You are on page 1of 34

የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር

የመርሃግብር አተገባበር መመሪያ (መተመ)

ለውሳኔ ሰጪዎች
መስከረም 2009
ማውጫ
የቃላት ትርጉም.....................................................................................................................................................II
1. መግቢያ............................................................................................................................................................1
2. ስለ መርሃግብሩ መግለጫ..............................................................................................................................2
2.1 የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሃግብር (ልሴኔመ) የፖሊሲ አቅጣጫና አላማዎች..................................2
2.2. የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃግብር ስልታዊ ዘዴዎች...........................................................................3
2.3. የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብርመሰረታዊ መመሪያዎች...............................................................4
2.4. መርሃ ግብሩ በተፈጥሮ አካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንዳያስከትል
የሚደረጉ ጥንቃቄዎች.........................................................................................................................6
2.5. የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር የዕቅድ አሰራር ሂደት...................................................................7
3. የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር ዝርዝር ፕሮግራሞች................................................................................8
4. ለውሳኔ ሰጪዎች ትኩረትን የሚሹ ጉዳዮች................................................................................................10
4.1. የመረሃግብሩ አገባብና አወጣጥ፣ መሰረታዊ መመሪያዎች፣ ሀላፊነቶችና ግዴታዎች......................10
4.2. የክፍያ አፍጻጸም መሠረታዊ መመሪያዎች.........................................................................................13
4.3. የግዢ ሥርዓቶችና አጀማመራቸው....................................................................................................14
5. የውሣኔ ሠጪዎች ዋና ዋና ሥራዎችና ኃላፊነቶች........................................................................................15
5.1. በበጀት አስተዳደር..............................................................................................................................15
5.2. የልሴኔመ የምግብ አስተዳደር.............................................................................................................18
5.3. በልሴኔመ የቁሳዊ ሐብት አያያዝ ......................................................................................................20
6. በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር ማህበራዊ ተጠያቂነት...........................................................................20
7. የልሴኔመ 4 ከቀደሙት ምዕራፎች ልዩ የሚያደርጉት ዋና ዋና ፈጠራዎች................................................21
8. በልሴኔመ 4 የተሻሉ ዉጤቶችን ለማምጣት መተግበር ያለባቸው ቁልፍ ተግባራት...............................23
8.1. የማስተባበር እቅድ............................................................................................................................23
8.2. የመርሀ ግብሩ ቅንጅትና ተደጋጋፊነቶች...........................................................................................24
8.3. ችግርን የመቋቋምን አቅም መገንባት................................................................................................24
8.4. የመረጃ አያያዝ ዘዴዎች....................................................................................................................25
8.5. የአቅም ግንባታ ስልት.......................................................................................................................26
I
የቃላት ትርጉም

ቅድመ ሁኔታ ሙሉ አካል ያላቸው ጐልማሳ ቤተሰቦች በማህበረሰብ ልማት ውስጥ እንዲሳተፉ
ይጠበቃል ፡፡ ነፍስጡርና ጡት የሚያጠቡ እናቶች የራሳቸውንና የሕፃኑን
ጤንነትና ደህንነት ለመጠበቅ እንዲችሉ ወደ ጊዜያዊ ተጠቃሚነት ይሸጋገራሉ፡፡
በቅድመ ሁኔታ አሠራር ውስጥ ቤተሰብ ስለአለበት ሀላፊነት የሚነገረው ሲሆን
ክትትልም ይደረግበታል፡፡ ነገር ግን በቅጣት አይነት ከሚያገኘው ጥቅም
ምንም አይቀነስበትም ፡፡

መጠባበቂያ በጀት የመጠባበቂያ በጀቱ በመጠባበቂያ እቅዱ በልማታዊ ሴፍቲኔት መረሀግብር


አደጋዎችን ለመከላከል እንዲቻል አስፋፍቶ ለመስራት የሚጠቅም በጀት ነው፡
፡ ጠቅላላ በጀት ሥራ ከተካሄደ በኃላ (የሚተላለፉ ስጦታዎች፣ የካፒታል እና
የአስተዳደራዊ ወጭዎችን ጨምሮና ለመተዳደሪያ ማሻሻያ ለአቅም ግንባታ
ወጪዎች ሳይጨምር) ወረዳው ለህዝብ የሚተላለፈውንና ለማህበረሰቡ ልማት
ተጠቃሚዎች የሚተላለፈውን ጠቅላላ በጀት አምስት በመቶ አስልቶ በጠቅላላ
በጀቱ ላይ የሚጨምረው ነው፡፡

የፆታ እኩልነት የፆታ እኩልነት የሴቶችንና የወንዶችን ልዩ ፈላጐቶችን፣ ዝንባሌዎችንና


አቅማቸውን ያገናዘብ በእኩልነት በመርሀ ግብሩ እንዲጠቀሙ ለማስቻል ነው።
ይህ የሚደረገው ሁሉቱም ወንዶችና ሴቶች በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር
ውሳኔ አሰጣጥ መዋቅር ውስጥ እኩል በማስተፍ ነው፡፡

ማህበራዊ ማህበራዊ ተጠያቂነት ማለት ማንኛውም ዜጋ በመሠረታዊ ህዝባዊ አገልግሎት


ተጠያቂነት ተጠቃሚ የሆነ ሁሉ የሚያስፈልገውን ፍላጐቶችና ስሜቶች የሚገልፅበት
እንዲሁም የፖሊሲ አውጪዎችና አገልግሎት ሰጪዎች ስለስራቸው አፈፃፀም
ተጠያቂ የሚያደርጉበት አሰራር መፍጠርያ ዘዴ ነው፡፡ የሂደቱም አላማ
የሚፈለጉት መሠረታዊ አገልግሎቶች በጥራት እንዲቀርቡለት ለማስቻል ነው።

ምልመላ ምልመላ ማለት በልሴኔመ አካባቢዎችንና ተጠቃሚዎችን ለማሳተፍ የመምረጫ


ዘዴ ነው፡፡ ምልመላውም ሆነ ቅድሚያ አሰጣጡም ለደሀ ተጠቃሚዎች
ቅድሚያ ይሠጣል።

ክፍያ ክፍያ የጥሬ ገንዘብ ክፍያንና ወይም በልሴኔመ የሚከፋፈል ምግብ በማህበረሰብ
ልማት ስራ ተሳታፊዎች ውስጥ ወይም ለቀጥታ ቋሚ ተጠቃሚዎች የሚከፈል
ክፍያ ነው፡፡

II
ምህረ ቃላት

ልሴኔመ ልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሃግብር

ልሴኔት ልማታዊ ሴፍቲ ኔት

መተመ የመርሃግብር አተገባበር መመሪያ

መያድ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች

ማጥፖ የማህበራዊ ጥበቃ ፖሊሲ

ምዋማዳ ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት

ምዋዴ ምግብ ዋስትና ዴስክ

ሰማጉሚ የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር

ሰማጉቢ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ

ቤሃግመ ቤተሰብ ሃብት ግንባታ መርሃ ግብር

ብስምፖ ብሔራዊ የሥርአተ ምግብ ፖሊሲ

አስመፖ አደጋ ስጋት መከላከል ፖሊሲ

አንለማአኢ አየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ

ኢማተመ የኢትዮጵያ የማህበራዊ ተጠያቂነት መርሃ ግብር

ዓምፕ የዓለም የምግብ ፕሮግራም

ዕትፕ ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ፕላን

ጥአልኢ ጥቃቅንና አነስተኛ ልማት ኢነተርፕራይዞች

III
IV
I. መግቢያ

የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር (ልሴኔት/PSNP/) በ1994/95 በኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን የድርቅ
አደጋ ተከትሎ በሰብአዊና በንብረት ላይ ያስከተለውን አደጋ መፍትሔ ለመስጠትና ችግሩ በተከሰተ ቁጥርም
የለጋሾችን እርዳታ መጠየቅ ህይወት እንዳይጠፋ ቢከላከልም የደሃውን ንብረት ከመጥፋት አላዳነውም፡
፡ የምግብ ዋስትናንም በኢትዮጵያ ውስጥ ለማረጋገጥ አልቻለም፡፡ ችግሩንም ለመፍታት ከተደረጉ ጥልቅ
ውይይቶች የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር ሊጀመር ችሏል፡፡ መርሃ ግብሩ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ
የቀሰማቸውን ልምዶች በመጠቀም እያደገ አራተኛ ምእራፍ ላይ ይገኛል፡፡

ይህ የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሃ ግብር በህዝብ ብዛቷ 2ኛ በሆነች ኢትዮጽያ ትልቁ የሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር
ሲሆን ብዙ ባለድርሻ አካላትንም ያሳትፋል፡፡ ይህ የአራተኛው ምእራፍ የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሃ ግብር
አተገባበር መመሪያ ተዘጋጅቶና ተከልሶ የመርሃ ግብሩን መግለጫ፣ በቅደም ተከተል የሚሰሩ ድርጊቶችን፣
በተለያየ ደረጃ ያሉ የባለ ድርሻ አካላትን የስራ ድርሻና ኃላፊነቶችን ይዟል፡፡

የትኛውም የመርሃ ግብሩ ፈፃሚ አካል ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንዲችል የመርሃ ግብሩን አተገባበር
ሙሉ በሙሉ ሊረዳው ይገባል፡፡ ሆኖም ለአያያዝና ለአጠቃቀም እንዲመች በአጭሩ የተዘጋጀ ለታዳሚው
አካል ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ፈፃሚ አካላትም በሶስት አይነት ተከፍለዋል፡፡ እነርሱም፡- ውሳኔ
ሰጪ አካላት፣ ባለሙያዎችና በመስክ ላይ የሚገኙ ፈፃሚዎች ናቸው፡፡ ይህም ትንሽ መፅሐፍ በክልል፣ በዞን፣
በወረዳ ደረጃ ለሚገኝ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች (መያድ) ውሳኔ ሰጪዎች እንዲገለገሉበት
የተዘጋጀ ነው፡፡

በዚች መመሪያ ውስጥ ለየልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሃ ግብር የፖሊሲ አቅጣጫዎች፣ በመርሃ ግብሩ የታቀዱ ግብና
ውጤቶች፣ መሰረታዊ መመሪያዎች፣ ውሳኔ ሰጪዎች ፣ በአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ያለተፈለጉና
ጎጂ የሆኑ ውጤቶች እንዳይፈጠሩ ማድረግ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች፣ የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሃ ግብር
እንደ አሰራር ስርዓት እና የዕቅድ ሂደቱን ይዟል፡፡ የአተገባበር መመሪያው የመርሃ ግብሩን የተለያዩ ክፍሎችና
እንዴት ከተለያዩ የፖሊሲ አቅጣጫዎች ጋር እንደሚገናኝ ያስረዳል፡፡ ቀጥሎም ውሳኔ ሰጪዎች የመርሃ
ግብሩ ተጠቃሚዎች አመራረጥና እንዴት መመረቅ እንደሚገባቸው፣ የጥቅማ ጥቅም ክፍያን ለተጠቃሚዎች
ማስተላለፍና፣ የግዢ ጣሪያንም ይዟል፡፡ በመመሪያው ውስጥ የውሳኔ ሰጪዎች በገንዘብ፣ በምግብና በሌሎች
ቁሳዊ ሀብቶች ላይ ያላቸው የስራ ድርሻና ኃላፊነቶች ተዘርዝረዋ፡፡ በተጨማሪም በልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሃ
ግብር ውስጥ ስለ ማህበራዊ ተጠያቂነትና ወሳኝ የሆኑ ፈጠራዎች በዚህ በአራተኛ ምዕራፍ ውስጥ ቀድመው
ከነበሩት ምዕራፎች የተሻለ እንዲሆን የሚያደርጉ ክፍሎችንም ይዟል፡፡ የመመሪያው የመጨረሻ ክፍል
የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሃ ግብር አራተኛ ምዕራፍ ውጤታማ ሊያደርጉት የሚችሉትን ዝርዝር ጉዳዮች
ጠቅለል አድርጎ ያቀርባል፡፡

1
II. ስለ መርሃግብሩ መግለጫ

2.1 የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሃግብር (ልሴኔመ) የፖሊሲ አቅጣጫና አላማዎች


በስራ ላይ ያለው የኢትዮጵያ መንግስት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ፕላን (GTP) የአነስተኛ ገበሬዎችና አርብቶ
አደሮቸና ምርትን ምርታማነትን ማሳደግ፣ ግብይትን ማጠናከር፣ በግል ክፍለ ኢኮኖሚ የተሰማሩትን ተሳትፎ
ማጠናከር፣ በመስኖ የሚለማውን መሬት መጠን ማስፋት፣ እና የምግብ ዋስትናቸው ያልተረጋገጠላቸውን
ቤተሰቦች ቁጥር መቀነስ ነው፡፡ የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሃ ግብር እነዚህን ዓላማዎች ለማሳካት አስተዋፅኦ
የሚያደርግ ሲሆን ለአራት ፖሊሲዎችም አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡

እነዚህም፡- የማህበራዊ ጥበቃ ፖሊሲ (Social protection policy)


- የአደጋ መከላከልና አስተዳደር ፖሊሲ (Disaster Risk Management)
- የብሔራዊ የሥርአተ ምግብ መርሀግብር (National Nutrition Program) እና
- የአረንጓዴ ልማት ኢኮኖሚ ፖሊሲ (Climate Resilient Green Economy) ናቸው፡፡

ፖሊሲና አላማው የውጤት መመዘኛዎች


የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ፕላን • -ከድህነት ወለል በታች የሚገኙትን የልማታዊ
በህዝቧ ነፃና ቀጥተኛ ተሳትፎ ዲሞክራሲያዊ፣ መልካም ሴፍቲ ኔት መርሃ ግብር ተጠቃሚዎችን ቁጥር
አስተዳደር እና ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት፣ አሁን መቀነስ፡፡
ካለችበት የድህነት ደረጃ ወደ መካከለኛ ገቢ ካለችው • -ድህነትን ለመቀነስ የሚደረገውን ወጪ ከዓመታዊ
አገሮች ምድብ ከ2020-2025 (እ.ኤ.አ) መግባት። አጠቃላይ ምርት (GDP) በመቶኛ መጨመር።
የማህበራዊ ጥበቃ ፖሊሲ • -ከድህነት ወለል በታች እንገኛለን ብለው
ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የተሻሻለ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ራሳቸውን የሚመድቡ የሴፍቲ ኔት ተጠቃሚዎች
ማህበራዊ ፍትህ ማግኘት ብዛት
• -መርሃ ግብሩ ከሚሰጠው የነፃ ክፍያና በሁኔታዎች
ከተወሰኑ የሥርአተ ምግብ ተጠቃሚዎች ብዛት
የአደጋ ስጋት መከላከል (DRM) • -የሴፍቲ ኔት ተጠቃሚዎች የተፈጥሮ አደጋ
የአደጋ ስጋቶችንና አደጋዎች የሚያስከትሉትን ውጤቶች ሲደርስባቸው የምግብ ፍላጎታቸውን ለማሟላት
ለመቀነስ የተቀናጀና የተጠናከረ የአደጋ ስጋቶች የማምረቻ እሴቶችን ተገደው ይሽጡ እንደነበረው
ማስወገጃ ስልት በመንደፍ ዘላቂነት ያለው ዕድገት ከመሽጥ ይታቀባሉ፡፡
ማምጣት • - በከፍተኛ የምግብ እጥረት የሚጎዱ ህፃናት ቁጥር
ይቀንሳል፡፡
ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ -በተሻሻለ ተፋሰስ ልማትና የግጦሽ መሬት አያያዝ
መገንባት በመቶኛ ሲታይ ተሻሽሎ ይገኛል።
በ2025 (እኤአ) በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር፣ -በህዝብ ልማት ተሳትፎ ስራ ወደ ከባቢ አየር
የካርቦን ልቀት መጠን የቀነሰና አገሪቱን መካከለኛ ገቢ እንዳይለቀቅ የተከለከለ የካርቦንዳይ ኦክሳይድ መጠን
ካላቸው ምድብ ውስጥ ማስገባት (በሜትሪክ ቶን) ይቀንሳል።
ብሔራዊ የሥርአተ ምግብ መርሃ ግብር - መርሃ ግብሩ በሚሰራባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ከ5
የኢትዮጵያውያን እናቶችና ህፃናት የሥርአተ ምግብ ዓመት ዕድሜ በታች የሆኑ የሚቀጭጩ ህፃናትን ቁጥር
ማሻሻል መቀነስ

2
ከላይ በተዘረዘሩት የፖሊሲ ማዕቀፍ ላይ በመመስረት የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሃ ግብር የሚጠበቀውን
ውጤት እንደሚከተለው አድርጓል፡፡

የመርሃ ግብሩ ግብ
“የምግብ ዋስትና ያልተረጋገጠላቸው የገጠር ቤተሰቦች ከሚገጥሟቸው ችግሮች በፍጥነት
የሚያገግሙ፣ አናኗራቸው የተሻሻለ፣ የምግብ ዋስትናቸውና ሥርዓተ-ምግባቸው የተሻሻለ ይሆናል፡፡”

ከመርሃ ግብሩ የሚጠበቅ ውጤት


“የምግብ ዋስትናቸው ያልተረጋገጠላቸው ቤተሰቦች ለገጠሩ በተዘጋጀው ልማታዊ ሴፍቲ ኔት የምግብና
የሥርዓተ-ምግባቸው ዋስትና አገልግሎቶች ላይ በተሻለ ሁኔታ ይሳተፋሉ፡፡”

2.2. የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃግብር ስልታዊ ዘዴዎች


ይህ አራተኛው የልማታዊ ሴፈቲ ኔት መርሀ ግብር ከአንድ ራሱን ከቻለ መርሃ ግብር የማህበራዊ ጥበቃን፣
የአደጋ ስጋትን ለመቆጣጠር፣ የሥርአተ ምግብ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ
ለመገንባት በሚያስችሉ ፖሊሲዎች ማዕከል ሆኖ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን ለማስፈፀም
እንዲያስችል ሆኖ ተዘጋጅቷል፡፡ መርሃ ግብሩ በተቀናጀ ሁኔታ የጥቅሞችን ማስተላለፍ፣ ከሚሰሩ የልማት
ስራዎች ጋር የተቀናጀ፣ ከጤናና የሥርአተ ምግብ አገልግሎቶች ጋር ተቀናጅቶ የተጠቃሚዎችን ከመርሃ ግብሩ
ለማስመረቅ ድጋፍ ይሰጣል፡፡

ስለዚህም አራተኛው የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር የአሰራር ለውጥን አምጥቷል፡፡የአሰራር ለውጡም
ወጥ የሆነ አስተዳደራዊ ስልቶችንና መሳሪያዎችን በመጠቀም የፖሊሲ፣ ተቋማዊና የተበጣጠሰ የበጀት
አስተዳደርን ለመቀነስ ይረዳል፡፡ የማህበራዊ ጥበቃውና የአደጋ ስጋት መቆጣጠሪያ ስልቶች ለአደጋ ተጋላጭ
ለሆኑ ቤተሰቦች የሚጠቅሙ መጠነኛ አገልግሎቶችን ያዘጋጀ ሲሆን የተለያዩ ፈፃሚዎችም ወጥ በሆነ ዕቅድና
የማስተባበሪያ መዋቅሮች ከስራ ድርሻቸውና ኃላፊነታቸው ጋር ይዟል፡፡ በመጨረሻም ተጠቃሚዎችን
የሚያገለግሉ ድርጅቶች ሁሉ ወጥ የሆኑ መጠቀሚያ ዘዴዎችን፣ መሳሪያዎችንና አቀራረቦችን በመጠቀም
ወጪን በአግባቡ መጠቀምና የተሻለ ውጤት ማምጣታቸውን ማረጋገጥ ይገባቸዋል፡፡ ለአገልግሎት
የሚውሉ ዘዴዎችና መሳሪያዎችም ለ6 ቅድሚያ ለሚገባቸው ጉዳዮች ማለትም የተጠቃሚዎች ምርጫ፣
የመረጃ ልውውጥ ዘዴዎች፣ የአደጋ ስጋት መከላከል ዘዴዎች፣ ዕቅድ ስራ የማስተባበርና ማስተዳደር፣
ማህበራዊ ተጠያቂነትና የአቅም ግንባታ ስልቶችን መንደፍ፣ መምከርና የተሻለውን ስልት አስፋፍቶ መጠቀም
ይገባቸዋል፡፡

የመርሃ ግብሩ የአሰራር ስልትና ለአራቱ ከላይ የተዘረዘሩት ፖሊሲዎች (ማህበራዊ ጥበቃ፣ የአደጋ ስጋትን
መከላከል፣ ለአየር ንብረት መለወጥ አለመበገር፣ የሥርአተ ምግብ) ትግበራ ውጤት አስተዋፅኦ የሚያደርግ
ሲሆን ለውጤቱ ግን የተቀናጀ የአሰራር መዋቅርና ጉዳዮችን በጥልቀት መመልከትን ይጠይቃል፡፡ የቀድሞው
የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር እና የቤተሰብ ሃብት ግንባታ መርሃ ግብር (HABP) በዚህ ምዕራፍ በአንድ
ላይ ተጠቃለው የሚመዘኑ ሆነዋል፡፡ በዚህ ስራ ላይ የሚሳተፉት ዘርፎችና ሚኒስቴር መ/ቤቶችም ከቀድሞው
ጨምረዋል፡፡
3
2.3. የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር መሰረታዊ መመሪያዎች

መርሃ ግብሩን በሁሉም ደረጃ ለመቅረፅና ለመተግበር የሚያገለግሉ የሚከተሉትን ዋነኛ መመሪያዎችን ይዟል፡

1. ፍትሐዊነትና ግልፀኝነት የተሞላበት የተጠቃሚዎች ምርጫ፡ ተጠቃሚዎች ማህበረሰቡን ባሳተፈ


መልኩ መመረጥ የሚገባቸውን የሚመርጡበት፣ መመረጥ የማይገባቸውም እንዳይመረጡ ስህተትን
ለመከላከል ነው፡፡ ለተጠቃሚነት የተመረጡ ሰዎች ስም ዝርዝር በህዝብ ስብሰባ ላይ ይነበባል፣ ውይይት
ይደረግበታል፡፡ የተመራጮችም ስም ዝርዝር በግልፅ ለህዝብ በሚታይ ስፍራ ይለጠፋል፡፡

2. በጊዜው፣ ዓይነቱና አግባብነቱ የታወቀ ክፍያ ማስተላለፍ፡ ለሴፈቲ ኔት ተግባራዊነት ለተጠቃሚዎች


ሁልጊዜ የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር ተጠቃሚ መሆናቸውን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል፡፡ የመርሃ
ግብሩ ተጠቃሚዎች ስለሚተላለፍላቸው ጥቅሞች እርግጠኛ የሚሆኑት ለመርሃ ግብሩ ተጠቃሚነት
ሙሉ መብት እንዳላቸው ሲያውቁና ምን አይነት ጥቅሞችን በምን መጠንና መቼ እንደሚቀበሉ ሲያውቁ
ነው፡፡ በአመት ውስጥ ሊከፈላቸው የሚገባው ጥቅም በወቅቱ አግኝተዋል የሚባለው ልክ በጊዜው
ወይም ከሚያስፈልግበት ወቅት ቀድሞ ሲቀበሉ ነው፡፡ ይህም ደግሞ ቀድሞ ለዕደላ በተሰራ የጊዜ ሰሌዳ
መሰረት መሆን ይገባዋል፡፡ የሚቀበሉት ጥቅማ ጥቅም አግባብነት አለው የሚባለው በፍላጎታቸው ላይ
የተመሰረተ ሲሆን ነው፡፡ ገንዘብ የሚሰጣቸው ከገበያ መግዛት የሚፈልጉትን መግኘት በሚችሉበት
ሁኔታ ሲሆን፣ የምግብ እህል በገበያ የማይገኝ ወይም ዋጋው ውድ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ የምግብ
እህል እንዲቀበሉ ያደርጋል፡፡ የሚተላለፈው ጥቅማ ጥቅም ተስማሚና ተገቢ ነው የሚባለው በገንዘብም
ሆነ በምግብ ዓይነት እኩል ዋጋ ሲኖራቸው ነው፡፡

3. የክፍያዎች አስፈላጊነት (Primacy of transfers)፡ ዋናው የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር አላማ
ሊከተል የሚችል አደጋን መከላከል እንደመሆኑ የመርሃ ግብሩ ተጠቃሚዎች ሊተላለፍላቸው
የሚገባቸውን እንዲያገኙ ከሁሉ ጉዳዮች ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ በምንም ምክንያት ሊከፈላቸው
የሚገባቸው ክፍያ ሊዘገይባቸው አይገባም፡፡

4. ልማታዊ ሴፍቲኔት፡-የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር ልማታዊ መርሃ ግብር ነው የሚያሰኘው


ምግብ ለሚያስፈልጋቸው ምግብ መስጠት ወይም የማምረቻ ሃብታቸው በችግር ምክንያት ያለ
አግባብ እንዳይባክን ለመከላከል ብቻ አይደለም፡፡ ነገር ግን ለምግብ ዋስትና አለመረጋገጥ ዋነኛ
ለሆኑ ምክንያቶች መፍትሄ ለመስጠትና ለኢኮኖሚ እድገት አስተዋፅኦ ለማድረግም ነው፡፡ ልማታዊ
የሚያደርገውም የመሰረተ ልማት መዋቅሮችንና የተፈጥሮ ሃብቶችን ማሻሻል ከልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ
ግብር የጉልበት ስራ ውጤቶችና ወደ ህዝቡ የሚተላለፈው ገንዘብ በኢኮኖሚ ውስጥ የሚያመጣቸው
ተጨማሪ ውጤቶች ናቸው፡፡

5. የመተዳደሪያ መፍትሄ አምጪነት፡ የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር 1ኛ/ ቤተሰቦችና ግለሰቦች እንደ
አቅማቸው 2ኛ/ ሶስቱም ዓይነቶች የመተዳደሪያ መንገዶች [Pathways](የሰብልና እንስሳት እርባታ፣
ከግብርና ጋር ተያያዥነት የሌላቸው የገቢ ምንጮችና ለደሞዝ ተቀጣሪነት) ተቋማዊ አቅምን ይገነባል፡፡

4
6. ከልማት ስራዎች ጋር መዋሃድ፡- የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር በራሱ ፕሮጀክት አይደለም፡፡ ሆኖም
ከአካባቢያዊ የልማት ዕቅዶች ጋር ተዋህዶ የሚሰራ የልማት አካል ነው፡፡ ስለዚህ የልሴኔመ ከወረዳ፣
ከዞን፣ ክልልና የፌደራል ደረጃ ጋር የሚሰሩ የልማት ዕቅዶች አካል ነው፡፡

7. እንደ አስፈላጊነቱ የሚሰፋ፡- የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር የህዝቡን አኗኗር የሚያቃውሱ ሁኔታዎች
ሲፈጠሩ ችግሮቹ በተፈጠሩባቸው ወረዳዎች ውስጥ በችግሩ ለተጎዱ ቤተሰቦች የምግብ ዋስትናቸው
ወደ ከፋ ሁኔታ እንዳይገባ ተጨማሪ ድጋፍ ይደረግላቸዋል፡፡ ሆኖም የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር
የተጨማሪ ድጋፍ በሚያስፈልግበት ሁኔታ በችግሩ የተጎዱ ቤተሰቦች በአደጋ መከላከል መርሃ ግብር
(Emergency response) ድጋፍ ይደረግላቸዋል፡፡

8. ጥሬ ገንዘብ በቅድሚያ- በተቻለ መጠን ጥሬ ገንዘብ ለተጠቃሚዎች ከሚተላለፉት ድጋፎች ቅድሚያ


የሚሰጠው ይሆናል፡፡ ይህም ገንዘብ በአካባቢው ገበያ ላይ የሚሰራጭ በመሆኑ ገበያውም ይነቃቃል፡
፡ ከምግብ ዕርዳታ ለመውጣትም ያስችላል፡፡ ሆኖም የምግብ እህል አቅርቦት እጥረት በአካባቢው
ገበያዎች ሲታይና የምግብ ዋጋ በጣም ሲጨምር የምግብ ዕርዳታ ይደረጋል፡፡ ይህም የመርሃ ግብሩነን
ተጠቃሚዎች ከምግብ ዕጥረትና ሀብታቸውን ለምግብ ግዥ ከማሟጠጥ ይጠብቃቸዋል፡፡

9. የፆታ እኩልነት፡- የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር የወንዶችና ሴቶችን ልዩ ፍላጎቶች፣ ጥቅሞችና
አቅምን ባገናዘበ ሁኔታ ከመርሃ ግብሩ በዕኩልነት መጠቀማቸውን ለማረጋገጥ ተዘጋጅቷል፡፡ ይህም
የሚደረገው የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር ተጠቃሚ ወንዶችና ሴቶች በሚመለከታቸው ጉዳዮች
ላይ ውሳኔ ሰጪነት በመሳተፍ እና ሴቶችም በምርትና በፆታ ሃላፊነታቸው በሚመለከታቸው ስራዎች
ላይ ትኩረትን በማድረግ በተለየ ሁኔታ ሴቶች የቤተሰብ አስተዳዳሪ በሆኑበት ደግሞ የተለየ ድጋፍን
በማድረግ ነው፡፡

5
2.4. መርሃ ግብሩ በተፈጥሮ አካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንዳያስከትል የሚደረጉ
ጥንቃቄዎች
የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር በተፈጥሮ አካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንዳያስከትል
ሆኖ ተዘጋጅቷል፡፡ መደረግ የሚገባቸውም ጥንቃቄዎች በየመርሃ ግብሮቹ ዓይነት እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

የመርሃ ግብሩ አይነት ጥንቃቄ

አጠቃላይ -የመብትና ሃላፊነት ደንቦች


-ለቅሬታ የሚደረግ የካሳ ክፍያ ደንቦች አሰራር
-ማህበራዊ ተጠያቂነት

የመርሃ ግብሩ አጀማመርና አወጣጥ - የተጠቃሚዎች ዝርዝር ለህዝብ ዕይታ ይለጠፋል


- ለቅሬታዎች የካሳ ክፍያ ጥያቄ ማቅረብ
- ከመርሃ ግብሩ ለመመረቅ አንድ ዓመት የእፎይታ
ጊዜ መስጠት

የህዝብ ስራዎች - የአካባቢያዊና ማህበራዊ አያያዝ ማዕቀፍ


- በየልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር በህዝብ
የሚሰሩ ስራዎች ዕቅድ በቀበሌ ደረጃ ተሰርቶ በወረዳ የምግብ
ዋስትና ግብረ ሃይል ይፀድቃል
መተዳደሪያዎች - የአካባቢያዊና ማህበራዊ አያያዝ ማዕቀፍ
- ለቅሬታ የካሳ ክፍያ

ክፍያዎች - የተጠቃሚነት ካርድና የቀን ውሎ መቆጣጠሪያና


መክፈያ ቅፅ
- ለቅሬታ የካሳ ክፍያ

የሃብት አስተዳደር - የኦዲት ስራ

6
2.5 የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር የዕቅድ አሰራር ሂደት

የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀ ግብር የዕቅድ አሰራር ሂደት በተለያየ ደረጃ የሚካሄድ ሲሆን ከታች ወደላይና
ከላይ ወደታች የሚካሄዱ ዓመታዊ የሴፍቲ ኔት ዕቅዶችን ያዘጋጃል።

ፌዴራል፡ ከክልሎች የተላከለትን እቅድ መርምሮ ግንቦት መጨረሻ


በየደረጃው ላይ በማጠናቀቅ ሰኔ ወር ማጠናቀቂያ ላይ ለወረዳዎችና ቀበሌዎች
የተመደበው በጀት ይደርሳል።
ለእቅዱ አሰራር
እንዲመች ከላይ ክልል (ዞን እንደ አስፈላጊነቱ)፡ ከወረዳዎች የተላከውን እቅድ መገምገምና
ካሉት አካላት ወደ ማፅደቅ በኤፕሪል ወር መጨረሻ፤ የክልሎች እቅድ ለፌደራል ደረጃ ሜይ 1
ታች ላሉት አካላት ቀን ይቀርባል። ።
ይተላለፋል።
ወረዳ፡ ከቀበሌዎች የተላከውን እቅድ እስከ ማርች መጨረሻ መገምገምና
ማፅደቅ በኤፕሪል 1 የወረዳውን እቅድ ለዞን እና/ወይም ክልል ማቅረብ።

ቀበሌ፡እቅዱን አዘጋጅቶ ለቀበሌ መጋቢት አንድ ቀን ያቀርባል።

ማህበረሰብ፡ እቅዳቸውን አዘጋጅተው ለቀበሌ ያቀርባሉ።

የዕቅድ አሰራር ሂደቱም የሚከተሉትን ሂደቶች ያጠቃልላል፡-

1. በቀበሌው የልማት ሰራተኛ ድጋፍ የቀበሌው ማህበረሰብ የቀበሌውን እቅድ በማዘጋጀት ይጀመራል፡፡
የተዘጋጀውም እቅድ በቀበሌው ተገምግሞ ከፀደቀ በኋላ የመርሃ ግብር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከተመረጡት
ሰዎች ዝርዝር ጋር የቀበሌው የሴፍቲ ኔት እቅድ ይሆናል፡፡

2. የወረዳ ዓመታዊ የሴፍቲኔት ዕቅድ የቀበሌዎችን ዕቅድ በማጠቃለልና በወረዳዉ የሚያስፈልገዉን የስራ
ዕቅዶች ይጨምራል፡፡

3. የክልል ዓመታዊ የሴፍቲነት ዕቅድ የወረዳዎችን ዕቅድ አጠቃልሎና የክልሉን ሥራዎች ጨምሮ ይይዛል፡

4. የፌዴራል ዓምታዊ የሴፍቲኔት ዕቅድ በከፍተኛ ደረጃ የሚገኝ የዓመታዊ ዕቅድ አጠቃልሎ የያዘ
የመርሃ ግቡሩ ሠነድ ሲሆን በተከታይ የአመት በፌዴራል ደረጃ ሊሠጥ የሚገባችውን ስራዎች የያዘ
ነው፡፡
______________________
ዞኖች እቅዶችን የመገምገምና የማጠናቀር ሚና በሚጫወቱባቼው ክልሎች፥ ወረዳዎች እቅዳቸውን የሚሰጡት ለዞናቸው ይሆናል።
ዞኖችም እቅዱን አጠቃለው በተወሰነው የጊዜ ገደብ ውስጥ ለክልል ገቢ ማድረግ አለባቸው።
7
3. የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር ዝርዝር ፕሮግራሞች

የሥራ ውጤቶች ቁልፍ ተግባራት የፖሊሲ መነሾ


የሥራ ውጤት 1- የተመረጡ የተጠቃሚ ምርጫ (ለመግባትና ማጥፖ፣ የአስመፖ፣ አንለማአኢ፣
መሣሪያዎች ውጤታማ የሆነ ለመውጣት) ብስምፖ
የማህበራዊ ጥብቃና የአደጋ የመረጃ ልውውጥ ዘዴዎች አስመፖ
ስጋቶችን ለመከላከል ሥራ ላይ
ለህብረተሰብ ሥራ ተሳትፎ ሥራዎች አስመፖ፣ አንለማአኢ
ይውላሉ፡፡
የመረጃ ቋት አለቸው
የአንድ ጊዜ ምዝገባ ማጥፖ
የአንድ ጊዜ ምዝገባ አስመፖ
ዕቅድ፤ማስተባበር ፤ማስተዳደር የማጥፖ፣ አስመፖ፣ አንለማአኢ፣
ብስምፖ
የማህበራዊ ተጠያቂነትና ለተጎዱ የካሣ ማጥፖ
ክፍያ አሠራር
የአቅም ማሻሻል የማጥፖ፣ አስመፖ፣ አንለማአኢ፣
ብስምፖ
የሥራ ውጤት 2- ውንዶችና - በስራው ለሚሳተፉ ተጠቃሚዎች የአስመፖ
ሴቶች ተጠቃሚዎች ተስማሚ የ6 ወራት የጥቅም ድጋፍ (ጥሬ
የሆኑ ጥቅሞችን በጊዜውና ገንዘብና ምግብ በጊዜያዊነት ድጋፍ
በቅርበት ይቀበላሉ ለሚደረግላቸው የ6 ወር ፤እና በቋሚነት
ድጋፍ ለሚደርግላቸው ለ12 ወራቶች
ይደረግላቸዋል።
- የአደጋ ስጋቶችን ለመቀነስ የሚያስችሉ
ዘዴዎችን በመጠቀም አደጋዎች ሲገጥሙ
የሴፍቲነት ድጋፍን በማስፋት ድጋፍ
ማድረግ።
የሥራ ውጤት 3- ህብረተሰቡ - የህብረተስቡን መተዳደሪያ፤ የአስመፖ፣ አንለማአኢ
ዘላቄታዊነት ባለው ሁኔታ ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለአየር
ንብረት ያፈራሉ፤ ማህበራዊ ንብረት ለውጥ የማይበገርና የሥርአተ
አገልግሎቶችም የተሻለ ምግብና የአስተሳሰብና ባህርይ ለውጥ
ይቀርቡለታል ፡፡ የሚያስፈልጉ ስራዎች ታቅደው
ይተገበራሉ።
- በህብረተስቡ የሚሠሩ ሥራዎች
የማህበረሰቡን የአስተሳሰብ ለውጥ፣
የገንዘብን አያያዝ ላይ መፃፍና ማንበብ
ይጨምራሉ።
- በሁኔታዎች ላይ የተመሠረተ ጊዜያዊ
የቀጥታ ድጋፍ ተጠቃሚዊች የጤናና
የሥርአተ ምግብን አገልግሎትን
ለመድረስ ይሠራሉ ፡፡

8
የሥራ ውጤት 4- የሥራ ውጤት 4- ተጠቃሚዎች የማጥፖ፣ የአስመፖ፣ አንለማአኢ፣
ተጠቃሚዎች በሦስት በሦስት የመተዳደሪያ መንገዶች ብስምፖ
የመተዳደሪያ መንገዶች ማለትም በስብልና እንስሳት ፤ከግብርና
ማለትም በስብልና እንስሳት ጋር ያልተያያዙ የገቢ ምንጮችና
፤ከግብርና ጋር ያልተያያዙ ከተቀጣሪነት/ደመወዝተኝነት ሊመነጩ
የገቢ ምንጮችና ከተቀጣሪነት/ ይችላሉ ፡፤
ደመወዝተኝነት ሊመነጩ
ይችላሉ ፡፤
የሥራ ውጤት 5- - የሰው ሃይል አስተዳደር የማጥፖ፣ የአስመፖ፣ አንለማአኢ፣
መርሃግብርሩን በአግባቡና - ተጠያቂነት ያለበት ብስምፖ
ውጤታማ ለማድረግ የመርሃግብሩ አስትዳደርና የተጠናከረ
የሚያስችሉ የሥራ አይነቶች የክትትል ግምገማ ሂደት በስራ ላይ
ይከናወናሉ። ይውላል
- ተጠያቂነት ያለበት የበጀትና
የገንዘብ አስተዳደር ይኖራል
- ተጠያቂነት ያለበት የምግብ
አያያዝ አስተዳደር ይተገበራል
- ተጠያቂነት ያለበት የንብረት
አስተዳደር ይተገበራል

9
4. ለውሳኔ ሰጪዎች ትኩረትን የሚሹ ጉዳዮች

4.1. የመረሃግብሩ አገባብና አወጣጥ፣ መሰረታዊ መመሪያዎች፣ ሀላፊነቶችና ግዴታዎች


በሁሉም ደረጃ የሚገኙ ውሳኔ ሰጪዎች መርሃ ግብሩን ለመጀመርና እና ለመጨረስ የሚከተሉትን መሰረታዊ
መመሪያዎች መከተል ይገባቸዋል፡፡

• ተሳትፏዊ ማድረግ፡- ህዝቡ የመርሃግብሩ ተጠቃሚዎችን በመምረጥና በማጽደቅ ሂደት ውስጥ ተሳታፊ
መሆን ይገባዋል፡፡

• ሚዛናዊነት፡- ቤተሰቦች ለተጠቃሚነት መመረጥ የሚገባቸው ለምርጫ በተቀመጠው መስፈርት እንጂ


በግል ግንኙንት ወይም ጥላቻ ምክንያት ሊመረጥ ወይም ሊወገድ አይገባም፡፡

• ግልጸኝነት፡- ማህበረሰቡ እና ቤተሰቦች ተጠቃሚዎች የሚመርጡበትን መመዘኛ እና እነማን


ለተጠቃሚነት እንደተመረጡ ማወቅ ይገባቸዋል፡፡ የተጠቃሚዎች ስም ዝርዝር በስብሰባ ላይ ስማቸው
እየተነበበ በትክክለኝነቱ ላይ ውይይት ሊደረግበት ይገባል፡፡ የተመረጡ ሰዎች ስም ዝርዝርም ማህበረሰቡ
እንዲያየው በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ መለጠፍ ይገባዋል፡፡

• ቅሬታዎችን የማቅረቢያ መንገዶች፡- ቤተሰቦች በመርሃግብሩ ለመታቀፍ ወይም ያልታቀፉበት ምክንያት


ለማወቅ ቅሬታዎችን ማቅረብ እንዲችሉ መፍቀድ ይኖርበታል፡፡

• በመረጃ ላይ የተመሰረተ ምረቃ፡- ቤተሰቦች ከመርሃግብሩ መመረቅ የሚገባቸው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ


ዝርዝር ጥናት ተደርጎ በመረጃ በተደገፈ እና ለመመረቅ አግባብነት ባለው መመዘኛ መሰረት ታይቶ
ሊሆን ይገባዋል፡፡ በምንም መልኩ የቤተሰቦች መርሃግብር ምረቃ በፖሊሲ አቅዋም ላይ የተመሰረተ
ሊሆን አይችልም፣ አይገባም፡፡ በክልል፣ በወረዳ እና በቀበሌ ደረጃ የሚገኙ ውሳኔ ሰጪዎች ስለመርሀ
ግብሩ አገባብ እና አወጣጥ ከዚህ የሚከተሉት የስራ ድርሻዎችና ሃላፊነቶች አሉባቸው።

• መርሃግብሩ በአዲስ ወረዳዎች እንዲተገበር ለማድረግ በቂ አቅም


መኖሩን ለማረጋገጥ መረጃ ይሰጣል ፡፡
የክልል ምግብ • መርሃግብሩ ወደሚሳተፍባቸው ወረዳዎች የስልጣንና አቅም ማሻሻል
ዋስትና ድጋፍ ይሰጣል፡፡
• ለተጠቃሚዎች የሚያገለግሉ ካርዶችን አሳትሞ ያሰራጫል

• ወደ መርሃግብሩ ሊጨመሩ የሚገባቸውን አዳዲስ ቀበሌዎቸን ይመርጣ


የወረዳ የምግብ የተጠቃሚዎች ቁጥር ለመጨመርም ይወስናል፡፡
ዋስትና • ለእያንዳንዱ ቀበሌ የተጠቃሚዎችን ቁጥር እንዴት መጨመር
እንደሚችል ይገመግማል፡፡
ግብረሃይል
• በወረዳው የተጠቃሚዎች ዝርዝር ላይ ውሳኔ ይሰጣል፡፡

10
የወረዳው የስራ እና
ማህበራዊ ጉዳይ የወረዳው የምግብ ዋስትና ግብረሃይል አባል ሆኖ አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡
ጽህፈት ቤት

የወረዳው የምግብ • የተጠቃሚዎች ካርድ ፎቶግራፎች እንዲያነሱ ፎቶአንሺ ይቀጥራል፡፡


ዋስትናው ዲስክ • የተጠቃሚዎችን ካርድ ለቀበሌዎች ያከፋፍላል፡፡

የመተዳደሪያ
ለምረቃ ጠቃሚ ዘዴዎችን በማዘጋጀት በየቀበሌው የተመራቂ ቤተሰቦች
አካባቢዎች አጥኚ
ቁጥር ላይ መግባባት ያደርጋል፡፡
ቡድን

• በተለያዩ ማህበረሰብ ውሥጥ በመርሃ ግብር መታቀ የሚገባቸውን


ተጠቃሚዎች መታቀ ተነጋግሮ ይወሰናል፡፡
የቀበሌ ምግብ ዋስትና • በማህበረሰብ የምግብ ዋስትና ግብረሃይል የቀረቡትን የተጠቃሚዎች
ግብረ ሃይል ብዛት ገምግሞ ይወስናል።
• የተጠቃሚዎች ካርድ ስርጭት ላይ ድጋፍ ያደርጋል፡፡

የመጣባበቂያ በጅትን አስመልክቶ የወረዳ ደረጃ ሥራዎችና ኃላፊነቶች


ለወረዳው ጠቅላላ በጅት (ለተጠቃሚዎች የሚተላለፈዉን፤የካፒታልና አስተዳደራዊ ወጪን ጨምሮ)
ወረዳዉ በልማታዊ ስራ ለሚሳተፉ ክፍያ ጠቅላላ ድምር 5% በማስላት የመጠባበቂያ በጀት ይጨምራል፡፡
የወረዳዉ የተለያዩ አካላት የስራ ድርሻና ሃላፊነቶች በመጠባበቂያ በጀት አጠቃቀም ከዚህ እንደሚከተለው
ይሆናል፡፡

• በወረዳና በፌዴራል ደረጃ ያለውን የመጠባበቂያ በጀት መጠን


ያስተያያል ፡፡
• ከቅድመ ማስጠንቄያና ምላሽ ዲስክ ሂደት ጋር በመመካከር ለወረዳው
የመጠባበቂያ በጀት ዝግጅት አስተዋጾኦ ያደርጋል።
• ከመጠባበቂያ በጀቱ ድጋፍ ሊደረግላቸው ለሚገባቸው ቤተሰቦች
የምግብ ዋስትናው
ምርጫ ላይ ድጋፍ ያደርጋል ፡፡
ዴስክ/ ሂደት • የሚመለከታቸው ጽ/ቤቶች የልማት ሥራዎችን ለማስፋፋት፤ በጤናና
የሥርአተ ምግብ ሥራዎችን ለማቀናጀት መሳተፋቸውን ያረጋግጣል።
• በክፍያ ሂደት ክፍያ ለሚገባችው ጅማሬውንና አፊጻጸሙን ይከታተል
• የመጠባበቂ በጅት አጠቃቀም ከአጠቃላይ የልማታዊ ሴፍቲ ኔት
መርሀግብር ጋር ረፖርት ያቀርባል።

11
• የወረዳውን የመጠባበቂያ በጀት ያቀርባል፡
የወረዳው • ከፌዴራል ደራጃ የተላከውን የመጠባበቂያ በጀት ያስተዳድራል
የፋይናንስ ድ/ቤት • የመክፍያ ቀጽ በማዘጋጀት ከመጠባበቂ በጀት ክፍያ ለሚገባቸው ክፍያ
ይፈፅማል።

• ለወረዳው የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀግብር በጀት እንዲደግፍ


የወረዳውን የመጠባበቂያ በጀት ያዘጋጃል፤ያሻሽላል
የቅድመ • በመጠባበቂያ በጀቱ የሚሰሩ ስራዎች ከሌሎች የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማስጠንቀቂያና ጋር በበቂ ሁኔታ መቀናጀታቸውን ያረጋግጣል
ምላሽ ዴስክ / • የመጠባበቂያ በጀቱ ከየልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀግብር ሃብቶች
ሂደት ጋር በቅንጅት እንዲስራ የምግብ ዋስትና ዴስክን /ሂደት እና
ለሚመለከታቸው ለቀበሌዎች ድጋፍ ያደርጋል
• በምግብ መልክ የሚቀርብን የመጠባበቂያ በጅት ያስተዳድራል ፡፡

• ለተጨማሪ ምግብ ዕደል (targeted supplementary feeding)


ምልመላ በሚደረገበት ወቅት የተመረጡት የህፃናት ተንከባካቢዎች
በሴፍቲነት መርሃ ግብር ስለመታቀፍቸውና አለመታቀፍቸው በመጠየቅ
የወረዳ ጤና መልሳቸውን ይሞላል
ፅ/ቤት • ለተጨማሪ ምግብ ዕድል (targeted supplementary feeding) ልጆች
ያላቸውን ቤተሰቦች እንዲሁም በልሴመግ የታቀፉ ወይም ያልታቀፉ
መሆናቸውን በማካተት ዝርዝራቸውን ለምግብ ዋስትና ዴስክ ይሰጣል ፡፡
• እንደ አስፍላጊነቱ የአደጋ መከላከል ሥራዎችን ይሠራል፡፡

• በመንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በሚድገፉ ወረዳዎች


• በሚያስፍልገው መጠን የመጠባበቂያ በጅት ያቀርባል
• ለቅድ ማስንቁቂያ ስራዎችና የመጠባበቂያ ስራዎችና የመጠባበቂያ በጅት
መያድ ያቀርባል
• ለቅድመ ማስጠንቁቂያ ስራዎች የመጠባበቂያ በጅት ዝግጅት ስራዎች
እንደ አስፈላጊነት የቴክንክ ድጋፍ ይሠጣሉ፡፡
• ለአደጋዎች የስብአዊ ድጋፍ ስራዎች ላይ ያስተባብራሉ ፡፡

12
የቅድመ ማስጠንቀቂያና ምላሽ ዳይሬክቶሬት ድንገተኛ አድጋዎችን ለማስወገድ የሚያስችሉ የዕቅድ ስልቶችን
በእያንዳንዱ የስራው ወረዳዎች ለመስራት እንዲቻል አዘጋጅቷል፡፡ እነዚህ የድንገተኛ ዕቅዶች ስጋቶችን
ለማስወገድ ከሴፍቲነት ስራዎች ጋር ተጣጥመው እንዲሰሩ ይከለሳል፡፡ ይህ ሲደረግ ዕቅዶች የሚከተሉትን
ጉዳዮች ማካተት ይኖርባቸዋል፡፡

• እንዴት እና በምን ሁኔታ በህዝብ የሚሠሩ ሥራዎች ተስፋፍተው መሰራት እንደሚገባቸው


• በህዝብ ብዛት ሊሰሩ የተወስኑ ሥራዎች እንዴትና በፍጥነት ተስፋፍተው መሠራት እንደሚገባቸው
• በምን ሁኔታ የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀግብር ክፍያዎች በጉልበት ሥራ ለማይሳተፉ ሰዎች መሰጠት
እንደሚችሉ
• የአከፍፈል አተገባበር ሂደትን።

4.2. የክፍያ አፍጻጸም መሠረታዊ መመሪያዎች

የክፍያ አፈጻጸም መሠረታዊ መመሪያዎች ዝርዝር ከዚህ እንደሚከተለው ቀርበዋል

• ጥሬ ገንዘብ ክፍያ የመጀመሪያ አማራጭ ነው፡- በተቻለ መጠን ጥሬ ገንዘብ ክፍያ የመጀመሪያ
አማራጭ መሆን አለበት፡፡ የምግብ ክፍያ የሚደረገው በአካባቢውና በጊዜው የምግብ ሰብል በገበያ
በማይኖርበትና የገበያ ዋጋው በጣም ከፍተኛ በሚሆንበት ሁኔታ ነው፡፡ ይህም አሠራር የተጠቃሚዎችን
ምግብ እጥረትና ሃብታቸው እንዳይሸረሸር ይረዳል።
• የክፍያ ቀደምትነት፡- ክፍያዎች ለጉልበት ስራ የሚደረገውን ጨምሮ በምንም ምክንያት ሊዘገይ
አይገባም፡፡ ተጠቃሚዎች ሊቀበሉት የሚገባችው ክፍያ በቴክኒካዊም ሆነ አስተዳደራዊ ጉዳዩች
ሊዘገይባቸው አይገባም። በተጨማሪም ምን ክፍያና መቼ እንደሚቀርብለቸው የማወቅ መብት
አላቸው፡፡
• የቀጥተኛ ተከፋዮች የክፍያ ጊዜ ፡- በቋሚነት የነፃ ክፍያ ተጠቃሚዎች ከ 2009 በጀት ዓመት የመጀመሪያ
ወር ጀምሮ የተፈቀደላቸውን ክፍያ በየዓመቱ ለ12 ወራት ይቀበላሉ።
• በልማት ሥራ ላይ ለሚሣተፉ የክፍያ ጊዜ፡- በሥራ ላይ ለሚሳተፉ የክፍያ ጊዜያአቸውን የሚወስኑት
የአካባቢው የዝናብ ወቅት፡ የግብርና ሥራ የሚበዛበት ወቅት፤ የምግብ እጥረት የሚኖርበትና ወዘተ
ናቸው፡፡ አለበለዚያ ወረዳዎችና ክልሎች የልማት ስራዎችና ክፍያዎች የሚፈፀሙበትን ጊዜ እንደ
አካባቢያቸው ሁኔታ ሊወስኑ ይችላሉ፡ በወረዳዎች ፍላጎት ላይ ተመስርቶ በህዝቡ የሚሠሩት ሥራዎች
የክፍያ ጊዜ በሚከተሉት መርሆዎች ላይ መመሥረት ይገባቸዋል።
o ለአተገባበር ቅለት እያንዳንዱ ክልል ከ2-3 ያልበለጡ የክፍያ ጊዜ ለወረዳዎች ማውጣት
አለበት፡፡
o የክፍያ ጊዜን መጠበቅ ቅድሚያ የሚሠጠው ነው፡፡ የክፍያ ጊዜው መቼም ቢሆን ክልሎችና
ወረዳዎች የጥሬ ገንዘብ ክፍያን በ20 ቀናት ውስጥ፣ የምግብ ክፍያን በ30 ቀናት ውስጥ
ማጠናቀቅ ይገባቸዋል። ይህም ማለት ሥራው በታህሣሥ ወር የሚጠናቀቅ ከሆነ ህዝቡን
ለጉልበት ሥራ በጥር ወር ለማሣተፍ ክፍያውን በታህሣሥ ወር አጥናቆ ከ20-30 ቀን ውስጥ
መጠናቀቅ አለበት ፡፡

• የጉልበት ሥራ የሚሠራባቸው ወራት የግድ በየወሩ መሆን የለበትም፡፡ የምዕራፍ 4 የጉልበት ሥራ


ለልማት እና ለክፍያ ጊዜ ከ2008 የዕቅድ ሥራ ላይ ተካትቶ ይሠራል፡፡ ሆኖም በሚገኙት ልምዶች
ላይ በመመሥረት እንዳ አስፍላጊነቱ ማሻሻል ይቻላል።

13
4.3 የግዢ ሥርዓቶችና መነሻ ተመኖች

የልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀግብር የግዢ ሠነድ እንደ ግዢው ዓይነትና መጠን ሊለያይ ይችላል ፡፡ስምምነት
የተደረገባችው የአገለግሎቶች፤ ሥራዎችና ማማከርን የማይጠይቁ አገልግሎቶች ከዚህ የሚከተሉት ናቸው

• ዓለም አቀፍ የጨረታ ውድድር


• በሃገር ውስጥ የሚደረግ የጨረታ ውድድር
• ግዢ/ ያለ ጨረታ
• የተወሰነ ዓለም አቀፍ ጨረታ
• በቀጥታ መዋዋል
• ከተመድ ግዢ
• የማህብረስብ ተሳትፎ

በዓለም አቀፍ የጨረታ ውድድር የሚከናወን የዕቃዎችና አገልግሎቶች ግዢ በፌዴራል መንግስት ደረጃ ብቻ
የሚካሔድ ሲሆን የግዢ ሥርዓቱም በዓለም ባንክ የግዢ ደንብ ይካሔዳል፡፡ በሌላ በኩል በሀገር ውስጥ
የሚደረግ ግዢ በዓለም ባንክ ተቀባይነት ባለው የግዥ ስርአት በፌዴራል መንግስት የግዢ ሥርዓት መሠረት
የሚከናወን ሲሆን በመርሀ ግብሩ የአፈጻጸም መመሪያ 14.5.6 ማየት ያስፈልጋል።

የሥራዎች፤ ንብረቶች እና የማማከር አገልግሎቶችን የማይጨምሩ ግዢዎች መነሻ ዋጋ በሚከተለው


ሰንጠረዥ ቀርቧል፡፡
የግዢ መጠን ግምት (በአሜሪካን ዶላር)
የግዢዎች ዓይነት የማማከር የጨረታ መጠቀሚያ
ሥራዎች ንብረቶች
አገልግሎቶች ደንቦች
ዓለም አቀፍ ጨረታ 10 ሚሊዮንና በላይ 1 ሚሊዮንና በላይ 1 ሚሊዮንና በላይ የዓለም ባንክየግዢ
መመሪያ
የቅድመ ግምገማ
7 ሚሊዩንና በላይ 1 ሚሊዩንና በላይ 1 ሚሊዩንና በላይ
መነሻ
ከ 2 መቶ ሺ የፌዴራል መንግስት
እስከ 10 ሚሊዩን ከ 100,000- ከ 100,000- የግዢ መመሪያ
በሀገር ውስጥ ግዢ
(የቅድመ ግምገማ 7 1,000,000 1,000,000 ከተወስኑ ገደቦች
ሚሊዩን በላይ በስተቀር
ከ 100,000
ግዢ (ያለ ጨረታ) ከ 200,000 በታች ከ 100,000 በታች የመሽጫ ዋጋ በመጠየቅ
በታች
የተወሰነ ዓለም አቀፍ አግልገሎቱን ወይም ዕቃውን ሊያቀርቡ የሚችሉት የታወቁና ብዛታቸው አነስተኛ
ጨረታ በሚሆንበት ወቅት ነው።
ዋጋው ከ $ 5000 ያነሰ ከሆነ በውስጥ የመንግስት መ/ቤቶች ግምገማ ሲሆን ከ $ 5000
በቀጥታ መዋዋል
በላይ ከሆነ በቅድሚያ በአለም ባንክ መገምገም ይኖርበታል፡፡
በህዝብ ተሳትፎ
ግዢው የሚፈፀመው በማህበርሰቡ ተሳትፎ ይሆናል፡፡
ግዢ

14
V. የውሣኔ ሠጪዎች ዋና ዋና ሥራዎችና ኃላፊነቶች
በክልልና በወረዳ መንግስታዊ እንዲሁም መያድ ውሣኔ ሠጪዎች በልማታዊ ሴፍቲ ኔት መርሀግብር የየእለት
ሥራዎች ውስጥ ወሳኝ ሚና አላቸው፡፡ የአደጋ ስጋትን ለመከላከል፣ የገንዘብ አያያዝ፣ የምግብ አያያዝና
የሌሎች ሐብቶች አስተዳደር ላይ ዋነኛ የሆኑ ውሣኔዎችን ይሠጣሉ ፡፡

5.1. በበጀት አስተዳደር

ከዚህ የሚከተሉት የወረዳ፣ የክልልና የመያድ ውሣኔ ሠጪዎች በበጀት አስተዳደር ላይ ያላቸውን ዋና ዋና
ሥራዎችና ኃላፊነቶች ናቸው፡፡
በክልል ደረጃ፡-
• አግባብ ያለው የሂሣብ አያያዝ ሥርዓት በክልልና በወረዳ ደረጃ
መቋቋማቸውን ያረጋግጣል ፡፡
• ለወረዳ የኢኮኖሚና ፍይናንስ ጽ/ቤቶች፣ ለክልል ግብርና፣ ለክልል
ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ፤ለማህበራት ማደራጃ ቢሮ፣ ለክልል
ጥቃቀንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ማስፋፊያ እንደ አስፍላጊነቱ ገንዘብ
ያስተላልፍላቸዋል ፡፡
• ከወረዳዎች ከግብርና ቢሮና ከሠራተኛና ማህበራዊ ቢሮ የሚሰበሰቡ
የፋይናንስና የበጀት ሠነዶችንና መረጃዎችን ያደራጃል።
• የወረዳዎችን የሂሣብ አያያዝ በመገመገም አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍና
ኢኮኖሚ ዕርዳታ ያደርጋል ፡፡
ትብብር • የሩብ እና ዓመታዊ የፍይናንስ ሪፖርት ያዘጋጃል
• ለስራ እንዲጠቁሙበት የተላለፈላቸውን በጀት በኃላፊነት ያስተዳድራል፡፡

በወረዳ ደረጃ
• ለሴፍቲኔት የተመደበላቸው በጀት በጊዜው መረከባቸውን ያረጋግጣሉ፡፡
• ለዓመቱ የተመደበውን በጀት ያቀርባል።
• ለተጥቃሚ ቤተሰቦች ወቅቱን ጠብቆ ክፍያ ይፈፅማል ፡፡
• አስፈላጊውን የበጀት አጠቃቀም ለክልል የፋይናንስ ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ
የወርና የሩብ አመት ሪፖርት ያቀርባል።

15
በክልል ደረጃ
• የክልሉን የሥራ ዕቅድና በጀት ያደራጃል
• ከክልሉ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ የሚተላለፍለትን የሥራ
ማስኬጃ በጀት የግብርና ቢሮን ወክሎ ያስተዳደራል ፡፡
• በክልል ደረጃ የሚገኙትን የመርሃ ግብሩ ፈፃሚዎችና ተቆጣጣሪዎች
የምግብ ዋስትና ለአስተዳደራዊ ና ካፒታል ወጪዎች የሚመደበውን ለመወሰን ስብስባ
ይጠራል ፡፡
ማስተባበሪያ
ዳይሬክቶሬት በወረዳ ደረጃ
• የወርዳ የሥራ ዕቅድና በጀት ያደራጃል
• የወረዳውን የመርሃ ግብሩን ፈፃሚዎችና ተቆጣጣሪዎች በመሰብሰብ
ለአስተዳደራዊና ካፒታል ወጪዎች የሚመደበውን በጀት ያስወስናል ፡፡
• የተጠቃሚዎችን የስም መቆጣጥሪያና ክፍያ መክፍያ ዝርዝር በማዘጋጀት
ለተጠቃሚዎች ክፍያ በወቅቱ እንዲከፈል ያደርጋል።

የክልሉ
• ከፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ የሚተላለፍለትን በጀት
የሰራተኛና ያስተዳድራል፡፡
ማህበራዊ ጉዳይ የወረዳ
• ለሚተላላፍበት በጀት ኃላፊነት ይወስዳል ፡፡

በክልል ደረጃ
• በህዝብ ሥራ ተሳትፎ ክፍሉ አማካይነት ከክልል የምግብ ዋስትና
የተፈጥሮ ሃብት የተላለፈለትን ማንኛውንም አይነት የሃብት አጠቃቀም ሁኔታ ሪፖርት
አጠቃቀም ያደርጋል
ዳይሬክቶሬት በወረዳ ደረጃ
• ለህዝብ ስራ ተሳትፎ የሚተላለፍለትን የካፒታል በጀት እያስተዳደረ
ለተገቢው ስራ መመደቡንና ሥራ ላይ መዋሉን ይከታተላል።

በክልል ደረጃ
• አመታዊ የአተገባበር እና ባጀት እቅድን አጠናቅሮ ለክልሉ ያቀርባል፡
• በክልሉ ፋይናንስ እና ኢኮኖሚ የሚተላለፍለትን ባጀት ያስተዳድራል፡፡
• የአስተዳደር እና ካፒታል ወጪ በተመለከተ ሰብሰባዎችን በመምራት
የምግብ ዋስትና ለሚመለከታቸው የትግበራ እና ተቆጣጣሪ አካላት እንዲመደብ
ማሰተባበሪያ ያስተባብራል
ዴስክ
በወረዳ ደረጃ
• ለህዝብ መተዳደሪያ ማሻሻያና አቅም ግንባታ የሚተላለፍለትን በጀት
እያስተዳደረ ለተጠቃሚዎች በአግባቡ መመደቡንና ለተለያዩ የሥራ
ክፍሎች መተላለፉን ያረጋግጣል ፡፡

16
• የሚያስፈልግውን ሃብት ያቀርባሉ።
መንግስታዊ • በመርሃ ግቡሩ የማስፈፀሚያ መመሪያ (Program Implementation
ያልሆኑ ድርጅቶች Manual) መሰረት የስራ ዕቅድና በጀት ያዘጋጀሉ፡፡
• ለሀብቱ ሃላፊነት እየወሰዱ ሪፖርት ይቀርባሉ።

17
አስተዳደራዊ በጀት፡- የአስተዳደራዊ በጀት ለሰዉ ሃይል፤ ለጥቃቅን የፅ/ቤት ዕቃዎችና መሳሪያዎች፤
ለጉዞና አበል፤ ለስልጠና፤ ለክትትልና ግምገማ፤ እና ሌሎች ወጪዎች (ከአስቸካይ ጊዜ ዕርዳታ ጋር የተያያዙ)
የሚይዝ ሲሆን የተጠቃሚዎች መተዳደሪያ ለማሻሻል የሚወጡ ወጪዎችን አያጠቃልልም። የወረዳው
የምግብ ዋስትና ግብር ሃይል ለፈፃሚ ጽ/ቤቶች ለአስተዳደራዊ ወጪዎች የሚስፈልገውን በጀት እየመደበ
ያፀድቃል ፡፡

በህዝቡ ላይ የባህርይ ለውጥ ለማምጣት የሚያስፈለገውን በጀት በጤና ጽ/ቤቶች በጀት የሚሽፈን ሲሆን
ለክትትልና ግምገማና ለአነስተኛ የማሣተሚያና ማባዥያ አገልገሎት የሚያስፈልጉ ወጪዎች ከልማመዊ
ሴፍቲኔት መርሀግብር የአስተዳደራዊ በጀት ሊሸፈን ይችላል፡፡ የቀበሌ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ለማቋቋምና
ሥራውን ለማከናውን የሚያስፈልጉ ወጪዎች በሁሉም የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር ተጠቃሚ ወረዳዎች
በወረዳው የአስተዳደራዊ በጀት ይሸፈናል፡፡

5.2 የልሴኔመ የምግብ አስተዳደር

ከዚህ የሚከተሉት የወረዳ፣ የክልልና የመያድ ውሣኔ ሠጪዎች በበጀት አስተዳደር ላይ ያላቸውን ዋና ዋና
ሥራዎችና ኃላፊነቶች ናቸው፡፡
በክልል ደረጃ
• ለምግብና ገንዘብ ክፍፍል ለውጥ እንዲደረግ ሲጠየቅ ያረጋግጣል
• የወረዳዎች የሩብ ዓመት የምግብ አጠቃቀም ሪፖርት ያጠናቅራል ፡፡
• በምግብ ላይ የተደረጉ የኦዲት ሥራ ግኝቶች በጊዜው መፍትሔ
የምግብ ዋስትና ማግኘታቸውን ይከታተላል፡፡
ማስተባበሪያ በወረዳ ደረጃ
ዳይሬክቶሬት • የምግብ እንቅስቃሴ መረጃዎችን በበቂ ሁኔታ ይይዛል
• የወርና የሩብ ዓመት የምግብ አጠቃቀም ሪፖርቶች ያዘጋጃል ፡፡
• በወረዳዎች የምግብ ሃብት አያያዝን ይከታተላል
• ለቅድመ ማስጠንቃቂያና እርዳታ ዴስክ አስፈላጊ መረጃዎችን ይሠጣል፡

በክልል ደረጃ
• የምግብ እንቅስቃሴን ይከታተላል
• በየወሩ ከወረዳዎች ሪፖርት እየተቀበለ በማቀናበር ለፌዴራል ደረጃ
ይልካል፡
• በመጋዘን ውስጥ ያለ አያያዝን ጨምሮ አስፈላጊ መመሪያ በአግባቡ
የምግብ መተግበራቸውን ይከታተላል፡፡
አስተዳደር • የአዲት ግኝቶችን እየተከታተለ አስፈላጊ የእርምት እርምጃዎች በክልል
ክፍል ውስጥ እንዲወስዱ ያደርጋል።
በወረዳ ደረጃ
• ምግብ ለወረዳው ይላካል በተባለው መሠረት መድረሱን ያረጋግጣል
• ምግብ በአግባቡ መከማቸቱንና መያዙን ያርጋግጣል
• የምግብ ጉድለት ከተገኘ ለሚመለከተው ኃላፊ ያሳውቃል፡፡
• ወርሃዊ የምግብ አጠቃቀምን ሪፖርት እያዘጋጀ ያቀርባል።
18
• በሱማሌ ክልል የሚሠሩትን የቤተሰብ ሀብት መጠሪያ ኮሚቴዎችን
(Hubs & Spokes) በአጋዥ ሊቀመንበርነት ይመራል
• ከምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት (ምዋማዳ) ወደ ምግብ
የዓለም ማድረሻ ጣቢያዎች እንዲደርስ ከአጓጓዦች ጋር ስምምነት ይፈፅማል
• ምግብ በማከፋፈያ ጣቢያዎች መድርሱን ያረጋጣል።
የምግብ • ምግብ በአግባቡ መከማቸቱንና መያዙን በቅርበት ይከታተላል
ፕሮግራም • በየአካባቢው የሚገኙ ሠራተኞችን በምግብ እህል አያያዝ ላይ የአቅም
ግንባታ ያደርጋል፡፡
• ምግብ በአግባብ ባለው መንገድ መድረሱን ወደሚገባው ሥፍራ ሁሉ
መሠራጨቱን ይከታተላል፡፡

• ምግብን በጊዜው በመግዛት በሃገር ውስጥ ደርሶ መሠራጨት በሚገባው


ስፍራ ላይ መድረሱን ያረጋግጣሉ ፡፡
• ምግብ ስርጭት ቦታዎች እንዲደርሱ የስርጭት ዕቅድ ያዘጋጀሉ ፡፡
• ምግብ ወደማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲደርስ ያሠራጫሉ፡፡
መያድ • ምግብ በአገባቡ መከማቸቱን መያዙን ያረጋጣሉ።
• የባከነ ምግብ ቢኖር በአሜረካ የልማት ተራዶኦ/USAD/ ደንብ ቁጥር 11
መሠረት ይፈፅማሉ፡፡
• በምግብ አጠቃቀም ላይ ሪፖርት እያዘጋጁ ያቀርባሉ፡፡

19
5.3 በልሴኔመ የቁሳዊ ሐብት አያያዝ

የቁሳዊ ሐብት አያያዝ በአጠቃላይ የተሸከርካሪና ሞተር ብስክሌቶች፤ ህንፃዎችና መሣሪዎች እንዲሁም
የአሽከርካሪዎች የትራፊክ ጥንቃቄን ያጠቃልላል ፡፡

የቁሳዊ ሐብት አያያዝ በአግባቡ ለማከናውን የኢትዩጵያ መንግስት ፖሊሲዎችና መመሪያዎች እንደ የመንግስት
ቋሚ ንብረት አያያዝ መመሪያ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተሸከርካሪ አያያዝ አጠቃቀም መመሪያ
የኢትዮጵያ ትራንስፖርት ባለስልጣንና የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር አተገባበር መመሪያ (Programm
Implementation Manual) እየታዩ መጠበቅ ይኖርባቸዋል፡፡

በወረዳ የቁሳዊ ሐብት አስተዳደር የሚመለከታቸው ተቋማት የወረዳ አስተዳደርን፣ የወረዳ ግብርና ጽ/ቤትና
የምግብ ዋስትና ፤የወረዳ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት፤ የወረዳ ንግድና ትራንስፖርትና ኢንዱስትሪ ጽ/
ቤቶች ናቸው ፡፡

እያንዳንዱ የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር ፈፃሚ ተቋም የራሱን ቁሳዊ ሀብት የማስተዳደር ኃላፊነት
አለበት።

VI. በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር ማህበራዊ ተጠያቂነት

ማህበራዊ ተጠያቂነት ማለት ማህበረሰቡ በሚሳተፍባቸዉ የተለያዩ ሥራዎችና በሚሰጡ አገልግሎቶች


ሀሳቡን የሚገልፅበት፤ ለሚታዩ ዋና ዋና ችግሮች አስተያየትና መፍትሔ እየሰጠ ኃላፊነትን የሚወስድበትና
በዚህም ማህበራዊ ተቋማት የሚጠናከሩበት የአሠራር መንገድ ነዉ፡፡

ማህበራዊ ተጠያቂነት በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር 4 ዉስጥ በመርሃ ግብሩ አነዳደፍ ውስጥ የመርሃ
ግብሩ ተጠቃሚዎችና ሌሎች የማህበረሰቡ አባላት ሃሳባቸዉን በፕሮግራሙ አሠራር ላይ አስተያየት እየሰጡ
አፈፃፀሙ እንዲሻሻል ያደርጋሉ፡፡በተጨማሪም ተጠቃሚዎችና የማህበረሰቡ አባላት በመርሃ ግብሩ የአሰራር
መንገድና አፈፃፀም ላይ ቅሬታቸዉን እያቀረቡ መልስ እንዲያገኙበት የሚደረግበት አሰራር ነዉ፡፡

በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር 4 ማህበራዊ ተጠያቂነት ሰፋ ካለዉ ከኢትዮጵያ መንግስት የማህበራዊ


ተጠያቂነት መርሃ ግብር (ኢማተመ) ተያይዟል፡፡ ይህም ማህበራዊ ተጠያቂነት በሁሉም አይነት የወረዳ
ልማት ስራዎች ጋር እንዲቀናጅ አላስፈላጊ የሆኑ የአሰራር ድግግሞሽን ለማስወገድ ነዉ፡

የኢመተማ የኢትዮጵያን መንግስት ወክሎ በሚሠራ ነፃ በሆነ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር በሚመራ
የባለ ደርሻ አካላት ኮሚቴ ይመራል፡፡

ኢመተማ ከህዝቡ ጋር ጠንካራ ግንኙነት ካላቸዉ የማህበረዊ አገልግሎት ከሚሰጡ የማህበረሰብ ድርጅቶች
ጋር አገልግሎታቸዉን እንዲያሻሽሉ አጠናክሮ ይሰራል፡፡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የተለያዩ ስራዎችን
ለመስራት እንዲችሉና አገልግሎት ሰጪዎችን ለማሳተፍ የስራ ማስኬጃ የገንዘብ ድጋፍ ከአስተዳደር ድርጅቱ
መጠየቅ ይችላሉ፡፡ የሲቪል ማህበረሰቦች አመቺ ነው የሚሉትን ዘዴ መጠቀም ቢችሉም በአብዛኛዉ
በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር ለማህበራዊ ተጠቃሚነት መጠቀም ያለባቸዉ መሳሪያዎች የሚከተሉትን
ነው፡፡
20
• የማህበረሰብ የነጥብ መስጫ ካርድ (Community Score Card): ሁለቱንም የልማታዊ
ሴፍቲኔት መርሀግብር ተጠቃሚዎች የሚቀበሉትንና አገልግሎቱን አቅራቢዎች የሚሰጡትን
የአገልግሎት ጥራት ለመመዘን የሚያስችል አሰራር ነው። ምዘናው በሁለቱም አካላት ከተካሄደ
በኋላ አገልግሎት ተቀባዮችና አገልግሎት ሰጪዎች በስብሰባ ተገናኝተው ሁኔታዎች ለወደፊት
እንዲሻሻሉ ምክክር የሚያደርጉበት መድረክ መፍጠሪያ ነው።

• የዜጎች ሪፖርት ማቅረቢያ ካርድ፡ በአንድ ወረዳ ውስጥ አንድ አገልግሎት የሚጠቀሙ ሰዎች
የተሰጣቸውን አገልግሎት ጥራት ሁኔታ ለመግለጽ የሚጠቀሙበት መረጃ መሰብሰቢያ መንገድ
ነው። እንደ የማህበረሰብ የነጥብ መስጫ ካርድ ስህተቱ/ችግሩ ምን እንደሆነ የሚገለጽበት
አሰራር ሳይሆን የታዩ ችግሮች የሚፈቱበትን መንገድ ለመስማማት የሚያስችል አሰራር ነው።
ይህም አሰራር እያንዳነዱ ሰው የሚሰማውን ቅሬታ ለማቅረብ ሳይሆን የታዩ ግድፈቶችን
ማስተካከያ እርምጃ ለመውሰድ ትኩረት ይሰጣል።

VII. የልሴኔመ 4 ከቀደሙት ምዕራፎች ልዩ የሚያደርጉት ዋና ዋና ፈጠራዎች


የልሴኔመ 4 ከቀደሙት ምዕራፎችና ቀድሞ ከተገኙ ልምዶች በአብዛኛዉ ዉጤታማ የሆኑትን ፈጠራዎች
ወስዷል፡፡

1. ወደ ተቀናጀ የአገልግሎት አሰራር መሸጋገር፡- ይህ ምዕራፍ በጊዜ ከተገደቡ መርሃ ግብሮች ቀልጣፋና
ዉጤታማ ወደ ሆነ ማህበራዊ ጥበቃና የአደጋ ስጋት መከላከልን ወደ ማከናወን ተሸጋግሯል፡፡

2. የተጠቃሚዎች መተዳደሪያ ከ ልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር ጋር መቀናጀት፡- የሴፍቲኔት ስራዎችና


መተዳደሪያን ለማሻሻል የሚሰሩት በአንድ ላይ በሚመዘን መርሃግብር ተዋህዷል፡፡

3. የሚተላለፍላቸዉን የድጋፍ መጠን መጨመር፡- ለአንድ ሰዉ በወር የሚተላለፍለት የ 15 ኪ.ግ የብርዕ


እህሎችና 4 ኪ.ግ ጥራጥሬ ከፕሮቲንና የሃይል ይዘት ለተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት የሚረዳ ከመሆኑም
በላይ በፍጥነት ከጉዳት ለማገገምና በከፍተኛ የገበያ ዋጋዉ ሃብትን ከመሸርሸር ይከላከላል፡፡

4. የ 12 ወራት ድጋፍ በቋሚነት ድጋፍ ለሚደረግላቸዉ ተጠቃሚዎች፡- ሙሉ አካል ያለዉና በቋሚነት


ድጋፍ ሊሰጣቸዉ የሚችል ለሌላቸው ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ሰዎችን በቋሚነት በሚያስፈልጋቸዉ ሁሉ
መደገፍ፡፡

5. የተጠናከረና ተከታታይ የሆነ ለአደጋ ድጋፍ መስጠት፡- በአንድ ወቅት የሚሰጠዉን የአደጋ ጊዜ ድጋፍ
በማጠናከር በአካባቢ የተወሰነ ወይም ተስፋፍቶ የሚገኝን ወቅታዊ አደጋ ለመቋቋም በአንድ ስፍራ
ያልተማከለ ነገር ግን በየአካባቢዉ ዉሳኔ በመስጠት ድጋፍ መጀመር ማስቻሉ፡፡

6. በህዝብ የሚሰሩ ስራዎች እንደ አስፈላጊነቱ ተለዋዋጭ መሆናቸዉ፡- የሚሰሩት የማህበረሰብ ልማት
ስራዎች በየአካባቢዉ በተመሰረተ ፍላጎት የማህበራዊ ተቋማትን፤ የሥርአተ ምግብ ፤ የአየር ንብረት
ለመቋቋምና የአደጋ ስጋቶችን ለመከላከል መቻሉ፡፡

7. የተለየ ድጋፍ የሚፈልጉ ሁኔታዎች መብዛታቸዉ፡- የቀደመዉ መርሃ ግብር ማስፈፀሚያ መመሪያ
ለተወሰኑ ዓይነት የሙያ ስልጠናዎችና የባህርይ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ መልእክቶችን ያጠቃለለ
ነበር። በዚህ ምእራፍ ግን መመሪያው ለብዙ ዓይነት ሁኔታዎች ፈቅዷል፡፡
21
8. ሦስት ዓይነት የመተዳደሪያ ማሻሻያ መንገዶች ድጋፍ ያደርጋል፡- ሦስቱ የመተዳደሪያ መንገዶች ማለትም
የሰብልና የእንስሳት እርባታ፤ ከግብርና ጋር ያልተያያዙ የገቢ ምንጮችና በደመወዝ ተቀጣሪነት ናቸዉ፡
፡እያንዳንዱ የመተዳደሪያ መንገድም በተሻለ ቅንጅትና ተከታታይነት ያላቸዉ ድጋፎች ይሠጣሉ፡፡
በተጨማሪም ለችግር ተጋላጭነታቸዉ የከፋ ቤተሰቦች እና የብድር አገልግሎት አማራጭ የሌላቸው
የመተዳደሪያ ክፍያ ተጠቃሚ ይሆናሉ።

9. የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር (ሰማጉሚ) ደረጃ በደረጃ የቋሚ ድጋፍ የሚያገኙ ተጠቃሚዎችን
ሙሉ ሃላፊነት ይወስዳል፡- የአቅም ግንባታን ለማድረግ በተደረገዉ ዕቅድ፤ የሰማጉሚ ሚና አቅም
ግንባታ በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር ቀስ በቀስ በቋሚነት ተጠቃሚ የሆኑትን ተላልፈዉለት ወጥ
በሆነ የመርሃ ግብር አሰራር ይደግፋል፡፡

10. በፆታ እኩልነት ላይ የተጠናከረ ትኩረት ይደረጋል፡- የፆታ እኩልነት ከስምንቱ የልሴኔመ መሰረታዊ
መመሪያዎች አንዱ ቢሆኑም የሴቶችን ሙሉ ተሳትፎና ጥቅማቸዉን ሙሉ ለሙሉ አላስጠበቁም ነበር፡
፡ ስለዚህ የልሴኔመ በተቀናጀ መንገድ የሴቶችን የተለያዩ ፍላጎቶች ለሟሟላት በተለይም በሥርአተ
ምግብ፤ በቤተሰብ የንብረት አያያዝ፤ በማህረሰብ ዉስጥ ዉህደት፣ ዘለቄታዊና ትርጉም ያለዉ የፆታ
እኩልነትን በማምጣት ከሚገኙት የልማት ዉጤቶች እኩል ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ፡፡

11. የኢትዮጵያ መንግሰት ቀስ በቀስ የሚያደርገዉን የገንዘብ አስተዋጽኦ ይጨምራል፡- የኢትዮጵያ


መንግስት ለማህበራዊ ጥበቃ የሚያደርገዉን የገንዘብ ድጋፍ ለማጠናከር በሚያስችለዉ መልኩ
ለልሴኔመ 4 የገንዘብ አስተዋፆ እያደረገ በ 10 ዓመት ጊዜ ዉስጥ ሙሉ በሙሉ መርሃ ግብሩን በዓመታዊ
በጀት እነዲሸፈን ነው፡፡ የመንግስት ለመርሃ ግብሩ የሚስፈልገዉን ድጋፍ $500,000,000 (አምስት
መቶ ሚሊዮን ዶላር) እንደሚሆን ሲገመት $285 ሚሊዮን በጥሬ ገንዘብ ለመርሃ ግብሩ ማስፈፀሚያ
በሚሠራበት የገንዘብ ቋት ዉስጥ ያስቀምጣል፡፡

የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር 4 ፈጠራዎች አዳዲስ የክፍያ ዓይነቶች እንደ ኤሌክትሮኒክስና የካርድ
ክፍያን ዘዴ ይይዛል፡፡ በኤሌክትሮኒክ የሚከፈለዉ የክፍያ ዓይነት በሦስተኛ ወገን (ማይክሮ ፋይናንስ
ተቋማት ፤ተንቀሳቃሽ የገንዘብ ማስተላለፍያ) የመሳሰሉትን ያጠቃልላል፡፡ የማህበራዊ ተጠያቂነት አሰራርን
ማስተዋወቁም ተጨማሪ ፈጠራ ነዉ፡፡

የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር 4 ለብሔራዊ የሥርአተ ምግብ አሰራሮችን አሳይቷል፡፡ እነዚህም


• የከሡ ህፃናት የሚገኙባቸውና ለችግር የተጋለጡ ቤተሰቦች በበቂ ሁኔታ በሴፍቲ ኔት ሥራዎች
ዉስጥ መታቀፋቸዉን ያረጋግጣል፣
• ለምግብነት በሚቀርቡ ድጋፎች ዉስጥ የአልሚ ምግብነት ባህርያቸዉ የተሻሻለ ወይም ተመጣጣኝ
የገንዘብ ክፍያ
• የሥርአተ ምግብ ተኮር የሆኑ የማህበረሰብ የልማት ሥራዎችን ማስፋፋት፣
• የባህርይ ለዉጥ ለማምጣት በሚደረጉ ስብሰባዎች ወይም ሌላ አገልግሎት ለመቀበል በጤና
አጠባበቅ ባህርይ ለውጥ ለማምጣት ቀለል ያሉ ቅድመ ሁኔታዎች ማስተዋወቅ፣
• ለጤና አገልግሎት የሚደረግ ክፍያን በአንድ ዓይነት መዝገብ መጠቀም ናቸው።

22
VIII. በልሴኔመ 4 የተሻሉ ዉጤቶችን ለማምጣት መተግበር ያለባቸው ቁልፍ ተግባራት
የልሴኔመ 4 የታሰቡ ዉጤቶችን ለማምጣት እንዲችል በተሻሻሉ አሰራሮች ላይ ትኩረት ያደርጋል እነዚህም
የማስተባበር ዕቅድ የመርሃ ግብር ቅንጅቶችን መዘርጋት እና የአቅም ግንባታ ናቸዉ፡፡

8.1. የማስተባበር እቅድ

የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሀግብር አላማን ለማስፈፀም ማስተባበር አስፈላጊ ነዉ፡፡ ማስተባበር እኛ ልንሰራዉ
የሚገባዉ እንጂ በራሱ የሚመጣ አይደለም፡፡ ስለዚህ እንደማንኛዉም ስራ ልናቅደዉ ይገባል፡፡በወረዳ ደረጃ
የሚሰራ የማስተባብር እቅድ ቅደ ተከተል ከዚህ እንደሚከተለዉ ነዉ፡፡

ደረጃ አንድ፡- የወረዳ ምግብ ዋስትና ግብረሀይል (ወምዋግሀ) በወረዳ ደረጃ ለማስተባበር የሚያስፈልጉትን
ሁኔታዎችና ለማስተባብር ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚገባቸውን አሰራሮች ያዘጋጃል፡፡የስራዎችን አይነቶችና ቀኖች
እንደ ሌሎቹ ስራዎች በግልፅ ሊለያቸው ይገባል፡፡ለማስተባብር አስፈላጊዉን ጥንቃቄ የሚሹ ጉዳዮችም፣-

• ማህበራዊ አገልግሎቶች ለምሳሌ ፡-በማህበራዊ ሰራተኞች የሚሰሩ ስራዎችና ሌሎች የማህበራዊ ጥበቃ
ጅማሬዎች፣
• እንደ የጤና ኤክስቴንሽን መርሃ ግብር የመሳሰሉ የጤና አገልግሎቶች፣
• የሥርአተ ምግብ አገልግሎት እንደ በማህበረሰብ የሚሰሩ የሥርአተ ምግብ ስራዎችና ሌሎች የብሔራዊ
የሥርአተ ምግብ መርሃ ግበር ስራዎች
• የመተዳደርያና የኢኮኖሚ የማበልፀግ መርሃግብሮች ለምሳሌ ፡- የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ልማት
መርሃ ግብር፤ የግብርና እድገት እና የ መያድ መርሃ ግብሮች
• የመሬት አያያዝ መርሃ ግብር ለምሳሌ፡- ዘለቄታዊ የመሬት አያያዝ መርሃ ግብር
• ለአየር ለዉጥ መቋቋም የሚሰሩ ስራዎች ለምሳሌ ፡- ከአየሩ ንብረት ጋር የሚስማሙ ጅማሮዎች

ደረጃ ሁለት፡- የወምዋግሀ ያዘጋጀዉን የማስተባበርያ ስራዎች ለሁሉም የባለድርሻ አካላት አስተላልፎ
እነርሱም ሀላፊነታቸዉን ለመወጣት በአመታዊ ዕቅዳቸዉ ዉሰጥ ማስገባታቸዉን ያረጋግጣል፡፡

ደረጃ ሶስት፡- የወምዋግህ ያዘጋጃቸዉን ዝርዝር የሥራ ዕቅዶች በሚከተለዉ አመት ዉሰጥ በስራ ላይ
እንዲውሉ ያደርጋቸዋል፡፡

ደረጃ አራት፡- የወምዋግህ የማስተባበሩን ስራ ለመስራት የሚያስችለዉን በቂ ሀበት እንዳለዉ ያረጋግጣል፣


ተጨማሪ ሃብትም ከተገኘ የዓመቱን እቅድ ለማስፈፀም ይጠቀምበታል፡፡

ደረጃ አምስት፡- የወምዋግህ የማስተባበሪያ ዕቅዱን በወረዳዉ የሴፍቲ ኔት ዕቅድ ወስጥ አስገብቶ ለክልል
ያቀርባል፡፡

23
8.2. የመርሀ ግብሩ ቅንጅትና ተደጋጋፊነቶች

8.2.1. ለመተዳደርያ ከሚደረጉ ድጋፎች ጋር ያለ ቅንጅት፡

በልሴኔመ የማህበረሰብ ልማት ስራና ለመተዳደሪያ ድጋፍ የሚደረጉ ቅንጅቶችና ተደጋጋፊነቶች፣ ለመተዳደሪያ
የሚደረጉ ድጋፎች ከሌሎች የመተዳደሪያ ማሻሻያ ከሚደረጉ ስራዎች ጋር ያለው ቅንጅት ሌላው የልሴኔመ
ውጤታማ ተግባር ነው ፡፡ የልሴኔመ 4 ለሦስት የመተዳደርያ መንገዶች ማለትም የሰብልና የእንስሳት
፤ከግብርና ጋር ያልተያያዙ የገቢ ማግኛ ሥራዎች እና በደመወዝ ተቀጣሪነት ትኩረት ያለው ድጋፍ ያደርጋል፡
፡ የስብልና የእንስሳት እርባታ መተዳደሪያ ወይም ከግብርና ጋር ተያያዥነት ያለውን ሥራ የመረጡ የቤተስብ
አባለት ከዚህ የሚከተሉትን አገልግሎቶች ይቀበላሉ ፡፡

• የቴክኒክ ስልጠና
• የንግድና የግብይት ስልጠና
• የንግድ ስራ እቅድ አዘገጃጀት
• በግብይት ላይ ምክር

በተመሳስይ ሁኔታ በተቀጣሪነት የሚሳተፉት በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ (ሰማጉቢ)፤ በየክልል ጥቃቅንና
አነስተኛ ልማት ኢነተርፕራይዞች (ጥአልኢ) እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ማዕከላት አሰራር መሰረት ለቅጥር
የሚፈልጉ ኢንደስትሪዎችንና ሰፋፊ እርሻዎች ያላቸውን የስራ እድል ይለያሉ፡፡ በተቀጣሪነት ለመሳተፍ
የመረጡ ተጠቃሚዎች በአንድ ያገልግሎት መስጫ ማአከል ውስጥ ስማቸው ይመዘገባል፡፡ የቴክኒክና ሙያ
ስልጠና ማዕከላት ስራ በሚፈለግበት ሞያ ስልጠና ይሰጣሉ፡፡ መርሀግብሩ በተጨማሪም በስራ ላይ ላሉት
የሙያ ስልጠና ወይም የስራ ላይ ልምምድ በተወሰነ ደረጃ ልምድ ላላቸው ስልጣኞች የተሻላ ተቀጣሪነት እና
ለመቀጠር እድላቸውን ለማስፋትና በራስ መቀጠርን ሙከራ እንዲያደርጉ ያበረታታል፡፡

8.2.2. ከጤናና የሥርአተ ምግብ አገልግሎቶች ጋር የሚደረግ ቅንጅት

መርሀግብሩ ለጤናና ለሥርአተ ምግብ አገልግሎቶች በተላይም ለነፍስጡርና ለሚያጠቡ እናቶች ቅድመ
ወሊድ ጥንቃቄ ለሚያደርጉት ወደ ቀጥታ ድጋፍ ተጠቃሚነት ይሸጋገራሉ፡፡ የጉልበት ስራ ተጠቃሚዎችን
በየሥርአተ ምግብ የባህሪ ለውጥ ለማግኘት በሚደረጉ ስብሰባዎች ሲሳተፉ ለጉልበት ስራ የሚያገኙትን
ጥቅም ያገኛሉ።

8.3. ችግርን የመቋቋምን አቅም መገንባት

ከችግር የመቋቋም አቅም ግንባታ የልሴኔመ 4 የእቅዱ፤ የትግበራው ፤የክትትልና ሪፓርት ማእከል ነው፡፡
የልሴኔመ 4 የአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም
ቤተሰቦች አደጋዎችን ለመቋቋም እንዲችሉ የምግብ ዋስትናቸውንና አኗኗራቸውን በማሻሻል ነው፡፡
በተጨማሪም የካርበን ልቀትን በመቀነስና በሕዝብ ስራ ተሳትፎ የካርበን መጠን መመጠጥን በመጨመር
ነው። ለዚህም የሚያስፈልጉ ስራዎች፡

24
• ከአየር ንብረት ጋር ተስማሚ የሆኑትን አሰራሮችን በማልማትና በማላመድ፣
• የሚሰሩ የማህበረሰብ የልማት ስራዎችና የመተዳደሪያ ማሻሻያ ስራዎች ስለአየር ንብረት ለውጥ
ጥንቃቄ ማድረግና እና የካርበን ልቀት ዝቅተኛ እንዲሆን ልዩ ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል።
• የአየር ንብረት ለዉጥን ዉጤት አና የካርበን አመጣጠጥ ማመሳከርያ በመዉሰድ እና ክትትል
በማድረግ ከአየር ንብረት ተቋማት ለስራ ማስኬጃ የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ትኩረት ማድረግ፡፡

የልሴኔመ 4 ለድርቅ ድንገተኛ አደጋ ስጋቶችን ለመቋቋም ይረዳል፡፡በክፍለ አህጉር ደረጃ የምስራቅ አፍሪካ በይነ
መንግስታት ሕብረት የድርቅ አደጋ ዘለቄታዊ መቋቋምያ ጅማሮ (IGAD’s Drought Disaster Resileince
and Sustainability Initaitve) የኢኮኖሚ እድገትን ለማምጣት በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ ይህ አካል የክፍለ
አህጉርና ብሔራዊ የመርሃ ግብር ሰነዶች እና ተያያዥ መዋእለኑዋይ መርሃግብሮች አሉት። በኢትዮጵያም ይህ
ሰነድ በ 2012 (እ.ኤ.አ) በግብርና ሚኒስቴር መሪነት የምግብና የሥርአተ ምግብን ለማሻሻልና የአደጋ ስጋቶችን
የመቋቋም አቅምን ለመገንባት በተለይም ለድርቅ ተጠቂ በሆኑ ማህበረሰቦች አካባቢ ይሰራል፡፡ይህም ሰነድ
6 ዋና ዋና ስራዎችን ሲይዝ እነዚህም ፡- የተፈጥሮ ሀብት አያያዝ፤ የገበያ ቀረቤታና ንግድ፣ የመተዳደሪያ
ማሻሻያ ድጋፍ፣ የአርብቶ አደር የአደጋ ስጋቶችን መቀነስ፤ ምርምርና የእውቀት አጠቃቀም እንዲሁም የሰላም
ግንባታና እርቅን ማምጣት ናቸው፡፡ የልሴኔመ 4 ከብሄራዊ መርሀግብር ሰነድ ጋር ጠንካራ ትስስርና ኖሮት
በተደጋጋፊነት በሚሠሩ ሥራዎች ለድርቅ አደጋ ተጠቂ የሆኑትን ማህበረሰቦች ለመድረስ ይሰራል፡፡

8.4. የመረጃ አያያዝ ዘዴዎች

በዚህ ምዕራፍ ቀድመው የነበሩ በተጠያቂነትና የመጠባብቅያ በጀት አጠቃቀምና አጀማመር ላይ የነብሩትን
ጉድለቶች ለማሻሻል ይሰራል፡፡ ይህም ስራ የመጠባበቀያ በጀት አጠቃቀምን (ጥሬ ገንዘብና ምግብ) ቀላል
ለማድረግ፤ የመጠባበቀያ በጀት አጠቃቀም ከስልሴኔመ በጀት አጠቃቀም አንድ አይነት ሆኖ እንዲሰራ እና
ለድጋፍ አሰጣጥ የሚጠቅሙትን መሣሪያዎች አጠቃቀም አቅም ለመገንባት ያስፈልጋል፡፡

የልሴኔመ 4 የቅድመ ማስጠንቀቅያ መረጃ በኢትዮጵያ ዉስጥ በዋነኝነት ጥቅም ላይ ይውላል፡፡ በቅርብ
የተሰራው የአደጋ ስጋት መከላከያ ሰነድ ከቅድመ ማስጠንቀቅያና ምላሽ ዳይሬክቶሬት ሁሉን አቀፍ የሆነዉን
የተቀናጀ ማሕበረሰብ ጥበቃና የአደጋ ስጋቶችን መከላከያ ስርዐቶችን ለማደራጀት ይጠቅማል፡፡ የዚህም ሂደት
ውጤት ግልፅ የሆኑ መረጃዎችን ለመሰብሰብና ለመተንተን፣ የመጠባበቂያ በጀትን በተለያየ ደረጃ ለመጠቀም
ያስችላል፡፡ ይህን በመካሄድ ላይ ያለው የመንግስት የቅድመ ማስጠንቀቂያና የአደጋ ስጋቶችን መከታተያ ዘዴ
ነው፡፡ ይህም የሚያጠቃልለው፡-

• የቅድም ማስጠንቀቂያ መረጃ አሰባሰብ ስራዎችን የአደጋ መከላከል ስራዎች በተጠናከረ ሁኔታ እንዲሰራ
ድጋፍ ያደርጋል ፡፡ ለዚህም በወረዳና በክልል ደረጃዎች አቅምን ለመገንባት የሚያስፈልግ የገንዘብ
ድጋፍ ያደርጋል፣
• በወረዳና በክልል ደረጃ ለአደጋ ጊዜ የሚሰጡ ድጋፎችን አጀማመር እያደራጀ ስራ ላይ ማዋልን፣
• ወሳኝ የሆኑ ደረጃዎችነ ተንትኖ በወረዳና በክልል ደረጃ ውሳኔ ሰጪዎች የመተንተን አቅምን ይገነባል፡፡
ይህም አግባብ ያለው ውሳኔ በወቅቱ ለመወስን ያስችላል ፡፡

25
8.5. የአቅም ግንባታ ስልት

የልሴኔመ 4 የአጠቃላይ መርሀግብሩን ማጠናከሪያና ከአቅም ግንባታ ጋር የተስማማ እንዲሆን አቅምን


የመገንባት ስልት አደራጅቷል፡፡ በልሴኔመ 4 የ አቅም ግንባታ የስልት ግብ እጥፍ ናቸዉ፡፡

1. የልሴኔመ 4 አሰራር ለማጠናከር


2. የኢትዮጵያ መንግስት ተቋሟዊ አቅምን ለመገንባት
የመንግስት ሐገራዊ የልማት አቅጣጫ የልሴኔመ 4 በአራት ስልታዊ ዓላማዎች የተዋቀረ ነው፡፡ እነርሱም

1. የልሴኔመ 4ን ለመተግበር በቂ የሆነ የሰው ሃይልና ቁሳዊ ሃብት መኖሩን ማረጋገጥ፣


2. ለአጠቅላይ የልሴኔመ ትግበራ የሀገራዊ ልማትን አቅጣጫ በአግባቡ መጠቅም፣
3. መርሃ ግብሩን በአግባቡ ለመተግበር የተጓደሉ ቴክኒካዊ ጉዳዩችን ለማሟላት በፍላጎት ላይ
4. የተመሠረተ የልማት መርሀግብሮችን በማደራጀት መተግበር፣
5. የተሻሻለ የመርሃ ግብር አተገባበር ለማድረግ በቅንጅት መስራት
6. የመርሃ ግብሩ ማጠናቀቂያ ስልት በመንደፍ በመንግስት አሠራር ውስጥ የአቅም ግንባታን ተቋማዊ
ማድረግ

ዕቅዱ በኢትዮጵያ መንግስት የልሴኔመ ፈፃሚ ተቋማት የሚከናወን ሲሆን መንግስታዊ ባልሆኑ ፈፃሚ
አካላትና ለአቅም ግንባታ የሚያስፈልገዉን የገንዘብ ድጋፍ በሚያደርጉ አጋሮች ይከናወናል፡፡ የአቅም ግንባታን
የሚያደርጉ ማዕከላት የአቅም ግንባታ ስራ ብቻ ይሰራሉ እንጂ በልሴኔመ አተገባበር ዉስጥ ድርሻ የላቸዉም፡፡

26
28

You might also like