Professional Documents
Culture Documents
ስኬቶችና ተግዳሮቶች
ሐምሌ 2006
0
የህዳሴ ጉዞአችን የሚገኝበት ሁኔታ
መግቢያ
1
ርብርብ እያደረግን እንገኛለን። የኢንዱስትሪ ልማታችን በቀጣይነት በመገንባት የሀገራችን
ህዳሴ እውን ማድረግ የሚያስችሉን አበራታች ስኬቶች በማስመዝገብ ላይ ስንሆን በዘርፉ
ያሉት ማነቆዎችን ለመፍታት አቅጣጫዎች ተቀምጠው ርብርብ እየተደረገ ይገኛል ።
2
በሁሉም ዘርፎች ያስመዘገብናቸው ዘርፈ ብዙ ስኬቶች የሀገራችን ህዳሴ እውን ለማድረግ
እውነታኛ ማሳያዎቸ ቢሆኑም በየዘርፉ ያሉብን ተግዳሮቶች በቀጣይነት እየፈተሹ ወቅታዊ
ምላሽ የመስጠቱ ጉዳይም እንዲሁ ከፍተኛ ትኩረት የሚሻ ነው። በመሆኑም እዚህም
እዚያም የሚያጋጥሙን ተግዳሮቾት አንዳንዶቹ ፈጣኑ ልማታችን የወለዳቸው የልማት
ውጤቶች ስለሆኑ መፍትሔውም ልማታችን ማፋጠን ሲሆን ሌሎች ከኪራይ ሰብሳቢነት
አስተሳሰብ እና አመለካከት የሚመነጩት ደግሞ ልማታዊ ፖለቲካል ኢኮኖሚ በመገንባት
አቅጣጫ ለመፍታት ያለሰለሰ ጥረት ማድረግ ይኖርብናል።
3
ግብርናችን በከፍተኛ ፍጥነት ማደጉን ተያይዞታል። ለዘመናት ምርቱን ወደ ገበያ ማቅረብ
ቀርቶ ቤተሰቡን እንኳን በአግባቡ መመገብ ባለመቻሉ አብዛኛው ህዝባችን በአስከፊ
ድህነት ውስጥ ይማቅቅ የነበረበት የትላንት ታሪካችን በመሰረቱ እየተቀየረ መጥቶ በአሁኑ
ሰዓት በሚልዮኖች የሚቆጠር ሃብት መቋጠር የጀመሩ በርካታ አርሶና አርብቶ አደሮች
ማፍራት ችለናል። የግብርና ልማታችን ለህዳሴ ጉዟችን እያበረከተው ያለው አስተዋፆና
ያለበት ሁኔታ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
4
ሙያተኞችን በማሰልጠንም በየገጠር ቀበሌው በእንስሳት ሃብት ልማት፤ በሰብል ልማትና
በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማት ዘርፎች ሶስት ሙያተኞችን፣ መስኖ ባለበት አካባቢ
ደግሞ የመስኖ ልማት ሙያተኛ በመጨመር አርሶ አደሩን በተደራጀ ሁኔታ
የኤክስቴንሽን አገልግሎት ተጠቃሚ የማድረግ ስራ እየተሰራ ነው፡፡
5
ዝቅተኛ መሆንና ታካችነት እንዲሁም በአርሶ አደሩ የሚታይ የጠባቂነት ሁኔታ ለመቅረፍ
ቀጣይ ርብርብ የሚጠይቅ ይሆናል። የባለሙያዎች ድጋፍ በተመለከተም እንዲሁ ከጊዜ
ወደ ጊዜ እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም የአርሶ አደሩ ምርትና ምታማነት በቀጣይነት
ለማሳደግ የሚደረግ ደጋፍ በብዙ መልኩ መሻሻል ይገባዋል።
የግል ባለሃብቱ ለዘመናዊ ግብርና ዕድገትና ቀጣይነት ከአርሶ አደሩ ቀጥሎ የሚሰለፍ
ኃይል ነው። መንግስት የግል ባለሃብቱን ለመደገፍ ሁሉን አቀፍ ርብርብ እያደረገ ሲሆን
ባለሃብቱም የተፈጠረለትን ምቹ ሁኔታ ተጠቅሞ እንቅስቃሴ ማድረግ ጀምሯል።
በመንግስት በኩል በግብርና ኢንቨስትመንት መሰማራት ለሚፈልጉ ባለሃብቶች ሁለት
መሰረታዊ አማራጮች ተቀምጠዋል። አንደኛው አማራጭ የግል ባለሃብቱ በደጋማና
በከተሞች አካባቢ በአነስተኛ መሬት ላይ ሰፊ ጉልበት፣ ካፒታል እና ቴክኖሎጂ ተጠቅመው
የአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን በማምረት የተሻለ ገቢ ማግኘት ማስቻል ሲሆን
ሁለተኛው አማራጭ ደግሞ ሕዝብ ባልሰፈረባቸው በሀገሪቱ ቆላማ አካባቢዎች በሚገኙ
ሰፋፊ መሬቶች ዘመናዊ የማምረቻ መሳሪያዎችን እና አነስተኛ ጉልበትን በመጠቀም
ለኢንዱስትሪ ጥሬ እቃነት እና ለምግብነት የሚውሉ የሰብል ምርቶችን በስፋት ማምረት
ነው፡፡
የግብርናው ኢንቨስትመንት የስራ ዕድል ከመፍጠር አኳያም ፋይዳው የጎላ ሲሆን በ2003
ዓ.ም ላይ ዘርፉ 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ፈጥሯል። በ1992
6
ከነበረው 400ሺህ ጋር ሲነፃፀር የለውጡን ከፍተኛነት መገንዘብ ይቻላል። ይህ ዘርፍ
በየዓመቱ 4 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለውጭና ለሃገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ
ላይ ነው፡፡ ለገበያ ከሚቀርቡት ምርቶች መካከል ጥጥ፣ ሰሊጥ፣ ቡና፣ አኩሪ አተር፣
ፍራፍሬና ባዮ ፊዩል ይገኙበታል፡፡
የግብርናው ዘርፍ እያደገ ቢሆንም ከውጭም ሆነ ከውስጥ በርካታ ተግዳሮቶች ያሉት ነው።
በተለይ ሰፋፊ የሆኑ የግብርና ኢንቬስትመንት በሚካሄዱባቸው አካባቢዎች ነዋሪዎች
እየተፈናቀሉ ነው፣ ሰፋፊ መሬቶች ለውጭ ባለሃብቶች በመስጠት መንግስት በርካሽ ዋጋ
መሬት እየሸጠ ነው፣ የመሬት ወረራ እየተካሄደ ነው፤ … ወዘተ የሚሉ ከኒዮልበራል ኃይሉ
የሚሰዘነሩ መሰረተ ቢስና የተዛቡ ውንጀላዎች ይስተዋላሉ። የኒዮልበራል ሃይሉን
ውንጀላዎች በማራገብ ላይ ያተኮሩት የሀገር ውስጥ ፀረ ልማት ሃይሎችና ግለሰቦችም
ተመሳሳይ የሆኑ አፍራሽ አሉባልታዎችን በማሰራጨት በእነዚህ አካባቢዎች እየተካሄደ
7
ያለውን ልማት ለማደናቀፍ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም። በመሆኑም የዚህ የተዛባ
አመለካከት መሰረተ ቢስነት ከጊዜ ወደ ጊዜ ግንዛቤ እየተያዘበት ቢሆንም ህዝባችን የተሟላ
መረጃና ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲኖረው መስራት ይኖርብናል፡፡
8
የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂያችን ያለንነ ሃብት በአግባቡ ተጠቅመን ቀጣይ ዕድገታችን
ለማረጋገጥ የሚያስችል ትክክለኛ አቅጣጫ መሆኑን በማስመስከር ላይ ነው።
ሀገራችን ኢትዮጵያ በአግሮ ፕሮሰሲንግ ዘርፍ እምብዛም ያልተነካ እምቅ ሀብት ቢኖራትም
አብዛኞቹ የግብርና ምርቶች ኤክስፖርት የሚደረጉት ፕሮሰስ ሳይደረጉ በመሆኑ ከዘርፉ
ማግኘት የሚገባንን ጥቅም እንድናገኝ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት መሰራት ያለበት ነው።
ለምሳሌ ሀገራችን በእንስሳት ሃብት ብዛት በተለይ ደግሞ በቀንድ ከብት ብዛት ከአፍሪካ
ቀዳሚ ብትሆንም ከእንስሳት ሃብቷ እያገኘት ያለችው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ግን መሻሻል
እያሳየ ቢሆንም ብዙ የሚቀረው ነው። በየአካባቢው ማቆጥቆጥ የጀማመሩ የአግሮ
9
ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪዎች የቀጣይ ሀገራዊ ዕድገታችን ተስፋ ቢሆኑም በዘርፉ ያለን
እምቅ ሃብት ከመጠቀም አንፃር አሁንም ብዙ ርቀት መጓዝ ይጠይቃል።
ከዝናብ ጥገኝነት የተላቀቀ ግብርና ለመፍጠር እየተደረገ ባለው ሁሉን አቀፍ ርብርብ
የመስኖ ልማት ስራው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱ በዓመት አንድ ጊዜ ያውም
ዝናብ ጠብቆ ይካሄድ የነበረው የግብርና ስራ በዓመት ሁለትና ከዛ በላይ ማምረት
በሚቻልበት የመስኖ ልማት እየተተካ ይገኛል። የግብርና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ
እንዲቻል ባህላዊና ዘመናዊ የመስኖ ልማት ስራው አጠናክረን መቀጠል እንዳለብን በፅኑ
በማመን በሁለቱም አቅጣጫዎች ስኬታማ ተግባራት በማከናወን እንገኛለን።
10
በመጀመሪያው ምዕራፍ እንደየቅደም ተከተላቸው 77.2 በመቶ እና 84 በመቶ፣ የርብ
መስኖ ፕሮጀክት 59.45 በመቶ፣ የቆቦ ጊራና ፕሮጀክት 67 በመቶ እንዲሁም ራያ 94
በመቶ ደርሰዋል።
በሌላ በኩል ለባህላዊ መስኖ በተሰጠው ከፍተኛ ትኩረት መሰረት ሁሉም አርሶ አደር
አማራጭ የውሃ ምንጮችን እንዲጠቀም ለማድረግ በተሰራው ሰፊ ስራ አበረታች ውጤት
እያስመዘገብን እንገኛለን። አርሶ አደሩ በየትኛውም ወቅት የተገኘችውን የዝናብ ጠብታ
በአግባቡ በማጠራቀም በምርትና ምርታማነት ላይ መጫወት የሚችለውን አስተዋፅኦ
በሙሉ ለማበርከት በመረባረቡ የተረጂዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲቀንስ ምክንያት
ሆኗል። በዚህ መሰረትም በ2006ዓ.ም ብቻ ከ3ነጥብ 1 ሚልዮን ሄክታር በላይ መሬት
በመስኖ ለማልማት ዕቅድ ተይዞ ስኬታማ በሆነ ሁኔታ ተፈጽሟል። ያም ሆኖ አሁንም
ሀገራችን ከመስኖ ልማት መጠቀም ከሚገባት ደረጃ ላይ አልደረስንም፡፡ አሁንም የመስኖ
ልማትን እንደ ወሳኝ የግብርና ልማት ዘርፍ አድርጎ ያለማየት ችግር ይስተዋላል፡፡ ሁሉም
አርሶ አደር የውሃ አማራጭ እንዲኖረው የማድረግ ግባችን ለማሳካት ቀጣይ ርብርብ
ይጠይቃል፡፡
11
ሲሆን በተለይ ደግሞ ዋነኛ የስራ ዕድል መፍጠሪያ ለሆነው የአነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት
ልማት ዘርፍ የተሰጠው ትኩረት ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ላይ ነው። የሀገራችንን
የኢንዱስትሪ ዕድገት ቀጣይነት ለማረጋገጥ ለመካከለኛና ትላልቅ ኢንዱስትሪዎች ዘርፍም
እንዲሁ ተገቢው ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል።
12
የጥቃቅንና አነስተኛ ልማት ስራ ከጅምሩ በርካታ ፀረ-ልማት ሃይሎችና ግለሰቦች የተለያዩ
ስያሜዎችን በመስጠት ቢያብጠለጥሉትም የእነዚህን አፍራሽ ሃይሎች አሉባልታና
የማጥላላት ዘመቻ በተግባር በማምከን የበርካታ ዜጎችን ህይወት ከማሻሻሉም በላይ በሀገር
ኢኮኖሚ ላይም የማይናቅ አስተዋፅኦ በማበርከት ላይ ይገኛል፡፡ አሁን አሁን ከቴክኒክና
ሙያና ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡ ወጣቶች በዘርፉ እየተሰማሩ
ይገኛሉ፡፡ ከ2004 እስከ 2006 ባሉት ግዜያት ብቻ 146 ሺህ 545 የዩንቨርሲቲና የኮሌጅ
ምሩቃን ዘርፉን ተቀላቅለዋል፡፡
13
2.2 የመካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት መጀመራቸው
የደርግ ስርዓት በተገረሰሰበት ማግስት የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ተንገራግጮ የቆመበት ሁኔታ ነበር
የተፈጠረው፡፡ የነበሩት ጥቂት የኢንዱስትሪ ተቋማትም ለሰራተኛ ደመወዝ እንኳ መክፈል
አቅቷቸው ከፍተኛ ችግር ውስጥ ወድቀው ነበር፡፡ ይህንን ሁኔታ በሚገባ በመገንዘብ ምንም
እንኳን ሀገሪቱ የተጠራቀመ ካፒታልና በዘርፉ የሰለጠነ በቂ ባለሙያ ባይኖራትም ባላት
ውስን አቅም የኢንዱስትሪው ዘርፍ መጫወት የሚገባውን ሚና በአግባቡ እንዲወጣ ግልፅ
አቅጣጫ ተቀምጦ ነበር፡፡ ያለንን ውስን ዓቅም አሟጠን እየተጠቀምን በቀጣይነት ደግሞ
አቅማችንን እየገነባን እንደምንሄድ ታሳቢ ያደረጉ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን ተቀርጸው
ተግባራዊ በመሆን ላይ ይገኛሉ፡፡
የሀገራችን የኢንዱስትሪ ዘርፍም ከዚህ መሰረታዊ እምነት በመነሳት ከፍተኛ የስራ እድል
መፍጠሪያ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግሩ ማዕከልና የኢንዱስትሪ መስፋፋት መሰረት በሆኑት
በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አማካኝነት ለግሉ ባለሃብት የተመቻቸ ሁኔታ
ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራበት ያለ ነው። በዚህም ባለፉት 23 ዓመታት ከ2
ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ የግል ባለሃብቶች በተለያዩ ዘርፎች በመሰማራት 30 ቢሊዮን 333
14
ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል በማንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ፡፡ የውጭ ሀገር ባለሃብቶችም
መዋእለ ንዋያቸውን በማፍሰስ ሃገራችን ለኢንቨስትመንት የተመቸች ሃገር መሆኗን
ምስክርነታቸውን እየሰጡ ናቸው፡፡ ባለፉት 23 ዓመታትም 7 ሺህ 270 የውጭ ሃገር
ባለሃብቶች ከ89 ቢሊዮን 78 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል በማንቀሳቀስ በሀገር ኢኮኖሚ
ላይ አስተዋፅኦ እያበረከቱ ናቸው፡፡
15
ሚኒስቴር ከየከተሞቹ የተረከበ ሲሆን የኢንዱስትሪ ዞኖችን የማልማት ስራም እየተጠናከረ
ነው፡፡ የግል ባለሃብቶችን ተሳትፎ ከማበረታታት አንፃር አስፈላጊ የሆኑ ዕቃዎች ከውጭ
ሲያስገቡ ከቀረጥ ነፃ በማድረግ፣ የግብር ክፍያ የእፎይታ ግዜ በመስጠት እንዲሁም
የመሬት አቅርቦት እየተመቻቸላቸው ይገኛል። በውጤትም ከተለያዩ የዓለማችን
አካባቢዎች የተለያዩ ባለሃብቶች ወደ ሀገራችን በመግባት በጨርቃ ጨርቅ፣ ቆዳና የቆዳ
ውጤቶች፣ አግሮ ኢንዱስትሪና መሰል የኢንዱስትሪ መስኮች ላይ እየተሰማሩ ይገኛሉ፡፡
16
ለመወዳደር ኤክስፖርቱ በፍጥነትና በጥራት እየጎመራ መሄድና በውጭ ገበያ ተወዳዳሪ
የሆኑ ምርቶችን ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
17
2.4 ዘመናዊ አከታተምና የህዳሴ ጉዞአችን
ከተሞቻችን በከፋ ድህነት ውስጥ ተዘፍቀው የስራ አጦች መኖሪያ ሆነው ቆይተዋል፡፡
ያልተማከለ አስተዳደር ሳይዘረጋላቸው፣ ራሳቸው የማስተዳደር ስልጣን ሳይኖራቸው ለበላይ
አካል ብቻ እየታዘዙ በመቆየታቸው የመልካም አስተዳደር፣ የህግ የበላይነት፣ የግልፅነትና
የአሳታፊነት ስርዓት ሳይሰፍንባቸው ቆይቷል፡፡ የከተሞቻችን አመሰራረት ከገጠር ጋር
የነበረው ትስስር የተጠናከረ አልነበረም፡፡ ከተሞቻችን ባለፉት ስርዓቶች ያሳለፉትን
ችግርና ብሶት በመሰረቱ መፍታት ይቻል ዘንድ ለከተሞች ዕድገት ልዩ ትኩረት ሰጥተን
እየሰራን እንገኛለን።
18
ችግሮች እንዲሁም ጎታች ልማዳዊ አሰራሮች በመሰረቱ ይቀየሩና እነዚህ ችግሮች
በቀጣይነት እየተፈቱ ይሄዳሉ።
19
የህዝብ ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የአረንጋዴ ቦታዎችን አካተው በመስራት ረገድም
በርካታ ውስንነቶች ይታይባቸዋል።
በአንድ ሀገር የሚፈለገውን ዕድገትና ልማት በማምጣት ቀጣይነት ወዳለው የስኬት ጎዳና
ለመገስገስ የሰው ኃብት ልማት ወሳኝ ነው። ሀገራችን የተያያዘችውን የተሃድሶ ጉዞ
በሚፈለገው ደረጃ ለማሳካት በዕውቀት የዳበረ፣ በክህሎት የተካነና በአመለካከቱ የተቃና
ዜጋ ማፍራት የግድ ይላል፡፡ በዚህም በርካታ ስኬቶችን በማስመዝገብ ላይ ነን። በሰው
ሃብት ልማት ዘርፍ የህዳሴ ጉዟችን የሚገኘበት ሁኔታ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
20
በተመሳሳይ ሁኔታ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርትን ሽፋን ለማሳደግ በተደረገው ሁሉን አቀፍ
ጥረትም በርካታ ውጤቶች ማስመዝገብ ተችሏል። በ1983ዓ.ም ወደ 416ሺህ የሚጠጉ
ተማሪዎች ብቻ በማስተናገድ 6 በመቶ ብቻ የነበረውን የሁለተኛ ደረጃ የትምህርት ሽፋን
በ2006 ዓ.ም ከ40 በመቶ በላይ ማድረስ የተቻለ ሲሆን ከ2 ሚልዮን በላይ ተማሪዎች
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ይገኛሉ።
21
የሚሰጠውን ትምህርት ጥራትና አግባብነት በቀጣይነት በማሻሻል ዓለም አቀፍ ደረጃውን
ለመጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ኢኮኖሚው የሚፈልገውን ከፍተኛ ብቃት ያለው የሰው ሃይል ማፍራት እንዲቻል አጠቃላይ
የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ካለፉ ተማሪዎች መካከል 40 በመቶ በምህንድስና፣ 30
በመቶ በሌሎች የተፈጥሮ ሳይንስ መስኮች የቀሩት 30 በመቶዎች ደግሞ በተለያዩ
የማህበራዊ ሳይንስ መስኮች እንዲማሩ አቅጣጫ ተቀምጦ ተግባራዊ እየሆነ ይገኛል።
22
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ጉልህ ሚና ይጫዎታሉ። እነዚህ ተቋማት
መደበኛ እና አጫጭር ስልጠናዎች በመስጠት የኢንዱስትሪውን ፍላጎት በማሟላት
የሀገራችን የኢንዱስትሪ ዕድገት በመደገፍ ላይ ይገኛሉ።
23
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፕሮግራሙ ስራ ፈጣሪ ዜጋ በማፍራትም ሆነ ለኢንዱስትሪው
የሚያስፈልገውን መካከለኛ ሙያ ያለው የሰለጠነ የሰው ኃይል በማምረት ረገድ ውጤታማ
ስራዎች ያከናወኑ ቢሆንም ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻል ቢያሳይም አሁንም ተቋማቱ በሌላ
መንገድ መማር ያልቻሉ የወደቁ ሰዎች የሚሰበሰቡባቸው አድርጎ የማየት የተሳሳተ
አመለካከት በአመራሩም ሆነ በፈጻሚው ዘንድ ይታያል፡፡ ዘርፉ አማራጭ ያጡ ዜጎች
የሚሰበሰቡበት ሳይሆን ዜጎች ህይወታቸውን ለመምራት የሚያስችላቸውን ሙያ ለማግኘት
አልመው የሚገቡበት እና በአመለካከት፣ በዕውቀት እና በክህሎት የሚዳብሩበት ትልቅ
የዓቅም ግንባታ ዘርፍ እንደሆነ በቀጣይነት የማስገንዘብ ስራው ተጠናክሮ መቀጠል
የሚገባው ሲሆን ዋናው ትኩረት ግን ተቋማቱ በሚያካሂዱት የእለት ተእለት ግንባታ እና
ከተቋማቱ የሚወጡ ዜጎች በሚያሳዩት የተግባር ብቃት ይህን የተዛባ አመለካከት
የሚሰብሩበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይሆናል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ ለአንድ ሀገር መዘመንና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝና የማይተካ ሚና አለው።
የኢንዱስትሪ አብዮት ተከትሎ የአውሮፓ ሀገራት ራሳቸውን ለማሳደግና ታላቅ ሀገር
ለመባል በትጋት በመስራታቸው እንደየትጋታቸው ከዘርፉ በመጠቀም አስተማማኝ ለውጥ
ማምጣት አስችሏችዋል። የለውጡ ማጠንጠኛ ደግሞ ጊዜው የሚጠይቀውን ቴክኖሎጂ
አሟልቶ መገኘት ነበር። ይህን እውነታ በመረዳት በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በማደግ
ላይ ያሉ ሀገራት የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ዕድገታቸው እውን ለማድረግ ደፋ
ቀና ሲሉ ይታያሉ።
24
ጉዟችን የሚያግዙ በሌሎች ሀገራት የተፈጠሩ ቴክኖሎጂዎችን መኮረጅና በላቀ ፍጥነትና
ብቃት የመጠቀም ዓቅማችን በመገንባት ሌሎች የበለፀጉ ሀገራት የደረሱበት ደረጃ ላይ
መድረስ ነው።
25
የጤና ፖሊሲያችን ሰፊውን ህዝብ ለማገልገል የተቃኘና በመሰረታዊ የጤና አገልግሎት
ላይ ያተኮረ በመሆኑ ህዝባዊ ተቀባይነት ያለውና የህዝቡን ተጨባጭ የጤና ችግሮች
በመፍታት ረገድ ውጤታማነቱን የተመሰከረለት ነው። ባለፉት 23 አመታት በተከናወኑ
ውጤታማ ስራዎች ሀገር አቀፍ የጤና ሽፋናችን በቀጣይነት እየተሻሻለ ይገኛል። ሀገር
አቀፍ የመሠረታዊ ጤና አገልግሎት ሽፋናችንን በ1983ዓ.ም ከነበረበት 41 በመቶ
በ2005 ወደ 93.4 በመቶ ከፍ ማድረግ ችለናል።
እስከ 1983 ዓ.ም ድረስ በሀገሪቱ የነበሩ የጤና ተቋማት ብዛት እጅግ አነስተኛ ሲሆን
ፋሽስታዊው የደርግ ስርዓት ከተገረሰሰ ወዲህ ግን የጤና አገልግሎት ተቋማት ብዛትና
ተደራሽነት በቀጣይነት በማደግ ላይ ይገኛል። ለምሳሌ በ1983ዓ.ም 72 የነበረው
የሆስፒታሎች ቁጥር በ2006 ዓ.ም ወደ 310 ያደገ ሲሆን የጤና ጣቢያዎች ቁጥርም ከ154
ወደ 3ሺህ 250 ከፍ ማድረግ ችለናል። በሽግግር ዘመኑ ምንም ያልነበረውን የጤና ኬላ
ግንባታም በያዝነው ዓመት ከ16 ሺህ በላይ ማሳደግ ተችሏል። በየደረጃው የሚገኙ የጤና
ባለሙያዎች ቁጥርም በተመሳሳይ ሁኔታ እያደገ ይገኛል። ለዘርፉ በተሰጠው ልዩ ትኩረት
መሰረት የአገልግሎት ሽፋኑን በቀጣይነት በማሳደግ ሀገራችን የህፃናትን ሞት በመቀነስ፤
ወባንና ሌሎች በሽታዎችን እንዲሁም የኤችአይቪ ኤድስ ስርጭትን በመግታት ለዓለም
አቀፉ ደረጃ አርአያ እንድትሆን አስችሏታል።
4. የመሰረተ ልማት
26
ይኖርብናል። የመሰረተ ልማት ተቋማት በስፋትና በጥራት ባልተሟሉበት ሁኔታ
የጀመርነውን ፈጣን ዕድገት ዳር ማድረስ አይቻልም። በመሆኑም ልማታዊ መንግስታችን
ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ሀገር በቀል የፖሊሲ ማዕቀፍ በማዘጋጀትና የህዝቡን
ተሳትፎ ባረጋገጠ መልኩ በከፍተኛ ቁርጠኝነት በመንቀሳቀሱ ባለፉት 23 ዓመታት
ውጤታማ ስራዎች በማከናወን የሀገሪቱ የመሰረተ ልማት ተደራሽነት ትርጉም ባለው
መልኩ ማሻሻል ተችሏል። በመሰረተ ልማት ረገድ የህዳሴ ጉዞችን የሚገኝበትን ሁኔታ
እንደሚከተለው እንመልከት፡፡
በሌላም በኩል ሀገራችን ከጎረቤት ሀገራት በተለይ ደግሞ ከወደቦች ጋር የሚያገናኙ ዓለም
አቀፍ ደረጃቸው የጠበቁ መንገዶች ያስፈልጓታል። ሀገራችን የምታመርታቸው ምርቶችና
አገልግሎቶች በአጭር ጊዜ ወደ ወደቦች በማድረስ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ መሰረት
ወደየመዳራሻቸው በመላክ ተወዳደሪነታችን በመገንባት በኩልም መንገድ በጣም አስፈላጊ
ቅድመ ሁኔታ ነው።
27
የመንገድ ዘርፍን አስፈላጊነትና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በአግባቡ በመገንዘብ ባለፉት 23
ዓመታት ከፍተኛ ስራዎች ማከናወን ተችሏል። ስለሆነም እስከ 1983 ዓ.ም ድረስ 18 ሺህ
81 ኪሎ ሜትር ብቻ የነበረው የሀገራችን የመንገድ ርዝመት በ2005ዓ.ም ወደ 86 ሺ ኪሎ
ሜትር ገደማ ከፍ ማድረግ ተችሏል። በመንገድ ዘርፍ የተመዘገበው ዕድገት በመንገዶች
ርዝመት ብቻ ሳይሆን በጥራትም ጭምር ነው፡፡ ለአብነት በ1989 በጥሩ እና በደህና ይዞታ
ላይ የሚገኝ መንገድ 48 በመቶ ብቻ የነበረ ሲሆን ይህ ምጣኔ በ2005 ወደ 90 በመቶ ከፍ
ማድረግ ተችሏል፡፡
28
ሜትር የሚሆን አጠቃላይ ርዝመት የሚሸፍን ነው፡፡በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዳችን
ውስጥም 2 ሺህ 395 ኪሎ ሜትር የባቡር መስመር ለመዘርጋት አቅደን እየተረባረብን
እንገኛለን፡፡ ፕሮጀክቱ በአንድ በኩል የሀገራችን ወጪና ገቢ ምርቶችን በተሻለ ፍጥነት
በማስወጣትና በማስገባት በጉዞ ይባክን የነበረውን ጊዜ በመቆጠብ አገራችን ከዘርፉ
የምታገኘው ጥቅም የሚያሳድግ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያን ከጎረቤት አገሮች
ጋር በማገናኘት በአገራቱ መካከል የሚኖረውን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ
ግንኙነትና ትስስር በእጅጉ የተሳለጠ ያደርገዋል።
ከአገር አቋራጭ የባቡር መስመር ዝርጋታ በተጨማሪ በመዲናችን አዲስ አበባ የሚገነባው
የቀላል ባቡር ፕሮጀክት ስራው ሲጠናቀቅ በሁለት አቅጣጫ በአንድ ሰዓት 80 ሺህ
መንገደኞችን ማጓጓዝ እንዲችል ተደርጎ እየተገነባ ነው፡፡ አጠቃላይ ርዝመቱ 34.35 ኪሎ
ሜትር የሚሸፍነው ይህ ፕሮጀክት በመጭው አመት አጋማሽ ለማጠናቀቅ ርብርብ
እየተደረገ ይገኛል፡፡
29
ዓቅማችን በቀጣይነት በማሳደግ ረገድ የበርካታ ስኬቶች ባለቤት ሆነናል። በባለፉት
ስርዓቶች በከተሞች ብቻ ታጥሮ የነበረውን የሀገራችን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት
በቀየስነው ፍትሐዊ የኃይል አቅርቦትና ተደራሽነት ስትራቴጂ መሰረት በየጊዜው በማደግ
ከፍተኛ ስኬቶችን በማስመዝገብ ላይ እንገኛለን፡፡ እስከ 1983ዓ.ም ድረስ በ361 ሜጋ ዋት
ላይ ብቻ ታጥሮ የነበረው የሀገራችን የኤሌክትሪክ ኃይል በአሁኑ ወቅት ወደ 2 ሺህ 177
ሜጋ ዋት ከፍ ብሏል።
የሀገራችን የኢኔርጂ ምንጮች ከታዳሽ ሃይል የሚገኙና ቀጣዩ የሀገራችን የዕድገት አቅጣጫ
ግምት ውስጥ በማስገባት እየተከናወኑ የሚገኙ መሆናቸው ደግሞ የዘርፉን ዕድገት
አስተማማኝ ያደርገዋል። ለዘርፉ በሰጠነው ከፍተኛ ትኩረት መሰረት ሀገራችን ያላት
የታዳሽ ሃይል (የውሃ፣ የንፋስ፣ የፀሃይ፣ የጂኦቴርማልና የባዮ ፊዩል) ምንጮችን በአግባቡ
በማልማት የራሳችን የልማት ፍላጎት ከማሟላት ባሻገር ለጎረቤት ሀገራት ጭምር
የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ጎረቤቶቻችንንም ጭምር የምንጠቅምበት ሁኔታ እየፈጠርን
እንገኛለን።
ሀገራችን ከፍተኛ የውሃ፣ የነፋስ፣ የፀሐይና የእንፋሎት ታዳሽ ሃይሎች የኤሌክትሪክ ኃይል
የማመንጨት ዓቅም አላት። በመሆኑም ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመገንባት
በምናደርገው ያለሰለሰ ርብርብ ለእድገታችን በቂ እና ከበቂ በላይ የሆነ መልማት የሚችል
እምቅ ኃይል ይዘን ወደፊት ለመገስገስ የሚያስችለን የተመቻቻ ሁኔታ ያለን ነን። እናም
በዘርፉ ያለንን ያልተነካ ሃብት በአግባቡ እያለማን የራሳችን ፍላጎት ከማሟላት በላይ
ለጎረቤቶቻችን እና ለሌሎች አካባቢዎችም መሸጥ እንችላለን። የወደፊቱ
የኢንዱስትራያላዜሽን ዕድገታችን በየጊዜው ከሚዋዥቀው የዓለም የነዳጅ ገበያ በከፍተኛ
ሁኔታ የተላቀቀ እና በራሳችን አስተማማኝ ዓቅም ላይ የተገነባ ለማድረግ የሚያስችሉን
አቅጣጫዎች ነድፈን በመንቀሳቀሳችን ውጤቱን ከወዲሁ ማጣጣም ጀምረናል።
30
በኢነርጂ ዘርፍ ያገኘው ስኬት ግን አልጋ ባልጋ የተገኘ አልነበረም። ዘርፉ ካሉት
ፈተናዎቹ መካከል በዋናነት የሚጠቀሰው የፋይናንስና የማስፈፀም ዓቅም ማነስ ነው።
በተለይ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶቻችን በተያዘላቸው ጊዜ መሰረት
ለማከናወን ከፍተኛ ካፒታልና ክህሎት የሚጠይቁ በመሆናቸው በተፈለገው ፍጥነት
ከመፈፀም አንፃር በርካታ ፈተናዎች የበዙበት ቢሆንም መንግስትና ህዝብ በሚያደርጉት
ርብርብ ችግሮቹን ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
31
ስርዓት በመዘርጋቱ የመረጃ ፍሰቱን የተሳለጠ እያደረጉት ይገኛል፡፡ እነዚህ
የቴሌኮሚዩንኬሽን አገልግሎትን መሰረት አድርገው የተጀማመሩ አሰራሮች በቀጣይም
ተጠናክረው የሚቀጥሉ ይሆናል።
32
5.1 የሕገ መንግስታችን መሰረታዊ መርሆዎች፣
33
የመንግስትና የሃይማኖት መለያየትም ሌላኛው የሕገ መንግስቱ ወሳኝ መርሆ ነው። ሕገ
መንግስታችን ካለፉት የአገራችን መንግስታት ህገ መንግስቶች በተለየ መልኩ ተራማጅና
ዴሞክራሲያዊ ባህርይ ከሚያለብሱት ጉዳዮች አንዱና ዋነኛው በመንግስትና በሃይማኖት
መካከል ያለውን ግንኙነት በግልጽና በማያሻማ መንገድ ማስቀመጡ ነው። በኢፌዲሪ ህገ
መንግስት መንግስትና ሃይማኖት የተለያዩ መሆናቸውን፣ መንግስታዊ ሃይማኖት
እንደማይኖር እንዲሁም መንግስት በሃይማኖት፣ ሃይማኖት ደግሞ በመንግስት ጉዳይ ላይ
ጣልቃ መግባት እንደማይችሉ ግልፅ የሆነ ሕገ መንግስታዊ ክልከላ ተበጅቶላቸዋል።
34
እየተረባረቡ ይገኛሉ። እነዚህ ኃይሎች በአገራችን ብዝሃነት እንዳይኖር ቢኖርም በመልክአ
ምድር ከፋፍሎ ማስተዳደር እንጂ ማንነትና የህዝብ ፈቃድን መሰረት አድርጎ መደራጀትን
አምርረው የሚኮንኑ ጥገኞች ናቸው።
35
ሲያደርሳቸውና ከየወቅቱ ገዥዎች ሲያፋልማቸው የነበረው ይህ የእኩልነት ጥያቄ እስከ
1983ዓ.ም ደረስ ትክክለኛ ምላሽ ሳያገኝ ቆይቷል። የደርግን ስርዓት ለመገርሰስም ከግንባር
ቀደም ምክንያቶቹ አንዱ ነበር የብሔር ጥያቄ።
ይሁን እንጂ የድሮ ስርዓት ናፋቂ ኃይሎችና ግለሰቦች “አንድ ሀገር፣ አንድ ቋንቋ፣ አንድ
ሃይማኖት” የሚል ያረጀ ያፈጀ ፀረ ህዝብ አስተሳሰብ በማቀንቀን ይህ መብት ሀገር
ይበታትናል በማለት ህዝቦች በረዥምና መራራ ትግላቸው የተጎናፀፉትን መብት
ሲያብጠለጥሉት ይታያሉ። የባለፉት 23 ዓመታት ተሞክሮአችን የሚያሳየው ግን እነዚህ
ሃይሎች እንዳራገቡት መበታተንን ሳይሆን አብሮነትና በመከባበር ላይ የተመሰረተ
ዴሞከራሲያዊ ስርዓት የተገነባባትና በከፍተኛ ፍጥነት ህዳሴዋን ለማረጋገጥ ወደ ፊት
እየገሰገሰች ያለች ሀገርን ነው። ሁሉም የሀገራችን ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች እጅ
ለእጅ ተያይዘው በፀረ ድህነት ትግሉ ላይ ባካሄዱት ያላሰለሰ ጥረትም እነሆ ሀገራችን
እጅግ ፈጣን ዕድገት ከሚያስመዘግቡ ጥቂት የዓለማችን ሀገራት አንዷ ሆናለች።
አንድነታችንም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከረና የጋራ ራዕያችን ለማሳካት የምናደርጋቸው
እንቅስቃሴዎችም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበቱና ከአንድ ስኬት ወደቀጣዩ ከፍተኛ ስኬት
እየተሸጋገሩ ይገኛሉ።
36
5.2.2 የሃይማኖቶች እኩልነት፣ የእምነት ነፃነትና ሴኩላሪዝም ለህዳሴአችን፣
ይሁን እንጂ ይህ መብት በአግባቡ ተከብሮ እያለ ምንም ዓይነት ሃይማኖታዊ ይዘት
የሌላቸው ነገር ግን ፖለቲካዊ ግብ ያነገቡ የአክራሪነትና የፅንፈኝነት እንቅስቃሴዎች
ይታያሉ። በሃይማኖት ስም የሚካሄድ አክራሪነት የመጨረሻ ግቡ ሃይማኖታዊ መንግስት
ማቋቋም ነውና ኢ-ህገመንግስታዊ አስተሳሰብና ድርጊት ነው፡፡ አክራሪነት በሃገራችን
ለዘመናት የቆየውን በሃይማኖቶች መካከል ተቻችሎ የመኖር እሴት በመሸርሸር
በሃይማኖቶችና ተከታዮቹ መካከል ግጭትና አለመተማመን የመፍጠር ስልትን የሚከተል
የአንድነታችን ፀርም ጭምር ነው፡፡
37
የማስከበር ህገ መንግስታዊ ኃላፊነቱ መወጣት ይችል ዘንድ ፀረ-አክራሪነትና ፅንፈኝነት
ትግሉ ማጠናከርና አክራሪነትና ፅንፈኝነትን መመከት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ ገባ
የሚያስብል ምንም ዓይነት ምክንያታዊ ጥያቄ የሚያስነሳ ባለመሆኑ በዚህ ረገድ የሚነሳ
ቅሬታም ተቀባይነት የሌለው ተራ ማደናገሪያ ተደርጎ የሚወሰድ ነው።
ለዚህም ነበር የዓፈናና የጭቆና ስርዓቱ ለመገርሰስ በተካሄደው መራራ ትግል ሴቶች
ከወንዶች ጋር እኩል የተዋደቁት። በከፈሉት ክቡር መስዋእትነትም የፆታ እኩልነት
ተረጋግጧል። የኢፌዴሪ ሕገ መንግስትም ሁሉም ሰዎች በሕግ ፊት እኩል መሆናቸውንና
በመካከላቸውም ማንኛውም ዓይነት ልዩነት ሳይደረግባቸው እኩል የሕግ ጥበቃ
እንደሚደረግላቸው በግልፅ በመደንገግ የፆታንም ሆነ ማንኛውንም ዓይነት መበላለጥ ሕገ
ወጥ አድርጎታል። ሕገ መንግስታችን ሴቶች ከወንዶች ጋር እኩል መሆናቸውን ከመደንገጉ
በተጨማሪ ሴቶች በበታችነትና በልዩነት በመታየታቸው የደረሰባቸውን የታሪክ ቅሪት
ከግምት ውስጥ በማስገባት እንዲታረምላቸው ተጨማሪ የድጋፍ መብት ተጠቃሚ መሆን
እንደሚገባቸው ያስቀምጣል።
38
የማሳተፍ ጉዳይ ነው፡፡ በተጨባጭ አሁን እየተመዘገበ ያለው ፈጣን፣ ቀጣይነት ያለውና
ፍትሐዊ ዕድገትም የሴቶች ሁሉን አቀፍ ተሳትፎና ተጠቃሚነት በማረጋገጣችን ያገኘነው
ስኬት ነው። በመሆኑም የሴቶች እኩልነት የማረጋገጥ ጉዳይ የዴሞክራሲ መርህ ስለሆነ
ብቻ ሳይሆን ሀገራችን የተያያዘችው የህዳሴ ጉዞ እውን ለማድረግ አማራጭ የሌለው አጀንዳ
በመሆኑ እየተጠናከረና እየጎለበተ የሚሄድ ነው።
39
በመገንዘብ ተቋማቱ የሚጠበቅባቸው አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ሌት ተቀን እየተጋ
ይገኛል።
በዚህ ረገድ ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ እየተጫወተ ያለው ግንባር ቀደም ሚና ታሪካዊ ነው
ማለት ይቻላል። ኢህአዴግ የሀገሪቱ ሕገ መንግስትንና ሌሎች ሕጎች አክብረው በሰላማዊ
መንገድ የተቃውሞ ፕሮግራሞቻቸውን የሚያራምዱ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በህዝብ
ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ ቢኖራቸውም ባይኖራቸውም አብሮ ለመስራት በገባው
ቃል መሰረት ከ2003ዓ.ም ጀምሮ ሀገር አቀፍ የጋራ ምክር ቤት አቋቁሞ እየሰራ ሲሆን
በአሁን ወቅትም ከስምንት ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች ጋር አብሮ እየሰራ ይገኛል። ይህም
ድርጅቱ ለመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ላለው ቁርጠኝነት ግልፅ
ማረጋገጫ ተደርጎ የሚወሰድ ነው።
40
ትምህርቶች እየተሰጠ ያለው የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ስርፀት በማጠናከር በዴሞክራሲያዊ
ባህል የዳበረ ትውልድ የመገንባት ስራችን ለዴሞክራሲያችን ማበብ ወሳኝ ሚና እየተወጣ
ነው፡፡
41
ውጤቶች ታይተዋል፡፡ ይሁን እንጂ አሁንም የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር
በሚፈለገው ደረጃ በልማታዊ አስተሳሰብ አልተተካም፡፡
ስለሆነም የሀገራችን ቀጣይ ዕድገት በማረጋገጥ ህዳሴእችን እውን ይሆን ዘንድ የኪራይ
ሰብሳቢነት ፖለቲካል ኢኮኖሚ መሰረት መናድና ልማታዊነትን በማጠናከር የሀገራችን
ብሩህ ተስፋ የማስቀጠል ጉዳይ በአማራጭነት የሚቀርብ ሳይሆን የህልውና ጥያቄ በመሆኑ
ከፍተኛ የሆነ ትግልና ርብርብ ማድረግ ይኖርብናል። የትግሉን ግለትና አድማስ በማስፋት
ልማታዊ አስተሳሰብና ተግባር ማጠናከር የምንችለው ደግሞ መላውን ህዝብ ባሳተፈ መልኩ
በቁርጠኝነት መታገል ሲቻል ነው። ኪራይ ሰብሳቢነት የህዳሴ ጉዟችን እንቅፋት መሆኑን
የጋራ መግባባት ፈጥሮ የልማታዊ አስተሳሰብና ተግባር የበላይነቱን እንዲይዝ አበክረን
መስራት ይኖርብናል፡፡ በሌላ ጽኁፍ በዝርዝር የቀረበውን የኪራይ ሰብሳቢነት መሸሸጊያ
ዋሻ የሆኑትን ትምክህትና ጠባብነት የመታገል ጉዳይም ከዚሁ ጋር ተያይዞ መታየት
ይኖርበታል፡፡
42
አሁን ባለው ሁኔታ ግን በየጊዜው የማስፈፀም አቅማችን እየገነባን እና በርካታ ውጤታማ
ስራዎች እያከናውንን ብንሆንም የህዝባችን እርካታ በማረጋገጥ ረገድ በርካታ ችግሮች
አሉብን። እንዲያው ከህዝቡ በየወቅቱ ከሚነሱ መሰረታዊ ጥያቄዎች መካከል የመልካም
አስተዳደር ችግር እየሆነ መጥቷል። ችግሮቹም ከተሳትፎ፣ ግልፅነትና ተጠያቂነት ማነስ
እንዲሁም ከቀልጣፋነትና ውጤታማነት ጋር የተያያዙ ናቸው ማለት ይቻላል።
ከሁሉም በላይ ደግሞ አሁን ለህዝቡ እየሰጠን ያለነው አገልግሎት በቀጣይነት በማሻሻል
ቀልጣፋና ውጤታማ ማድረግ ይኖርብናል። ህዝቡ እየተማረረብን ካሉ የመልካም
አስተዳደር ጉድለቶች መካከል አብዛኞቹ በፍጥነት ትክክለኛ ምላሽ ካለመስጠት
የሚመነጩ ናቸው ማለት ይቻላል። ለህዝባችን የምንሰጠው አገልግሎት ቀልጣፋና
43
ውጤታማ ማድረግ ቻልን ማለት በአንድ በኩል የህዝባችን እርካታ አረጋገጥን ማለት ሲሆን
በሌላ በኩል ደግሞ ህዝቡ አገልግሎቱን ለማግኘት የሚያጠፋው ጊዜ ወደ ልማት ስራው
በማዞር በተያያዝነው የህዳሴ ጉዞ ላይ የሚያደርገው ተሳትፎ ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ
ያስችለናል ማለት ነው።
44
በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ስጋት የደቀነው ሽብርተኝነትም በተመሳሳይ ሁኔታ የሀራችን
የሰላም፣ የልማትና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጉዞአችን ተጨባጭ አደጋ እየሆነ ይገኛል።
በመሰረቱ ሽብርተኝነት ማለት የአንድን ቡድን የፖለቲካ፣ የሃይማኖት ወይም የርእዮተ
አለም ዓላማን በሌሎች ላይ በሃይል ለመጫን በመንግስትና በህዝብ ላይ እንዲሁም
በመንግስትና በህዝብ ንብረት ላይ ከፍተኛ የሆነ አደጋ በመፍጠር ወይም የአደጋ ስጋቶችን
በመደቀን በዜጎች ላይ ሽብርና አለመረጋጋት የመፍጠር ዓላማ ያለው ተግባር ነው። እናም
በተለይ ሀገራችን ከምትገኝበት የምስራቅ አፍሪካ በተለይ ደግሞ ከአፍሪካ ቀንድ አካባቢ
የሚነሱ የሽብር አደጋዎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሀገራችን ሰላምና መረጋጋት በማወክ
ረገድ ከፍተኛ ሚና አላቸው።
45
ዓለም እና የርእዮ ዓለሙ አክራሪዎች በህዳሴ ጉዞአችን ላይ ሊፈጥሩት የሚችሉት አፍራሽ
ሚናን ይሆናል።
46