You are on page 1of 26

በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ

የልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት

የአንደኛው ዙር የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን

አመራርና ባለሙያዎች ስልጠና የፖለቲካ ዘርፍ

ማጠቃለያ ሪፖርት

ነሐሴ/2009 ዓ.ም
ደብረ ዘይት

ማውጫ
ርዕስ ገጽ

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 0


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

1. መግቢያ..................................................................................................................................................................3
2. በስልጠናው አስፈላጊነት ላይ የተደረገው አጠቃላይ ግምገማን በተመለከተ.................................................................................4
3.1.1. 2.1 የ EBC አመራሮችንና ባለሙያወችን አቅም ከመገንባት አንጻር በስልጠናው አስፈላጊነት ላይ የተደረገ አጠቃላይ ግምገማ........4
3.1.2. 2.2 ከኮርፖሬሽኑ ተልኮና ተግባራት አንፃር የስልጠናው አስፈላጊነትና ወቅታዊነት በተመለከተ........................................7
3.1.3. 2.3 የተሃድሶ መስመርና የኢት/ያ ህዳሴ ላይ የኮርፖሬሽኑ አመራርና ባለሙያ የተሟላ ግልፅነት እንዲፈጥሩ የማድረግ
አስፈላጊነትን በተመለከተ..............................................................................................................13
3.1.4. 2.4. ልማታዊ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ለኢት/ያ ህዳሴና የሚድያው/EBC /ሚና ላይ የተሟላ ግንዛቤ
የመፍጠር
አስፈላጊነት……………………………………………………………………………………………………… ..
3.1.5. 2.5. ሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሙሽን ዕቅድ ዙሪያ ግንዛቤን የመፍጠር
አስፈላጊነት……………………..
3.1.6. 2.6. በኢት/ያ ፌዴራሊዝም ስርዓት ግንባታ ስኬቶችና የወደፊት አቅጣጫዎች ዙሪያ ግንዛቤን የመፍጠር
አስፈላጊነትን በተመለከተ..............................................................................................................17
3.1.7. 2.5. የህዳሴ ጉዟችንና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲያችንን የመገንዘብ አስፈላጊነትን በተመለከተ..........................25
3.1.8. 2.6. በአዎንታዊ አስተሳሰብ ዙሪያ ግንዛቤ የመፍጠር አስፈላጊነት በተመለከተ……………………………….…28
3. በየሰነዱ የተቀመጡ የስልጠና ግቦች መሳካትን በተመለከተ......................................................................................................34
3.1.9. 3.1. የተሃድሶ መስመርና የኢት/ያ ህዳሴ ላይ ግልፅነት ተፈጥሯል................................................................34
3.1.10. 3.2. የልማታዊ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ለኢት/ያ ህዳሴ ላይ የኮርፖሬሽኑ( EBC)ሚና ምን ሊሆን
እንደሚችል ግልፅነት ተፈጥሯል.................................................................................................35
3.1.11. 3.3. በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ ግልፅነት
ተፈጥሯል------------------------------------------
3.1.12. 3.4. የኢት/ያ ፌዴራል ስርዓት ግንባታ ስኬቶች፣ የወደፊት አቅጣጫዎችና በዲሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት ፅንሰ ሃሳብ ላይ በአመራሩና
በባለሙያው ግልፅነት ተፈጥሯል......................................................................................................35
3.1.13. 3.5. የሃገራችን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዎች ላይ በኮርፖሬሽኑ አመራርና ባለሙያዎች ግልጸኝነት ተፈጥሯል..................36
3.1.14. 3.6.በአዎንታዊ አስተሳሰብ ዙሪያ ግንዛቤ ተፈጥሯል..................................................................................37
4. ከአመለካከት አኳያ ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን በተመለከተ...........................................................................................39
5. በሰነዱ መካተትና መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች ተብለው የቀረቡ፤...........................................................................................42
3.1.15. 5.1. የተሃድሶ መስመርና የኢት/ያ ህዳሴ ሰነድ ላይ .............................................................................34
3.1.16. 5.2. ልማታዊ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ለኢት/ያ ህዳሴ ................................................................35
3.1.17. 5.3. የሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ
………………………------------------------------------------
3.1.18. 5.3 የኢት/ያ ፌዴራል ስርዓት ግንባታ ስኬቶችና የወደፊት አቅጣጫዎች.............................................................35
3.1.19. 5.4 የሃገራችን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ..............................................................................................36
3.1.20. 5.5. አዎንታዊ አስተሳሰብ ሰነድ.......................................................................................................37
6. የስልጠናውን አጠቃላይ አመራርና አካሄድ በተመለከተ....................................................................................................45
3.1.21. 6.1. መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚን በተመለከተ.....................................................................................45
3.1.22. 6.2. አሰልጣኝ (ዋና መምህራን) አመራረጥ፣ ገለጻና ማጠቃለያ አቀራረብ..................................................46

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 1


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

3.1.23. 6.3. የአካዳሚዉ አደረጃጀትና የአመራሩ ጠንካራና ደካማ ጐን በተመለከተ..........................................................49


3.1.24. 6.4. ኳሊቲ ሰርክልና ፕሮዳክሽን ቲምን በተመለከተ.............................................................................52
3.1.25. 6.5 እያንዳንዱ ሰልጣኝ ለስልጠናው የሰጠው ትኩረትና ተሳትፎን በተመለከተ.......................................................54
7.ሰልጣኙ በስልጠና ቆይታው በተለያ አካላት ማስተካከያ ሊደረግባቸው በሚል ያነሳቸው ጉዳች..........................................................60
8. ማጠቃለያ..................................................................................................................................................................60

ክፍል አንድ

1. መግቢያ

ሀገራችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ድህነትን ተረት በማድረግ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለመሰለፍ
የአመራሩንና የፈፃሚ አካሉን በአመለካከት፣ በክህሎትና በእውቀት መገንባት ቀዳሚ ተግባር መሆኑን በማመን መንግስት

በየደረጃው ያለውን አመራርና ባለሙያ አቅም በስልጠናና በተለያዩ የተሞክሮ ልውውጥ መድረኮች የመገንባት ስራ
እየሰራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የልማታዊ መንግስቱ የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ሴክተሮች በየፊናቸው የአመራርና

ሙያተኛ አቅም በመገንባት የተነደፉትን ግቦች ለማሳካት ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ የመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚም
ይህንን የስልጠና ስራ ለማከናወን ተልዕኮ ተሰጥቶት ወደ ተግባር ገብቷል፡፡

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽንም ህዝብን የማስተማር፣ የማሳወቅና የማዝናናት በሂደቱም በዋና ዋና


አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ብሄራዊ መግባባት እንዲፈጠር ሚናውን የመጫወት ተልዕኮ የተሰጠው የህዝብ ተቋም
መሆኑ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም የተቋሙ አመራርና ባለሙያ በዋና ዋና ሀገራዊ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ዙሪያ
የጠራ ግንዛቤና የጋራ አመለካከት መያዙ ተቋሙ የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት እንዲወጣ ያስችለዋል፡፡ በመሆኑም
በኮርፖሬሽኑ ያለዉ አመራርና ሙያተኛ በሃገራችን ቀጣይ የልማት ግቦችና የአፈፃፀም አቅጣጫዎች ላይ ተገቢዉን ግንዛቤና
የዳበረ አመለካከት ፈጥሮ ኮርፖሬሽኑ የሚጠበቅበትን ሚና እንዲጫዎት በየደረጃው ያሉትን የኢቢሲ አመራሮችና
ባለሙያዎች በመንግስት ፖሊሲና ስትራቴጂዎች እንዲሁም ኢቢሲ ሀገራችን በተያያዘችው የህዳሴ ጉዞ ላይ ባለው ጉልህ ሚና
ላይ በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ በነባራዊ ሁኔታ ግምገማ የተለዩ የፖሊሲና ስትራቴጂ እውቀትና የግንዛቤ ክፍተቶችን
መሙላት እንዲቻል ከኮርፖሬሽኑ የስራ ባህሪ አንፃር በተመረጡ አጀንዳዎች ላይ ለኮርፖሬሽኑ/EBC/
አመራርና ባለሙያ ስልጠና መስጠት በማስፈለጉ የልዩ ስልጠና ፕሮግራሞች ዳይሬክቶሬት ከ EBC ተቋም ጋር
በመቀናጀት የስልጠና ፍላጎታቸውን መሰረት በማድረግ ሰልጣኞችን በኮርፖሬሽኑ ውስጥ ባሉ 10 ዘርፎች በማከፋፈል
መረጃዎቹ ተደራጅተው እንዲመጡ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ስልጠናውን የመስጠትና የማደራጀት ስራ
ተከናውኗል፡፡፡፡

ስልጠናውን በሁለት ዙር ለመስጠት የታቀደ ሲሆን የመጀመሪያውን ዙር ስልጠና ከነሃሴ 08/2009 እስከ ነሃሴ 28/2009
ዓ.ም ድረስ የተሰጠ ሲሆን በዚህም ዙር 204 ሰልጣኞችን በደብረ ዘይት ስራ አመራር ማሰልጠኛ ማዕከል ለማሰልጠን

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 2


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

የታሰበ ቢሆንም ወደ ስልጠና ማዕከሉ ቀርበው የተመዘገቡና ስልጠናቸውን ለመከታተል ከጀመሩት ወንድ 148 ሴት 45
በድምሩ 193 (94.6%) ሰልጣኞች መካከል --------------- ሰልጣኞች በድሲፕሊን ከስልጠናው
በመሰናበታቸውና---------- ያክሉት ደግሞ በህመም ምክንያት እንድሁም---------- ሰልጣኞች በአስቸኳይ የተቋሙ ስራ
ምክንያት በድምሩ------------ ሰልጣኞች ስልጠናውን ያቋረጡ ሲሆን በአጠቃላይ------------- ሰልጣኞች ስልጠናውን
ተከታትለው አጠናቀዋል፡፡ ዳይሬክቶሬቱ ከኮርፖሬሽኑ ጋር በመተባበር የሰልጣኞችን ዝርዝር በማሰባሰብ የተለያዩ የስራ
ዘርፎችን ተዋጽኦ በጠበቀ መልኩ በቡድን የመደልደል ስራ እንዲከናወን በማድረግ ሰልጣኞች ወደ ስልጠና ቦታ ሲመጡ
ለምዝገባ በሚመች መልኩ የማደራጀትና ሰልጣኞችን የመመዝገብ ስራ ተከናውኗል፡፡

በዚሁ መሰረት የዚህ ዙር ስልጠና ከቅድመ ዝግጅት እስከ አቀባበልና አጀማመር የተከናወኑ ተግባራትን

በሚመለከት በአቀባበል ሪፖርት የተገለፀ ሲሆን ለዙሩ ከተመረጡት ስድስት ሰነዶች ማለትም የመጀመሪያ

የስልጠና ሰነድ ከሆነው የተሃድሶው መስመርና የኢት/ያ ህዳሴ(አጀንዳ /ሰነድ/1) ጀምሮ እስከ መጨረሻው

አዎንታዊ አስተሳሰብ ሰነድ ድረስ የቀረቡት ሰነዶች በተያዘላቸው የስልጠናው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት

ተጠናቀዋል፡፡ በእነዚህም የስልጠና አጀንዳዎች የተፈጠረውን አቅምና የስልጠና ሂደቱን መገምገም አስፈላጊ

በመሆኑ በስልጠናው ሂደት ከተፈጠሩት አደረጃጀቶችና ከምልከታ በተገኘ መረጃ መሰረት የተገኘው ውጤት

ለቀጣይ ሰነድ ግብዓት ሆኖ እንዲያገለግል በሚያስችል መልኩ የሰነዶችን የፖለቲካ ዘርፍ ስራዎች በዝርዝር

ተካተው ሪፖርቱ እንደሚከተለው ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡

2. በስልጠናው አስፈላጊነት ላይ የተደረገው አጠቃላይ ግምገማን በተመለከተ


 የኮርፖሬሽኑን አደረጃጀት በማጠናከር በሃገራዊ ልማት ላይ ያለውን ተሳትፎ ለማሳደግ፤

 የምንገኝበት ዓለም በፈጣን የመረጃ ቴክኖሎጂና ሚዲያ ስርፀት የመጠቀ ነው፡፡ ይሁን እንጂ አሁን
ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የመረጃ ተደራሽነትና ስርፀት ጉዳይ በሃገራችን በሚፈለገው ደረጃ ያልደረፀና
ብዙ ሥራ የሚጠይቅ ነው፡፡
 የሃገራችን ዜጎችም ሆኑ ውጭዎች ስለሃገራችንና አጠቃላይ አለም አቀፍ ሁኔታዎች ማወቅ
ስለሚፈልጓቸው በርካታ ፖለቲካዊ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች መረጃ ለመስጠት
የተቋቋመው ኢቢሲ በዘመናዊ መልኩ የሚጠበቅበትን ጉልህ ሚና እንዲጫወት የህዳሴውን ጉዞ
ለማሳለጥ የሚያስችል የአመለካከት፣ የዕዉቀትና የክህሎት ደረጃ ተላብሶ በመገኘት በኩል በአግባቡ
ያላሳካቸው ማነቆዎች ነበሩ፡፡

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 3


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 ከዚህ አንጻር የኮርፖሬሽኑ አመራርና ባለሙያ የተጣለባቸውን ተልዕኮ በመረዳት ኮርፖሬሽኑን


የሚያጠናክርና አፈፃፀሙን የሚያጎለብት አመራርና ባለሙያ በመፍጠር አገራችን የጀመረችዉን
ህዳሴ ለማስቀጠል የበኩሉን ሚና የሚጫወት ሚዲያ ለመፍጠር የሚያስችል ሥልጠና መስጠት
አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
 በዚህም መሠረት ሥልጠናው የኮርፖሬሽኑን አመራርና ባለሙያ የተዛባ አመለካከት
በማስተካከል፣ዕውቀቱን በማሳደግና ክህሎቱን በማዳበር ባጠቃላይ የማስፈጸምና የመፈፀም አቅም
ችግሩን ለመቅረፍና በመንግስት የልማታዊ ሚዲያ ፖለቲክል ኢኮኖሚ አቅጣጫ መሰረት በአለም
አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሚዲያ ለመፍጠር የሚያሰችል እና በስልጠና ሰልጣኙ እርስ በርስ
የተማማረበትና ልምድ ልውውጥ ያደረገበት በመሆኑ የተሰጠዉ ስልጠና በጣም አስፈላጊ ነው፡፡

 የኮርፖሬሽኑን አመራሮች ፖለቲካዊ አቅም በቀጣይነት ለመገንባት በተመለከተ፦

 በየእርከኑ ያለውን የኮርፖሬሽኑነን አመራር የፖለቲካ አቅም መገንባት አገራችን የተያያዘችውን


የሁለተኛ ዙር የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለማሳካትና የዜጎችን መረጃ የማግኘት ጥያቄ
ለመመለስ በጠንካራ የአመራር ትግልና ያሉትን አቅሞች አሟጦ ለመጠቀም ወሳኝ በመሆኑ
አስፈላጊነቱ አያጠያይቅም፡፡
 አብዛኛው ሰልጣኝ በአመራር አነስተኛ ልምድ ያላቸው መሆናቸው በኮርፖሬሽኑ ተልዕኮና
አሰራር፣በሃገሪቱ የልማትና የዕድገት ፓኬጅና ስትራቴጅዎች፣ በኢትዮጵያ ፌደራል ስርዓት
ግንባታ፣ በልማታዊ ሚድያና ኮሚኒኬሽን ረገድ የኮርፖሬሽኑ አመራርና ባለሙያ ሊኖራቸዉ

ስለሚገባ ሚና እና በአወንታዊ አስተሳሰብ ዙሪያ የግልፅነት መጓደል የታየበት ነው፡፡ ስለሆነም


በነዚህ ዙሪያ ለኮርፖሬሽኑ አመራርና ባለሙያ ስልጠና እንዲሰጥ መደረጉ ተገቢና ወቅታዊ ስልጠና
እንደሆነ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡

2.1. የኮርፖሬሽኑን አመራር እና ባለሙያ በዋና ዋና የመንግስት ፖሊሲዎች እና ስትራቴጂዎች ዙሪያ


ግንዛቤያቸውን የመገንባት አስፈላጊነት፤

2.1.1. ከስልጠናው በፊት የሰልጣኙ ግንዛቤና አመለካከት ፣

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 4


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 አብዛኛዎቹ ሰልጣኞች የሚሰጠውን ስልጠና የአሰለጣጠን ሂደቱ በሀይል መድረክ ገለጻና በቡድን ፣ በህዋስ እንዲሁም
ኳሊቲ ሰርክልና ፕሮዳክሽን ቲም ውይይቶች በመታገዝ የሚሰጥ የተደራጀ ስልጠና እንደሚሆን ያልገመቱ
መሆኑን፤
 የስልጠና ሰአት አጠቃቀሙም በስልጠናው ሂደት ካዩት በተሻለ በቂ እረፍትና የሚዝናኑበትን ጊዜ
የሚሰጣቸው እንደሚሆን ይጠብቁ እንደነበር አንስተዋል፡፡
 ስልጠናውን ከመጀመራቸው በፊት መድረኩ ሀሳባቸውን በነጻነት ማንሸራሸር የማይችሉበት፣
በኮርፖሬሽኑ የሚንጸባረቁ የአመለካከት ችግሮችን ባወጣ እፈረጃለሁ ብሎ የመስጋት ሁኔታዎች
እንደነበሩባቸውና የተሳሳተ አመለካከት ቢያንጸባርቁ የሚያስጠይቃቸው እንደሆነ ይገምቱ እንደነበር
አንስተዋል፡፡
 ሰልጣኞች ከሚጠበቅባቸው ሚና አንጻር ለስልጠናው በተለዩት አጀንዳዎች ላይ በቂ ግንዛቤ የሌላቸው
መሆኑ፣ የአመለካከት፣ የክህሎትና የግንዛቤ ክፍተት የነበረባቸው መሆኑና የነበራቸው ግንዛቤም በተለያየ
ደረጃ ላይ የሚገኝ እንደነበር በሰጡት አስተያየተም ሆነ በቡድን ውይይቶች ከሚያነሷቸው የተሳሳቱ ሀሳቦችና
አመለካከቶች መረዳት ተችሏል፡፡ በተለይም፡-
 በልማታዊ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን፣ በልማታዊ ደሚክራሲ ፅንሰ ሃሳብና በአወንታዊ አስተሳሰብ
ዙሪያ በቂ ግንዛቤ ያልነበረበት እንዲሁም ጋዜጠኛው ተልዕኳቸውን ከልማታዊ ደሚክራሲ
አስተሳሰብ አኳያ እንዴት መፈፀም እንዳለባቸው የነበረው ግልጽነት አናሳ ነበር ማለት
ይቻላል፡፡

 በስልጠናው አጀንዳዎችም ሆነ በሁለንተናዊ ጉዳዮች ዙሪያ የተደበላለቀ አመለካከትና


አስተሳሰብ፣ወጥና ተራማጅ፣ እንዲሁም አብዮታዊና ልማታዊ የሆነ አስተሳሰብ ጉድለት
የነበረበት መሆኑን በየስልጠና አጀንዳዎች የውይይት ሂደት ለመታዘብ ተችሏል፡፡
 ሰልጣኙ ሃገራችን የምትከተላቸው የልማትና የዕድገት ፓኬጅና ፖሊሲዎች ምንነት እና
አስፈላጊነት፣ በሀገራችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ዕድገት ላይ ስለሚኖረዉ
አስተዋጽኦ እና አተገባበር ላይ የተሟላ የግንዛቤ አልነበረውም፡፡
 በፌዴራል ስርዓታችን እና የአገራችን ዘላቂ ሰላም የማረጋገጥ መርሆዎችና የዲሞክራሲያዊ
ብሄርተኝነት ፅንሰ ሃሳብ በመረዳት ረገድ በኢቢሲ ሰልጣኞች ዙሪያ ችግር እንደነበረ ማየት
ተችሏል፡፡
 ሰልጣኙ ስለወደፊቷ ኢትዮጵያና የሌሎች አገሮች ልምድ ላይ አተኩሮ የመስራት አዝማሚ እንጅ ስላለፈ
የኢትዮጵያ ታሪክ ጊዜ ወስዶ ማሰብ ተገቢ አይደለም የሚል አስተሳሰብ ተይዞ ነበር፡፡

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 5


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 የኢቢሲ ባለሙያዎች ኮርፖሬሽኑ ከገጠመው የተዓማኝነትና ተወዳዳሪነት ችግር ለመውጣት


ያላቸውን ሚና ያለመረዳትና የዳር ተመልካችነት እና የጠባቂነት አመለካከት እንደነበረባቸው
መገንዘብ ተችሏል፡፡

ስለሆነም ስልጠናውየወጣት ሊግ አመራሮችን ፖለቲካዊአቅምበማጎልበትና ለተልእኮ በማዘጋጀትረገድወሳኝሚና ያለውና


አስፈላጊ መሆኑን መገንዘብ ተችሏል፡፡

2.1.2. ከስልጠናው በኋላ ሰልጣኙ የፈጠረው ግንዛቤና አመለካከት፣

 መግቢያ ላይ የተሰጠውኦረንቴሽን ሰልጣኞች አጠቃላይ የስልጠናውን ባህሪይና ሂደት እንዲሁም ሊጠብቁት


የሚገባ ስነምግባር ምን መሆን እንዳለበት እንዲረዱ ያስቻላቸውና ሊከተሉት የሚገባውን አቅጣጫ
ያመላከታቸው በመሆኑ በማእከሉ በሚኖራቸው ቆይታ ለስልጠናው ትልቅትኩረት በመስጠት ለመሰልጠን
መነሳሳት የፈጠረላቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡

 በቡድንም ሆነ በዶርም የሰልጣኝ አመዳደብን በተመለከተ አመዳደቡ ከተለያየ የስራ ዘርፎች የተውጣጡ
ሰልጣኞችን በማሰባጠር መሆኑ ሠልጣኞች የእርስ በእርስ ግንኙነታቸው እንዲዳብርና ትስስራቸው
እንዲጎለብት ያደረገ በመሆኑ ስልጠናውን በጥሩ መነቃቃት እንዲከታተሉ ያገዛቸው መሆኑን
ገምግመዋል፡፡

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 6


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 የተሃዲሶው መስመርና የወደፊት አቅጣጫወች ላይ ግልፅነት ተፈጥሯል፡፡ የልማታዊ ደሞክራሲና


ልማታዊ ሚዲያ ምንነት ላይ ግንዛቤ ተይዞበታል፡፡ በዚህም ረገድ የኢቢሲ ሚናና ተልዕኮ ምን እንደሆነ
በቂ ግንዛቤ ጨብጠዋል፡፡ የልማታዊና ዴሞክራሲያዊ መስመር ልዕልና እንዲጎለብትና በሁሉም የህብረተሰብ
ክፍሎች ዘንድ እንዲሰርጽና ለሚደረገው ርብርብ የኮርፖሬሽኑ ጋዜጠኞች የበኩላቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱና
መገንዘብ ችለዋል፡፡
 በአገራችን የፌዴራል ስርዓት ልዩ ባህሪያት፣ ስኬቶችና የወደፊት አቅጣጫዎች ላይ በብዝሃነት፣
ህብረብሔራዊነት፣ ህብረብሔራዊ ዴሞክራሲያዊነት ላይ የተሻለ አስተሳሰብ መፍጠር ተችሏል፡፡
የፌዴራል ስርዓታችን እና የአገራችን ዘላቂ ሰላም የማረጋገጥ መርሆዎችና በዲሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት
ፅንሰ ሃሳብ ዙሪያ በአመራሩና በባለሙያው ግልፅነት ተፈጥሯል ፡፡
 ሰልጣኞች የኮርፖሬሽኑን ተልዕኮ ከስልጠናው ካገኙ በኋላ ተልዕኳቸውን ለመፈፀም ይቻል ዘንድ የቀደመ
የሀገራችን ገፅታ ማለትም ነፃነቷን ጠብቃ የቆየች ሀገር እንደሆነች ፣ ከገናና የስልጣኔ ታሪክ ባለቤት
የነበረች መሆኗ፣ ሀገራችን ብዝሃነትን ሳታስተናገድ መቆየቷ እና የህዝቦችን መብትና ጥቅም ለማስከበር

ያልተቋረጠ ትግል የተደረገባት በመሆኗ የአገራችን ታሪክ ማወቅ አስፈላጊ መሆኑን ተረድተዋል፡፡ ከዚህ
በተጨማሪም ታሪክን ማወቅ ከታሪክነቱ ባሻገር ካለዉ ጊዜ ድክመታችንና ጥንካሬአችን ለመማር
እንደሆነ ግንዛቤ ተይዟል፡፡ ኢትዮጵያ አገራችን ከታላቅ ስልጣኔ ለማሽቆልቆል ጉዞ የተዳረገችዉ ባለፉት
ስርዓቶች ብዝሃነትን ማስተናገድ አቅቶን እንደነበር የተሻለ ግንዛቤ ተይዟል፡፡
 የሁለተኛው ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ፖኬጅ ምንነትና አስፈላጊነት፣ በፓኬጁ ውስጥ በተዘረዘሩ
መሠረታዊ ጉዳዮች እና በአተገባበር ሂደት ሚዲያው ያለው ሚና ላይ መግባባት ተደርሷል፡፡
 የአወንታዊ አስተሳሰብ መገንባት በጋዜጠኛው ሚና ላይ ያለው አስተዋፅኦ ምን ሊሆን እንደሚችል
የተሟላ ግልጸኝነት ተፈጥሯል፡፡ በአጠቃላይ ባለሙያው/የኢቢሲ ጋዜጠኛ/ በሀሉም አጀንዳዎች የተሻለ
እና ለተልዕኮ የሚመጥን አቅም ፈጥሮ በአገራችን ልማት፣ መልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት
ግንባታ ላይ ያገባኛል የሚል የጠራ አስተሳሰብ ፈጥሯል፡፡

2.2. ከኮርፖሬሽኑ ተልኮና ተግባራት አንፃር የስልጠናው አስፈላጊነትና ወቅታዊነት በተመለከተ


 የስልጠና ሰነድ መረጣን በተመለተ፡-

በጥንካሬ፡-

የስልጠናው አጀንዳዎች ለኮርፖሬሽኑ ስራ ምን ያህል ጠቃሚና አግባብነት ነበራቸው? (Relevant and


Appropriate) ናቸው ወይ?

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 7


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 የተመረጡት የስልጠና አጀንዳዎች ተገቢ ሲሆኑ የኮርፖሬሽኑ አመራርና ባለሙያ ተልዕኮውንና ሃገሪቷ
የምትመራበትን ፖሊሲዎች በግልጽ ተረድቶና አውቆ የተሟላ አቅም ፈጥሮ የኢቢሲን ዓላማና ግቦች
ለማሳካትና በሃገራችን ልማት የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዲችል የሚያስችለው ስለሆነ ስልጠናዉ
ታስቦ መሰጠቱ ጥሩ ነው፡፡
 ኮርፖሬሽኑ በመንግስት የልማታዊ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ፍልስፍና መሰረት ጋዜጠኛው ስራውን
እንዲሰራና ልማትን የሚያፋጥን ስራ ለመስራት የተሻለ ግንዛቤ የፈጠረበት በመሆኑ፣
 የስልጠናው ቅደም ተከተልም በአግባቡ የታየና የርዕሶቹን ተከታታይነትና ተመጋጋቢነት የጠበቀ በመሆኑ
ጥሩ ነበር፤
 በኢትዮጵያ ፌዴራል ስርዓት የብሄሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች መብት መከበር አስፈላጊ የሆነበትን፣
የብዝሃነትና ዴሞክራያዊ ብሄርተኝነትን ወዘተ… የነበረውን የተሳሳተ አመለከካከት ለማስተካከል
የተሟላ ዕውቀት ያስጨበጠ በመሆኑ፣
 ሰልጣኞች በስልጠናው የአወንታዊ አመለካከት ጥበብን ለጋዜጠኝነት ሙያ ያለውን ወሳኝነት
የተገነዘቡበት ስለሆነ ለተግባራዊ እንቅስቃሴ የሚረዳ ክህሎት በመፍጠሩ፣

በአጠቃላይ በስልጠናው የተሰጡት አጀንዳዎች/ርዕሶች/ ለልማታዊ ሚዲያና ለጋዜጠኝነት ሙያ አጋዥና


በሙያው ዙሪያ ግናዛቤ የሚያስጨብጡ እና አግባብነት ያላቸዉ ናቸው፡፡ በመሆኑም ስልጠናው ዓለማቀፋዊ
ነባራዊ ተጨባጭ ሁኔታወችን ያገናዘበ እውቀትና ክህሎት ለሰልጣኞች በመጨበጥ ኢቢሲን ተፎካካሪና ተራጭ
ሚዲያ በማድረግ ረገድ ስልጠናው በጣም አስፈላጊና ወቅታዊ ነው፡፡

በቀጣይ ሊስተካከል የሚገባው፤

 ሃገራችን ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ትራንስፎርም እያደረገች ስለሆነ በዚህ ስልጠና


የኢንዱስትሪ መር ፖሊሲያችንና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስትራቴጂዎቻችን ተካተው ቢሰጡ ጥሩ ነበር፡፡
 ሃገራችን የምትከተላቸው ሁሉም ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ደረጃ በደረጃ በተከታታይ ለጋዜጠኛው
በአጫጭር መድረኮች ሊሰጡ ይገባል፡፡
 ከሙያችን ተጨባጭ ስራዎቻችን ጋር ይበልጥ ተቀራራቢና ተያያዥ የሆኑና የአዘጋገብ ክፍተቶቻችንን
ሊያሳይ በሚችል መልኩ ከዘገባዎቻችን ሳምፕል ተወስዶ ሙያ ነክ የሆኑ አጀንዳዎች ቢካተቱ ጥሩ
ነበር፡፡
 የኢዲቶሪያል ፖሊሲያችንና የዲሲፕሊን መመሪያዎች በስልጠናው አጀንዳ ውስጥ ቢካተትበት ጥሩ
ነበር፡፡
 የአጀንዳ መረጣው የት/ርትና ስልጠና ዲፓርትመንታችን በያዘው የክህሎት ክፍተት መሰረት ቢደረግ፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 8


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

2.3. የተሃድሶ መስመር መነሻ፣ ቀጣይ አቅጣጫና መድረሻ ላይ ግልፅነትና የጠራ ግንዛቤ የመፍጠር
አስፈላጊነት

3.1.26. ከስልጠናው በፊት የሰልጣኙ ግንዛቤና አመለካከት በተመለከተ


ከስልጠናው በፊት ይንጸባረቁ የነበሩ የአመለካከት፣ የግንዛቤና የክህሎት ክፍተቶችንም ስንመለከት፡-

 ሀገራችን ያለፈችባቸውን የታሪክ ሂደቶችና መለያዎችን መገንዘብ ለዛሬው ትውልድ ያለውን


ፋይዳ ምን እንደሆነ ግንዛቤው ያልነበራቸው በመሆኑ ባለፉት የታሪክ ጊዜያት የነበሩ የሀገራችን
መጥፎ ገጽታዎች እንዳይደገሙ ለማደረግና አኩሪ ታሪካችንን ደግሞ ለማጎልበት የሚኖራቸውን
ሚና አሳንሶ በማየት ያለፉትን የሀገራችን ታሪክ ዛሬ ላይ ማንሳት አስፈላጊ እንዳልሆነ አድርገው
ይወስዱ የነበረ መሆኑ፣
 በልማታዊ ደሞክራሲ ስርዓት 10% ኪራይ ሰብሳቢነት ሊኖር እንደሚችል መታሰቡ ስርዓቱ ኪራይ
ሰብሳቢነትን ያሚያበረታታ ነው ብሎ የመገንዘብ ሁኔታ መኖሩ፤
 ሰነዱ ልማታዊ ደሞክራሲን ልክ እንደ ፅድቅና ኒዩ ሊብራሊዝምን እንደ ጭራቅ አድርጎ የሳለና የኒዩ
ሊብራል ተከታይ ሃገራትን ህብም የሳለበት አግባብ ከአውነታው ያፈነገጠ ነው ብለው ያስቡ
እንደነበር፤ከምናወግዘው የሚጠቅመንን ነግር ብንወስድ ይሻላል የሚል አመለካከት መኖሩ፤
 የልማታዊ ደሞክራሲ አስተሳሰብ ሲታይ የብዙሃን ልማት ስለሚል እኩል እንደግ ከሚለው
የሶሻሊዝም ስርዓት ፅንሰ ሃሳብ ነው እንጂ ሁላችን በአንድነት አድገን እንደት ካፒታሊዝም ሊባል
ይችላል የሚል አመለካከት መኖሩ፤
 በአውራ ፓርቲና መልቲ ፓርቲ ስርዓት መካከል ልዩነት የለም ብሎ የመገንዘብና ፤መንግስት አሁን
ያለው ፓርቲ ክልቀጠለ አማራጭ የለም እያለ መድበለ ፓርቲ ፅንሰ ሃሳብ ተግባራዊ አይሁንም
የሚል ሁኔታ መኖሩ፤
 ቴክኖሎጂ ከመኮረጅ ይልቅ መፍጠር ላይ ትኩረት መስጠት አለብን የሚል አስተሳሰብ በውይይት
ወቅት መታየቱ፤
 የኮርያና ታይዋን ተሞክሮ እንላለን እንጂ በተግባር ግን የቻይናን ነው የተገበርነው የሚሉ የነበረ
መሆኑ፤
 በሃገራችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት የለም የሚል ግንዛቤ መኖሩ፤

3.1.27. ከስልጠናው በኋላ ሰልጣኙ የፈጠረው ግንዛቤና አመለካከት፣

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 9


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 ሀገራችን ያለፈችባቸውን የታሪክ ሂደቶች መገንዘብ ለዛሬው ትውልድ ያለውን ፋይዳ፤ ለተሃድሶ
መስመራችን መነሻ በሆነው ጉዳይ፣ በቀጣይ አቅጣጫና መድረሻ በጥቅሉ በሃገራዊ ህዳሴያችን
አቅጣጫና መዳረሻ፣ ለኢቢሲ አመራሮች ባለሙያዎች/ልማታዊ ጋዜጠኞች/ አንዲሁም ለሚያገለግሉት ሰፊው
ህዝብ ሁለንተናዊ እድገት ላይ ባላቸው እንድምታ ዙሪያ ሰልጣኞች ለመገንዘብ ችለዋል፤ ልማታዊና
ዲሞክራሲያዊ መንግስታችን ለመሰረታዊ ለውጥ የበቃው የተሃድሶ መስመር ነድፎ፣ ይህንኑ
በተደራጀ የህዝብ ንቅናቄና ተሳታፊነት ተግባራዊ ማድረግ በመቻሉ መሆኑንም ጭምር ግልፅነት
ተይዟል፡፡
 ከዕድገቱ ጋር በተያያዘ አኳኋን የኪራይ ሰብሳቢነት መልሶ መላልሶ እያገረሸ ፈጣኑን የዕድገት
ጉዟችንን እንደሚፈታተን፤ በመሆኑም ሃገራዊ ህዳሴያችንን ለማሳካት የሚያስችል እና ኪራይ
ሰብሳቢነትን ይበልጥ የሚያዳክም ሁኔታ ለመፍጠር ያለመ ስራ መስራት የምንችልበትን ሁኔታ
መፍጠር እንደሚቻል ግልፅነት ተፈጥሯል፡፡
 ኒዩ ሊብራሊዝም ትንሽ የህ/ሰብ ክፍልን ይዞ ካፒታሊዝም እንደሚገባና ልማታዊ ደሞክራሲ ግን
አብዛኛውን የህ/ሰብ ክፍል በማበልፀግ ወደ ካፒታሊዝም እንደሚገባና እኛም አብዛኛው ህ/ሰባችን
ድሃ ስለሆነ ከድህነት ለመውጣት ልማታዊ ደሞክራሲ የተሻለ አማራጭ መሆኑን የኮርፖሬሽኑ
አመራርና ሙያተኞች በልማታዊነትና ዲሞክራሲያዊነት መካከል ያለውን መሰረታዊ ልዩነት፣
በሁለቱ መካከል የሚደረገውን ትግልና የትግል ስልቶችን በሚገባ ተገንዝቦ ከልማታዊና
ዲሞክራሲያዊ አቅጣጫ የመነጩትን በልማታዊ መንግስታችን የተነደፉ ፕሮግራሞችና ግቦች በተሟላ
መንገድ እንዲያሳኩ ግንዛቤያቸውን ማሳደግ ተችሏል፤ኒዩ ልብራሊዝምም አሁን ባለንበት ነባራዊ
ሁኔታ ለኢት/ያም ሆነ ለአፍሪካ አይሰራም በሚል መግባባት ተችሏል፤
 በሃገራችን ለመመጀመሪያ ጊዜ የብዝሃ ፓርቲ ስርዓት የተፈጠረው በ 1983 ዓ.ም መሆኑንና
በመጠናከርም ላይ ያለበት ሁኔታ ላይ ነው በሚል መግባባት ተደርሷል፤
 አሁን ካለን አቅም አንፃር ቴክኖሎጂ ካላቸው ሃገራት እየኮረጂን ቀስ በቀስም ጎን ለጎን የቴክኖሎጂ
ፈጠራን ማሳደግ ትኩረት እንደሚሰጠው መግባባት ተችሏል፡፡
 ልማታዊ ደሞክራሲያዊ መስመር አማራጭነቱን ህዝቡ ተገንዝቦ ይህን የሚያስከትል ፓርቲ
እንዲፈጠር በማድረግ የህ/ሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እምዲቻል እንጅ ህ/ሰቡ ሌላ አስተሳሰብ
የሚከተል ፓርቲ ከመረጠም የሚችል መሁኑንና በዚህም መድበለ ፓርቲ ስርዓቱን የማገድ
አስተሳሰብ እንዳልሆነ ግንዛቤ ተይዞበታል፤

2.4. የልማታዊ ጋዜጠኝነት ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ለኢትዮጵያ ህዳሴ ፍልስፍና በሚሉት መሰረተ ሃሳቦችና
መነሻዎች የኢቢሲ አመራርና ባለሙያዎችን ዕውቀትና ክህሎት የመገንባት አስፈላጊነት፣

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 10


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

3.1.28. ከስልጠናው በፊት የሰልጣኙ ግንዛቤና አመለካከት በተመለከተ

 በልማታዊ ሚድያና ኮሚኒኬሽንና በኒዩ ሊብራሊዝም ጋዜጠኝነት ፍልስፍና መካከል ያለው ልዩነት ግልፅነት
ያልተያዘበትና የኒዩ ሊብራል ጋዜጠኝነት አቀንቃኝነት ስሜት የተንፀባረቀበት ሁኔታ መኖሩ በቡድን ውይይት
ወቅት ተንፀባርቋል፤
 ኢቢስ ባለቤትነቱ የማን እንደሁነ ማለትም የህዝብ ወይስ የመንግስት እንደሆነ በሰልጣኞች በውል
ያልታወቀበት ሁኔታ መኖሩ፤
 መንግስት ለኮርፖሬሽኑ/ኢቢሲ/ በቂ ድጋፍ እያደረገ እንዳልሆነና በአሰራር ላይም ጣልቃ እየገባ መሆኑን
አድርገው ማየትና ይህ ባሆነበት ሁኔታ ኮርፖሬሽኑ የተጣለበትን አላማ ከግብ ለማድረስና ተልእኮውን
በአግባቡ መወጣት አይችልም የሚል የጨለምተኝነት አስተሳሰብና በኮርፖሬሽኑ የሚታዩ የአፈጻጸም
ችግሮችን በዕውቀት ላይ ተመስርቶ ማረም የሚያስችል አቅም ያልነበረውና ታግሎ ማስተካከልም አይቻልም
የሚል የስጋት አመለካከት የነበረ መሆኑ፣

 ልማታዊ ጋዜጠኝነት በሰነዱ ላይ የቀረበበት አግባብ ከሳይንሳዊ ትንታኔ የራቀ ነው የሚል


አስተሳሰበ መኖሩ፤
 ሠልጣኙ የልማታዊ ሚዲያን ተልዕኮ፣ ዓላማና ሚና፣ ከፖለቲካል ኢኮኖሚ ጋር ያለውን
ትስስር በመረዳት ዙሪያ የነበራቸዉ ግንዛቤ በጣም ዝቅተኛ መሆኑ፣

3.1.29. ከስልጠናው በኋላ ሰልጣኙ የፈጠረው ግንዛቤና አመለካከት፣


2.5. ለሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ስኬት የአመራሩን አቅም የማጎልበትና ዝግጁነቱን የማረጋገጥ
አስፈላጊነት
በጥልቀት በመታደስ ግምገማ እንደተረጋገጠው አገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት 25 ዓመታት በተለይም ደግሞ ባለፉት 15
አመታት በሁሉም የልማት መስኮች ስኬታማ የሆኑ ለውጦች ተመዝግቧል፡፡ በሃገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በገጠርና
በከተሞች በተደረገው እንቅስቃሴ የመጀመሪያ ደረጃ ካፒታል ክምችት የፈጠረች ሃገር መገንባት ተችሏል፡፡ ይህ በጐ ጎኑ
እንደተጠበቀ ሆኖ የማስፈፀም አቅም ችግራችን በሚፈለገው ደረጃ ባለመቀረፉና ይህ ችግር ከለውጥ ሥራችን መዳከም
ጋር ተዳምረው ሃገራችንንም ሆነ መንግስታችንን ለአደጋ የማጋለጥ ሁኔታ እየተፈጠረ መጥቷል፡፡ የኪራይ ሰብሳቢነት

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 11


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

የፖለቲካ ኢኮኖሚ በሚፈለገው ፍጥነትና መጠን አልከሰመም፡፡ የትምክህት ፣ የጠባብነትና የሃይማኖት አክራሪነት
እንዲሁም ፀረ-ዴሞክራሲያዊ እንቅስቃሴዎች ከመዳከም ይልቅ እየተጠናከሩ የመጡበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡

በአመራሩና በባለሙያው ውስጥ የሚታየው የአድርባይነት፣ የጎራ መደበላለቅ፣ የኪራይ ሰብሳቢነትና ስራን በትጋት፣
በተነሳሽነትና ውጤታማነት የመፈፀም ችግርም በአግባቡ አልተቀረፈም፡፡ ፀረ-ዴሞክራሲያዊነት፣ ውሳኔን በወቅቱ
ያለመወሰን፣ የህዝብን ችግሮች አዳምጦ ያለመፍታት፣ የህዝብ የተደራጀ ተሳትፎን ያለማጠናከር፣ በኔት ወርክ
መጠቀምም....ወዘተ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከረ መጥቷል፡፡ በመሆኑም የመልካም አስተዳደር ችግሮች ጎልተው
በመታየታቸው ህዝቡ ምሬት ውስጥ ከመግባት አልፎ የፀረ-ሰላም ሃይሎች መጠቀሚያ ጭምር እየሆነ መምጣቱን
በጥልቀት የመታደስ ግምገማው ተረጋግጧል፡፡ እነዚህን ችግሮች በፍጥነት በመፍታት የሁለተኛው የዕድገትና
ትራንስፎርሜሽን ዕቅዳችንን የቀጣይ ተከታታይ ሶስት ዓመት ግቦች ማሳካት እንደሚገባ ግልፅ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

በሁለተኛው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የኪራይ ሰብሳቢነት የፖለቲካል ኢኮኖሚ የበላይነትን በልማታዊ
የፖለቲካል ኢኮኖሚ በመቀየር መሰረታዊ ለውጥ የማረጋገጥ ጉዳይ የሞትሽረት ስራ ተደርጐ ተወስዷል፡፡ ይህንኑ
ለማረጋገጥም በአንድ በኩል ከወትሮ በተለየ ሁኔታ ልማታዊነትን የሚያጎለብቱ ድጋፎችንና ስራዎችን በመስራት በሌላ
በኩል የኪራይ ሰብሳቢነት ዋነኛ ምንጮች ሆነው የተለዩ ጉዳዮችን በማምከን ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በቁጥጥር ስር
በማዋል ልማታዊነት የበለጠ እንዲጎመራና የበላይነት እንዲይዝ በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባው አፅንኦት
ተሰጥቶታል፡፡ ይህንኑ እውን ለማድረግ የኢቢሲ አመራሩንና ባለሙያውን ለተልዕኮው በብቃት ማዘጋጀት ይገባናል፡፡

የሁለተኛው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ በመገንባትና በኢኮኖሚው መታየት
የጀመሩትን የሚዛን ክፍተቶች በማስተካከል ኢኮኖሚውን 11 በመቶ ማሳደግና ለሃገራዊ ራዕይ መሳካት አስተዋጽኦ
ማድረግ፣ አገራዊ የኢንጂነሪንግና ፋብሪኬሽን አቅማችንን በማሳደግ የአምራች ዘርፎች ምርታማነት፣ ጥራትንና
ተወዳዳሪነትን በማጎልበት የኢኮኖሚ መወቅራዊ ለውጥን ማረጋገጥ፣ የህዝብን የተደራጀ አቅም በቀጣይነት መገንባትና
የልማቱ ባለቤትና ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻል፣ እና ዴሞክራሲያዊና ልማታዊ መንግስትን በማጠናከር ልማታዊ
የፖለቲካ ኢኮኖሚን መገንባት እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጦለታል፡፡ የኢቢሲ አመራርና ባለሙያዎች ከአንደኛው
የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ትግበራ ሊወስዱ በሚገቡ ጠቃሚ ልምዶችና የሁለተኛው የዕቅድና
ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መሰረታዊ መነሻዎች፣ አቅጣጫዎች ላይ ተነሳሽነትና የመፈፀም ቁርጠኝነት ተላብሶ በተደራጀ
የህዝብ ንቅናቄ በልማታዊ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ስራዎች የማስፈጸም አቅሙን መገንባት ይጠይቃል፡፡

ከዚህም በመነሳት ሃገሪቱ በ 2008 በጀት ዓመት የሁለተኛውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ትግበራ በጀመረችበት
ወቅት በአንዳንድ የሃገሪቱ አካባቢዎች በኢሊኖ ምክንያት በተከሰተው የድርቅ አደጋ በዜጐችና በእንስሳት ሃብታችን ላይ
ያጋጠመውን ችግር በራሳችን አቅም ለመቋቋም በተደረገው ጥረት ችግሩን መቆጣጠር የተቻለ ቢሆንም የችግሩ
መፈጠር መንግስት በዕቅድ ዘመኑ የያዛቸውን ሰፋፊ የልማት ስራዎች በተያዘላቸው ዕቅድ መሰረት እንዳይከናወኑ የራሱ
አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል፡፡ በተጨማሪም በመንግስታችን ውስጥ በተፈጠረው የአስተሳሰብና የአፈፃፀም ብልሽትና
ይህንኑ አጋጣሚ በመጠቀም በፀረ-ልማትና ፀረ-ሰላም ሃይሎች አማካይነት የተቀሰቀሱት አለመረጋጋቶች በልማትና

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 12


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

የሃገር ግንባታ ስራዎቻችን ላይ የበኩላቸውን አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድረው አልፈዋል፡፡ በመሆኑም የሁለተኛውን የዕድገትና
የትራንስፎርሜሽን ትግበራ የባከነውን ጊዜ በሚያካክስና የላቀ ውጤት በሚያመጣ አኳኋን በውጤታማነት እንዲፈፀም
የኢቢሲ አመራሩና ባለሙያው ለዚህ ትልቅ ሃገራዊና ከባቢያዊ ተልዕኮ መገንባት ልዩ ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ሆኖ ይገኛል፡፡
በመሆኑም ለሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ስኬት የኢቢሲ አመራርና ባለሙያውን ለማዘጋጀትና
ለማብቃት ስልጠናው መሰጠቱ በጣም ያስፈልጋል፡፡

2.6. የኢትዮጵያ ፌዴራል ስርዓት ባህሪያት የዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባታ ሂደት ስኬቶችና የወደፊት
አቅጣጫዎችን የመገንዘብ አስፈላጊነት
በኢትዮጵያ ሃገራዊ ለውጥ ለማምጣትና የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እንድንጀምር የግድ ያሉን ሁለት
መሰረታዊ ጉዳዮች ናቸው፡፡ የመጀመሪያው የትላንቷ ኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ
የህዝቡና የልማታዊ መንግስታችን የልማትና የለውጥ ፍላጐት ነው፡፡ አምባገነኑ የደርግ መንግስት በኢህአዴግ
መሪነት በተካሄደው ህዝባዊ ትግል ከተወገደ ማግስት ጀምሮ ከላይ የተቀመጠውን መሰረታዊ እውነታ
መሰረት በማድረግ በኢትዮጵያ መሰረታዊ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊና የውጭ ግንኙነት
ተግባራትን በማካሄድ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ ይህም በመሆኑ በሃገሪቱ ባሉ ሁሉም አካባቢዎች
በተነፃፃሪ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እየጎለበተ መጥቷል፡፡ አስተማማኝ ሰላምም ሰፍኗል፡፡ ለልማትና ዲሞክራሲ
ስርዓት ግንባታም መሰረት ተጥሏል፡፡ በዚህም ምክንያት አዲሲቷ ኢትዮጵያ የትላንቱን አሮጌ ባህሪ ትታ
አዲሱን ባህሪ ለመላበስ በሚያስችል የሽግግር ምዕራፍ ውስጥ ትገኛለች፡፡ ከትላንቱ የድህነት አዙሪት ወጥታ
የነገን ባህሪ ሙሉ በሙሉ የተላበሰች ሃገር ለመሆን የሚያስችላትን የህዳሴ ጉዞ ጀምራለች፡፡ ይህንን በጎ
ጅምር አጐልብቶ መቀጠል ይገባል፡፡

በመሆኑም በማንኛውም የሽግግር ህብረተሰብ ውስጥ የሚታዩ አስተሳሰቦችና የፖለቲካ አዝማሚያዎችን


በመገንዘብ ሃገሩንና ህብረተሰቡን ለመለወጥ የሚተጋ ማንኛውም ሃይል በየወቅቱ የሚታዩትን አሉታዊና
አዎንታዊ አስተሳሰቦች ተገንዝቦ አዎንታዊ አስተሳሰቡ በአሸናፊነት እንዲወጣ በማድረግ የበኩሉን የትግል
አስተዋጽኦ ማበርከት እንዲችል ማስቻል ይኖርበታል፡፡ በኢቢሲ ስር ያሉ አመራርና ሙያተኞች የኮርፖሬሽን
መስሪያ ቤቱን አቅጣጫዎች በተሟላ መልኩ በመተግበር የተቀመጡ ግቦችን እንዲያሳካ ከተፈለገ የሃገራችንን
ዕድገት እንዲቀጭጭ ያደረጉና የሚያደርጉ ነባርና አዳዲስ ችግሮችንና አፈታታቸውን፣ ልማታዊነትንና
ዲሞክራሲያዊነትን ለማፋጠንና የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማስፋፋት ያስቻሉንን የለውጥ ተግባራት ምንነትና
እንዴት ማጎልበትና ለከፍተኛ ዕድገት ማብቃት እንደሚቻል ግንዛቤያቸው ካደገ ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም ይኸው
ጉዳይ በኢቢሲ ስር የሚሰለጥኑ አመራርና ሙያተኞችን አቅም ለመገንባት ስልጠናው ያስፈልጋል፡፡

2.7. የህዳሴ ጉዟችንና ውጫዊው ሁኔታን የመገንዘብ አስፈላጊነት፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 13


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

የጀመርነው የልማትና የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታና የዚሁ ማስፈፀሚያ የሆኑት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን
ዕቅዶችና ሀገራችን የተያያዘችው የህዳሴ ጉዞ በወሳኝነት ተግባራዊ ሊሆኑ የሚችሉት በውስጣዊ አቅማችን
የተጠናከረ ልማታዊ መንግስት በመፍጠር ነው፡፡ ስለሆነም ውስጣዊ ፈፃሚ ሃይሎቻችንን በብቃት ማዘጋጀትን
ስናስብ የኢቢሲ አመራርና ባለሙያዎቻችንን የብቃትና የሙያዊ ስብእና አቅም ማሳደግን ያካትታል፡፡ ይሁንና
ልማታዊና ዲሞክራሲያዊ መንግስታችን የሚሰራበት ከባቢያዊና አለምአቀፋዊ ሁኔታዎች መልካም
ዕድሎችንና ፈተናዎችን ይዘው የሚመጡ በመሆናቸው በተሃድሶ ጉዟችን ላይ የማፋጠን ወይም የሟጓተት
ተፅዕኖ ሊያሳርፉ እንደሚችሉ በተደጋጋሚ ተገልጿል፡፡ ልማታዊ መንግስታችን ልማታችንን የሚያፋጥኑ
መልካም ዕድሎችን በማስፋትና በመጠቀም፣ ለልማታችን እንቅፋት የሚሆኑ ፈተናዎችንና አሉታዊ
ተፅዕኖዎችን ደግሞ በመቀነስ የህዳሴ ጉዟችንን ይበልጥ ሊያራምድ የሚችለው ይህንኑ ውጫዊ ሁኔታ የተገነዘበ
እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም ውጫዊ ሁኔታን አስመልክቶ ልማታዊ መንግስቱ ያለውን ግምገማ፣ የትኩረት
አቅጣጫ፣ መልካም ዕድሎችን አሟጦ ለመጠቀም እንዲሁም ለማስፋትና ተግዳሮቶቹን ለመቀነስ
የሚከተላቸውን አቅጣጫዎችና ስትራቴጅዎች የኢቢሲ አመራሮቻችንና ባለሙያዎች እንዲገነዘቡ ማድረግ
ያስፈልጋል፡፡ በተጨማሪም ልማታችንን የሚያፋጥኑ መልካም ዕድሎችን በማስፋትና በመጠቀም በልማታችን
ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያሳርፉትን ለመቀነስ የሚያስችላቸውን የማስፈጸም አቅማቸውን መገንባት ይገባል፡፡
በመሆኑም የህዳሴ ጉዟችንና ውጫዊው ሁኔታን የመገንዘብ ጉዳይ ለኢቢሲ አመራሮችና ጋዜጠኞች
ስልጠናው መሰጠት ይኖርበታል፡፡

2.7. በአዎንታዊ አስተሳሰብ ዙሪያ ግንዛቤ የመፍጠር አስፈላጊነት

ሰልጣኞች በስልጠናው የአወንታዊ አመለካከት ጥበብ ለጋዜጠኝነት ሙያ ያለውን ወሳኝነት በመረዳት ወደ


ተግባራዊ እንቅስቃሴ ለመግባትና ህዝቡ ከሚዲያው የሚፈልገውን የጠራ መረጃ ተደራሽ ለማድረግ የሚረዳ
ክህሎት ማካበት የስችላቸው ዘንድ አወንታዊ አስተሳሰብን ለማጎልበት የሚስችል ስልጠና መስጠት
የሚያስፈልግ እንደነበረ ከስልጠና ሂደቱ ለማወቅ ተችሏል፡፡

4. በየሰነዱ የተቀመጡ የስልጠና ግቦች መሳካትን በተመለከተ

4.1.1. የተሃድሶ መስመርና የኢት/ያ ህዳሴ ላይ ግልፅነት ተፈጥሯል

4.2.1. በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ ግልፅነት ተፈጥሯል

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 14


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

4.2.2. የኢት/ያ ፌዴራል ስርዓት ግንባታ ስኬቶች፣ የወደፊት አቅጣጫዎችና በዲሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት ፅንሰ ሃሳብ ላይ
በአመራሩና በባለሙያው ግልፅነት ተፈጥሯል

4.2.3. የሃገራችን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዎች ላይ በኮርፖሬሽኑ አመራርና ባለሙያዎች ግልጸኝነት ተፈጥሯል

4.2.4. በአዎንታዊ አስተሳሰብ ዙሪያ ግንዛቤ ተፈጥሯል

5. ከአመለካከት አኳያ ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን በተመለከተ፦

ሰልጣኙ በሁሉም ሰነዶች ከሚያነሳቸዉ ሀሳቦችና በጥያቄ መልክ ወደ አካዳሚዎች ከሚቀርቡ ሪፖርቶች ከተደረገው
ግምገማ አንጻር ሲታይ መሰረታዊ የአመለካከት ችግሮች እንደነበሩ የሚያመላክት ቢሆንም በዉይይት ወቅት ከተካሄዱት
መተጋገሎችና በዋና አሰልጠኞች በኩል በተሰጠዉ መልስ መግባባት ላይ የተደረሰባቸው እንደሆነ ተገምግሟል፡፡

ይሁን እንጂ ደጋግመዉ ሲነሱ የነበሩና ሰፊ ክርክር ተካሄዶባቸዉ ስምምነት ላይ የተደረሰባቸው ጉዳዮች ቢሆኑም ቀጣይ
ክትትል የሚያስፈልጋቸዉ እንደሆነ ተገምግሞ ከሁሉም ሰነዶች በተደጋጋሚ ይንጸባረቁ የነበሩና ዋና ዋና የአመለካከት
ችግሮች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

6. በሰነዱ መካተትና መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች ተብለው የቀረቡ

7. የስልጠናውን አጠቃላይ አመራርና አካሄድ በተመለከተ


7.1.1. በመለስ ዜናዊ አካዳሚ የልዩ ስልጠና ፕሮግራሞችን በተመለከተ
ሀ/ በጥንካሬ

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 15


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 አካዳሚው ስልጠናው የሚመራበት እቅድ አስቀድሞ በመላክ ማእከላቱ በዝግጅት ምእራፍ በመነሻነት
ከራሳቸው ነባራዊ ሁኔታ አንጻር በውቅቱ እቅድ እንዲያዘጋጁ ያገዘ መሆኑ፤

 የስልጠና ሰነዶች በወቅቱ እንዲደርሱ መደረጉ፤

 ስልጠናው በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ እንዲከናወን ክክትትል መደረጉ፣

 ወቅታዊ የድጋፍና ክትትል /ሱፐርቪዥን መደረጉ

 ብቃት ያላቸው አሰልጣኞችን በመመደብ መቻሉ፤

 የጊዜ አመዳደቡ ተለይቶ ለሠልጣኙ እንዲታወቅ መደረጉ፣


 የሱፐርቪዥን ስራ ቼክ ሊስት ተዘጋጅቶ ቀድሞ መላኩ

 በስልጠናው አካሄድ ላይ በሃይል መድረክና የቡድን ውይይት እንዲኖር መደረጉ፤ ይህም፤

 በኃይል መድረክና በቡድን መከፋፈሉ መረጃዎችን በጠባብ መድረክ ለመለዋወጥ፣አንድነትን


ለማጠናክርና የሁሉንም ልምድ ለማስፋት መርዳቱ፡፡
 ቡድኖች ቁጥራቸው የተመጠነ መሆኑ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ አግዟል፡፡
 የባህል ትውውቅ ለማድረግ ዕድል ፈጥሯል፡፡
 መነሻ የስልጠና ማስፈፀሚያ እቅድ እና የፖለቲካና የአደረጃጀት ዕቅዶችን መላኩ፣ የአካል ሱፐርቪዥን ስራ
ማካሄዱ በጥንካሬ የሚታይ ነው፡፡

ለ/ በድክመት

 የሚላኩ የሪፖርት ፎርማቶች በወቅቱ የመላክ ውስንነቶች፣ ለሚላኩ ሪፖርቶች በተለይም በሁለተኛ መጽሃፍ
ግምገማ ላይ ግብረ መልስ የመስጠት ውስንነቶች መኖራቸው፣ በመጨረሻው መጽሃፍ ላይ በየአካዳሚው አንደኛ
የወጡ የእቅድ አቅራቢ ሰልጣኞች በቀጥታ በፕላዝማ እንደሚያቀርቡ ሲገባ አሰልጣኟ እንድታቀርበው መደረጉ
በዚህም ለአሰልጣኟና ለማዕከላት ቀድሞ የማሳወቅ ውስንነቶች ነበሩ፡፡
 የስልጠና ርዕሶች መብዛትና ለስልጠናዉ የተሰጠዉ ጊዜ ማጠር መታረም አለበት

 ስልጠናው የሚከናወንበት ፋይናንስ በወቅቱ አለመላክ፣ለስልጠና መስኬጃ በቂ በጀት ያለመያዝና


አካዳሚዎች ከራሳቸው የስራ ማስኬጃ በጀት እንዲይዙ መደረጉ ችግር በመሆና በተደጋጋሚ
የምናነሳው ጉዳይ ስለሆነ የሚስተካከልበት ሁኔታ ቢፈጠር፣

 ዋና መምህራን የስልጠና ማእከላቱን የስልጠና ሰአት በማክበር ለሰልጣኙ ምሳሌ እንዲሆኑ


ያለማስጨበጥ/ያለማስተካከል፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 16


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 ዋና መምህራን ሊከተሉት የሚገባውን የስልጠኛ ዘዴ አስመልክቶ በአግባቡ አቅጣጫ አለማስያዝ


በተለይ በእቅድ ልምምድ ወቅት ሰልጣኙ ያዘጋጀውን እቅድ እራሱ እንዲያቀርብ አለመደረጉ ሰልጣኙ
ከተበቀው ውጪ መሆኑ አሉታዊ ተጽእኖ ነበረው፣

 ወቅታዊ የጽሁፍ ግብረ-መልስ በመስጠት በኩል ክፍተት መኖሩ፣

 ከየብሄራዊ ወደ አካዳሚው የተላኩ ሰልጣኞች እኩል ባለመሆኑ ሁሉም ቡድኖች ብሔራዊ


ድርጅቶችንና አጋር ድርጅቶችን አለማካተቱ

7.1.2. አሰልጣኝ (ዋናመምህራንን) አመራረጥ፣ ገለፃና ማጠቃለያ አቀራረብን በተመለከተ፣

የወጣት ሊግ አመራሮችን ስልጠና ለማሰልጠን የተመረጡት ዋና መምህራን በሚያቀርቡት ሰነድ ላይ ጠለቅ


ያለና በቂ እውቀት ያለቸው መሆናቸው በጥንካሬ የተገመገመ ሲሆን እንዳጠቃላይ በገለጻ አቀራረባቸው
የነበረውን ጠንካራ ጎንና መስተካከል ያለባቸውን ጉዳዮች በማእከል ደረጃ ተገምግሞ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ለስልጠናው የተመደቡ ሁሉም ዋና አሠልጣኞች የየራሳቸው የአቀራረብ ልዩነት ቢኖርም ስልጠናውን ውጤታማ
ለማድረግ በአመለካከትና በክህሎት የተሻሉ በመሆናቸው ለቀጣይ ሊጠናከሩና ሊበረታቱ ይገባል፡፡ በመሆኑም በየአሰልጣኙ
የቀረቡ ጥንካሬዎችና መሻሻል ያለባቸው ጉዳዮች እንደሚከተለው ተጠቃልለው ቀርበዋል፡፡

በአሰልጣኞች አመዳደብ፣ በስልጠናው አሰጣጥ፣ ገለፃ አቀራረብና ማጠቃለያ አሰጣጥ ላይ ትክክለኛ


መደምደሚያ በማስያዝ በኩል፣(ዋና መምህራን፣ አስተባባሪዎችና ቡድን መሪዎች በሚል ተለይተው ማቅረብ
አለበት)፣

7.1.3. በዋና መምህራን ሰነድ 1

ሀ)በጥንካሬ፦
 የገለጻ አሠጣጡ ከሞላ ጎደል ዕውቀትን ሊያስጨብጥ በሚችል መልኩ መሰጠቱ፣
 የሚሠጡት ገለጻዎች በሚያዝናና መልኩ መስጠታቸው፣
 በሠልጣኙ መካከል ብዥታ የፈጠሩ አስተሳቦችን ከተጨባጭ መረጃ ጋር በማስረዳት መቅረፍ
መቻሉ፣
 የአገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታ፣የመለስን ለጋሲ በማጣቀስ ግልጽ በሆነ መንገድ ዘርዝሮ ማስረዳት
መቻሉ፣
 ለተነሱ ጥያቄዎች በአብዛኛው በበቂ ማብራሪያ ላይ ተመርኩዞ መሰጠቱ፣

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 17


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 የትግል ተሞክሮን በማጣቀሻነት እያቀረቡ ግንዛቤ ማስጨበጥ መቻሉ፣


 የሚሠጡ መደምደሚያዎች ለቀጣይ ተልዕኮ ስንቅ የሆኑና ለወጣቱ ምክር አዘል ተልዕኮ
ማስጨበጣቸው፣
ለ)በድክመት፦
 የተገመገመ የለም
7.1.4. የሊግ መሰረተ ሃሳብ፣ ተልዕኮ፣ ፕሮግራም፣ አሰራርና አደረጃጀት መርሆዎችያሰለጠኑትን አሰልጣኝ
አቶ በረከት ስሞኦንን በተመለከተ
ሀ/ ጠንካራ ጎኖች

 ሀገራችን ያለፈችባቸውን ታሪካዊ ሂደቶችና ነባራዊ ሁኔታ እንደመነሻ መግለጹ ሰልጣኙን


ግንዛቤ ያጎለበተ መሆኑ

 አቅራቢው በስልጠናው ጭብጥ ላይ በቂ ዕዉቀት ያለዉ፣ በቂ ዝግጅት ያደረገና ገለጻው


ለማስታወሻ አያያዝ ምቹ መሆኑነ በብቃት ያቀረበ መሆኑ፤

 የተጠየቁትን ጥያቄዎች ላይ በቂ ትንታኔ በመስጠት መመለስሳቸው ሰልጣኙ የረካበት መሆ


ተገምግሟል፡፡
 በገለፃውና በማጠቃለያው የሊጎችን ግልፅ ተልዕኮ ማሳየት መቻሉና በሌሎች ሀገራት ያለውን
ልምድ ጭምር በማሳየትንድፈ ሃሳብን ከተግባር ጋር በማጣጣም በጥሩ ሁኔታ ማስጨበጥ እና
ለተጠየቁት ጥያቄዎችተገቢ ምላሽ መስጠት መቻሉ፣
 ካለው ተሞኩሮ በመያያዝ ለሰልጣኙ ለማሰረዳትመሞከሩ

ለ/ መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች

በፕሮግራሙ ላይ በተቀመጠው ሰአት አለማክበሩና ጠዋት አርፍዶ የመጀመር ሁኔታ ቢስተካከልና በማእከሉ
የስልጠና ሰአት በቀጣይ ቢከበር
 በገለፃ ወቅት 2፡00 ሰዓት መጀመር ሲገባ 2፡30 መጀመሩ እንዲሁም ከሰዓት 8፡00 መጀመር ሲገባ
8፡30 መጀመሩ በሰልጣኙ የሰዓት አጠቃቀም ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩ በቀጣይ ሊሻሻል
ይገባል፡፡ ከዚሁ በተጨማሪ አሰልጣኙ ካለው ልምድ አኳያ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት
ከአዲስ አበባ ስለሚያገኘው ልዩ ጥቅምየድርጅት አቋምን ከማንፀባረቅ ይልቅ የግልን አስተሳሰብ
ማንፀባረቁ ተገቢ ባለመሆኑ ለወደፊቱ ቢስተካከል የተሻለ ነው፡፡
 ጥያቀዌዎች ከተነበቡ በኃላ ለተጠየቁ ጥያቄዎችን አደራጅቶ በሚገባ ያለመመለስ፣

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 18


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

- በቂ ዝግጅት አድርጎ አለመምጣት ለሚነሱ ለሀገራዊ ጉዳይ ጥያቄዎች ብዥታ


የሚያጋጥም መልስ መስጠት ለምሳሌ፡- የወልቃይት የማንነት ጥያቄ፣የኦሮሚያና አዲስ
አበባ ማስተርፕላን በተመለከተ የተነሳ ጥያቄ።
- ጥያቄዎች በዝርዝር አንብቦ ተገቢውን መልስ አለመስጠት።
- በገለፃ ፍጥነት ስላላቸው መስታወሻ ለመያዝ ያስቸግራል።
- አቅራቢው የሊጉ ተልዕኮ ሰነዱና በፓኬጁ ሰነድ ጋር አጃምሎ የማቅረብ ካለው ልምድ
አንፃር የተለያዩ ሀገራት ተሞክሮ አለማቅረብ።
- የሚሰጡ ገለፃና መልስ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ድርጅት ወክሎ የተቀመጡ ስለሆኑ ሲያቀርቡ
“ይመስለኛል” የሚልና በግሌ ያለኝ አቋም እያሉ ባይገልፁ እንደ ድርጅት ቢችሉ ግልፅ
ያልሆነላቸው ነገር ካለ አጣርቶና ተናበው መልስ ማቅረብ ቢችሉ።

7.1.5. የከተማና የገጠር የወጣቶች የልማትና የእድገት ፖኬጅና ስትራቴጂ ያሰለጠኑትን አሰልጣኝ አቶ ርስቱ
ይርዳን በተመለከተ
ሀ/ ጠንካራ ጎኖች
 በስልጠናው ጭብጥ ላይ በቂ ዕዉቀት ያለዉ፣ በቂ ዝግጅት ያደረገና በብቃት ያቀረበ መሆኑ

 ሰዓትን በአግባቡ መጠቀሙ፣ገለጻው ለማስታወሻ አያያዝ ምቹ መሆኑ፣


 ሙያዊና ፖለቲካዊ የሆኑ ጉዳዮችን አስተሳስሮ በማቅረብ በኩል የነበረው ሁኔታ በጥንካሬ
የሚታይ ነው፡፡
 በተረጋጋና ማስታወሻ ለመያዝ በሚያመች መልኩ ትምህርቱን ማቅረብ መቻሉ፣
 ሰነዱን በዝርዝርና ግልፅ በሆነ ሁኔታ መረጃና በተደራጀ ዝግጅት ለሰልጣኙ የሰጠው ገለፃ እና
የጥያቄ መልስ አሰጣጥ የተሻለ ነበር፡፡

ለ/ መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች

 ሰነዱን ከሀገራዊ፣አህጉራዊና ከአለም አቀፋዊ ተሞክሮች ጋር ጋር በማያዝ አለማቅረብ

 ከጠቅላይ ሚንስትሩ ሌጋሲ ጋር በማያያዝ አለማቅረብ

 የሀሳብ መደጋገምና ምላሽ ሲሰጥ ተመሳሳይ ጥያቄዎችን አለማቀናጀት

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 19


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 የመጀመሪያዉ ገለጻ ድግግሞሽ የነበረበት መሆኑ፣ እንዲሁም እንደሃገር በሚሰጥ ስልጠና ላይ አርብ
ዕለት ለሙስሊም ሰልጣኞች ጁማ በመሆኑ በሚል መልዕክት ማስተላለፉ ከአካዳሚዎች የስልጠና
ደንብና አሰራር አኳያ የሚጋጭ መሆኑ፣
- አሰልጣኙ በመጀመሪያ ገለፃው በስልጠና ፕሮግራሙ መሰረት ወጣቶች ፓኬጅን ማቅረበገለፃ
አቀራረባቸው ግልፅና ምቹ መኖሩ
 ብ ሲገባው ስትራቴጅውን ማቅረቡ በሰልጣኙ ላይ መደናገር የፈጠረ መሆኑ፣

ሀ/ በጠንካራ ጎኖች

ለ/ ቢስተካከሉ ተብለው የተቀመጡ ጉዳዮች


- በመልስ ፍጥነት በመኖሩ መስታወሻ ለመያዝ አመቺ አለመሆን
- የመልስ አሰጣጥ በጠቅል የመስጠት በአብዛኛው የመንደርደሪያ ሀሳብ በማብዛት ግዜ
የሚፈጅበት ሁኔታ፣የመደጋገም
- የወጣቶች የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚነት ለመረጋገጥ የተሰጠውን ማብራርያ በቂ አለመሆን

7.1.6. የፌዴራል ስርዓታችን ግንባታና የአገራችን ዘላቂ ሰላምያሰለጠኑትን አሰልጣኝ አቶ ካሳ


ተ/ብርሃንን በተመለከተ

ሀ)ጠንካራ ጎኖች

ለ) ቢሻሻሉ ተብሎ የቀረቡ ጉዳዮች


7.1.7. የወጣቱ ስብዕና ግንባታ እና ማሕበራዊ ጠንቆች በማስወገድ ረገድ የወጣት አመራር
ሚናያሰለጠኑትን አሰልጣኝ አቶ ለሁሉ ደነቀውን በተመለከተ
ሀ) በጥንካሬ

ለ) ቢስተካከሉ ተብለው የቀረቡ

7.1.8. የአብዮታዊ ዲሞክራሲ የአመራር ጥያቄ፣ ያሰለጠኑትን አሰልጣኝ ወ/ሮሙፌሪያት ከማልን


በተመለከተ
ሀ) ጠንካራ ጎኖች

ለ) ቢስተካከሉ ተብለው የተነሱ ነጥቦች

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 20


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

7.1.9. የአካዳሚዉ አደረጃጀትና የአመራሩ ጠንካራና ደካማ ጐን በተመለከተ

7.1.10. አስተባባሪ ኮሚቴን በተመለከተ


የአደረጃጀት ዘርፍ ኮሚቴ (በዚህ ስልጠና የቡድን ዋናና ረዳት አወያዮች የተካተቱበት ሲሆን) በሚመለከት፡-

በጥንካሬ

 በየዕለቱ ማታ ማታ በመገናኘት የዕለት ከዕለት ስራዎችን እየገመገሙ መሆኑ፤


 የሴቶች አደረጃጀት ባይኖርም የሴቶችን ተሳትፎ ለማጠናከር ልዩ ትኩረት በማድረግ ሴቶችን
የማጠናከሩን ስራ መገምገሙ፤
 አደረጃጀቶች (ቡድኖች፣ ኳሊቲ ሰርክልና ፕሮዳክሽን ቲሞች) ለስልጠናው የሚጠበቅባቸውን
ተግባርና ኃላፊነት በአግባቡ እየተወጡ መሆናቸውን፤

በክፍተት

 በስልጠናው አፈፃፀም ወቅት የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመለየት ወደ ሁሉም ቡድኖች


ማስፋፋት ላይ ውስንነት መኖሩ፤
 በተደረገው ክትትል የመጣ የሰልጣኞች ለውጥን መለየት ላይ ክፍተቶች መኖሩ፤
 ሴት ሰልጣኞችን ከዚህ የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችል የሴቶች አደረጃጀት ራሱን ችሎ አለመኖሩ፤

7.1.11. ቡድን መሪዎችን በተመለከተ

በጥንካሬ
 ፍትሃዊ፣አሳታፊ፣ ነፃና ዴሞክራሲያዊ መድረክ መፍጠር መቻላቸው፤
 አዳዲስሀሳቦች እንዲወጡ ማበረታታቸው፤
 ውይይቱ አሳታፊ እንዲሆን ሀሳቦች በደቂቃ እንዲገደቡ ማድረግ፤
 ትኩረት የሚያስፈልጋቸውና አከራካሪ ጉዳዩችን ለይተው ለቡድኑ በመስጠት ሰልጣኙ የጋራ መግባባት
ላይ እንዲደርስ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር የጠራ አመለካከት ለማስያዝ ጥረት ማድረጋቸው፤
 ከአጀንዳ ሲወጣና ግልፅ ላልሆነ ጥያቄ እና ሀሳብ አቅጣጫ መስጠት መቻላቸው፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 21


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 ውይይቶችና ክርክሮች ከግለሰብ ጋር ሳይገናኙ ሀሳብ ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ መምራት መቻላቸው፤


 የቡድን አባላት ዲሲፕሊን በመተማመን እንዲከበር ለማድረግ መጣራቸው፤
 ለራሳቸው ሰፊ ሰዓት በመውሰድ የሌሎች ተሳትፎ እንዲገደብ ከማድረግ በመቆጠብ በጣም አጭር ጊዜ
መውሰድ፤
 ውይይቱ አሰልቺ እንዳይሆን በመሀል ዘና የሚያደርጉ ሰልጣኞችን በመጋበዝ ስልጠናው ቀለል ያለ እንዲሆን
ለማድረግ መሞከራቸው፤
 ከቡድን የተነሱ ጥያቄዎች አደረጅተው ሲጨርሱ መጀመሪያ ለቡድኑ አባላት በማቅረብ የተረሳ ካለ ለማካተት
መሞከሩና የተመረጡ ጥያቄዎችን አባላቱ ጋር ተስማምተው ለኃይል መድረክ እንዲቀርቡ ማድረጋቸው፤
 አቴንዳንስ በአግባቡ መያዝና የአቋም ልዩነት ያላቸው ተሳታፊዎች (በአካሄዱላይ) በኳሊቲ ሰርክልና
ፕሮዳክሽን ቲሞች እንዲገማገሙ በማድረግ እንዲያሻሽሉ መደረጉ፤
 ቡድን የማመቻቸት ስራዎችን ከስልጠናው ጋር ደርበውና አዋህደው መስራት መቻላቸው፤
 በሰልጣኞች መካከል ተቀራራቢ አቅም እንድፈጠር መጣራቸው፤

በድክመት
 መጀመሪያ አካባቢ ጥያቄ ለመጠየቅና ሃሳብ ለመስጠት ረጅም ጊዜ የሚወስዱ ተወያዮችን ሃሳባቸውን
እንዲያሳጥሩ ባለማድረግ የሌሎችን ተሳታፊዎች ጊዜ መሻማቱ፤
 ከስልጠናው አጀንዳ ውጪ የሆኑ ጥያቄዎችና የውይይት ሀሳቦች ሲነሱ የውይይቱን አቅጣጫ ባለማስያዛቸው
ምክንያት ምላሽ ያላገኙ ጥያቄዎች እንዲኖሩ ምክንያት መሆን፤ የቡድን ውይይቶችን አቅጣጫ የማስያዝ
ውስንነት መኖሩ፤
 በሰልጣኞች መካከል ተመጣጣኝ እውቀት እንዲኖር ጥረት የተደረገ ቢሆንም የተወሰነ ድክመት ያለ
መሆኑ፤

7.1.12. ኳሊቲ ሰርክልና ፕሮዳክሽን ቲሞች በተመለከተ፡-

በጥንካሬ

 በሃይል መድረክም ሆነ በቡድን ውይይት በተነሱ ጥያቄዎችም ሆነ ያልበሰሉ ሀሳቦች መካከል ግልፅ
ባልሆኑ ጉዳዩች ላይ ሰፊ ጊዜ ሰጥተው መወያየታቸውና ወደ ቡድን ቀርቦ ውይይት ሊደረግባቸው
የሚገቡትን በመለየት ረገድ ጥሩ ጥረት መደረጉ፤
 በየለቱ በመገናኘት የውሎ ግምገማ ማድረግ መቻላቸው፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 22


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 ራስ በራስ የመተማመንና ውስጡን ራሱን እንዲያይ ማድገግ መቻሉ፤

 አባላት የስልጠና ሰነዱን እንዲያነቡና ለስልጠናው በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ መደገፋቸው፤


 ሰልጣኙ ጥሩ ዲሲፕሊን እንዲኖረው የሚደረግ ጥረት መኖሩ፤

በክፍተት የታዩ፡-

 የኳሊቲ ሰርክልና ፕሮዳክሽን ቲም አባላትን በተሟላ መልኩ ወደ ተመጣጣኝ አቅም ማምጣት


ይቀራል፤
 የአባላትን ተሳትፎ፣ አመለካከትና ብስለት በመከታተል ጉድለትን ሊያሻሽል የሚችል ተከታታይ
ግንባታና ድጋፍ ማድረግ ላይ ክተት መኖሩ፤
 በመካከላቸው ያለውን ተነፃፃሪ አቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት 1 ለ 1 እንድደጋገፉ ማድረግ ላይ
ውስንነት መኖሩ፤
 አንዳንድ ሰልጣኞች የስልጠና ድሲፕሊን ችግር ያለባቸው መሆኑ፤
 ሰልጣኞች በተለያየ ሆቴሎችና በስልጠና ማዕከሉ በማረፍቸው ምክንያት ለውይይቱ አመች ቦታ
ያለመኖሩ፤
 በውይይት ወቅት ሰፊ ጊዜ ወስደው የማብሰልና ክርክር በማድረግ በኩል ውስንነት መኖሩ፤

8. የሰልጣኞች ተሳትፎን በተመለከተ

ስልጠኙ ለሀይል መድረክ ከሚሰጠው ማብራሪያ፣ ከሰነድና በግሉ ከነበረው ግንዛቤ ተነስቶ ሃሳቦችን፣
ልምዶችንና አመለካከቶችን በነፃነት በማንሸራሸር ግንዛቤውን እንዲያዳብር ይረዳ ዘንድ የስልጠናው ስነ ዘዴ
ሰልጣኝ ተኮር ሆኖ እንዲመራ ይፈለጋል፡፡ በዚህም በቡድኖችና በህዋስ ውይይት አባሉ በንቃት እንዲሳትፍ
ይጠበቃል፡፡ ከዚህ አንፃር የነበረው እንቅስቃሴ እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

በጥንካሬ፡-

 የስልጠናው ከሰዓት በማክበር በጥሩ ዲሲፕሊን መከታተላቸው፤


 አብዛኛው ሰልጣኞች በገለፃ ወቅት ማስታወሻ በአግባቡ የመያዝ ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ
መምጣቱ፤
 አብዛኛው ሰልጣኝ በኳሊቲ ሰርክልና ፕሮዳክሽን ቲሞች አደረጃጀት ላይ በአግባቡ መሳተፋቸው፤
 ሰልጣኙ በተግባር እንቅስቃሴ የገጠሟቸውን ችግሮችና መልካም ልምዶች ጋር በማስተሳሰር
በያገባኛል መንፈስ ጥሩ ውይይት ማድረግ መቻሉ፣
 አብዛኛው ሰልጣኝ ስልጠናውን በጥሩ ድሲፕሊን መከታተል መቻላቸው፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 23


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

 ሰልጣኙ በዶርምና አዳራሽ ወዘተ… ጥሩ ግንኙነትና ውህደት የነበረው መሆኑ፤


 ከሁሉም የስራ ዘርፎች ተውጣጥተው በቡድን ተደልድለው መወያየታቸው ለልምድ ልውውጥ እና
መደጋገፍ ትልቅ እገዛ አድርጓል፤
 የተለየ ድጋፍ የሚያስፈልገው /መስማት የማይችል/ ሰልጣኝ መኖሩ፤
 አጀንዳዎች አገር አቀፍ ሁኔታን ለመገንዘብ ማስቻሉ፤

በድክመት፡-

 የተጠናከረ ተሳትፎ ያለማድረግ፤


 በተወሰኑ ሰልጣኞች ማስታወሻ የመያዝ ውስንነት መኖሩ፤
 የተሰጣቸውን ሰነዶች በአግባቡ አለማንበባቸው፤
 ንቁ፣ መሳጭና ከፍተኛ ተሳትፎ አለማድረጋቸው፤
 አስተማሪና አዝናኝ ተሞክሮዎች ማቅረብ ላይ እጥረት መኖሩ፤
 አንዳንድ ሰልጣኞች የድሲፕሊን ችግር ያለባቸው መሆኑ፤
 የሴቶች ተሳትፎ በጣም አናሳና ጭራሽ የሉም በሚያስችል መልኩ መሆኑ፤

3.1. ያጋጠሙ ችግሮች፡-

 በስልጠናው የተለየ ድጋፍ የሚያስፈልገው አንድ መስማት የማይችል ሰልጣኝ መኖሩ፤

 የቴሌቪዥን አገልግሎት ቢስተካከል


 በሃይል መድረክ የተጠናከረ መዝናኛ አለመኖሩ
 ስልጠናውን የሚያጠናክሩ የተለያዩ አስተማሪና ተያያዥ ዘጋቢ ፊልሞችና ፓናል ውይይቶች
አለመኖራቸው፤
 አንዳንድ ቡድኖች የሚያዘጋጁትን ሪፖርት በሪፖርት በፎርማቱ መሰረት ያለማዘጋጀትና በወቅቱ
አለመላካቸው፤
 የደ/ዘይት የስልጠና ማዕከል ለሁሉም ሰልጣኝ ማረፊያ በቂ አልጋ ያለመኖሩ፤
 የቁርስ ሰዓት በጊዜው ያለማቅረብ በዚህም ከማሰልጠኛ ማዕከሉ ውጪ አልጋ የተያዘላቸው ሳታፊዎች
የሚጠለሉበት ቦታ የማጣት ሁኔታ መኖሩ፤

9. ማጠቃለያ፤

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 24


በኢፌድሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ የ EBC የመጀመሪያ ዙር አመራርና ባለሙያወች ስልጠና ሪፖርት

በልዩ ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ Page 25

You might also like