You are on page 1of 7

2012 .


ዕቅድ
ዓ ም ስልጠና

ሐምሌ 2012 ዓ.ም


መግቢያ

በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 አስተዳደር የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት ከ 2012
የበጀት ዓመት የስልጠና ዕቅድ መነሻ በማድረግ በ 2013 ዓ.ም የጽ/ቤቱን ዕቅድና እንዲሁም ስለ ጽ/ቤታችን
ስላለው አሰራር እና ስለሚሰጠው አገልግሎት ለህብረተሰቡ ፣ለባለድርሻ አካላት፣አደረጃጀቶች፣ እና በወረዳው
ውስጥ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ያላቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ የሰራተኞችን ክህሎት ለማጎልበት ይህ የስልጠና
እቅድ ማቀድ አስፈጓ፡፡

ራዕይ
በ 2013 ዓ.ም በከተማችን ያሉ የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ሰፊ የስራ እድል
የፈጠሩ የተሻለ ገቢ ያላቸው በምርት አገልገሎት ጥራት ዋጋና አቅርቦት በገበያ ተወዳዳሪ በራሳቸው
የሚተማመኑ ዘመናዊ የአስተዳደር ስርአት ያላቸውና ሰፊ የኢንደስትሬ መሰረት የሚሆን ልማታዊ
ባለሃብቶች ተስፋፍቶ ማየት

ተልዕኮ
 በስትራቴጂው የተቀመጡ ድጋፎችን በአንድ መአከል በማደራጀት ፈጣን ቀልጣፋና የተቀናጀ ድጋፍ
በመስጠት ስራ አጥ ዜጎችን የስራ ባለቤት ማድረግ እንዲሁም ነባር ኢንተርፕራይዞችን በገበያ
ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በማስቻል የከተማዋን ህ/ብ ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እና
ጥ/አ/ኢንተርፐራይዞችን ወደ ኢንደስትሪ ለሚደረገው ሽግግር መሰረት እንዲሆኑ ማስቻል፡ -
 በዋና ዋና ሀገራዊ እና ከተማ አቀፍ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባትን መፍጠር
 የህዝብን ትክክለኛ የመረጃ ፍላጎት ማርካት፣ ተሳትፎና ተጠቃሚነቱ
በቀጣይነት ማሳደግ፣ የከተማዋንና የሀገራችንን መልካም ገፀታ መገንባት
እሴቶች
 ተጠያቂነት
 ግልጽነት
 የላቀ አገልግሎት መስጠት
 በእውቀት በእምነት መመራት፣ መስራት
 ለለውጥ ዝግጁነት
 በከተማችን የገጽ ግንባር ስኬት ግንባር ቀደም ሚና እንጫወታለን
 የጋራ መግባባት ለመፍጠር እንተጋለን
 ለጊዜ ላቅ ያለ ዋጋ እንሰጣለን

የእቅዱ መነሻ ሁኔታዎች


 ባለድርሻ አካላት በተለይም የዘርፉን ስራ ተረድቶ ወደ ስራ ያለመግባት
 የኔነትና የባለቤትነት ስሜት ያለመኖር
 የአመለካከት ለውጥ ያለማምጣት
 ስለሚሰጠው አግልግሎት ህብረተሰቡ ያለው ግንዛቤ አነስተኛ ስለሆነ
 በሚሰጠው ስልጠና፣ የግንዛቤ መድረኮች ትምህርት ወስዶ ወደ ስራ አለመግባት
 የክህሎት የአመለካከት ክፍት ያለባቸው ባለሙያዎችን ባለድርሻ አካላትን ስራ አጥ ወጣቶችንና
ሴቶችን ተጠቃሚ ማድረግ፡፡
ግብ
በወረዳ ውስጥ የሚኖሩት ስራ አጥ ዜጎችን ግንዛቤ እንዲያገኙ ማድረግ በማእከሉ መጥተው ምዝገባ ከተመዘገቡ በኃላ
በመረጡት ዘርፍ ስለጠናውን ከሰለጠኑ በሃላ ተደራጅተው እራሳቸውን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ እንደዚሁም
ህብረተሰቡ ወቅታዊ የሆነ መረጃን እንዲያገኝ በተለያዩ በበራሪ ወረቀቶች፣ በብሮሸር፣ በተለያዩ መፈክሮች ፣ባነር በተለያዩ
ቦታች በመስቀል፤ መረጃን ከህዝብ ለመንግስት ፣ከመንግስት ለህብረተሰቡ እንዲደርስ የሚያደርግ ድልድይ ስለሆነ
በማንኛውም ቦታና ሰዓት በመገኘት ስራን ሰርቶ የህብረተሰቡን፣ ባለድርሻ አካላት ፍላጎት በማሟላት በስራዎች ላይ ተሳታፊ
እንዲሆኑ ማድረግ ነው ፡፡

ዝርዝር ግቦች

ግብ 1 ፡- የህዝብ ክንፍን በተመለከተ

 ከወረዳው ማህበረሰብ ጋር ተቀራርበው በመስርት ላይ የሚገኙት የህዝብ ክንፍ የሆኑት አደረጃጀቶችን


ማለትም ወጣቶች ማህበር፣ ሴቶች ማህበር፣ ወጣቶች ፎረሞች፣ ነዋሪዎች
ፎረሞች፣የአንቀሳቃሽየልማት ቡድን፣ የእድሮች ምክር ቤት የሚሳተፉ አባላትና አመራሮችን ማሰልጠን
 ከቀጠናና ከየመንደሩ የተመረጡ የስራ እድል ፈጠራ ኮሚቴዎን የግንዛቤ ስልጠና መስጠት፡፡
 ለ 25 ፈፃሚዎች ለ 248 ነባር ኢንተርፐራይዞች የአመለካከትና የማስፈጸም ክህሎት በአመት 2 ጊዜ
ስልጠና እንዲያገኙና በአመለካከት ክህሎት እንዲለወጡ ማድረግ፡፡

ግብ 2 ፡- የመንግስት ክንፍ

 በወረዳው ውስጥ የሚገኙ ሴክተር ቢሮዎች (ባለድርሻ ጽ/ቤቶችን) አመራረሮች ፣የስራ ሂደቶችና ግንባር
ቀደም ሰራተኞችን ዘርፉ በሚስጣቸው አገልገሎጦች ዙርያ ስልጠና መስጠት፡፡

ግብ 3 ፡- የፓርቲ ክንፍን በተመለከተ

 ከወረዳው ማህበረሰብ ጋር ተቀራርበው ፖለቲካዊና ማህበራዊ ችግሮችን ለመፍታት እየሰሩ የሚገኙትን


ወጣቶችና ሴቶች ሊግ አደረጃጀቶች አባላትና አመራሮች ማሰልጠን፡፡
የሚያጋጥሙ ችግሮች

 ስልጠናዎች በወቅቱ ያለመስጠት


 የፋይናንስ እጥረት ችግር
 የሰለጠኑት ሌሎችን የማብቃት ሥራ ያለመስራት
 የሰለጠኑትም ቢሆኑ ተከታታይ ሥራ ያለመሠራት
 በ ሞርኒግ ብሪፊንግ የተደራጀ ንቁ ኃይል ያለመሆን

የመፍትሄ አቅጣጫ

 የሰለጠኑትን ዕውቅና እየሰጡ መደገፍ


 የሰለጠኑበትን ሙያ የማስተላለፍ አቅም መፍጠር
 በተደራጀ ሁኔታዎች አመቻችተው መደገፍ

ድጋፍና ክትትል

 በጽ/ቤቱ በኩል አስፈላጊው እገዛ በመስጠት ድጋፍ ማድረግ


 የለውጥ የኮሙኒኬሽን ሰራዊትን በተደራጀ አግባብ መምራት መደገፍ
 በየወቅቱ የግንኙነት ጊዜ በማስቀመጥ ስራዎችን መገምገም
 በተገመገመ ልክ ቼክሊስትና ግብረ-መልስ በመስጠት የማስተካከያ እርምጃ መውሰድ

ማጠቃለያ

በወረዳችን ውስጥ ያለው ማህበረሰብ አስተሳሰብ ለመቀየር የባለቤትነት ስሜት በመፍጠር የተሻለ
የዘርፉን ሰራዊት በመገንባት ስለ ጽ/ቤቱ አገልግሎት አሰጣጡና ስለሚሰጠው የአገልግሎት አይነት የአመለካከት
ለውጥ ማምጣት ማስቻል ነው፡፡
የአመለካከት ለውጥ መሠረት ባለድርሻ አከላትና ማህበረሰቡ ሲሆን ተጋግዞ ተረዳድቶ እንዲሰራ
የለውጥ ምዕራፍ አካል እንዲሆን ስልጠና ኃይል መሆኑን ግንዛቤ በመውሰድ መስራት ማስቻል ሲሆን ለውጡን
በመገምገም ውጤቱን ተደራሽ ማድረግ ነው፡፡
የወረዳ 2 አስተዳደር ስራ ዕድል ፈጠራ ኢ/ል/ጽ/ቤት
የ 2012 ዓ.ም የስልጠና ዕቅድ አክሽን ፕላን

ተ.ቁ ዝርዝር እቅድ (ግብ) መለኪያ ብዛት የሚፈጸምበት ፈፃሚ ብር


ወቅት
 ከወረዳው ማህበረሰብ ጋር ተቀራርበው በመስርት ላይ የሚገኙት 3500
የህዝብ ክንፍ የሆኑት አደረጃጀቶችን ማለትም ወጣቶች ማህበር፣
ሴቶች ማህበር፣ አንቀሳቃሽ የልማት ቡድን፣ ነዋሪዎች
ፎረሞች፣የነጋዴዎች ፎረሞች፣ የእድሮች ምክር ቤት የሚሳተፉ የስራ ሂደቶችና

አባላትና አመራሮችን ማሰልጠን በቁጥር 350 ከሃምሌ 01/2011 - ጽ/ቤት ሀላፊ

 ከብሎክና ከየመንደሩ የተመረጡ የስራ እድል ፈጠራ ኮሚቴዎን ታህሳስ 30/2012


1 የግንዛቤ ስልጠና መስጠት፡፡ ዓ.ም

 ለ 25 ፈፃሚዎች ለ 495 ነባር ኢንተርፐራይዞች የአመለካከትና


የማስፈጸም ክህሎት በአመት ጊዜ ስልጠና እንዲያገኙና
በአመለካከት ክህሎት እንዲለወጡ ማድረግ፡፡

 በወረዳው ውስጥ የሚገኙ ሴክተር ቢሮዎች (ባለድርሻ ጽ/ቤቶችን) ከጥር 01/2011- 4400
አመራረሮች ፣የስራ ሂደቶችና ግንባር ቀደም ሰራተኞችን ዘርፉ መጋቢት 30/2011
በሚስጣቸው አገልገሎቶች ዙርያ ስልጠና መስጠት፡፡ በቁጥር 44 ዓ.ም ጽ/ቤትሀላፊ
2
 ከወረዳው ማህበረሰብ ጋር ተቀራርበው ፖለቲካዊና ማህበራዊ 3000
ችግሮችን ለመፍታት እየሰሩ የሚገኙትን ወጣቶችና ሴቶች ሊግ
አደረጃጀቶች አባላትና አመራሮች ማሰልጠን ፡፡ በቁጥር 30 ከሚያዝያ 01/2011- ጽ/ቤት ሀላፊ
3
ሰኔ 30/2011 ዓ.ም
በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ
02 የስ/ዕ/ፈ/ኢ/ል/ ጽ/ቤት
የ 2013 ዓ.ም ስልጠና
ዕቅድ

ሀምሌ 2012 ዓ.ም

You might also like