You are on page 1of 21

ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ

የልዩ ስልጠና ፕሮግራሞች ዳይሬክቶሬት

ድፕሎማና ከዛ በታች ያላቸው የአካዳሚው ሰራተኞች

ስልጠና የአደራጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

ታህሳስ /2010 ዓ.ም


አ/ አ

ማውጫ

ተ.ቁ ርዕስ ገጽ

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 0


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

1. ክፍል አንድ
1.1. መግቢያ--------------------------------------------------------------------------------------2
1.2. የተለዩ ሰልጣኞች ድልድልና አገባብ ሁኔታ-------------------------------------------3
1.3. በልዩ ስልጠናና በሰው ሃብት ልማት ዳይሬክቶሬት የተከናወኑ ተግባራት------5

1.3.1. በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተከናወኑ ተግባራት----------------------


1.3.2. በሰው ሃብት ልማት ዳይሬክቶሬት የተከናወኑ ተግባራት---------------

2. ክፍል ሁለት
አደረጃጀቶች የነበራቸውን እንቅስቃሴ በተመለከተ

2.1. በአደረጃጀት የተከናወኑ ተግባራት፡------------------------------------------------7

2.1.1. በቡድን የተከናወኑ ተግባራት በጥንካሬና በክፍተት-----------------------8

2.1.2. የቡድን መሪዎች እንቅስቃሴ-------------------------------------------------9


የቡድን አዎያዩችና የቡድኖች ደረጃ ፍረጃ--------------------------------
2.1.3. በ 1 ለ 5 አደረጃጀቶች የተከናወኑ ተግባራት---------------------------------11
2.2. የሰልጣኞች ተሳትፎ ሁኔታ -------------------------------------------------------------13

2.2.1. የሰልጣኞች የደረጃ ፍረጃ----------------------------------------------------------


2.2.2. የሴቶች ተሳትፎን በተመለከተ-----------------------------------------------21

3. ክፍል ሶስት

በምልከታ የተገኙ መረጃዎች

3.1. የሃይል መድረክን በተመለከተ-----------------------------------------------------------23


3.2. የአደረጃጀቶችን እንቅስቃሴ በሚመለከት---------------------------------------------23

3.3. ኮሚቴዎችን በተመለከት-----------------------------------------------------------------25

3.4. የክትትልና ሪፖርት ስርዓት------------------------------------------------------------26

3.5. ያጋጠሙ ችግሮች------------------------------------------------------------------------26

ክፍል አንድ

1.1. መግቢያ

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 1


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

ሀገራችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ድህነትን ተረት በማድረግ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለመሰለፍ
የአመራሩንና የፈፃሚ አካሉን/ባለሙያውን/ በአመለካከት፣ በክህሎትና በእውቀት መገንባት ቀዳሚ ተግባር መሆኑን

በማመን መንግስት በየደረጃው ያለውን አመራርና ባለሙያዎችን አቅም በስልጠናና በተለያዩ የተሞክሮ ልውውጥ

መድረኮች የመገንባት ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡

የመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚም በየደረጃው ያሉ አመራርና ባለሙያዎችን በመንግስት ፖሊሲና ስትራቴጂዎች
እንዲሁም የልማት አቅጣጫዎች ላይ የምንከተለውን ልማታዊ አስተሳሰብ የማስተማር፣ የማስረጽና
የማሳወቅ በሂደቱም በዋና ዋና አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ብሄራዊ መግባባት እንዲፈጠር ሚናውን የመጫወት
ተልዕኮ የተሰጠው የመንግስት ተቋም መሆኑ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ተቋሙ የተሰጠውን ይህን ትልቅ ሃገራዊ
ተልዕኮ ለማሳካት የተቋሙ የውስጥ አቅም መብቃትና ማጎልበት ይኖርበታል፡፡ በመሆኑም የአካዳሚው
አመራርና ባለሙያ በዋና ዋና ሀገራዊ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ዙሪያ የጠራ ግንዛቤና የጋራ አመለካከት
እንድይዙ ከዚህ በፊት ስልጠና ያልወሰዱትን ድፖሎማና ከዚያ በታች ያላቸውን የአካዳሚው ሰራተኞችን
በመንግስት ፖሊሲና ስትራቴጂዎች እንዲሁም አካዳሚው ሀገራችን በተያያዘችው የህዳሴ ጉዞ ላይ ባለው ጉልህ ሚና ላይ
በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ በታቀደው እቅድ መሰረት ሰልጣኞችን በአካዳሚው ውስጥ ካሉ 10 ዳይሬክቶሬቶች በማከፋፈል
መረጃዎቹ ተደራጅተው እንዲመጡ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ስልጠናውን የማደራጀት ስራ ተከናውኗል፡፡ ይህ
ለድፖሎማና ከዛበታች ላላቸው ባለሙያዎች የሚሰጥ ስልጠና ከህዳር 20/2010 እስከ ታህሳስ 06/2010 ዓ.ም
ለመስጠት ዝግጅቱን በማጠናቀቅ 47 ሰልጣኞችን ለማሰልጠን የታቀደ ቢሆንም ወደ ስልጠና ማዕከሉ (አ/አ ስራ አመራር
ኢንስቲትዩት) ቀርበው የተመዘገቡና ስልጠናቸውን መከታተል የጀመሩት ወንድ 17፣ ሴት 20 በድምሩ 37 (መሰልጠን
ካለባቸው 78.7%) ሰልጣኞች ናቸው፡፡ የልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት ከሰው ሃብት ልማት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር
የሰልጣኞችን ዝርዝር በማሰባሰብ የተለያዩ የስራ ዳይሬክቶሬቶችን ተዋጽኦ በጠበቀ መልኩ በቡድን የመደልደል ስራ
እንዲከናወን በማድረግ ሰልጣኞች ወደ ስልጠና ቦታ ሲመጡ ለምዝገባ በሚመች መልኩ የማደራጀትና ሰልጣኞችን
የመመዝገብ ስራ ተከናውኗል፡፡

በዚሁ መሰረት የዚህ ስልጠና ከቅድመ ዝግጅት እስከ አቀባበልና አጀማመር የተከናወኑ ተግባራትን በሚመለከት

በአቀባበል ሪፖርት የተገለፀ ሲሆን ለስልጠናው የተዘጋጁ ሰነዶች ማለትም የተሃድሶው መስመርና የኢት/ያ

ህዳሴ፣ የኢትዮጵያ ፌዴራል ስርዓት ባህርያት፤የዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባታ ሂደት፤ስኬቶችና የወደፊት


አቅጣጫዎች፣ የኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ስትራቴጅ፣ የግብርና ልማት ስትራቴጂና የኢት/ያ ህዳሴና

የህዳሴው ጉዟችንና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በሚል የቀረቡት ሰነዶች በተያዘላቸው የስልጠና የጊዜ ሰሌዳ

መሰረት ተጠናቀዋል፡፡ በእነዚህም የስልጠና አጀንዳዎች የተፈጠረውን አቅምና የስልጠና ሂደቱን መገምገም

አስፈላጊ በመሆኑ በስልጠናው ሂደት የተፈጠሩ አደረጃጀቶችን እንቅስቃሴ ከአደረጃጀቶችና ከምልከታ በተገኘ

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 2


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

መረጃ መሰረት የተገኘው ውጤት ለቀጣይ ስልጠና ግብዓት ሆኖ እንዲያገለግል በሚያስችል መልኩ

በስልጠናው ማጠቃለያ የአደረጃጀት ስራዎች በሦስት ምዕራፍ በመክፈል ማለትም ምዕራፍ አንድ መግቢያ፤

መሰልጠን ያለባቸው ድፕሎማና ከዛ በታች የሆኑ ሰልጣኞች ድልድልና በልዩ ስልጠናና በሰው ሃይል ልማት
ዳይሬክቶሬት የተከናወኑ ተግባራን ያካተተ ሲሆን፤ በአደረጃጀት የተከናወኑ ተግባራትን በምዕራፍ ሁለት ፣

አንዲሁም በምልከታ የተገኙ መረጃዎችንና ያጋጠሙ ችግሮች በተመለከተ በምዕራፍ ሶስት ተካተው ሪፖርቱ

እንደሚከተለው ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡

1.2. ከየዳይሬክቶሬቶች መሰልጠን ያለባቸው ሰልጣኞች ድልድልና አገባብ

ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው ባለሙያዎች የሚሰጠውን ስልጠና መሰልጠን ያለባቸው ሰልጣኞች በሁሉም
የአካዳሚው የስራ ክፍሎች/ዳይሬክተሮች/ ድልድል የተደረገ ሲሆን በመመልመያ መስፈርቱ መሰረት ሰልጣኞች
ተመልምለው ወደ ሰልጠና እንዲላኩ በማድረግ በምልመላ ሂዴቱ ላይ የክትትል ስራ በዳይሬክቶሬታችን
ተሰርቷል፡፡ የልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የሚቀየሩና በሌላ የተተኩ ሰልጣኞችን በስዓቱ እንዲቀየሩ የማድረጉን
ስራ በጥብቅ ለማከናወን የሞከረ ቢሆንም አንዳንድ ሰልጣኞች ዘግይተው የመግባትና የመንጠባጠብ ሁኔታ
በሰፊው ታይቷል፡፡ በተለይም የሰልጣኝ መንጠባጠብ ችግር እስከ መጨረሻው ሰዓት የቀጠለና ሰፊም ነበር፡፡
ከዚህ በመነሳት ለስራ ክፍሎች/ዳይሬክቶሬቶች/ የተሰጠ የሰልጣኞች ድልድል፣ የገባ ሰልጣኝና የቀረ ሰልጣኝ
በየዳይሬክቶሬቶች እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ሰንጠረዥ 1፤ በአካዳሚያችን ዳይሬክቶሬቶች ስር ድፕሎማና ከዛ በታች ያላቸውና መሰልጠን ያለባቸው


ሰልጣኞች ድልድል፣ ወደ ስልጠናው የገቡና ያልገቡ ሰልጣኞች መረጃ፤

መሰልጠን የገባ ሰልጣኝ የገቡ ወደ ስልጠና


ስልጠናውን ውን
ተ. የስራ ዘርፍ ያለባቸው ወ ሴ ድ በ% ስልጠናው ያልገቡ
ያቋረጡ ያጠናቀ
ቁ ያልገቡ በ% ቁ
ብዛት

ብዛት

በ% በ%
1 ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት 3 1 2 3 100 - - 2 66.7 1
2 ፋይናንስ አስተዳደር 5 1 2 3 60 2 40 3
ዳይሬክቶሬት
3 ጠቅላላ አገ/ን/አስ/ር 21 10 4 14 66.7 7 33.3 7 50 7
ዳይሬክቶሬት
4 እቅድ ክትትልና ግምገማ 2 - 2 2 100 - - 2
ዳይሬክቶሬት

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 3


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

5 ት/ርትና ስልጠና ዘርፍ 2 - 2 2 100 - - 1 50 1


6 የውስጥ ኦድት 1 - 1 1 100 - - 1
7 የስልጠና አመራር 6 4 2 6 100 - - 1 16.7 5
ዳይሬክቶሬት
8 የአመራር አቅም 1 - 1 1 100 - - 1 100 0
ማጎልበት ዳይሬክቶሬት
9 የሰው ሃብት ልማት 4 1 2 3 75 1 25 1 33.3 2
ዳይሬክቶሬት
10 ምርምርና ልማት 2 - 2 2 100 - - 2
ዳይሬክቶሬት
ድምር 47 17 20 37 78.7 10 21.3 13 35.1 24 64.9

ከመረጃው ለማየት እንደሚቻለው በአካዳሚው ያሉት ሁሉም ዳይሬክቶሬቶች በተሻለ ሰልጣኞችን ወደ


ስልጣናው የላኩ ሲሆን ነገር ግን አንዳንድ ዳይሬክቶሬቶች ለስልጠናው የተመለመሉ ሰራተኞቻቸውን
ለስልጠናው መላክ ሲገባቸው ያልላኩ አሉ፡፡ መሰልጠን ያለባቸውን ሰልጣኞች ከመላክ አንፃር በሰፊው ክፍተት
የታየባቸው ዳይሬክቶሬቶችን ስናይ፤

 ከጠቅላላ አገ/ን/አስ/ር ዳይሬክቶሬት (መሰልጠን ካለባቸው ውስጥ 7 ሰራተኞች ወይም 33.3%) ፣


ከፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት (2 ሰልጣኝ ወይም መሰልጠን ካለባቸው 40%)፣ ከሰው ሃብት ልማት
ዳይሬክቶሬት (1 ሰልጣኝ ወይም መሰልጠን ካለባቸው 25%) በድምሩ መግባት ከነበረባቸው ውስጥ
10 ሰልጣኞች(21.3%) የሚሆኑ ሰልጣኞች ከነዚህ ዳይሬክቶሬቶች ከስልጠናው የቀሩ ሲሆን፤
 በአንፃሩ ከሰንጠረዡ መረዳት እንደሚቻለው ሌሎች የተቀሩት 7 ቱ ዳይሬክቶሬቶች መሰልጠን
ካለባቸው ሰልጣኞች ውስጥ ሁሉም የመጡ ወይም ምንም ከስልጠናው የቀረ ሰልጣኝ የሌለባቸው
ናቸው፡፡
 ወደ ስልጠናው ከገቡ በኋላ በተለያዩ ምክንያቶች ከስልጠናው መቅረት በማባዛታቸው በስልጠና
ኮሚቴው ውሳኔ የተባረሩና በጤና እክልና በሌሎች አስገዳጅ ሁኔታወችም ስልጠናውን ያቋረጡ
ሰልጣኞችን ስናይ ከጠቅላላ አገ/ን/አስ/ር ዳይሬክቶሬት ለስልጠናው ከመጡት 14 ሰልጣኞች መካከል 7 ቱ
(50%) ፣ ከፕሬዚዳንት ጽ/ቤት 2 ሰልጣኝ(66.7) እንድሁም ከስልጠና አመራር፣ ከአመራ አቅም ማጎልበት፣
ከት/ርትና ስልጠና ዘርፍና ከሰው ሃለብት ልማት ዳይሬክቶሬት አንድ አንድ ሰልጣኝ በድምሩ 13
ሰልጣኝ(ለስልጠናው ከገቡት ውስጥ 35.1%) ቢሮ ለስራ በመፈለግ ምክንያት ስልጠናውን
አቋርጠዋል፡፡

በአጠቃላይ በዚህ ስልጠና መሰልጠን ካለባቸው 47 ሰልጣኞች መካከል 37 ቱ (78.7%) በስልጠናው የተገኙ
ሲሆን፤ 10 ሰልጣኝ ወይም ከጠቅላላው 21.3% የሚሆኑ ሰልጣኞች ወደ ስልጠናው አልገቡም፡፡ በተጨማሪም
13 ሰልጣኞች (ለስልጠናው ከገቡት ውስጥ 35.1%) ቢሮ ለስራ በመፈለግና በህመም ምክንያት ቀሪ
በማብዛታቸው በስልጠና ኮሚቴው ውሳኔ ስልጠናውን ያቋረጡ ሲሆን ወደ ስልጠናው ከገቡት ውስጥ 24

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 4


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

ሰልጣኞች(64.91%) ብቻ ስልጠናውን ተከታትለው ጨርሰዋል፡፡ ለስልጠና የገባን ሰራተኛ በሃላፊው በኩል


ለስራ መጠራት የዚህ ስልጠና ስር የሰደደ ችግር ስለነበር በቀጣዩ ይህ ችግር ተፈቶ ከስልጠናው ያቋረጡና የቀሩ
ሰልጣኞች አስፈላጊውን ስልጠና እንዲያገኙ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት ይኖርበታል፡፡

1.3. በልዩ ስልጠናና በሰው ሃብት ልማት ዳይሬክቶሬቶች የተከናወኑ ተግባራት በጥንካሬና በጉድለት

1.3.1. በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተከናወኑ ተግባራት

የልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት በዋናነት ከሰው ሃብት ልማት ዳይሬክቶሬት ጋር እንድሁም በተዋረድ ጉዳዩ
ከሚመለከታቸው ሌሎች ዳይሬክቶሬቶች ጋር በመተባበር ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ የጋራ እቅድ በማቀድ ወደ
ስራ ለመግባት ጥረት ተደርጓል፡፡ በዚህም ስልጠናው የተቀመጠለትን የውስጥ አቅምን የመገንባት ግብ ማሳካት
እንዲቻል የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመፍጠር፣ አፈፃፀማቸውን የመገምገምና ኦረንቴሽን የመስጠት ስራ
ተሰርቷል፡፡ ከዚህም አንፃር ዳይሬክቶሬቱ እነዚህ ሰነዶች ሲሰጡ ያከናወናቸው ተግባራት ከእቅድ አንፃር
ተግባራትን በመገምገም እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

በጥንካሬ፤

 ድፕሎማና ከዛ በታች ያላቸው ሰራተኞችን ለማሰልጠን ተግባራትን ለመመዘን በሚያስችልና ከሰው

ሃብት ልማትና ከሌሎች ዳይሬክቶሬቶች ጋር በቅንጅት ሊያሰራ በሚያስችል መልኩ የስልጠና

ማስፈፀሚያ እቅድ መዘጋጀቱ፤


 ከአካዳሚያችን የስራ ባህሪና ከሰልጣኞች የት/ርት ደረጃና አቅም ጋር የሚመጣጠኑ የስልጠና
አጀንዳዎች መምረጥ መቻሉ፤
 ከዚህ በፊት የተካሄዱ ስልጠናዎች አፈፃፀም ላይ የተገኙትን ልምድና ተሞክሮዎች እንደ ግብአት

መጠቀም መቻሉ፤

 አስፈላጊ መረጃዎችን የያዘ የሰልጣኞች መመዝገቢያ ቅጽ በማዘጋጀት የሰልጣኞች ምዘገባ መደረጉ፤


 በምዝገባ ወቅት ለስልጠናው የተመለመሉትን ሰልጣኞች የማጣራት ሥራና ፈጣን ምዝገባ መካሄዱ፤
 የተለያዩ የስልጠና ቅፃቅፆችንና ሰነዶችን በማባዛት ለሁሉም ቡድኖችና ሰልጣኞች ማዳረስ መቻሉ፤

 የቡድን አወያዮችን በመሰብሰብ በስልጠና ወቅት አብረን የምንሰራቸውን ስራወችና የአደረጃጀትና


የአቅም ማጎልበቻ ሪፖርት ፎርማቶችን እንደት እንደሚሞሉልንና እንደሚልኩልን ገለፃ የማድረግና
የማስረዳት ስራ መሰራቱ፤
 መረጃዎችን የማጥራትና ያልተሟሉትን እንዲሟሉ የማድረግ ስራ መከናወኑ፣

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 5


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

 የኢንተርኔት አገልግሎት ለሰልጣኙ ምቹ እንዲሆን ለማመቻቸት መሞከሩ፣

 የሰልጣኞች፣ የቡድን እንደ አካል፣ የቡድን መሪ እና የረዳት ቡድን መሪዎች የየራሳቸው መመዘኛ
(መገምገሚያ) ነጥቦች ከሰልጣኞች አንፃር መዘጋጀቱ፤
 የስልጠናውን የእለታዊ የድርጊት መርሃ ግብር ማዘጋጀት መቻሉ፤
 የስልጠናውን ቦታና ቀን መወሰኑ፤
 ስልጠናውን የሚያስተባብሩ ንዑስ አደረጃጀቶችን በማዋቀር ወደ ስራ መገባቱ፤
 በመስፈርቱ መሰረት አወያዩችን መመልመላቸውና መመደባቸው፤
 ከስልጠናው ኮሚቴ ጋር በጋራ በመሆን የስልተናውን ሂደት በመገምገም እርምጃ እስከመውሰድ የደረሱ
መፍትሄዎች ላይ በጋራ መስራት መቻሉ፤

በድክመት፤
 የስልጠና ሰነዶች ኮፒና በእጅ ስቴፕለር የተመቱ በመሆናቸው ለእይታ የማይስቡና ለማንበብ አመች
ያለመሆናቸው፤

1.3.2. በከሰው ሃብት ልማት ዳይሬክቶሬት የተከናወኑ ስራዎች

በጥንካሬ
 በአካዳሚችን ውስጥ ባሉ ሁሉም ዳይሬክቶሬቶች ስር ያሉ ድፕሎማና ከዛ በታች ያላቸውን
ሰራተኞች መረጃ በዝርዝር በመለየት በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ስራ መግባት መቻሉ፤
 ስልጠናውን በጋራ የሚያሰራን የጋራ እቅድ መታቀዱ፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 6


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

 የቡድን ዋና አወያዮችንና ረዳት አወያዮችን እንዲሁም ሰልጣኞች (በስብጥር) በየቡድኑ


የመደልደሉ ስራ በጋራ መሰራቱ፤
 ለስልጠና የተመለመሉ ሰልጣኞችን ዝርዝር በስዓቱ ማሳወቅ መቻሉ፤
 የበጀት ፕሮፖዛል ማዘጋጀትና ማስወሰን መቻሉ፤

በክፍተት

 የለም

ክፍል ሁለት

አደረጃጀቶች የነበራቸው እንቅስቃሴ፡-

ድፕሎማና ከዛ በታች ያላቸውን የአካዳሚያችንን ሰራተኞች በመንግስት ፖሊሲና ስታራቴጅ ላይ ስልጠና


ለማሰልጠን ከታቀደው 47 ሰልጣኞች ውስጥ 37 ስልጣኞች ወደ ስልጠናው ሲገቡ፤ 13 ሰልጣኞች በስራ
መፈለግና በህመም ምክንያት ስልጠናውን ያቋረጡ ሲሆን ስልጠናው በያዘለት ጊዜ ተሰጥቶ ተጠናቋል፡፡

ስልጠናውን ሁሉን አቀፍና አሳታፊ ለማድረግ ያመች ዘንድ ሰልጣኙን በተለያዩ አደረጃጀቶች በማደራጀትና
እንዲታቀፉ በማድረግ የሚማማሩበትን ሁኔታ መፍጠር ተችሏል፡፡ ስለሆነም ሰልጣኞችን በ 2 ቡድኖችና

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 7


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

በአምስት የ 1 ለ 5 ህዋሶች በማደራጀትና ኦረንቴሽን በመስጠት ስራዎችን ከማሳወቅ ጀምሮ እያንዳንዱ


አደረጃጀት የሚኖረውን ተግባርና ኃላፊነት በመግለጽና ለእያንዳንዱ ቡድንም የአቅም ማጎልበትና የአደረጃጀት
አስተባባሪዎች በመመደብ ወደ የስልጠና ስራዎች እንዲገቡ የማስተባበር ስራም ተከናውኗል፡፡ በዚሁ መሰረት
ሁሉም የቡድን መሪዎች እስከ ስልጠናው ፍፃሜ ድረስ ለሰልጣኞችና ለ 1 ለ 5 ህዋሶች ድጋፍና ክትትል
አድርገዋል፡፡

2.1. በአደረጃጀት የተከናወኑ ተግባራት፡-

እያንዳንዱን ቡድን የሚያስተባብሩ ሁለት ቡድን መሪዎች(ዋናና ረዳት ቡድን መሪ) ያሉ ሲሆን የአቅም
ማጎልበት ስራዎችን በዋና ቡድን መሪዎች እንድሁም የአደረጃጀት ስራዎችን በረዳት የቡድን አወያይዩች
አማካኝነት ክትትልና ድጋፍ እየተደረገና እየተመሩ ወደተግባር ገብተው ስልጠናው ተጠናቋል፡፡

በዚህም መሰረት ከአደረጃጀት አንፃር በቡድን፣ በአወያዩችና በ 1 ለ 5 ህዋሶች የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት


በዚህ ምዕረፍ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

2.1.1. በቡድን የተከናወኑ ተግባራት፤

በጥንካሬ፡-

 የእያንዳንዱ አደረጃጀት መነሻ እቅድ መታቀዱና ወደ ስራ የተገባ መሆኑ፤ ማለትም፡-


 እያንዳንዱ ቡድን የራሳቸውን እቅድ ማቀዳቸው፤
 እያንዳንዱ ሰልጣን በነፍስ ወከፍ ራስን የማብቅት የግለሰብ እቅድ ማቀዱ፤
 ውይይቱ ፍፁም ዴሞክራሲያዊ፣ አሳታፊና ነፃ ውይይት መሆኑ፤
 አብዛኛው አባላት በቡድን ውይይትም ሆነ በኃይል መድረክ ከተጠበቀው በላይ ንቁ ተሳትፎ ማድረጋቸው፤
 የቡድን ውይይቱ በፅብረቃ መጀመሩ፤
 በስልጠና ወቅት ማስታወሻና መፅሐፍ/ሰነድ/ የመያዝ ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱና በተሻለ
መንገድ መቀረፍ መቻሉ፤
 የቡድን አባላቱ በሰዓቱ በስብሰባ ቦታ መገኘታቸው፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 8


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

 በተፈጠሩት አደረጃጀቶች መወያየታቸውና የቡድኖችንና የኃይል መድረኩን በመገምገም ማስተካከያዎችን


ማድረጋቸው፤
 መፅሐፍ እያነበቡ በመጥቀስ ጭምር መከራከራቸውና በቀረበው አጀንዳ ዙሪያ ብቻ መወያየታቸው፤
 የቡድን ውይይቶችን በቃለጉባኤ መያዝ መቻሉ፤
 የሂስ ግለሂስ ግምገማውን በጥሩ ሁኔታና በሃላፊነት ስሜት ማድረጋቸው፤
 ዘና የሚያደርጉና አነቃቂ ቀልዶች በመሃል መኖራቸው፤
 ቡድኖች ሰልጣኝ አባላትን እንዲያስተባብሩና እንድከታተሉ ጥረት መደረጉ፤

በክፍተት፡-
 አንዳንድ የተመደቡ የቡድን አወያዩች በተለያዩ ምክንያቶች አለመገኘታቸውና ስልጠናው ባልተሟላ
የቡድን አመያዩች መካሄዱ፤
 አንዳንድ የቡድን አባላት የስዓት ፊርማ በስዓቱ ያለመፈረም፤
 አልፎ አልፎ በኃይል መድረክ ወጣ ገባ የማለትና ከሻይ እበፍት የመንጠባጠብ ሁኔታ፤
 አንዳንድ ሰልጣኞች በቡድን ውይይት ወቅት ጥሩ እየተሳተፉ በሃይል መድረክ ግን ንቁ ተሳትፎ ያለማድረጋቸው፤

2.1.2. የቡድን መሪዎች እንቅስቃሴን በሚመለከት

በጥንካሬ
 ፍትሃዊ፣አሳታፊ፣ ነፃና ዴሞክራሲያዊ መድረክ መፍጠር መቻላቸው፤
 አዳዲስ ሀሳቦች እንዲወጡ ማበረታታቸው፤
 ውይይቱ ሁሉንም አሳታፊ እንዲሆን በስም በመጥራት ጭምር ጥረት ማድረጋቸው፤
 ትኩረት የሚያስፈልጋቸውና አከራካሪ ጉዳዩችን ለይተው ለቡድኑ በመግለፅና በመስጠት ሰልጣኙ የጋራ
መግባባት ላይ እንዲደርስ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር የጠራ አመለካከት ለማስያዝ ጥረት
ማድረጋቸው፤
 ከአጀንዳ ሲወጣና ግልፅ ላልሆነ ጥያቄ እና ሀሳብ አቅጣጫ መስጠት መቻላቸው፤
 ውይይቶችና ክርክሮች ከግለሰብ ጋር ሳይገናኙ/ሃሳብን ከግለሰብ በመለየት/ ሀሳብ ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ
መምራት መቻላቸው፤
 ለራሳቸው ሰፊ ሰዓት በመውሰድ የሌሎች ተሳትፎ እንዲገደብ ከማድረግ በመቆጠብ በጣም አጭር ጊዜ
መውሰድ፤
 ውይይቱ አሰልቺ እንዳይሆን በመሀል ዘና የሚያደርጉ ቀልዶችን መጠቀማቸው፤
 ከቡድን የተነሱ ጥያቄዎች አደራጅተው ሲጨርሱ መጀመሪያ ለቡድኑ አባላት በማቅረብ የተረሳ ካለ ለማካተት
መሞከሩና የተመረጡ ጥያቄዎችን አባላቱ ጋር ተስማምተው ለኃይል መድረክ እንዲቀርቡ ማድረጋቸው፤
 የቀሩ/ያረፈዱ/ ሰልጣኞችን መለየትና ለአስተባባሪ ኮሚቴው መጠቆም መቻላቸው፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 9


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

 በሰልጣኞች መካከል ተቀራራቢ አቅም እንድፈጠር መጣራቸው፤


 የሃሳብ መሰረቅ ሲያጋጥም ወደ ውይይቱ መስመር የመመለስ ሂደት መኖሩ፤
 በስራቸው ላሉ ለ 1 ለ 5 ህዋሳት ክትትልና ድጋፍ ማድረጋቸው፤

በድክመት
 ረዳት የቡድን አወያይ ባለመኖሩ ምክንያት የስራ ጫና በመኖሩ ለሃይል መድረክ የሚሄዱ ጥያቄዎችን በስዓቱ
ለማስተላለፍ መቸገር፤
 በአንዳንድ ተሳታፊዎች ሃሳብ ሲደጋገም ያለማስቆም፤
 በሰልጣኞች መካከል ተመጣጣኝ እውቀት እንዲኖር ጥረት የተደረገ ቢሆንም የተወሰነ ድክመት ያለ
መሆኑ፤
ሰንጠረዥ 2፤ ቡድን እንደ አካል ሲገመገምና የቡድን መሪዎች ደረጃ ፍረጃ

ቡድን እንደ አካል ለቡድን መሪዎች የተሰጠ ደረጃ


ቡድን ሲገመገም ለቡድኑ የተሰጠ ለረዳት ቡድን መሪ ምርመራ
ደረጃ ለዋና ቡድን መሪ (አወያይ)
1 A A A
2 A A - ረዳት አወያይ
የለም

ጠ/ድምር 2 2 1

የሰንጠረዡ ማብራሪያ፤

 የቡድን ደረጃ ምደባ እንደአካል ሲታይ ከተገመገሙት 15 ቡድኖች መካከል ሁሉም ቡድን
በ A ደረጃ ተፈርጀዋል፡፡

 በ 2 ቡድኖች ከተመደቡት 3 ዋናና ረዳት አወያዮች ውስጥ ሁሉም ቡድኖች ለዋና አወያዩቻቸው(ቡድን
መሪዎቻቸው) እና ለረዳት አወያዩቻቸው ማለትም ለሁለቱም አወያዩቻቸው A ደረጃ የሰጡ መሆኑን
መረጃው ያሳያል፡፡

 ይህም የሚያሳየው በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ቡድኖችና አወያዮቻቸው ጥሩ መሻሻሎችን


ማሳየታቸውንና መልካም ቁመና ላይ መሆናቸውን ነው፡፡

2.1.3. በ 1 ለ 5 አደረጃጀቶች የተከናወኑ ተግባራት በጥንካሬና በድክመት፡-

በጥንካሬ

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 10


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

 በሃይል መድረክም ሆነ በቡድን ውይይት በተነሱ ጥያቄዎችም ሆነ ያልበሰሉ ሀሳቦች መካከል ግልፅ
ባልሆኑ ጉዳዩች ላይ ሰፊ ጊዜ ሰጥተው መወያየታቸውና ወደ ቡድን ቀርቦ ውይይት ሊደረግባቸው
የሚገቡትን በመለየት ረገድ ጥሩ ጥረት መደረጉ፤
 የህዋስ ውይይቶችንና የሂስ ግለሂስ ሪፖርቶችን በአግባቡ አዘጋጅተው ማቅረባቸው፤
 አባላት የስልጠና ሰነዱን እንዲያነቡና ለስልጠናው በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ መደገፋቸው፤
 ሰልጣኙ ጥሩ ዲሲፕሊን እንዲኖረውና ወደ ተመጣጣኝ አቅም እንድመጣ የተሞከረ ጥረት መኖሩ፤

በክፍተት የታዩ፡-

 በስዓት እጥረትና በሰርቪስ ስዓት መድረስ ምክንያት በየለቱ በመገናኘት የውሎ ግምገማ
አለማድረጋቸው፤
 ህዋስ አባላትን በተሟላ መልኩ ወደ ተመጣጣኝ አቅም ማምጣት ላይ ውስንነት መኖሩ፤
 የአባላትን ተሳትፎ፣ አመለካከትና ብስለት በመከታተል ጉድለትን ሊያሻሽል የሚችል ተከታታይ
ግንባታና ድጋፍ ማድረግ ላይ ክፍተት መኖሩ፤
 በመካከላቸው ያለውን ተነፃፃሪ አቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት 1 ለ 1 እንድደጋገፉ ማድረግ ላይ
ውስንነት መኖሩ፤
 በውይይት ወቅት ሰፊ ጊዜ ወስደው የማብሰልና ክርክር በማድረግ በኩል ውስንነት መኖሩ፤

2.2. የሰልጣኞች ተሳትፎን በተመለከተ

ስልጠኙ ለሀይል መድረክ ከሚሰጠው ማብራሪያ፣ ከሰነድና በግሉ ከነበረው ግንዛቤ ተነስቶ ሃሳቦችንና
አመለካከቶችን በነፃነት በማንሸራሸር ግንዛቤውን እንዲያዳብር ይረዳ ዘንድ የስልጠናው ስነ ዘዴ ሰልጣኝ ተኮር
ሆኖ እንዲመራ ተደርጓል፡፡ በዚህም በቡድኖችና በህዋስ ውይይት አባሉ በንቃት እንዲሳትፍ ተደርጓል፡፡ ከዚህ
አንፃር የነበረው እንቅስቃሴ እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 11


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

በጥንካሬ፡-

 አብዛኛው ሰልጣኝ በውይይትም ሆነ በኃይል መድረክ ከተጠበቀው በላይ ንቁ ተሳትፎና በሳል ሃሳቦችን
ማንሸራሸር መቻላቸው፤
 በገለፃ ወቅት ማስታወሻ የመያዝ ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱ፤
 አብዛኛው ሰልጣኝ በ 1 ለ 5 /ህዋስ/ አደረጃጀት ላይ በአግባቡ መሳተፋቸው፤
 ሰልጣኞች በአፈፃፀም የታዘቡዋቸውን ችግሮች ከመልካም ልምዶች ጋር በማስተሳሰር በያገባኛል
መንፈስ ጥሩ ውይይት ማድረግ መቻሉ፣
 ሰልጣኙ በስልጠና አዳራሽና በውይይት ክፍሎች ጥሩ ግንኙነትና ውህደት የነበረው መሆኑ፤
 ከሁሉም ዳይሬክተሮቶች ተውጣጥተው በቡድን ተደልድለው መወያየታቸው ለልምድ ልውውጥ
እና መደጋገፉ ትልቅ እገዛ ማድረጉ፤
 አጀንዳዎች አገር አቀፍ ሁኔታንና የአካዳሚያችንን ሚና ለመገንዘብ ማስቻላቸው፤
 የሴቶች ተሳትፎ ከስልጠናው አጋማሽ በኃላ እየተጠናከረ መምጣቱ፤
 ያን ያክል የጎላ የስነምግባር ችግር ያለባቸው ሰልጣኞች አለመኖራቸውና ስልጠናውን በጥሩ
ድሲፕሊን መከታተል መቻላቸው፤

በድክመት፡-

 የስልጠናው ቦታ ለቢሮ ቅርብ በመሆኑ ምክንያት ሰልጣኞች በስልጠና ወቅት ለስራ በሃላፊዎቻቸው
በመጠራታቸው የመሄድና የመቅረት እንድሁም የማርፈድ ሁኔታ በመኖሩ የስልጠናውን ሰዓት በአግባቡ
መጠቀም ላይ እንቅፋት መፍጠሩ፤
 ሰልጣኖች ማስታወሻ የመያዝ ውስንነት መኖሩ፤
 የተሰጣቸውን ሰነዶች በአግባቡ አለማንበባቸው፤
 አንዳንድ ሰልጣኞች እስከ ስልጠናው መጨረሻ ድረስ ንቁ፣ መሳጭና የተጠናከረ ተሳትፎ ያለማድረጋቸው፤
 አስተማሪና አዝናኝ ቀልዶችን ማቅረብ ላይ ውስንነት መኖሩ፤
 የሴቶች ተሳትፎ ወደ ስልጠናው መጨረሻ ላይ መሻሻል ቢያሳይም በሚፈለገው መልኩ ያለመሆኑ፤

2.2.1. የሰልጣኞችን የደረጃ ምደባ በሚመለከት

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 12


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

በአካዳሚው የስልጠና ሂደት መሰረት እያንዳንዱ ሰነድ ሲጠናቀቅ ሰልጣኞች በእያንዳንዱ የስልጠና አጀንዳዎች
ያመጡትን ለውጥ ለማየት ያስችል ዘንድ የሰልጣኞችና የቡድን እንድሁም የህዋሶች የደረጃ ፍረጃ ግምገማ የሚደረግ
ቢሆንም ይህ ስልጠና በአብዛኛው ድፕሎማና ከዛ በታች ያላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሳተፉበት በመሆኑና
ከስልጠና ጊዜ መጣበብ ጋር ተዳምሮ ሂስ ግለሂሱን በእያንዳንዱ የስልጠና ሰነድ ከማድረግ ይልቅ በስልጠናው ማጠናቀቂያ
ላይ ብቻ ማየቱ የሚበቃ መሆኑ ስለታመነበት የቡድኖች ደረጃ ፍረጃና የአወያዩችና የሰልጣኞች ሂስ ግለሂስ በስልጠናው
መጨረሻ ላይ ብቻ ተካሂዶ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 13


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

ሰንጠረዥ 3.የሰልጣኞች ደረጃ ፍረጃ

በ%
የስራ ዘርፍ ድምር
ፋይናንስ እቅድ አመ/ር አቅም የሰው
ቡድን ደረጃ ጠቅላላ ት/ርትና የውስ የስልጠና ምርምር
ፕሬዚዳን አስተዳደ ክትትልና ሃብት
አገ/ን/አስ/ ስልጠና ጥ አመራር ማጎልበት ና ልማት
ት ጽ/ቤት ር ግምገማ ልማት
ር ዳ/ሬት ዘርፍ ኦድት ዳ/ሬት ዳ/ሬት
ዳ/ቶሬት ዳ/ሬት ዳ/ሬት ዳ/ሬት
A ወ 1 1 2
ሴ 1 1
ድ 1 1 1 3 27.3
ወ 1 1 2 4
1 B ሴ 1 1 1 1 4
ድ 1 2 1 1 3 8 72.7
ወ -
C ሴ -
ድ -
ጠ/ድምር 1 3 2 1 4 11 100
A ወ 0
ሴ 0
ድ - - - - - - - - - - 0
ወ 2 2
2 B ሴ 1 1 1 1 1 5
ድ 3 1 1 1 1 7 70
ወ -
C ሴ 1 2 3
ድ - - - - 1 - - - - 2 3 30
ጠ/ድምር - - 3 1 1 1 1 1 2 10 100
ጠቅላላ A 0 1 1 - - - 1 - - - 3 14.3
ጠቅላላ B 1 2 4 2 - 1 5 - - - 15 71.4
ጠቅላላ C 1 2 3 14.3
ጠቅላላ ድምር 1 3 5 2 1 1 6 2 21 100

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 14


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

ማሳሰቢያ፤

 ከቡድን 1 ሶስት ሰልጣኞች ፈተናውን ተፈትነው ከስዓት በመቅረታቸው ምክንያት የደረጃ ፍረጃ
አልተደረገላቸውም፡፡

ከዚህ ከሰንጠረዥ መረዳት እንደሚቻለው፤

 በቡድን ደረጃ ሲታይ፤


 ከቡድን 1 ሰልጣኞች ውስጥ 3 ሰልጣኞች(27.3%) በከፍተኛ ደረጃ A የተፈረጁ ሲሆኑ የተቀሩት 8
ሰልጣኞች(72.7%) በመካከለኛ B ደረጃ ተፈርጀዋል፡፡በዚህ ቡድን ዝቅተኛ ደረጃ C የተፈረጀ ሰልጣኝ
የለም፡፡
 ከቡድን 2 ሰልጣኞች ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ A የተፈረጀ ሰልጣኝ የሌለ ሲሆን 7 ሰልጣኞች(70%)
በመካከለኛ B ደረጃ፤ የተቀሩት 3 ቱ(30%)ደግሞ በዝቅተኛ ደረጃ C ተፈርጀዋል፡፡
 ስለሆነም በቡድን 2 በከፍተኛ A ደረጃ የተፈረጁ ሰልጣኞች ከቡድን 1 ጋር በአንፃራዊ መልኩ ሲታይ
በጣም ዝቅተኛ (0%) መጠን አሳይቷል፡፡በዚህ ቡድን ብዙ ሰልጣኞች በመካከለኛ ደረጃ የተፈረጁና
ቀሪዎቹ በዝቅተኛ ደረጃ የተፈረጁ ናቸው፡፡ ስለዚህ በቡድን እንቅስቃሴውና በተሳትፎው ቡድን 1 የተሻለ
እንደነበር ያሳያል፡፡

 በአጠቃላይ የሰልጣኞች ዝርዝር ሁኔታ ሲታይ የደረጃ ምደባ ግምገማ ካደረጉት 21 ሰልጣኞች መካከል
አብዛኞቹ ሰልጣኞች ማለትም ከጠቅላላው 15 ሰልጣኞች (71.4%) በመካከለኛ B ደረጃ ላይ ሲሆን በከፍተኛ
ደረጃ A የተፈረጁት 3 ሰልጣኞች(ከጠቀላላው 14.3%) ናቸው፡፡ የተቀሩት 3 ሰልጣኞች (ከጠቅላላው 14.3%)
ደግሞ በዝቅተኛ ደረጃ C ተፈርጀዋል፡፡ ይህም አብዛኞቹ ሰልጣኞች በመካከለኞ ደረጃ ላይ ያረፉና ተቀራራቢ
የሆነ የእውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት ደረጃ እንዳላቸው ያሳያል፡፡

2.2.2. የሴቶች ተሳትፎን በተመለከተ፡-

የሴቶችን ተሳትፎና የደረጃምደባ በየቡድኑ ምን እንደሚመስል ለማየት ከላይ የሰልጣኞች ደረጃ ምደባ ሰንጠረዡን
መረጃ መሰረት በማድረግ እንደሚከተለው ማየት ይቻላል፡፡

ሰንጠረዥ 4. የሴቶች ተሳትፎ በየቡድኑ

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 15


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

ቡድን በቡድኑ የተገመገሙ ያገኙት የደረጃ ምደባ


ሴቶች ብዛት ምርመራ
A በ% B በ% C በ%
1 5 1 20 4 80 - - በጣም ጥሩ ተሳትፎ
2 8 - - 5 62.5 3 37.5 ዝቅተኛ ተሳትፎ

ጠ/ድምር 13 1 7.7% 9 69.2% 3 23.1 መካከለኛ ተሳትፎ

ከዚህ ሰንጠረዥ መረዳት እንደሚቻለው፤

 የደረጃ ምደባ ግምገማ ካደረጉት 13 ሴት ሰልጣኞች መካከል አብዛኞቹ ማለትም 9 (69.2%) በ መካከለኛ B ደገጃ
ሲፈረጁ አንድ ሴት ሰልጣኝ ብቻ በ A ደረጃና ቀሪ 3 (23.1%) ሴቶች በእቅተኛ ደረጃ C የተፈረጁ ናቸው፡፡
 በመረጃው መሰረት የሴቶች ተሳትፎ በአንፃራዊ መልኩ ሲታይ፡-
 ቡድን 1 በጣም ጥሩ የሴቶች ተሳትፎ ያለበት ቡድን ሲሆን በዚህ ቡድን ካሉት ሴቶች ውስጥ አንድ ሴት
ሰልጣኝ በ A ደረጃ የተፈረጀችና ሌሎች ሁሎችም በመካከለኛ ደረጃ ላይ ናቸው፡፡
 በአንፃሩ ሲታይ ቡድን 2 በጣም ዝቅተኛ የሴቶች ተሳትፎ ማለትም በቡድኑ ካሉት ሴቶች ውስጥ
0% በከፍተኛ ደረጃና 3 ሰልጣኞች በ C ደረጃ(37.5%) ላይ የተፈረጁ ሲሆን ይህ ቡድን ዝቅተኛ
የሴቶች ተሳትፎ ታይቶበታል፡፡
 ከዚህ መረዳት የሚቻለው እንደ አጠቃላይ በዚህ ስልጠና ላይ የሴቶች ተሳትፎ በመካከለኛ ደረጃ B
(ከጠቅላላ ሴቶች 9 ኙ ወይም 69.2%) እንደሆነ ነው፡፡

ማሳሰቢያ፤የቡድን 1 አባል የሆነች አንድ ሴት ሰልጣኝ የደረጃ ፍረጃ አልተደረገላትም፡፡

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 16


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

ክፍል ሶስት

በምልከታ የተገኙ መረጃዎች

የአደረጃጀቶችን እንቅስቃሴ ለማየት በተደረገው ምልከታ የሃይል መድረኩን፣ የቡድኖችን፣ የ 1 ለ 5 አደረጃጀቶችን


ውይይት ሂደት በሚከተለው መልኩ በጥንካሬና በድክመት ለማየት ተሞክሯል፤

3.1. የሃይል መድረክን በተመለከተ፤

በጥንክሬ፡-

 የሰልጣኞች ቁጥር አናሳ ስለሆነ ሃይል መድረኩን ለመቆጣጠርና ለመከታተል አመች መሆኑ፤
 አብዛኛው ሰልጣኝ ለሃይል መድረኩ በጊዜ ቀድመው መገኘታቸው፤
 ሰልጣኞች በዋና አሰልጣኙ ገለፃ ሲሰጥ ማስታወሻ መያዛቸው ሁኔታ መሻሻሎች ማሳየታቸው፤
 ሰነዶቹ ከሌሎች ሰነዶችና ዓለም አቀፋዊ ተሞክሮዎች ጋር እየተዛመደ መቅረብ መቻላቸው፤
 በዋና አሰልጣኞች የተሰጠው ገለፃ በምሳሌዎች የተደገፈና ለሰልጣኞች ግልፅ በሆነ መልኩ መቅረቡ፤

በክፍተት፡-

 አንዳንድ ሰልጣኞች ለሽንትና በሌላ ሰበቦች በሃይል መድረክና በቡድን ውይይት ወቅት መውጣት
መግባት መኖሩ፤
 በአንዳንድ ሰልጣኞች ስዓት ያለማክበርና መንጠባጠብ መኖሩ፤
 አብዛኞቹ ሰልጣኞች በሃይል መድረክ ገለፃ ወቅት ማስታወሻ ያለመያዛቸው፤

3.2. የአደረጃጀቶችን እንቅስቃሴ በሚመለከት

በጥንካሬ

 የቡድንና ህዋስ አደረጃጀቶች በጋራና በቅንጅት ወደ ተግባር መግባታቸው፤


 በአፈፃፀም ረገድ በአካዳሚያችን የሚታዩ ችግሮች ተነስተው ውይይት መደረጉ፤
 ቡድኖች ሁሉም ሰልጣኝ ወደ ተቀራረበ ቁመና እንድመጣ ጥረት ማድረጋቸው፤
 የቡድኖች ውይይቶች በቃለ ጉባዔ መያዙ፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 17


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

 ሰልጣኞች በሃይል መድረክ ገለፃም ሆነ በውይይት ወቅት ማስታወሻ የመያዛቸው ሁኔታ ወደ መጨረሻ
ላይ ጥሩ መሻሻሎችን ማሳየቱ፤
 ውይይቱ ፍፁም ዴሞክራሲያዊ፣ ነፃና አሳታፊ ውይይት መሆኑ፤
 የቡድን አባላት በኃይል መድረክ ላይ ሀሳብ በመስጠትና በመከራከር የሚሳተፉ መሆናቸው፤
 በየአደረጃጀቶቹ ያሉ አባላት በስልጠናው ሂደት ላይ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ክርክርና ውይይት ማድረግ
መቻላቸው፤

በድክመት፤

 አብዛኛው ሰልጣኞች የስልጠና ሰነዱን ቀድመው አንብበው ያለመምጣታቸው፤


 አንዳንድ ሰልጣኞች ሃይል መድረክ ገለፃ ላይ ማስታወሻ ያለመያዛቸው፤
 በተለይ በመጀመሪያዎቹ ሰነዶች አንዳንድ ሰልጣኞች ንቁ ተሳትፎ ያለማድረጋቸው፤ በተለይ የሴቶች
ተሳትፎ በጣም ደካማና የነበረ መሆኑ፤
 የፓናል ውይይትና ኬዝ ስተዲስ ባለመኖሩ የቡድን አባላቱ በአጀንዳዎቹ ላይ ከዚህ የበለጠ ጥልቅ
ውይይት ማድረግ አለመቻላቸው፤
 በጊዜ እጥረት ምክንያት የሚነሱ ሃሳቦችን በጥልቀት መወያየት ላይ ውስንነት መኖሩ፤
 በአንዳንድ ሰልጣኞች የሃሳብ መደጋገምና ሃሳብን አደራጅቶ ማቅረብ ላይ ውስንነቶች መኖሩ፤
 ከስልጠና ሰነዱ በተጨማሪ ተያያዥ ማጣቀሻ መጽሕፍትን ለማቅረብ የሚያስችል የላይበራሪ
አገልግሎት አለመኖሩ፤
 የውይይት ማደማደሚያዎችን በቂ ጊዜ ሰጥቶ በአግባቡ ውይይቶችን ከማደማደም አንፃር ውስንነት
መኖሩ/በተለይ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ስልጠና ሰነድ አሰለልጣኑ ባለመምጣቱ ከቡድኖች የተነሱ
ጥያቄዎችን በቡድን አወያዩችና በአስተባባሪዎች ብቻ ለማደማደም መገደድ/፤
 የ 1 ለ 5 ህዋሳትን በተጠናከረና ተከታታይነት ባለው መልኩ በመደገፍ ረገድ ውስንነት መኖሩና የህዋሳት
ውይይት ለማካሄድ የጊዜ እጥረት መኖሩ፤
 የተመደቡ የቡድን አወያዩች በተለያዩ ምክንያቶች ባለመገኘታቸው ምክንያት የነበሩትን
በማቀያየር/በመበተን/ እና ባልተሟሉ የቡድን አወያዩች ለመስራት መገደድና በዚህም የተነሳ የቡድን
ሪፖርቶች በወቅቱና በፎርማቱ መሰረት ማዘጋጀትና መላክ ላይ ውስንነት መኖሩ፤
 የመዝናኛ ኮሚቴ ባለመኖሩ ስልጠናውን እያዋዙ ለመስጠት አለመቻሉ፤

3.3. ኮሚቴዎችን በተመለከተ

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 18


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

የአደረጃጀት ዘርፍ ኮሚቴ (በዚህ ስልጠና የቡድን ዋናና ረዳት አወያዮች የተካተቱበት ሲሆን) በሚመለከት፡-

በጥንካሬ

 አቴንዳንስ በአግባቡ መያዙና በተደጋጋሚ የቀሩ ሰልጣኞች ላይ ከስልጠና እስከ ማባረር ድረስ ርምጃ
መውሰድ መቻሉ፤
 በስራ ጫና ምክንያት በየዕለቱ ማድረግ ባይቻልም በየሳምንቱ መጨረሻ በመገናኘት ስራዎችን
መገምገም መቻሉ፤
 የሴቶች አደረጃጀት ባይኖርም የሴቶችን ተሳትፎ ለማጠናከር ልዩ ትኩረት በማድረግ ሴቶችን
የማጠናከሩን ስራ በአወያዩቹ መሰራቱ፤
 አደረጃጀቶች (ቡድኖች፣ ህዋሶች) ለስልጠናው የሚጠበቅባቸውን ተግባርና ኃላፊነት በአግባቡ
እየተወጡ መሆናቸው፤

በክፍተት

 በየዕለቱ ማታ ማታ በመገናኘት የዕለት ከዕለት ስራዎችን ያለመገምገማቸው፤


 በስልጠናው አፈፃፀም ወቅት የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመለየት ወደ ሁሉም ቡድኖች
ማስፋፋት ላይ ውስንነት መኖሩ፤
 ሴት ሰልጣኞችን ከዚህ የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችል የሴቶች አደረጃጀት ራሱን ችሎ አለመኖሩ፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 19


ድፕሎማና ከዛ በታች ላላቸው የአካዳሚያችን ሰራተኞች የተሰጠ ስልጠና የአደረጃጀት ማጠቃለያ ሪፖርት

3.4. የክትትልና ሪፖርት ስርዓት

በጥንካሬ

 ሰልጣኞችን የመከታተል፣ ወደ ኋላ የቀሩትንና ችግር ያለባቸውን የመለየትና የሚደገፉበትና


የሚታረሙበት አደረጃጀት መፈጠሩ፤
 የቡድን መሪዎችን የመድረክ አያያዝና አመራር ብቃት ክትትል መደረጉ፤
 አደረጃጀቶች ወቅቱን የጠበቀ ሪፖርት ማቅረባቸው፤
 በስልጠናው ወቅት የውስጥ ክትትል ስራው በተጠናከረ መልኩ መደረጉና በቃልም ቢሆን ግብረ መልስ
መሰጠቱ፤

በክፍተት

 ቡድን መሪዎች፣ የ 1 ለ 5 አደረጃጀቶችን አፈፃፀም በተጠናከረና ቀጣይነት ባለው መልኩ ክትትል


ያለማድረጋቸው፣
 አንዳንድ አደረጃጀቶች ወቅቱን የጠበቀ ሪፖርት ባለማቅረባቸው የተነሳ ጥቅል ሪፖርት ለመስራት
ችግር መፍጠሩ፤

3.5. ያጋጠሙ ችግሮች፡-

የሚከተሉት በስልጠናው ወቅት ጎልተው የታዩና ስልጠናው ላይ ተፅዕኖ ያደረጉ ችግሮች ነበሩ፡፡
እነሱም፡-

 የስልጠናው ቦታ ለቢሮ ቅርብ በመሆኑ ምክንያት ሰልጣኞች በስልጠና ወቅት ለስራ በሃላፊዎቻቸው
በመጠራታቸው የመሄድና የመቅረት እንድሁም የማርፈድ ሁኔታ በመኖሩ የስልጠናውን ሰዓት በአግባቡ
መጠቀም ላይ ችግር መፍጠሩና ብዙ ሰልጣኞችም እንዲያቋርጡ ምክንያት መሆኑ፤
 የተመደቡ የቡድን አወያዩች በተለያዩ ምክንያቶች ባለመገኘታቸው ምክንያት የነበሩትን
በማቀያየር/በመበተን/ እና ባልተሟሉ የቡድን አወያዩች ለመስራት መገደድና በዚህም የተነሳ የቡድን
ሪፖርቶች በወቅቱና በፎርማቱ መሰረት ማዘጋጀትና መላክ ላይ ውስንነት መኖሩ፤
 አንዳንድ አሰልጣኞች በማደማደሚያ ወቅት ያለመገኘታቸውና ውይይቶችን ከማደማደም አንፃር
ውስንነት መኖሩ/በተለይ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ስልጠና ሰነድ አሰለልጣኑ ባለመምጣቱ ከቡድኖች
የተነሱ ጥያቄዎችን በቡድን አወያዩችና በአስተባባሪዎች ብቻ ለማደማደም መገደድ/፤
 ስልጠናውን የሚያጠናክሩ የተለያዩ ኬዝ ስተዲዎችና ፓናል ውይይቶች አለመኖራቸው፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 20

You might also like