You are on page 1of 6

የ2011ዓ.

ም የሳ/ወ/ዓ/ማዛጋጃ /ጽ/ቤት

የመልከም አስተዳደር እቅድ

መግቢያ

የክልሉ መንግስት የከተማ መሬትን በህግ ለማስተዳደር ይረደው ዘንድ በደንብ ቁጥር 123/2007 እና መማሪያ
ቁጥር 07/08 አውጥቶ በስራ ላይ ያዋለ ቢሆንም ነገር ግን የመሬት ልማት ማኔጅመንት ተግባራችን በርካታ
የመልካም አስተዳደር ችግር መፍለቂያ ሆኖ በከተማችን ላይ ለበርካታ የማ/ሰብ ጥያቄዎች ዋናኛ ምንጭ ሆኖ
ይገኛል

በዚህም መሰረት በመሰረተ ልማት ፡በማዘጋጃ ቤተዊ አ/ት አሰጣጥና የመሬት ጋር የተያያዙ ያሉ የመልካም
አስተዳደር ችግሮችን ለማፍታት ግልጽ እንድሁም ሊተገበር የሚችል የመልካም አስተዳደር እቅድን አቅዶ ወደ ስራ
መግበት የግድ ስለሆነ ይህ የመልካም አስተዳደር እቅድ ተቅዶዋል፡፡

የእቅዱ ዋና ዋና አላማ

ያደሩና ያልተፈቱ አቤቱታዎችን ትክክለኝነት እያረገጋጡ መለያት


የተለዩትን የልተፈቱትን ችግሮችን መፍትሄ መስቀመጥ

አለአግባብ የተነሱ የመብት ጥያቄዎችን መለየት እና ከግለ ሰቦቹ ጋር በመተመማን ጥየቄየቸው


ተገቢ የለመሆኑን ማሰዋቅ

በከተማው ውስጥ የመሬት አቤቱታ አቅራቢዎችን በተያዘው በጃት ዓመት ዜሮ ማድረስ

የእቅዱ ዋናዋና ግብ

1. ከዚህ በፊት መሬታቸው ለልማት የተወሰዳባቸው የከተማ ነዋሪዎች የካሳ ጥያቄ መመለስ ፣
2. በመሬት ጉዳይ በማዘጋጃ ቤት ፣በከተማ ልማት እንዲሁም በወረዳውና ከዚያ በላይ ባሉ መዋቅሮች
የሚንገላቱትን አቤቱታ አቅራቢዎች መቀነስ፣
3. ሁሉም የወረዳውን ነዋሪ በአስተዳደሩ እምነት እንዲኖረው ሁሉም ፈጻሚ ከሌብነት ውጭ
በፍጹም ጫዋነት እቅዱን ማስፋጸም በመመሪያ ና ደንብ መተግበር

የእቅዱ መነሻ ሁኔታ

 በወረዳው ውስጥ በተለያዩ ጊዜ በኪራይ ውል፣


በሊዝ ውል የተላለፋ መሬቶች ከህግና መምሪያ ውጭ የተፋጸሙ በርካታ ስህተቶች ስላሉ
እቅዱን ለመፋጸም ተግዳሮት ሊሆኑበት ይችላሉ፡፡
 የማስፋፊያ ስራ ሊከናወን መሬታቸውን እንዲለቁ የተደረጉ ሰዎች በደንብና መመሪያዉ
መሰረት የትክ እና የካሳ ተግባራቶች ስላልተመሩ የአቤቱታ አቅራቢውን ቁጥር ከፍተኛ
አድርጎት ይገኛል፡፡
 ለልማት የተነሱ ግለሰቦች በወቅቱ የተሰጠው የትክ መሬት በሙሉ ባለመስጠቱ ቀሪ መሬት
ይቀርሀል ተብያለው ብሎ ማቅረቡ፡፡
 የገንዘብ ካሳም ሆነ የመሬት ትክ ለመስጠት የሚኖረው የወረዳው ጣቅላላ አቅም ሁሉንም
አቤቱታ አቅራቢዎች ሊያስተና ግድ አለመቻሉ ፡፡

እቅዱን ለመፋጸም ያሉ ምቹ ሁኔታዎች

 አንደምተወቀው በወረዳችን ወጣቶች የተናሱ በርካታ የመልካም አ/ር ችግሮች


ተነስቶ ፡ለነዚህም ለህዝብ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት የስችል ዘንድ ፡አጠሪ
ኮሚቴ ተመድቦ ችግሮች አንድ በአንድ መለየተቸው ፡ምቹ ሁኔታ ስለምፈጥር ፡
 የአቤቱታ አቅራቢዎች ጥቅል ዝርዝር መረጃ መኖሩ
 አመራሩ የያዘው ቁርጠኛ አቋም የአቤቱታ አቅራቢዎችን የጉዳት ጥልቀት
በመመርመር ቅዳም ተከተል በማስያዝ በመሬት ትክ ያሚያገኙ እና በገንዘብ
ካሳ ያሚያገኙትን ለይቶ ውሳኔ ለመስጠት ዝግጁ መሆኑ፣
 ማዘጋጃ ቤቱ የካሳ ግምቱን በኮሚቴ ሰርቶ ያቀርባል

የእቅዱ ዝርዝር ተግባራት

በዚህ ተግባር ውስጥ የሚፋቱት ጉዳዮች ከአቤቱታ አቅራቢዎች ጋር እና


ከአቤቱታቸው ይዘት ጋር ተያይዞ የሚቀመጥ ሲሆን ማን እንደሚፋጽመው ፤መቼ
እንደሚፋጸም ፤በምን መልኩ እንደሚፋጸም (ማለትም ካሳ /ምትክ )ወዘተ ተሰቶት
እንደሚፋታ ለሁሉም አቤቱታ አቅራቢ በዝርዝር የሚቀመጥ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህም
መሰረት
1. በ2010 ዓ/ም መሬታቸው ለልማት የሄደባቸው አ/አደሮች በተመለከተ ፣

በሴክተረችን አማካኝነት መሬታቸው ለልማት የሄዳባቸው አ/አዳሮች በአዳሻ


ቀበሌ ፣አወልያ መንደር እና ዚኮ ዶሎሎ ቀበሌ ይገኛሉ ፡፡
በአዳሻ ቀበሌ መሬታቸው ለልማት የሄደበቸው አ/አደሮች ቁጥር
23አ/አደሮች ሲሆኑ ፣አወልያ መንደር 12 አ/አደሮች በዚኮ ዶሎሎ 11አ/አደሮች
፣ ሰንኩራ ት/ት 08 እና በኮሌጅ አ/ቢ 03 አ/ አደሮች ናቸው በጥቅሉ 58
አ/አደሮች መሬታቸው ለልማት ተወስዷል፡፡
- የሚፋጸሙ ተግባራት
1.1 የመሬት ምትክ አሰጣጡ ሲፋጸም አላግባብ የተሰጣቸውን ልጆች መሬት ባንክ መመለስ፡፡ የልጅ ስም በዝርዝር
ይታወቃል ስለሆነም ከአዋጅና መመሪያ ውጭ የተፋጸመውን ተግባር ማስተካካል

- የከፋሉት የአፋር ግብር ገንዘብ ተለቅም ፣ካርኒው ታጥፎ ገንዘብ ለግለሰቦቹ መመለስ ይገበዋል
- የእነዝህን ልጆች ወለጆች ማወያየት ይጣይቃል
- ተግባሩ በወረዳው አስተዳደር ፣ከተማ ልማት ጽ/ቤት እና ገቢ ጽ/ቤት በጋራ ይፈፀማል
ተግባሩ በዚህ ወር እስከ ጳጉሜ 1 ተፋጽሞ ይጠናቀቃል፡፡

1.2 የመሬት ምትክ አሰጣጡ ሲተገበር መሬት ያልተሰጣቸው የአ/አደሩ ልጆች (መስፈርቱን
የሚያሟሉት )200 ካሬ እንዲያገኙ ይደረጋል ተግባሩ ከተራ ቁጥር 1 ጋር በተመሳሳይ ይፋጸማል

1.3 አ/አደሮቹ በመመሪያው መሰረት በአባወራ 500 ካሬ ሜትር እንዲሁም 18 ዓመት የሞላቸው ና
ከዚያ በላይ ለሆኑት አብሮ ተጣቃሚ ለሆኑት ምንም ኣይነት የከተማ ቦታ /ቤት በከተማው ውስጥ
በስማቸው ወይም በትደር አጋራቸው ስም የሌላቸው እንዲሁም 18 ዓመት ባልሞላቸው ልጆቻቸው
ስም እንዲሁም ቤት/ቦታ በከተማው ውስጥ የሌላቸው የባለ ይዞታው ልጆች 200 ካ ሜ እንዲረከቡ
ማድረግ ይህም ስራ እንቀለጠፍ ዘንድ ከከተማ ልማት ጽ/ቤት ጋር በጋራ መሆን እስከ መስከረም
10/2011 ዓ/ም ተፈፃሚ ይሆናል፡፡

1.4 በተራ ቁጥር 1.3 ላይ የተመዘገበው በተገቢው ከተከናወነ በትርፍ መሬታቸው ላይ የብር
ካሳ በኮሚቴ መሰረት ለሁሉም አ/አደሮች ፤ከዛም የተሰራውን የገንዘብ ካሳ ለአ/አደሩ
በማስፋረም ባባንክ አካውንት እንዲገባለት ማድረግ

- የሁሉም አ/አደር የኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ወይም የሌላ ያማንኛውም ባንክ ቡክ ማመቻቸት
ማስከፈት በወረዳው አስተዳደር ጽ/ቤት በጣም ባጭር ጊዜ
- የተቋቋመው ካሳ ገመች ኮሚቴ በ1 ሳምንት የሁሉንም መሬት የሄደባቸዉን የካሳ ግመታ ሰርቶ
ለመዘጋጃ መኔጅማንት ማቅረብ
- የተሰራውን የካሳ ግመታ በአስተባባሪው አስገምግሞ ለልምት ተነሺዎች ማስረከብ እስከ መስከረም
10 /2011 ዓ/ም ድረስ
1.5 ሁሉንም መሬት ከ3ኛው ወገን ንጹህ በማድረግ እስከ መስከረም 30 /2011 ዓ/ም
በሲ/ሰርቨንቱ፣በመምህራን ፣በነዋሪዎች ለተደረጁ ማህባራቶች የቤት መስሪያ ቦታ ማስረከብ ፣
- ይህ በሚፋጸምበት ጊዜ ከ400 በለይ አበወራ የከተማው ነዋሪዎች ከፍተኛ የሆነ የመኖሪያ ቤት
መስሪያ ቦታ ችግር በመቅረፍ የአስተዳደሩን ሞጋች ጥያቄ ምላሽ ማስጠት

- ከከተማ ልማት እና ከወረዳው አስተዳደር ጋር በጋራ በመሆን ይፈፀማል የሪፖርት ግንኙነት በየቀኑ
ይሆናል፡፡

2. ከ2005 ዓ/ም እስከ 2009 ዓ/ም ድረስ ያሉ የልማት ተነሺዎች በተመለከተ


በወረዳችን በርካታ ባለይዞታዎች በተለየዩ ጊዜ መሬታቸው ለልማት ተነስቶባቸው ነገር ግን
አስፈላጊውን የመሬት ትክ እና የመሬት ካሳ ባለማስረቱ በአሁን ሰዓት ከፍተኛ የአቤቱታ ምንጮች
ከመሆናቸውም በላይ ፈታኝ ጉዳዮች ሆነዋል፡፡ ስለሆነም በተገቢው አደራጅቶ የችግሮቹን አይነት
ለይቶና ቅደም ተከተል አስይዞ መፍታት ይገባናል፡፡

የአቤቱታዎቹ አይነቶች
ሀ. ከውልባረግ ሀላባ ዋናው አስፓልት ሲሰራ ቤት ፋረሰብኝ ካሳ አልተሰጠኝም ፤የመሬት ምትክም
አልተሰጠኝም
ለ. ለተለያዩ ልማት የእርሻ መሬቴ ስነሳብኝ ፤የተሰጠኝ የመሬት መጠን አነስተኛ ነው፤በቀሪውም መሬቴ
የገንዘብ ካሳ አልተሰለልኝም
ሐ. ለልማት ተብሎ መሬቴ ከተነሳብኝ ብኋላ የትክ መሬት ሲሰጠኝ ፤በሙሉ ሳይሰጠኝ ቀርቶ
ይጨመርልሀል ተብያለሁ በማለት የሚነሱ ናቸው፡፡
የአቤቱታዎቹ አፋታት ዘዴ
- በቅድሚያ ሁሉንም አቤቱታ አቅራቢዎች መመዝገብ እና መያዝ እንዲሁም በተውጣጣ ባለሙያ (
ከከተማ ልማት ) ጋር በጋራ በመሆን የአቤቱታዎቹን ይዘት መለየት
- ቤት ፋርሶባቸው የቤት ማንሺያ ካሳ ያልተሰጠቸውን
- የትክ ስርዓቱ ሲፋጸም ከመመሪያ ውጭ የተፋጸማባቸውን መለየት (ልጆቻቸው መሬት
ማግኛት ሲገባቸው ያልተሰጠቸው (ከ2007ዓ/ም ወዲህ ያለውን ) መለየት
- ምትክ በምዳባ ከተሰጠቸው ብኋላ የተወሰዳበቸው የመሬት መጣን
- በገንዘብ ምትክ ስም መሬት የተሰጣቸውን ባለይዞታዎች መለየት
ተግባሩን እስከ መስከረም 10/2011 ዓ/ም መፈጸም (ታክስ ፎርሱ የደረሰበትን ግኝት
መጠቀም)
- እነዚህን ተግባራቶች ከተከናወኑ በኋላ በወረዳው አስተዳደር ከአቤቱታ አቅራቢዎች ጋር ስለሁኔታው
መወያየት እና ድምዳሜ ላይ መድረስ መሞከር (አላግባብ አቤቱታ የአቀረቡ ግለሰቦች ጥያቄያቸዉን
እነዲያነሱ ማድረግ)
- ከውይይቱ በኋላ ለይተን ንጹህ ካደረግነው መሬት ላይ ከፍታኛ ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ ምላሽ
ሰጥቶ የቅሬታ አቅራቢዎችን እምባ ማበስ እስከ መስከረም 30/2011 ዓ/ም ድረስ
- ለዚህ ተግባር ይረዳ ዘንድ አቤቱታ አቅራቢዎች በሙሉ እንዲመዘገቡ ተደርጓል፡፡

3. ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር የሚፈቱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በተመለከተ፣


ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጋር ተያይዞ በርካታ የከተማው ነዋሪዎች አቤቱታ ሲየነሱ
መቆየታቸው ባሳለፍነቸው የህዝብ መድረኮች አረጋግጠን የተቀበልነው ጉዳይ ነው፤ይህን ጉዳይ ምላሽ
ለመስጠት አቅዶ መተግበር ተጋቢ ነው፡፡
3.1 አቤቱታ አቅራቢዎች የሚያነሷቸው አንኳር ጥያቄዎች
- የቤት ግንባታ ፍቃድ መስጠት
- የአጥር ፍቃድ
- የስም ዝውውር ግምት
- የቦታ ማረጋገጫ በዋስትና ከተያዘ ብኋላ ዋስትና ሲወርድ ሰነድን ማግኘት
- የ cpo አመላላስ ከጫረታ ብኋላ (መጥፋት ፣መቀያየር ወዘታ….)
- የአፈር ግብር ሲገብሩ የሚነሱ ጥየቄዎች
- የወሰን ይከበርልኝ ጥያቄ ያይዞታ ማረጋገጫ መግኘት አገልግሎት
- የይዞታ ማረጋገጫ ማግኘት አገልግሎት ወዘተ ሲሆን
3.2 ለአቤቱታዎቹ መንስኤ የሆኑ ምክንያቶች

- ባለሙያ ሙሉ ጊዜውን በቢሮ ቁጭ ብሎ አገልግሎት አለመስጠቱ


- ባለሙያው በቅንነትና በታማኝነት አንድም አገልግሎት ጠያቂ ግለሰብ አለአግባብ እንዳይገላታብኝ
ብሎ አለመጨነቅ
ተግባራቶችን በተግባር ሁሌ አለመገምገም
- ባለሙያው አለአግበብ ጥቅም ፍላጊና ጠያቂ መሆን (ባለሙያዉ ዉስጥ የስነምግባር ችግር ያለባቸዉ
ሙያተኞች አለመለየታቸዉ)
- ተጠያቂነት ያለው አሰራር አለመከተል
- እቅድ አቅዶ ለማፍታት አለመቀሳቀስ ዋናዋናዎቹ ናቸው ፡፡

3.3 ማዘጋጃ ቤታዊ ተግባራትን ውጤታማ አድርገን መከተል የሚገባን ሁኔታዎች

- በቅድሚያ በተቋማችን ውስጥ ያሉትን መደቦች ባለሙያ ማደራጀት የጽ/ቤቱን ማኔጅመንት


ማጠናከር (በፅ/ቤቱ ሃላፊ እየተሰራ ያለዉ ተግባር መጠናቀቅ ይገበዋል)
- ባለሙያ በየስራ መስኩ የሚፈጽመውን የሂዳት እቅድ አቅዶ ማቅረብ
- ሁሉንም የአገልግሎት አይነቶች በተቀመጠላቸው ስተንዳርድ መሰረት አለ ማህበረ ሰብ እንግልት
መፋጸም
- ተግባር የሚጥሉ፣ልዩ ጥቆማ የሚሰጥባቸውን የስነ ምግባር ችግር ያለባቸውን ፋጸሚዎች እርምጃ
መውሰድ
- ተግባራቶችን በየጊዜው መገምገም የተጠናቀረ እውነተኛ ሪፖርት ማቅረብ

4. ከመሰረተ ልማት ጋር የተያያዙ የመልካም አስተዳደር ጥየቄዎች

- በከተማችን የመንገድ፣የውሃ ፣የመንገድ መብራት፣የተፋሰስ፣የሼድ አቅርቦትጥያቄዎች ከፍተኛ እንደሆኑ


ይታወቃል፡፡
- የመሰረተ ልማት አቅርቦት በተመለካተ አቅም በፈቀደ በበጀት የሚፋጸሙ ተግባራቶች መሆናቸው
እሙን ነው ስለሆነም ፡-
በ2011 ዓ/ም የሚፋጸሙ ተግባራቶች
ተ.ቁ ተግባራት መለኪያ እቅድ ፋጻሚ
1 የአድስ መንገድ ግንባታ ኪ.ሜ 5 ኪ.ሜ ማዘጋጃ ቤት
2 መንገድ ጥጋና ኪ.ሜ 5 ኪ.ሜ ማዘጋጃ ቤት
3 አድስ የድች ስራ ቁጥር 10 ››
4 የድች ጥጋና ስራ ቁጥር 10 ››
5 የሼድ ግንባታ ቁጥር 20 ከተማ ልማት
6 የመንገድ መብራት ኪ.ሜ 5ኪሜ ማዘጋጃ ቤት
7 የውሃ ቧንቧ ዝርጋታ ኪ.ሜ 5 ኪ.ሜ ማዘጋጃ ቤት

የመንገድ ልማት

 ከዚህ በፊት በከተማው ውስጥ ቦሮ እና ሬዳሽ ደፍቶ መንገዶች ለማህበረሰቡ ምቹ ከማድረግ አንጻር
የነበረው አፋጻጸም ዝቅታኛ እንደነበረ የሚያጠያይቅ አይደለም፡፡

በ2011 በጀት ዓመት የወረዳው አስተዳደር በሰጠው ልዩ ትኩረት የተጀመረው የመንገድ ልማት ቀላል አይደለም

ስለሆነም ይህንኑ በእቅዱ እየተመሩ ማስቀጠል የግድ ይለናል፡፡

በመንገድ መሰረተ ልማት ሊየገጥሙን ያሚችሉ ተግዳሮቶች

- ከቅድመ ማቴሪያል አቅርቦት በፊት ያሉ የህግ አሰራሮች ግልጸኝነት ችግር (የጨረታ ሂደቱን ግልጽነቱን
አለማረጋገጥ)
- ወደ ተግባር ሲገባ የሬድ አሽ/ቦሮ መጠን ማነስ
- የባለሙያ ቁርጣኝነት ችግር
- የተዳፋው ቦሮ /ሬዳሽ በጊዜው ያለመበተን
- የበጀት ውስንነት
የሚወሰዱ መፍትሄዎች
ከቅድመ ማቴሪያል በፊት የሚከናወኑ የጫረታ ፣የውል ተግባራቶችን ሁሉም አስፋጻሚ አካለት ባለበት
ማስኬድ
የሬድ አሽ/ቦሮ መጠኑን በየጊዜው በጥብቅ በባለሙያ ማከታተል፤ስራውን በህዝብ ወገንተኝነት
መፈጸም
የበጀት ውስንነቱን ለመፍታት የከተማውን ማህበረ ሰብ አነቃንቆ ተጨማሪ አቅም መፍጠር
የመንገድ መብራት ልማት
በ2011 ዓ/ም ከሚከናወኑ ቁልፍ ተግባሮቻችን ውስጥ ከተማችንን ከጫለማ የጻዳች ከተማ ማድረግ
ነው በዚህም 5 ኪ.ሜ ሽፋን ያለው የመንገድ መብራት ልማት እንዲከናወን ማድረግ ነው፡፡

You might also like