞቹን አደራጅቶ ድጋፍ እየሰጠ ያለው የመንግስት ተቋምም ቢሆን
ከመነሻው በተገቢው መረጃ ላይ የተመሰረተ ተከታታይ ድጋፍና ክትትል ከማድረግ አንጻር ክፍተት
የሚታይበት መሆኑን በጥናቱ ተረጋግጧል፡፡ ስለሆነም ዋናው ጉዳይ በኢንተርፕራይዞቹ ላይ የሚሰራ
አመለካከት የመቀየር ስራ ቢሆንም የሚደረጉ ድጋፎችና ክትትሎች በመረጃና በሳይንሳዊ ትንታኔዎች
በመታገዝ ከኢንተርፕራይዞቹ ጋር መተማመን የሚያስችል ሽግግር መፍጠር ይጠይቃል፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ መነሻ ካፒታል ከማይጠይቁ ወይም ከሌሎች የሥራ ዘርፎች ጋር ሲነጻጸር በትንሽ
ከፒታል ሊከናወኑ በሚችሉ የስራ ዘርፎች ከተደራጁት ኢንተርፕራይዞች ወደ እድገት ተኮር ዘርፎች
በተለይም ወደ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የማሸጋገር ሥራ በትኩረት ቢሠራ ተመራጭ ይሆናል፡፡

4.5 የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የድጋፍ ማዕቀፍ አፈጻጸም

ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተደራጁበትን ዓላማ ግቡን እንዲመታ ተገቢዉን የድጋፍ


አገልግሎት መስጠት አስፈላጊ ነዉ፡፡ ድጋፉ ኢንተርፕራይዞቹ ከተሰማሩበት መስክ እና የዕድገት
ደረጃ አንጻር እየተመዘነ ወደሚፈለገዉ ዉጤት ሊመራ የሚያስችል መሆን ይጠበቅበታል፡፡ ለዚህም
ሲባል የሚሰጡ የድጋፍ አገልግሎቶች የተመረጡና አፈጻጸማቸዉም እንደአስፈላጊነቱ በዉጤት ተኮር
ቅኝት የሚገመገሙ መሆን አለባቸዉ፡፡ የድጋፍ ማዕቀፍ አተገባበር በሚከተለዉ መልኩ በዝርዝር
ቀርቧል፡፡
46
4.5.1 የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የብድር/ፋይናንስ ድጋፍ አገልግሎት

የብድር ወይም የፋይናንስ ድጋፍ አገልግሎት ያገኙትንና ያላገኙትን እንዲሁም በሂደት ላይ ያሉትን
ኢንተርፕራይዞች በሚመለከት በግራፍ4 ተመልክተዋል፡፡ የብድር ድጋፍ ከማግኘት እና ካለማግኘት
ጋር ተያይዞ 25399 ኢንተርፕራይዞች ተጠይቀዉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ዉጤቱ እንደሚያሳየዉ 25
ከመቶ ያህሉ የብድር አገልግሎት እንዳገኙ ሲገልጹ አብዘኛዎቹ ማለትም 75 ከመቶ የሚጠጉቱ
አገልግሎቱን እንዳላገኙ ገልጸዋል፡፡ ይህም የብድር አገልግሎት አፈጻጸሙ ደከማ መሆኑን በግልጽ
ያመላክታል፡፡ ይህም በቀጣይ ሊስተካከሉ ከሚገቡ ጉዳዮች ዉስጥ ገብቶ በከተማ አስተዳደሩ
ማስተካከያ ሊደረግበት ይገባል፡፡ ምክንያቱም ኢንተርፕራይዞቹ ዉጤታማ የሚሆኑት ለሚያከናዉኑት
ተግባር ከፋይናንስ ጋር የተቆራኙትን ተግዳሮቶች በአግባቡ መመለስ ሲችል በመሆኑ ነዉ፡፡
በመቶኛ

አዎን አይደለም መመዘኛዎችን በሟሟላት ላይ ሌላ


የሚገኙ

የብድር/ፋይናንስ ድጋፍ አገልግሎት

ግራፍ 4፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የብድር/ፋይናንስ ድጋፍ አገልግሎት


ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
የብድር/ፋይናንስ አገልግሎቱን ያላገኙት ኢንተርፕራይዞች ለምን ብድር ማግኘት እንዳልቻሉ
ተጠይቀዉ በሰጡት ምላሽ የተለያዩ ምክንያቶችእንዳሉዋቸዉ ገልጸዋል፡፡ ምክንያቶቻቸዉንም
በመጠይቁ ከተሰጡት አማራጮች በመምረጥ መልሰዋል፡፡ ይህም በሚከተለዉ ሠንጠረዥ ቀርቧል፡፡
በድምሩ 25399 ኢንተርፕራይዞች ተጠይቀዉ ምላሽ የሰጡ ሲሆን ባለመፈለግ ምክንያት የብድር
ድጋፍ አገልግሎት ያላገኙ ኢንተርፕራይዞች በርካታ መሆናቸዉን ለመረዳት ተችሏል፡፡ አንድ
በአንድ ዝርዝሩን ብንመለከት በጠቅላላ ከተጠየቁትና ምላሽ ከሰጡት 25399 ኢንተርፕራይዞች
መካከል የብድር/ፋይናንስ ድጋፍ አገልግሎት ባለመፈለግ ተጠቃሚ ያልሆኑት 41 ከመቶ ያህሉ
ናቸዉ፡፡ ከላይ በስፋት ለማየት እንደተሞከረዉ 74.5 በመቶ ኢንተርፕራይዞች የብድር አገልግሎት
ያልተጠቀሙ ከመሆናቸዉ ጋር ሲመዘን ከግማሽ በላይ ኢንተርፕራይዞች የብድር ድጋፍ አገልግሎት
የማግኘት ፍላጎት አልነበራቸዉም፡፡

47
የጥናት ዉጤቱ እንደሚያሳየዉ 41 ከመቶ ብድሩን ያላገኙት ባለመፈለግ እንደሆነ፤ 17.1 በመቶ
ደግሞ በዋስትና ችግር ምክንያት፡ 6.4 በመቶ ትርፋማ ባለመሆን፤ 5.4 በመቶ የብድር ድጋፍ
አገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ ባለመሆኑ ምክንያት የብድር/ፋይናንስ ድጋፍ አገልግሎት ማግኘት
አለመቻላቸዉን መረጃ ሰጥተዋል፡፡ በቂ ከፕታል ስላለን አልፈለግንም ያሉ ደግሞ 1.7 በመቶ
ያህሎቹ ናቸዉ፡፡ ቁጥራቸዉ በጣም ጥቂት የሚባሉ እንተርፕራይዞች የአበዳሪ ተቋማት በቂ ፋይናንስ
ማቅረብ አለመቻላቸዉን፤ የብድር ድጋፍ አገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋ አለመሆን እንዲሁም
የአባላትን አለመስማማት ላለመበደራቸዉ እ ንደ ምክንያት አቅርበዋል፡፡ ከ2 በመቶ በታች
ኢንተርፕራይዞች በቂ ከፕታል አለን ባሉበት ሁኔታ ለምን 41 በመቶ የብድር/ፋይናንስ አገልግሎት
ማግኘት እንዳልፈለጉ ምክንያታቸውን የአለመጠየቅ ውስንነት ታይቷል፡፡ በዚህ ምክንያት ለምን
የብድር አገልግሎት እንዳልፈለጉ ለማወቅ አልተቻለም፡፡ ሆኖም ችግሩ የሚያመላክተው በብድር
አስፈላጊነት፤ ጠቃሜታ፤ አጠቃቀም እና አመላለስ ላይ በቂ የግንዛቤ ሥራ አለመሠራቱን ነዉ፡፡
ስለዚህ በቀጣይ የግንዛቤ ማዳበሪያ ሥልጠናዎችን ትኩረት ሰጥቶ ተግባራዊ ማድረግ ተገቢ እንደሆነ
መገንዘብ ጠቃሚ ነው (ሠንጠረዥ 15)፡፡

ሠንጠረዥ15፡ ኢንተርፕራይዞች ብድር ላለማግኘታቸዉ የሰጡአቸዉ የተለያዩ ምክንያቶች


የተሰጠዉ ምላሽ በቁጥር በመቶኛ
ብድር አገልግሎቱን ያላገኘበት ምክንያት
አይደለም 14991 59.0
የብድር አገልግሎት ድጋፉን ባለመፈለግ አዎን 10408 41.0
ድ ምር 25399 100.0
አይደለም 21054 82.9
በብድር ዋስትና ምክንያት አዎን 4345 17.1
ድ ምር 25399 100.0
አይደለም 24962 98.3
ኢንተርፕራይዙ በቂ የሆነ ካፒታል ስላለዉ አዎን 437 1.7
ድ ምር 25399 100.0
አይደለም 24022 94.6
የብድር ድጋፍ አገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ ባለመሆኑ አዎን 1377 5.4
ድ ምር 25399 100.0
አይደለም 25092 98.8
በአበዳፊ ተቋማት በቂ ፋይናንስ አለመቅረብ አዎን 307 1.2
ድ ምር 25399 100.0
አይደለም 23773 93.6
የዘርፉ ትርፋማ አለመሆን አዎን 1626 6.4
ድ ምር 25399 100.0
አይደለም 25262 99.5
የአባላት አለመስማማት አዎን 137 .5
ድ ምር 25399 100.0
አይደለም 24924 98.1
ሌላ አዎን 475 1.9
ድ ምር 25399 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

48
የብድር አገልግሎት ድጋፍ ያገኙትን ኢንተርፕራይዞች በሚመለከት በድግግሞሽ ድጋፉን ስንት ጊዜ
እንዳገኙ ለተጠየቀዉ ጥያቄ የተሰጠዉ ምላሽ ቀጥሎ ቀርቧል፡፡ በጠቅላላ ከተጠየቁት መካከል 75.4
ከመቶ በላይ ምላሽ አልሰጡም፡፡ ብድር ካገኙት መካከል አብዘኛዎቹ ማለትም ምላሽ ከሰጡት
መካከል 98.8 ከመቶ ወይም ከጠቅላላዉ ሲሰላ 24.6 ከመቶ ያህሉ ያገኙት የብድር ድግግሞሽ ከ1-5
ጊዜ ባለዉ ዉስጥ ነዉ፡፡ ከ5 ጊዜ በላይ ብድር ያገኙት 1.2 በመቶ ብቻ መሆኑ ሲታይ ብዛቱ እዚህ
ግባ የሚባል አለመሆኑን የጥናት ዉጤቱ (ሠንጠረዥ 16) ያሳያል፡፡

ሠንጠረዥ16፡ ኢንተርፕራይዞች የብድር አገልግሎት ድግግሞሽ/ብዛት


ከጠቅላላ በመቶኛ ከመለሱት
የብድር አገልግሎት ብዛት/ድግግሞሽ በቁጥር በመቶኛ
ከ1-5 ጊዜ 6177 24.3 98.8
ከ5 ጊዜ በላይ 73 0.3 1.2
ድ ምር 6250 24.6 100.0
ሪፖርት ያላደረጉ 19149 75.4 …
ጠቅላላ ድምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

ኢንተርፕራይዞች ለመጨረሻ ጊዜ ያገኙትን የብድር መጠን በሠንጠረዥ 17 በዝርዝር


እንደተመለከተዉ 64 በመቶ (ምላሽ ከሰጡት መካከል) ለመጨረሻ ጊዜ ያገኙት ብድር ከሰላሳ ሺህ
ብር የማይበልጥ መሆኑን ከጥናቱ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ከ75 በመቶ ያህሉ ሪፖርት አለማድረጋቸዉ
በዋናነት የሚያያዘዉ ብድሩን ካለማግኘታቸዉ ጋር ነዉ፡፡ ከመለሱት መካከል 12.6 በመቶ ብቻ
ከአንድ መቶ ሺህ ብር በላይ የብድር ድጋፍ አገልግሎት ለመጨራሻ ጊዜ እንዳገኙ ለመረዳት
ተችሏል፡፡ ይህም ለብድር የሚሆን የፋይናንስ መጠን አቅርቦት ከከተማ አስተዳደሩ አጠቃላይ አቅም
ይሁን በሌላ ምክንያት መጠኑ ዝቅተኛ እንደሆነ ለማወቅ የተቻለ ሲሆን ለወደፊቱ መሻሸል እንዳለበት
የጥናት ዉጤቱ በበቂ ሁኔታ ይጠቁማል፡፡የብድር አቅርቦቱ በተለያዩ ምክንያቶች ታንቆ የተያዘ
በመሆኑ በተለይ በተጨባጭ ካለው ፍላጎት አንጻር አቅርቦቱ እዚህ ግባ የሚባል እንዳልሆነ መገንዘብ
አያዳግትም፡፡ በተለይ ለብድር አቅርቦት እጥረት መሰረታዊ መንስኤዎች በዘርፉ የተሰማሩ
ኃይሎችም ሆኑ ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ከቁጠባ ባህል ጋር በተያያዘ ያሉ አመለካከቶች
በሚፈለገው ደረጃ ሊስተካከሉ ባለመቻሉ በብድር አቅርቦት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ሊያሳድር ይችላል፡፡
ሌላው እንደ መንስኤ የሚወሰደው የተሰራጩ ብድሮችን ለታለመለት አላማ አውሎ በወቅቱ ብድሩን
ከማስመለስ አንጻር የነበሩ ተግዳሮቶች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከቅድመ ቁጠባ ጊዜና
አቅም እንዲሁም ከብድር ዋስትና ጋር በተያያዘ የነበሩ ችግሮችም ለብድር ስርጭቱ መጓተትና ማነስ
የበኩላቸዉ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል፡፡

49
ሠንጠረዥ17፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለመጨራሻ ጊዜ ያገኙት የብድር መጠን
ለመጨራሻ ጊዜ የተገኘ የብድር መጠን (በብር) በቁጥር ከጠቅላላ ከመለሱት በመቶኛ
በመቶኛ
እስከ 10000 2871 11.3 46.0
ከ10001-20000 636 2.5 10.2
ከ20001-30000 513 2.0 8.2
ከ30001-40000 202 0.8 3.2
ከ40001-50000 646 2.5 10.3
ከ50001-100000 590 2.3 9.4
ከ100001-200000 301 1.2 4.8
ከ200001-300000 236 0.9 3.8
ከ300000 በላይ 249 1.0 4.0
ድ ምር 6244 24.6 100.0
ሪፖርት ያላደረጉ 19155 75.4 ….
ጠቅላላ ድምር 25499 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

የአዲስ አበባ ከተማ ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ለመጨረሻ ጊዜ ብድር ያገኙበት ዓ/ም መቼ
እንደሆነ ተጠይቀው ከሰጡት ምላሽ ለመረዳት እንደተቻለዉና የጥናት ዉጤቱ እንደሚያመለክተዉ
(ሠንጠረዥ18 እና ግራፍ5) የብድር ድጋፍ አገልግሎት ተቋማዊ በሆነ መልኩ መስጠት የተጀመረዉ
ከ1996 ዓ/ም ጀምሮ መሆኑን ግንዛቤ ለመዉሰድ ተችሏል፡፡ የብድር ድጋፍ አገልግሎቱን ያገኙትን
ተቋማት ብዛት ስንመለከት ግን መጠኑ ትርጉም ባለዉ ደረጃ የጨመረዉ ከ2004 ዓ/ም እስከ 2008
ዓ/ም ባሉት ዓመታት መካከል እንደሆነ የጥናቱ ግኝት ያሳያል፡፡ ለመጥቀስም ያህል በእነዚህ
ዓመታት የብድር ድጋፍ አገልግሎት ያገኙት (ምላሽ ከሰጡት መካከል) 74.8 ከመቶ ናቸዉ፡፡ ይህም
ከ1996 ዓ/ም እስከ 2003 ዓ/ም ብድር ካገኙት ኢንተርፕራይዞች ብዛት ጋር ሲነጻጸር መጠኑ እጅግ
ብዙ ነዉ፡፡በተለይም 2007 ዓ/ም እና 2008 ዓ/ም እምርታ የታየበት ነዉ ለማለት ይቻላል፡፡ ለዚህም
የሚገመተዉ ምክንያት ስለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የነበረዉ አመለካከት እየተሻሻለ
መምጣቱን በዚህም ምክንያት አዲስ የሚደራጁትና አደረጃጀቱንም ተከትሎ ብድር አገልግሎት
የሚያገኙት ኢንተርፕራይዞች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የሚያሳይ ሲሆን በሌላ
በኩል ደግሞ ኢንተርፕራይዞቹ ወደሚቀጥለዉ ደረጃ እያደጉ አለመሆኑን ያሳያል፡፡ ስለዚህ
ለወደፊቱም ቢሆን የማደራጀቱ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትና ካሉበት ደረጃ ወደሚቀጥለዉ
ደረጃ ለሚደረገዉ ዕድገት በቂ ድጋፍ ሊሰጥ እንደሚገባ የጥናቱ ዉጤት ያመላክታል፡፡

50
ሠንጠረዥ18፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለመጨራሻ ጊዜ ብድር ያገኙበት ዓ/ም
ለመጨራሻ ጊዜ ብድር የተገኘበት ዓ/ም ያገኙት ብዛት ከጠቅላላ በመቶኛ ከመለሱት በመቶኛ
ከ1996 በፊት 33 0.1 0.5
1996 121 0.5 2.0
1997 373 1.5 6.0
1998 184 0.7 3.0
1999 74 0.3 1.2
2000 137 0.5 2.2
2001 133 0.9 2.1
2002 227 1.1 3.7
2003 270 2.0 4.4
2004 510 2.3 8.2
2005 590 3.6 9.5
2006 912 5.9 14.7
2007 1499 4.4 24.2
2008 1125 24.4 18.2
ድ ምር 6188 4.4 100.0
ሪፖርት ያላደረጉ 19211 24.4 ….
ጠቅላላ ድምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በመቶኛ

ኢንተርፕራይዞች ለመጨራሻ ጊዜ ብድር ያገኙበት ዓ/ም

ግራፍ5፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለመጨራሻ ጊዜ ብድር ያገኙበት ዓ/ም


ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

የብድር ድጋፍ አገልግሎት ዋነኛ ዓላማ ኢንተርፕራይዞች የተገኘዉን የብድር ድጋፍ መልካም
አጋጣም ተጠቅመዉ በፋይናስ እጥረት ምክንያት ሊከሰት የሚችለዉን ችግር እንዲቀርፉ ነዉ፡፡
ከዚያም ብድሩን በገቡት ዉል መሠረት ተመላሽ ማድረግ ደግሞ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ብድሩ ተመላሽ
የማይሆን ከሆነ ግን ተቋማቱ በዕዳ ምክንያት ከሚያጋጥማቸዉ ችግር በተጨማሪ ሌሎች ተከታይ

51
ተቋማት መበደር አይችሉም፡፡የአዲስ አበባ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በተለያየ ጊዜ
ከተበደሩት ገንዘብ ተመላሽ ያደረጉት በሠንጠረዥ 19 ተመልክቷል፡፡ የብድር ድጋፉን ካገኙት
መካከል 56 በመቶ ያህሉ እስከ 10 ሺህ ብር፤ 12 በመቶ ያህሉ ከ10 ሺህ እስከ 20 ሺህ፤ 8 በመቶ
ያህል ደግሞ ከ20 ሺህ እስከ 30 ሺህ በድምር 84 በመቶ ያህል ኢንተርፕራይዞች ከወሰዱት የብድር
ድጋፍ እስከ 30 ሺህ የሚደርስ የገንዘብ መጠን መልሰዋል፡፡ ቀደም ሲል ለማሳየት እንደተሞከረዉም
ለመጨረሻ ጊዜ እስከ 30 ሺህ ብር ድረስ የብድር አገልግሎት ድጋፍ ያገኙት 64.4 በመቶ ያህል
ናቸዉ፡፡ ከላይ በብድር ድጋፍ አመላለስ የተገኘዉ የጥናት ዉጤት የሚያሳየዉ ከ30 ሺህ ብር በላይ
ከተበደሩት ኢንተርፕራይዞች መካከል የሚፈለግባቸዉን ብድር ያልመለሱ መኖራቸዉን ነዉ፡፡ ይህም
የሚያሳየዉ የተለየ ዕቅድ በማዘጋጀት የክትትል ሥራ ተሠርቶ ብድሩን ተመላሽ ማድረግ
እንደሚያስፈልግ ነዉ፡፡

ሠንጠረዥ 19፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ተመላሽ ያደረጉት የብር መጠን

ተመላሽ የተደረገ ብድር (በብር) በቁጥር ከጠቅላላ በመቶኛ ከመለሱት በመቶኛ


እስከ 10000 3306 13.0 55.7
ከ10001-20000 705 2.8 11.9
ከ20001-30000 449 1.8 7.6
ከ30001-40000 218 0.9 3.7
ከ40001-50000 322 1.3 5.4
ከ50001-100000 438 1.7 7.4
ከ100001-200000 223 0.9 3.8
ከ200001-300000 132 0.5 2.2
ከ300000 በላይ 139 0.5 2.3
ድ ምር 5932 23.4 100.0
ሪፖርት ያላደረጉ 19467 76.6 …
ጠቅላላ ድምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


የአዲስ አበባ ከተማ ኢንተርፕራይዞች ብድር ወይም የፋይናንስ ድጋፍ በዋናነት (ብድር ካገኙት
መካከል 96.4 በመቶ) ከአዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋም ማግኘታቸዉን ገልጸዋል፡፡ ይህም በዋናነት
የሚያያዛዉ ከተሻሻለዉ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማትና ድጋፍ አሰጣጥ ስትራቴጂ
ጋር ነው፡፡ የተሻሻለው ስትራቴጂ ለኢንተርፕራይዞቹ ብድርን ጨምሮ የተለያዩ ድጋፎች መደረግ
እንዳለበት አጽንኦት ስለሚሰጥ ነው፡፡ የብድር ምንጩ ከአዲስ ብድርና ቁጠባ የመሆኑ ምክንያት
ደግሞ አዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋም የተቋቋመበት ዋነኛዉ ዓላማ የኢንተርፕራይዞችን የብድር ፍላጎት
መሙላት በመሆኑ ነው፡፡ ሁሉም ማለት በሚቻል ደረጃ የብድር አገልግሎት የተገኘዉ ከአዲስ
ብድርና ቁጠባ ተቋም የመሆኑ ምክንያት ከላይ በተገጸው አግባብ ሲሆን ከዚሁ ጋር ተያይዞ በተቋሙ
እንዲሟሉ የሚጠየቁ ቅድመ ሁኔታዎች ከሌሎች አበዳሪ ተቋማት ጋር ሲነጻጸር የተሻለና
በስትራቴጂው ማዕቀፍ መሠረት መሆኑ ነው፡፡

52
ለዚህም ነው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር ድጋፍ ያገኙት ቁጥራቸው በጣም ዝቅተኛ የሆነው፡፡
በሌላ በኩል ከተለያዩ ምንጮች የብድር አገልግሎት ማግኘታቸዉን የገለጹት 3.3 በመቶ ብቻ
ናቸዉ፡፡ ይህም በሠንጠረዥ 20 ታይቷል፡፡

ሠንጠረዥ20፡ ኢንተርፕራይዞች ብድር ወይም የፋይናንስ ድጋፍ ያገኙበት ተቋም


ብድር የተገኘበት ተቋም ቁጥር ከጠቅላላ በመቶኛ ከመለሱት በመቶኛ
አዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋም 5759 22.7 96.4
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 14 0.1 0.2
ሌላ 200 0.8 3.3
ድ ምር 5973 23.5 100.0
ሪፖርት ያላደረጉት 19426 76.5 ...
ጠቅላላ ድምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

53
ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢንተርፕራይዞቹ ስለ ብድር ድጋፍ አሰጣጥ መጠንና ወቅታዊነት ተጠይቀዉ
አስተያየታቸዉን ሰጥተዋል፡፡ ከመጠን አንጻር ከሞላ ጎደል ሁሉም አስተያየት ከመስጠት የተቆጠቡ
ይመስላል፡፡ ለመጥቀስም ያህል በጠቅላላ 25399 ኢንተርፕራይዞች ከተጠየቁት መካከል 199 (1
ከመቶ በታች) ብቻ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ምላሹ የጥቂቶች ብቻ ቢሆንም ምላሽ ከሰጡት መካከል 54
በመቶ የብድር ድጋፉ በሚፈለገዉ መጠን ነዉ ሲሉ 33 በመቶ ደግሞ በከፍል በሚፈለገዉ መጠን
መሆኑን በመግለጽ በድምር 87 በመቶ እርካታቸዉን ገልጸዋል፡፡ የብድር ድጋፍ አገልግሎት አሰጣጥ
ወቅታዊነት በተመለከተ በአንፃራዊነት ብዙዎች (7194 ከ25399 ወይም 28 ከመቶ) አስተያየታቸዉን
የሰጡ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 56 በመቶ ወቅቱን የጠበቀ ነዉ ሲሉ 23 በመቶ ደግሞ በከፍል
ወቅቱን የጠበቀ ስለመሆኑ አስተያየታቸዉን ሰጥተዋል፡፡ ሆኖም 21 ከመቶ የማያንሱ
ኢንተርፕራይዞች ወቅቱን ያልጠበቀ ነዉ ብለዉ በአገልግሎቱ አለመርካታቸዉን የገለጹ ስለሆነ
የእነዚህን ተገልጋዮች እርካታ ለማረጋገጥ ተጨማሪ የማሻሸያ ሥ ራዎ ች ታቅደዉ መከናወን
እንዳለባቸዉ የጥናት ዉጤቱ ያመላክታል (በሠንጠረዥ 21)፡፡

ሠንጠረዥ21፡ የተሰጠዉ የብድር ድጋፍ አገልግሎት በሚፈለገዉ መጠንና እና ወቅት ስለመሆኑ


የብድር ድጋፍ ኢንተርፕራይዞቹ የሰጡት ምላሽ በቁጥር ከጠቅላላ ከመለሱት
አገልግሎት በመቶኛ በመቶኛ
በሚፈለገዉ መጠን ይገኛል 105 0.42 53.57
በሚፈለገዉ መጠን በከፍል ይገኛል 64 0.25 32.65
ከመጠን አንጻር በሚፈለገዉ መጠን አይገኝም 27 0.11 13.77
ሌላ 3 0.01 1.53
ድ ምር 199 0.78 100.0
ሪፖርት ያላደረጉ 25200 99.22 …
ጠቅላላ ድምር 25399 100.0 100.0
በሚፈለገዉ ጊዜ ይገኛል 4019 15.82 55.87
በሚፈለገዉ ጊዜ በከፍል ይገኛል 1635 6.44 22.73
ከጊዜ አንጻር በሚፈለገዉ ጊዜ አይገኝም 1540 6.06 21.41
ድ ምር 7194 28.32 100.00
ሪፖርት ያላደረጉ 18205 71.68 ….
ጠቅላላ ድምር 25399 100.00 100.00

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

4.5.2 የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የገበያ ትስስር ድጋፍ

ኢንተርፕራይዞች ምርታቸዉን ለተጠቃሚዎች ማቅረብ ምርቱን ለማስቀጠል ከፍተኛ ዋጋ አለዉ፡፡


ከዚህም ሌላ የገበያ ትስስር ድጋፍ አገልግሎት ለኢንተርፕራይዞች መቀጠል አለመቀጠል ወሳኝ ሚና
ይጫወታል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ያገኙትን የገበያ ትስስር
በሚመለከት ለተጠየቁት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ሲሆን የገበያ ትስስር ዓይነትም በተጓዳኝ ቀርቧል፡፡
ከጠቅላላ መረጃ ከተሰበሰበባቸዉ 25399 ኢንተርፕራይዞች 7131 (28.1 በመቶ) የገበያ ትስስር ድጋፍ

54
አገልግሎት ማግኘታቸዉን ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል 71.9 በመቶ ኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር
ድጋፍ አገልግሎት አለማግኘታቸዉን ገልጸዋል፡፡

ይህንን ጉዳይ በሁለት ከፍሎ ማየት ያስፈልጋል፡፡ በአንድ በኩል መረዳት የሚቻለዉ
ለኢንተርፕራይዞቹ የገበያ ትስስር አለመኖር ትልቅ ተግዳሮት መሆኑን ነዉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ
ቀደም ሲል ከጥናቱ ውጠየት ለመረዳት እንደተቻለዉ እጅግ የሚበዙት ኢንተርፕራይዞች በጥቃቅን
ደረጃ የሚገኙ ከመሆናቸው ጋር በቤተሰብ አቅም የሚሠሩና የተለየ የገበያ ድጋፍ የማይፈልጉ
መሆናቸው ነው፡፡ ለምሳሌ በንግድ አገልግሎት ከተሰማሩት መካከል አነስተኛ የችርቻሮ ሱቅ ላይ
የሚሰሩትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ በሌላ በኩል አንዳንድ በከተማው የልማት እንቅስቃሴ ምክንያት
የተፈጠሩ ሥራዎችና ይህንኑ ተከትሎ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች በቀጥታ ስራዉ ስለሚሰጣቸው
ሥራዉ ባለበት ወቅት ሙሉ በሙሉ ገበያ የሚያገኙ መሆናቸው ነው፡፡ ለመጥቀስም ያህል በጌጠኛ
ድንጋይ ምንጣፎ፤ በኮንዶሚነየም ቤቶች ግንባታ እና በመሳሰሉት የተሠማሩ ኢንተርፕራይዞች የዚህ
ዓይነት ባህርይ ስላላቸዉ ሥራዉ በሚከናወንበት ወቅት ገበያ የማግኘት ዕድል አላቸው፡፡ የገበያ
ትስስር ያገኙት ኢንተፕራይዞች ቁጥር አነስተኛ የሆነው እንደነዚህ ያሉት ግምት ውስጥ ሳይገቡ
ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱም ቋሚ መስሪያ ቦታ ስለማይኖራቸዉ መረጃቸዉ እነርሱን በአካል አግኝቶ
የሚሰበሰብበት ዕድል ስለሚቀንስ ነው፡፡ ይህ እንደተጠበቀ የገበያ ትስስር አለብን ላሉት ከተማ
አስተዳደሩ በቂ አጽንኦት በመስጠት የገበያ ችግር በአጭርና ረዥም ጊዜ ዕቅድ በማዉጣት መፍታት
ይጠበቅበታል፡፡

የገበያ ትስስር ዓይነትን በሚመለከት ከጠቅላላ ኢንተርፕራይዞች መካከል 7084 (27.9 በመቶ)
ስለገበያ ትስስሩ ዓይነት ተጠይቀዉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ምላሽ ከሰጡት መካከል 94.4 በመቶ ያገኙት
የአከባቢ ገበያ ድጋፍ እንደሆነ መልስ ሰጥተዋል፡፡ የክልል ገበያ፤ የዉጭ ገበያ፤ እንዲሁም ሁሉንም
ዓይነት ገበያ ያገኙት እንደየቅድም ተከተላቸዉ 5.3 በመቶ፤ 0.2 በመቶ፤ እና 0.1 በመቶ ናቸዉ፡፡
የገበያ ትስስሩ በመሠረታዊነት የአከባቢ የሆነበት ምክንያት አብዘኛዎቹ ኢንተርፕራይዞች ጥቃቅን
ከመሆናቸዉ ጋር የሚያያዝ ነዉ፡፡ ከአደረጃጀታቸውና አሁን ካሉበት የዕድገት ደረጃ አንጻር በዋናነት
መወዳደር የሚችሉትና የሚያስፈልጋቸውም የአከባቢ ገበያ በመሆኑ ነው፡፡

55
ሠንጠረዥ22፡ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተሰጡ የገበያ ትስስር ድጋፍ አገልግሎቶቸ
ኢንተርፕራይዞቹ የሰጡት በቁጥር ከጠቅላላ ከመለሱት
የገበያ ትስስር ድጋፍ አገልግሎት ምላሽ በመቶኛ በመቶኛ
አግኝቷል 7131 28.1 28.1
የገበያ ትስስር ድጋፍ አላገኘም 18268 71.9 71.9
ድ ምር 25399 100.0 100.0
የአከባቢ 6690 26.3 94.4
የክልል 372 1.5 5.3
የገበያ ትስስር ዓይነት የዉጭ 14 0.1 0.2
ሁሉንም 8 0.0 0.1
ድ ምር 7084 27.9 100.0
ሪፖርት ያላደረጉ 18315 72.1 …
ጠቅላላ ድምር 25399 100.0 100.0
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

የገበያ ዓይነቱ የአከባቢ መሆኑ ከላይ በተጠቀሰወ ምክንያት ሆኖ በገበያ ትስስሩ የተገኘዉ የገንዘብ
መጠን ዝቅተኛ መሆኑን የጥናት ዉጤቱ አሳይቷል፡፡ የገበያ ትስስር ካገኙት መካከል 35 በመቶ
ያህል የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር ያስገኘላቸዉ የገንዘብ መጠን እስከ 10
ሺህ ብር ብቻ ነዉ፡፡

በአጠቃላይ ምላሽ ከሰጡት መካከል የገበያ ትስስሩ አንድ መቶ ሺህ እና በላይ ያስገኘላቸዉ


ብዛታቸዉ ከጠቅላላዉ 26.4 በመቶ እንደማይበልጥ የጥናት ዉጤቱ አሳይቷል፡፡ ከዚህ መረዳት
የሚቻለዉ በርካታዎቹ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በገበያ ትስስሩ ያገኙት የብር መጠን
ዝቅተኛ መሆኑን ነዉ፡፡ ይህም በተፈለገዉ ደረጃ መሻሻል እንዲያሳይ ጠቃሜታዉ ከግምት ዉስጥ
ገብቶ በትኩረት ታቅዶ አፈጻጸሙም ክትትል እየተደረገበት ሊከናወን ይገባል፡፡

ሠንጠረዥ23፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ባገኙት የገበያ ትስስር የተገኘ የብር መጠን
ተመላሽ የተደረገ ብድር (በብር) በቁጥር ከጠቅላላ በመቶኛ ከመለሱት በመቶኛ
እስከ 10000 2301 9.1 34.8
ከ10001-20000 501 2.0 7.6
ከ20001-30000 421 1.7 6.4
ከ30001-40000 378 1.5 5.7
ከ40001-50000 363 1.4 5.5
ከ50001-100000 904 3.6 13.7
ከ100001-200000 636 2.5 9.6
ከ200001-300000 279 1.1 4.2
ከ300000 በላይ 835 3.3 12.6
ድ ምር 6618 26.1 100.0
ሪፖርት ያላደረጉ 18781 73.9 …
ጠቅላላ ድምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


4.5.3 የሰዉ ኃይል ልማትና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ

የሰዉ ሀይል ልማት ትልቁና የለዉጥ ሁሉ ዋነኛ መሳሪያ እንደሆነ የሚያከራክር አይደለም፡፡ ያለሰዉ
ሀይል ልማት ሌላዉን ዓይነት ልማት ማምጣት የሚታሰብ አለመሆኑን ብዙ ተሞክሮዎች
56
አሳይተዋል፡፡ የሰዉ ሀይል ልማትና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ ሥር የተለያዩ
ጉዳዮችን ለመዳሰስ ጥረት ተደርጓል፡፡ ይህም በሚከተሉት ሁለት ሠንጠረዦች ተመልክቷል፡፡
ሠንጠረዥ 24ሀ በተለያየ መልክ በተሰጡ ሥልጠናዎች ላይ ያተኮረ ሲሆን ሠንጠረዥ 24ለ ደግሞ
ከሥልጠና ባሻገር በነበሩ የድጋፍ ዓይነቶቸ ያተኮረ ነዉ፡፡ ምንም እንኳን ሥልጠናና ከሥልጠና
ዉጭ ያሉ ድጋፎች እርስበርስ የሚመጋገቡ ቢሆንም ከሥልጠና ጋር የተያያዙ ተግባራት በዋናነት
ከሰዉ ሀይል ልማት ጋር የተቆራኙ ናቸዉ፡፡

የኢንተርፕሪነርሺፕ ሥልጠና አስመልክቶ ከጠቅላላ ተሳታፊዎች ማለትም ከ25399 ከተጠየቁት


ኢንተርፕራይዞች መካከል ግማሽ ያህል (49.7 በመቶ)የኢንተርፕሪነርሺፕ ሥልጠና ማግኘታቸዉን
ሲገልጹ ግማሽ ያህሉ (50.3 በመቶ) ደግሞ ይህንን ሥልጠና አለማግኘታቸዉን ገልጸዋል፡፡ ሁሉም
ሥልጠናዉን ቢያገኙ ተገቢ ስለሚሆን ለቀጣይ ሊሠራበት ይገባል፡፡ ሌሎች የአቅም ግንባታ
ሥልጠናዎች አፈጻጸም ሲታይ ከዚህም ዝቅ ያለ መሆኑን መረጃዉ ያሳያል፡፡ ምሳሌ የጥራትና
ምርታማነት ማሻሸያ ሥልጠና ሥራ አመራር ቴክኒክ ካይዘን ጋር የተያያዘዉ ሥልጠና 25 ከመቶ
ብቻ ሲሆን የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ደግሞ 27 በመቶ ብቻ መሆኑን የጥናት ዉጤቱ ያሳያል፡፡

የግብይት ክህሎት ማሳደጊያ ሥልጠናም ቢሆን አፈጻጸሙ 33 በመቶ ብቻ በመሆኑ ከዝቅተኞቹ


ተርታ እንዳይሰለፍ የሚያደርገዉ ነገር የለም፡፡ በአጠቃላይ መልኩ ሲታይ የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች የአቅም ግንባታ ሥልጠና አፈጻጸም ደካማ ነዉ፡፡ በዋናነት ከእንተርፕሪነርሺፕ
በስተቀር ሌሎች ሥልጠናዎች ከኢንተርፕራይዞቹ ከአንድ ሶ ስተ ኛ በላይ ማሳተፍ እንኳን
አለመቻለቸዉን ጥናቱ ያስረዳል፡፡ ይህ የሚያመላክተዉ በዚህ ተግባር ዙሪያ ለቀጣይ ብዙ ሥራ
እንደሚጠብቅ በመሆኑ በዚሁ ልክ ታቅዶና አፈጻጸሙ ክትትል እየተደረገበት ሊሠራ ይገባል፡፡

ሠንጠረዥ 24ሀ፡ የሰዉ ኃይል ልማትና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን የሥልጠና ድጋፍ አገልግሎት
የሥልጠና ድጋፍ ዓይነት ኢንተርፕራይዞቹ የሰጡት በቁጥር በመቶኛ
ምላሽ
አይደለም 12780 50.3
የኢንተርፕሪነርሺፕ አዎን 12619 49.7
ድ ምር 25399 100.0
አይደለም 13770 54.2
የንግድ ሥራ አመራር አዎን 11629 45.8
ድ ምር 25399 100.0
አይደለም 17051 67.1
የግብይት ክህሎት ማሳደጊያ አዎን 8348 32.9
ድ ምር 25399 100.0
የጥራትና ምርታማነት ማሻሸያ ሥራ አመራር አይደለም 18994 74.8
ቴክኒክ ካይዘን አዎን 6405 25.2
ድ ምር 25399 100.0
አይደለም 18548 73.0
የቴክኒክ እና ሙያ አዎን 6851 27.0
ድ ምር 25399 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


57
ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች መጎልበትና የሚፈለገዉን ዉጤት እንዲያመጡ ከሥልጠና
በተጨማሪ ሌሎች ድጋፎችም እንደሚያስፈልጉ ታዉቆ የጥቃቅንና አነስተኛ ስትራቴጂ አካል ሆነዉ
እየተሰራባቸዉ ስለመሆኑ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ በዚሁ መሰረት ከሥልጠና ባሻገር የተሰጡትን የድጋፍ
አገልግሎቶች በሠንጠረዥ 24ለ ለማሳየት ተሞክሯል፡፡ ከመረጃዉ ትንተና ለመረዳት እንደተቻለዉ
ከሥልጠና ዉጪ ከተሰጡት የድጋፍ ዓይነቶች የተሻለ አፈጻጸም የተመዘገበዉ የምክርና ድጋፍ (44
በመቶ) ሲሆን እጅግ ዝቅተኛ አፈጻጸም የታየዉ ደግሞ እንደቅደምተከተሉ የጥቃቅንና አነስተኛ ድህረ
ገጽ ዳይረክቶሬት አጠቃቀም (2 በመቶ) እና የምርጥ ተሞክሮ ቅመራና ማስተላለፍ (7.5 በመቶ)
ናቸዉ፡፡ በሌላ በኩል የተሟላ መረጃ የመስጠት (15 በመቶ)፤ የንግድ ልማት አገልግሎት (23
በመቶ)፤ እንዲሁም የሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ሠርተፊኬት (25 በመቶ) አፈጻጸም
ተመዝግቧል፡፡

ሠንጠረዥ 24ለ፡ የሰዉ ኃይል ልማትና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ከሥልጠና ውጭ የተሰጡ ድጋፍ
አገልግሎቶች
ከሥልጠና ሌሎች ዓይነት ድጋፎች ኢንተርፕራይዞቹ የሰጡት በቁጥር ከጠቅላላ ከመለሱት
ምላሽ በመቶኛ በመቶኛ
አይደለም 19535 76.9 76.9
የንግድ ልማት አገልግሎት አዎን 5864 23.1 23.1
ድ ምር 25399 100.0 100.0
የሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ሠርተፊኬት አይደለም 18959 74.6 74.6
አዎን 6440 25.4 25.4
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 21588 85.0 85.0
የተሟላ መረጃ ማግኘት አዎን 3811 15.0 15.0
ድ ምር 25399 100.0 100.0
የምርጥ ተሞክሮ ቅመራና ማስተላለፍ አይደለም 23488 92.5 92.5
አዎን 1911 7.5 7.5
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 14202 55.9 55.9
ምክርና ድጋፍ አዎን 11197 44.1 44.1
ድ ምር 25399 100.0 100.0
የጥቃቅንና አነስተኛ ድህረ ገጽ አይደለም 24841 97.8 97.8
ዳይረክቶሬት አጠቃቀም አዎን 558 2.2 2.2
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 25172 99.1 99.1
ሌላ ድጋፍ አዎን 227 0.9 0.9
ድ ምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


ከሥልጠና ጋር የተያያዘም ሆነ ከሥልጠና ዉጪ ያሉት የሰዉ ሀይል ልማትና ኢንዱስትሪ
ኤክስቴንሽን ድጋፍ አገልግሎቶች ያገኙት ኢንተርፕራይዞች በቁጥር በጣም አነስተኛ ናቸዉ፡፡ ይህ
ተግባር በጣም ዉስብስብ ያልሆነና በቀላሉ ሊፈጸም የሚችል ሆኖ ሳለ ግማሽ ያህል እንኳን ለመፈጸም
አለመቻሉ ሊታረም የሚገባ ነው፡፡ የሰዉ ሀይል ልማትና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ
አገልግሎት በሥልጠናም ሆነ ሥልጠና ነክ ባልሆኑ የአቅም ግንባታ ተግባራት ያስመዘገበዉ ዉጤት

58
ደካማ ነዉ፡፡ ይህንን ያህል ዝቅተኛ ዉጤት ይዞ ከኢንተርፕራይዞቹ ዉጤት መጠበቅ ደግሞ ላም
ባልዋለበት ኩበት ለቀማ ስለሚሆን ለወደፊቱ ለደካማ አፈጻጸም ምክንያት በሆኑ ጉዳዮች ላይ
የማስተካከያ እርምጃ በማድረግ ለቀጣይ የተሻለ ዉጤት ማስመዝገብ ያስፈልጋል፡፡

በዚህ ክፍል ሌላ መታየት የሚገባዉ የመሣሪያ ሊዝ ድጋፍ ነዉ፡፡ ምክንያቱም የመሣሪያ ሊዝ ድጋፍ
አገልግሎት በራሱ ለአቅም ግንባታ ያለዉ ፋይዳ ትልቅ ሲሆን በሌላ በኩል ከኢንዱስትሪ
ኤክስቴንሽን ጋር የተቆራኘ በመሆኑ ነዉ፡፡ ይህንን አገልግሎት ያገኙት ኢንተርፕራይዞች 7 ከመቶ
በታች ሲሆኑ 1 ከመቶ በታች የሚሆኑት መመዘኛዎችን በሟሟላት ላይ እንደሚገኙና 1.5 በመቶ ስለ
አገልግሎቱ መረጃ እንደሌላቸዉ ሪፖርት አድርገዋል፡፡ በዚህ ረገድ የታየዉ አፈጻጸም እጅግ በጣም
ዝቅተኛ ብቻ ሳይሆን ሪፖርት ለማድረግ እንኳን በማያስችል ደረጃ በመሆኑ ተግባሩ እንደ አዲስ
ታቅዶ ብቁ የሆነ የአመራርና በዘርፉ አግባቢነት ያላቸዉ ባለሙያዎች ድጋፍ እየተሰጠ ሊመራ
ይገባል፡፡

ሠንጠረዥ 25፡ ለኢንተርፕራይዞች የተሰጠ የመሣሪያ ሊዝ ድጋፍ


የመሣሪያ ሊዝ ድጋፍ አገልግሎት በቁጥር በመቶኛ
አዎን 1738 6.8
አይደለም 23169 91.2
መመዘኛዎችን በሟሟላት ላይ 109 0.4
ስለ አገልግሎቱ መረጃ የሌላ 370 1.5
ሌላ 13 0.1
ድ ምር 25399 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

4.5.4 የቴክኖሎጂ ዕድገት ድጋፍ አገልግሎት

ተስማሚ ቴክኖሎጂ ድጋፍአገልግሎት ለጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ዕድገት ቁልፍ ተግባር መሆኑን
ከግንዛቤ ዉስጥ በማስገባት አልፎ አልፎም ቢሆን ሲሰራበት ቆይቷል፡፡ የድጋፍ አገልግሎቱን አሰጣጥ
አፈጻጸምና ድጋፉ ይሰጥበት የነበረዉን አግባብ እንዲሁም የዉጤታማነቱን ደረጃ ለመገምገም
የተለያዩ ጥያቄዎች ለኢንተርፕራይዞቹ ቀርበው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ የጥናቱ ዉጤት
የሚያመለክተዉ (ሠንጠረዥ 26) ግን ተግባሩ ያልተፈጸመ ነዉ በሚባል ደረጃ ዝቅተኛ መሆኑን
ነዉ፡፡ የቴክኖሎጂ ዕድገት ድጋፍ ያካትታል ተብለዉ ከተዘረዘሩት መካከል ተስማሚ ቴክኖሎጂ
አቅርቦት፤ ፕሮጄክት ፕሮፋይሎችን ማዘጋጀት፤ ማምረቻ መሣሪያ አቅርቦት፤ የጥገና፤ ዕድሳትና
መለዋወጫ አካላት ድጋፍ፤ የአፈር ምርመራ፤ ግብዓትና ምርት ፍተሻ አገልግሎት ይገኛሉ፡፡
በጠቅላላ መረጃ ከሰጡት 25399 ኢንተርፕራይዞች መካከል እነዚህን የድጋፍ አገልግሎቶች ያገኙት
ብዛታቸዉ ሲታይ በጣም አነስተኛ ነዉ፡፡ ለመጥቀስ ያህል ከተዘረዘሩ አገልግሎቶች መካከል ድጋፉ
የተሰጣቸዉ በሁሉም ዓይነት የቴክኖሎጂ ዕድገት ድጋፍ አገልግሎቱን ያገኙት 3 ከመቶ በታች

59
ናቸዉ፡፡ ከዚህ የምንረዳዉ የቴክኖሎጂ ዕድገት አገልግሎት ማዕቀፍ ያለዉን ፋይዳ በትክክል
ተረድቶ በማቀድ መፈጸም ማስፈለጉን ነዉ፡፡

ሠንጠረዥ26፡ የቴክኖሎጂ ዕድገት ድጋፍ አገልግሎት


የቴክኖሎጂ ዕድገት ድጋፍ ዓይነት ኢንተርፕራይዞቹ በቁጥር ከጠቅላላ ከመለሱት
የሰጡት ምላሽ በመቶኛ በመቶኛ
አይደለም 24829 97.8 97.8
የተስማሚ ቴክኖሎጂ ድጋፍ አዎን 570 2.2 2.2
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 24862 97.9 97.9
ፕሮጀክት ፕሮፋየሎችን የማዘጋጀት ድጋፍ አዎን 537 2.1 2.1
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 24675 97.1 97.1
የቴክኖሎጂ እና የማምረቻ መሣሪያ ድጋፍ አዎን 724 2.9 2.9
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 25218 99.3 99.3
የጥገና የእድሳትና የመለዋወጫ አካላት ድጋፍ አዎን 181 0.7 0.7
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 25251 99.4 99.4
የአፈር ምርመራ፤ የግብአትና ምርት ፍተሻ አገልግሎት አዎን 148 0.6 0.6
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 23106 91.0 91.0
ሌላ ዓይነት ድጋፍ አዎን 2293 9.0 9.0
ድ ምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

4.5.5 የገበያ ልማትና ግብይት ድጋፍ አገልግሎት

የገበያ ልማትና የግብይት ድጋፍ አገልገሎት ለኢንተርፕራይዞቹ ያለዉ አስተዋዕጾ ከፍተኛመሆኑ


የሚያከራክር አይደለም፡፡ ይህ ወሳኝ አገልግሎት ምን ያህል ዉጤታማ በሆነ መንገድ እየተሰጠ ነበር
የሚለዉን ጥያቄ ለመመለስ ኢንተርፕራይዞቹ እራሳቸዉ ከሚሉት በላይ አስረጂ ይመጣል ብሎ
ማሰብ ያስቸግራል፡፡ ሠንጠረዥ27 እንደሚያሳየዉ ዋና ዋና የገበያ ልማትና የግብይት ድጋፍ
አገልግሎት አፈጻጸማቸዉ 7 ከመቶ በታች ነዉ፡፡ በዚህ ሂደት 1 ከመቶ በታች አፈጻጸሞችም
ታይተዋል፡፡ በዝርዝር ሲታይ እንደቅደም ተከተሉ በአንጻራዊነት ትልቅ የሚባለዉ አፈጻጸም የታየዉ
የኢግዚቢሽንና ባዛር ድጋፍ፤ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ከዚያም የሰብ ኮንትራክቲንግ ግብይት ሥርዓት
ድጋፍ ከዚያም የአዉትሶርሲንግ የግብይት ሥርዓት ድጋፍ አገልግሎቶች ሲሆኑ በአሀዝ ሲለኩ
እንደቅደም ተከተላቸዉ 6.9 ከመቶ፤ 6.1 ከመቶ፤ 5.7 ከመቶ እና 3.6 ከመቶ ሆኖ እናገኛለን፡፡

60
ሠንጠረዥ27፡ የገበያ ልማትና የግብይት ድጋፍ አገልግሎት
የገበያ ልማትና የግብይት ድጋፍ አገልግሎት ኢንተርፕራይዞቹ በቁጥር ከጠቅላላ ከመለሱት
የሰጡት ምላሽ በመቶኛ በመቶኛ
አይደለም 23952 94.3 94.3
የሰብ ኮንትራክቲንግ የግብይት ሥርዓት ድጋፍ አዎን 1447 5.7 5.7
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 24486 96.4 96.4
የአዉትሶርሲንግ የግብይት ሥርዓት ድጋፍ አዎን 913 3.6 3.6
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 25343 99.8 99.8
የፍራንቻይዚንግ የግብይት ሥርዓት ድጋፍ አዎን 56 0.2 0.2
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 25229 99.3 99.3
የአዉትግሮወር ግብይት ሥርዓት ድጋፍ አዎን 170 0.7 0.7
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 23838 93.9 93.9
የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ድጋፍ አዎን 1561 6.1 6.1
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 23656 93.1 93.1
የኢግዚቢሽንና ባዛር ድጋፍ አዎን 1743 6.9 6.9
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 25329 99.7 99.7
ሌላ ዓይነት ድጋፍ አዎን 70 0.3 0.3
ድ ምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በአንጻራዊነት ትልቅ አፈጻጸም አስመዝግበዋል የተባሉ አገልግሎቶችም ቢሆኑ ከትርጉም አንጻር
እዚህ ግባ የሚባሉ አይደሉም፡፡ በዚህ ዝቅተኛ አፈጻጸም ሥርዓት ዉስጥም ሆኖ እጅግ በጣም ዝቅ
ያሉ አፈጻጸሞችን ያስመዘገቡ ድጋፎች የአዉትግሮወር ግብይት ሥርዓት ድጋፍ (0.7 ከመቶ) እና
የፍራንቻይዚንግ የግብይት ሥርዓት ድጋፍ (0.2 ከመቶ) ናቸዉ፡፡ በሌሎች ላይ እንደተሰጠዉ
አስተያየት በተመሳሳይ መልኩ የገበያ ልማትና የግብይት አገልግሎትም ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት
በዕቅድና ክትትል ተደግፎ ብቁ አመራርና የሙያ ድጋፍ እየተሰጠዉ ሊመራ ይገባል፡፡

4.5.6 የፋይናንስና ብድር አገልግሎት ዉጤታማ ለማድረግ የተሰጡ ሌሎች ድጋፎች

ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስና ብድር ድጋፍ ማግኘት በጣም አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑ የሚሰመርበት
ቢሆንም በራሱ ግብ ባለመሆኑ የተሰጠዉ የፋይናንስና ብድር ድጋፍ ዉጤታማ እንዲሆን የሚያግዙ
ሌሎች ድጋፎችን መስጠት ኢንተርፕራይዞቹ የተቋቋሙበትን አላማ ከማሳካት አንጻር ትኩረት
አግኝቶ ሊመዘን የሚገባ ተግባር ነዉ፡፡ በዚሁ መሠረት ኢንተርፕራይዞቹ የተሰጣቸዉን የፋይናንስና
ብድር ድጋፍ ዉጤታማ ለማድረግ ምን ዓይነት ድጋፍ ተሰጣቸዉ የሚለዉ ጥያቄ ተጠይቀዉ
የየራሳቸዉን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በዚህ ድጋፍ አገልግሎት ሥር የተመለከቱት ግንዛቤ ከመፍጠር ጋር
ቁርኝት ያላቸዉ ተግባራት ሲሆኑ የመሳሪያ ሊዝ አጠቃቀምም ተካቷል፡፡ አፈጻጸሙ የድጋፍ
አገልግሎቱን ካገኙት ኢንተርፕራይዞች አንጻር ሲመዘን ከቀደምት አፈጻጸሞች የተሻለ መሆኑ

61
እንደተጠበቀ ሆኖ ከጠቅላላ ኢንተርፕራይዞች ብዛት አንፃር ሲመዘን ግን አሁንም ትንሽ እንደሆነ
ለመረዳት አያዳግትም (ሠንጠረዥ 28)፡፡ ግንዛቤ ከመፍጠር አኳያ በቂ የሆነ ግንዛቤ በቁጠባና ብድር
ዙሪያ የመፍጠር ድጋፍ ማግኘታቸዉን የሚስማሙት 35.5 ከመቶ ሲሆኑ በቂ የሆነ ግንዛቤ በሂሳብ
አያያዝ ዙሪያ የመፍጠር ድጋፍ አገልግሎት ያገኙት 27.9 በመቶ መሆናቸዉን የጥናት ዉጤቱ
ያሳያል፡፡ የመምረቻ መሳሪያ ሊዝ ፕሮግራም ተጠቃሚነት ጋር ያለዉ አፈጻጸም 3.2 በመቶ መሆኑ
አሁንም ችግሩ መኖሩን የሚያመላክት ነዉ፡፡ የፋይናንስና ብድር ድጋፍ ዉጤታማ ለማድረግ
የተሰጡ ድጋፍ አገልግሎቶች ከሌሎቹ ጋር ሲነጻጸር መሻሻል የታየበት መሆኑ ዕዉቅና ማግኘት
ያለበት ሆኖ አሁንም ብዙ ርቀት መጓዝ እንደሚጠይቅ የጥናት ዉጤቱ ያስረዳል፡፡

ሠንጠረዥ28፡ የፋይናንስና ብድር ድጋፍ ዉጤታማ ለማድረግ የተሰጠ ድጋፍ አገልግሎት


የፋይናንስና ብድር ድጋፍ ዉጤታማ ኢንተርፕራይዞቹ የሰጡት በቁጥር ከጠቅላላ ከመለሱት
ለማድረግ የተሰጠ ድጋፍ አገልግሎት ምላሽ በመቶኛ በመቶኛ
በቂ የሆነ ግንዛቤ በቁጠባና በብድር ዙሪያ አይደለም 16378 64.5 64.5
አዎን 9021 35.5 35.5
ድ ምር 25399 100.0 100.0
በቂ የሆነ ግንዛቤ በሂሳብ አያያዝ ዙሪያ አይደለም 18301 72.1 72.1
አዎን 7098 27.9 27.9
ድ ምር 25399 100.0 100.0
የመምረቻ መሳሪያ ሊዝ ፕሮግራም አይደለም 24588 96.8 96.8
ተጠቃሚ አዎን 811 3.2 3.2
ድ ምር 25399 100.0 100.0
ሌላ ድጋፍ አይደለም 25296 99.6 99.6
አዎን 103 0.4 0.4
ድ ምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

4.5.7 የሚሰጡ የድጋፍ ዓይነቶች ችግር ፈቺነት እና ወቅታዊነት

የሚሰጡ ድጋፎች አግባቢነት ከሚለካበት መንገድ አንዱ ምን ያህል ችግር ፈቺ እና ወቅታዊ ነዉ


የሚለዉን ጥያቄ በአግባቡ በመመለስ ነዉ፡፡ ይህንንም አስመልክቶ እንተርፕራይዞች ተጠይቀዉ
የሰጡት ምላሽ ተተንትኗል፡፡ ይህም በግራፍ 6 ታይቷል፡፡ የድጋፍ አገልግሎት ችግር ፈቺነት እና
ወቅታዊነት ለየብቻ ቢተነተኑ የተሻለ አረዳድ እንደሚፈጥር ይታመናል፡፡ ምክንያቱም የድጋፍ
አገልግሎት አሰጣት ወቅታዊ ሆኖ ችግር ፈቺ ያለመሆን ወይም በተቀራኒዉ ችግር ፈቺነቱ
እንደተጠበቀ ሆኖ ወቅታነትን ላያሳካ ስለሚችል ነዉ፡፡ የጥናት ዉጤቱን እንደሚያሳየዉ 60 ከመቶ
ኢንተርፕራይዞች የሚሰጡ የድጋፍ ዓይነቶች ችግር ፈቺነትም ሆነ ወቅታዊነት አስመልክቶ በሰጡት
ምላሽ በከፊል ነዉ ይላሉ፡፡ ሙሉ በሙሉ ችግር ፈቺ ነዉ፤ ወቅታዊም ነዉ ያሉ ኢንተርፕራይዞች
14.4 ከመቶ ናቸዉ፡፡ በከፊል ወቅታዊ እንዲሁም በከፊል ችግር ፈቺ ነዉ ያሉትን ብንደምራቸዉ

62
ከ74 በመቶ የሚበልጡት ይሁንታቸዉን ሰጥተዋል፡፡ ይህ አፈጻጸም ከቀደምቶቹ ጋር ሲነጻጸር ጥሩ
ነዉ ሊባል የሚችል ነዉ፡፡

ቀደም ባሉት የውይይት ክፍሎች እዚህም እዚያም እንዳየነዉ በአንዳንድ የድጋፍ አገልግሎቶች
የተጠቃሚዎች ቁጥር እጅግ በጣም አነስተኛ ሲሆን በአንዳንድ ድጋፍ አገልግሎቶች የተሻለ የድጋፍ
አገልግሎት መሰጠቱን የሚያሳዩ መረጃዎች ምን ያህል የሁሉንም ኢንተርፕራይዞች የድጋፍ
አገልግሎት የሚወክሉ ናቸዉ የሚለዉ አሁንም አነጋጋሪ መሆኑ ከግንዛቤ ዉስጥ ገብቶ ሊታይ የሚገባ
ነጥብ ነዉ፡፡
በመቶኛ

ሙሉ በሙሉ ናቸዉ በከፍል ናቸዉ አይደሉም

የድጋፍ ዓይነቶች ችግር ፈቺነት እና ወቅታዊነት

ግራፍ6፡ የሚሰጡ የድጋፍ ዓይነቶች ችግር ፈቺነት እና ወቅታዊነት


ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

4.5.8 የመስሪያ ቦታ ድጋፍ አገልግሎት

ለኢንተርፕራይዞች ወሳኝ ከሆኑ ድጋፎች መካከል የመስሪያ ቦታ ዋነኛዉ ነዉ ቢባል ማጋነን


አይሆንም፡፡ መስሪያ ቦታ መኖር አለመኖር፡ የመስሪያ ቦታ መጠንና ምቹነት … ወዘተ
የኢንተርፕራይዞቹን የመወዳደር አቅም ብቻም ሳይሆን የመኖር አለመኖር ህሊዉናም ጭምር
ይወስናል፡፡ ከኢንተርፕራይዞች መስሪያ ቦታ ጋር የሚገናኙ አግባቢነት ያላቸዉ ጥያቄዎች
በመጠይቅ ዉ ስጥ ተካተዉ ለኢንተርፕራይዞቹ ቀርበዉ ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ ከጠቅላላ 25399
ኢንተርፕራይዞች መካከል 18699 (73.6 በመቶ) የመስሪያ ቦታ ድጋፍ አገልግሎት እንዳገኙ ምላሽ
የሰጡ ሲሆን ቀሪዎቹ 26 ከመቶ ያህሉ የመስሪያ ቦታ ድጋፍ አገልግሎት አለማግኘታቸዉን
ለመረዳት ተችሏል፡፡ ይህም እንተርፕራይዞቹን ዉጤታማ አለማድረግ ብቻም ሳይሆን
ከኢንተርፕራይዞቹ መኖር አለመኖር ህሊዉና ጭምር የሚተሳሰር በመሆኑ ብዙዎቹ የዚህ አገልግሎት

63
ተጠቃሚ መሆን እንደ ጥሩ አፈጻጸም መገምገም ያለበት ሆኖ ሳያገኙ የቀሩትም ቢሆኑ ብዛታቸዉ
በጣም ጥቂት የሚባል ባለመሆኑ አፋጣኝ መፍትሔ የሚሻ ጉዳይ ይሆናል፡፡ የመስሪያ ቦታ እንደ
የዕድገት ዘርፎቹ ባህርይና እድገት ደረጃ የሚለያይ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ አንዳንዶቹ የዕድገት
ዘርፎች ያለመስሪያ ቦታ ምንም ማድረግ እስከማይችሉ ድረስ ተጽዕኖ የማሳደር አቅም አለዉ፡፡ ይህ
እዉነት ግምት ዉስጥ ገብቶ የመስሪያ ቦታ ድጋፍ እንደ ዕድገት ዘርፉ ባህርይና የዕድገት ደረጃ
እየተመዘነ ቢሰጥ የበለጠ ዉጤታማ እንደሚሆን ይታመናል፡፡

ሠንጠረዥ29፡ የመስሪያ ቦታ ድጋፍ አገልግሎት


የመስሪያ ቦታ ድጋፍ በቁጥር በመቶኛ
አግኝቷል 18699 73.6
አላገኘም 6700 26.4
ድ ምር 25399 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የመስሪያ ቦታ ስፋት ምጣኔ እንደየዕድገት ዘርፉ የሚወሰን


ነዉ፡፡ አንዳንድ የዕድገት ተኮር የሥራ መስኮች ሰፋ ያለ ቦታ የሚፈልጉ ሲሆን አንዳንዶቹ ግን
በአነስተኛ ቦታ ላይ ለመስራት የሚያስቻሉ ናቸዉ፡፡ ከዚህም የተነሣ የተለያዩ ኢንተርፕራይዞች
የተለያየ ስፋት ያላቸዉ መስሪያ ቦታዎች ሊኖሩአቸዉ እንደሚችሉ ይገመታል (ሠንጠረዥ30)፡፡
ከጠቅላላ 25399 ኢንተርፕራይዞች 18243 (71.8 በመቶ) የተለያየ ስፋት ያላቸዉን መስሪያ ቦታ
ድጋፍ እንዳገኙ ከመስክ የተሰበሰበዉ መረጃ ያሳያል፡፡ ከእነዚህም መካከል ግማሽ ያህሉ (51.5
በመቶ) ያገኙት የቦታ ስፋት እስከ 5 ካሬ ሜትር ብቻ ሲሆን 10.3 በመቶ ከ5 እስከ 10 ካሬ ሜትር
እንዲሁም 10.2 በመቶ ከ10 እስከ 20 ካሬ ሜትር ስፋት ያለዉን የመስሪያ ቦታ ማግኘታቸዉን
ገልጸዋል፡፡ ይህም ሲጠቃለል በድምሩ 72 ከመቶ ኢንተርፕራይዞች ከዝቅተኛ አንስቶ እስከ 20 ካሬ
ሜት ር ስፋት ያለዉን የመስሪያ ቦታ ድጋፍ አግኝተዋል፡፡ በድምሩ 14.5 ከመቶ ያህል
ኢንተርፕራይዞች 50 ካሬ ሜትር እና ከዚያ በላይ ስፋት ያላቸዉን የመስሪያ ቦታ ማግኘታቸዉን
ገልጸዋል፡፡ከኢንተርፕራይዞቹ መካከል 28 በመቶ ያህሉ ምላሽ ያልሰጡ ሲሆን ከእነዚህም አብዘኛዎቹ
ሊሆኑ የሚችሉት የመስሪያ ቦታ ድጋፍ አገልግሎት ያላገኙት ናቸዉ፡፡ ሆኖም ጥቂት የሚባሉ
የመስሪያ ቦታ ድጋፍ አገልግሎት ካገኙት መካከል ስለመስሪያ ቦታቸዉ ስፋት ለመግለጽ ያልፈለጉ
መኖራቸዉን የጥናት ዉጤቱ ያሳያል፡፡

64
ሠንጠረዥ30፡ የመስሪያ ቦታ ስፋት (በካሬ ሜትር)
የመስሪያ ቦታ ስፋት (በካሬ ሜትር) በቁጥር ከጠቅላላ በመቶኛ ከመለሱት በመቶኛ
እ ስከ 5 9394 37.0 51.5
ከ5.1-10 1870 7.4 10.3
ከ10.1-20 1868 7.4 10.2
ከ20.1-30 752 3.0 4.1
ከ30.1-40 632 2.5 3.5
ከ40.1-50 329 1.3 1.8
ከ51-100 1313 5.2 7.2
ከ101-200 1336 5.3 7.3
ከ201-300 453 1.8 2.5
ከ300 በላይ 292 1.1 1.6
ድ ምር 18243 71.8 100.0
ሪፖርት ያላደረጉ 7156 28.2 …
ጠቅላላ ድምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

ከጠቅላላ 25399 ኢንተርፕራይዞች 18315 (72.1 በመቶ) የመስሪያ ቦታ ያገኙበትን ዓ/ም


አስረድተዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የመስሪያ ቦታ ያገኙት
በተለያዩ ዓመታት መሆኑን ምላሽ የሰጡት ኢንተርፕራይዞች ገልጸዋል፡፡ ኢንተርፕራይዞቹ በተለያዩ
ዓመታት የመስሪያ ቦታ ያግኙ እንጂ ምላሽ ከሰጡት ኢንተርፕራይዞች መካከል 81 ከመቶ የመስሪያ
ቦታ ያገኙት በመጀመሪያዎቹ ሁለት ዓመታት (1996 ዓ/ም እና 1997 ዓ/ም) እንዲሁም
በመጨራሻዎቹ አራት ዓመታት (ከ2005 ዓ/ም እስከ 2008 ዓ/ም) እንደነበረ የጥናቱ ዉጤት
ያሳያል፡፡ በመጀመሪያዎቹ ሁለት ዓመታት 33.2 በመቶ የመስሪያ ቦታ አግኝተዋል፡፡ ቦታዉ
የተገኘበት ወቅት/ጊዜ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የድህነት ቀናሽ ተቋማት እንደሆኑ
ግንዛቤ የተወሰደበት እና ከዚህም የተነሣ ተቋማዊ ይዘት ኖሮአቸዉ የተደራጁበት ነዉ፡፡ ሆኖም
ከ1998 ዓ/ም እስከ 2004 ዓ/ም ድረስ ከፍተኛ መቀዛቀዝ (ግራፍ 7) ታይቷል፡፡ (ከ2005 ዓ/ም እስከ
2008 ዓ/ም) ባለዉ ጊዜ እንደገና መንሰራራት ታይቷል፡፡ ለዚህ መንሰራራት ምክንያቱ ምን እንደሆነ
በመረጃ ባይካተትም በጥቅሉ ግን የሚደራጁት ኢንተርፕራይዞች ከጊዜ ወደ ጊዜ የመጨመር ወይም
ቅድመ ሁኔታዎች እስኪሟሉ የዘገዩት በመጨረሻዎቹ ዓመታት ያገኙበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል፡፡

65
በመቶኛ

ግራፍ 7፡ ለኢንተርፕራይዞች የመስሪያ ቦታ የተሰጠበት ዓ/ም


ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

ከጠቅላላዉ 25399 ኢንተርፕራይዞች መካከል 16147 (63.6 በመቶ) ስለመስሪያ ቦታቸዉ ዓይነት
ሪፖርት አድርገዋል፡፡ ምላሽ ከሰጡት 42.5 በመቶ ሼድ/ወርክሾፕ፤ 35.8 በመቶ ተለጣፊ ሱቅ፤
እንዲሁም 15.8 በመቶ ህንጻ ሲሆን ይህ ውጤት ሲጠቃለል 94.1 በመቶ ነዉ፡፡ ይህም ማለት
ለሻወርና ሽንት ቤት፤ ለመኪና እጥበት እና የመሳሰሉት ድርሻቸዉ በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡ ምክንያቱን
በሚመለከት ራሱን አስችሎ መረጃ የተሰበሰበ ባይሆንም መረዳት የሚቻለው የመስሪያ ቦታ ዓይነት
እንደ የአግልግሎቱ የሚለይ በመሆኑ ነዉ (ሠንጠረዥ 31)፡፡ ይህንንም ግራፍ 8 ከመስሪያ ቦታ
አገልግሎት ጋር በማነጻጸር የተሻለ መረዳት መፍጠር ይቻላል፡፡

ሠንጠረዥ31፡ ኢንተርፕራይዞች ያገኙት የመስሪያ ቦታ ዓይነት


የመስሪያ ቦታ ዓይነት በቁጥር ከጠቅላላ በመቶኛ ከመለሱት በመቶኛ
ሼድ/ወርክሾፕ (G+0) 6867 27.0 42.5
ተለጣፊ ሱቅ 5788 22.8 35.8
ለሻወርና ሽንት ቤት 130 0.5 0.8
ህንፃ (G+1 and above) 2546 10.0 15.8
ለመኪና እጥበት 130 0.5 0.8
ሌላ 686 2.7 4.2
ድ ምር 16147 63.6 100.0
ምላሽ ያልሰጡ 9252 36.4 …
ጠቅላላ ድምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


66
የአዲስ አበባ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተሰጣቸዉን ቦታ ለ ምን አገልግሎት
እንደሚጠቀሙ ከጠቅላላዉ 72.4 በመቶ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ኢንተርፕራይዞቹ ካገኙአቸዉ የመስሪያ
ቦታ አብዘኛዎቹ ወይም ምላሽ ከሰጡት መካከል 47.7 በመቶ ቦታዉን የሚገለገሉት ለመሸጫ ብቻ
እንደሆነ፡ 29.2 በመቶ ደግሞ ለማምረቻ ብቻ እንደሚጠቀሙ እንዲሁም 23.1 በመቶ ለማምረቻና
ለመሸጫ እንደሚጠቀሙ ገልጸዋል፡፡
በመቶኛ

ለማምረቻ ብቻ ለመሸጫ ብቻ ለማምረቻናለመሸጫ

የመስሪያቦታ አገልግሎት
ግራፍ8፡ ኢንተርፕራይዞች ያገኙት የመስሪያ ቦታ አገልግሎት
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
የመስሪያ ቦታ ማግኘት ለኢንተርፕራይዞቹ ዕድገት በጣም አስፈላጊ መሆኑ ቢታመንም መስሪያ
ቦታዉ በመሰረተ ልማት የተደገፈና ከተለያዩ ችግሮች የተላቀቀ ካልሆነ ኢንተርፕራይዞቹ ከመስሪያ
ቦታ ማግኘት የሚገባቸዉን ጥቅም ሊያገኙ አይችሉም፡፡ የሚፈለገዉን አገልግሎት በብቃት
ለመስጠት መስሪያ ቦታዎቹ ለሥራ አመቺ፡ ተደራሽ … ወዘተ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡ የአዲስ አበባ
ከተማ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከመስሪያ ቦታ ጋር የተያያዙ ችግሮች እንዳሉባቸዉ
ገልጸዋል፡፡ እነዚህን ችግሮች ከመሰረተ ልማት ጋር የተያያዙና ሌሎች ብዙም ከመሰረተ ልማት ጋር
ቁርኝት የሌላቸዉን ለየብቻ ወደ ሁለት ከፍሎ ማየት የተሻል ሥዕል ስለሚሰጥ በዚሁ ልክ
ተከናዉኗል (ሠንጠረዥ 32ሀ እና ሠንጠረዥ 32ለ)፡፡ ከመሰረተ ልማት አንጻር ሲለካ ከጠቅላላ
ኢንተርፕራይዞች መካከል ግማሽ ያህሉ ችግር አለብን ያሉት በመጸዳጃ ቤት አቅርቦትና የዉሀ ቧንቧ
መስመር ችግሮች ናቸዉ፡፡ የመጸዳጃ ቤት ችግር አለብን ያሉት 50.8 ከመቶ ሲሆኑ የዉሀ ቧንቧ
ችግር አለብን ያሉት ደግሞ 43.3 ከመቶ ናቸዉ፡፡ እንዲሁም የማረፊያ ቤትና የመብራት ችግር
አለብን ያሉት እንደቅደም ተከተላቸዉ 25 ከመቶ እና 23 ከመቶ ናቸዉ፡፡ ይህ ነዉ የሚባል ችግር
ያልቀረበዉ ከቤት ቁጥር/አድራሻ ጋር ተያይዞ ነዉ፡፡ ለዚህም ምክንያት ሊሆን የሚችለዉ
67
ኢንተርፕራይዞቹ ሲደራጁና የተለያዩ አገልግሎቶችን ሲጠይቁ የአድራሻ መኖር እንደአስፈላጊ ቅድመ
ሁኔታ ስለሚታይ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል፡፡

ሠንጠረዥ32ሀ፡ ከመሰረተ ልማት አቅርቦት ጋር የተያያዙ የመስሪያ ቦታ ችግሮች


ከመሰረተ ልማት ጋር የተያያዙ የመስሪያ ኢንተርፕራይዞቹ የሰጡት በቁጥር ከጠቅላላ ከመለሱት
ቦታ ችግሮች ምላሽ በመቶኛ በመቶኛ
የዉሀ መስመር አይደለም 14413 56.7 56.7
አዎን 10986 43.3 43.3
ድ ምር 25399 100.0 100.0
መብራት አይደለም 19552 77.0 77.0
አዎን 5847 23.0 23.0
ድ ምር 25399 100.0 100.0
የማረፊያ ቦታ አይደለም 18956 74.6 74.6
አዎን 6443 25.4 25.4
ድ ምር 25399 100.0 100.0
የመጸዳጃ ቤት አይደለም 12508 49.2 49.2
አዎን 12891 50.8 50.8
ድ ምር 25399 100.0 100.0
መንገድ አይደለም 22074 86.9 86.9
አዎን 3325 13.1 13.1
ድ ምር 25399 100.0 100.0
የቤት ቁጥር /አድራሻ/ አይደለም 24798 97.6 97.6
አዎን 601 2.4 2.4
ድ ምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


መጠኑና ዓይነቱ እንደየዕድገት ተኮር ዘርፍ ባህርይና የዕድገት ደረጃ የሚለያይ ቢሆንም ጥቃቅንና
አነስተኛ ተቋማት ከላይ ከተጠቀሱት መሰረተ ልማት ተያያዥ ችግሮች በተጨማሪ ሌሎች ችግሮች
እንዳሉባቸዉ ተጠይቀዉ ችግሮቹ መኖራቸዉን (ሠንጠረዥ 32ለ) አልሸሸጉም፡፡ እነዚህ ችግሮች
የሚያያዙት ከዲዛይን፤ ኢንተርፕራይዞቹን በአግባቡ ከመምራትና ማስተዳደር እንዲሁም ከመስሪያ
ቦታ አመቺነት ጋር የተያያዙ እንደሆነ የተሰበሰበዉ መረጃ ያሳያል፡፡ በዚህ ረገድ ትልቁ ችግር
የመስሪያ ቦታ አመቺ አለመሆኑ ነዉ፡፡ ይህም 29 ከመቶ ድርሻ አለዉ፡፡ ከመስሪያ ቦታ አመቺነት
ማጣት ችግር ቀጥለዉ የመጡት ችግሮች እንደቅደም ተከተላቸዉ የዲዛይን ችግር (10.1 ከመቶ) እና
ማዕከላትን በአግባቡ ለማስተዳደር አለመቻል (6.1 ከመቶ) ናቸዉ፡፡ በሌላ በኩል 11 ከመቶ የሚሆኑ
ኢንተርፕራይዞች ምንም ችግር እንደሌለባቸዉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ዉጤቱ እንደሚያመላክተዉ
እነዚህን ችግሮች መቅረፍ ከኢንተርፕራይዞች የሚጠበቀዉን ሥራ ዕድል የመፍጠር እና ድህነትን
የመቀነስ ሚናቸዉን እንዲወጡ ስለሚያደርጋቸዉ ችግር ነዉ ተብለዉ የተ ለ ዩ ጉዳዮች
እንዲፈቱላቸዉ አስፈላጊዉን ሁሉ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

68
ሠንጠረዥ32ለ፡ ሌሎች የመስሪያ ቦታ ችግሮች
ከመስሪያ ቦታ ጋር የተያያዙ ሌሎች ኢንተርፕራይዞቹ በቁጥር ከጠቅላላ ከመለሱት
ችግሮች የሰጡት ምላሽ በመቶኛ በመቶኛ
አይደለም 22838 89.9 89.9
የዲዛይን አዎን 2561 10.1 10.1
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 23843 93.9 93.9
ማዕከላትን የማስተዳደር ችግር አዎን 1556 6.1 6.1
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 18036 71.0 71.0
የቦታዉ አመቺነት አዎን 7363 29.0 29.0
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 22508 88.6 88.6
ምንም ችግር የለም አዎን 2891 11.4 11.4
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 24889 98.0 98.0
ሌላ አዎን 510 2.0 2.0
ድ ምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

የመስሪያ ቦታ በተለያየ ምክንያት ያላገኙትን አስመልክቶ አሁን የት እየሠሩ እንደሆነ ተጠይቀዉ


የተለያየ ምክንያት ሰጥተዋል (ግራፍ 9)፡፡ ቀደም ሲል በነበረዉ የትንተና ክፍል እንደተገለጸዉ
ከጠቅላላ 25399 ኢንተርፕራይዞች መካከል ቦታ እንዳላገኙ ሪፖርት ያደረጉት 6700 (26.4 በመቶ)
እንደነበረ ተመልክተናል፡፡ እነዚህ መረጃዉ በሚሰበሰብበት ወቅት የት እየሠሩ እንደሆነ ለማወቅ
ለቀረበዉ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ከ6700 መካከል 5510 ወይንም 82.2 ከመቶ የመስሪያ ቦታ
አላገኘንም ካሉት መካከል እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከእነዚህ ምላሽ ከሰጡት 37.3 በመቶ
ከግለሰብ ተከራይተዉ፤ 24.6 ከመቶ በመኖሪያ ቤታቸዉ፤ 19.2 በመቶ ከመንግሥት ተከራይተዉ፤
እንዲሁም 10 ከመቶ ያህሉ በግል ይዞታቸዉ፡ 9 በመቶ ያህሉ በሌላ መንገድ እየሠሩ መሆናቸዉን
ሪፖርት አድርገዋል፡፡ በድምር ሲታይ ተከራይተዉ የሚሠሩት 56.5 ከመቶ ሲሆኑ በግል ይዞታቸዉ
የሚሠሩት ደግሞ 34.6 መቶ እንደሆኑ መረጃዉ ያሳያል፡፡ በሌላ በኩል ከመንግስት ተከራይተው
የሚሰሩትን በሚመለከት አገልግሎቱን መንግስት ያመቻቸ መሆኑን በመገንዘብ ለኢንተርፕራይዞቹ
ከመንግስት የተደረገ ድጋፍ ነው ብሎ መውሰድ ይቻላል፡፡

69
በመቶኛ

ከግለሰብ በኪራይ በ ግል ይ ዞ ታ ከመንግሥት በኪራይ በመኖሪያ ቤት ሌላ

አሁን እየሰሩ ያሉበት ሁኔታ

ግራፍ 9 ኢንተርፕራይዞች አሁን እየሰሩ ያሉበት ሁኔታ


ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በመኖሪያ ቤታቸዉ የሚሠሩትን አስመልክቶ የተለየ ጥንቃቄ የሚሻ ጉዳይ ነዉ፡፡ በአንድ በኩል
ከአገርቱና ከከተማ አስተዳደሩ የንግድ ህግጋቶች ጋር ተመሳክሮ አግባቢነቱ መፈተሽ ያለበት መሆኑ
እንደተጠበቀ ሆኖ በሌላ በኩል ደግሞ ከማህበራዊ ጤና እናም የከተማ መሬት አጠቃቀም ሥርዓት
ጋር ተያይዞ አግባቢነት የሌለው ተግባር መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል፡፡ ምክንያቱም እንደየሥራ ዘርፉ
ባህርይ የሚለያይ ቢሆንም ከመኖሪያ አከባቢ ጋር የማይጣጣሙ የሥራ ዓይነቶች መኖራቸው ምስክር
የማይሻ ጉዳይ በመሆኑ ነው፡፡ ለምሳሌ የጎሚስታ፤ ጋራዥ፤ ብረታብረትና እንጨት ሥራ ድርጅቶችን
መጥቀስ ይቻላል፡፡ ለዚህ ነው ከአደረጃጀት ጀምሮ ጥንቃቄ ማድረግና በሥራ ላይም እያሉ ተገቢዉን
ክትትልና ድጋፍ ማድረግ አስፈላጊ የሚሆነው፡፡

4.5.9 ኢንተርፕራይዞች የሚደረግላቸዉ ድጋፍ ግልጽነት፤ ፍትሃዊነት እና ተደራሽነት

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የታለመላቸዉን ስትራቴጂክ ግብ ለመምታት ከመንግስት


የሚደረገዉ የተለያየ ድጋፍ ግልጽ፤ ፍትሃዊ እና ተደራሽ መሆን ይኖርበታል፡፡ ግልጽነት እና
ፍትሀዊነት የጎደለዉ ከሆነ ጤናማ ያልሆነ ዉድድር በመካከላቸዉ ይፈጠራል፡ የሥራ ሞራላቸዉ
ይዳሽቃል፡ ዓላማቸዉም ግቡን የመምታት ሁኔታ እጅጉን አጠራጣሪ የመሆን ዕድሉ ሰፊ ነዉ፡፡ በዚህ
ዙሪያ ኢንተርፕራይዞቹ ተጠይቀዉ ስለአፈጻጸሙ ያላቸዉን አስተያየት ሰጥተዋል (ሠንጠረዥ 33)፡፡
በመንግስት ለኢንተርፕራይዞቹ በሚሰጡ አገልግሎቶች ፍትሀዊነት፤ ግልጽነት እና ተደራሽነት ላይ
ብዙዎቹ ኢንተርፕራይዞች ይስማማሉ፡፡ የመንግስት ድጋፋዊ አገልግሎት አሰጣጥ ግልጽና በዕዉቀት

70
ላይ የተመሰረተ ስለመሆኑ የሚስማሙት 33.7 ከመቶ፤ በከፊል የሚስማሙት ደግሞ 39.2 በድምሩ
73.4 ከመቶ ኢንተርፕራይዞች ስምምነታቸዉን ገልጸዋል፡፡ አሳታፊ መድረክ ስለመኖሩ ደግሞ 32.8
በስምምነትና 38.3 በከፊል ስምምነት በድምሩ 71 ከመቶ ሀሳባቸዉን ሰጥተዋል፡፡ መስተንግዶን
ያለአድልዖ ለሁሉም በእኩልነት መስጠትን በሚመለከት 40.2 በስምምነት 28.3 በከፍል በመስማማት
በድምሩ 68.5 የመስማማትና በከፊል የመስማማት ሀሳባቸዉን ገልጸዋል፡፡ ከሁሉም ዝቀተኛ ይሁንታ
ያገኙት እንደቅደምተከተላቸዉ ለችግሮች አፋጣኝ ምላሽ የማግኘት (54.1 ከመቶ በድምር) ጉዳይና
የመንግስት ድጋፋዊ አገልግሎቶችን በቀላሉ ማግኘት (55.6 ከመቶ በድምር) መቻሉ ላይ ነዉ፡፡
በእነዚህ አገልግሎቶች እንደቅደም ተከተላቸዉ የሚስማሙትና በከፊል የሚስማሙት አፋጣኝ ምላሽን
አስመልክቶ 17 ከመቶ እና 37.1 ከመቶ በድምር 54.1 እንዲሁም መንግስታዊ የድጋፍ
አገልግሎቶችን በቀላሉ ማግኘትን አስመልክቶ 18.6 ከመቶ እና 37 ከመቶ በድምር 55.6 ከመቶ
ናቸዉ፡፡ እነዚህ ሁለቱ ጉዳዮች እርስበርስ የሚመጋገቡ ናቸዉ፡፡ ምክንያቱም አፋጣኝ ምላሽ
የመስጠት ባህል በሌለበት መንግስታዊ አገልግሎቶችን በቀላሉ ማግኘት ይቻላል ብሎ መጠበቅ
ትክክል ስለማይሆንና ስለማይሳካም ጭምር ነዉ፡፡ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠትና አገልግሎቶች በቀላሉ
እንዲገኙ ከሚያስፈልጉ ጉዳዮች መካከል ቢሮክሮሲዉን ቀልጣፋ ማድረግና የማስፈጸም አቅም
ግንባታ አጠናክሮ መሥራት እንደ ቁልፍ ጉዳይ መታየት ያለበት ይሆናል፡፡

ሠንጠረዥ 33፡ በሚሰጡ ድጋፋዊ አገልግሎቶች ላይ ኢንተርፕራይዞቹ ያላቸዉ አስተያየት


በከፍል ሪፖርት ጠቅላላ ድምር
በሚሰጡ የድጋፍ ማዕቀፎች እስማማለሁ እስማማለሁ አልስማማም ድምር ያላደረጉ
ቁጥር % ቁጥር % ቁጥር % ቁጥር % ቁጥር % ቁጥር %
ግልጽና በቂ ዕዉቀት መኖሩን
8554 33.7 10083 39.7 6144 24.2 24781 97.6 618 2.4 25399 100.0
አሳታፍ መድረክ መኖሩን
8338 32.8 9727 38.3 6240 24.6 24305 95.7 1094 4.3 25399 100.0
በዕድገት ደረጃ መሠረት መሆኑን
5741 22.6 9417 37.1 8737 34.4 23895 94.1 1504 5.9 25399 100.0
ለችግሮች አፋጣኝ ምላሽ መገኘቱ
4322 17.0 9422 37.1 10381 40.9 24125 95.0 1274 5.0 25399 100.0
ሁሉም በእኩልነት ማግኘቱ
10205 40.2 7180 28.3 6609 26.0 23994 94.5 1405 5.5 25399 100.0
ድጋፎቹ በቀላሉ ስለመገኘታቸዉ
4726 18.6 9394 37.0 9190 36.2 23310 91.8 2089 8.2 25399 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

4.5.10 የሚሰጠዉ ድጋፍ እንደዘርፉ ባህርይ እና በደረሰበት ዕድገት ደረጃ መሰረት ስለመሆኑ

ለኢንተርፕራይዞቹ የሚሰጠዉ ድጋፍ በግልጸኝነት፤ ፍትሀዊነትና ተደራሽነት ላይ የተመሰረተ


የመሆኑን ጠቃሜታ ከላይ በዝርዝር ተመልክተናል፡፡ ከዚሁ ጎን ለጎንለኢንተርፕራይዞች የሚሰጠዉ
ድጋፍ ዉጤታማ ሊሆን የሚችለዉ እንደየዕድገት ዘርፉ ባህርይና ከደረሰበት የዕድገት ደረጃ ሲሰጥ
ብቻ ነዉ፡፡ ድጋፉ በዚህ አግባብ ስለመፈጸም አለመፈጸሙ በጥናቱ ለመፈተሽ ተሞክሯል (ግራፍ
10)፡፡

71
በመቶኛ

ሙሉ በሙሉ ያገኛል በከፍል ያገኛል አያገኝም እንደየዘርፉ ባህርይና የደረሰበት ሌላ


ደረጃ አያገኝም

እንደዘርፉ ባህርይና ከደረሰበት የዕድገት ደረጃ አንፃር ድጋፍ ስለመሰጠቱ

ግራፍ10፡ የሚሰጡ ድጋፎች እንደዘርፉ ባህርይ እና ከደረሰበት የዕድገት ደረጃ አንፃር ስለመሆኑ
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

የአዲስ አበባ ከተማ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚደረግላቸዉ ድጋፍ ወቅቱን የጠበቀ
ስለመሆኑና እንዲሁም ከደረሱበት የእድገት ደረጃ አንጻር እየተመዘነ የሚሰጥ ስለመሆኑ በጠቅላላ
25399 ኢንተርፕራይዞች ከተጠየቁት መካከል 24725 (97.3 በመቶ) መልስ የሰጡ ሲሆን ይህም
አሀዝ ከተሳትፎ አንጻር እስከአሁን ካየነዉ ትልቁ ነዉ ለማለት ይቻላል፡፡ ኢንተርፕራይዞቹ ይህንኑ
አስመልክቶ ለቀረበላቸዉ ጥያቄ ከሰጡት ምላሽ ለመረዳት እንደተቻለዉና ከመለሱት መካከል
የተነጻጸረዉ መረጃ እንደሚያመለክተዉ ድጋፉ በዚህ አግባብ ሙሉ በሙሉ ይገኛል ያሉት 9.56
ከመቶ ሲሆኑ በከፊል ይገኛል ያሉት ደግሞ 54.95 በመቶ ናቸዉ፡፡ የሙሉና የከፊል ስምምነት
ድም ር 64.51 በመሆኑ ከግማሽ በላይ ይሁንታቸዉን እንደሰጡ ለመረዳት ይቻላል፡፡ ድጋፍ
ስለመገኘቱ ያልተቀበሉት 29.64 ከመቶ ሲሆኑ 5.76 ከመቶ ደግሞ ድጋፍ እንደሚገኝ ሆኖም ግን
ድጋፉ እንደዘርፉ ባህርይና የዕድገት ደረጃ እንደማይሰጥ ገልጸዋል፡፡ በዚሁ ዙሪያ ያለዉ አፈጻጸም
በአጠቃላይ መልኩ ሲታይ የተሻለ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነዉ፡፡

ለዚህ የቆጠራና የጥናት ስራ በተዘጋጀው ክፍት የጽሑፍ መጠይቅ ከተሰበሰበው መረጃ ለመረዳት
እንደተቻለው በንግድ ዘርፍ ብዛት ያለቸው ኢንተረፕራይዞች የተደራጁት በተለያዩ የንግድ ዘርፎች
ላይ ስለ ሆ ነ አንድ ዓይነት ስራ የሚሰሩት (እንደየዘርፋችን) በአንድ አካባቢ ላይ መሥራት
72
የሚችሉበት ሁኔታ እንዲፈጠር ይፈልጋሉ፡፡ ባለሱቆች በብዛት ሱቆቻቸውን ስለሚዘጉ ይህ እንዳይሆን
ክትትልና ድጋፍ እንዲደረግ፣ የስራ ተነሳሽነት የስልጠና ድጋፍ እንዲሰጥ ፣ ባዛር ላይ የሚሳተፉት
አምራቾች ብቻ ናቸው የሚለው መመሪያ እንዲሻሻልና ለነጋዴዎችም በባዛር ተጠቃሚ የሚሆኑበት
መንገድ እንዲመቻች፤ ሼድ የተሰጣቸው ማህበራትም ሆኑ ግለሰቦች በሙሉ ወደ ስራ እንዲገቡ ፣
ሼድ ወስደው ወደ ሥራ በማይገቡት ላይ ተገቢው እርምጃ እንዲወሰድ፤ የሚሰሩና የማይሰሩ
ኢንተርፕራይዞች ተለይተው ድጋፍ እንዲሰጥ ፣አመራሮች ወደ ታች ወርደው የሚሰሩትን ስራዎች
ማየትና መከታተል እንዲችሉ፣ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና እንዲሰጥ እና የኮሚፒዩተር
ሙያዊ ድጋፍ እንዲደረግ በሚል አስተያታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በአገልግሎት ዘርፍ የሚሰሩ ኢንተርፕራየዞች እንደዚሁ የደረጃ ለውጥ ላይ የተቀመጠው የብር


መጠን ዝቅ ቢል ኢንተርፕራይዞች አሁን ካሉበት ደረጃ ወደ ሌላ የማደግ አድል ይኖራቸዋል፤
የብድር አገልግሎት ለማግኘት የንብረት ዋስትና ስለሚጠየቅ ለዚህ ሌላ መፍትሔ ቢኖር፤ የመሰረተ
ልማት አቅርቦት ችግር (የመብራት፣ የውሃ የመንገድና የመሳሰሉት) ቢቀረፉ ኢንተርፕራይዞች
ስራቸው ውጤታማ ይሆናል፤ ህብረተሰቡ በግንዛቤ ማነስ ምክንያት የኢንተርፕራይዞቹን ስራ ዝቅ
አድርጎ የማየት ሁኔተዎች ስላሉ የግዛቤ ማስጨበጫ ስ ራዎ ች ቢ ሰሩ በሚል አስተያታቸውን
ሰጥተዋል፡፡

የኮንስትራክሽን ዘርፍም እንደዚሁ የመሠረት ልማት በተለይ የመንድ ችግር እና የጥሬ ዕቃ አቅርቦት
ችግሮች ቢቀረፉ፣ የማምረቻና የመሸጫ ቦታዎች በመቻቹልን ፣ የብድር አገልግሎትና የገበያ ትስስሩ
በበቂ ቢኖሩ እንደዚሁም የሚወጡት የስራ ትስስሮች ወቅታዊና ቀልጣፋ ቢሆኑ፤ የስራ ትስስሮቹ
አቅምን ያገናዘቡ ቢሆኑና ሥራ መስጠት ላይ ፍትሐዊነት ቢኖር፤ የሉት የድጋፍ ማዕቀፎች ላይ
ለኢንተረፕራይዞቹ በወቅቱ መረጃ ቢሰጥ፣ የፍትሐዊነት የተደራሽነት ስራ ተጠናክሮ ቢሰራ ፣ሥራው
ከተጠናቀቀ በኋላ የክፍያ ጊዜ ስለሚጓተት ቢስተካከል የሚሉ አስተያየቶችን ሰጥተዋል፡፡

ከአራዳ ክ/ከተማ በቃለ መጠይቅ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በስትራትጂክ የድጋፍ ማእቀፍ
የተሟላ ድጋፍ ማለት ኢንተርፕራይዙ በሚያስፈልገው መልኩ ድጋፍ መስጠት ሲሆን በዚህ መልኩ
ድጋፍ ያገኙ ኢንተርፕራይዞች እንዳሉ ተገልጧል፡፡ ነገር ግን ድጋፍ ያገኙና ያላገኙ ተብለው
በቁጥር የተለዩ እንደሌሉ እንዲሁ መረጃው ይገልፃል፡፡ እነዚህ በዓይነት ሲገለፁ በስራ አመራር፣
በጤና በስራ ፈጠራና በካይዝን የመሳሰሉት ሲሆን የሚሰጠው ስለልጣናም ሆነ ሊሰጥ የታሰበው
ስልጠና በተለያዩ ከኣቅም በላይ በሆኑ ምክኒያቶች ለምሳሌ የስልጠና ቦታ እጦት፣በዘርፉ ብቃት
ያለው አሰልጣኝ ያለመኖር፣ የበጀት ጉድለት መኖርና ለስልጠናው ትኩረት ያለመስጠት ችግር
በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

73

4.6 የኢንተርፕራይዞቹ የልማት አስተዋዕጾ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጥቃቅንነና አነስተኛ ዘርፍን ለማጠናከርና ለመደገፍ የሚረዱ
ፓኬጆችንና የሥራ ዘፎች ለይቶና አዋጭነታቸውን በማረጋገጥ በተግባር በማዋሉ በርካታ የሥራ
ዘርፎች ላይ ዜ ጎች ተደራጅተው ወደ ሥራ በመግባት ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን መርዳት
ከመቻላቸውም በላይ ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የሥራ እድል መፍጠርና አንዳንዶችም ወደ
መካከለኛ ባለሀብት ለመቀየር ችለዋል፡፡ ከዚህ አንጻር በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዘርፉ
የተደራጁ አንቀሳቃሾችና ያስገኙት የሥራ ዕድል በሚመለከት ዝርዝር ትንተና በሚከተሉት ክፍሎች
ቀርቧል፡፡

4.6.1 በኢንተርፕራይዞቹ የታቀፉ አባላት

ኢንተርፕራይዞች በተደራጁበት የመጀመሪያዎቹ አመታት የተመዘገቡት አባላት 139727 ሲሆኑ ከዚህ


ዉስጥ 83667(59.9%) ወንዶች ሲሆኑ 56060 (40.1%) ሴቶች ናቸዉ፡፡ የአባላቱ ሁኔታ በየክፍለ ከተማ
ሲታይ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ አባላት ተመዝግበዉ የነበሩት በየካ ክፍለ ከተማ ሲሆን ይህም ከጠቅላላዉ
22.8% ድርሻ ይይዛል፡፡ ከየካ ክፍለ ከተማ ቀጥሎ የተሻለ የኢንተርፕራይዞች አባላት የነበረዉ በንፋስ
ስልክ ክፍለ ከተማ ሲሆን 17.1% ድርሻ ነበረዉ፡፡ በአንፃራዊነት አነስተኛ የአባላት ቁጥር ያላቸዉ ክፍለ
ከተሞች ቂርቆስ (4.6%) እና አራዳ (5.2%) ናቸዉ፡፡ ኮልፌ፤ ጉለሌ፤ አቃቂ፤ ልደታ፤ ቦሌ እና አዲስ
ከተማ 10.8%፣9%፣8.6%፣7.7%፣6.7%፣ እና 5.8% አባላት ድርሻ እንደየቅደም ተከተላቸዉ ነበሩኣቸዉ፡፡

ሠንጠረዥ 34፡በኢንተርፕራይዞች መነሻ አደረጃጀት የተመዘገቡ አባላት ብዛት

���� ���� ���� ���


�/��� �� ��� ���
��� 3072 4179 7251
��� ��� 3500 3978 7478
�� 4139 10250 14389
�� 16812 15117 31929
��� ��� 3664 7529 11193
��� ��� ��� 8124 15737 23861
��� 4757 6869 11626
���� 2768 3718 6486
��� 3827 6578 10405
��� ���� 5397 9712 15109
��� 56060 83667 139727

የኢንተርፕራይዞችን አባላት አደረጃጀት በትምህርት ደረጃ ስንመለከት በመነሻ አደረጃጀት ወቅት


ከተመዘገቡት 139727 አባላት 96595 (24.5%) ከ1ኛ እስከ 12ኛ የትምህርት ደረጃ ያላቸዉ ሲሆን 21291

74
(15.2%) አባላት የኮሌጅ ድፕሎማ የትምህርት ደረጃ ያላቸዉ ናቸዉ፡፡የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት
ደረጃ ያላቸዉ 4576 (3.3%) ሲሆኑ ከመጀመሪያ ድግሪ በላይ ያላቸዉ አባላት 625 (0.4%) ብቻ ናቸዉ፡፡
ቀሪዎቹ 16640 (11.9%) አባላት ማንበብና መጻፍ የማይችሉ ሲሆኑ ከዚህ ዉስጥ አብዘኞቹ 57.9%
(9634) ሴቶች ናቸዉ፡፡ የኮሌጅ ድፕሎማ የትምህርት ደረጃ ካላቸዉ አባላት መካከልም አብዘኞቹ
(61.8%) ሴቶች ናቸዉ፡፡ ዲግሪና ከዲግሪ በላይ ካላቸዉ አባላት የወንዶች ቁጥር በእጅጉ የሚበልጥ መሆኑ
የጥናቱ ዉጤት ያሳያል፡፡ ይህም የሚያመለክተዉ በኢንተርፕራይዞች ከሚደራጁት አባላት በአንፃራዊነት
የተሻለ የትምህርት ደረጃ ያላቸዉ ወንዶች መሆኑን ነዉ፡፡

160000

140000

120000

100000

80000

60000

40000

20000

0
ማንበብና መጻፍ
1-12 ክፍል ዲፕሎማ ዲ ግሪ ከዲግሪ በላይ ድምር
የማይችል
ሲደራጅ የነበሩ አባላት ሴት 9634 31942 13152 1111 221 56060
ሲደራጅ የነበሩ አባላት ወንድ 7006 64653 8139 3465 404 83667
ሲደራጅ የነበሩ አባላት ድምር 16640 96595 21291 4576 625 139727

ግራፍ 11፡ በኢንተርፕራይዞች መነሻ አደረጃጀት የተመዘገቡ አባላት ብዛት በትምህርት ደረጃ
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በአጠቃላይ በ1996 ዓ.ም ከተመዘገቡት 139727 አባላት መካካል አሁን በሥራ ላይ ያሉት አባላት
116280 (83..2%) ሲሆኑ በየኢንተርፕራይዙ የአባላት ቁጥር ለመቀነስ መነሻ ምክንያት ይሆናሉ ተብለዉ
ከታሳቡ ምክንያቶች የየራሳቸዉን ሀሳብ እንዲሠጡ የኢንተርፕራይዞች አንቀሳቃሾች ተጠይቀዉ አብዘኞቹ
የሰጡት ምክንያት በዋናነት በአባላት መካከል የሚፈጠር አለመግባባት፣ ኪሳራና ለሚያመርቱት ወይም
ለሚሰጡት አገልግሎት በቂ ገበያ ያለማግኘት እንደሆነ የጥናቱ ዉጤት ያመላክታል፡፡በአባላት መካከል
ለግጭትና አለመግባበት መነሻ የሚሆነዉ ኢንተርፕራይዞች ሲደራጁ የሙያ ስብጥርና ተስማሚነት ከግምት
ውስጥ ስለማይገባ የኢንተርፕራይዞች አባላት ከመስማማት ይልቅ ለግጭትና ያለመስማማት ይዳረጋሉ፡፡
ከተለያየ የሙያ ዘርፍ በአንድነት ሲደራጁ ከፍተቱን ለመሙላት ረዥም ጊዜ የሚጠይቅ በመሆኑ በዚህ
ዙሪያ ከመነሻዉ አንስቶ በቂ ኦረንተሸን መስጠት ያስፈልጋል፡፡ አሁን ባሉት ኢንተርፕራይዞች ዉስጥ

75
ከሚገኙት አባላት 85792 (73.8%) ወንዶች እና 30488 (26.2%) ሴቶች ናቸዉ፡፡ይህም የሚያመለክተዉ
የከተማዉ ህዝብ አጋማሽ የሚሆነዉ ድርሻ ያላቸዉ ሴቶች በኢንተርፕራይዞች ልማት ያላቸዉ ተሳትፎ
አነስተኛ መሆኑን ነዉ፡፡

140000

120000

100000

80000

60000

40000

20000

0
አዲስ አቃቂ ንፋስ ኮልፊ
አ ራዳ ቦሌ የካ ጉለሌ ቂርቆስ ልዳታ ድምር
ከተማ ቃሊ ቲ ስልክ ቀራንዬ
አሁን ያሉ አባላት ብዛት ሴት 2439 2222 2441 4557 2774 4078 3499 2256 2614 3608 30488
አሁን ያሉ አባላት ብዛት ወንድ 3157 3378 6149 40278 5538 7951 5667 2852 4631 6181 85792
አሁን ያሉ አባላት ብዛት ድምር 5596 5600 8590 44835 8312 12029 9166 5108 7245 9789 116280

ግራፍ 12፡ አሁን በሥራ ላይ ባሉ ኢንተርፕራይዞች የተመዘገቡ የአባላት ብዛት


ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
አሁን በሥራ ላይ ካሉት አባላት መካከል ከፍተኛዉን ድርሻ (38.6%) የያዘዉ የየካ ክፍለ ከተማ ሲሆን
የንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ 13.2% ድርሻ ያለዉ ሲሆን ቀጥሎ ኮልፌ 11.7% የአባላት ድርሻ ያለዉ ክፍለ
ከተማ ነዉ፡፡ ጉለሌ፣ አቃቂ ቃሊቲ፣ልደታ፣ አዲስ ከተማ እና አራዳ ክፍለ ከተሞች
11.5%፣10.4%፣8.6%፣7.3%፣6.9% አባላት ድርሻ እንደየቅደም ተከተላቸዉ አላቸዉ፡፡ ቂርቆስ እና ቦሌ
6.3% እና 5.6% ድርሻ በቅደም ተከተል በመያዝ ዝቅተኛ የኢንተርፕራይዞች አባላት ቁጥር ያላቸዉ
ክፍለ ከተሞች ናቸዉ፡፡

ከታች በሠንጠረዥ እንደተመለከተዉ አሁን ያሉ ኢንተርፕራይዞች አባላት በትምህርት ደረጃ ስንመለከት


ከ116280 አባላት መካከል 79.0% ከ1ኛ እስከ 12ኛ የትምህርት ደረጃ ያላቸዉ ሲሆን 8.2% አባላት
የኮሌጅ ድፕሎማ የትምህርት ደረጃ ያላቸዉ ናቸዉ፡፡የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ያለቸዉ 3.5%
ሲሆኑ ከመጀመሪያ ድግሪ በላይ ያላቸዉ አባላት 0.4% ብቻ ናቸዉ፡፡ ቀሪዎቹ 8.9% አባላት ማንበብና
መጻፍ የማይችሉ ናቸዉ፡፡

76

ሠንጠረዥ 35፡ ኢንተርፕራይዞች የአባላት ብዛት በትምህርት ደረጃ


��� �� ����
������ ��� �� ��� ���
����� ��� ����� 5868 4426 10294
1-12 ��� 20775 71073 91848
���� 2734 6769 9503
��� 958 3165 4123
���� ��� 153 359 512
��� 30488 85792 116280
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
ከዚህ በታች በግራፍ 14 እንደተመለከተዉ በተግባር ላይ ባሉት ኢንተርፕራይዞች ከተመዘገቡት አባላት
መካከል 38% (44204)እድሜያቸዉ ከ18-28 አመት ባለዉ የአድሜ ክልል የሚገኙ ናቸዉ፡፡እድሜያቸዉ
ከ29-39አመት ክልል ዉስጥ የሚገኙት 40.1% (47567) ሲሆኑ 40 እና ከዚያ በላይ አመት የሆኑት
አባላት 21.1% (24509)ናቸዉ፡፡

ድምር

40 እና በላይ

29-39

18-28

0 20000 40000 60000 80000 100000 120000 140000

ግራፍ 13፡ ኢንተርፕራይዞች የአባላት ብዛት በዕድሜ


ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
4.6.2 የተፈጠሩ የሥራ ዕድሎች

ኢንተርፕራይዞቹ ከተደራጁባቸዉ አላማዎች ዋነኛዉ ለራሳቸዉ ሥራ ፈጥረዉ ከዚያም


ለቤተሰቦቻቸዉና ለህብረተሰቡ የሥራ ዕድል መፍጠር እንደሆነ ተደጋግሞ የተገለጸ ጉዳይ ነዉ፡፡
በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ በከተሞቻችን ሰፊ የስራ ዕድል እንዲፈጠር
በማድረግ በርካታ ወጣቶችና ሴቶች የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ ዘርፉን ከመደገፍና

77
ከማብቃትም አኳያ የአደረጃጀት፣ የስልጠና፣ የብድር፣ የመሥሪያና የመሸጫ ቦታ፣ የገበያ፣የመረጃና
ሌሎች ድጋፎችን በመስጠት በዘርፉ ለተሰማሩ በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሥራ ዕድል በመፍጠር
የተሻለ ኑሮና ገቢ እንዲኖራቸዉ ጥረት ተደርጓል፡፡ በዚህ መሠረት በርካታ የሥራ ዘርፎች ላይ
ዜጎች ተደራጅተው ወደ ሥራ በመግባት ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን መርዳት ከመቻላቸውም በላይ
ከራሳቸው አልፈው ሌሎች ቁጥራቸዉ ቀላል ለማይባል በርካታ ሥራ ፈላጊዎች ወጣቶችና ሴቶች
የሥራ እድል መፍጠርና አንዳንዶችም ወደ መካከለኛ ባለሀብት ለመቀየር ችለዋል፡፡በዚህ ዘርፍ
የከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ምሩቃኖችም ጭምር ወደ ዘርፉ መቀላቀል ችለዋል፡፡
በመሆኑም በአዲስ አበባ ከተማ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ለ14225 ቋሚና ለ51289 ጊዜያዊ
በድምሩ ለ65514 ሥራ ፈላጊዎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ተችሏል፡፡ ይሁን እንጂ አጠቃላይ
በከተማዉ ከሚኖሩ ስራ ፈላጊ ዜጎች አንጻር ሲመዘን የተፈጠረዉ የሥራ ዕድል ይህንን ፍላጎት
የሚመጥን እንዳልሆነ መረዳት ይቻላል፡፡

ሠንጠረዥ 36፡ ከአባላት ወጭ በኢንተርፕራይዞች የተፈጠረ ቋሚ እና ጊዜያዊ የስራ እድል

ቋሚ ጊዜያዊ አጠቃላይ ድምር


ክ/ከተማ ሴት ወንድ ድምር ሴት ወንድ ድምር ሴት ወንድ ድምር
አራዳ 328 458 786 868 2928 3796 1196 3386 4582
አዲስ ከተማ 198 300 498 728 1143 1871 926 1443 2369
ቦሌ 604 1212 1816 1560 4744 6304 2164 5956 8120
የካ 736 1370 2106 2328 6031 8359 3064 7401 10465
አቃቂ ቃሊቲ 444 399 843 1469 4307 5776 1913 4706 6619
ንፋስ ስልክ ላፍቶ 884 1433 2317 3103 6704 9807 3987 8137 12124
ጉለሌ 1295 1556 2851 1310 2627 3937 2605 4183 6788
ቂርቆስ 442 503 945 1211 3128 4339 1653 3631 5284
ልዳታ 156 265 421 577 1248 1825 733 1513 2246
ኮልፊ ቀራንዬ 643 999 1642 1241 4034 5275 1884 5033 6917
ድምር 5730 8495 14225 14395 36894 51289 20125 45389 65514
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በአጠቃላይ የስራ ዕድል ፈጠራ ስራዉ በርካታ ተግዳሮቶች እንደነበሩት ከመስክ በቃለ መጠይቅና
ምልከታ የተገኘዉ መረጃ ያስረዳል፡፡ በየዓመቱ የሚደረገው የስራ ፈላጊዎች ልየታና ምዝገባ በጠራ መረጃ
ላይ ተመስርቶ እንዲመዘገቡ በማድረግና አማራጭ የስራ ዕድሎች ምን እንደሆኑ ለይቶ በመያዝ ስራ ፈላጊ
ዜጎች ተገቢውን ግንዛቤ እንዲያገኙ በማድረግ ወደ ስራ ከማሰማራት አንጻር እጥረት ያለበት መሆኑን
ጥናቱ ያመለክታል፡፡ በየክፍለ ከተማ የተፈጠረው የስራ ዕድልም ቢሆን ከድግግሞሽ ነጻ በሆነ አኳኋን
በጠራ የመረጃ /data base/ ስርዓት የስራ ስምሪት እንዲያገኝ ባለመደረጉ አንድ ስራ የተፈጠረለት ዜጋ
(በተለይ በጊዜያዊ ስራ ዕድል) ከአንድና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ሪፖርት ሊደረግ የሚችልበት ዕድል ዝግ
እንዳልነበረ ለጥናቱ ከተሰበሰበዉ መረጃ መገንዘብ ይቻላል፡፡ የመረጃ ስርዓቱን በአንድ ማዕከል አገልግሎት

78
ላይ በማዘመን የመረጃ ጥራቱና ተዓማኒነቱ በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ በቀጣይ ሰፊ ስራ መስራት
ይጠይቃል፡፡

ከላይ ለማቅረብ እንደተሞከረው አጠቃላይ ስራ ዕድል ፈጠራው የተሻለ ቢሆንም የኢንተርፕራይዝ ልማቱን
ከማስፋፋት አንጻር የሚፈጠሩ አብዛኞቹ የስራ ዕድሎች በቋሚ ስራ ላይ በተለይም በአምራች ዘርፉ ላይ
እንዲሆን ከማድረግ አንጻር ብዙ መሥራት ይጠበቃል፡፡ ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠሪያ አማራጮች
የመኖራቸውን ያህል በዚህ ዘርፍ የሚሰማሩ ዜጎች ዝርዝር መረጃ ከመያዝ አንስቶ ተከታታይ የሆነ ግንዛቤ
በመፍጠርና በማሳመን ላይ የተመሰረተ የማያቋርጥ የቁጠባ ሥርዓት እንዲፈጠር በጥብቅ ዲሲፕሊን ቢሰራ
ኖሮ በስትራተጂው መሰረት በርካቶችን ወደ መካከለኛ ኢንዱስትሪ በማሸጋገር ቋሚ ስራ ዕድል መፍጠር
ይቻል ነበር፡፡

79
4.7 በተላያዩ ምክንያቶች የከሰሙ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች

ኢንተርፕራይዞች እንዲከስሙ የተለያዩ ውስጣዊና ዉጫዊ ምክንያቶች አስተዋዕጾ ያደርጋሉ፡፡


የኢንተርፕራይዞቹ የዕድገት ማነቆዎች በወቅቱና በአግባቡ ካልተፈቱ ውለው አድረዉ
ኢንተርፕራይዞቹን ማክሰማቸዉ አይቀርም፡፡

4.7.1 የከሰሙ ኢንተርፕራይዞች ስራ ያቆሙበት ዘመን

የተዘጉ

የኢንተርፕራይዝች ሁኔታ
የኢንተርፕራይዝች ብዛት

ለሦስተኛ ወገን የተላለፉ

የተዘጉበት/ለሦስተኛ ወገን የተላለፉበት ዘመን


ግራፍ 14፡ የከሰሙ ኢንተርፕራይዞች የተዘጉበት ወይም ለሶስተኛ ወገን የተለለፉበት ዘመን
ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ
በግራፉ እንደተመለከተው የከሰሙ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ
የተዘጉበት/ለሦስተኛ ወገን የተላለፉበት ዘመን ሲታይ ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ እየጨመረ የመጣ ቢሆንም
በ2007 ዓ.ም ከፍተኛ የቁጥር ዕድገት(ከ30% በላይ) ታይቷል ፡፡ ስለዚህ መንግስት ምክንያቱን አዉቆ
በጥናት ላይ የተመሰረተ መፍትሄ ሊስጥ ይገባል፡፡

80
4.7.2 ኢንተርፕራይዞቹ አሁን ያሉበት ሁኔታ

ሠንጠረዥ 37 የከሰሙ ኢንተርፕራይዞች ሁኔታ


የኢንተርፕራይዙ አይነት
አሁን ያለበት ሁኔታ ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
የከሰመ 3304 152 3456 (95.5%)
ለሶስተኛ ወገን የተላለፉ 142 1 153 (4.2%)
ሪፖርት ያላደረጉ 17 1 18 (0.5%)
ድ ምር 3463 (95.7%) 154 (4.3%) 3617

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በሰንጠረዥ 37 እንደተመለከተው አብዛኛዎቹ (95.5%) ከናካቴው ስራ ያቆሙ ሲሆን በጣም ጥቂት
የሚሆኑት (4.2%) ደግሞ ለሶስተኛ ወገን የተላለፉ ናቸው፡፡ የከሰሙት ወይንም ለሶስተኛ ወገን
የተላለፉትኢንተርፕራይዞች በአይነት ሲታይም 95.7%ቱ ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ሲሆኑ 4.3%ቱ
ደግሞ አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ናቸው፡፡ ይህ የሚያሳየዉ ብዙዎቹ ጥቃቅን ላይ አንዳሉ የሚከስሙ
እንደሆነና ልዩ ትኩረት የሚሻ መሆኑን ነው፡፡

ሠንጠረዥ 38፡ የከሰሙ ኢንተርፕራይዞች ሁኔታ በክፍለ ከተማ


ኢንተርፕራይዙ አሁን ያለበት ሁኔታ
ክ/ከተማ የከሰመ ለሶስተኛ ወገን የተላለፈ ድ ምር
አራዳ 220 52 272 (7.52%)
አዲስ ከተማ 505 42 547 (15.12%)
ቦሌ 70 0 70 (1.94%)
የካ 495 9 504 (13.93%)
አቃቂ ቃሊቲ 209 0 209 (5.78%)
ንፋስ ስልክ 263 1 264 (7.3%)
ጉለሌ 408 13 421 (11.64%)
ቂርቆስ 222 21 243 (6.72%)
ልደታ 196 3 199 (5.5%)
ኮለፌ ቀራንዮ 884 4 888 (24.55%)
ድ ምር 3472 145 3617

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


የከሰሙ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ስርጭት በክ/ከተማ ሲታይ አብዛኛዎቹ ኮልፌ ቀራንዮ
የሚገኙ ሲሆን በአዲስ ከተማ፣ የካ እና ጉለሌ ክ/ከተማም እንዲሁ በርካታ ኢንተርፕራይዞች
ከስመዋል፡፡ ለሶስተኛ ወገን የተላለፉትን ስናይ ግን በብዛት አራዳክ/ከተማ ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡
በቂርቆስ እና ጉለሌ ክ/ከተሞችም እንዲሁ የተወሰኑ ለሶስተኛ ወገን ተላልፈዋል፡፡ በነዚህ ክ/ከተሞች
ኤጀንሲው የችግሩን ምንጭ ፈትሾ መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል፡፡

81
4.7.3 ኢንተርፕራይዞች ለሦስተኛ ወገን የተላለፉበት ምክንያት

ሠንጠረዥ 39፡ ኢንተርፕራይዞች ለሶስተኛ ወገን የተላለፉበት ሁኔታ በክ/ከተማ


የተላለፈበትሁኔታ
ክ/ከተማ በስጦታ በ ው ክል ና በኪራይ በሽያጭ ሌላ ድ ምር
አራዳ 2 14 32 0 4 52
አዲስከተማ 0 5 34 1 2 42
ቦሌ 0 0 0 0 0 0
የካ 0 2 5 0 2 9
አቃቂቃሊቲ 0 0 0 0 0 0
ንፋስስልክ 0 0 1 0 0 1
ጉለሌ 3 4 4 2 0 13
ቂርቆስ 0 21 0 0 0 21
ልደታ 0 1 1 1 0 3
ኮለፌቀራንዮ 0 0 4 0 0 4
ድ ምር 5 47 81 4 8 145

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በሠንጠረዥ39 እንደተመለከተው ለሶስተኛ ወገን የተላለፉ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
የተላለፉበት ሁኔታ 81 በኪራይ፣ 47ቱ በዉክልና፣ 5ቱ በስጦታ፣ 4ቱ በሽያጭ እና 8ቱ በሌሎች
ምክንያቶች ነው፡፡ አንቀሳቃሾች በአብዛኛው በኪራይ ወይም በውክልና ለሌሎች ያስተላለፉት የድጋፍ
ወይም የአቅም ማነስ ሊሆን ስለሚችል ኤጀንሲው ትኩረት ሊሰጥበት ይገባል፡፡

4.7.4 የኢንተርፕራይዞችአይነት

ሠንጠረዥ 40፡ የከሰሙ/ለሶስተኛ ወገን የተላለፉ ኢንተርፕራይዞች አይነት በክ/ከተማ


ኢንተርፕራይዙ አይነት
ክ/ከተማ ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
አራዳ 259 13 272 (7.52%)
አዲስ ከተማ 544 3 547 (15.12%)
ቦሌ 59 11 70 (1.94%)
የካ 478 26 504 (13.93%)
አቃቂ ቃሊቲ 207 2 209 (5.78%)
ንፋስ ስልክ 232 32 264 (7.3%)
ጉለሌ 406 15 421 (11.64%)
ቂርቆስ 238 5 243 (6.72%)
ልደታ 175 24 199 (5.5%)
ኮለፌ ቀራንዮ 865 23 888 (24.55%)
ድ ምር 3463 (95.74%) 154 (4.26%) 3617

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በሠንጠረዥ 40 እንደተመለከተው ከከሰሙት ወይም ለሶስተኛ ወገን ከተላለፉት ኢንተርፕራይዞች
መካከል 95.74%ቱ ጥቃቅን ሲሆኑ 4.26%ቱ ደግሞ አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ናቸው፡፡
82
ስርጭታቸዉ በክ/ከተማ ሲታይ አብዛኛዎቹ (24.55%) በኮለፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ የሚገኙ ሲሆን
15.12%ቱ በአዲስ ከ ተማ ፣13.93%ቱ በየካ ክ/ከተማ እንዲሁም 11.64%ቱ በጉለሌ ክ/ከተማ
ይገኛሉ፡፡ በጣም ዝቅተኛ ቁጥር ያለቸው ኢንተርፕራይዞች የከሰሙት ቦሌክ/ከተማ ነው፡፡ ስለዚህ
የአዲስ አበባ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ኤጀንሲ ከአዲስ ከተማ ፣ ከኮለፌ ቀራንዮ፣
ከየካ፣ከጉለሌ የድጋፍ አሰጣጡን ማሻሻል ይኖርበታል፡፡

4.7.5 የኢንተርፕራይዞች ህጋዊ አደረጃጀት


ሠንጠረዥ 41፡ የከሰሙ/ለሶስተኛ ወገን የተላለፉ ኢንተርፕራይዞች ህጋዊ አደረጃጀት
ኢንተርፕራይዞቹ ያሉበት ሁኔታ
ህጋዊ አደረጃጀት የከሰመ ለሶስተኛ ወገን የተላለፈ ድ ምር
በግል 1130 135 1265 (34.97%)
በህብረት/ሽርክና 877 5 884 (24.44%)
ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር 207 0 207 (5.72%)
በህብረት ሥራ ማህበር 992 5 997 (27.56%)
በአክሲዮን ማህበር 36 0 36 (1.0%)
ሌላ 228 0 228 (6.3%)
ድ ምር 3472 145 3617

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በሰንጠረዥ 41 እንደተመለከተው ከከሰሙት ወይም ለሶስተኛ ወገን ከተላለፉት ኢንተርፕራይዞች
መካከል ትልቁን ድርሻ የያዙት በግል ተይዘው የነበሩ (34.97%) ሲሆን በህብረት ሥራ ማህበር
(27.56%) እና በህብረት ሽርክና (24.44%) ሁለተኛና ሦስተኛ ደረጃን ይይዛሉ፡፡
4.7.6 ኢንተርፕራይዞች ተሰማርተዉበት የነበረ ዋና የስራ ዘርፍ
ሠንጠረዥ 42፡ ኢንተርፕራይዞቹ ተሰማርተዉበት የነበረ ዋና የስራ ዘርፍ በክ/ከተማ
የስራዘርፍ
ክ/ከተማ ማኑፋክቸሪንግ ኮንስትራክሽን አገልግሎት ከተማግብርና ንግድ ድ ምር
አራዳ 40 55 53 5 118 272
አዲስ ከተማ 256 100 77 30 84 547
ቦሌ 20 29 11 4 6 70
የካ 22 366 19 3 94 504
አቃቂ ቃሊቲ 46 82 44 8 29 209
ንፋስ ስልክ 49 137 39 2 37 264
ጉለሌ 131 137 69 47 37 421
ቂርቆስ 36 57 26 1 123 243
ልደታ 52 111 24 10 2 199
ኮለፌ ቀራንዮ 313 243 132 115 85 888
965 1318 494 225 615 3617
ድ ምር 26.68% 36.44% 13.66% 6.22% 17.00%

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በሰንጠረዥ 42 እንደተመለከተው የከሰሙ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ተሰማርተውባቸው
ከነበሩ ዋና ዋና የስራ ዘርፎች መካከል ኮንስትራክሽን (36.44%) የመጀመሪያውን ደረጃ ይይዛል፡፡
83
ማኑፋክቸሪንግ (26.68%) እና ንግድ (17%) ሁለተኛና ሦስተኛ ደረጃን ይይዛሉ፡፡ አገልግሎት
(13.66%) እና ከተማ ግብርና (6.22%) አራተኛና አምስተኛ ደረጃ ላይ ናቸው፡፡ ይህ ማለት ከ60%
በላይ ችግሩ ያለዉ ኮንስትራክሽንና ማኑፋክቸሪንግ ሴክተር ላይ ነዉ፡፡ ይህ ደግሞ መንግስት
ካስቀመጠው የትኩረት አቅጣጫ አንጻር ሲታይ መፍትሄ የሚሻ ጉዳይ ነዉ፡፡

4.7.7 ኢንተርፕራይዞች ተሰማርተዉበት የነበረ ንዑስ የስራ ዘርፍ

ሠንጠረዥ 43፡ የከሰሙ/የተላለፉ ኢንተርፕራይዞች በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ


የኢንተርፕራይዙ አይነት
ንዑስ ዘርፍ
ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
ጨርቃ ጨርቅና ስፌት 125 3 128 (13.21%)
ቆዳና የቆዳ ውጤቶች 103 0 103 (10.63%)
የምግብና መጠጥ ዝግጅት 377 9 386 (39.83%)
የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ምርቶች 91 6 97 (10.1%)
የእንጨት ሥራዎች 153 6 159 (16.41%)
ባህላዊ የዕደ ጥበብና ጌጣጌጥ ሥራዎች 17 0 17 (1.75%)
አግሮ ፕሮሰሲንግ 11 0 11 (1.14%)
የግንባታ ግብዓት ምርቶች 39 9 48 (4.95%)
ሌሎች ንዑስ ዘርፎች 20 0 20 (2.06%)
ድ ምር 936 33 969

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በሠንጠረዥ 43 እንደተመለከተው ከከሰሙ የማኑፋክቸሪንግ ጥቃቅንና አነስተኛ ንዑስ ዘርፍ መካከል
አብዛኛዎቹ(39.83%)በምግብና መጠጥ ዝግጅት የተሰማሩት ናቸው፡፡በእንጨት ሥራዎች፣ ጨርቃ ጨርቅና
ስፌት እና ቆዳና የቆዳ ውጤቶች ተሰማርተው የነበሩ በርካታ ኢንተርፕራይዞችምእንደዚሁ ከስመዋል፡፡ እነዚህ
የከሰሙ ንዑስ ዘርፎች ከመንግስት የትኩረት አቅጣጫ አንጻር መጠናከር የሚገባቸው ነበሩ፡፡

ሠንጠረዥ 44፡ የከሰሙ/የተላለፉ በኮንስትራክሽን ዘርፍ


የኢንተርፕራይዙ አይነት
ንዑስ ዘርፍ
ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
ሥራ ተቋራጭነት 220 23 243 (21.72%)
ንዑስ ሥራ ተቋራጭነ 122 7 129 (11.53%)
ባህላዊ የማዕድን ሥራዎች 18 1 19 (1.70%)
ኮብል ስቶን ሥራዎች 566 7 573 (51.21%)
የመሠረተ ልማት ግንባታ ንዑስ ተቋራጭነት 71 26 97 (8.67%)
የከበሩ ድንጋይ ልማት 16 0 16 (1.43%)
ሌሎች ንዑስ ዘርፎች 42 0 42 (3.75%)
ድ ምር 1055 64 1119

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በሠንጠረዥ 44 እንደተመለከተው በኮንስትራክሽን ንዑስ ዘርፍ ከከሰሙት ዉስጥ ከግማሽ በላይ
የሚሆኑት በኮብል ስቶን ሥራዎች የተሰማሩ ናቸዉ፡፡ እንደዚሁም በሥራ ተቋራጭነት እና ንዑስ
ሥራ ተቋራጭነት የተሰማሩ በርከት ያሉ ኢንተርፕራይዞች ከስመዋል ወይም ስራ አቋርጠዋል፡፡

84
የአዲስ አበባ አስተዳደር በኮብል ስቶን ሥራዎች የተሰማሩኢንተርፕራይዞችን ሲያበረታታ የነበረ
ቢሆንም ለምን አብዛኛዎቹ እንደከሰሙ ለማወቅ ተጨማሪ መረጃ ያስፈልጋል፡፡

ሠንጠረዥ 45፡ የከሰሙ/የተላለፉ በአገልግሎት ዘርፍ


የኢንተርፕራይዙ አይነት
ንዑስ ዘርፍ
ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
የገጠር አነስተኛ ትራንስፖረት አገልግሎት 2 0 2 (0.45%)
ካፌና ሬስቶራንት 79 2 81 (18.12%)
የማከማቻ አገልግሎት 1 0 1 (0.22%)
የማሸጊያ አገልግሎት 0 1 1 (0.22%)
የሥራ አመራር አገልግሎት 5 0 5 (1.12%)
የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት 28 4 32 (7.16%)
የፕሮጀክት ኢንጂነሪንግ አገልግሎት 1 0 1 (0.22%)
የምርት ዲዛይንና ልማት አገልግሎት 12 1 13 (2.91%)
የግቢ ውበት፤ የጥበቃ እና ጽዳት አገልግሎት 34 0 34 (7.61%)
የጥገና አገልግሎት 38 0 38 (8.5%)
የውበት ሳሎን ሥራዎች 82 1 83 (18.57%)
የኤሌክትሮኒክስና ሶፍት ዌር ልማት 28 5 33 (7.38%)
የዲኮር ሥራ 6 0 6 (1.34%)
ኢንተርኔት ካፌ 10 0 10 (2.24%)
ሌሎች ንዑስ ዘርፎች 107 0 107 (23.94%)
ድ ምር 433 14 447

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በሠንጠረዥ 45 እንደተመለከተው በአገልግሎት ዘርፍ በተለይ ካፌና ሬስቶራንት እንዲሁም የውበት ሳሎን
ሥራዎች ንዑስ ዘርፍ ላይ ከሌሎች አንጻር ሲታይ ብዙ ኢንተርፕራይዞች ከስመዋል ወይም ስራ አቋርጠዋል፡፡

ሠንጠረዥ 46፡ የከሰሙ/የተላለፉ በከተማ ግብርና ዘርፍ


የኢንተርፕራይዙ አይነት
ንዑስ ዘርፍ
ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
ዘመናዊ የእንስሳት እርባታ 39 4 43 (19.72%)
የዶሮ እርባታ 141 0 141 (64.68%)
የንብ ማንባት 2 0 2 (0.92%)
የእንስሳት መኖ ዝግጅት 1 0 1 (0.46%)
ዘመናዊ የደን ልማት 3 0 3 (1.38%)
አትክልትና ፍራፋሬ 12 0 12 (5.5%)
ሌሎች ንዑስ ዘርፎች 16 0 16 (7.34%)
ድ ምር 214 4 218

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በሰንጠረዥ 46 እንደታየው ከ85% በላይ በዘመናዊ የእንስሳት እርባታና የዶሮ እርባታ የተሰማሩ
የከተማ ግብርና ዘርፍ ኢንተርፕራይዞች ከስመዋል ወይም ስራ አቋርጠዋል፡፡ ለወደፊቱ ተመሳሳይ
ችግር እንዳያጋትም ልዩ ትኩረት ያስፈልጋል፡፡

85
ሠንጠረዥ 47፡ የከሰሙ/የተላለፉ በንግድ ዘርፍ
የንግድ ዘርፍ
ንዑስ ዘርፍ
ጥቃቅን አነስተኛ ድ ምር
የሀገር ውስጥ ምርቶች ጅምላ ሽያጭ 14 3 17 (3.24%)
የሀገር ውስጥ ምርቶች ችርቻሮ ንግድ 489 6 495 (94.29%)
የጥሬ ዕቃ አቅርቦት 6 0 6 (1.14%)
ሌሎች ንዑስ ዘርፎች 7 0 7 (1.33%)
ድ ምር 516 9 525

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በንግድ ዘርፍም እንደዚሁ ከ94% በላይ የከሰሙት በሀገር ውስጥ ምርቶች ችርቻሮ ንግድ የተሰማሩት
ናቸው፡፡ ለዚህም ዋነኛው ምክንያት ቀደም ሲል እንደተመለከትነው 90 ከመቶ የሚደርሱት
ኢንተርፕራይዞች ደረጃ ጥቃቅን እና በስፋት የከሰሙትም እነኚሁ ከመሆናቸዉ ጋር ይያያዛል፡፡

4.7.8 ኢንተርፕራይዞች ሲቋቋሙ እና ስራ ሲያቆሙ የነበራቸዉ የዕድገት ደረጃ

ሠንጠረዥ 48፡ ኢንተርፕራይዞቹ ሲቋቋሙ እና ስራ ሲያቆሙ የነበራቸዉ የዕድገት ደረጃ


የዕድገትደረጃ ሲቋቋሙ ስራ ሲያቆሙ
የምስረታ/ጀማሪ 3557 3446
የታዳጊ/መስፋፋት 12 62
የመብቃት - 10
ታዳጊ መካከለኛ 1 8
ድ ምር 3570 3526

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በሠንጠረዥ 48 እንደታየው አብዛኛዎቹ ኢንተርፕራይዞች ስራ ሲያቆሙ በምስረታ/ጀማሪ የዕድገት
ደረጃ ላይ የነበሩ ናቸው፡፡ ይህ የሚያሳየዉ በዚህ የዕድገት ደረጃ ላይ ትኩረት መሰጠት እንዳለበትና
አስፈላጊውን ድጋፍ በመስጠት ወደሚቀጥለው ደረጃ እንዲተላለፉ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

86
4.7.9 ለኢንተርፕራይዞች የተሰጠ የድጋፍ አይነት

ሠንጠረዥ 49 ለኢንተርፕራይዙ የተሰጡ የድጋፍ አይነቶች


የድጋፍ አይነቶች በቁጥር %
የስራ ፈጠራ ክህሎት ስልጠና 1589 43.9
የንግድ ክህሎት ስልጠና 1070 29.6
የግብይት ማሳደጊያ ስልጠና 610 16.9
የካይዘን ስልጠና 304 8.4
የቴክኖሎጅ ድጋፍ 64 1.8
የመስሪያ ቦታ ድጋፍ 593 16.4
የመሸጫ ቦታ ድጋፍ 519 14.3
የብድር ድጋፍ 181 5.0
የገበያ/የስራ ትስስር ድጋፍ 497 13.7
የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ 260 7.2
ሌላ ካለ 41 1.1

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በሠንጠረዥ 49 እንደሚታየው በአዲስ አበባ አስተዳደር ለኢንተርፕራይዞቹ የተሰጡ ድጋፎች የስራ
ፈጠራ ክህሎት ስልጠና (43.9%)፣ የንግድ ክህሎት ስልጠና (29.6%)፣ የግብይት ማሳደጊያ ስልጠና
(16.9%)፣ የመስሪያ ቦታ ድጋፍ (16.4%)፣ የመሸጫ ቦታ ድጋፍ (14.3%)፣የገበያ/የስራ ትስስር ድጋፍ
(13.7%) ወዘተ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ ምንም እንኳን ከላ የተጠቀሱት ድጋፎች የተሰጡ ቢሆን በቂ
ባለመሆኑ ሊከስሙ ችለዋል፡፡

4.7.10 ኢንተርፕራይዞች የከሰሙበት ምክንያት

ሠንጠረዥ 50፡ ኢንተርፕራይዙ የከሰመባቸው/ለሦስተኛ ወገን የተላለፈባቸው ምክንያቶች


የከሰሙበት ምክንያት ቁጥር %
የእርስበርስግጭት 448 12.4
ዘርፍበመቀየር 296 8.2
በመክሰር ወይም ገበያበማጣት 1327 36.7
የስልጠናና ምክር አገልግሎት ባለማግኘት 169 4.7
ተወዳዳሪ መሆን ባለመቻል 939 26
የመስሪያና መሸጫ ቦታ ባለማግኘት 609 16.8
የብድር ድጋፍ ባለማግኘት 280 7.7
ሌላ ካለ ይፃፉ 629 17.4

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


በሠንጠረዥ 50 እንደተገለጸው ኢንተርፕራይዞች ከከሰሙባቸው/ለሦስተኛ ወገን ከተላለፉባቸው
ምክንያቶች ዋናዎቹ በመክሰር/ገበያ በማጣት፣ ተወዳዳሪ መሆን ባለመቻል፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታ
ባለማግኘት እና የእርስ በርስ ግጭት በቅደም ተከተል ይገኙበታል፡፡ እነዚህ ደግሞ በመግስት ድጋፍ
ሊስተካከሉ የሚችሉ ነበሩ፡፡

87
4.7.11 ኢንተርፕራይዞች ሲደራጁና ስራ ሲያቆሙ የነበራቸዉ የአባላት ብዛት

ሠንጠረዥ 51፡ ኢንተርፕራይዞች ሲደራጁና ስራ ሲያቆሙ የነበራቸዉ የአባላት ብዛት

እ ድሜ ሲደራጁ የነበራቸዉ አባላት ብዛት ስራ ሲያቆሙ የነበራቸዉ አባላት ብዛት


ሴት ወንድ ድ ምር ሴት ወንድ ድ ምር
18-28 3644 8635 12247 2345 5531 7828
29-39 2245 2748 4978 1719 2326 4004
ከ 40 በላይ 621 541 1126 510 499 994
ድ ምር 6510 11924 18351 4574 8356 12826
አካል ጉዳተኛ ካለ 17 47 59 15 43 58
ጠ. ድምር 6527 11971 18410 4589 8399 12884

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ


የአዲስ ከተማን ሳይጨምር በሌሎች ክ/ከተሞች የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች ሲደራጅና ስራ ሲያቆሙ
የነበራቸውን የአባላት ብዛት በተመለከተ ሲደራጁ የነበራቸዉ አባላት ስራ ሲያቆሙ ከነበራቸዉ አባላት
ይበልጣል፡፡

4.8 የኢንተፕራይዞች የዕድገት ማናቆዎች

ከዚህ በላይ በታዩ በርካታ የትንተና ክፍሎች ለማየት እንደተሞከረዉ ከኢንተርፕራይዞቹ ድጋፍ
አገልግሎት አሰጣጥ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች አፈጻጸም በተለያየ ደረጃ ይገኛል፡፡ አንዳንድ የድጋፍ
አገልግቶች የተሻለ አፈጻጸም ሲኖራቸዉ የአንዳንዶቹ ደከም ያለ አፈጻጸም እንደነበር ለማየት
ተችሏል፡፡ የአንዳንዶቹ ደግሞ ከነጭራሹ አገልግሎቱ መኖሩ ጭምር በሚያነጋግር ደረጃ ዝቅተኛ
አፈጻጸም የታየበት ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ኢንተርፕራይዞቹ ዕድገታቸዉን የሚገቱ በርካታ
ማነቆዎች እንዳሉባቸዉ ገልጸዋል፡፡ የጥናቱ ዉጤት እንደሚያመለክተዉ የኢንተርፕራይዞቹ ዕድገት
በተለያዩ ማነቆዎች መፈታተኑን ነዉ፡፡ ኢንተርፕራይዞቹ በራሳቸዉ ደረጃ አድገዉና ተለዉጠዉ
ለከተማ አስተዳደሩ ብሎም ለአገር የኢኮኖሚ ልማት በርካታ አስተዋዕጾ ማበርከት የሚጠበቅባቸዉ
ቢሆንም ይህንን ከግብ ለማድረስ ማነቆዎቹን መሻገር የግድ ይላል፡፡ ማነቆዎቹን ለመሻገር ደግሞ
ማነቆዎቹ ምንና በምን ምክንያት እንዲሁም እንዴት የሚከሰቱ መሆናቸዉን በቅድሚያ ማወቅ
ከዚያም መፍታት የግድ ይላል፡፡

88
ሠንጠረዥ 52፡ ኢንተርፕራይዞቹ ሥራቸዉን በሚያከናዉኑበት ወቅት ያጋጠሙ ዋና ዋና ችግሮች
ዋና ዋና ችግሮች ኢንተርፕራይዞቹ የሰጡት በቁጥር ከጠቅላላ ከመለሱት
ምላሽ በመቶኛ በመቶኛ
አይደለም 16272 64.1 64.1
የደንበኛ አለመኖር አዎን 9127 35.9 35.9
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 20710 81.5 81.5
ተወዳዳሪ አለመሆን አዎን 4689 18.5 18.5
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 19028 74.9 74.9
የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ችግር አዎን 6371 25.1 25.1
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 11748 46.3 46.3
ገበያ የማጣት አዎን 13651 53.7 53.7
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 23461 92.4 92.4
የክህሎትና ዕዉቀት ማነስ አዎን 1938 7.6 7.6
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 21120 83.2 83.2
አስፈላጊዉን ቴክኖሎጂ አለማግኘት አዎን 4279 16.8 16.8
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 21841 86.0 86.0
የመንግስት ህግና ደንብ ጫና አዎን 3558 14.0 14.0
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 21215 83.5 83.5
የመረጃ እጥረት አዎን 4184 16.5 16.5
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 16175 63.7 63.7
በቂ የሆነ ማምረቻ እና መሸጫ ቦታ አዎን
አለመኖር 9224 36.3 36.3
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 23886 94.0 94.0
ምንም ችግር የለም አዎን 1513 6.0 6.0
ድ ምር 25399 100.0 100.0
አይደለም 24590 96.8 96.8
ሌላ አዎን 809 3.2 3.2
ድ ምር 25399 100.0 100.0

ምንጭ፡ ከመስክ መረጃ የተሰላ

ኢንተርፕራይዞቹ እያጋጠሙአቸዉ ካሉት ዋና ዋና የዕድገት ማነቆዎች መካከል ዋነኛዉ የገበያ


ማጣት (53.7 ከመቶ) ሲሆን ቀጥሎም በቂ የሆነ ማምረቻ እና መሻጫ ቦታ አለመኖር (36.3 ከመቶ)
ከዚያ የደንበኛ አለመሮር (35.9 ከመቶ) መሆኑን የጥናት ዉጤቱ ያሳያል፡፡ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት

89
ችግር (25.1 ከመቶ)፤ ተወዳዳሪ አለመሆን (18.5 ከመቶ)፤ ተስማሚና አስፈላጊዉን ቴክኖሎጂ
አለማግኘት (16.8 በመቶ)፤ እንዲሁም የመንግሥት ህግና ደንብ ጫና (14 ከመቶ) እንደየቅደም
ተከተላቸዉ በችግርነት ተጠቅሰዋል፡፡ ከኢንተርፕራይዞቹ መካከል 6 ከመቶ ያህሉ ምንም ችግር
የለብንም በማለት ገልጸዋል፡፡

ቀደም ሲል እንደተገለጸዉ የገበያ ድጋፍ ያገኙት 28 ከመቶ ብቻ ከመሆናቸዉ አንጻር ገበያ ማጣት
እንደ መሰረታዊ ችግር መጠቀሱ የሚገርም አይሆንም፡፡ ደንበኛ አለመኖር ችግርም ሆነ በቂ የሆነ
ማምረቻና መሸጫ ቦታ አለመኖርም ቢሆን ከዚሁ ከገበያ ችግሩ ጋር አብሮ የሚታይ ነዉ፡፡ ስለዚህ
የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ማነቆ ለመፍታት እንደ ዋነኛ ስትራቴጂ መወሰድ ያለበት
ጉዳይ በተለያዩ የድጋፍ አሰጣጥ ሥርዓት ላይ እምርታዊ ለዉጥ ማምጣት መሆኑ የወቅቱን ጥያቄ
በማያዳግም መልኩ መመለስ ይሆናል፡፡
መረጃ በሚሰበሰብበት ወቅት በምልከታ ጥናት የተገኙ በዘርፉ የሚታዩ ዋና ዋና ችግሮች የመስሪያ
ቦታ ወይም የመሬት አቅርቦት ችግር፣ የፋይናንስ ድጋፍ አገልግሎት እጥረት ፣ የገበያ ትትስስር
በጣም አናሳ መሆን ፣ የቴክኖሎጂ አቅርቦትና አጠቃቀም ችግር ፣ የመሠረተ ልማት አቅርቦት
(የመንገድ፣ የውሃ፣ የመብራት የፈሳሽና ደረገቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ፣ የመጸዳጃ ቤት እና
ሌሎች) ችግሮች፣ የሼዶችና ሌሎ ች ከመንግስት የሚሰጣቸው የማምረቻና የመሸጫ ቦታዎች
ላልተፈለገ ዓላማ ማዋል (ለምሳሌ ለከብት እርባታ ስራ የተሰጠውን ቦታ የመኖሪያ ቤት ሰርቶበት
ማከራየት)፣ የሃብት ብክነት ለምሳሌ ትላልቅ ህንጻዎች በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንፕራይዞች ስም
ተይዘው ያለሥራ ተዘግቶ መቀመጥና ያለምንም እሴት መጨመር ህንጻዎቹ ለእርጅና መጨመር
ምክንያት መሆን፣ በከፍለ ከተሞችና በወረዳዎች የኢንተርፕራይዞች እንቅስቃሴ ዙሪያ የክትትልና
የድጋፍ አናሳ መሆን፣ ከፍተኛ የካፒታል አቅም መፍጠር በሚችሉ የእድገት ተኮር ዘርፎች ካለው
የአባላቱ ጾታዊ ስብጥር አንጻር ሲታይ የሴቶች ተሳትፎ አናሳ መሆንና አብዛኞቹ ሴት አባላት በቀላል
የስራ መስኮች ለምሳሌ በምግብ ዝግጅትና በሻይ ቡና ማፍላት ስራ ላይ በብዛት መሳተፍ፣ ህገወጥነት
መስፋፋትና የመልካም አስተዳደር እጦት፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካለት ተቀናጅቶ የመስራት
ውስንነት፣ የመረጃ አያያዝ ችግር … ወዘተ ናቸው (ለበለጠ መረጃ ሠንጠረዥ 52 ይመልከቱ)፡፡

4.9 ማጠቃለያ

ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሥራ ዕ ድል በመፍጠር፤የቴክኖሎጂ ሽግግር በማፋጠን


እንዲሁም ገበያን በማሳለጥ ለአገር ዕድገት የማይተካ ሚና አላቸዉ፡፡ ኢንተርፕራይዞቹ ይህንን
ሀላፊነታቸዉን እንዲወጡ ከሆነ በተመረጠ ሁኔታ የሚሰጠዉን ድጋፍ ማጠናከር ወሳኝነት አለዉ፡፡
በዚሁ መሠረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጥናቱ የተመለከቱትን ጥንካሬዎችን በማስቀጠል
እና በጉድለት የታዩትን ችግሮች በመፍታት ከኢንተርፕራይዞቹ ሊገኝ የሚገባዉን ጥቅም ህብረተሰቡ
ተጠቃሚ እንዲሆን ከዕቅድ እስከ ትግበራና ክትትል ተገቢዉን ሁሉ ሊያደርግ ይገባል፡፡
90
ምዕራፍ አምስት፡ የጥናቱ ድምዳሜ እና የወደ ፊት የትኩረት አቅጣጫዎች

5.1 መግቢያ

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራቴጂው ቀደም ሲል የተገኙትን ውጤቶች በተሻለ


መንገድ ለማስቀጠል፣ ለዘርፉ በመንግስት የተቀመጡ አቅጣጫዎች ለማሳካት፣ እንዲሁም በፓኬጅ
ትግበራ የተገኙትን ልምዶች በመቀመር እና ከውጭ ሀገር የተገኙትን ምርጥ ልምዶችን በማጥናትና
ከሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማጣጣም ተዘጋጅቶ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ በዚሁ መሠረት ባለፉት
አመታት በአጠቃላይ በሀገራችን በኢንተርፕራይዞች ልማት እና በሥራ እድል ፈጠራ ሥራዎች
ከፍተኛ አመርቂ ውጤት የተመዘገበ መሆኑ በየደረጃው ከተካሄዱ ግምገማዎች ማረጋገጥ ተችሏል፡፡
በዚሁ መሰረት በአገር አቀፍ ደረጃ ከተጣለው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የሥራ ዕድል
ፈጠራ ግቦች አንጻር በአምስት አመቱ አጠቃላይ 3 ሚሊዮን የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ 10.66
ሚሊዮን ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል የተፈጠረ መሆኑን የከተማ ልማት ቤቶች ሚንሰቴር ሪፖርት
ያመለክታል፡፡በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ዘር ፍ የሚታየውን የአመለካከትና
የክህሎት ክፍተት ለመቅረፍና የንግድ ሥራ አመራርና የቴክኒክ ክህሎት ለማዳበር እንዲቻል
ለኢንተርፕራይዞቹ አንቀሳቃሾች በንግድ ሥራ-አመራር እና በተለያዩ የቴክኒክ ክህሎት ዘርፎች
ለነባርና አዲስ የኢንተርፕራይዞቹ አንቀሳቃሾች የአመለካከትና የክ ህ ሎ ት ሥልጠና
ተሰጥቷል፡፡ለኢንተርፕራይዞች መሬት በማዘጋጀት ሼድና ህንጻ በመገንባት፣ብድር በመስጠትና የገበያ
ትስስር በመፍጠር ሚሊየኖች በዘርፉ ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም እንዲሁ ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ምርትና ምርታማነታቸው
ለማሳደግና በገበያ ላይ ተወዳዳሪ ሆነው እንዲቀርቡ ለማድረግ የሚታይባቸውን የክህሎት ክፍተት
በመሙላት የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረግ ለዘርፉ ልማት ወሳኝ በመሆኑ
ኢንተርፕራይዞቹ ከተደራጁበት ጊዜ አንስቶ ለአንቀሳቃሾች በንግድ ሥራ አመራር ስልጠና፣ የንግድ
ልማት የም ክ ር ድጋፍ በመስጠት ተቀባይነትን ያገኙ ተ ስ ማሚ ቴክኖሎጂዎችን በማሰራጨት
ኢንደስትራሊስቶችን ለማፍራት ጥረት ተደርጎኣል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አገራችን ኢትዮጵያ በተከታታይ እያስመዘገበች ካለው የኢኮኖሚ እድገት
ተቋዳሽ ብትሆንም ስራ አጥነትና ድህነት በከተማዋ ለዘመናት ሰፍኖ የቆየ ችግር ከመሆኑ ጋር
ተያይዞ በየጊዜው አያሌ ሰዎች ከገጠር ወደ ከተማ በሚያደርጉት ፍልሰት፣ ከተለያዩ ተቋማት
ትምህርታቸውን አጠናቀው የሚወጡትን ጨምሮ የስራ አጡ ቁጥር እና ከድህነት ወለል በታች
የሚኖረው ህዝብ ብዛት አሁንም ቀላል በማይባል ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ ይህንን ስራ-አጥነትና ድህነት
ለመቅረፍ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማትን የሚያጠናክር፤የሚደግፍና

91
ብሎም ዘርፉ ለከተማው ነዋሪ አማራጭ የሥራ እድሎችን መፍጠሪያና ድህነትን መቀነሻ ስልት
እንዲሆን የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ፓኬጀን በመቅረጽ ላለፉት 12 ዓመታት
በተግባር በማዋል ለበርካታ ሥራ ፈላጊ ዜጎች የሥራ እድል በመፍጠር ብዙዎችን ደግሞ በልማታዊ
መስመር ተጉዘውና መንግስት ያመቻቸላቸውን የድጋፍ ፓኬጆች በመጠቀም ሀብት እንዲያፈሩ
አስችሏል፡፡በዚህ ሂደት የተመዘገበዉ ዉጤት አበራታች ቢሆንም በርካታ ተግዳሮቶችና እጥረቶች
ተስተዉለዋል፡፡ በዚህ ምዕራፍ በጥናቱ የተዳሰሱ ዋና ዋና ተግዳሮቶችና የትኩረት አቅጣጫዎች ከዚህ
በታች ባሉት ክፍሎች ተጠቁመዋል፡፡

5.2 የጥናቱ ድምዳሜ

የጥቃቅናና አስተ ኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራተጂ አቅጣጫዎች የጥቃቅንና አነስተኛ


ኢንተርፕራይዞች ልማት ዋና ማዕከሉ በከተሞች የሚገኘውን ስራ አጥነትና ድህነት ለመቀነስ ሰፊ የስራ
ዕድል መፍጠርና ለኢንዱስትሪ ልማት ሰፊ መሠረት የሚሆኑ ልማታዊ አስተሳሰብ የተላበሱ ተቋማትን
መፍጠር ነው፡፡ የስትራቲጂዉ ዋና ማጠንጠኛ በከተሞች ለሚኖሩ ስራ ፈላጊ ዜጐች በተለያዩ የስራ
ዘርፎች እንዲሰማሩ በማድረግ እለታዊ ገቢያቸውን በማሳደግ በዝቅተኛ ደረጃ የሚኖረውን የከተማ ነዋሪውን
ኑሮ ማሻሻል ከመሆኑም በላይ የኢንዱስትሪውን ልማት ለማሳደግ መሰረት የሚሆኑ የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች በማብቃት ሁሉም ዜጋ ከልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻል ነው፡፡

ባለፉት ዓመታት በአዲስ አበባ ከተማ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ ሰፊ የስራ ዕድል
እንዲፈጠር በማድረግ በርካታ ወጣቶችና ሴቶች የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ በየጊዜው
በተሰራው ሥራ ቁጥራቸዉ ቀላል ለማይባል ስራ ፈላጊ ዜጎች የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸዉ ሲሆን
የከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ምሩቃኖች ጭምር ወደ ዘርፉ መቀላቀል ችለዋል፡፡ ይሁን እንጂ
የስራ ዕድል ፈጠራ ስራዉ በርካታ ተግዳሮቶች እንደነበሩት ከመስክ በመጠይቅ፣ በቃለ መጠይቅና
ምልከታ የተገኘዉ መረጃ ያስረዳል፡፡ የኢንተርፕራይዞች አደረጃጀት በጾታ ሲታይ በተቋማቱ ሀላፊነትም
ሆነ አባልነት ያሉት አብዘኞቹ ወንዶች መሆናቸዉ የጥናቱ ዉጤት ያሳያል፡፡ ይህም የሚያመለክተዉ
የከተማዉ ህዝብ አጋማሽ የሚሆነዉ ድርሻ ያላቸዉ ሴቶች በኢንተርፕራይዞች ልማት ያላቸዉ ተሳትፎ
አነስተኛ መሆኑን ነዉ፡፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ዕድሜ ሲታይ የጥናት ዉጤቱ
የሚያሳየዉ የበወጣትነት ዕድሜ ክልል ያሉትን አምራችና ዉጤታማ የተባለዉን የህብረተሰብ ክፍል
የሚያካትት በመሆኑና የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን የወደፊት እድገት እና የድጋፍ አይነት
የሚወስን በመሆኑ ሊጠናከር የሚገባ ነዉ፡፡ በዚህ የልማት ዘርፍ የተሰማረዉን የሰዉ ሀይል የትምህርት
ደረጃ ስንመለከት የጥናት ዉጤት የሚያሳየዉ ምንም እንኳን በመዲናችን ብዙ የተማረ ሥራ አጥ ወጣት
ያለ ቢሆንም በአመለካከት ላይ በቂ ሥራ ስላልተሰራ የጥቃቅንና አነስተኛ ሥራ የዝቅተኛ ትምህርት
ያላቸዉ ተደርጎ የተወሰደ ይመስላል፡፡ የጥቃቅን አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዘርፍ ከገቢ ማስገኘትና ሥራ

92
አጥነትን ችግር ከመቅረፍ በዘለለ ያለዉ ፋይዳ የተሟላ ግንዛቤ የተያዘበት አለመሆኑን ከጥናቱ መረጃ
መገንዘብ ይቻላል፡፡

ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንጻር በዘርፉ በርካታ የሥራ ዕድሎች የተፈጠሩ ቢሆንም በከተማዉ ከሚኖሩ ስራ
ፈላጊ ዜጎች አንጻር ሲታይ ግን የተፈጠረዉ የሥራ እድል በቂ እንዳልነበረ የጥናቱ ዉጤት ያሳያል፡፡
የኢንተርፕራይዞች ልማት ከማስፋፋት አንጻር የተፈጠሩት አብዛኞቹ የስራ ዕድሎችም ቢሆኑ በቋሚ ስራ
ላይ በተለይም በአምራች ዘርፉ ላይ እንዲሆን ከማድረግ አንጻር የተሰራው ስራም ሆነ ውጤቱ እጥረት
ያለበት ነበር፡፡ ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠሪያ አማራጮች በርካታ የመሆናቸውን ያህል በዚህ ዘርፍ
የሚሰማሩ ዜጎች በዘርፉ ስትራተጂው መሰረት ወደ ቋሚ ስራ ዕድል ከማሸጋገር አንጻር የተሠራዉ ሥራ
ዉጤት አመርቂ እንዳልሆነ ከላይ ከጥናቱ መረጃ ትንተና መረደት ይቻላል፡፡የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንትርፕራይዞች ልማት የኢንዱስትሪ ልማትን በማፋጠን ልማታዊ የኢንዱስትሪ ባለሀብት የሚፈጠርበት
መሆኑን የኢንዱስትሪ ልማትና የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራቴጂዎች አቅጣጫ
ተቀምጧል፡፡ ከዚህ አቅጣጫ አንጻር የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዋናው ትኩረት የሥራ ዕድል
መፍጠርና ድህነትን መቀነስ አስፈላጊነት እንደተጠበቀ ሆኖ በአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ላይ
የተመሰረተ ማኑፋክቸሪንግ ማስፋፋት እና ኢንዱስትሪያሊስት ባለሀብቶችን በብዛትና በጥራት ማፍራት
ነው፡፡በከተማዉ እስካሁን በአንተርፕራይዞች ልማት በተሠረዉ ሥራ በማኑፋክቸርንግ ዘርፍ የተሰማሩ
ኢንተርፕይዞች በድምር ከ24% በላይ አይደሉም፡፡ የደረጃ ዕድገታቸውም ያን ያህል አመርቂ አይደለም፡፡

በዘርፉ በ12 አመት ዉስጥ ወደ መካከለኛ ደረጃ የተሸጋገሩ ኢንተርፕራዞች 10.4% ብቻ ናቸዉ፡፡ይህ
አፈጻጸም ካለው ፍላጎትና ተደራሽነት አንጻር በስትራተጂዎቹ ከተቀመጠዉ አኳያ አፈጻፀሙ ዝቅተኛ
ነዉ፡፡ በአጠቃላይ በኢንተርፕራይዞች በተለይም በከፍተኛ ዕድገት ደረጃ ላይ በሚገኙት ኢንተርፕራይዞች
የተደረገዉ የእድገት ሽግግር እጅግ ዝቅተኛ ነው፡ የጥናቱ ዉጤት እንደሚያመለክተዉ በጥቃቅንና
አነስተኛ ተቋማት ልማት ዘርፍ እየተሰማራ ያለው የሰው ኃይልና የዘርፉን ልማት ለመደገፍ የተሰረው
ሥራ የዘርፉ የልማት ስትራተጂ የሰጠውን ትኩረት የሚመልስ ሆኖ አልተገኘም፡፡ የአብዛኛው ኃይል
ስምሪት ሲታይ ቅኝቱ ከዘርፉ ሰትራተጂ አቅጣጫ ያለው ተናባቢነት ጠንካራ አይደለም፡፡ በከፍተኛ ቁጥር
የተሰማራው በንግድና አገልግሎት ዘርፎች ሲሆን በአምራች ዘርፍ እየታየ ያለዉ ተሳትፎ በተነጻጻሪ
ዝቅተኛ ሆኖ ታይቷል፡፡ በዚህ ጥናት ለነዚህ ችግሮች መነሻ ምክንያት የሚሆኑ መሠረታዊ ጉዳዮች
ተለይተዋል፡፡ በመጠይቅ ከኢንተርፕራይዞች የተገኘዉ መረጃ እንዳለ ሁኖ በየደረጃው የሚገኙ ጥቃቅንና
አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ፅ/ቤት ባለሙያዎችና ሓለፊዎች፣ ከሌሎች ከሚመለከታቸው ተቋማት
በተደረገው ውይይቶችና ቃለ-መጠይቆች፣ እንዲሁም ዘርፉን አስመልክተው ካሁን በፊት በተለያዩ አካላት
የተጠኑ ጥናቶች መሰረት በማድረግ በተደረገው ትንተና መሰረት በአዲስ አበባ ከተማ ጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ልማትና እድገት ማነቆ ሆነው እየታዩ ያሉት ችግሮች በዋናነነት ከአመለካከትና
ከድጋፍ አሰጣጥ ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡
93
ከአመለካከት ጋር ያለው ችግር በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ተሰማርቶ መስራት ሌላ አማራጭ
እስከሚገኝ እንደመቆያ አማራጭ እንጂ ዘርፉ ወሳኝ የሀብት መፍለቂያ መንገድ አድርጎ መወሰድ ጉዳይ
ላይ የነበረ አመለካካት ተሟልቶ እንዳልተቀረፈ ለመረዳት ተችሏል፡፡ አብዘኛዉ ሀይል በንግድና
በአገልግሎት ዘርፍ መሰማራቱን የመረጠዉ ከዚህ አመለካከት ጋር በተያየዘ ነዉ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ
የሚታየዉ ሌላው የአመለካከት ችግር በተለይ የሀገራችን የገበያ ሁኔታ ንግዱና አገልግሎቱ ያልተገደበ
የዋጋ ንረት ስለሚታይበት በእነዚህ ዘርፎች ባጭር ጊዜ፣ በጥቂት ወጪ እና በአነስተኛ ጥረት ከፍተኛ
ሀብት ማካበት የመፈለግ አዝማሚያ የወጣቱን ትኩረት ስቧል፡፡ እንደዚሁም በኢንተርፕራይዞቹ ዘንድ
የሚታየው ሌላው ችግር ከመንግስት ከሚሰጣቸው ድጋፍ ላለመላቀቅ ባለው ፍላጎት ለሚቀጥለዉ የእድገት
ደረጃ የሚያሸጋግር ብቃት እያለቸዉም የደረጃ ሽግግር ላለማድረግ ካፒታላቸውን ከመደበቅ አንስቶ
የሚደረጉ የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከቶች መኖራቸዉንም የጥናቱ ውጤት ያመለክታል፡፡

በዚህ ዘርፍ ለተመዘገበው ዝቅተኛ አፈጻፀም ምክንያቶች መካከል በኢንተርፕራይዞቹ ወይም አንቀሳቃሾቹ
በራሳቸው ዘን ድ የሚታየውና በአንጻራዊነት አድካሚ ባልሆኑና በፍጥነት ት ርፍ በሚገኝባቸው
በአገልግሎትና በንግድ ላይ ብቻ የመሰማራት ፍላጎትና አመለካከት ያለ ቢሆንም ኢንተርፕራይዞቹን
አደራጅቶ ድጋፍ እየሰጠ ያለው የመንግስት ተቋምም ቢሆን ከመነሻው በተገቢው መረጃ ላይ የተመሰረተ
ተከታታይ ድጋፍና ክትትል ከማድረግ አንጻር ክፍተት የሚታይበት መሆኑን በጥናቱ ተረጋግጧል፡፡
የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራቴጂው በዘርፉ የሚሰማሩ ኢንተርፐራይዞች በዋናነት
ዕድገት ተኮር በሆኑ ዘርፎች በተለይ በማኑፋክቸርንግ እንዲሰማሩና የኢንዱስትሪ ሰፊ መሰረት እንዲኖረው
ከማድረግ በዘለለ በነዚህ ዘርፎች የሚሰማራ ኃይል ከመሰረቱ በመኮትኮት ልማታዊ ዕይታ እንዲኖራቸው
እንዲደረግና በሀገራችን ኢንዱስትሪ ልማታዊ አስተሳሰብ እንዲሰፍን ብሎም ልማታዊ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ
እንዲጠናከር ተልዕኮ ያነገበ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ዘርፉን ለማጠናከር የተሰጠዉ ድጋፍ ተሟላ አለመሆኑን
የጥናቱ ግኝት ያመለክታል፡፡ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ምርትና ምርታማነታቸው ለማሳደግና በገበያ ላይ
ተወዳዳሪ ሆነው እንዲቀርቡ ለማድረግ የሚታይባቸውን የክህሎት ክፍተት በመሙላት የቴክኖሎጂ
ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ለአንቀሳቃሾች በንግድ ሥራ አመራር ስልጠና፣ የንግድ ልማት የምክር
ድጋፍ በመስጠትና ተቀባይነትን ያገኙ ተስማሚ ቴክኖሎጂዎችን በማሰራጨት ኢንዱስትሪያሊስቶችን
ለማፍራት የተደረጉ ጥረቶች የነበሩ ቢሆንም ለተቋማቱ የተሰጡ የድጋፍ አገልግልቶች ከተደራሽነት
አንጻር ችግሮች የነበረባቸዉ ከመሆኑም ባሻገር የተሰጡ አገልግሎቶችም ቢሆን የተሟላ የኢንደስትሪ
ኤክስቴንሽን ፓኬጅ ከመስጠት አንጻር እጥረት ያለበት መሆኑን ጥናቱ ያመለክታል፡፡ የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች አጠቃላይ የሚሰጡ ድጋፎች እንደዘርፉ ባህርይና ከደረሱበት የዕድገት ደረጃ አንፃር
ስለመሆኑ ከተጠየቁት ከግማሽ በላይ የሰጡት ምላሽ የሚሠጠዉ ድጋፍ የተሟላ እንዳልሆነ
ያመላክታል፡፡መሰረተ ልማትና የማምረቻና መሸጫ ማዕከላት አቅርቦት ያለመሟላት፤ ኢንተርፕራይዞቹ
በገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የቴክኖሎጂ አቅርቦት፣ ለሚያመርቱት ምርትና ለሚያቀርቡት አገልግሎት በቂ

94
የገበያ ትስስር አለመፍጠርና ሌሎች በመንግስት የሚሰጡ ድጋፎች የኢንተርፕራይዞቹን የዕድገት ደረጃ
መሰረት ያደረጉ ሆነዉ ተግባራዊ አለመደረጉ በዘርፉ ለተመዘገበው ዝቅተኛ ውጤት የበኩሉን አስተዋጽኦ
አድርጓል፡፡

5.3 ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች

የሀገራችን ኢኮኖሚና ማህበራዊ እድገት ቀጣይነት ባለው ሁኔታ በጽኑ መሰረት ላይ የታነጸ እንዲሆን
እንዲሁም አዲስ አበባን ጨምሮ በከተሞች የሚታየውን ድህነትና ስራ አጥነት ደረጃ በደረጃ በመቀነስ
የኢንዱስትሪውን ክፍለ ኢኮኖሚ የበላይነት ለማረጋገጥ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ወሳኝ
ሚና እንዳላቸው በዚህ ጥናት ተመላክቷል፡፡

በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራቴጂ ዕድገት ተኮር ማለትም ኮንስትራክሽን፣


ማኑፋክቸርንግና ከተማ ግብርና ለሆኑ ዘርፎች የላቀ ትኩረት እንደሚሻ ተመልክቷል፡፡ የጥቃቅንና
አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ተቋማት የነገዎቹ ኢንዱስትሪያሊስቶች የሚፈጠሩበት ዋነኛ መሠረት
ናቸው፡፡ ከዚህ አንፃር የሀገር ውስጥ ባለሀብት ምንጭ ከመሆናቸውም በተጨማሪ ከጥቃቅንና አነስተኛ
የሚያድጉ ኢንተርፕይዞች ወጣት ኢንተርፕርነርስ የማፍራት አቅም ይኖራቸዋል፡፡ በመሆኑም
የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራዞች በአምራች ኢንዱስትሪው ተሰማርተው በዘርፉ ልማት ዋና
ተዋናይ እና ውጤታማ እንደሆኑ በስትራቴጂው በግልፅ መቀመጡ ለሃገር ውስጥ ባለሀብቱ ዋነኛ እና
አንዱ መሰረታችን የጥቃቅንና አነስተኛ አንቀሳቃሾች መሆናቸውን መረዳት አያዳግትም፡፡ ስለዚህ
እነዚህ ተቋማት በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ዋናዎቹ አምራች ኃይሎች መሆናቸው ስለማይቀር ጠንካራና
በተግባር የተፈተኑ የልማታዊ ባለሀብት መፈልፈያ መሳሪያዎች እንዲሆኑ ያላባቸውን ማነቆዎች
በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥ ተገቢ ይሆናል፡፡

በዚሁ ረገድ በጥናት ውጤቱ የተመለከቱ ትንታኔዎች እንዲሁም በድምዳሜ መልክ የተቀመጡ
ጉዳዮች እንደተጠበቁ ሆነው የሚከተሉት የትኩረት አቅጣጫዎች ትርጉም ተሰጥቶአቸዉ በሥራ ላይ
ሊውሉ ይገባል፡፡

1. የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች እንቀሳቃሾች በአብዛኛው ወንዶች መሆናቸው በዘርፉ


የሴቶችን የተሻለ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ለወደፊት ሊረባረቡ እንደሚገባ
የሚያሳይ ነው፡ እንደዚሁም የአንቀሳቃሾች የትምህርት ደረጃ እና በዘርፉ ያላቸው ክህሎት
የሚፈለገውን ያህል አለመሆኑ በዘርፉ ብዙ መስራት እንደሚገባ አመላካች ነው፡፡
2. በመንግስት ትኩረት ከሚሹ ማስተካከያዎች መካከል አንዱ ና ዋናዉ ለኢንተርፕራይዞቹ
የሚሰጠው ድጋፍ እንደ ዘርፉ ባህርይና ዕድገት ደረጃ እየተመዘነ እንዲሆን የማድረግ ጉዳይ
ነው፡፡ የባለድርሻ አካላትን በማስተባበር የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን የዕድገት ደረጃ
መሰረት ያደረገ፣ መ ጠነ ሰፊና ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ቀጣይነት ባለው መልኩ መስጠት

95
ኢንተርፕራይዞቹ ውጤታማ እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የሌሎች አገሮችን ተሞክሮ
በምንመዝንበት ጊዜ ትምህርት የሚገኝበት መሆኑን ማየት ይቻላል፡፡ የሌሎች ሀገሮች ተሞክሮ
እንደሚያሳየው ለኢንተርፕራይዞቹ የሚሰጠው ድጋፍ እንደ የእድገት ደረጃቸው ነው፡፡ ለምሳሌ
በተዛማጅ ጽሑፎች ለማሳየት እንደተሞከረው የሌሎች አገሮች ተሞክሮ እንደሚያሳየው በምስረታ
ደረጃ ላይ ለሚገኙ የሚሰጡ ድጋፎች የሰለጠነ የሰው ሀይልና ጥሬ ዕቃ እንዲያገኙ፤ መሠረተ
ልማት እንዲሟላላቸውና የገበያ እውቀት እንዲኖራቸው ማድረግ ነው፡፡ በእድገት ደረጃ ላይ ላሉ
ደግሞ የብቃት ማረጋገጫ መስጠት፣ የገበያ ልማት፣ የታክስ ተጠቃሚነትና የክህሎት ስልጠና
ድጋፍ መስጠት ነው፡፡ እንዲሁም በመስፋፋት ደረጃ ለሚገኙ የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ፣ የስራ
አመራር ብቃት ግንባታ፣ የንግድ ምልክት፣ የሽያጭ አውታሮች፣ የኢንፎርሚሽንና ኮሚኒኬሽን
መሠረተ ልማት .. ወዘተ መስጠትና በማብቃት ደረጃ ለደረሱ ኢንተርፕራይዞች የዲዛይን አቅም
ግንባታ፣ የንግድ ምልክት ትውውቅ፣ የኢንዱስትሪ ማስፋፊያና የውጭ ኢንቨስትመንት ድጋፍ
መስጠትን ያካትታሉ፡፡ እነዚህንና መሰል የሌሎች አገሮችን ተሞክሮዎች ከእኛ ተጨባጭ ሁኔታ
ጋር እያስተያዩና እየገመገሙ አዋጭ የሆኑትን ተግባራዊ ማድረግ ይገባል፡፡
3. አብዛኛዎቹ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ባሉበት አደረጃጀት ውስጥ የሚደረገውን
ሽግግርም ሆነ ካሉበት አደረጃጀት ወደሚሚቀጥለው የዕድገት ደረጃ ከመሸጋገር ይልቅ ባሉበት
የመቆየት አዝማሚያ ይታያል፡፡ ይህ አመለካከት እንዲቀየር ስትራቴጂውን መሣሪያ አድርጎ
መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ ምክንያቱም ዕድገት ማሳየት በተለይም በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ
የሚታየው በጎ ለውጥ ለአገርቱ ኢንዲስትሪ ዕድገት ወሳኝ ሚና ስለሚኖረው ነው፡፡ ይህም ማለት
አሁን ከዘርፍ አንጻር ሲታይ አሁን የሚታየውን የብዙዎች በንግድና ኮንስትራክሽን ዘርፍ
የማተኩር ዘቅጣጫ መቀየር ተገቢ ይሆናል፡፡
4. በየደረጃው በዘርፉ አገልግሎት በመስጠትም ሆነ በመምራት ረገድ የሚታየውን የፈጻሚዎችና
የአመራር አቅም ችግር በመፍታት ወቅቱ የሚጠይቀውን ድጋፍና ክትትል ማድረግ የግድ
ይላል፡፡ የፈጻሚዎችንና የአመራር ሚና ወደሚፈለገው ደረጃ በማድረስ ኢንተርፕራይዞቹን
ውጤታማነት እየተፈታተኑ ያሉትን የፋይናንስ፤ መሰረተ ልማት፣ የሥልጠና፣ መልካም አስተዳደር
እና መሰል ችግሮችን መፍታት ይችላል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በአንቀሳቃሾቹ በራሳቸው ዘንድ
የሚታዩትን ከአፈጻጸም፤ አደረጃጀትና አመለካከት ጋር የተያያዙ ችግሮች መፍታት ያስፈልጋል፡፡

96

ዋቤ ማጣቀሻዎች

የጥ/አ/ኢ/ኤ(2005).በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ኤጀንሲ ሁለተኛ ዐትም አዲስ


አበባ.

CSA. (2003). Report on Urban Informal Sector sample Survey. AA: Ethiopia

Haftu et al. (2009). Financial Needs of Micro and Small Enterprises (MSE) Operators in Ethiopia:
Association of Ethiopian Micro-Finance Institutions Occasional Paper No. 24. Addis Ababa,
Ethiopia.

ILO. (2003): Guidelines Concerning a Statistical Definition of Informal Employment, Endorsed by the
Seventeenth International Conference of Labour Statisticians (November-December 2003); Geneva.

Konjit D. (2014). Women in the Development of Micro & Small Enterprises to Ensure Sustainable
Development & Food Security

Ministry of International Trade and industry, ‘MITI’ (2005). “The Third Industrial Master Plan (IMP3)”,
KualaLumpurMalaysia.

MoFED. (2010). Growth and Transformation Plan 2010/11—2014/2015, November, 2010, Addis Ababa.

OECD. (2004). “Evaluationof SME Policies and Programs”.Working Paper, OECD, Paris.

SMIDEC.(2002). “SMI Development Plan (2001–2005)”, Percetakan Nasional Malaysia Berhad, Kuala
Lumpur.

Tegegne and Helmsing.(2005). Local Economic Development in Africa: Enterprises, Communities, and
Local Government.

Thorbecke, Erik. (2000). The Evolution of the Development Doctrine, 1950-2005. United Nations
University, World Institute for Development Economics Research. Research Paper No. 2006/155
December 2006 Helsinki, Finland.

Todaro (2000). Economic Development, 7th ed. Pearson Education Publisher, New York University.

Tulus T.(2006). Micro, Small and Medium Enterprises and Economic Growth. Working Paper Series No.
14. Center for Industry and SME Studies. Faculty of Economics, University of Trisakti.

¾›Ç=e ›uv Ÿ}T ›e}ÇÅ` ›eðéT>“ ¾T²ÒÍ u?ƒ ›ÑMÓKAƒ ›"Lƒ �”ÅÑ“ TssT>Á ›ªÏ&
›ªÏ lØ` V5/2g=4¯.U.

97
አባ ሪዎች

አባሪ አንድ፡ በእንቅስቃሴ ላይ ላሉ ኢንተርፕራይዞች የተዘጋጀ ቃለ-መጠይቅ አዲስ አበባ ከተማ


አስተዳደር ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ የተደራጁ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዝርዝር መረጃ
ማሰባሰቢያ ቅጽ(01)

ክፍል አንድ
አጠቃላይ የኢንተርፕራይዙ መረጃዎች
1 2 3 4 5 6 7 8
የጥናት የተቋቋመበት ሳይት/ክላ የሼድ/ የቤት/ የቦታውል
ዘመን የኢንተርፕራይዙስም ወርናዓ.ም ክ/ከተማ ወረዳ ስተር የሱቅቁጥር ዩስም

9 10 11
የንግድ ምዝገባ ቁጥር የንግድ ፈቃድ ቁጥር የግብርመክፈያ መለያ ቁጥር

ተ.
ቁ ጥያቄዎች ኮድ
12 የስራአስኪያጅ/ሰብሳቢ/ ስም ጾታ እ ድሜ የትምህርትደረጃ ስልክቁጥር

13 የኢንተርፕራይዙአይነትምንድንነው?
ጥቃቅን------------------- አነስተኛ ---------------
- 1 -- 2

14 የኢንተርፕራይዙህጋዊየአደረጃጀትአይነትምንድንነው?
በግል -------------------------- በህብረትሥራማህበር ---------
------ 1 ----- 5
በህብረትሽርክና -------------
-------- 2 ሌላካለይጻፍ---------------------
ኃላፊነቱየተወሰነየግልማህበ
ር ------ 3
በአክሲዮንማህበር -----------
---- 4
15 ኢንተርፕራይዙየተሰማራበትዋናዘርፍምንድንነው?
ማኑፋክቸሪንግ---------- ከተማግብርና -------------------------
----------- 1 ---- 4
ኮንስትራክሽን --------- ንግድ ----------------------------------
------------ 2 --- 5
አገልግሎት -----------
------------ 3 ሌላካለይጻፉ--------

98
16 ኢንተርፕራይዙየተሰማራበትንዑስዘርፍምንድንነው?
የማኑፋክቸሪንግዘርፍ/1/
ጨርቃጨርቅናስፌት ------- ባህላዊየዕደጥበብናጌጣጌጥሥራዎች
-------- 11 ------- 16
ቆዳናየቆዳውጤቶች -------- አግሮፕሮሰሲንግ ---------------------
------- 12 ---- 17
የምግብናመጠጥዝግጅት --- የግንባታግብዓትምርቶች -----------
--------- 13 ------ 18
የብረታብረትናኢንጂነሪንግ
ምርቶች ---- 14 ሌላካለይጻፍ --------------
የእንጨትሥራዎች ---------
---------- 15
የኮንስትራክሽንዘርፍ/2/
ሥራተቋራጭነት ------------ ኮብልስቶንሥራዎች -----------------
---- 21 ---- 24
ንዑስሥራተቋራጭነ-- ------ የመሠረተልማትግንባታንዑስተቋራ
21
----- ጭነት-- 25
ባህላዊየማዕድንሥራዎች --- የከበሩድንጋይልማት ----------------
-------- 23 ----- 26
ሌላካለይጻፍ --------------------
ተ.
ቁ ጥያቄ ኮድ
የአገልግሎትዘርፍ/3/
የገጠርአነስተኛትራንስፖረ የምርትዲዛይንናልማትአገልግሎት-
ትአገ ---------- 31 ------- 39
ካፌናሬስቶራንት ------------ የግቢውበት፤የጥበቃእናጽዳትአገል
32
--------- ግሎት- 310
የማከማቻአገልግሎት ------- የጥገናአገልግሎት --------------------
----------- 33 -------- 311
የቱሪስትአገልግሎት -------- የውበትሳሎንሥራዎች --------------
------------ 34 -------- 312
የማሸጊያአገልግሎት -------- የኤሌክትሮኒክስናሶፍትዌርልማት
------------ 35 ---------- 313
የሥራአመራርአገልግሎት - የዲኮርሥራ ---------------------------
-------------- 36 ---- 314
የማዘጋጃቤታዊአገልግሎት ኢንተርኔትካፌ -----------------------
------------- 37 ------ 315
የፕሮጀክትኢንጂነሪንግአገ የጋራዥናመገጣጠምስራዎች ------
ልግሎት ------ 38 ----------- 316
ሌላካለይጻፍ ----------------
የከተማግብርናዘርፍ/4/
ዘመናዊየእንስሳትእርባታ - እንስሳትመኖማቀነባበሪያ-- ---------
------------ 41 --------- 45
የዶሮእርባታ -------------- ዘመናዊየደንልማት ----------------
---------- 42 --------- 46
የንብማንባት ---------------- አትክልትናፍራፋሬ -----------------
-------- 43 ---------- 47
ዘመናዊየመስኖስራ ---------
-------- 44 ሌላካለይጻፍ -------------
የንግድዘርፍ/5/
የጥሬዕቃአቅርቦ
የሀገርውስጥምርቶችጅምላሽያጭ --------------- 51 ት-------- 53
የሀገርውጥምርቶችችርቻሮንግድ---------------- 52
99
ሌላካለይጻፍ ----------------
በአሁኑወቅትኢንተርፕራይዙእየሰጠያለውአገልግሎት/የሚያከናውነውተግባር/
17 ምንድንነው?
___________________________________________________

ክፍ ል ሁ ለ ት
የኢንተርፕራዙንየእድገትደረጃየሚያሳዩመረጃዎች
18. ኢንተርፕራይዙሲደራጅየነበረውየአባላትብዛትእናአሁንያለውየአባላትብዛትስንትነው?
ሲደራጅየነበረዉየአባላትብዛት አሁንያለውየአባላትብዛት
ድም
እ ድሜ የትምህርትደረጃ ሴት ወንድ ድም ር ሴት ወንድ ር
ማንበብእናመጻፍየማይ
ችል
እስከ 12 ክፍል
18-28
ኮሌጅዲፕሎማ
ዲግሪ
ከዲግሪበላይ
ማንበብእናመጻፍየማይ
ችል
እስከ 12 ክፍል
29-39
ኮሌጅዲፕሎማ
ዲግሪ
ከዲግሪበላይ
ማንበብእናመጻፍየማይ
ችል
ከ40 እስከ 12 ክፍል
በላይ ኮሌጅዲፕሎማ
ዲግሪ
ከዲግሪበላይ
ድ ምር
አካልጉዳተኛካለ
ተ.
ቁ ጥያቄ ኮድ
የኢንተርፕራይዙአባላትቁጥርከጨመረየጨመረበትምክንያትምንድንነው?(ከአንድበላይመ
19 ልስይቻላል)፡፡
ኢንተርፕራይዙአትራፊበመሆኑ --------------
----- 1
ተቀጣሪሰራተኞችወደአባልነትስለመጡ ----
-------- 2
በገበያትስስርድጋፍምክንያትሰፊስራበመገኝ
ቱ------- 3
በግዴታየአባላትንቁጥርአሳድጉበመባሉ -----
--- 4
ሌላካለይጻፍ --------------

የኢንተርፕራይዙአባላትቁጥርከቀነሰየቀነሰበትምክንያትምንድንነው?
20 (ከአንድበላይመልስይቻላል)፡፡
እርስበርስግጭት----------------------------------
-- 1
በመክሰርናተወዳዳሪአለመሆን------------------ 2
100
-----
የገበያማጣት -------------------------------------
--- 3
አባላትየተሻለነገርስላገኙ ---------------------
-- 4
ሌላካለይጻፍ ---------------

21 ኢንተርፕራይዙሲደራጅየነበረውመነሻካፒታልስንትነው? በብር

መነሻካፒታል ----
---------

22 ኢንተርፕራይዙአሁንያለውካፒታልስንትነው? በብር

አሁንያለካፒታል-
---------

23. ከአባላትውጭቋሚእናጊዜያዊየሥራእድልየተፈጠረላቸውዜጎችብዛትሰንትናቸው?
ቋሚየስራእድል ጊዜያዊየስራእድል
ድም
እ ድሜ የትምህርትደረጃ ሴት ወንድ ድም ር ሴት ወንድ ር
ማንበብእናመጻፍየማይ
ችል
እስከ 12 ክፍል
18-28 ኮሌጅዲፕሎማ

ዲግሪ
ከዲግሪበላይ
ማንበብእናመጻፍየማይ
ችል
እስከ 12 ክፍል
29-39
ኮሌጅዲፕሎማ
ዲግሪ
ከዲግሪበላይ
ማንበብእናመጻፍየማይ
ችል
ከ40 እስከ 12 ክፍል
በላይ ኮሌጅዲፕሎማ
ዲግሪ
ከዲግሪበላይ
ድ ምር
አካልጉዳተኛካለ

ተ.
ቁ ጥያቄ ኮድ
24 ኢንተርፕራይዙሲደራጅየነበረበትየእድገትደረጃ?
የምስረታወይምጀማሪደረጃ---------- 1

101
ታዳጊወይምመስፋፋትደረጃ ---------- 2
መብቃት ----------------------------- 3
ታዳጊመካከለኛ ---------------------- 4
25 ኢንተርፕራይዙአሁንየደረሰበትየእድገትደረጃ?
የምስረታወይምጀማሪደረጃ----------- 1
ታዳጊወይምመስፋፋትደረጃ --------- 2
መብቃት ---------------------------- 3
ታዳጊመካከለኛ --------------------- 4
26 ኢንተርፕራይዙሲደራጅየነበረበትእናአሁንየደረሰበትየእድገትደረጃልዩነትካለውአሁንየደረ ዓመት
ሰበትየእድገትደረጃለመድረስምንያህልዓመትፈጀበት?

ክፍልሦስት
የድጋፍማዕቀፍአገልግሎትአሰጣጥእናአፈጻጸምየሚያሳዩመረጃዎች
ተ.
ቁ ጥያቄዎች ኮድ
27 ኢንተርፕራይዙየብድር/ፍይናንስ/ ድጋፍአገልግሎትአግኝቶያውቃል?
አግኝቷል --------------- አስፈላጊውንመስፈርትበማሟላትሂደትላይ-
-- 1 ------ 3
አላገኘም ----------------
- 2 ሌላካለይጻፍ- --------------------------------

28 ኢንተርፕራይዙየመሳሪያሊዝድጋፍአገልግሎትአግኝቶያውቃል?
አግኝቷል --------------- አስፈላጊውንመስፈርትበማሟላትሂደትላይ-
-- 1 ------ 3
አላገኘም ---------------- ስለአገልግሎቱመረጃየለኝም------------------
- 2 -- 4
ሌላካለይጻፍ --------------
29 ኢንተርፕራይዙየብድርድጋፍአገልግሎትካላገኝያላገኝበትምክንያትምንደንነው?
(ከአንድበላይመልስይቻላል)፡፡
የብድርአገልግሎትባለመፈለግምክን በአበዳሪተቋማትበቂፋይናንስአለመቅ
ያት --- 1 ረብ--5
በብድርዋስትናምክንያት -------------- የዘርፉትርፋማአለመሆን --------------
--- 2 ----6
ኢንተርፕራዙበቂየሆነካፒታልስላለው የአባላትአለመስማማት------------------
---------------- 3 ---7
የብድርድጋፍአገልግሎትአሰጣጡቀልጣፋባለመሆኑ ------
- 4
ሌላካለይጻፍ -------------

30 ኢንተርፕራይዙየብድርድጋፍአገልግሎትካገኝየሚከተሉትጥያቄዎችይመልሱ፡፡ በቁጥር
ኢንተርፕራይዙከተቋቋመጀምሮየተገኝየብድርአገልግሎትብዛት /በድግግሞሽ/---------
----
ብር
ለመጨረሻጊዜየተገኝየብድርመጠንበብር -- -----------------------------------------------
ዓ. ም
ለመጨረሻጊዜብድርየተገኘበትዓመተምህረት--- --------------------------------------------
ብር
ተመላሽየተደረገየብድርመጠንበብር -------------------------------------------------------

102
31 ኢንተርፕራይዙየብድር/ፋይናንስ/ ድጋፍያገኘበትተቋም?
አዲስብድርቁጠባተቋም------ የኢትዮጲያንግድባንክ
--- 1 ------- 2
ሌላካለይጻፍ
ተ.
ቁ ጥያቄ ኮድ
በብድርአመላለስዙሪያያጋጠሙዋናዋናችግሮችምንምንናቸው
32 ?(ከአንድበላይመምረጥይቻላል)
ኢንተርፕራዙአትራፊአለመሆኑ ----------------------- 1
የአባላትአለመስማማት-------------------------------- 2
ብድሩንካገኙበኃላለአባላትቁጥርመመንመን------------------
- 3
የግንዛቤማነስ----------------------------------------- 4
ሌላካለይጻፍ--------------

33 ለኢንተርፕራይዞችየሚሰጠውየብድርድጋፍአገልግሎትበሚፈለገውመጠንእናወቅትስለመሆ
ኑአባላትያላቸዉአስተያየት? (ከአንድበላይመልስይቻላል)፡፡ ሀ
ሀ. ከመጠንአንጻር ለ. ከጊዜአንጻር
በሚፈለገውጊዜይገኛል ------
በሚፈለገውመጠንይገኛል ------ 1 ------ 4
በሚፈለገውመጠንበከፊልይገኛ በሚፈለገውጊዜበከፊልይገኛ
ል 2 ል ----- 5 ለ
በሚፈለገውመጠንአይገኘም ---- በሚፈለገውጊዜአይገኘም ----
-- 3 ------ 6
ሌላይጻፍ ----------------------

34 ኢንተርፕራይዙከተቋቋመጀምሮየገበያትስስር/የስራትስስር/ አግኝቷል?
አግኝቷል----- 1 አላገኘም -------- 2

ኢንተርፕራይዙየትኛዉንየገበያ/የስራትስስርአይነትአግኝቷል?(ከአንድበላይመልስይቻላል)
35 ፡፡
የአካባቢ --------------- ሁሉንምየገበያትስስርአይነ
--- 1 ት----- 4
የክልል ------------------
-- 2
የዉጭ ------------------
-- 3

36 ኢንተርፕራይዙከተቋቋመጀምሮያገኛቸውየገበያትስስርድጋፍብዛትእናየብርመጠንይጻፍ፡፡
የገበያትስስርድጋፍአይ በትስስሩየተገኝየብር
ነት የተገኝየገበያትስስርበቁጥር መጠን
የአካባቢ
የክልል
የውጭ

ድም ር

37 ኢንተርፕራይዙየሰውኃይልልማትእናየኢንዱስትሪኤክስቴንሽንአገልግሎትበተመለከተያገ
ኘውንየድጋፍአይነትከታችየተዘረዘሩትንይምረጡ፡፡(ከአንድበላይመልስይቻላል)፡፡

103
የኢንተርፕሪነርሺፕስልጠና---------------------------------------------------
-- 1
የንግድሥራአመራርስልጠና-------------------------------------- ------------ 2
የግብይትክህሎትማሳደጊያስልጠና ------------------------------------------
----- 3
የንግድልማትአገልግሎት ----------------------------------------------- 4
የጥራትናምርታማትማሻሻያሥራአመራርቴክኒክካይዘንስልጠና --------
--------- 5
የሙያብቃትምዘናማረጋገጫሰርተፊኬት------------------------------------
------ 6
የተሟላመረጃማግኝት -------------------------------------------------- 7
የምርጥተሞክሮቅመራናማስተላለፍድጋፍ ------------------------------- 8
የቴክኒክእናሙያስልጠና ----------------------------------------------- 9
የምክርእናድጋፍአገልግሎት -------------------------------------------- 10
የጥቃቅንእናአነስተኛድህረገጽዳይሪክቶሪትአጠቃቀምድጋፍ -----------
-- 11
ሌላካለይጻፍ --------------
ተ.
ቁ ጥያቄ ኮድ
38 ኢንተርፕራይዙየቴክኖሎጂዕድገትድጋፍአገልግሎትበተመለከተያገኘውንድጋፍአይነትከታ
ችከተዘረዘሩትይምረጡ፡(ከአንድበላይመልስይቻላል)፡፡
ተስማሚየቴክኖሎጂድጋፍ ---------------------------- 1
ፕሮጀክትፕሮፋይሎችንየማዘጋጀትድጋፍ --------------- 2
የቴክኖሎጂእናየማምረቻመሣሪያድጋፍ ---------------- 3
የጥገናየእድሳትናየመለዋወጫአካላትድጋፍ ------------- 4
የአፈርምርመራ፤የግብአትናምርትፍተሻአገልግሎት ---- 5
ሌላካለይጻፍ --------------
39 ኢንተርፕራይዙያገኘውንየገበያልማትናግብይትድጋፍአገልግሎትአይነትከዚህበታችየተዘረ
ዘሩትንይምረጡ፡፡ (ከአንድበላይመልስይቻላል)፡፡
የሰብኮንትራክቲንግየግብይትሥርዓትድጋፍ ------------ 1
የአውትሶርሲንግየግብይትሥርዓትድጋፍ ---------------- 2
የፍራንቻይዚንግየግብይትሥርዓትድጋፍ ---------------- 3
የአውትግሮወርግብይትሥርዓትድጋፍ ------------------- 4
የጥሬእቃአቅርቦትድጋፍ ------------------------------ 5
የኢግዚቢሽንናባዛርድጋፍ ----------------------------- 6
ሌላካለይጻፍ --------------

40 ኢንተርፕራይዙያገኘውንየፋይናንስናብድርአገልግሎትውጤታማለማድረግየተሰጡድጋፍች
ካሉከዚህበታችከተዘረዘሩትይምረጡ፡፡(ከአንድበላይመልስይቻላል)፡፡
በቂየሆነግንዛቤበቁጠባናበብድርዙሪያ ------ 1
በቂየሆነግንዘቤበሂሰብአያያዝዙሪያ -------- 2
የማምረቻመሳሪያሊዝፕሮግራምተጠቃሚ --
- 3
ሌላካለይጻፍ -------------------------

41 የሚሰጡየድጋፍአይነቶችችግርፈቺእናወቅታዊስለመሆናቸው?
104
ሙሉበሙሉናቸው--------------- 1
በከፊልናቸው -------------------- 2
አይደሉም ------------------------ 3
42 ኢንተርፕራይዙመስሪያቦታድጋፍአገልግሎት?
አግኝቷል ----- 1 አላገኘም--------- 2

43 ኢንተርፕራይዙየመስሪያቦታድጋፍካገኘየሚከተሉትንጥያቄዎችይመልሱ፡፡ በካሬ
የመስሪያቦታዉስፋትበካሬ ----------------------------
ዓ.ም
የመስሪያቦታዉየተሰጠበትዓ.ም ----------------------
-
44 ኢንተርፕራይዙያገኘውየመስሪያቦታአይነትምንድንነው?
ሼድ/ወርክሾፕ(G+0) - ህንፃ(G+1 and above) ------------
----- 1 ----- 2
ለመኪናእጥበት------------------------
ተለጣፊሱቅ-------------- 3 --- 4
ለሻወርእናሽንትቤት---
-- 4 ሌላካለይጻፍ --------------

45 ኢንተርፕራይዙያገኘውየመስሪያቦታአገልግሎቱምንድንነው?
ማምረቻብቻ ----------- 1 ለማምረቻናመሸጫአገልግሎት --------3
መሸጫብቻ ------------- 2
ተ.
ቁ ጥያቄ ኮድ
46 የመስሪያቦታዋናችግርምንድንነዉ? (ከአንድበላይመልስይቻላል)፡፡
የመሠረተልማትችግር
የውሃመስመር ---------- የመጸዳጃቤት ---------
--- 1 --- 4
የመብራት--------------- መንገድ ---------------
-- 2 ---- 5
የማረፊያቦታ ----------- የቤትቁጥር/አድራሻ/--
--- 3 ---- 6
ሌሎችችግሮች
የዲዛይን --------------------------- የቦታውአመቺነት -----------
---- 7 ------- 9
ማዕከላትንየማስተዳደርችግር- - ምንምችግርየለብንም----------
-- 8 ------ 10
ሌላካለይጻፍ ------------------
47 ኢንተርፕራይዙየመስሪያቦታድጋፍካላገኘአሁንእየሰራያለበትሁኔታ?
ከግለሰብበኪራይ ------- ከመንግስትበኪራይ ---------
--- 1 ---- 3
በግልይዞታ ------------- በመኖሪያቤት-----------------
--- 2 -- 4
ሌላካለይጻፍ -----------------
48 ጥቃቅንናአነስተኛኢንተርፕራይዞችየታለመላቸውንስትራቴጂክግብለመምታትከመንግስትየ
ሚደረገውየተለያየድጋፍግልጽ፤ፍትሃዊእናተደራሽስለመሆኑየኢንተርፕራይዙአባላትያላቸ

105
ውአስተያየትምንድንነው ?
(አንድበላይመልስይቻላል)፡፡በተቀመጠውሀሳብየሚስማሙከሆነ1(እስማማለሁ)
ተብሎይጻፍ፤በከፊልየሚስማሙከሆነ2(በከፊልእስማማለሁ)፤የማይስማሙከሆነ3(አልስማማ
ም) ተብሎይጻፍ፡፡
የሚሰጡየድጋፍማእቀፎችዙሪያግልጽናበቂእውቀትአለን --------------------------------
በሚሰጡየድጋፍመእቀፎችዙሪያአሳታፊመድረክአለ ------------------------------------
የሚሰጡየድጋፍማእቀፎችበእድገትደረጃመሰረትናቸው ----------------------------------
በሚፈጠሩችግሮችዙሪያአፋጣኝምላሽይገኛል---------------------------------------------
የሚሰጡድጋፎችከአድሎነጻሁሉምበእኩልነትያገኛል -------------------------------------
ደጋፎችንበቀላሉማግኘትይቻላል ---------------------------------------------------------
ሌላካለይጻፍ-------------------------------
49 ኢንተርፕራይዙበጥቃቅንናአነስተኛኢንተርፕራይዞችልማትስትራቴጂበተቀመጠውየድጋፍ
ማዕቀፎችመሠረትድጋፎችንእንደዘርፉባህርይእናበደረሱበትዕድገትደረጃመሰረትእያገኘነው
?
ሙሉበሙሉያገኛል----------
------ 1 አያገኝም---------- 3
በከፊልያገኛል----------------- እንደየዘርፉባህርይናየደረሰበትደረጃአያገኘ
------- 2 ም--- 4
ሌላካለይጻፍ--------------
50 ኢንተርፕራይዙስራዉንበሚያከናዉንበትወቅትያጋጠመውዋናዋናችግርምንድንነዉ?(እንደ
ችግሮቹክብደትበደረጃይቀመጥ)
የደንበኛአለመኖር ----------- አስፈላጊውንቴክኖሉጂአለማግኝት
--------- 1 --------- 6
ተወዳዳሪአለመሆን ---------- የመንግስትህግናደንብጫና ---------
--------- 2 ------- 7
የጥሬእቃአቅርቦትችግር ---- የመረጃእጥረት -----------------------
--------- 3 ---- 8
የገበያማጣት ----------------- በቂየሆነማምረቻእናመሸጫቦታያለ
-------- 4 መኖር-- 9
የክህሎትናእውቀትማነስ --- ምንምችግርየለብንም-----------------
------------ 5 ------- 10
ሌላካለይጻፍ --------------------
ችግሮቹንለመፍታትመወሰድያለባቸውየመፍትሄሀሳቦችምንመሆንአለባቸውብለውያስባሉ?/
51 ይጻፍ/

_______
መረጃንየሰጠውአባል/አንቀሳቃሽስም____________________ _______
________ ፊርማ_____________ ቀን ___
ቀን
________ _______
መረጃውንየሰበሰበውባለሙያስም ________ _______
______________________________ ፊርማ_____________ _ ___
_______
መረጃውንያረጋገጠውባለሙያስም _______
______________________________ ፊርማ_____________ ቀን ___

106
107

አባሪሁለት፡ለአዲስ አበባ ከተማ የጥቃቅንና አነስተኛ ለከሰሙኢንተርፕራይዞችየተዘጋጀቃለ-መጠይቅ

የከሰሙወይምለሦስተኛ ወገንየተላለፉየጥቃቅንናአነስተኛኢንተርፕራይዞችቆጠራናጥናትቅጽ

በአዲስአበባከተማ አስተ ዳደርከ1996ዓ.ምጀ ምሮተደራጅተ ውየከሰሙወ ይምለሦስተኛወገንየተላለፉ

የጥ ቃቅንናአነስተኛኢ ንተርፕራይዞችዝርዝርመ ረጃማሰባ ሰብያቅጽ(02)

����� ��������������(�����������)
1 23 45 6
���� � � � � � � � � � � � � � � /� 3� � � �
��� ����������� � � � � .� � � � � � � � � � � � .� � /� � �
���

7
8 910
� � � /� � � � ���� �� �� � � � /� � / � � � � � � � � /� � � � � � � � � � �

� .� � � � � � � �
11� � � � � � � � � � � � � � � � � �
� � � � ---------------------------------- 1� � � � � � � � � � � � � --------------
---------------2
12� � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � ?
� � � � ----------------------------------1� � � � -------------------------
------------------------3
� � � � � --------------------------------2� � � � --------------------------
----------------------4
� � � � � � � _________________________________________________________6

13� � � � � � � � � � � � � � � � � � � � ?
� � � � ----------------------------------1� � � � � ------------------------
----------------------- 2
14� � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � ?
� � � ----------------------------------- 1� � � � � � � � � � � ----------------
----4
� � � � � � � � � ----------------------2� � � � � � � � � � -----------------------
---5
� � � � � � � � � � � � � � � � � ---3� � � � � � � ___________________ 6
15� � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � ?
108

� � � � � � � � ------------------------- 1� � � � � � � -------------------------
------4
� � � � � � � � ------------------------- 2� � � ------------------------------
-----------5
� � � � � �-�-�-�-�-�-�-�-_-_-_-_-_-_-_____________ 6
16� � � � � � � � � � �-�-�-�-�-�-�-�-�-�-�-�
-�-3
� ��� �� ���?
������������/1/
� � � � � � � � � � -------------------- 11� � � � � � � � � ----------------------- 15
� � � � � � � � � � ------------------------ 12� � � � � � � � � � � � � � � � � � � ----16
� � � � � � � � � � � � ----------------- 13� � � � � � � � � ---------------------------
17
� � � � � � � � � � � � � � � � � � � ----14� � � � � � � � � � � � -------------------18
� � � � � � � _________________________________________________________________

������������/2/
� � � � � � � � ------------------------�-�-�-21� � � � � � � --------------
� � � � � � � � � � � ------------------22�- �-
�-�-�---�-�-�-�-� �
2�4� � � � � � � 2
� � � � � � � � � � � � � ------------------- 23� � � � � � � � � � � � ------------5-------- 26

� � � � � � � _____________________________________________________________27
����������/3/
���������� �� ���� � � � � � � � � � � � � � � � � � � � ---- 39
3
������ ���������������� �� �� 31
1
� � � � � � � � � -----------------------�-�-�-�--� 3�2� � � � --------------0----------- 311
� � � � � � � � � � � ----------------------�3�3� � � � � � � � � ------------------ 312
� � � � � � � � � � � ---------------------�-�-�-� 3�4� � � � � � � � � � � � � ----- 313
� � � � � � � � � � � ---------------------�-�-�-� 35� � -------------------------------- 314
� � � � � � � � � � � � � --------------- 36 � � � � � � � � ----------------------------315
� � � � � � � � � � � � � � ---------------37� � � � � � � � � � � � � � -------------316
� � � � � � � � � � � � � � � � � � � ------38 � � � � � � � ___________________ 317
���������� �� � � � � � � � 2008� .� Page1

109

��� ������ ��������� ���� ��������������� ������� ��


���
�. ����� ��
� �����������/4/
� � � � � � � � � � � � � � ------------------ 41� � � � � � � � � � � � � � -------------
---45
� � � � � � � ----------------------------------42� � � � -�-�-�-�-�-�------
-�
� � � � � � � ----------------------------------43� � � � � --- �-�-�-�--
-46
-------
----------------47
���� ���� � � -------------------------
44� � � � � � � ___________________ 48
�������/5/
� � � � � � � � � � � � � � � � � -------------------------------------------
----------------------------- 51
� � � � � � � � � � � � � � � � � -------------------------------------------
--------------------------------- 52
� � � � � � � � � � ---------------------------------------------------
------------------------------------------- 53
� � � � � � � _________________________________________________________
____54
� � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � /� � � � � � � � � � � � � � /� � � � � � � ?
(� � � � � � � � � � � � )__________________________________________________
_
17

� � � � � � � � � � � � /� � � � � � � � � � � � � � � � � � � (� � � )� � � � � � � � ? (� � � )

18
� � � � � � � � � � � � /� � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � ?
� � � � � /� � � ------------------------------- 1� � � � � ------------------
-------------------3
19
� � � � /� � � � � -----------------------------2� � � � � � � � ---------------
----------------4
�������� ��������� ��� ������� ���� ���� ���������� � ��?
� � � � � /� � � -------------------------�-�-�-�-�-- --1-------------------
20 � � � � /� � � � � ----------------------------------2 -----------3
���� ���� ���������� �������� � �� ? � � � � � � � � -----------------
� � � � � � � � � � � � � � -------------- 1 - - - - - - --------4
� � � � � � � � � � � � ---------------------2
� � � � � � � � � � � � � � -----------------3
21 � � � � � � � � � � ---------------
� � � � � � � � � ------------------------- -------------4
--6
� � � � � � � � � -------------------------�-�-�-�5� � � � � ----------------
� � � � � � � ___________________________-_-_-_-_-_-_-_-__ 7_____________________
____11 � � � � � � � -----------------
--------------8
� � � � /� � � � � � � � � � -----------
� � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � �-�-�-�-�-�-�9� ��������
� � � � � � � � � � � � � -----------
------- 10

���� ��� ��� ������ ��ቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የ��� ሪፖርት

1� � � � � � � � � � � (� � � )
2� � � � � � � � � � � � � � � � ( � � � )

������������������ ���������� ��� ����� ���������������


� � � � � � � � � � � � � � � (� � � � � � � � � � � � � � )
� � � � � � � � � � -----------------------�-�-�-1 � � � � � � � � � � -----------
� � � � � � � � -------------------------------------5-2� � � � � � � � � �� � � � � � � --
-----6
� � � � � /� � � � � � � ---------------------- 3� � � � � � � � � � � � � -------------
-----7
������ ��� ������ ������4
� � � � � � � � ________________________________________________________
____8

24 � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � ?
� .� � � � � � � � � � � � � � � � � � .� � � � � � � � � � � � � � � � � � �
��� ����������������
18-
28
29-
39
� 40� � �
���
���� ��� ��

����� ���� � � � /� � � � � �
� � ____________________________� � � ______________� �
����� ������ ���� ��
_______________________________� � � ______________� �
��������������� ��
______________________________� � � ______________� �

Pa g
� � � � � � � � � � � � � � � � � � � 2008� .�

� � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � /� /� / � � � � 111

���� ��� ��� ������ ��ቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የ��� ሪፖርት

አባሪሦስት፡ አግባብነትላላቸዉየሥራሀላፊዎችናባለሙያዎችየተዘጋጀየቃለ-መጠይቅጋይድ

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ቆጠራና ጥናት ስራን አስመልክቶ በአስሩ ከፍለ


ከተሞች በ117 ወረዳዎች ስር ያሉትን ኢንተርፕራይዞች ያሉበትን ሁኔታ ለመዳሰስ
ከጽሁፍ መጠይቅ ከሚገኘው መረጃ በተጨማሪ ስለ ኢንተረፕራይዞቹ አጠቃላይ ሁኔታ
የቢሮው መዋቅር (የኢንተርፕራይዞቹ አደራጅ) አስታያየት ምን ይመስላል ለሚለው
መሰረታዊ ጥያቄ ምላሽ ለማግኘት ሲባል በተመረጡ ሶስት ክፍለ ከተሞች አራዳ፣ በየካ
እና በአቃቂ ቃሊቲ ላሉ የጥቃቅንና አነስተኛ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊዎች የቀረበ አጭር ቃለ
መጠይቅ (Interview)

የቃለ መጠይቁ ሂደት (Interview Guidelines)

ቃለ መጠይቅ አድራጊው እራሱን በማስተዋወቅና መላሹን በማመስገን ወደ ጥያቄዎቹ


ከመግባቱ በፊት የሚከተሉትን የመላሽ ግላዊ መረጃ (Interviwee’s personal data)
በማስታወሻው ላይ ማስፈር ይኖርበታል፡፡

ሀ) ለክፍለ ከተማ ጥ/አ/ኢ/ፕራይዞች ልማት ቢሮ ሃላፊዎች የቀረበ ቃለ-መጠይቅ

የኃላፊው ሙሉ ሥም------------------------- ጾታ-----------

የት/ት ደረጃ------------------------ የትምህርት መስክ------------------

ሃላፊነት------------------------------

በመ/ቤቱ የቆየበት ጊዜ---------------

1. በከፍለ ከተማችሁ ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ ከተደራጁት ኢንተ/ፕራይዞች መካከል አብዛኞቹ


በህጋዊ መንገድ የተደራጁት ምን ያህል ይሆናሉ? ህጋዊ የሆኑትስ ከመቼ ጀምሮ ነው
ብለው ያምናሉ?
2. የኢን/ፕራይዞቹ የአደረጃጀት ሁኔታ በእድገት ተኮር ዘርፎች እይታ እና በጾታዊ
ስብጥር አንጻር ያለዎት አስተያየት ምን ይመስላል?

� � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � /� /� / � � � � 112

���� ��� ��� ������ ��ቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የ��� ሪፖርት

3. በስትራቴጂክ የድጋፍ ማዕቀፍ የተሟላ ድጋፍ ያገኙና ያለገኙ ኢንተርፕራይዞች


ተለይተዋልን? የተሟላ ድጋፍ ሲባልስ እንዴት ይገለጻል/ በዓይነት ቢገልጹልን?
4. ከሥራ ዕድል ፈጠራ አኳያ ሲታይስ የቋሚና የጊዜያዊ የስራ እድል ፈጠራው እንዴት
ይመዘናል?
5. በክፍለ ከተማችሁ ኢንተርፕራይዞቹ ከነበሩበት ወደሚቀጥለው ደረጃ የማሸጋገሩ ሁኔታ
በተቀመጠው ደንብና መመሪያ መሠረት አየተተገበረ ነው ብለው ያምናሉ? ካለሆነ
ለ ም ን?
6. በሂደት የከሰሙ ወይም ለሶስተኛ ወገን የተላለፉ ኢንተረፕራየዞችስ ተለይተዋል?
የከሰሙበት ወይም ለሌላ ሶስተኛ ወገን የተላለፉበት ምክንያትስ ታውቋልን?
7. ለኢንተረፕራይዞቹ አጠቃላይ እድገትም ሆነ ለመንግስት አሰራር ማነቆ የሆኑ ዋና
ዋና ችግሮች ምን ምን ናቸው ብለው ያስባሉ? መፍትሄዎቻቸውስ?

ስለ ትብብርዎ እናመሰግናለን!!

� � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � � /� /� / � � � � 113

You might also like