Professional Documents
Culture Documents
የአርሶ አደሩ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር በማድረግ ለምግብ ዋስትና መረጋገጥና ለሥራ
ዕድል ፈጠራ ምቹ መደላድል ለመፍጠር ይቻል ዘንድ ቀደም ሲል የተጀመሩትን የተፋሰስ ልማት
ሥራዎች ማስቀጠል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
ባለፉት ዓመታት የተከናወኑት የተፋሰስ ልማት ሥራዎች ከፍተኛ የሰው ጉልበትና የገንዘብ ወጪ
ተደርጐባቸው እንዲለሙ የተደረገ ቢሆንም ዘላቂነታቸውን ለማረጋገጥ የተፋሰሱ ተጠቃሚዎች
በባለቤትነት ስሜት ተረክበው የተፈጥሮ ሀብቶችን የሚያስተዳድሩበት የርክክብ፣ የአጠቃቀም፣
የአጠባበቅና የተጠያቂነት አሠራር ማስፈን ተገቢ ሆኖ በመገኘቱ፤
ክፍል አንድ
ጠቅላላ ድንጋጌዎች
፩/ አጭር ርዕስ
ይህ አዋጅ የማኅበረሰብ ተፋሰሶች፣ ልማት፣ አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር ፪ሺ፲፪ ዓ/ም
ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል።
1
፪/ ትርጓሜ
፪/ “ማኅበር” ማለት በጋራ ፍላጐት ተነሳስተው በዚህ አዋጅ መሠረት የተደራጁና የተመዘገቡ
የማህበረሰብ ተፋሰስ ተጠቃሚዎች በአባልነት የታቀፉበት አካል ነው።
፫/ “ሰው” ማለት የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ማለት ነው።
፱/ “የተፈጥሮ ኃብት ተቋም” ማለት ተፋሰሱ በሚገኝበት አካባቢ ወይም ወረዳ የተፈጥሮ
ኃብትን ለመንከባከብ፣ ለማልማትና አጠቃቀሙን ለመወሰን የተቋቋመ መንግሥታዊ
ተቋም ነው።
2
፲/ “ተሳትፎ” ማለት በውሳኔ ሊነኩ በሚችሉ ሃብቶች ላይ ባሕላዊ ወይም ሕጋዊ መብት
ያላቸው ሰዎች በውሳኔ ሰጪነት ሂደት ውስጥ የመሳተፍ መብት ማለት ነው።
፫/ የፆታ አገላለጽ
፬/ የተፈፃሚነት ወሰን
ክፍል ሁለት
ስለ ተፋሰስ ዕቅድና ልማት
፭/ የተፋሰስ ዓይነቶች
፮/ የማኅበረሰብ ተፋሰስ
3
፪/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፩ ሥር በተደነገገው መሠረት የማኅበረሰብ ተፋሰሱ ከ፭፻
ሄክታር በላይ በሚሆንበት ጊዜ ይህንኑ እንደ አመችነቱ ከፋፍሎ ማልማትና መንከባከብ
ይቻላል።
፯/ ዋና ተፋሰስ
፪/ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 9 ንዑስ አንቀጽ 3 መሰረት የማህበረሰብ ተፋሰስ የሚያለሙ አካላት
በቅድሚያ የማህበረሰብ ተፋሰስ ዕቅድ ማዘጋጀት አለባቸው፡፡
፫/ ማኅበር ከመቋቋሙ በፊት የተፋሰስ ዕቀድ የሚዘጋጅ ከሆነ በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፩ ንዑስ
አንቀጽ ፭ የተጠቀሰው ማኅበር መሥራች ኮሚቴ የተፋሰስ ተጠቃሚዎች ማኅበሩን
ከማደራጀት ጎን ለጎን በሚመለከተው የተፈጥሮ ሀብት ተቋም በመታገዝ ዕቅዱን ማዘጋጀት
አለበት።
4
፬/ በሚዘጋጀው ዕቅድ ውስጥ የሚካተቱ ተግባራት የአካባቢ መራቆትንና የተፈጥሮ ሀብት
መመናመንን ለመከላከል፣ የውኃ ሀብትን ለማጎልበትና የሙቀት አማቂ ጋዞችን ልቀት
በመቀነስ የመሬት የማምረት አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ መሆን አለባቸው።
፱/ አንድ የማህበረሰብ ተፋሰስ በካርታ የተደገፈ የተሟላ የረዥም ጊዜ ዕቅድ ሊኖረው ይገባል።
፲፪/ በማኅበሩ የተዘጋጀው ዕቅድ ከአንድ ወረዳ በላይ ወሰን ተሸጋሪ ከሆነ ዕቅዱ ጉዳዩ
ለሚመለከታቸው ወረዳዎች ሁሉ ቀርቦ በወረዳዎቹ የተፈጥሮ ሀብት ተቋማት ስምምነት
መጽደቅ አለበት፡፡ ዝርዝሩ በደንብ ይወሰናል፡፡
5
፱/ የማኅበረሰብ ተፋሰስ ልማት
፬/ የማኅበረሰብ ተፋሰስ ዕቅድ በተፈጥሮ ተፋሰስና በአስተዳደር ወሰን መካከል ልዩነት ባለው
ቦታ ላይ የሚያርፍ በሆነ ጊዜ ዕቅዱ የሚተገበረው የአስተዳደር ወሰንን በመከተል ይሆናል፡፡
6
፲/ የማህበረሰብ ተፋሰስ አልሚዎች ተፈጥሯዊ የግብርና ግብዓቶችን እንዲጠቀሙ
ይበረታታሉ።
ክፍል ሦስት
ስለማህበረሰብ ተፋሰስ ተጠቃሚዎች ማኅበር አመሠራረት
፬/ ማኅበሩ በማህበረሰብ ተፋሰሱ ስፋት ወይም ወሰን መሠረት መቋቋም አለበት። ሆኖም ግን
የማህበረሰብ ተፋሰሱና የአስተዳደር ወሰኖች የሚለያዩ ከሆነ ማኅበሩ የወረዳውን ወሰን
ተከትሎ መቋቋም አለበት፡፡ ዝርዝሩ በደንብ ይወሰናል፡፡
7
፱/ በዚህ አንቀጽ ንዑሰ አንቀጽ ፯ ለጠቅላላ ጉባዔው ቀርቦ የፀደቀው የተፋሰስ ተጠቃሚዎች
መመስረቻና መተዳደሪያ ደንቦች ፩ ቅጅ ተፋሰሱ ለታቀፈበት ቀበሌ/ዎች አስተዳደር ጽ/ቤት
እንዲያውቀው መላክ አለበት።
፲፩/ ከተፋሰሱ የሚገኙ የተፈጥሮ ሀብት ውጤቶች እንደ ሣር፣ ደን እና የደን ውጤቶች ወይም
መሰል የተፈጥሮ ሀብት ውጤቶች በዓይነትም ሆነ በገንዘብ ተሽጠው ከተገኘው ገንዘብ ላይ
ለአባላት የሚከፋፈልና ለተፋሰሱ ልማት ዓላማ በማኅበሩ ስም በሚከፈት የባንከ ሂሳብ
ተቀማጭ የሚሆነው የገንዘብ መጠን በማኅበሩ የውስጥ ደንብ ይወሰናል።
መ/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፩ የተደነገገው ቢኖርም በተፋሰስ ክልሉ ውስጥ የመሬት
ይዞታ ያላቸውና ዕድሜያቸው ከ፲፰ ዓመት በታች የሆኑ ሰዎች በአሳዳሪያቸው አማካኝነት
በአባልነት ሊመዘገቡ ይችላሉ።
8
፲፪/ ከዋና አባልነት ስለመሰናበት
9
፲፮/ የተፋሰስ ተጠቃሚዎች ማኅበር አባላት መብት
፮/ የተፋሰሱ ተጠቃሚ ሆነው ነገር ግን የማኅበሩ አባል ያልሆኑ ሰዎች በዚህ አንቀጽ ንዑስ
አንቀጽ ፬ እና ፭ የተደነገጉት መብቶች አይኖራቸውም።
፯/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፮ የተጠቀሱ ሰዎች በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፩ የተደነገገው
መብት በግል ይዞታቸው እና በማኅበረሰቡ ወይም በሕጋዊ አካል በተረጋገጠ የወል ይዞታ
ላይ ብቻ ተፈጻሚ ይሆናል።
በዚህ አዋጅ መሠረት የተፋሰስ ተጠቃሚዎች ማኅበር አባል የሆነ ማንኛውም ሰው የሚከተሉት
ዝርዝር ግዴታዎች ይኖሩበታል፡፡
10
፪/ በተፋሰሱ ክልል ያሉትን ተፈጥሯዊና በልማት የተገኙ ሀብቶች ከውድመት የመጠበቅና
የመከላከል፣
ማኅበሩ በዚህ አዋጅ የተሰጡትን መብትና ግዴታዎች ለመወጣት የሚከተሉት አካላት ይኖሩታል፡
ጠቅላላ ጉባዔው የማኅበሩ ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሲሆን የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባራት
ይኖሩታል፤
ሸ) በማኅበሩ ውስጠ ደንብ መሠረት ከተወሰነ ዋጋ በላይ ያላቸውን ወይም ለማኅበሩ ከፍተኛ
ዋጋ ያላቸውን ውሎች የማጽደቅ፤
፪/ የጠቅላላ ጉባዔው ምልዓተ ጉባዔ የሚሆነው ከማኅበሩ አባላት መካከል ከግማሽ በላይ
የሚሆኑት በስብሰባው ላይ ሲገኙ ይሆናል።
፩/ እያንዳንዱ ማኅበር ቁጥራቸው ከአምስት ያላነሰ ወይም ከአሥራ አንድ ያልበለጠ አባላት
ያሉት ሥራ አመራር ኮሚቴ ይኖረዋል።
12
፪/ የሥራ አመራር ኮሚቴው ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር፣ ፀሐፊ፣ ገንዘብ ያዥ፣
የተፋሰስ ልማት አስተባበሪ እንዲሁም ሌሎች አባላት ይኖሩታል።
፬/ የሥራ አመራር ኮሚቴው አባላት ምርጫ የሴቶችን ተሳትፎ ግምት ውስጥ ያስገባ ሆኖ
ቁጥራቸው ከአባላቱ ቢያንስ ፴ በመቶ መያዝ ይኖርበታል።
፯/ ከሥራ አመራር ኮሚቴው አባላት ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ከተገኙ ኮሚቴው
ስብስባዎችን ሊያካሂድ እና ውሣኔዎችን በድምጽ ብልጫ ሊያሣልፍ ይችላል።
፪/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፩ መሠረት የሚቋቋሙት ኮሚቴዎች ከዚህ በታች በተዘረዘሩት
ሳይወሰኑ የሚከተሉትን ያካትታሉ።
13
ለ) የቅሬታ አፈታት ኮሚቴ
ሐ) የቁጥጥር ኮሚቴ
ክፍል አራት
የተፋሰስ ጥበቃ፣ አስተዳደርና አጠቃቀም
ሠ) በተፋሰሱ ክልል ውስጥ የሚገኝ ባለይዞታ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (መ) የተጣለውን
ግዴታ ለመወጣት ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ያጋጠመው እንደሆነ ይህንኑ
ለሚመለከተው የተፈጥሮ ሃብት ተቋምና ለማህበሩ ማሳወቅ አለበት፡፡
15
፳፭/ ስለ እንጨት፣ እንጨት ያልሆኑ የደን ውጤቶች እና ሣር አጠቃቀም
፩/ በተፋሰሱ ክልል ውስጥ በግል ወይም በወል ይዞታዎች ላይ የመጠቀም መብት ያላቸው
ሰዎች በእነዚህ ይዞታዎች ላይ የለሙትን ወይም የተተከሉትን ደረቅ እንጨት፣ ዛፍ፣
ቁጥቋጦ፣ ሣር እና እንጨት ያልሆኑ የደን ውጤቶች የመጠቀም መብት አላቸው።
፪/ በተፋሰሱ ክልል ውስጥ በታቀፈና የወል ወይም የመንግሥት ይዞታ በሆነ ሥፍራ ላይ
የሚገኝ ድንጋይና አሸዋ ንብረትነቱ የማኅበሩ ሲሆን የማዕድን ሥራዎች አዋጅ
በሚፈቅደው መሠረት ድንጋይና አሸዋውን ለተፋሰሱ ልማት ሊጠቀሙበት ይችላሉ።
በማህበረሰብ ተፋሰስ ክልል ውስጥ የሚገኘውን የውሃ ሃብት አጠቃቀም የውሃ ሃብት አስተዳደር
አዋጅ በሚፈቅደው መሠረት ይሆናል::
16
፳፰/ ስለ ሥርዓተ ምሕዳር አገልግሎት ክፍያ
ከማኅበሩ አባላት ውጭ ተፋሰሱ በመልማቱ ምክንያት ተጠቃሚ የሆኑ አካላት ለተፋሰሱ ልማት
የሥርዓተ-ምህዳር አገልግሎት ክፍያ የመክፈል ግዴታ አለባቸው።
በመሠረተ ልማት ግንባታ ወይም በሌላ ምክንያት በማንኛውም ሁኔታ በተፋሰሱ ወይም በተፋሰስ
ተጠቃሚዎች ላይ ጉዳት ያደረሱ አካላት ላደረሱት ጉዳት ተመጣጣኝ ካሣ መክፈልና አካባቢውን
ተመጣጣኝ ወደ ሆነ ስነ-ምህዳር የመመለስ ግዴታ አለባቸው።
ክፍል አምስት
የተፋሰስ ማኅበረሰቡን የሚመለከቱ ሌሎች ጉዳዮች
፴/ የተጠናቀቁ የተፋሰስ ሥራዎች ርክክብ
፩/ ማንኛውም የግል ወይም የወል ባለይዞታ በራሱ፣ በኅብረተሰቡ፣ በማኅበሩ ወይም ሥራውን
አጠናቀው በሚያስረክቡ መንግሥታዊ ወይም መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች
የተከናወኑትን የተፋሰስ ልማት ሥራዎች ቆጥሮ መረከብ አለበት።
፴፩/ ስለማበረታቻ
17
፴፪/ ስለ ሥርዓተ-ፆታ እና ልዩ ትከረት የሚሹ የኅብረተሰብ ክፍሎች
የሚመለከተው የተፈጥሮ ሃበት ተቋም ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ሳይወሰን የሚከተሉት ተግባርና
ኃላፊነቶች አሉበት፡፡
18
ሐ/ የማህበረሰብ ተፋሰስ ማህበር አባላት የተጠቃሚዎች ቡድን በመመስረት ገቢ በሚያስገኙ
ስራዎች ላይ እነዲሰማሩ ይደግፋል፣ ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፡፡
ክፍል ስድስት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
፴፮/ ኃላፊነት
፪/ ቀደም ሲል በነበረው አሠራር የተቋቋመ የተፋሰስ ኮሚቴ የዚህን አዋጅ መውጣት ተከትሎ
በሚቋቋመው ማኅበር ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እስከሚተካ ድረስ ተቀባይነት ይኖረዋል።
19
ከዚህ አዋጅ ጋር የሚቃረን ማናቸውም አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ ወይም ልማዳዊ አሠራር በዚህ
አዋጅ ውስጥ በተሸፈኑ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚነት አይኖረውም።
ሳሕለወርቅ ዘውዴ
20