You are on page 1of 6

የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ

የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ


I. አጠቃላይ መግለጫ
የመሥሪያ ቤቱ ስም የሥራ መደቡ መጠሪያ የሥራ ዘርፍ/የሥራ ሂደት
የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የዌብ-ሳይት ሪፖርተር IV የይዘት ማበልፀግና ኢንፎርሜሽን
ስርጭት

በሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር/ቢሮ ብቻ የሚሞላ


የቅርብ ኃላፊ የሥራ መደብ /ተጠሪነት የሥራው ደረጃ የሥራው ኮድ

መሥሪያ ቤቱ የሚገኝበት ቦታ

II. የሥራ መደቡ ዋና ዓላማ፣ ውጤቶችና ተግባራት


2.1. የሥራ መደቡ ዓላማ፡-
 ጥናት በማድረግ፣ ዌብ-ሳይቶችን በመከታተልና በመተንተን፣ ይዘቶችን በማዘጋጀትና በማሰራጨት፣ ግንኙነቶችን
ማጠናከርና የዌብ-ሳይት ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆን አስተዋጽኦ ማድረግ ነው፡፡
2.2. የሥራ መደቡ ውጤቶችና ተግባራት
ውጤት 1፡ የጥናት ሥራዎችን ማከናወንና አሰራር ሥርዓትን ማጠናከር፣

 በዌብ ሳይት የሚጫኑ ይዘቶች ዝግጅት፣ስጭትና ክትትል ደረጃን በጠበቀ መልኩ የሚከናወንበት ሁኔታን ያጣናል፣
 ከተለያዩ አገሮችና ድርጅቶች ተሞክሮዎችን ይቀምራል፣ አሠራሮችን ያጠናል፣ አዳዲስ ሃሳቦችን የሚያካትት ረቂቅ
መመሪያ ያዘጋጃል፣ ለሚመለከተው ያቀርባል፤

 የአገሪቱን የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና የልማት ዕንቅስቃሴዎች በበጎ ጎኑ ከሚመለከቱና ከሚደግፉ የተለያዩ ድህረ-ገጾች ጋር
ግንኙነት ይፈጥራል፣ በአገራዊ አጀንዳ ዙሪያ ያሰባስባል፣ ከተቋሙ ዌብ-ሳይት ጋር ያስተሳስራል፣
 በተቋሙ ዌብ-ሳይት በሚጫኑ ይዘቶች ዙሪያ መልእክቶችን እንዲደግፉና እንዲጋሩ /Like, Share, Subscribe
እንዲያደርጉ/ ደጋፊዎችን ይጋብዛል፣ በመልእክቶቹ ዙሪያ ያከራክራል፣
 የተቋሙን ዌብ-ሳይት ከተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ዌብ-ሳይቶት ጋር ያስተሳስራል፣ መረጃዎችን መለዋወጥ
የሚቻልበትን ሁኔታን አጥንቶ ለውሳኔ ያቀርባል
 የተቋሙ የውስጥ ተገልጋዮች በተቋሙ ውስጥ በሚከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮች በኢንተራኔት/interanet/ መረጃ
የሚለዋወጡበትን ሁኔታ አጥንቶ ለውሳኔ ያቀርባል፣ ስፈቀድም ሙያዊ ሥራን ያከናውናል፣
 የፌዴራል፣ የክልልና የተቋሙን ሃላፊዎችና፣ ኮሙዩኒኬተሮችና ሠራተኞች የድህረገጽ ስልጠና ፍለጎት ዳሰሳ ጥናት
ያደርጋል፣

 የቡድኑ እቅድ ሲዘጋጅ ግብዓት ይሰጣል፣ ከቡድኑ ዕቅድ በመነሳት የስራ ዕቅዱን አዘጋጅቶ ያቀርባል፣ በዕቅዱ
መሠረት ሥራዎችን ያከናውናል፣
 በየወቅቱ ስለ ስራው ክንውን ወቅታዊ ሪፖርት በማዘጋጀት ያቀርባል።
ውጤት 2፡ የዌብ-ሳይት ይዘቶችን በማዘጋጀት ማሰራጨት ፤
 የመንግሥት ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችን፣ ዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮችን፣ የመንግሥት ተቋማት እቅድ
አፈጻጸሞችን፣ ሀገራዊና ከሀገራችን ጋር ተያያዥነት ያላቸው ዓለም አቀፋዊ ወቅታዊ ጉዳዮችን መነሻ በማድረግ
ለሀገራዊ የጋራ መግባባትና ገጽታ ግንባታ የሚሆኑ ይዘቶችን/መልእክቶችን/ ጽሁፎችን፣ ምስሎችን፣ቪዲዮዎችን፣
የመሳሰሉትን/ ያዘጋጃል፣ የአርትኦት ሥራ ይሰራል፣ በተቋሙ ዌብ-ሳይት ይጭናል፣
 ከሌሎች ባለድርሻ አካላት/ከተለያዩ ፌዴራልና ክልል ተቋማትና ግለሰቦች/ ተዘጋጅተው የሚደርሱትን ይዘቶች ከሀገሪቱ
ፖሊሲዎች፣ ስትራተጂዎች፣የአፈጻጸም መመሪያዎችና ሌሎች ህጎች አንፃር የተቃኙ መሆናቸውን አረጋግጦ
በተቋሙ ዌብ-ሳይት ይጭናል፣ መስተካከል የሚገባቸው ይዘቶችን ለይቶ ያቀርባል፣
 አከራካሪ የሆኑ፣ ጥንቃቄ የሚሹና በህግ የሚያስጠይቁ ጉዳዮችን የያዙ መረጃዎችን ለይቶ ለቅርብ ኃላፊ ያቀርባል፣ ማስተካከያ
ሲደረግባቸው በተቋሙ ዌብ-ሳይት ይጭናል፣
 ከአገራችን ጋር ተያያዥነት ያላቸው አለም አቀፋዊና ሀገራዊ ሁነቶች፣ ኮንፍረንሶችና መግለጫዎች ሲኖሩ
ይዘቶችን በተለያየ አግባብ ሳቢና የጥራት ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ ያዘጋጃል፣ የአርትኦት ሥራ ይሰራል፣ በተቋሙ
ዌብ-ሳይት ላይ ይጭናል፣
 በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ የፌዴራል መንግስትና የክልል መስተዳድሮች ፖሊሲዎች፣ አዋጆች፣ ደንቦችና
መመሪያዎች ወዘተ ማህበረሰቡ እንዲያውቃቸው የዌብሳይት ሰታንዳርድን መሠረት በማድረግ ይዘቶችን
ያዘጋጃል፣ የአርኦት ሥራ ይሰራል፣ በተቋሙ ዌብ-ሳይት ላይ ይጭናል፣
 በፌዴራልና ክልል የመንግሥት ተቋማት ዌብሳይቶች የሚጫኑ መረጃዎችን ከሀገራዊ ፈይዳ አኳያ በመቃኘት
አሻሽሎ በተቋሙ ዌብ-ሳይት ይጭናል፣
 የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች የሚያደርጋቸውን የሥራ እንቅስቃሴዎች /ጉብኝቶች፣ መግለጫዎችና ማብራሪያዎች
እንዲሁም በተቋማዊ፣ አገራዊ፣ አከባቢያዊ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ ጉዳዮች ላይ የሚያደርጓቸው ውይይቶችና
ስምምነቶች፣ የመሣሰሉት/ ዙሪያ በቅርበት በመከታተል መልዕክቶችን ለዌብ-ሳይት በሚመጥን መልኩ በተለያየ
አግባብ/ዜና፣ ፊውቸር አርትክል፣ በዶክመንትሪ፣ በፎቶና በመሳሰሉ/ ያዘጋጃል፣ የአርትኦት ሥራ ይሰራል በተቋሙ
ዌብ-ሳይት ይጭናል፣
ውጤት 3፡- የዌብ-ሳይት ይዘቶችን መከታተልና መተንተን
 በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ድረ-ገጾች የሚጫኑ መረጃዎችን ይዘት የመንግስት አቋምንና አቅጣጫን
የሚያንጸባርቁና ለአገር ገጽታ ግንባታና አገራዊ የጋራ መግባባት ከሚኖራቸውን ፋይዳ አንጻር ያላቸውን ጠቀሜታ
ለዌብ-ሳይት በሚመጥን መልኩ ተዘጋጅተው መጫናቸውን ይከታተላል፣ ይተነትናል፣ ክትትልና ድጋፍ
ሊደረግባቸው የሚገቡ ጉዳዮችን እንዲሁም አገራዊ ፋይዳ ያላቸውና ለተቋሙ ዌብ-ሳይት ግብዓት የሚሆኑ
መረጃዎችን ይለያል፣ ለሚመለከተው ያቀርባል፣
 አገራችን አስመልክቶ በተለያዩ ዌብ-ሳይቶች የሚሰራጩ መረጃዎችን ከአገራችን ነባራዊና ተጨባጭ ሁኔታ
አገናዝቦ ይከታተላል፣ ይዘታቸውን ይተነትናል፣ ፈጣን አጸፋዊ ምላሽ /በጽሑፍ፣ በፎቶና በቪዲዮ/ ያዘጋጃል፣
ይጭናል፣ በሌሎች ምላሽ ልሰጥባቸው የሚገቡ ጉዳዮችን ይለያል፣ ለቅርብ ኃላፊ ያቀርባል፣ በአዎንታዊነት
የሚወሰዱትን ለይቶ በግብዓትነት ይጠቀማል፣
 በመስሪያ ቤቱ ድረ-ገጽ የሚጫኑ መልዕክቶች ዙሪያ የሚሰነዘሩ አስተያየቶችን/ግብረመልሶችን/ ይከታተተላል፣
ይዘታቸውን ይተነትናል፣ ይገመግማል፣ ምላሽ ለሚያሻቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ፈጣን አጸፋዊ ምላሽ ይሰጣል፣
ሌሎች ምላሽ እንዲሰጡበት የሚገቡ ጉዳዮችን ለይቶ ለቅርብ ኃላፊ ያቀርባል፣ አዎንታዊነት የሚወሰዱትን
በግብዓትነት ይጠቀማል፣
III. የሥራው ባህሪ መግለጫዎች
3.1. የሥራ ውስብስብነት
 ሥራው የዌብ-ሳይት ተሞክሮዎችን የመቀመር፣ ረቂቅ የአሰራር ስርዓት መመሪያ የማዘጋጀት፣ ለሀገራዊ የጋራ
መግባባትና ገጽታ ግንባታ የሚሆኑ መልእክቶችን በተለያዩ አግባቦች የማዘጋጀት፣ የአርትኦት ሥራን የመስራት፣
አገራዊና ከአገራችን ጋር ተያያዥነት ያላቸው አለም አቀፋዊ ሁነቶችን መሠረት በማድረግ መልእክቶችን
በተለያየ አግባብ አጭር፣ ግልጽ፣ ሳቢና የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ አድርጎ የማዘጋጀትን፣ የዌብ-ሳይት ይዘትን
የመከታተልና የመተንተን፣ የዌብ-ሳይት ግንኙነቶችን የማጠናከር ተግባራትን ማከናወን ነው።
 በሥራ ክንውን ወቅት ተሞክሮ ለመቀመርና ረቂቅ የአሰራር ሥርዓት መመሪያ ለማዘጋጀት ዌብ-ሳይት በአገራች
ተጨባጭ ሁኔታ ገና ያልተስፋፋ መሆኑ፣ ዌብ-ሳይት በባህሪው አለም አቀፋዊ ይዘት ያለው መሆኑ፣ በስራው ሂደት
የቴክኖሎጂ ተለዋዋጭ መሆን የሚያጋጥሙ ችግሮች ሲሆኑ ችግሮችን ለመፍታት በዌብ-ሳይት አጠቃቀም
ተሞክሮ ካላቸው ዓለም አቀፋዊ ድርጅቶችና ካደጉት ሃገሮች ስልጠናዎችን መውሰድና ልምዶችን በመቅሰም፣
በአዳዲስ ቴክኖሎጂ በመታገዝ፣ አዳዲስ የቴክኖሎጂ አማራጮችን በመምረጥ የመፍትሄ እርምጃ በመውሰድ እና
የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ትንተና በማድረግ ችግሮቹን መፍታትን ይጠይቃል፡፡
3.2. ራስን ችሎ መስራት

3.2.1. ሥራው የሚከናወንበት አግባብ

 ሥራው ሀገር አቀፍ የድረ-ገጽ/ ፖርታል/ ፖሊሲና የአፈጻጸም መመሪያን መሠረት በማድረግ ይከናወናል፡፡
3.2.2. ሥራው የሚጠይቀው የክትትልና ድጋፍ ደረጃ
 ሥራው ውጤትን ከማምጣት አንጻር ከስራው ልዩ ባህሪይ ጋር ተያይዞ ለሚዲያ ክትትል ሥራ ፈጣን ምላሽ
ከመስጠት አኳያ እንደ አስፈላጊነቱ ተከታታይ የመረጃ ልውውጥ ያደርጋል፣ በቅርብ ኃላፊው በመጨረሻ አጠቃላይ
ግምገማ ይደረግበታል፡፣
3.3.ተጠያቂነት
3.3.1. ተጠያቂነት ለሥራ ውጤት /

 ሥራው የዌብ-ሳይት ተሞክሮዎችን የመቀመር፣ ረቂቅ የአሰራር ስርዓት መመሪያ የማዘጋጀት፣ ለሀገራዊ የጋራ
መግባባትና ገጽታ ግንባታ የሚሆኑ መልእክቶችን በተለያዩ አግባቦች የማዘጋጀት፣ የአርትኦት ሥራን የመስራት፣
አገራዊና ከአገራችን ጋር ተያያዥነት ያለቸው አለም አቀፋዊ ሁነቶችን መሰረት በማድረግ መልእክቶችን በተለያየ
አግባብ አጭር፣ ግልጽ፣ ሳቢና የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ አድርጎ የማዘጋጀትን፣ የዌብ-ሳይት ይዘትን የመከታተልና
የመተንተን፣ የዌብ-ሳይት ግንኙነቶችን የማጠናከር ተግባራትን በሚጠበቀው የጥራት ደረጃ እና በአግባቡ ባይከናወን
ወይም በስራ ክንውን ወቅት የሚከሰቱ ችግሮች በወቅቱ ባይታረሙ ተቋሙ ለሌሎች ተገልጋዮች የሚሰጠውን
አገልግሎት ያስተጓጉላል፣ ተቋሙ ከተለያዩ የመንግስትና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር ያለውን ግንኙነት
ያሻክራል፣ በጎ ገጽታ ግንባታ ውጤታማ እንዳይሆን ምክንያት ይሆናል። በአጠቃላይ የዌብ-ሳይት ስራን
በማስተጓጎል በዳሬክቶሬቱ ዕቅድ አፈጻጸም ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳድራል።

3.3.2. ተጠያቂነት ለምስጢራዊ መረጃ


 ሥራው ለዌብ-ሳይት የሚጠናቀሩና የሚሰራጩ ሚስጢራዊነት ያላቸውን መረጃዎች አሉት። ሚስጢሮቹ
ቢባክኑ ወይም ሚስጢርነታቸውን ባይጠብቅ በመ/ቤቱና በአገልግሎት ተጠቃሚዎች መካከል ቅራኔ እና
አለመግባባት ይፈጥራል፣
3.4. ፈጠራ
 ሥራው በዌብ-ሳይት የሚጫኑ ይዘቶች ወቅታዊ፣ ሳቢ፣ተነባቢ/ተደማጭ/ እና የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ
እንዲሆኑና በተገልጋዮች ተፈላጊ ሆኖ እንዲጎበኙ የሚያስችሉ ከተለያዩ አገሮችና ድርጅቶች የዌብ-ሳይት ይዘት
አስተዳደርና የክትትል ተሞክሮዎች መቀመርንና አዳዲስ ተክኖሎጂ ጋር ፈጥኖ መላመድና ተግባራዊ ማድረግን
ይጠይቃል፡፡
3.5. የሥራ ግንኙነት /work communication/
3.5.1. የግንኙነቱ ዓይነትና ደረጃ
 ከውስጥ ከቅርብ ኃላፊው፣ በስራ ክፍሉ ካሉ ባለሞያዎች፣ ከልዩ ልዩ የሥራ ክፍሎች ኃላፊዎችና ሠራተኞች
እንዲሁም ከመ/ቤቱ ውጭ ከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር
ይገናኛል፣
3.5.2. የግንኙነቱ ዓላማ/አስፈላጊነት
 የግንኙነቱ ዓላማ የስራ መመሪያ ለመቀበልና ሪፖርት ለማቅረብ፣ መረጃ ለመስጠትና ለመቀበል፣ ከተቋሙ ውጭ
መረጃ ለመስጠትና ለመቀበል፣ ቃለ መጠይቅ ለማድረግ፣ በተመረጡ አጀንዳዎች ዙሪያ ለመከራከርና
ለማከራከር፣ በተሰራጩ መልእክቶችና በተቋሙ ዌብ-ሳይት ዙሪያ ደጋፊ ለማሰባሰብ ይገናኛል።
3.5.3. የግንኙነቱ ድግግሞሽ
 ከውስጥና ከውጭ አካላት ጋር የሚደረገው ግንኙነት ድግግሞሽ ከቀን የስራ ጊዜ 15 በመቶ ይሆናል፡፡
3.6. ኃላፊነት
3.6.1. ኃላፊነት ለሰው ሀብት
 የለበትም፡፡
3.6.1.1 በኃላፊነት የሚመራቸው ሠራተኞች ብዛት
 የለውም
3.6.1.2. የኃላፊነት ዓይነትና ደረጃ ፣
 የለውም
3.6.2. ኃላፊነት ለንዋይ፣
 የለበትም
3.6.3. ኃላፊነት ለንብረት
 ሥራውን ለማከናወን የሚገለግሉ መሣሪያዎች ማለትም ዴስክ ቶፕ ኮምፕውተር፣ ኢ-ቪዲዮ፣ላፕ ቶፕ
ኮምፒውተር፣ ፎቶ ካሜራ፣ ወንበር፣ ጠረጴዛ፣ መደሪደሪያ የመሣሠሉት ዋጋቸው እስከ 60000 የሚገመቱ
ንብረቶችን በአግባቡ የመያዝና የመጠቀም ኃላፊነት አለበት፡፡
3.7. ጥረት
3.7.1 የአዕምሮ ጥረት
 ሥራው የዌብ-ሳይት ተሞክሮዎችን የመቀመር፣ ረቂቅ የአሰራር ስርዓት መመሪያ የማዘጋጀት፣ ለሀገራዊ የጋራ
መግባባትና ገጽታ ግንባታ የሚሆኑ መልእክቶችን በተለያዩ አግባቦች የማዘጋጀት፣ የአርትኦት ሥራን የመስራት፣
አገራዊና ከአገራችን ጋር ተያያዥነት ያለቸው አለም አቀፋዊ ሁነቶችን መሰረት በማድረግ መልእክቶችን በተለያየ
አግባብ አጭር፣ ግልጽ፣ ሳቢና የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ አድርጎ የማዘጋጀትን፣ የዌብ-ሳይት ይዘትን የመከታተልና
የመተንተን፣ የዌብ-ሳይት ግንኙነቶችን የማጠናከር ተግባራትን እንዲሁም ወቅታዊ ሪፖርት ለማዘጋጀት አእምሮ
የሚጠይቅ ሲሆን ከመደበኛ የሥራ ጊዜው 65 % የአእምሮ ጥረትን ይጠይቃል።
3.7.2. ስነልቦናዊ ጥረት/Emotional effort/
 በዌብ-ሳይት የሚሰራጩ መልዕክቶችን አስመልክቶ ማንነታቸው በማይታወቅ ግለሰቦች የሚሰጡ አሉታዊ
አስተየቶች ሥነ-ልቦናዊ ጫና ሲለሚኖረው ሥነ-ልቦናዊ ሥረትን፣ የማሳመን፣ የማስረዳት እና እንዲሁም
የተጠቃሚዎችን ፍላጎት የመረዳትና መፍትሔ አመራጮችን መጠቆምን የመሳሰሉ የሥራ ትጋትና ትእግስትን
የሚጠይቅ ነው።
3.7.3. የዕይታ ጥረት፣
 ሥራው ይዘቶችን በጽሑፍ፣ በቪዲዮ፣ በፎቶና በመሳሰሉ አግባቦች ለማዘጋጀትና የአርትኦት ሥራን ለመሥራት
በኮምፒውተር ለረዥም ሰዓት በትኩረት ማንበብን፣ማዘጋጀትን፣ማሰራጨትንና መከታተልን የሚጠይቅ በመሆኑ
በአይን ላይ ድካም የሚያስከትሉ ተግባራት ያሉበት ሲሆን ከሥራ ጊዜው 60% ያህል ይሆናል።
3.7.4. የአካል ጥረት
 ሥራው 90 በመቶ በመቀመጥ፣ 10 በመቶ መረጃ ለመሰብሰብ በመንቀሳቀስ ይከናወናል፡፡
3.8. የሥራ ሁኔታ
3.8.1. ሥጋትና አደጋ፣
 ሥራው ለአደጋ ተጋላጭነት በሌለበት ሁኔታ የሚሠራ ነው፡፡
3.8.2 የሥራ አካባቢ ሁኔታ
 ሥራው ምቹ በሆነ አከባቢ የሚሰራ ነው፡፡
3.9. እውቀትና ክህሎት፣
3.9.1. የትምህርት
የትምህርት ደረጃ የትምህርት አይነት
በመጀመሪያ /ቢ ኤ፣ ቢኤስ ሲ /ዲግሪ በፖለቲካ ሳይንስ ፣ በቋንቋና ስነ-ጽሁፍ፣ በጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን፣
3.9.2 ሥራውን ለመጀመር የሚያስፈልግ የሥራ ልምድ
የሥራ ልምዱ ለማግኘት የሚጠይቀው ጊዜ ልምዱ የሚገኝበት የሥራ ዓይነት
6 ዓመት የህዝብ ግንኙነት ወይም በጋዜጠኝነት /በዌብ ሳይትና በማህበራዊ
ሚዲያ /
የሥራ ዝርዝሩን ያዘጋጀው ባለሙያ ሥም ፊርማ ቀን

የሥራ ዝርዝሩን ያጸደቀው የኃላፊው ሥም የሥራ መደቡ መጠሪያ ፊርማ ቀን

You might also like