Professional Documents
Culture Documents
ሚያዝያ 2010
ድሬዳዋ
ማውጫ
ርዕስ ገጽ
ክፍል አንድ
1
አጠቃላይ
1.1 መግቢያ..................................................................................................................................................................4
1.2 የሰነዱ ዓላማ.........................................................................................................................................................5
1.3 የሰነዱ አስፈላጊነት...................................................................................................................................................5
1.4 ከሰነዱ የሚጠበቁ ውጤቶች......................................................................................................................................6
ክፍል ሁለት
የአስተዳደር እና የመንግስት አስተዳደር ምንነት
2.1. የአስተዳደር ስርዓት ፅንሰ ሃሳብ.....................................................................................................................................7
2.2. የመንግስታዊ አስተዳደር ምንነት..............................................................................................................................8
ክፍል ሦስት
የመልካም አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ አመጣጥ፣ ምንነት እና መርሆዎች
3.1. የመልካም አስተዳደር ፅንሰ ሀሳብ አመጣጥና ምንነት..........................................................................................................11
3.1.1. የመልካም አስተዳደር ፅንሰ ሀሳብ ታሪካዊ ዳራ 11
3.1.2. የመልካም አስተዳደር ምንነት 14
3.2. የልማት፣ የዴሞክራሲ እና የመልካም አስተዳደር ትስስር.....................................................................................................19
3.3. መልካም አስተዳደር በኢትዮጵያ..................................................................................................................................20
3.4. የመልካም አስተዳደር መርሆዎች..................................................................................................................................24
3.5. የመልካም አስተዳደር መስፈን ያለው ጠቀሜታ................................................................................................................32
ክፍል አራት፡
መልካም ያልሆነ አስተዳደር ምንነት፣ መገለጫ ባህሪያትና የሚያስከትለው አደጋ
4.1. መልካም ያልሆነ አስተዳደር ምንነትና መገለጫ ባህሪያት......................................................................................................34
4.2. መልካም ያልሆነ አስተዳደር የሚያስከትለው አደጋ.............................................................................................................35
ክፍል አምስት፡
መልካም አስተዳደርን በማስፈን ረገድ የተለያዩ አካላት ሚና
5.1. የፐብሊክ ሰርቪሱ ሚና..............................................................................................................................................37
5.2. የህዝብ ክንፉ ሚና....................................................................................................................................................37
5.3. የህዝብ ተወካዮች ም/ቤቶች ሚና...........................................................................................................................38
5.4. የሚዲያ ሚና........................................................................................................................................................38
ክፍል ስድስት፡
የመልካም አስተዳደር ዕቅድ ዝግጅት እና ትግበራ
6.1. የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምንነት.....................................................................................................................39
6.2. የመልካም አስተዳደር ችግሮች መለያ የመረጃ ምንጮች.............................................................................................39
6.3. የመልካም አስተዳደር ችግሮች ትንተና.....................................................................................................................40
6.4. የመልካም አስተዳደር ግቦች ምንነት.........................................................................................................................46
2
6.5. የመልካም አስተዳደር ግቦች ትንተና.........................................................................................................................46
6.6. ግብ ተኮር ተግባራት ምንነትና መለያ ዘዴዎች...........................................................................................................48
6.7. የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍቻ መርሐ ግብር...................................................................................................49
6.8. የእቅድ ዝግጅት እና ትግበራ አቅጣጫዎች................................................................................................................50
6.8.1. የእቅድ ዝግጅት አቅጣጫዎች 50
6.8.2. የእቅድ ትግበራ አቅጣጫዎች 51
6.9. የክትትልና ድጋፍ ስርዓት.........................................................................................................................................54
6.10. በየደረጃው ያሉ የመንግስት አካላት ሚና.......................................................................................................................59
አባሪ፡- የመልካም አስተዳደር ሥራዎች አፈጻጸም ሪፖርት ማቅረቢያ ቅጾች..........................................................63
ክፍል አንድ
አጠቃላይ
1.1 መግቢያ
መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የጽንሰ-ሀሳቡን ምንነት፣ መርሆዎችን፤ ተያያዥ ጉዳዮችንና ዓለምአቀፋዊ
ባህሪውን ከአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማዛመድ በትክክል መገንዘብና ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ ህዝቡ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ችግሮች በተጨባጭ ለመፍታት የሚያስችል
የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍቻ እቅድ በማዘጋጀት ትግበራውን በጠንካራ ክትትልና ድጋፍ አሰራር
3
አስደግፎ መረባረብን ይጠይቃል፡፡ በመሆኑም ባለፉት ዓመታት ለህዝቡ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የጎላ
ሚና ያላቸው አደረጃጀቶችንና ተቋማትን በመልካም አስተዳደር ምንነት፣ መርሆዎችና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ
ግንዛቤ የማስፋትና በዚህም ተሳትፎአቸውን የማጎልበት ጥረት በየደረጃው በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡
በአሁኑ ወቅት የመልካም አስተዳደር ጉዳይ የአገራችን ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቁልፍ አጀንዳ የሆነበት
ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ተቋማት የውስጥና የውጭ መልካም አስተዳደር
ችግሮችን በመለየትና የድርጊት መርሐ-ግብር በማዘጋጀት የዜጋውን ጥያቄ ለመመለስ ጥረት እያደረጉ ይገኛል፡፡
ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ አሁንም በመልካም አስተዳደር ምንነት፣ እቅድ አዘገጃጀትና አተገባበር ዙሪያ በየደረጃው
ወጥነት ባለው መልኩ ግንዛቤ፣ ዕውቀትና ክህሎትን ለማሳደግ የሚያስችል አገራዊ ሰነድ ባለማዘጋጀቱ
በየመ/ቤቱ እየተዘጋጀ ያለው የመልካም አስተዳደር እቅድ አይነትና ይዘት እንዲለያይና የአተገባበር ክፍተት
እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል፡፡ ስላ መልካም አስተዳደር እየተሰጠ ያለው የዕውቀትና የክህሎት ማሳደጊያ
ስልጠናም ቢሆን በተደራጀና ወጥነት ባለው የስልጠና ሰነድ ላይ የተመሰረተ አይደለም፡፡ በመሆኑም በመልካም
አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ፣ ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ዙሪያ የሚታዩ የዕውቀትና የክህሎት ክፍተቶችን
በመሙላትና የመልካም አስተዳደር ዕቅድ አፈጻጸምን ውጤታማ በማድረግ የዜጎችን እርካታ ማረጋገጥ
እንዲቻል ይህ የመልካም አስተዳደር የስልጠናና የትግበራ ሰነድ ተዘጋጅቷል፡፡
ሰነዱ አጠቃላይ ሁኔታን የሚጠቁም መግቢያ፣ የሰነዱ ዓላማና አስፈላጊነትን የያዘ አንድ ክፍልና ሌሎች ሁለት
ዋና ዋና ክፍሎችን ይዟል፡፡ የመጀመሪያው ክፍል የመልካም አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ ምንነት፣ መልካም
አስተዳደር በተለያዩ ርዕዮተ ዓለሞች እይታ፣ የመልካም አስተዳደር መርሆዎች፣ መልካም አስተዳደርን
በማስፈን ሂደት የተለያዩ አካላት የሚኖራቸው ሚና፣ መልካም አስተዳደርን የማስፈን ጠቀሜታና ያለማስፈን
የሚያስከትለውን ጉዳት ያብራራል፡፡ ክፍል ሁለት ደግሞ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምን እንደሆኑ፣
ችግሮቹን እንዴት መለየትና በእቅድ ማስደገፍ እንደሚቻል፤ የዕቅድ ዝግጅት፤ የአፈጻጸም አቅጣጫና
የክትትልና ድጋፍ አግባቦች ምን እንደሆኑ በስፋት ይዳስሳል፡፡
4
የመንግስት ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎትና ከሚያከናውኑት የልማት ስራ ጋር ተያይዞ ዜጎች
በሚያነሷቸው የመልካም አስተዳደር ችግሮች፣ በችግሮቹ መንስኤ እና ችግሮቹን መፍታት
በሚያስችል የዕቅድ አዘገጃጀትና አተገባበር ዙሪያ ግንዛቤና ክህሎት ማሳደግ፣
የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመፍታትና የህዝቡን እርካታ ከማረጋገጥ አንጻር በየደረጃው
የሚታየውን የግንዛቤ፣ የክህሎትና የአፈጻጸም አለመመጣጠን ማጥበብ ናቸው፡፡
5
የአስተዳደር ስርዓት በተለያዩ አገላለፆች ጥቅም ላይ ዉሏል፡፡ ለምሳሌ የኮርፖሬት አስተዳደር ስርዓት፣ ዓለም
አቀፍ የአስተዳደር ስርዓት፣ ብሔራዊ የአስተዳደር ስርዓት፣ የአካባቢ አስተዳደር ስርዓት፣ ክልላዊ የአስተዳደር
ስርዓት፣ ወዘተ… በሚል በአንድ ሀገር የአስተዳደር ሥርዓት ዉስጥ መንግስት የሀገሪቱን ፖለቲካዊ፣
ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ሀብቶችን ለልማት ለማዋል የአመራር ስርዓቱን የሚተገብርበት ሥርዓት ነዉ
(የዓለም ባንክ፣ 2003)፡፡
የአስተዳደር ሥርዓት ፅንሰ ሃሳብ በአሁኑ ወቅት ዓለም አቀፍ ትኩረትን የሳበና በተለያዩ የአኗኗር ዘይቤዎችና
መገለጫዎች ማለትም በግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ፣ በመንግስት አሰራር፣ በተለያየ ደረጃ ላይ በሚገኝ ማህበረሰብ
አኗኗር፣ ለትርፍ ባልተቋቋሙ ተቋማትና በዓለም አቀፍ ተቋማት ጭምር በየዕለቱ የሚገለፅና ጥቅም ላይ
እየዋለ የሚገኝ ፅንሰ ሃሳብ ነዉ፡፡ ለዚህም እንደ ዋነኛ ምክንያት ተደርጎ የሚወሰደው የዓለም የኢኮኖሚ ትስስር
መጠናከር ባደጉትና ባላደጉት ሀገራት ከሚፈጠረዉ የሃብት /የካፒታል/ ፍላጎት መጨመር ጋር በተያያዘ በዓለም
አቀፍ ደረጃ የተጠናከረ የአሰራር ስርዓት እንዲኖር በማስፈለጉ ነው (ብሃሳ፣ 2004)፡፡
የአስተዳደር ሥርዓት በዋናነት መንግስት የአንድን ሃገር ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ሃብቶችን
የሚያስተዳድርበት፣ የአንድን ሃገር አጠቃላይ ደህንነት በተለያዩ ደረጃዎች የሚገልፅበትና ዜጎች የተሻለ የኑሮ
ደረጃ ላይ እንዲደርሱና የተሻለ ህይወት እንዲመሩ የሚያደርግበት የአሰራርና የአመራር ዓይነት ነዉ፡፡
የአስተዳደር ስርዓት ቀጣይነት ያለዉ ጽንሰ-ሃሳብ ሲሆን ዜጎች የተለያዩ ሃሳቦችንና ፍላጎቶችን በማቻቻልና
በማስታረቅ ለጋራ ጥቅም የሚሠሩበት ሂደት ነው፡፡
የአስተዳደር ሥርዓት ሦስት የተለዩ ዘርፎችን ይይዛል፡፡ እነሱም የህዝብ /ፐብሊክ/፣ የኮርፖሬትና የሲቪል
ማህበረሰብ ዘርፎች ናቸዉ፡፡ እንደ ዓለም ባንክ አገላለፅ የአስተዳደር ስርዓት ሦስት ንዑስ ክፍሎችን ይይዛል፡፡
እነሱም የፖለቲካ ስልጣን፣ የፖለቲካ ስልጣን የሚተገበርበት አሰራርና አካሄድ እንዲሁም የመንግስት
የማስፈፀም አቅም ናቸው፡፡ (የዓለም ባንክ፣ 1994)፡፡ ስለሆነም የአስተዳደር ሥርዓት የተቋማት የማስፈጸም
ውጤታማነት መሳሪያ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ በመሆኑም ተቋማት ትክክለኛና ውጤታማ የማስፈጸም አቅም
ከገነቡ መልካም አስተዳደርን የማስፈን እድላቸው ሰፊ ይሆናል፡፡
የአስተዳደር ስርዓት በብሔራዊ፣ በክልላዊና በአካባቢያዊ ደረጃ ውሳኔ የመስጠት ሂደት ሲሆን ባለድርሻ አካላት
የውሳኔዎችን መተግበር ወይም አለመተግበር የሚከታተሉበት ሂደት ነው፡፡ መንግስት በዚህ ስርዓት ዉስጥ
አንዱና ዋነኛዉ ተዋናኝ ነዉ (የአፍሪካ ህብረት፣ 2008) ፡፡
መንግሥታዊ አስተዳደር መልካም እንዲሁም መልካም ያልሆነ አስተዳደር ሊሆን ይችላል፡፡ መንግሥታዊ አስተዳደር መልካም
ወይም መልካም እንዳይሆን የሚያደርገው የፖሊሲና ኘሮግራሞች አተገባበር ሂደትና ውጤት ነው፡፡ በዚሁ መሰረት የልማት፤
የፖሊሲና ኘሮግራሞች አተገባበር ውጤታማነትንና ፍትሐዊ የልማት ተጠቃሚነትን ካረጋገጠና በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት
ካገኘ፤ እንዲሁም ህዝቡ በመንግስታዊ ተቋማት በሚሰጡት አገልግሎቶች ከረካ መልካም አስተዳደር ተረጋግጧል ማለት
ይቻላል፡፡
በዚሁ መሰረት በመንግስት አስተዳደር ውስጥ የመንግሥት ድርሻ በዋናነት በህግ አውጪው፣ በህግ ተርጓሚው፣ በህግ
አስፈጻሚው ወይም በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና በተቆጣጣሪ አካላት የሚፈፀም ይሆናል፡፡ በዚህም መንግሥት የህዝቡን
የኑሮ ሁኔታ በማሻሻል ከድህነት ለመላቀቅና ዘለቄታ ያለው ልማት ለማምጣት የሚያስችሉ ፖሊሲዎችንና ኘሮግራሞችን ቀርጾ
ተግባራዊ በማድረግ የህዝቡን እርካታ ሲያረጋግጥ እና የሰላም፣ የልማትና የዲሞክራሲ ፍላጐቱን ሲሟላ መልካም አስተዳደር
ሰፍኗል ማለት ይቻላል፡፡
ክፍል ሦስት
የመልካም አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ አመጣጥ፣ ምንነት እና መርሆዎች
3.1. የመልካም አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ አመጣጥና ምንነት
3.1.1. የመልካም አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ ታሪካዊ ዳራ
የመልካም አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ በተለያዩ ምሁራንና የፖለቲካ ተንታኞች ትኩረት ተሠጥቶት መነሳት የጀመረው የመንግስት
ሚና በፖለቲካውም ሆነ በኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ከታመነበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑ በመስኩ የተደረጉ
የተለያዩ ጥናቶች በሰፊው ያትታሉ፡፡ በተለይም መንግስት ከ 16 ኛው ጀምሮ እስከ 21 ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ በአውሮፓ፣
በአሜሪካና በኤስያ እድገት ላይ የልማት፣ ኢንቨስትመንትና ፖሊሲ ማዕከል በመሆን ለፖለቲካና ለኢኮኖሚ እድገት
ከፍተኛውን ሚና መጫወቱ በጥናት ጽሑፎች በሰፊው ተገልጿል፡፡ ለምሳሌ መንግስት በእንግሊዝ በ 18 ኛው፤ በጀርመን፤
በፈረንሳይና በአሜሪካ በ 19 ኛው በጃፓን፤ በኮሪያ፤ በታይዋን፤ በሲንጋፖርና ማሊዢያ እንዲሁም በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን
ለኢኮኖሚ ዕድገት መንግስት የተጫወተው ሚና ክፍተኛ እንደነበር በጥናታዊ ጽሑፎች ተገልጿል (አምስደን ቻንግ፣
2007)፡፡
7
የመልካም አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ ትኩረት ያገኘው በ 1980 ዓ.ም መጨረሻ በአልታሰብ የፖለቲካ ለውጥ ምክንያት መሆኑ
ይገልፃል፡፡ በተለይም በ 1989 የበርሊን ግንብ መፍረስ እና የሶቪየት ህብረት መፈረካከስ ይህንን ተከትሎ የተከሰተው
የምስራቅ ጎራ/ Eastern Block/ የኢኮኖሚና የፖለቲካ አንድነት መክሰም በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ የመንግስት ድርሻ ምን
መሆን እንዳለበት በወቅቱ የመልካም አስተዳደር የውይይት መነሻ መሆኑ በተለያዩ ጥናታዊ ፅሁፎች ተመልክቷል
(ኒኮል፣2010)፡፡
በሌላ በኩል ከቅኝ ግዛት ነጻ መውጣትን ተከትሎ የተዘረጋውና ዕድገትን ለሚያበረታቱ ሴክተሮች ትኩረት የሰጠው ፖሊሲ
(Post Colonization Policy) ውጤታማ ከመሆን ይልቅ የበጀት ውድቀትንና የአስተዳደር ችግርን በማስከተሉ ምክንያት
በዚህ ቀውስ ውስጥ የገቡ ድሃ አገሮችን ችግር ይፈታል ተብሎ በዓለም ባንክና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት የተዘረጋው
የኢኮኖሚ ፖሊሲ (Structural Adjustment Program-SAPs) የበጀት እጥረትን፣ ሙስናንና ኪራይ ሰብሳቢነትን
ከማባባስ በስተቀር ችግሩን መፍታት አልቻለም፡፡ ይህንን ችግር ተከትሎ እ.ኤ.አ በ 1989 “Sub-Saharan Africa-from
Crisis to Sustainable Growth” በሚል ርዕስ የዓለም ባንክ ባካሄደው የጥናት ጽሁፍ ውስጥ መልካም አስተዳደር
የሚለው ጽንሰ ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ መጠቀሱን ጽሁፎች ያስረዳሉ (የአለም ባንክ፣ 1989)፡፡ በመሆኑም የመንግስት
አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ መልካም አስተዳደርን ማስፈን እንደመፍትሄ ሀሳብ
መቅረቡን በተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎች ተጠቅሷል (ኒኮል፣2010፣ዋኢል፣2013)፡፡
በሌላ በኩል መልካም አስተዳደር እንደ አንድ የፐብሊክ ማኔጅመንት ሥርዓት ቀደም ሲል የነበሩ የፐብሊክ
የማኔጅመንት ዘይቤዎች ውስጥ የታዩትን ክፍተቶች ለመድፈን የህዝብ አመራር ሂደቱን ጠብቆ የመጣ ለውጥ
(Public management evolutions and changes) እንደሆነ ይገለጻል (ጆርጅ ማንሊቭ፣2006)፡፡ እንደ
ጸሐፊው አገላለጽ አሮጌው የፐብሊክ አመራር ዘይቤ (Traditional bureacratic public management/
በዋናነት የመንግስት አፈጻጸም ውጤታማና ቀልጣፋ ከማድረግና የኪራይ ሰብሳቢ ፖለቲከኞችና ቢሮክራሲያዊ
አሰራር ችግሮችን ከመፍታት አንጻር ክፍተት የሚታይበት በመሆኑ በነጻ ገበያ ስርዓት እና በመንግስት
8
እንዲፈጠርና ዜጎች በመንግስታቶቻቸው አሰራር እንዳይረኩ ምክንያት ሆኗል፡፡ ይህንን ክፍተት እንዲሞላ
የመልካም አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ እንደ አንድ የፐብሊክ አመራር አማራጭ ብቅ ማለቱንና በአሁኑ ወቅት
የፖለቲካ፣ የሃይማኖትና የኢኮኖሚ ዕድገት ልዩነት ሳይገድበው በሁሉም የዓለም አገራት ዘንድ ትኩረት አግኝቶ
የፐብሊክ አገልግሎትን ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግና የዜጎችን እርካታ ለማረጋገጥ እየተተገበረ ይገኛል፡፡
/ጆርጅ ማንሊቭ፣2006/፡፡
የመልካም አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ አመጣጥ ቀጥሎ በቀረበው ስዕል ጠቅለል ባለ መልኩ ለማስቀመጥ
ተሞክሯል፡፡
በጥቅሉ ሲታይ በአገራት ለመልካም አስተዳደር መጓደል ምክንያት የሆኑ ተግባራት፡-የሙስና መስፋፋት፣
ተጠያቂነት የጎደላቸው መንግስታት መበራከት እና ለሰብዓዊ መብት መከበር ትኩረት አለመስጠት እየተስፋፋ
እና አሳሳቢ እየሆነ በመምጣቱ ለውጥ እንደሚያስፈልግ የዓለም-አቀፍ ፍላጎት መጨመር፣ ዓለም አቀፋዊ
9
የኢኮኖሚ ተቋማት (የዓለም ባንክ፣ የዓለም የገንዘብ ተቋም) መከሰትና ተቋማቱ ብድርና የገንዘብ ድጋፍ
ለመስጠት የመልካም አስተዳዳር ጉዳይን አንደ አንድ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጥ እና ለአንድ አገር ዕድገት
መሰረቱ የኢኮኖሚ እድገት /Economic Growth/ ነው የሚለው አስተሳሰብ እየተሸረሸረና በምትኩ ለኢኮኖሚ
ልማት (Economic Development/ በተለይም ለማህበራዊ እድገትም የማተኮር አስተሳሰብ እየጠነከረ
መምጣት ለጽንሰ ሀሳቡ ጎልቶ መውጣትና በተለያዩ አገራት ትኩረት ተሰጥቶ ተግባራዊ መደረግ ምክንያት
መሆኑን የተለያዩ ጽሑፎች ይገልጻሉ፡፡
መልካም አስተዳደር በርካታ የመልካም መንግስታት ባህሪያትን ያካተተ በመሆኑ የጽንሰ ሀሳቡ እድገትና ታዋቂነት ከመንግስት
መልካም ገፅታ ጋር የተሳሰረ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
በበርካታ ተቋማት የሚጠቀሰው የዓለም ባንክ የመልካም አስተዳደር ትርጉም ግልፅነትና ተጠያቂነትን፣ ቅልጥፍናንና
ውጤታማነትን፤ የህግ የበላይትንና መንግስታት ከህዝባቸው ጋር የሚኖራቸው መልካም የፖለቲካ ግንኙነትን እንደ ዋነኛ
የመልካም አስተዳደር መገለጫ አድርጎ ይወስዳል፡፡ ነገር ግን በአንዳንድ ተመራማሪዎች እይታ ይህ የዓለም ባንክ ትርጉም
አሰጣጥ በጣም የጠበበና መልካም አስተዳደርን በተሟላ መልኩ ሊገልፅ የማይችል በመሆኑ ይተቻል፡፡ ይህም የሆነው የዓለም
ባንክ ለኢኮኖሚ እድገት ጉዳዮች የተለየ ትኩረት በመስጠት ሌሎች ለዘላቂ ልማትና ለዜጎች ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ወሳኝ የሆኑ
መሰረታዊ የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን ከግምት ውስጥ ባለማስገባቱ እንደሆነ ይገለፃል፡፡
በተመሳሳይ መልኩ የመልካም አስተዳደር መረጋገጥ አስፈላጊነትን አጉልቶ በማሳየት የሚታወቀው የተባበሩት መንግስታት
የልማት ፕሮግራም የህዝብ ተሳትፎን፣ ግልፅነትን፣ ተጠያቂነትን፣ ውጤታማነትን ፍትሐዊነትንና ሌሎች ጠቃሚ ባህሪያትን
መልካም አስተዳደር መገለጫዎች ሲል አስቀምጧቸዋል፡፡
እንዲሁም ተጠያቂነትን ማረጋገጥ፣ የመንግስት ፖሊሲዎችንና አሰራሮችን ለህዝብ ግልጽ ማድረግ፣ ሙስናን
በጽናት መዋጋት፣ በየደረጃው የህዝብ ተሳትፎን ማረጋገጥና ግልጽና በሁሉም አካባቢ ዜጎች ላይ በወጥነት
የሚተገበሩ ህጋዊና ፍትሐዊ አሰራሮችን መዘርጋት መልካም አስተዳደርን ለማስፈን አስፈላጊ ጉዳዮች
መሆናቸውን የአፍሪካ ልማት ባንክ አስቀምጧል፡፡ (ኢንተርናሽናል ፈንድ ፎር አግሪካልቸራል
ዴቬሎፕመንት፣1999) ፡፡
10
ከላይ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት የተቀመጡ የመልካም አስተዳደር ትረጓሜዎችና ባህሪያት እንደተጠበቁ ሆኖ መንግስት
መልካም አስተዳደርን ለማስፈን በዘላቂ ልማትና የዜጎች ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መረጋገጥ ላይ ከፍተኛ ቁርጠኝነት ያለው
መሆን ይኖርበታል፡፡ በሌላ አነጋገር መንግስት ድህነትን ለመቀነስ የሚረባረብ፤ የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ የሚፈጥርና
መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለዜጋው የሚያቀርብ መሆን ይኖርበታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ዳንኤል ኩፍማን የተባለ ጸሐፊ
መልካም አስተዳደርን ተግባራዊ ለማድረግ ተጠያቂነትን፣ የፖለቲካ መረጋጋትን፣ ውጤታማነትን፣ የህግ የበላይነትን ማስፈንና
ሙስናን በቁጥጥር ሥር ማዋል አስፈላጊ መሆኑን አብራርቷል፡፡
የመልካም አስተዳደር ትርጉም ከላይ በተገለጸው ብቻ የሚወሰን አይደለም፡፡ ይልቁንም እንደ ሀገራት አስተሳሰብና የፖለቲካ
ርዕዮተ ዓለም (ideology) በተለያየ መልኩ የሚተረጎም ነው፡፡ በተለይ አገሮች የሚከተሉት የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም
ከመልካም አስተዳደር አኳያ በዋነኛነት በሁለት ተከፍሎ የሚታይ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር አንደኛው በኒዮ-ሊብራል የፖለቲካ
ርዕዮተ ዓለም አመለካከት፤ ሌላው ደግሞ የልማታዊ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም አስተሳሰብ ላይ የተመሰረተው እንደሆነ
የተለያዩ ጽሁፎች ያስረዳሉ፡፡ በዚህ መሰረት ለመልካም አስተዳደር ትርጉም ከመስጠት ጋር በተያያዘ ጽንሰ ሀሳብ ትርጉም ላይ
የሁለቱን ጽንሰ ሃሳቦች መሰረታዊ ልዩነቶችና የልዩነቶቹን ምክንያት መዳሰስ ጠቃሚ ይሆናል፡፡
በኒዮ-ሊበራሊዝም ርዕዮተ ዓለም አተረጓጎም መልካም አስተዳደር ማለት የህግ የበላይነትን ማረጋገጥና ለነፃ ገበያ የተመቻቸ
ተቋማዊ ሁኔታ መፍጠር ነው፡፡ በመሆኑም መልካም አስተዳደርን የሚለኩት ለነጻ ገበያ ሥርዓቱ መጎልበት አመቺ በሆኑ የህግ
ማእቀፎች፣ ለግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ በሚሰጡ የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጣፌ ውጤታማነትና በመሳሰሉት የመልካም አስተዳደር
መርሆዎች ላይ በማተኮር ነው፡፡
ይሁን እንጂ በዚህ ርዕዮተ ዓለም ትርጉም ውስጥ ትኩረት ያለተሰጣቸው ሌሎች ለመልካም አስተዳደር መረጋጋጥ ወሳኝ የሆኑ
መርሆዎች አሉ፡፡ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ነባራዊ ሁኔታ አንጻር አንገብጋቢ የሆኑና ፍትሐዊነት፣ እኩል ተጠቃሚነት፣
ድህነት ቅነሳ፣ በድህነት ለሚኖሩ ህዝቦች ጥበቃና ከለላ፤ የአናሳዎች ተሳትፎና ተጠቃሚነት እና የሴቶችን እኩልነትና ፍትሐዊ
ተጠቃሚነት እና ሌሎች መሰል የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በመሰረታዊ ባህሪያቸው የመንግስትን አዎንታዊ ሚና የሚሹ
በመሆናቸው በኒዮሊብራሊዝም ርዕዮተ ዓለም እይታ አጥጋቢ ምላሽ ሊያገኙ አይችሉም፡፡ የኒዮሊበራሊዝም ርዕዮተ ዓለም
የመልካም አስተዳደር ትርጉም ሁለት መነሻዎች አሉት፡፡ የመጀመሪያውና ዋነኛው መንግስት በኢኮኖሚው ውስጥ
የሚኖረውን ሚና ማኮሰስ ወይም ማቀጨጭ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ዓለም አቀፍ ፖሊሲዎችንና የፖሊሲ ማዕቀፎችን
በማስቀመጥና ሞዴል የተባሉ ሀገሮች እንዲከተሉት በማድረግ የርዕዮተ ዓለሙን አስተሳሰብ በሌሎች ላይ ለመጫን ነው፡፡
11
ተፈፃሚ እንዲያደርጉ የተለያዩ ጫናዎችን በመፍጠር ነው፡፡ ይህን ተፈፃሚ በማያደርጉት ሀገሮች ላይ ደግሞ በውስጥ
ጉዳዮቻቸው ጭምር በሚደረግ ጣልቃ ገብነት የመልካም አስተዳደር አጀንዳን መሳሪያና ሽፋን ማድረግን አንደ አመቺ ስልት
ይጠቀማል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የዚህ ርዕዮተ ዓለም ጫና በዚህ ብቻ ሳይወሰን በእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች እና በተናጠል
እንዲሁም በጋራ የመንግስታት ስምምነቶች ላይ ጭምር እንደሚንፀባረቅ ሌሎች በመስኩ ጥናት ያካሄዱ ተመራማሪዎችም
ይገልፃሉ፡፡
በመሆኑም እንደ ሪታ አብረሃምሴን ገለጻ ኒዮ-ሊብራሊዝም የራሱን ፍላጎት በሌሎች ላይ ለመጫን የመልካም አስተዳደር
አጀንዳን ከመጠቀምም ባሻገር ከመንግስት ጣልቃ ገብነት ነፃ የሆነ የኢኮኖሚ አስተሳሰብ ፍጹም የበላይነት እንዲያገኝ
የማድረግ ዓላማ ያለው ርዕዮተ ዓለም ነው፡፡
ሌላው የኒዮሊብራሊዝም ስልት የሲቪል ማህበራት ተሳትፎን በሚመለከት መልካም አስተዳደርን እንደ መሳሪያ የመጠቀም
አስተሳሰብ ነው። በዚህ ረገድ ልማታዊ መንግስታትም ማህበራትና ሌሎች የህዝብ አደረጃጀቶች በልማትና በዴሞክራሲያዊ
ስርዓት ግንባታ ላይ ሰፊና ዙሪያ መለስ ተሳትፎ በማድረግ የውጤቱ ፍትሃዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑና መልካም አሰስተዳደር
የማስፈን ሂደቱን እንዲያጠናክሩ በጥብቅ እምነት ይዘው የሚተገብሩበትን አቅጣጫ የሚከተሉ ሲሆን የኒዮሊብራሊዝም አቋም
ግን በመሰረቱ ከዚህ የተለየ ነው፡፡ ይኼውም በስመ ሲቪል ማህበራት ተሳትፎ መላ ህዝቡ ሳይሆን የርዕዮተ ዓለሙ ጉዳይ
አስፈፃሚ የሆኑ ጥቂት ተፅዕኖ ፈጣሪ ድርጅቶች ብቻ የጎላ ሚና እንዲኖራቸውና በተለይ በደሃ አገራት መንግስታት ላይ ተፅዕኖ
እንዲያሳርፉ የሚያደርግ መሆኑ ነው፡፡ በመሆኑም በእነዚህ አገራት ጥቂት ተፅዕኖ ፈጣሪ ማህበራት ሁሉንም ነገር
እንዲቆጣጠሩ በማድረግ በታዳጊ ሀገራት መንግስታት በኢኮኖሚውም ይሁን በፖለቲካው የሚጫወቱት አዎንታዊ ሚና
እንዲቀንስ ታስቦ የሚሰራ ስራ መሆኑን በመስኩ የተካሄዱ ጥናቶች ያብራራሉ፡፡
ስለሆነም ከላይ እንደተገለፀው በኒዮሊብራሊዝም ርእዮተ ዓለም መልካም አስተዳደር ሲቀነቀን የፍትሐዊነትንና የእኩልነት
መርሆዎች፣ ድህነትን መቀነስና በድህነት ላይ የሚደረግ ትግል፣ ድሃዎችን ማገዝ፣ የመንግስት አዎንታዊ ሚና፣ ዴሞክራሲ
ለሁሉም እና የመሳሰሉት ጉዳዮች ትኩረት አይሰጣቸውም፡፡ በመሆኑም በዚህ ርእዮተ ዓለም መልካም አስተዳደርን የማስፈን
ጉዳይ በርካታውን የህረተሰብ ክፍል በተለይ ድሃውን ያገለለ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ሊዳስሳቸው ያልቻለ ትርጉም
ነው፡፡
ጠቅለል ተደርጎ ሲታይ የኒዮሊብራሊዝም የመልካም አስተዳደር ትርጉም እጅግ የጠበበና የህዝቦችን መሰረታዊ ጥያቄዎች
ሊመልስ የማይችል ነው፡፡ ከዚህም በላይ በልማትና መልካም አስተዳደር፤ በዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር መካከል
ያለውን ቀጥተኛ ዝምድናና ትስስር እንዲሁም የእነዚህን መስተጋብርና ጥምረት የሚያጠናክርና ህዝቦች ተጠቃሚ
የሚሆኑበትን ሁኔታ የሚያመቻች አይደለም፡፡
በሌላ በኩል የልማታዊ መንግስት ተልዕኮ የኪራይ ሰብሳቢነት ፖለቲካና ኢኮኖሚ የያዘውን የበላይነት ሁኔታ ደረጃ በደረጃ
የመቀየርና የልማታዊ አስተሳሰብን የበላይነት ማረጋገጥ፤ ለልማት ማነቆ የሆኑ የገበያ ጉድለቶችን በተመረጠና ውጤታማ በሆነ
12
አኳኋን ጣልቃ በመግባት ማስተካከልና የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው፡፡ በመሆኑም የልማታዊ መንግስት የመልካም
አስተዳደር እይታ እና የትኩረት ነጥቦች ከዚህ ተልእኮ የመነጩ ናቸው፡፡
በዚሁ መሰረት የልማታዊ መንግስት አስተሳሰብ መሰረታዊ በሆኑ እንደ ፍትሐዊነት፣ እኩል ተጠቃሚነት፣ ድህነት ቅነሳ፣
በድህነት ለሚኖሩ ህዝቦች ጥበቃና ከለላ፤ የአናሳዎች ተሳትፎና ተጠቃሚነት፣ የሴቶች እኩልነትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና
ሌሎች መሰል የመልካም አስተዳደር መርሆዎች መረጋገጥ ላይ ያተኩራል፡፡ በመሆኑም በባህሪያቸው የመንግስትን የጎላ ሚና
የሚሹ በዋነኝነት የህዝቦች ንቁ ተሳትፎ፤ ፍትሐዊ ተጠቃሚነትና ሌሎች መሰል መርሆዎች መረጋገጥን የመልካም አስተዳደር
መስፈን መለኪያ አድርጎ ይወስዳል፡፡
በዚህ ረገድ ልማታዊ መንግስታት ለህዝቦች ተሳትፎና ተጠቃሚነት መረጋገጥ በሚሰጡት ከፍተኛ ግምት ልማታዊ ማህበራትና
ሌሎች የህዝብ አደረጃጀቶች በልማትና በዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ላይ ሰፊና ዙሪያ መለስ ተሳትፎ በማድረግ የውጤቱ
ፍትሐዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑና መልካም አሰስተዳደር የማስፈን ሂደቱን እንዲያጠናክሩ በጥብቅ እምነት ይዘው ይተገብራሉ፡፡
ልማታዊ መንግስት በመልካም አስተዳደር አጀንዳው ውስጥ ከኒዮ-ሊብራሊዝም በተለየ ሁኔታ ፍትሐዊነት፣ እኩልነት፣
ድህነት ቅነሳና በድህነት ላይ የሚደረግ ትግልን ብሎም ድሃዎችን ማገዝን ለመሳሰሉ ጉዳዮች ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል፡፡
በመሆኑም በልማታዊ መንግስት አስተሳሰብ መልካም አስተዳደር ማለት የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ንቁ ተሳትፎና ፍትሐዊ
ተጠቃሚነት የሚረጋገጥበት፣ በመንግስት የተመረጠ ጣልቃ ገብነት የገበያ ጉድለት የሚሞላበት፤ የልማታዊ ባለሃብቱ ተሳትፎ
መጎልበትና ዘላቂ ልማት እውን የሚደረግበት ስርዓት ነው፡፡ ስለዚህ በልማታዊ መንግስት አስተሳሰብ በልማትና መልካም
አስተዳደር፤ በዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር መካከል ያለውን ቀጥተኛ ዝምድናና ትስስር እንዲሁም የእነዚህን
መስተጋብርና ጥምረት የሚያጠናክርና ህዝቦች ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ሁኔታ የሚያመቻች አስተሳሰብ ነው፡፡
13
ዳንኤል ኩፍማን Human Rights and Governance: The Empirical Challenge በሚል ርእስ ባቀረበው ጽሁፍ
ላይ እንዳብራራው በመልካም አስተዳደርና በልማት መካከል ያለው ዝምድናና ትስስር ጠንካራ መሆኑን አመላክቷል፡፡
በኩፍማን ጽሁፉ እንደተብራራው መልካም አስተዳደር ቀጣይነት ያለው ኢኮኖሚያዊ እድገትንና ማህበራዊ ልማትን
በማረጋገጥ ረገድ የማይተካ ሚና አለው፡፡ ከዚህ ጋራ ተያይዞ በዓለም ባንክ የተካሄዱ በርካታ ጥናቶች እንዳረጋገጡት መልካም
አስተዳደር ለኢኮኖሚያዊ እድገትና ማህበራዊ ልማት እንደጠቃሚ መሳሪያ የሚታይ ብቻ ሳይሆን የግድ የሚያስፈልግ ቅድመ
ሁኔታ ጭምርም ነው፡፡ በመሆኑም በአሁኑ ወቅት መልካም አስተዳደር ሲባል የሚያመለክተው ጉዳይ መንግስት በልማት ላይ
የተጫወተውን ሚና እና የአፈጻጸም ምዘናውን ብቻ ሳይሆን ልማቱ የመጣበትን የጠራ መንገድ ጭምር ነው፡፡ በአጠቃላይ
ሲታይ በአሁኑ ወቅት በተመራማሪዎች እና በዓለም ዓቀፍ ተቋማት የተደረሰበት የጋራ ስምምነት መልካም አስተዳደር ለልማት
እጅግ አስፈላጊና ጠቃሚ መሆኑ ነው፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በመስኩ በተደረጉ ጥናቶች መልካም ያልሆነ አስተዳደር ደካማ ተቋማትና መዋቅር እንዲፈጠሩ በማድረግ
ዘላቂ ልማትና የዜጎች ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን እንደሚያቀጭጭ እና ድህነትን ለመቀነስ የሚደረጉ ጥረቶችን እንደሚያደናቅፍ
ተረጋግጧል፡፡ በአንጻሩ የመልካም አስተዳደር መስፈን ድህነትን፣ የህፃናት ሞትን፣ ማይምነትን፣ ወዘተ በመቀነስና በማጥፋት
የድሃውን ህብረተሰብ የኑሮ ሁኔታ ለመቀየር እንደሚያግዝ ጥናቶች ያረጋግጣሉ፡፡
በመሆኑም ከሽግግሩ ወቅት ጀምሮ መንግስት በአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ መልካም አስተዳደር በሌለበት ፈጣንና ዘላቂ ልማት
ማረጋገጥም ሆነ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት የማይታሰብ መሆኑን በመረዳት የልማት፣ የሰላምና የዴሞክራሲ አጀንዳዎችን
ሲተገብር ቆይቷል፡፡
መልካም አስተዳደርን በማስፈን ሂደት ውስጥ አንዱና ዋነኛው ቅድመ ሁኔታ የዜጎችን የልማት፣ የሰላምና የዴሞክራሲ ጥያቄዎችን
በብቃት ለመመለስ የሚያስችሉ የህግና የፖሊሲ ማዕቀፎችን ማስቀመጥና ለተግባራዊነታቸው መረባረብ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ ገና ከጅምሩ
በሽግግሩ ቻርተር እና ይህን ተከትሎ በጸደቀው ህገ-መንግስት መልካም አስተዳደርን የማስፈን ጉዳይ ትኩረት እንዲያገኝ ተደርጓል፡፡
በመሆኑም የህጎች ሁሉ የበላይ የሆነው ህገ-መንግስት መልካም አስተዳደርን ከማስፈን አንጻር የህዝቦች ሉዓላዊነት፣ የህግ የበላይት፣
የመንግስት አሰራር ተጠያቂነት፣ ፍትሐዊ የልማት ተጠቃሚነት፣ ቀልጣፋ የመንግስት አገልግሎት የማግኘት መብቶችን አካቶ እንዲይዝ
ተደርጓል፡፡
14
ሌላው መልካም አስተዳደርን በማስፈን ሂደት ውስጥ ከተካሄዱት ስር ነቀል ለውጦች መካከል አሀዳዊ
የነበረውን የመንግስት አወቃቀር የህዝብ አሰፋፈርን፣ ቋንቋን እና ማንነትን መሰረት ወዳደረገ ፌደራላዊ ያልተማከለ
የመንግስት አወቃቀር መቀየር ነው፡፡ ይህም በአገራችን የሚገኙ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ተሳትፎን፣ እኩል ተጠቃሚነትንና የራስን
ዕድል ራስ የመወሰን መብትን በማረጋገጥ መልካም አስተዳደርን በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥ አስችሏል፡፡ በአገራችን የተዘረጋው ያልተማከለ
አስተዳደር ዜጎች በሚደረገው የአካባቢ አስተዳደርና ልማት ላይ ያላቸው ተሳትፎ የበለጠ እንዲጨምር፣ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና
ፖለቲካዊ ጉዳዮች ፍትሐዊ ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥ፣ ብሔራዊ አንድነት እንዲጎለብትና በየደረጃው ግልጽ፣ ጥራት ያለው፣
የተቀላጠፈና ውጤታማ የመንግስት የአግልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር በማድረግ መንግስት መልካም አስተዳደርን በማስፈን ረገድ ጉልህ
ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡
በሌላ በኩል መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ጉልህ ሚና የሚጫወቱ የተለያዩ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችንና ፕሮግራሞችን በመቅረጽ
እና ተግባራዊ እንዲሆኑ በማድረግ መንግስት ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ ይገኛል፡፡ ከነዚህ ውስጥ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲያዊ ሥርአት
ግንባታ ጉዳዮች እና የማስፈፀም አቅም ግንባታ ስትራቴጂና ኘሮግራም ዋንኞቹ ናቸው፡፡
በማስፈፀም አቅም ግንባታ ስትራቴጂው ላይ በመመስረት የሰው ኃይሉን በተግባር ሂደት ለማብቃትና መልካም
አስተዳደርን ለማስፈን አሰራርና አደረጃጀትን ማሻሻል የሚያስችል የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራም ቀርጾ ተግባራዊ
በማድረግ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
በኢትዮጵያ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ጉዳዮች በሚለው ጽሑፍ መልካም አስተዳደር በሀገራችን ፈጣን
ልማት ለማረጋገጥና የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታን እውን ለማድረግ እጅግ ተፈላጊ ጉዳይ እንደሆነ
ይገልፃል፡፡ በዚህ የፖሊሲ ሰነድ እንደተገለፀው ምንም ዓይነት የተስተካከለ ፖሊሲ ቢነደፍም መልካም
አስተዳደር ካልሰፈነ ዘላቂነት ያለው ልማትና የኢኮኖሚ ዕድገት ማረጋገጥ እንደማይቻል ግልፅ ነው፡፡
ስለዚህ በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ መልካም አስተዳደርን ማስፈን ከኢኮኖሚ ግንባታና ከዴሞክራሲ ስርዓት መስፈን ጋር
ቀጥተኛ ግኑኝነት ያለው በመሆኑ ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ ባሉት ፖሊሲዎች ላይ በግልጽ ተመላክቷል፡፡ ይህንን
አስመልክቶ በ 1994 የታተመው በኢትዮጵያ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ጉዳዮች በሚለው የፖሊሲ ሰነድ ገጽ 82 ላይ
እንደሚከተለው ተብራርቷል፡፡
15
በአንድ ሀገር ውስጥ መልካም አስተደደር እንዲኖር የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መኖር ይገባዋል፡፡ ይሁንና
የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ባለበት ሁሉ መልካም አስተዳደር ይኖራል ማለት አይደለም፡፡ የዴሞክራሲያዊ
ስርዓት ባለበት ሁሉ ቀልጣፋ የመንግስት አሰራር ይኖራል ማለት አይደለም፡፡ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት
ባለበት ሁሉ ከሙስና የጸዳ መንግስት ይኖራል ማለት አይደለም፡፡ ዴሞክራሲ ባለበት ሁሉ ህዝቡ
በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበት ፈጣን ልማት ይኖራል ማለት አይደለም፡፡ ቀልጣፋ የመንግስት አሰራር፣
ከሙስና የጸዳና ሙስና በቁጥጥር ስር የገባበት፣ ለፈጣን ዕድገት የተመቸ ሁኔታ የሚፈጥር መንግስት
ሲኖር ብቻ ነው መልካም አስተዳደር ሊኖር የሚችለው፡፡ በአገራችን ሁለቱም በጣምራ ካልተገኙ
ዴሞክራሲ አገራችንን ከጠቅላላ ጥፋት ሊታደግ አይችልም፡፡
መልካም አስተዳደር በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ልዩ ትኩረት የተሰጠውና የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰድ
መሆኑን ከላይ የቀረበው ሃሳብ በግልጽ ያስረዳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ መልካም አስተዳደር በአገራችን ህዝቡ በየደረጃው
ተጠቃሚ የሚሆንበት ፈጣን ልማት ለማምጣትና የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡ በሌላ በኩል
በአገራችን ፈጣን ልማት መረጋገጥ የሚችለውና የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ስር እየሰደደና እየጎለበተ የሚሄደው ህዝቡን
በማሳተፍና የጋራ መግባባት እየፈጠሩ በመሄድ ብቻ ነው፡፡
የዴሞክራሲ ሥርዓት ባለበት ሁሉ መልካም አስተዳደር ይኖራል ማለት እንዳልሆነ በበርካታ የላቲን አሜሪካ ሃገሮች በግልፅ
የተስተዋለ ጉዳይ ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ 1980 ዎቹና በ 1990 ዎቹ ወደ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የተሸጋገሩት የላቲን አሜሪካ ሀገሮች
ብልሹ አሰራርን፤ ሙስናንና ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ ተስኗቸው መታየቱ ዴሞክራሲ ብቻውን መልካም አስተዳደርን ሊያሰፍን
እንደማይችል በተግባር ተረጋግጧል፡፡ በአንጻሩ ዴሞክራሲ ባልሰፈነበት መልካም አስተዳደርን ማረጋገጥ እንደሚቻል በቻይና
የልማት ስኬት ዙሪያ በተካሄዱ ጥናቶች በተደጋጋሚ ተመላክቷል፡፡ እንደ ጥናቶቹ ግኝት በቻይና የመንግስት አሠራርን
ቀልጣፋ ማድግ፤ ከሞላ ጎደል ሙስናን በቁጥጥር ሥር ማዋል ፤ የህዝቡን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥና የመንግስት
አገልግሎት አሰጣጥን ውጤታማ ማድረግ መቻሉ፡፡ አንዳንድ በዴሞክራሲ ልምድ አዳብረዋል ተብለው ከሚገለፁ ሃገራት
የተሻለ መልካም አስተዳደር እንዳለ ተረጋግጧል፡፡ በሚል አብራርተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ፖሊሲዎችና ፕሮግራሞች ተገልጾ የምናገኘው ጉዳይ ግን በመሰረቱ ከሁለቱም አስተሳሰቦች የተለየ ነው፡፡
በመሆኑም ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር ሳይነጣጠሉ ሁለቱንም በጣምራ የማስኬድ አቅጣጫ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡
ዴሞክራሲ መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ መሠረት ሲሆን መልካም አስተዳደር ደግሞ ቀልጣፋ
የመንግስት አሠራርን፣ ፍትሐዊነትንና እኩልነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው፡፡ በመሆኑም መልካም አስተዳደርን በአገራችን
ማስፈን የሚቻለው ፈጣንና ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ልማትን በማረጋገጥ ህዝቡን ተጠቃሚ በማድረግና ዴሞክራሲ ስር እንዲሰድ
ጠንክሮ በመስራት ነው፡፡
በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ መልካም አስተዳደርን የማስፈን ጉዳይ ከአገልግሎት አሰጣጥ ባሻገር ሁሉንም ዜጋ
የሚያሳትፍ፤ የሁሉንም ዜጎች ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፍትሐዊ የሆነ ልማትንና ዴሞክራሲን በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች
የማስፈን አጀንዳና የህልውና ጉዳይ ጭምር ነው፡፡ በመሆኑም ዴሞክራሲም ሆነ የመልካም አስተዳደር ሥርአት በተሟላ
16
ሁኔታ ተግባራዊ የሚሆነው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መሰረት ሲፈጠር፣ የዴሞክራሲ ባህል እና አስተሳሰብ
ሲሰርጽና ለዚህ የሚሆኑ ተቋማትን መፍጠርና ማጠናከር ሲቻል ነው፡፡
በአጠቃላይ በአገራችን መልካም አስተዳደር የሚረጋገጠው የህዝቡን የልማት ፍላጎት ደረጃ በደረጃ
የሚያሟላና ፍትሃዊ ተጠቃሚነቱን ቀጣይነት ባለው መልኩ ማረጋገጥ የሚያስችል የተስተካከለ የልማትና
የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ፖሊሲ፣ ፍትሐዊና ቀልጣፋ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ፣ የግልፅነትና
የተጠያቂነት እንዲሁም ሙስናን በቁጥጥር ስር ማዋል የሚያስችል አሰራርን በውጤታማነት መተግመር ሲቻል ነው፡፡
3.4. የመልካም አስተዳደር መርሆዎች
የተለያዩ ጸሐፊዎች የተለያዩ የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን ያስቀምጣሉ፡፡ በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ስለመልካም አስተዳደር
ትርጓሜ መለያየት በመንስኤነት የተሰጠው ማብራሪያ ለመርሆዎቹም የሚሆን ነው፡፡ በሌላ አባባል እንደ መልካም
አስተዳደር ትርጓሜ ሁሉ መርሆዎቹም እንደ የመንግሰታትና ተቋማት አስተሳሰብ የሚተረጎሙ ነው፡፡ በተለያዩ ተቋማት እይታ
የመልካም አስተዳደር መርሆ ተብለው የተወሰዱትን ቀጥሎ ባለው ሰንጠረዥ ለአብነት ማየት ተገቢ ይሆናል፡፡
የኢኮኖሚ
የአፍሪካ የአቅም
የአፍሪካ የአለም የተባበሩት ትብብርና ከባህር ማዶ
ተ/ የመልካም አስተዳደር ግንባታ የመርሆው
ልማት ባንክ መንግስታት ልማት ልማት ተቋም
ቁ መርሆዎች ፋውንዴሽን ትርጉም
ባንክ (WB) (UN) ድርጅት (ODI)
(ACBF)
(OECD)
ተጠያቂነት
1 X x x x x x
(Accountability
ውጤታማነት
2 X x x x
(Effectiveness)
ውስን ሀብትን
ቅልጥፍና በቁጠባ መጠቀምና
3 X x x x x
(Efficiency) የተሻለ ውጤት
ማስመዝገብ
የውሳኔዎች
ግልጽነት
4 X x x x x x ግልጽነትና ክፍት
( Transparency)
መሆን
5 (Openness) X x x x
ተጠያቂነት
6 (Accountability X x x x x x
ውጤታማነት
7 X x x x
(Effectiveness)
ቅልጥፍና x
8 X x x x
(Efficiency)
ግልጽነት x
9 X x x x x
( Transparency)
10 (Openness) X x x x
17
የኢኮኖሚ
የአፍሪካ የአቅም
የአፍሪካ የአለም የተባበሩት ትብብርና ከባህር ማዶ
ተ/ የመልካም አስተዳደር ግንባታ የመርሆው
ልማት ባንክ መንግስታት ልማት ልማት ተቋም
ቁ መርሆዎች ፋውንዴሽን ትርጉም
ባንክ (WB) (UN) ድርጅት (ODI)
(ACBF)
(OECD)
ደንቦችና ህጎች
( Decency) x በዜጋው ላይ ጉዳት
11 x
ሳይሰከትሉ
1 ተግባራዊ ማድረግ
ህጎችና ደንቦች
ፍትሀዊነት በሁሉም ዜጋ ላይ
12 (Fairness) x x በእኩል ተግባራዊ
ማድረግ
ድህነት ቅነሳ(Poverty x x x
13
Reduction)
ሙስናን በጽናት መዋጋት
x
14 (Fighting
Corruption)
ድምር (Sum of 6
15 10 6 8 10 7
Principles)
Source. Adapted from Van Doeveren (2011). Van Doeveren, V. (2011). Rethinking governance identifying common
principles. Public Integrity, 13(4), 301–318.
በአጠቃላይ ሲታይ የተለያዩ ተቋማትና ፀሐፊዎች በዓይነትም ሆነ በቁጥር የተለያዩ የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን
ቢያስቀምጡም በመሰረታዊ ይዘታቸው ተመሳሳይ እንደሆኑ የተለያዩ ጽሁፎች ያስቀምጣሉ፡፡
ከዚህ አንጻር ‹‹የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ትግልና አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› በሚል ርእስ የተጻፈው ጽሁፍ፡- (ሀ)
ተሳትፎአዊነት፣ (ለ) የጋራ መግባባት፣ (ሐ) ቶሎ ምላሽ መስጠት፣ (መ) ግልፅነት፣ (ሰ) ተጠያቂነት፣ (ረ) ፍትሐዊነት፣ (ቀ)
የህግ የበላይነት መከተል እና (በ) ቀልጣፋና ውጤታማነት የመልካም አስተዳደር መርሆዎች መሆናቸውን የገጠር መልካም
አስተዳደር ፓኬጅንና ሌሎች የታወቁ ጸሐፊዎችን ጠቅሶ ያስቀምጣል (የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ትግልና አብዮታዊ
ዲሞክራሲ ፣1999፣ገጽ 107) ፡፡
በተመሳሳይ የከተማ አስተዳደር ፓኬጆችን የሚያብራራው ጽሑፍ (ሀ) ዘላቂነት ያለው የከተማ ልማትን ማረጋገጥ፣ (ለ)
ሥልጣንና ኃላፊነት እስከ ዝቅተኛው የአስተዳደር እርከን ማውረድ፣ (ሐ) ፍትሐዊ የሃብት አጠቃቀም እንዲኖር
18
ማድረግ፣ (መ) ቀልጣፋና ውጤታማ የሆነ አገልግሎት ማቅረብ፣ (ሰ) ግልፅነትና ተጠያቂነትን ማስፈን፣ (ረ) የህዝብ
ተሳትፎን ማሻሻልና የጋራ መግባባትን መፍጠር እና (ቀ) የህግ የበላይነትና የደህንነት ዋስትና ማረጋገጥ የሚሏቸው የመልካም አስተዳደር
መርሆዎች መሆናቸውን ዩኤን ሀቢታትን ያብራራል፡፡
በሁለቱም ሰነዶች የጋራ የሆኑትና ከአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር እንደ መልካም አስተዳደር መርሆዎች
ተወስደው ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉት መርሆዎች የህግ የበላይነት፣ ተሳትፎአዊነት፣ የጋራ መግባባት፣ ፈጣን
ምላሽ መስጠት፣ ግልፅነት፣ ተጠያቂነት፣ ፍትሐዊነት እንዲሁም ቀልጣፋነትና ውጤታማነት ናቸው፡፡
መርሆዎቹም እርስ በርሳቸው የተቆራኙና አንዱ ያለአንዱ ትርጉም የማይኖራቸው መሰረተ ሀሳቦች ናቸው፡፡
ይህንኑ ቁርኝታቸውን ከታች በቀረበው ስዕል ለማሳየት ተሞክሯል፡፡
19
በመሆኑም በአገራችን መልካም አስተዳደርን በተሟላ ሁኔታ ለማስፈን ሁሉም መርሆዎች እኩል ትኩረት
ተሰጥቷቸው ተሳስረውና ተመጋግበው ተግባራዊ በመደረግ ላይ ናቸው፡፡ ከዚህ ባሻገር መርሆዎቹ
ከዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታና ከልማት ጋር ተያይዘው የሚፈጸሙ ናቸው፡፡ የእያንዳንዱ መርሆ ምንነት
እንደሚከተለው በዝርዝር ቀርቧል፡፡
3.4.1. ተሳትፏዊነት
የመጀመሪያው የመልካም አስተዳደር መገለጫ ህዝባዊ ተሳትፎን ማረጋገጥ ነው፡፡ ያለ ህዝብ ተሳትፎ መልካም
አስተዳደር ሊረጋገጥ አይችልም፡፡ ስለዚህ በመንግሥታዊ አስተዳደር ውስጥ ህዝቡ በሚመለከተው ጉዳይ ላይ
ተሳትፎ ሊኖረው ይገባል፡፡ የተሳትፎው ዓይነትም በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ሊሆን ይችላል፡፡ መንግሥታዊ
አገልግሎት በሚሰጥባቸው ሁኔታዎች የሚመለከታቸው ሁሉ ከዕቅድ ጀምሮ በሁሉም የአመራር ዑደቶች
20
በባለቤትነት መንፈስ ሊሳተፉ ይገባል፡፡ እነዚህ የሚመለከታቸው አካላት ሃሳብ ከማመንጨት ጀምሮ እስከ
አተገባበሩ በሚገባ የተሳተፉበት ጉዳይ የመሳካት ዕድሉ እጅግ ከፍተኛ ይሆናል፡፡ ለዚህ መገለጫ ስኬትም
የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ተገቢ አደረጃጀትና አግባብ ፈጥረው ህዝቡ የሚሳተፍበትን መንገድ
መፍጠርና በተገቢው መንገድ መፈፀም ይጠበቅባቸዋል፡፡ በመሆኑም ከህዝብ የተነጠለ መንግሥታዊ አገልግሎተ
አሰጣጥ ስለማይኖ ህዝቡ ተደራጅቶ በመንግሥታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ አስተያየት የሚሰጥበት፣ ዕቅድን
የሚተችበትና አፈፃፀምን የሚገመግምበት ሥርዓት ሊዘረጋ ይገባል፡፡ በአጭሩ ተሳትፏዊነት ማለት
የሚመለከታቸው አካላት በሚገባ በመሳተፍ ባለቤት መሆን መቻላቸው የሚለካበት መርህ ነው፡፡
የጋራ መግባባት ማለት በጋራ ራዕይ፣ ግብ እና መርህ ላይ የጋራ አመለካከት በመያዝ ለጋራ ጉዞ የጋራ መነሻ
የሚሰጥ መርህ ነው፡፡ በመሆኑም በመንግሥታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ድርሻ ያላቸው አካላት በሙሉ
በአገራዊ ራዕይ፣ ግቦች፣ አፈጻጸሞችና ውጤቶች ላይ የጋራ መግባባት ላይ ሊደርሱ ይገባል፡፡ ነገር ግን ሁል ጊዜ
በሁሉም ጉዳዩች መግባባት ይኖራል ማለት አይደለም፡፡ በጋራ በሚፈፀም ጉዳይ ዙሪያ ልዩነቶች መፈጠራቸው
አይቀርም፡፡ በዚህ ጊዜ የሚፈጠሩ ልዩነቶችን በሠላማዊ መንገድ በማስተናገድና ለአብዛኛው ድምፅ በመገዛት
ለተግባራዊነቱ መትጋት የግድ አስፈላጊ ነው፡፡
የጋራ መግባባት ማለት መሠረታዊ የዴሞክራሲያዊ መርሆዎች ተጠብቀው፤ በአጠቃላይ ጉዳዮች ላይ ግልፅነት
ተፈጥሮና ሁሉም ድርሻውን በሚገባ ተረድቶ ወደ ተግባር ምዕራፍ የሚገባበትን ሁኔታ መፍጠር ማለት ነው፡፡
በጋራ መግባባት መታለፍ የሌለበት ጉዳይ የሁሉንም አካል የሚያስማማ ወሳኝ በሆነው ጉዳይ ላይ መስማማት
የግድ ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ የሀገራችንን ህዳሴ የማረጋገጥ፤ ድህነትን ከሀገራችን በመሰረታዊነት የመቀነስና
የማጥፋት አጀንዳ፣ የዴሞክራሲያዊ ሥርአት ግንባታ፣ ሃገራዊ ሰንደቅ ዓላማና የመሳሰሉት ሁሉም ዜጋ
ሊስማማባቸው የሚገቡ ጉዳዮች ናቸው፡፡
21
ሁል ጊዜ ጥያቄ የሚያነሱ አካላት በሚፈልጉት መንገድ ምላሽ ያገኛሉ ማለት አይደለም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ጥያቄ
አንሺዎች ከሚፈልጉት በተለየ መንገድ መፍትሔ መስጠት የሚያስፈልግ ከሆነ በወቅቱ በጥሞናና በግልፅ
ሳይታክቱ ማስረዳት ይገባል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ከአቅም በላይ በሆኑ አስገዳጅ ሁኔታዎች መፍትሔ መስጠት
ካልተቻለ ይህንኑ ሁኔታ በግልፅ ማስረዳት ይገባል፡፡ ዋናው ጉዳይ ለተነሱት ጥያቄዎችና ቅሬታዎች ትኩረት
ሰጥቶ መገኘት ስለሆነ ይህ በምንም መልኩ ሊዘነጋ አይገባም፡፡
3.4.4. ግልፅነት
ግልፅነት የመልካም አስተዳደር አንዱና መሠረታዊ መገለጫ ነው፡፡ የዚህ መርህ መሠረታዊ ቁም-ነገር ዜጎች በቂ
መረጃ ያላቸው (ያወቁ) ሆነው ተገቢውን አቋም መያዝ የሚያስችላቸው መሆኑ ነው፡፡ ግልፅነት በዋነኛነት
የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቱ ምን እንደሚመስል፣ በምን መርህና ህግ እንደሚመራ፣ እንዴት፣ በምን የአፈፃፀም
ስታንዳርድ፣ በማንና መቼ እንደሚፈፀም ወዘተ የመሳሰሉ ጉዳዮችን የሚመለከት መርህ ነው፡፡ ስለዚህ
ግልጽነት አጠቃላይ የአሰራር ሥርዓቱን ይፋ የሚደረግበት መርህ ነው፡፡ በተጨማሪም በአሰራር ሥርዓቱ
የተፈፀመውንና የተከናወነውን ሙሉ መረጃ ለጠያቂው ግልፅ የሚደረግበትን አሰራር የሚያሳይ ነው፡፡ የዚህ
መገለጫ መነሻው ዜጐች በቂና ወቅታዊ መረጃ ያላቸው እንዲሆኑ ማስቻል ሲሆን በዚህም የሚፈጠሩ
አለመግባባቶችን፣ አለመተማመኖችንና ጥርጣሬዎችን ማስወገድ የሚያስችል መሆኑ ነው፡፡ በተጨማሪም
ስህተቶችንና ክፍተቶችን በወቅቱ ለማረምና ለማስተካከል የሚረዳ መረጃ ለማግኘት የሚያግዝ መርህ ነው፡፡
መረጃዎችን ግልፅ ማድረግን በተመለከተ በህግ አግባብ የተለዩትን ሁኔታዎች አስቀድሞ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡
በህግ በምስጢር እንዲጠበቁ የሚያስገድዱትን ለይቶ በህግ አግባብ መፈፀም የግድ ይሆናል፡፡ በህግ አግባብ ግልፅ
እንዳይሆኑ ከተቀመጡ ጉዳዮች በስተቀር ሌሎቹ ሁሉ በዚሁ መሠረት ለሚጠይቅ አካል በህግ አግባብ ሊፈጸሙ
ይገባል፡፡
3.4.5. ተጠያቂነት
ተጠያቂነት ለወሰኑት ውሳኔና ለገቡት ቃል ውጤት ጥያቄ ለሚያቀርብ አካል ተገቢ መረጃና ምላሽ መስጠትና
ማሳወቅን የሚመለከት መርህ ነው፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም የተወሰኑት ውሳኔዎች በተገቢው መንገድ
ካልተፈፀሙ፣ እንዲሁም ቃል የተገባው ጉዳይ በተገባው ቃል መሰረት ካልተከናወነ ለሚፈጠረው ችግር ሁሉ
ኃላፊነትን የመውሰድን ሁኔታ የሚያሳይ መርህ ነው፡፡ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል የተጠያቂነት
ሥርዓት መዘርጋትና ቃል ለተገባለት አካል ማሳወቅ ይገባል፡፡ በዚህም የተወሰኑት ውሳኔዎች በአግባቡ
ካልተፈፀሙ ማን ኃላፊነቱን እንደሚወስድ በግልፅ ማመላከትና በተገቢው መንገድ መፈፀም ያስፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጠያቂነትን የማረጋገጥ መርህ ለተላለፉ ውሳኔዎችና ለዜጋው ለተገባ ቃል ተገቢውን ምላሽ
የመስጠትና በውጤቱም ተጠያቂ የሚያድረግ ስርዓት መተግበሩን የማረጋገጥ ተልእኮ ያለው መርህ ነው፡፡
3.4.6. ፍትሐዊነት
22
ፍትሐዊነት በመንግሥታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ተገልጋዮች ያለ አድልዎና በደል እንዲገለገሉ፣ እንዲስተናገዱና
ጥያቄና ቅሬታቸው በተገቢው መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ የሚያስችል ነው፡፡ በፍትሐዊነት መስተናገድና ምላሽ
ማግኘት የመልካም አስተዳደር አንዱ መገለጫ ነው፡፡ ኢ-ፍትሃዊ መስተንግዶ በዜጐች ዘንድ ቅሬታንና
አለመተማመንን ይፈጥራል፡፡ ፍትሐዊነት የጐደለው አልግሎት አሰጣጥ እና የልማት እንቅስቃሴ የዜጎችን
አመኔታ ክፉኛ በመናድ ህዝባዊ አመጽን ያስከትላል፡፡ ፍትሐዊነት የጐደለው አሰራር ለሙስናና ለኪራይ
ሰብሳቢነት ተግባር ምቹ ሁኔታን ስለሚፈጥር ልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መንግሥት ውጤታማ የመሆን እድሉ
እጅግ የጠበበ ይሆናል፡፡ ስለዚህ መንግሥታዊ አሰራር ያለ አድልዎ በፍትሐዊነት ሊፈፀም ይገባዋል፡፡ ይህም
በዜጐችና በመንግስት መካከል መተማመንና በጋራ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡
የህግ የበላይነት የሁሉም ዜጎች መብቶችና ጥቅሞች በእኩል የሚጠበቁበት የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሰረት
የሆነ መርህ ነው፡፡ በመሆኑም የህግ የበላይነት መከበር ሁሉም ዜጎች በህግ ፊት እኩል የሚዳኙበት አሰራርን
የሚያረጋገጥ መርህ ነው፡፡ በዚህም የሁሉም ዜጐች ጥቅሞችና መብቶች የሚከበሩበት፣ ግዴታዎቻቸውም
ግልፅ የሚደረጉበት፣ ኃላፊነታቸውን የማይወጡ አካላት የሚጠየቁበትና ህጋዊ አሰራር የሚረጋገጥበት ሥርዓት
እውን እንዲሆን የሚያደርግ መርህ ነው፡፡ የህግ የበላይነት የሚረጋገጠው ሁሉም በህግ ፊት እኩል የሚሆንበት
አግባብ ሲፈጠርና ይህም በተጨባጭ ተግባራዊ ሆኖ ሲገኝ ነው፡፡ በመሆኑም መንግሥታዊ የአገልግሎት አሰጣጥ
ተግባራት በህግ አግባብ የሚፈፀሙባቸውን ህጋዊ መሠረቶች ግልፅ የማድረግና አጠቃላይ አፈፃፀሙ በህግ
አግባብ ብቻ የሚከናወኑበትን ሁኔታ መፍጠር አስፈላጊ ይሆናል፡፡
የህግ የበላይነት በዋነኛነት በሁለት መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው፡፡ እነዚህም አንደኛው የመንግሥታዊ
አገልግሎት አሰጣጥ በህግ አግባብ ተደግፎ የመስጠት ጉዳይ ሲሆን ሁለተኛው ጉዳይ ደግሞ ሁሉም ዜጋ በህግ
ፊት እኩል ነው በሚል መርህ ዜጎች የሚስተናገዱበትን ሥርዓት የሚያመላክት ነው፡፡ በመሆኑም ማንኛውም
አገልግሎት ሲሰጥ በዘር፣ በሐይማኖት፣ በብሔር፣ ብሔረሰብ፣ በቀለም፣ በቋንቋ፣ በፖለቲካ አመለካከት፣
በሀብት ደረጃ፣ በትውልድ ወይም በሌላ አቋም ምክንያት ልዩነት መደረግ የለበትም፡፡ ለዚህም የህግ ዋስትና
መስጠትና በተጨባጭ ተግባራዊ መደረግ አለበ፡፡
በመሆኑም በመንግሥታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ውስጥ የሚሳተፍ ማንኛውም አካል በሚኖሩ የህግ
ማእቀፎች ዙሪያ ተገቢውን ግንዛቤ መጨበጥ አለበት፡፡ ግንዛቤ በጨበጠበት ብቻም ሳይሆን በተጨባጭ
ተግባራዊ ማድረግ አለበት፡፡ ከህግ አግባብ ውጭ የሆኑ አሰራሮችም ቦታ የሌላቸው መሆኑን መረዳት ይገባዋል፡፡
23
ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት መስጠት የመልካም አስተዳደር አንዱ መርሆ ነው፡፡ ቀልጣፋነት ማለት
የሚፈፀሙ መንግሥታዊ አገልግሎቶች ባጠረ ጊዜ፣ በተመጣጣኝ ወጪ እና ያለ ሀብት ብክነት አገልገሎት
መስጠት የመቻል ጉዳይ ነው፡፡ ውጤታማነት ማለት አንድን ሥራ የተቀመጠለትን ግብና ዓላማ ለማሳካት
በሚያስችል አኳኋን የመፈፀም ጉዳይ ነው፡፡
በአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍናንና ውጤታማነት የማረጋገጥ ጉዳይ ፈጣን ልማትን
እና የህዝቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ጉዳይ ስለሆነ አማራጭ የማይገኝለት የህልውና ጉዳይ ነው ማለት
ይቻላል፡፡ አንድን ሥራ ስራው የሚጠይቀውን አነስተኛ የጊዜና ገንዘብ ወጪ በማውጣት መስራት ትርጉም
የሚኖረው የተሰራው ሥራ የተቀመጠለትን ዓላማና ግብ ማሳካት እስከተቻለ ድረስ ብቻ ነው፡፡ ይህን በማያሳካ
አኳኋን የሚፈፀም የአገልግሎት አሰጣጥ በቅልጥፍናም ቢሰራ በቅልጥፍና የተሰራ ኪሳራ ከመሆን ያለፈ ፋይዳ
አይኖረውም፡፡ ከዚህ ጋራ ተያይዞ መረሳት የሌለበት ጉዳይ የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋነትና ውጤታማነት
የማረጋገጥ ስራ አንድ ጊዜ ተሰርቶ የሚያበቃ አለመሆኑ እና ከአዳዲስ ቴክኖሎጂና አሰራሮች መፈጠር ጋር
ተያይዞ ሊሻሻል እንደሚችል ነው፡፡ በመሆኑም ቅልጥፍናና ውጤታማነት የየራሳቸው ባህሪያትና ተፈላጊነት
ቢኖራቸውም ሁል ጊዜም ተያይዘው መታየትና መፈፀም ያለባቸው ጉዳዮች ናቸው፡፡ ውጤታማ ሆኖ ቀልጣፋ
መሆን ካልተቻለ በተሟላ መንገድ መልካም አስተዳደርን ማረጋገጥ አይቻልም፡፡
ለዜጎች /ተገልጋዮች/ ግልጽ መረጃ የሚሰጡ፣ ለሰሩት ስራና ለተናገሩት ቃል ለመረጣቸው አካል ተጠያቂ የሚሆኑ፣ ህጎችና
ደንቦች በሁሉም ላይ እኩል እንዲተገበሩ የሚያደርጉና በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ዜጎችን በሚነኩና ዜጎች በሚያገባቸው ጉዳይ
ላይ ከጅምሩ አሳታፊነትን የሚያረጋግጡ ተቋማት ላይ ዜጎች /ተገልጋዮች/ ያላቸው እምነት /TRUST/ ይጨምራል፡፡
አዎንታዊ አመለካከት /POSITIVE BEHAVIOURS / መኖር ለአንድ ተቋም ውጤታማነት ጉልህ ድርሻ እንዳለው ብዙ
ምሁራን ይገልጻሉ፡፡ የተቋሙን በህላዊ እሴቶች ለማክበርና ለማስከበር ነሳሽነትና ኃላፊነት የሚሰማቸውና ግልጽ ፖሊሲና
አሰራር ነድፈው የሚንቀሳቀሱ አመራሮችና ባለሙያዎች ተቋሙ የስራ ባህሉን ጠብቆ እንዲሄድ ያደርጋሉ፡፡ አንድ ተቋም
24
ከሚፈልገው አዎንታዊ አመለካከት /አሰራር/ ወጣ ያለ ጉዳይ ሲኖር ማስተካከል ወይም መልካም አስተዳደርን ማስፈን
ያስፈልጋል፡፡
3.5.3. ሙስናን፣ ብልሹ አመራርን ፣ የሀብት ብክነትንና ስጋትን ይቀንሳል
መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የሚያስችሉ አሰራሮችን ተግባራዊ የሚያደርጉ ተቋማት ስጋትን መቀነስ ይችላሉ፡፡ ምክንያቱም
ጠንካራ አስተዳደራዊ አሰራር የግልጽነት እና የታማኝነት ደረጃን ያዳብራል፤ አደጋን፣ ሙስናንና ብልሹ አመራርን ለመከላከልና
ለመቀነስ የሚያስችል ምቹ አካባቢን ለመፍጠር ያስችላል፡፡
3.5.4. ፍትሐዊ አሰራርን ያሰፍናል
ከኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ የመልካም አስተዳደር መስፈን የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ያፋጥናል፤ አስተማማኝ ሰላም
እንዲኖር ያደርጋል፤ የሁሉንም ብሔር፤ ብሔረሰቦችና ህዝቦች መብትና ጥቅም ያስከብራል፤ እኩል ተጠቃሚነታቸውንም
ያረጋግጣል፡፡
3.5.5. የኢኮኖሚያዊ እና የማህበራዊ እድገት ቀጣይነትን ያረጋግጣል
መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ቁርጠኛ የሆነ ተቋም ችግሮችን አስቀድሞ በመለየት የተቋሙ ህልውና አደጋ ላይ ከመውደቁ
አስቀድም መከላከል ወይም የአደጋውን መጠን መቀነስ ይችላል፡፡ የመንግስት ተቋማት የተሰጣቸውን ተልዕኮና ኃላፊነት ከዳር
እንዲያደርሱ ያግዛል፣ ድህነትን በመቀነስ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ስኬቶችን ቀጣይነት ባለው ሁኔታ ለማረጋገጥ
ያስችላል፡፡
ከአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር የመልካም አስተዳደር መስፈን እየተመዘገበ ያለውን ፈጣንና ተከታታይ የኢኮኖሚና
የማህበራዊ ልማት ዕድገትና የዲሞክራሲያዊ ግንባታ ሂደት ቀጣይነት /SUSTAINABILITY/ እንዲረጋገጥ ያደርጋል፡፡
ክፍል አራት፡
መልካም ያልሆነ አስተዳደር ምንነት፣ መገለጫ ባህሪያትና የሚያስከትለው አደጋ
4.1. መልካም ያልሆነ አስተዳደር ምንነትና መገለጫ ባህሪያት
መልካም ያልሆነ አስተዳደር የመልካም አስተዳደር ተቀራኒውን ገጽታ የያዘ ሲሆን ሙስናን የሰብዓዊ መብት
ጥሰትን፣ የግልጽነትና የተጠያቂነት አሰራር መጓደልን፣ ፈጣን ምላሽ አለመስጠትን፣ የመንግስትንና የህዝብን
ሀብት በቁጠባና በውጤታማነት ስራ ላይ አለማዋልን እና የህግ የበላይነት አሰራር አለመስፈንን የሚያጠቃልል
ነው (ዋኤል ኦምራን፡ 2013)፡፡ መልካም ያልሆነ አስተዳደር በአንድ አገር ወይም ማህበረሰብ ውስጥ ለሚታዩ
ብልሹ አሰራሮችና ድርጊቶች እንደ ዋነኛ መንስኤ እንደሆነ ብዙ ጥናታዊ ፅሁፎች ይገልጻሉ፡፡ መልካም ያልሆነ
አስተዳደር መገለጫዎች ውስጥ አንዱ ሙስናና ብልሹ አሰራር ነው፡፡ በብዙዎች ዘንድ የሚታወቀውና በጣም
ቀላሉ የሙስና ትርጉም የመንግስትን /የህዝብን/ ሀብት ለግል ጥቅም ማዋል ነው፡፡ (የዓለም ባንክ፣ 2012)፡፡
ለሙስና መንሰራፋትና መባባስ አስተዋጽኦ ከሚያደርጉ ተግባራት መካከል የተጠያቂነት አሰራር አለመኖር፣
ውጤታማና ቀልጣፋ ያልሆነ ተቋማዊ አሰራርና አደረጃጀት፣ የህጐች ደንቦችና መመሪያዎች ግልጽ
አለመሆን--- ወዘተ ነው፡፡
25
እንደ ራቸል (2012) አባባል ሙስና በግልጽነት መጓደል የሚከሰት ሲሆን በአንድ አገር አለመረጋጋትንና
ያልተጠበቀ አስተዳደራዊ ቀውስን የሚያስከትል አደገኛ ተግባር ነው፡፡ የግልጽነትና የተጠያቂነት አሰራር
መጓደል ሌላው የመልካም ያልሆነ አስተዳደር ባህርይ ነው፡፡ በመልካም ያልሆነ አስተዳደር ውስጥ ግልጽነትና
ተጠያቂነት አይኖርም፡፡ ይህ ማለት መንግስት የሚያስተላልፋቸው ውሳኔዎች የአገሪቷን ህግና ደንብ የተከተለ
አይሆንም ምክንያቱም የመንግስት ተቋማትም ሆኑ የግል ተቋማትና ሌሎችም ለዜጎች ምላሽ አይሰጡም፡፡
በዚህ ዓይነት አስተዳደር መሪዎች ወይም በስልጣን ላይ ያሉ አካላት ያሻቸውን የማድረግና የመወሰን ነጻነት
ይኖራቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ዜጎች ከመንግስት አጀንዳ ጋር የተያያዙ መረጃዎችን የማግኘት መብት
ስለሚነፈጉ ሙስናው እየሰፋ ይሄዳል፡፡ በአንድ አገር የኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ዜጎች ፍትሀዊ እና እኩል
ተጠቃሚ አለመሆን የመልካም ያልሆነ አስተዳደር መስፈንን ያመለክታል፡፡ ሌላው የመልካም ያልሆነ አስተዳደር
መገለጫ የሰላምና የተረጋጋ የፖለቲካ ሥርዓት አለመኖር ነው፡፡
መልካም አስተዳደርን ያለማረጋገጥ የአንድን አገር ኢኮኖሚ ዕድገት ያቀጭጫል፡፡ ኪራይ ሰብሳቢነት ለምጣኔ
ሀብት እድገት እንዲሁም መንግስት ለሚያከናውናቸው ማንኛውም የምጣኔ ሀብት ለውጥ ዋነኛ ተግዳሮት
ነው፡፡. የኪራይ ሰብሳቢነት ድርጊት በስፋት በሚፈጸምባቸው ሀገራት ማንኛውንም የለውጥ ስራ መተግበር
እጅግ አዳጋች ነው፡፡ የንግድ አሰራርን ቀልጣፋ፣ ዘመናዊና ተወዳዳሪ እንዲሁም የኢኮኖሚ ዕድገት አማራጮችን
ተግባራዊ ከማድረግ አንጻርም እንቅፋት ይሆናል፡፡ በዚህም ዜጎች ከመንግስት የሚጠብቁትን ማህበራዊና
ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት በሚፈልጉት መልክ እንዳያገኙ እና ፍትሐዊ የሆነ አሰራር እንዳይሰፍን ያደርጋል፡፡
በተጨማሪም የአገር ውስጥም ሆነ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በማቀጨጭ በወጪ ንግድ ስርዓቱ ላይ
አሉታዊ ጫና መፍጠሩ የማይቀር ነው፡፡ አገራችን እያስመዘገበች ያለውን የኢኮኖሚ ዕድገት ቀጣይነት
ለማረጋገጥ ብሎም የኢኮኖሚ ሽግግሩን ዕውን በማድረግ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ ለመሰለፍ
የምታደርገውን እንቅስቃሴ ማደናቀፉም ሆነ ማዘግየቱ የማይቀር ነው፡፡ በአጠቃላይ መልካም አስተዳደርን
አለማስፈን ከአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ በመነሳት የተጀመረው ፈጣን አገራዊ የልማት እንቅስቃሴንም ሆነ
የሕዳሴ ጉዞውን ያደናቅፋል፡፡
26
በአንድ አገር መልካም አስተዳደር ባልሰፈነበት ሁኔታ የተረጋጋ ፖለቲካዊ ሥርዓትን ማረጋገጥ አዳጋች ይሆናል፡፡
ምክንያቱም የመልካም አስተዳደር መጓደል የአንድን አገር ሰላም ያደፈርሳል፡፡ ሰላም ባልሰፈነበት ሁኔታ
ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን ማረጋገጥ አይቻልም፡፡ ይህ ደግሞ ፖለቲካዊ አለመረጋጋትን ለሚያስከትል
ችግር ምንጭ ይሆናል፡፡
በሌላ በኩል መልካም አስተዳደርን ያለማስፈን ህዝብ በመንግስት ላይ ያለውን እምነት ይሸረሽራል፡፡
የየትኛውም መንግስት ሥርዓት ተረጋግቶ ሊኖር የሚችለው ህዝቡ በመንግስት ላይ እምነት ሲኖረው ብቻ
ነው፡፡ የህዝብ አመኔታ በሌለበት ወይም ዝቅተኛ በሆነበት ሥርዓት የልማትም ሆነ የእድገት እቅዶችን ከግብ
ለማድረስ አዳጋች ነው፡፡ ዜጎችም ያላቸውን አቅም ሁሉ በመጠቀም የመንግስትን ፖሊሲና እስትራቴጂ መሬት
ለማውረድ ወይም ለመተግበር አይተጉም፡፡ በመሆኑም ማንኛውም የልማት እቅድ ከግብ ሳይደርስ የመቅረት
ዕድሉ ሰፊ ይሆናል፡፡
ክፍል አምስት፡
መልካም አስተዳደርን በማስፈን ረገድ የተለያዩ አካላት ሚና
መልካም አስተዳደርን በማስፈን ሂደት በርካታ ተዋናዮች አሉ፡፡ እነዚህን ተዋናዮች በሦስት ከፍሎ ማየት
ይቻላል፡፡ የመጀመሪያው፡- የመንግስት ሦስት ክፍሎች ሲሆኑ እነርሱም ህግ አውጪ፣ ህግ ተርጓሚ እና ህግ
አስፈፃሚ ናቸው፡፡ ሁለተኛዉ አካል የግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ ሲሆን ይህም የግል ካምፓኒዎችን፣ የግል ተቋማትንና
የንግድ ድርጅቶችን ያጠቃልላል፡፡ ሦስተኛዉ የሲቪል ማህበረሰብ ክፍል ሲሆን እነዚህም መንግስታዊ ያልሆኑ
ድርጅቶችን ጨምሮ የሙያ ማህበራትን፣ ሃይማኖታዊ ተቋማትንና የማህበረሰብ ድርጅቶችን የሚይዝ ነዉ፡፡
የተጠቀሱት ተዋናዮች ተከታታይና ዘላቂ ሱፐርቪዥን በማካሄድ የህብረተሰቡንና የግሉን ሴክተር ተሳትፎ
በማረጋገጥ መልካም አስተዳደርን በማስፈን ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና እንደሚኖራቸው የተለያዩ ጽሁፎች
ያስረዳሉ፡፡ በሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የጎላ ድርሻ የሚኖራቸው አካላትና
ሚናቸው እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መንግሥት በየጊዜው የሚያወጣቸውን ፖሊሲዎች፣
እስትራተጂዎች፣ ፕሮግራሞችና ዕቅዶች መረዳትና በባለቤትነት መፈፀም ይገባዋል፡፡ በመልካም አስተዳደር ዕቅድ ዝግጅትና
27
አፈጻጸም ወቅትና ህዝቡ የሚያነሳቸው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ሂደት ውስጥ በንቃት መሳተፍ
ይኖርባቸዋል፡፡ የመስሪያ ቤታቸውን የውስጥ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በመፍታት ሂደት ውስጥም ተመሳሳይ ንቁ
ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡
5.4. የሚዲያ ሚና
የመልካም አስተዳደር መርሆዎች ተፈጻሚነት ከሚዲያ ጋር ቀጥታ ግንኙነት አለው፡፡ ሚዲያው ለዜጎች የመልካም
አስተዳደር መርሆዎችን የማስተዋወቅ፣ የህዝብ ተሳትፎ ቀጣይነት እንዲኖረውና እንዲጎለብት የማድረግ፣ ለህዝቡ ወቅታዊ
መረጃ በመስጠት በመረጃና በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ትግል የማካሄድ ባህልን የማሳደግ ሚዲያው ሚናውን መጫወት
ይጠበቅበታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የመንግስት ኃላፊዎችና ሰራተኞች የሚሰጡትን ፍትሀዊ ያልሆነ አገልግሎት፤ለመልካም
አስተዳደር መጓደል መንስኤ የሆኑ አደናቃፊ ተግባራትንና ህገወጦችን ነቅሶ በማውጣት እንዲስተካከሉና የተጠያቂነት አሰራር
እንዲሰፍን ብቻ ሳይሆን በአራያነት የሚጠቀሱ ስራዎች እንዲበረታቱና እንዲስፋፉ በማድረግ፤ በመንግስት አገልግሎቶች
ቀልጣፋና የተሻሉ አሰራሮች የሚፈጠሩበትን መንገድ በመጠቆምና የአሰራር ክፍተቶች በሚታዩበት አከባቢ ግብአት በመስጠት
አገራዊ ድርሻውን መወጣት ይጠበቅበታል፡፡
28
ክፍል ስድስት፡
የመልካም አስተዳደር ዕቅድ ዝግጅት እና ትግበራ
ማንኛውም የመንግስት ተቋም የውስጥና የውጭ ተገልጋዮች ይኖሩታል፡፡ በዚሁ መሰረት ተቋማት ለተገልጋዮቻቸው
ከሚሰጡት አገልግሎት ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች የውስጥ እና የውጭ ተብለው ይለያሉ፡፡
የውስጥ የመልካም አስተዳደር ችግሮች የሚባሉት የመንግስት ተቋማት ለውስጥ ተገልጋዮቻቸው ከሚሰጧቸው አገልገሎቶች
ጋር ተያይዞ የተቋሙ ሰራተኛ የሚያነሳቸው ችግሮች ናቸው፡፡ ችግሮቹም በዋናነት ከሰው ሃብት ስራ አመራር ጉዳዮች (ቅጥር፣
ደረጃ እድገት፣ ዝውውር፣ ስንብት፣ ወዘተ)፣ ከግብአት አቅርቦት፣ ከተሳትፎ፤ ከአፈጻጸም ምዘና፣ ከስልጠናና የትምህርት እድል
እና ከመሳሰሉት አገልግሎቶች ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ ናቸው፡፡
የውጭ የመልካም አስተዳደር ችግሮች የሚባሉት የመንግስት ተቋማት አገልግሎት ፈልገው ወደ ተቋማቱ ለሚመጡ የውጭ
ተገልጋዮች ከሚሰጧቸው አገልገሎቶች ጋር ተያይዘው የሚፈጠሩና ተገልጋዮቹ የሚያነሷቸው ችግሮች ናቸው፡፡ ችግሮቹም
በዋናነት ዜጎችን በአግባቡ ካለማሳተፍ፣ ፈጣን፤ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ካለመስጠት፤ የግልጽነትና ተጠያቂነት
አሰራርን ከማጓደል፣ ፍትሐዊ እና አካታች አገልግሎት ካለመስጠት፣ ከህጎች፣ ደንቦች እና መመሪያዎች መጣስ እና ከመሳሰሉት
ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡
1. ከዜጎች፣ ከህዝብ ክንፍ (ሙያና ብዙሃን ማህበራት ወይም አደረጃጀቶች) እና ከባለድርሻ አካላት ከሚቀርቡ
ቅሬታዎችና ጥቆማዎች (በመድረኮች፣ በአስተያየት ማሰባሰቢያ መዝገብና በሃሳብ መስጫ ሳጥኖችና፣ በአካል
የሚቀርቡ)፣
3. ከዳሰሳ ጥናቶች፣
29
6.3. የመልካም አስተዳደር ችግሮች ትንተና
የውስጥና የውጭ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ትንተና ከላይ በተጠቀሱት የመረጃ ምንጮች የውስጥና የውጭ ችግሮች
በመለየት ከመልካም አስተዳደር መርሆዎች አንጻር የችግሮቹን መንስኤዎችና የምክንያትና ውጤት መስተጋብር ገላጭ በሆነ
መንገድ መተንተንን የሚያመላክት ሂደት ነው፡፡ በመልካም አስተዳደር ችግሮች ትንተና ሂደት የችግሮችን መንስኤዎች እና
የምክንያትና ውጤት ትስስር በስዕላዊ መግለጫ ማስቀመጥ ተገቢ ነው፡፡ ስእላዊ መግለጫው የተለዩ የመልካም አስተዳደር
ችግሮች ትክክለኛ መንስኤ ምን እንደሆነ በአግባቡ ነቅሶ በማውጣት፣ የመፍቻ ዕቅዱም ተፈላጊውን ዘላቂ መፍትሔ ማስገኘት
ይችል ዘንድ ተገቢውን የትኩረት ነጥብ በመለየትና ችግሩን ለመፍታት የሚያስችል አዋጭ እስትራቴጂያዊ ግብና ግብ ተኮር
ተግባራትን በመንደፍ ለመተግበር ጠቀሜታው የጎላ ነው፡፡ በዚህ ሂደትም በመልካም አስተዳደር ችግሮች ልየታና የመፍቻ
ተግባራት ቀረፃ ላይ በተደጋጋሚ የሚስተዋሉ የመንስኤና ውጤት መምታታት ክፍተቶችን በመቅረፍና በተለያዩ ስልቶች
ተለይተው በታወቁ ችግሮች ትክክለኛ መንስኤ ላይ በማተኮር ችግሮቹን መፍታት የሚቻልበት ሁኔታ ይፈጠራል፡፡ ስለዚህ
(Problem tree diagram) ተቋማት ለእያንዳንዱ የመልካም አስተዳደር ችግር ዋነኛ ምንጭ መለያ ዘዴ አድርገው
መጠቀም ይኖርባቸዋል፡፡ ነገር ግን ይህ ዘዴ የችግሮች ዋነኛ ምንጭ መለያ ዘዴ እንጂ የእቅድ አካል እንደማይሆን መታወቅ
ይገባዋል፡፡
ምሳሌ 1፡-
የተለየ የመልካም አስተዳደር ችግር፡- የመንገድ ትራፊክ አደጋ
ይህ ችግር የመንገድ ደህንነት ስርዓት የአሰራር ማእቀፎች በተገቢው ደረጃ ስራ ላይ ባለማዋል፣ በህብረተሰቡ
ንቁ ተሳትፎ የታገዘ የማሳወቅ፣ የማስተማርና የመከላከል ስራ ካለመስራትና ተገቢውን የተጠያቂነት ሥርዓት
ተግባራዊ ካለማድረግ የሚመነጭ የመልካም አስተዳደር ችግር ነው፡፡ በመሆኑም ችግሩ ተሳትፎ፣ የህግ
የበላይነትና ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት መስጠትን የተመለከቱ የመልካም አስተዳደር መርሆዎች በአግባቡ
ባለመተግበራቸው የሚፈጠር የመልካም አስተዳደር ችግር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ የዚህ ችግር
መንስኤዎችና የምክንያትና ውጤት ትስስር ስዕላዊ መግለጫ ለማሳያነት እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
30
ስዕል 1፡- የመንገድ ትራፊክ አደጋ ችግር ዋና ዋና መንስኤዎች እና የምክንያትና ውጤት ትስስር
ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና
ማህበራዊ ቀውስ
ውጤት
የንብረት ውድመት
የሰው ህይወት መቀጠፍ
መንስኤ
የአሽከርካሪዎች ብቃት የተሸከርካሪዎች ረጅም የተሸከርካሪዎች ወቅታዊ
ማነስ እና የእግረኞች ዓመት ያገለገሉ መሆን የቴክኒክ ብቃት ፍተሻ
ግንዛቤ ጉድለት በአግባቡ አለመደረግ
31
ቀደም ሲል ከቀረበው ስዕላዊ መግለጫ መረዳት እንደሚቻለው የመንገድ ትራፊክ አደጋ ህብረተሰቡን ያሳተፈ
የማስተማርና የመከላከል ስራን በቅንጅት ካለመተግበር፣ የማስፈፀም አቅም ማነስና የኪራይ ሰብሳቢነት
አመለካከትና ተግባር ከሚፈጥራቸው የአገልግሎት ጥራት መጓደሎች የተነሳ የመንገድ ደህንነት የአሰራር
ማዕቀፎችን በተገቢው ደረጃ ስራ ላይ ማዋል ባለመቻሉ ለሰው ህይወት መቀጠፍ፤ ለንብረት መውደምና
ለከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀውሶች መከሰት ምክንያት በመሆን ዜጎች በዚህ መስክ በሚያገኙት
አገልግሎት እንዳይረኩና ከትራንስፖርት ጋር የተያያዘው የእለት ተእለት ሰዎች በዕለት ተዕለት የትራንስፖርት
እንቅስቃሴያቸው ከስጋት የፀዳ እንዳይሆን እያደረገ ያለ ችግር በመሆኑ እንደ አንድ የመልካም አስተዳደር ችግር
ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው፡፡
በዚሁ መሰረት የመልካም አስተዳደር ችግሮች እቅድ ዝግጅት ተግባራትን በውጤታማነት ለማከናወን
በተመረጡ የመመዘኛ መስፈርቶች መሰረት ችግሮችን እንደየክብደታቸው ቅደም ተከተል እንዴት ማስቀመጥ
እንደሚቻል ለማሳየት በተመረጡ የንግድ ዘርፉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ በመመስረት የተዘጋጀ
ምሳሌ ቀጥሎ በቀረበው ሰንጠረዥ ተመላክቷል፡፡ ወደ ምዘናውና ደረጃ አሰጣጡ በቀጥታ ከመግባታችን በፊት
የመልካም አስተደዳደር ችግሮችን በቅደም ተከተል ለማስቀመጥ ለምዘና የምንጠቀምባቸውን ዋና ዋና
መስፈረቶች ምንነትና በምን አግባብ ጥቅም ላይ እንደምናውላቸው መረዳቱ ጠቃሚ ይሆናል፡፡ በዚሁ መሰረት
የእነዚህ የምዘና መስፈርቶች ማብራሪያ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
እርካታ የመፍጠር ተጽዕኖ፡- የአንድ የመልካም አስተዳደር ችግር መፈታት በዜጎች እርካታ ላይ የሚኖረው
የተጽዕኖ ደረጃ የሚመዘነው በዋናነት ችግሩ በመሰረታዊ ባህሪይው ከአገልግሎት ተጠቃሚው ዜጋ ጋር ያለውን
32
ቀጥተኛ ትስስር፣ በመቃለሉም የዜጎችን እርካታ ከማሳደግ አንጻር የሚኖረውን ድርሻና የተፈጠረው
አብዛኛዎቹ መርሆዎች በመጣሳቸው ምክንያት መሆኑን በጥልቀት በመፈተሽ ይሆናል፡፡
ገዥነት፡- የተለየው ችግር በመሰረታዊ ባህሪይው ቁልፍ፣ ከብዙ ጉዳዮች ጋር የተያያዘ፣ የሚወሰደው የመፍትሔ
እርምጃ ሌሎች ተያያዥነት ያላቸውንም ችግሮች አብሮ የሚፈታና ችግሩ በበርካታ መርሆዎች መጣስ
ምክንያት የተፈጠረ ከሆነ ገዥ ችግር ይሆናል፡፡
አንገብጋቢነት፡- ይህ መስፈርት የሚመዘነው ችግሩ ፈጣን ምላሽ የሚሻ፣ በወቅቱ ካልተፈታ ለተጨማሪ ወጪ
የሚዳርግና መፈታቱ ለሌሎች ችግሮች መፈታት በቅድመ ሁኔታነት የሚታይ መሆኑን በመፈተሽ ይሆናል፡፡
የሚያስከትለው አደጋ፡- አንድ የመልካም አስተዳደር ችግር ካልተፈታ የሚያስከትለው አደጋ የሚመዘነው
የዜጎች የእለት ተእለት እንቅስቃሴ ላይ የሚፈጥረውን ጫና፣ ዜጎች በአገልግሎት ሰጪው ተቋምና በመንግስት
ላይ በቀጣይ በሚኖራቸው አመኔታ ላይ የሚፈጥረውን አሉታዊ ተፅዕኖ እና ይህ ሁኔታም በአገልግሎት ሰጪው
ተቋም ህልውና እንዲሁም በአገር ደረጃ የሚኖረውን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ አንደምታ
በመፈተሽ ይሆናል፡፡
ምሳሌ.2.፡- በንግድ ዘርፍ የሚስተዋሉ ተብለው በተለዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ቅደም ተከተል ለመለየት
የዋለ
33
ከንግድ ስርአት ቁጥጥር መላላት ጋር
2 ተያይዞ የሚፈጠር የዋጋ ንረትና የኑሮ 4.7 4.3 4.5 4 17.5 2
ውድነት፣
ከላይ በቀረበው ሰንጠረዥ በንግድ ሴክተር ሊስተዋሉ ይችላሉ ተብለው ከሚታሰቡ የመልካም አስተዳደር
ችግሮች ውስጥ አምስቱ ተለይተው የቀረቡ ሲሆን እያንዳንዱ ችግር ከዜጎች እርካታ፣ ከገዥነት፣
ከአንገብጋቢነት፣ እንዲሁም ችግሩ በአግባቡ ካልተፈታ ከሚያስከትለው አደጋ አንፃር ተመዝኖ ነጥብ
ተሰጥቶታል፡፡ በመቀጠልም እያንዳንዱ ችግር ከእነዚህ የመመዘኛ መስፈርቶች አንፃር ከ 20% ያገኘው ነጥብ
ተደምሮ ከተቀመጠ በኋላ ባገኘው ነጥብ መሰረት ከሌሎቹ የመልካም አስተዳደር ችግሮች አንፃር የሚገኝበት
ደረጃ ተቀምጦለታል፡፡
በዚሁ መሠረት በንግዱ ዘርፍ በአሰራር፣ በአደረጃጀት እና በአመለካከት ክፍተት ምክንያት የሚፈጠሩ
የአገልግሎት መጓደሎች ችግር መስፈርቶቹን በመጠቀም በተደረገው ምዘና 18.2 ከ 20% በማግኘት በአንደኛ
ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፣ ከንግድ ስርአት ቁጥጥር መላላት ጋር ተያይዞ የሚፈጠር የዋጋ ንረትና የኑሮ ውድነት ችግር
17.5 ከ 20% በማግኘት ሁለተኛ፣ በድጎማ የሚቀርቡ መሰረታዊ ሸቀጦች ለሸማቹ ህብረተሰብ በአግባቡ
ተደራሽ ባለመሆናቸው የሚፈጠረው ደግሞ 17.3 ከ 20% በማግኘት በሦስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡ ከዚህ
በመነሳት ጉዳዩ የሚመለከተው ተቋም እነዚህን የተለዩ አምስት ችግሮች በአንድ ጊዜ ለመፍታት የማስፈፀም
አቅምና የግብዓት እጥረት ቢያጋጥመው በምዘናው መሰረት ከፍተኛ ነጥብ የተሰጠውን ችግር መፍታቱ ላይ
በማተኮር ሌሎቹንም እንደቅደም ተከተላቸውና እንደ ተቀራራቢነታቸው ተራ በተራ ወይም ጎን ለጎን እየፈታ
መሄድ የሚችልበትን አግባብ መፍጠር ይኖርበታል ማለት ነው፡፡
34
6.4. የመልካም አስተዳደር ግቦች ምንነት
የመልካም አስተዳደር ግቦች ሊለኩ የሚችሉና ውጤቶች የሚያሳኩ ቀጣይነት ያላቸው የማሻሻያ ክንውኖች ሆነው ለመረዳት ቀላል፤
አጭርና ገላጭ መሆን ይገባቸዋል፡፡ በመሆኑም ቀጣይነት ያለው ሂደትን የሚያሳዩ ድርጊት ተኮር ቃላትን (ማሻሻል፣ መጨመር፣
መቀነስ፣ ማሳደግ፣ ማጎልበት፣ ወዘተ ) በሚል መገለጽ ይኖርባቸዋል፡፡ ለምሳሌ፡- የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍናን ማሳደግ፣
የአገልግሎት መስጫ ጊዜን ማሳጠር፣ የዜጎችን እርካታ መጨመር፣ ወዘተ…፡፡
35
የተረጋጋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ
ውጤት
የአሽከርካሪዎች ክህሎት ማሳደግ የተሽካርካሪዎች ቴክኒካዊ ብቃት ማሳደግ የተሸከርካሪዎች ወቅታዊ የቴክኒክ ብቃት
ፍተሻ ማጎልበት ማረጋገጥ
የህብረተሰቡን ግንዛቤና
የማስፈጸም አቅምን የኪራይ ሰባሳቢነት አመለካከትና
ተሳትፎ ማሳደግ
ማጎልበት
ተግባርን ማክሰም
መንስኤ
ግብ ተኮር ተግባር በአንድ ተቋም የተለዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የተቀረጸውን ግብ
ለማሳካት ወሳኝነት ያለውና ቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቶት መፈፀም ያለበት ገዢ ክንውን ነው፡፡ ስለሆነም
36
የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት ሂደት ውስጥ ከሁሉም በላይ ተገቢው ትኩረት ተሰጥቶት መተግበር
የሚገባው ተግባር ነው፡፡ የግብ ተኮር ተግባራት መለያ ዘዴዎች፡-
1) ከተለዩት ተግባራት መካከል ችግርን ለመፍታት የበለጠ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ማረጋገጥ፣
2) ተግባሩ ለበርካታ ችግሮች መፈታት ምክንያት መሆኑን ማረጋገጥ፣
3) ተግባሩ ከራሱ ውጪ ለሌሎች ዝርዝር ተግባራት መፈፀም ጉልህ ተፅዕኖ ያለው መሆኑን ማረጋገጥ፣
4) መሠረታዊ የሆነ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል ተግባር መሆኑን መገንዘብ፣
በአንድ ተቋም የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን፣ ችግሮቹን ለመፍታት የሚነደፉ ግቦች፣ ግቡን
ለማሳካት የሚከናወኑ ግብ ተኮር ተግባራት እና የግብ ተኮር ተግባራቱን ውጤታማነት የሚደግፉ ሌሎች
ተግባራት ተለይተው የሚቀመጡበት ሁኔታ ቀጥሎ በቀረበው ምሳሌ 2 ላይ ተመልክቷል፡፡
ምሳሌ 2፡-
የተለየው የመልካም አስተዳደር ችግር፡- የፍትህ አገልግሎት ቅልጣፌ መጓደል
የችግሩ መንስኤዎች፡-
የፈጻሚዎች የአመለካከት፣ የዕውቀትና የክህሎት ክፍተቶች
ለአገልግሎት አሰጣጥ ማነቆ የሆኑ አሰራሮች፣
የተቋሙ አደረጃጀት ለአገልግሎት አሰጣጥ ምቹ ያለመሆን፣
ግብ፡-የፍትህ ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥ ቅልጣፌን ማሳደግ
ግብ ተኮር ተግባር፡- የፈጻሚዎችን የአመለካከት፣ የዕውቀትና የክህሎት ክፍተቶች የመሙላት
ተግባራትን ማከናወን፣
ዝርዝር ተግባራት፡-
ለአገልግሎት አሰጣጥ ማነቆ የሆኑ አሰራሮችን ማሻሻልና አዳዲስ አሰራሮችን መዘርጋት፣
የተቋሙ አደረጃጀት ለአገልግሎት አሰጣጥ ምቹ እንዲሆን ማድረግ፣
የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ማዕከል ያደረገ ዝርዝር ተቋማዊ መዋቅር መፍጠር፣
ከላይ ከቀረበው ምሳሌ መረዳት እንደሚቻለው የመልካም አስተዳደር ችግሮች በዋናነት በተቋሙ አደረጃጀት፣
አሰራር እና የሰው ኃይሉ አመለካከት፣ እውቀትና ክህሎት ላይ በሚስተዋሉ ክፍተቶች መንስኤነት የሚከሰቱ
ናቸው፡፡ ስለሆነም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመሰረታቸው ለመቅረፍ በፈጻሚዎች የአመለካከት፣
የዕውቀትና የክህሎት ክፍተቶች ምክንያት የሚፈጠሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እንዲሁም
ከአደረጃጀትና አሰራር ጋር ተያይዞ የሚታዩ ውስንነቶችን ቀጣይነት ባለው አግባብ እየፈተሹና እየፈቱ መሄድ
ይገባል፡፡
37
6.7. የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍቻ መርሐ-ግብር
የመንግስት ተቋማት ከላይ የተዘረዘሩትንና ሌሎች አማራጭ መንገዶችን (የመረጃ ምንጮችን) በመጠቀም የውስጥ እና የውጭ
የመልካም አስተዳደር ችግሮቻቸውን በአግባቡ መለየት አለባቸው፡፡ በዚህ አግባብ የተለዩትን የመልካም አስተዳደር ችግሮች
በቅደም ተከተል በማደራጀት ሊፈቱ የሚችሉበትን አግባብ (ስልት) ጭምር በመለየት ዝርዝር የመፍቻ ዕቅድ መንደፍ
ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም ይህንን ስራ በውጤታማነት ለመተግበር የሚከተሉትን ሂደቶች መከተል ጠቃሚ ይሆናል፡፡
እነዚህም፡-
3. ችግሮችን እንደየክብደታቸው (እርካታ የመፍጠር ተጽእኖ ገዥነት፣ አንገብጋቢነት፣ የሚያስከትለው አደጋ፣ የተጣሱ
መርሆዎች ብዛት፣ ወዘተ) በቅደም ተከተል ማስቀመጥ፣
4. ችግሮችን ከመልካም አስተዳደር መርሆዎች አንጻር ለይቶ መፈረጅ (እያንዳንዱ ችግር የተፈጠረው በየትኛው
የመልካም አስተዳደር መርሆ የአፈጻጸም ክፍተት ምክንያት እንደሆነ መለየትና መፈረጅ)፣
7. ተመሳሳይ መንስኤ ያላቸው ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ግቦች መቅርጽና ዝርዝር ተግባራትን መለየት፣
8. በተያዘው የበጀት ዓመት የሚፈቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የሚከናወኑ ተግባራትን በአጭር፣
በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ በመሸንሸን ዝርዝር የድርጊት መርሐ-ግብር ማዘጋጀት፡፡
38
በአገራችን ከፌዴራል መንግስት ተቋማት ጀምሮ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ስፋታቸውና
ጥልቀታቸው ቢለያይም በርካታ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንደሚታዩ ሕዝቡ በተለያዩ መድረኮችና
አገልግሎት በሚያገኝባቸው ሥፍራዎች ቅሬታውን እያሰማ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ከአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ
አኳያ የመላውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና ልማቱን በአስተማማኝ መሠረት ላይ ለመጣል የኪራይ
ሰብሳቢነት ፖለቲካል ኢኮኖሚን በመናድ በልማታዊ ፖለቲካል ኢኮኖሚ መተካት መልካም አስተዳደርን
ለማረጋገጥ አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑ እንደ አቅጣጫ ተይዟል፡፡ ይህንኑ ለማሳካት ሁሉም የፌዴራል እና
የክልል የመንግስት ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎትና ከሚያከናውኑት የልማት ሥራዎች አንፃር ዜጎችና
ተገልጋዮች የሚያነሷቸውን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ከነመንስኤያቸው በመለየትና ቸግሩን ለመቅረፍ
የሚያስችል እቅድ በማዘጋጀት ለተግባራዊነቱ ርብርብ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡
ይህንኑ አገራዊ አቅጣጫ መነሻ በማድረግ የተዘጋጁ የመልካም አስተዳደር ፓኬጆችንና በአገራዊው የዕድገትና
ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውስጥ የተነደፉ አገራዊ የመልካም አስተዳደር ግቦችን፣ ግቦቹን ለማሳካት የተቀመጡ
ስትራቴጂዎችንና የታቀዱ ዝርዝር ተግባራትን በአግባቡ መዳሰስና ለዓመታዊ የመልካም አስተዳደር ችግሮች
መፍቻ ዕቅድ ዝግጅቱ የሚያስፈልጉ የትኩረት ነጥቦችንና መረጃዎችን መለየቱ አስፈላጊ ይሆናል፡፡
በመሆኑም የመንግስት ተቋማት የመልካም አስተዳደር ዕቅዶቻቸውን ሲያዘጋጁ እንደ አገር የተያዘውን ዘላቂና
ፍትሐዊ ልማት የማረጋገጥ፣ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የመገንባት፣ መልካም አስተዳደርን የማስፈን እና
ሦስቱንም አጀንዳዎች ሳይነጣጠሉ የመፈፀም አቅጣጫን፣ እንዲሁም አገራዊና ተቋማዊ የመልካም አስተዳደር
ፓኬጆችንና የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን እንደ መነሻ መውሰድ ተገቢ ይሆናል፡፡
6.8.1.3. የመልካም አስተዳደር ችግሮች የአፈታት ስልቶችን በግልፅ ማስቀመጥ
የመልካም አስተዳደር ዕቅድ ሲዘጋጅ እቅዱ ወደ መሬት የሚወርድበትን አግባበና ስትራቴጅያዊ ችግሮቹን
ለመፍታት የሚያስችሉ ዋና ዋና ዝርዝር ተግባራትን በመለየት ተግባራዊ የሚደረጉበትን ስልት በመለየት
መፈጸም ይገባል፡፡
የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ትርጉም ባለው ደረጃ በመፍታት የዜጎችን እርካታ ማረጋገጥ የሚቻለው
በተበታተነ ሁኔታ ሳይሆን ከላይ እስከታች ተደራጅቶ እንደ አንድ አካል በሰራዊት አግባብ መንቀሳቀስ ሲቻል
ነው፡፡ በመሆኑም ሁሉንም የሰራዊት አቅሞች እና የግንኙነት መድረኮች የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍቻ
ቁልፍ ስልት አድርጎ መጠቀም ይገባል፡፡ በግንኙነት መድረኮቹ ለመልካም አስተዳደር መጓደልና ለዜጎች ቅሬታ
መንስኤ የሆኑትን የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር፤ ትምክህት፣ ጥበት፣ የሐይማኖት አክራሪነት፣
39
ሙስና እና ሌሎች ተያያዥ ችግሮችን የሰራዊቱ የእለት ተእለት የውይይት አጀንዳ በማድረግ የሰላ ትግል
እንዲካሄድባቸው ማድረግ ይገባል፡፡
6.8.2.2. የለውጥ መሣሪያዎችን አቀናጅቶ መጠቀም
ጊዜ የሚጠይቁ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተለያዩ አግባቦች ለመፍታት የሚደረገው ጥረት እንደተጠበቀ
ሆኖ በቀላሉና በአጭር ጊዜ ሊፈቱ የሚችሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በአፋጣኝ የሚፈቱበትን አማራጭ
ለይቶ ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ ፈጣን ምላሽ አምጭ (quick wins) ሥርዓት በመጠቀም
የሚፈቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየት ማቀድና መተግበር ይገባል፡፡
በዚህ ረገድ በተቋማት የአቅጣጫ ጠቋሚ ሰሌዳዎችን፣ የደረትና የጠረጴዛ ባጅ፣ የመረጃ ዴስክ ወዘተ.
ባለማደራጀት ምክንያት በአገልግሎት ፈላጊ ዜጎች ላይ የሚደርሱ እንግልቶችን ተያያዥ የመልካም አስተዳደር
ችግሮችን በፈጣን ለውጥ አምጪ እርምጃዎች መፍታት ተገቢ ይሆናል፡፡
6.8.2.4. በዜጎች የነቃ ተሳትፎ መፈጸም
ማንኛውም የመንግስት ተቋም በመልካም አስተዳደር ችግሮች ልየታ፣ ዕቅድ ዝግጅት፣ የዕቅድ አተገባበር
የአፈፃፀም ክትትልና ግምገማ ሂደቶች ላይ የህዝብ ክንፉንና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላትን በንቃትና በተደራጀ
አግባብ ማሳተፍ ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም የነዚህ አካላት ንቁ ተሳትፎ በሌለበት ሁኔታ የመልካም አስተዳደር
ችግሮች መፍቻ ዕቅድን በውጤታማነት መፈጸም አይቻልም፡፡ ይህ በሆነበት ደግሞ የዜጋውን እርካታ
በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አይቻልም፡፡
በመሆኑም በመልካም አስተዳደር ችግሮች አፈታት ሂደት የተቋማት፣ የህዝብ ክንፍና የሌሎች ባለድርሻ አካላት
የሚሳተፉበት አደረጃጀትና የአሰራር ስርዓት በዕቅዱ በግልፅ መቀመጥና ተግባራዊ መደረግ አለበት፡፡
40
6.8.2.5. የዜጎችና ተገልጋዮች እርካታን እየለኩና ውጤቱን በግብአትነት እየተጠቀሙ መፈጸም
በመንግስት ተቋማት በሚሰጡ አገልግሎቶችና በተፈቱት የመልካም አስተዳደር ችግሮች የዜጎች እርካታ ስለ
መረጋገጡ ተከታታይነት ያለው የዜጎች የእርካታ አዝማሚያን የመለየትና በየጊዜው ደረጃውን የጠበቀ ጥናት
በማካሄድ በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የዜጎች እርካታ ያለበትን ደረጃ የመለየት ስራ በመስራት ለቀጣይ
አገልግሎት መሻሻል በግብአትነት የመጠቀም አቅጣጫን መከተል አስፈላጊ ነው፡፡
በመሆኑም እያንዳንዱ ተቋም በሚያዘጋጃቸው የሃሳብ መስጫ ቅጾች፣ መዛግብትና ሳጥኖች ዜጎች
የሚሰጧቸውን አስተያየቶች መነሻ በማድረግና ያንን መረጃ በመተንተን ወርሐዊ የዜጎች እርካታ አዝማሚያን
እየለየ መሄድ ይጠበቅበታል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በአንድ የበጀት ዓመት አንድ ጊዜ ጥልቀት ያለው የዜጎች
እርካታ ዳሰሳ ጥናት ማካሄድ ይኖርበታል፡፡
6.8.2.6. ምርጥ ተሞክሮን መለየት፣ መቀመርና ማስፋት
የመንግስት ተቋማት መልካም አስተዳደርን ለማስፈን በሚያደርጉት ርብርብ ከሌሎች ተቋማት የተገኙ የላቁ
ተሞክሮዎችን በመለየት፤ በመቀመር፤ የማስፋት አቅጣጫን በመከተል ከራስ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማጣጣም
ተግባራዊ ማድረግ ይገባል፡፡
6.8.2.7. የድርጊት መርሀ ግብር ማዘጋጀትና ተግባራዊ ማድረግ
እያንዳንዱ የመንግስት ተቋም የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍቻ የድርጊት መርሀ ግብርን አዘጋጅቶ
በውጤታማነት መተግበር ይጠበቅበታል፡፡ የሚዘጋጀው የድርጊት መርሀ ግብርም በዋናነት የሚከተሉትን
ነጥቦች ማካተት ይጠበቅበታል፡፡
ሀ) በእቅድ አመቱ የሚፈቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች፣
ለ) የችግሮቹ መንስኤ (የሰው ሀይል፣ አደረጃጀትና አሰራር)፣
ሐ) ችግሮቹ በተፈጠሩበት የመልካም አስተዳደር መርሆዎች ጥሰት፤
መ) ችግሮችን ለመፍታት የተቀረጹ ስትራቴጂያዊ ግቦች፣
ሠ) ግቦችን ለማሳካት የሚከናወኑ ስትራቴጂያዊ ተግባራት፣
ረ) የተለዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች የሚፈቱበት የግዜ ገደብ (በአጭር፣ በመካከለኛ እና በረጅም
ጊዜ) ብሎ በግልፅ ማስቀመጥ፣
ሰ) የተጠያቂነት አሰራሩን ተግባራዊ ማድረግ እንዲቻል ችግሮቹን ማን እንደሚፈታቸው በግልጽ
ማመላከት፣
ሸ) ከእያንዳንዱ ግብ አፈጻጸም የሚጠበቅ ውጤት ፡፡
6.8.2.8. ተጠያቂነትን ማረጋገጥ
41
መልካም አስተዳደርን በማስፈን ሂደት የሚታቀዱ ዕቅዶች በውጤታማነት እንዲፈጸሙ በየደረጃው
ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ወሳኝ ይሆናል፡፡ በመሆኑም እያንዳንዱ የመንግስት ተቋም የውስጥና የውጭ የመልካም
አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት በሚያደርገው ጥረት ለመልካም አስተዳደር መጓደል መንስኤ የሆኑ አካላትን
ተጠያቂ የማድረግ አሰራርን መዘርጋትና ተግባራዊ ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡ በዚሁ መሰረት የመልካም
አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት ሂደት ከሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ውስጥ በየተቋማቱ ኃላፊነታቸውን
በአግባቡ ያልተወጡ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ የተሻለ ለፈፀሙት ደግሞ እውቅና የመስጠትና የማበረታታት
አቅጣጫን መከተል ተገቢ ነው፡፡ ይህ አቅጣጫ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የሚኖረው አዎንታዊ ሚና
የማይተካ በመሆኑ ለጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት ሊሰጠውና ያለምንም ክፍተትና መንጠባጠብ ተግባራዊ ሊደረግ
ይገባል፡6.9. የክትትልና ድጋፍ ስርዓት
ዜጎች የሚያነሷቸው አንገብጋቢ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በወቅቱ አጥጋቢ ምላሽ ማግኘታቸውን
ለማረጋገጥ ጠንካራ የክትትልና ድጋፍ ስርዓት መዘርጋትና ተግባራዊ ማድረግ ይገባል፡፡ የክትትልና ድጋፍ ስርዓት
በመዘርጋት ለልማትና ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ማነቆ የሆኑ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በተገቢው
ደረጃ መለየታቸውንና የችግሮቹን ትክክለኛ ምንጭ ማክሰም ለማክሰም የተቀረጹና ተግባራዊ የተደረጉ
ስልቶች ውጤት ማምጣታቸውን በመከታተል እና በመደገፍ ለሚመለከተው አካል ግብረ-መልስ መስጠት
እንዲቻል እያንዳንዱ የመንግስት ተቋም በዓመቱ መጀመሪያ ላይ ሁሉንም የለውጥ ሰራዊት አካላት በንቃት
ባሳተፈ አግባብ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍቻ ዕቅድ ማዘጋጀት ይጠበቅበታል፡፡ የመልካም አስተዳደር
እቅዱ አፈጻጸም ውጤታማ እንዲሆን በየደረጃው የሚገኙ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ተቋማት
በእቅዱ አፈጻጸም ላይ ተገቢውን የክትትልና ድጋፍ ስራ ማከናወን ይገባቸዋል፡፡ ለዚህ የክትትልና ድጋፍ ስራ
መሳለጥ ያመች ዘንድ እያንዳንዱ ተቋም ያዘጋጀውን የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍቻ እቅድ ትግበራ
ስራውን በቅርብ ለሚከታተል የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት አደረጃጀት ማድረስ ይጠበቅበታል፡፡
የክትትልና ድጋፍ ውጤቱንም ቀጣይ በሆነ መልኩ ለፈጻሚው፣ ለህዝብ ክንፉና ለባለድርሻ አካላት ማሳወቅ
አስፈላጊና ወሳኝ ነው፡፡ በተጓዳኝም በክትትልና ድጋፉ የታዩ ደካማ አፈፃፀሞችን ለማስተካከል የተወሰዱ
ማስተካከያዎችን ለሁሉም ለሚመለከተው አካል ሁሉ በወቅቱ መግለፅ ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም ሁሉም
የተቋማት የመልካም አስተዳደር ዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራና የአፈፃፀም ግምገማ ተግባራት ቀጥሎ በቀረቡት
የክትትልና ድጋፍ አግባቦች በጥብቅ ዲሲፕሊን ተይዘው ተግባራዊ መድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡ እነዚህ የክትትልና
ድጋፍ አግባቦችም፤
ሀ) ሪፖርትና ግብረ መልስ፣
ለ) ሱፐርቪዥንና ግብረ መልስ እና
ሐ) ግምገማና ግብረ መልስ
ሲሆኑ በእያንዳንዱ የክትትልና ድጋፍ አግባብ የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትም እንደሚከተለው ቀርበዋል፤
42
ሀ) ሪፖርትና ግብረ-መልስ
ሁሉም የመንግስት ተቋማት በተለያዩ ስልቶች በመጠቀም የተለዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት
የታቀዱ ተግባራትን አፈጻጸም በተመለከተ በተጨባጭ የተገኙ ውጤቶችን፣ ያጋጠሙ ችግሮችንና የተወሰዱ
መፍትሔዎችን የያዘ ዝርዝር ሪፖርት በየወሩ መጨረሻ ተቋማቸው በሚገኝበት የአስተዳደር ደረጃ ለሚገኙና
ስራውን በቅርብ ለሚከታተሉ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት አደረጃጀቶች መላክ ይጠበቅባቸዋል፡፡
የተቋማት የመልካም አስተዳደር ችግር መፍቻ ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ወጥነት እንዲኖረውና ለመልካም
አስተዳደር ሥራዎች ውጤታማነት ወሳኝ የሆኑ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንዲሆን የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱ ይዘት
ምን መምሰል እንዳለበት የሚያሳይ ፎርማት በየደረጃው በሚገኙ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት
አካላት ተዘጋጅቶ ለሁሉም የመንግስት ተቋማት እንዲደርስ ይደረጋል፡፡ እያንዳንዱ ተቋምም በየደረጃው
የተገመገመውን የመልካም አስተዳደር አፈጻጸም ሪፖርት በዕቅድ ትግበራው ጊዜ ውስጥ የተመዘገቡ
ውጤቶችን በማጠናቀር በፎርማቱ መሰረት ቀጣዩ ወር ገብቶ በ 5 (አምስት) ቀናት ውስጥ በየደረጃው ላሉ
የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት አካላት ማድረስ ይኖርበታል፡፡
የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ተቋማትም ከየተቋማቱ የሚላኩላቸው የመልካም አስተዳደር ችግሮች
መፍቻ ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርቶችን በዕቅዶቻቸው ከተቀመጡ ዒላማዎች አንጻር በመፈተሽና በመተንተን
የተጠቃለለ የጽሑፍ ግብረ መልስ አጠናቅረው ቀጣዩ ወር ገብቶ በ 15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ
ለየተቋማቱ ማድረስ ይኖርባቸዋል፡፡ ተቋማቱም የተሰጡ ግብረ መልሶችን በግብዓትነት በመጠቀም
ክፍተቶቻቸውን አርመው በቀጣይ በሚልኩት ሪፖርት በግብረ መልሱ የተጠቀሱ ክፍተቶች መስተካከላቸውን
የሚገልጽ ሪፖርት መላክ ይጠበቅባቸዋል፡፡
በተጨማሪም የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር የፌዴራል ተቋማት የመልካም አስተዳደር ዕቅድ አፈፃፀምን
ውጤታማ ለማድረግና ወደ ተቀራረበ ደረጃ ለማድረስ የሚያከናውናቸው የሱፐርቪዥን ስራዎችን ለማሳለጥ እያንዳንዱን
43
ተቋም የሚከታተሉ ፈፃሚዎችን በመመደብ ተከታታይ የክትትልና ድጋፍ ስራ በተጨማሪ በዓመት ሁለት ጊዜ የሱፐርቪዥን
ሥራ በማካሄድና የጽሑፍ ግብረ መልስ በመስጠት፣ በተጨማሪም ከተቋማት ከፍተኛ አመራር አካላት የጋራ መድረክ
በማዘጋጀት በሱፐርቪዥን ስራዎቹ የተገኙ ምርጥ ልምዶችና ተሞክሮዎችን ማስፋት በሚቻልበት ሁኔታ፣ እንዲሁም
በሱፐርቪዥኑ ግኝት ሪፖርት ላይ ግምገማ በማድረግ በሚደረስባቸው የመፍትሔ አቅጣጫዎች ላይ የጋራ መግባባት
በመፍጠር በቀጣይ ለተሻለ ለውጥ የሚሰማሩበትንና ለበለጠ መሻሻል የሚተጉበት ሁኔታ ሊፈጥር ይገባል፡፡ በክልሎችና ከተማ
አስተዳደሮች ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮዎች በኩልም በየአስተዳደር አካባቢዎቻቸው የራሳቸውን ነባራዊ
ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ተመሳሳይ ተግባራትን ማስተባበርና ማከናወን ይጠበቅባቸዋል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር እና የክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ፐብሊክ ሰርቪስና
የሰው ሀብት ልማት ቢሮዎች በየግማሽ ዓመቱ ከሁለቱም የተውጣጡ አባላትን የያዘ የሱፐርቪዥን ቡድን ማደራጀት
አለባቸው፡፡ ቡደኑ ተቋማት ላይ በመገኘት ከለውጥና መልካም አስተዳደር ዕቅዶች አፈፃፀም አንፃር በተጨባጭ
መሬት ላይ ያለውን አፈጻጸም መፈተሽና የሱፐርቪዥን ስራውን ግኝት ሪፖርት ለሚመለከተው አካል
ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ የሱፐርቪዥን ግምገማውን ግብረ-መልስ በሱፐርቪዥኑ ለተካተቱ ሁሉም ተቋማት
በመስጠትና በግብረ መልሱ ላይ የጋራ መግባባት በመፍጠር ወደ ስራ እንዲሰማሩ መደረግ ይኖርበታል፡፡
ይህ በአንድ የበጀት አመት ሁለቴ የሚደረገው አገራዊ የሱፐርቪዥን ሥራ እንደተጠበቀ ሆኖ ሌሎች የአካል ምልከታ
ሥራዎችም በራሳቸው በተቋማቱና በየደረጃው ባሉ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት አካላት በቀጣይነት
የሚያካሂዱበት ሁኔታ መኖር አለበት፡፡
ሐ) ግምገማና ግብረ-መልስ
ሁሉም የመንግስት ተቋማት የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን በየደረጃው ከሚያስተባብረው አካል ጋር የመልካም አስተዳደር
ሥራዎች አፈጻጸምና በተመዘገቡ ውጤቶች ላይ የጋራ ግምገማ ማካሄድ ይኖርበታል፡፡ በፌደራል ደረጃ የሚደረገው ግምገማ
የተቋማት ኃላፊዎችን የሚያሳትፍ ሲሆን ከየተቋማቱ የተላኩ የአፈጻጸም ሪፖርቶችን ላይ በየሩብ ዓመቱ መገምገምና በታዩ
ክፍተቶች ላይ የጋራ አቅጣጫ ማስቀመጥ ይኖርበታል፡፡ በተመሳሰይ ሁኔታ የክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የፐብሊክ
ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮዎች ከየተቋማቱ የሚላኩላቸው የሩብ አመት የመልካም አስተዳደር ዕቅድ አፈጻጸም
ሪፖርቶችን በጋራ በመገምገም የጋራ አቅጣጫ ማስቀመጥ አለባቸው፡፡
44
ከዚህም በተጨማሪ በፌደራልም ሆነ በየደረጃው ያሉ ተቋማት ከህዝብ ክንፎቻቸውና ባለድርሻ አካላት ጋር በየሩብ ዓመቱ፣
ከፍተኛ አመራሩ ከሠራተኞች ጋር በየወሩና ከመካከለኛ አመራሩ ጋር ደግሞ በየሁለት ሳምንቱ እና መካከለኛ አመራሩ ከለውጥ
ሠራዊቱ ጋር በየሳምንቱ በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ መወያየትና አፈጻጸሙን መገምገም ይኖርባቸዋል፡፡ እንዲሁም
ለመልካም አስተዳደር መረጋገጥ ማነቆ የሆነውን የኪራይ ሰብሳቢነት ማክሰሚያ እስትራቴጂ በመንደፍ የ 1 ለ 5 የለውጥ
ሠራዊት የውይይት አጀንዳ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡
በጋራ ግምገማ መድረኩ በሚሰጠው አቅጣጫ መሰረትም እያንዳንዱ የመንግስት ተቋም በሳምንት ጊዜ ውስጥ ሁሉንም
የለውጥ ኃይሎችን ያሣተፈ የተዋረድ ግምገማ በማድረግ የማስተካከያ እርምጃ መውሰድ ይኖርበታል፡፡ በተጨማሪም
በግምገማ መድረኩ ላይ ጠንካራና ደካማ አፈጻጸሞችን የተጠቃለለ የግምገማ ግብረ መልስ ለየተቋማት እንዲደርስ
ይደረጋል፡፡
ሀ. የዋና ተቋማት ሚና
1. የተቋሙን የክትትልና ድጋፍ እቅድ የውስጥ የስራ ክፍሎችን፣ ተጠሪ ተቋማትን፤ የህዝብ ክንፉንና ሌሎች
ባለድረሻ አካላትን በማሳተፍ እንዲዘጋጅ ማድረግ፣
2. የተቋሙን የውስጥ የስራ ሂደቶችና የተጠሪ ተቋማት የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈጻጸም መመዘኛ
መስፈርትን መቅረጽና ቼክ-ሊስቶችን በማዘጋጀት ተግባራዊ እንዲሆኑ ማድረግ፣
3. የውስጥ የስራ ሂደቶችና ተጠሪ ተቋማት የመልካም አስተዳደር እቅድ ዝግጅት መከታተልና መደገፍ፣
4. የውስጥ የስራ ሂደቶችና ተጠሪ ተቋማት የመልካም አስተዳደር እቅድ ትግበራን መከታተልና መደገፍ፣
5. ሁሉንም የሰራዊት አቅሞች አሟጦ በመጠቀም የዋናውን እና የተጠሪ ተቋማቱን የመልካም አስተዳደር እቅድ
አፈጻጸም መከታተልና መደገፍ፣
6. የክትትልና ድጋፍ ስራውን ውጤታማነት በየጊዜው በመገምገም አግባብነት ያለው የማሻሻያ እርምጃ መውሰድ፣
7. የተቋሙን የውስጥ የስራ ሂደቶችና የተጠሪ ተቋማት የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈጻጸም ደረጃን መለየት፣
እውቅና መስጠትና የተዘረጋውን የተጠያቂነት ስርአት ተግባራዊ ማድረግ፣
ለ. የተጠሪ ተቋማት ሚና
1. የውስጥ ስራ ክፍሎችን፣ የህዝብ ክንፉንና ሌሎች ባለድረሻ አካላትን በማሳተፍ እንዲዘጋጅ ማድረግ፣
2. የተቋሙን የውስጥ የስራ ሂደቶች የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈጻጸም መመዘኛ መስፈርት መቅረጽና
ቼክ-ሊስቶችን በማዘጋጀት ተግባራዊ እንዲሆኑ ማድረግ፣
3. የውስጥ የስራ ሂደቶች የመልካም አስተዳደር እቅድ ዝግጅት መከታተልና መደገፍ፣
45
4. የውስጥ የስራ ሂደቶች የመልካም አስተዳደር እቅድ ትግበራን መከታተልና መደገፍ፣
5. ሁሉንም የሰራዊት አቅሞች አሟጦ በመጠቀም የተቋሙን የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈጻጸም
መከታተልና መደገፍ፣
6. የክትትልና ድጋፍ ስራውን ውጤታማነት በየጊዜው በመገምገም አግባብነት ያለው የማሻሻያ እርምጃ
መውሰድ፣
7. የተቋሙን የውስጥ የስራ ሂደቶች የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈጻጸም ደረጃ መለየት፣ እውቅና
መስጠትና የተዘረጋውን የተጠያቂነት ስርአት ተግባራዊ ማድረግ፣
1. የተቋሙን የክትትልና ድጋፍ እቅድ የውስጥ የስራ ክፍሎችን፣ ተጠሪ ተቋማትን፤ የህዝብ ክንፉንና ሌሎች
ባለድረሻ አካላትን በማሳተፍ እንዲዘጋጅ ማድረግ፣
2. የተቋሙን የውስጥ የስራ ሂደቶችና የተጠሪ ተቋማትን የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈጻጸም መመዘኛ
መስፈርት መቅረጽ እና ቼክ-ሊስቶችን በማዘጋጀት ተግባራዊ እንዲሆኑ ማድረግ፣
3. የውስጥ የስራ ሂደቶችና የተጠሪ ተቋማትን የመልካም አስተዳደር እቅድ ዝግጅት እና ትግበራን መከታተልና
መደገፍ፣
4. ሁሉንም የሰራዊት አቅሞች አሟጦ በመጠቀም የዋናውን እና የተጠሪ ተቋማቱን የመልካም አስተዳደር እቅድ
አፈጻጸም መከታተልና መደገፍ፣
5. የክትትልና ድጋፍ ስራውን ውጤታማነት በየጊዜው በመገምገም አግባብነት ያለው የማሻሻያ እርምጃ መውሰድ፣
6. የተቋሙን የውስጥ የስራ ሂደቶችና የተጠሪ ተቋማት የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈጻጸም ደረጃ መለየት፣
እውቅና መስጠት እና የተዘረጋውን የተጠያቂነት ስርዓት ተግባራዊ ማድረግ፣
1. የተቋማት የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈጻጸም ክትትልና ድጋፍ የሚመራበትን ማእቀፍ ማዘጋጀት፣
2. የተቋማትን የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈጻጸም መመዘኛ መስፈርት መቅረጽና ቼክ -ሊስቶችን በማዘጋጀት
መከታተልና መደገፍ፣
3. የተቋማትን የመልካም አስተዳደር እቅድ ዝግጅት መከታተልና መደገፍ፣
4. የተቋማትን የመልካም አስተዳደር አፈጻጸም የክትትልና ድጋፍ እቅድ ሁሉንም የለውጥ ሰራዊቱ አካላት
በማሳተፍ እንዲዘጋጅ መከታተልና መደገፍ፣
5. የተቋማትን የመልካም አስተዳደር እቅድ ትግበራን መከታተልና መደገፍ፣
6. ሁሉንም የሰራዊት አቅሞች አሟጦ በመጠቀም የተቋማትን የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈጻጸም
መከታተልና መደገፍ፣
7. የክትትልና ድጋፍ ስራውን ውጤታማነት በየጊዜው በመገምገም አግባብነት ያለው የማሻሻያ እርምጃ
መውሰድ፣
46
8. የተቋማትን የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈጻጸም ደረጃ መለየት፣ እውቅና መስጠት እና የተዘረጋውን
የተጠያቂነት ስርዓት ተግባራዊ ማድረግ፣
በክትትልና ድጋፍ ስራ ውስጥ የህዝብ አደረጃጀቶችን ማሳተፍ የሥራዎች አፈፃፀም ደረጃ በቀጣይነት
እየተሻሻለ እንዲሄድ ከማገዝም ባሻገር የመንግስት ተቋማትን የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ተደራሽነት
በማጎልበት የዜጎችን እርካታ ለማሳደግ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡ በመሆኑም ህዝቡ በተደራጀ መልኩ
በተለያዩ የክትትልና ድጋፍ አግባቦች ላይ በንቃት ሲሳተፍ የመንግስት ተቋማት አፈፃፀምና የአገልግሎት ጥራት
እንዲሻሻል የራሱን ሚና ከመወጣቱም በላይ በአጠቃላይ ሂደቱ ላይ የሚፈጥረው የባለቤትነት ስሜት መልካም
አስተዳደርን በሁሉም የአስተዳደር ደረጃዎች ለማስፈን ለተነደፈው ግብ ውጤታማ አፈፃፀም ከፍተኛ
አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡
በዚሁ መሠረት በመልካም አስተዳደር ዕቅድ አፈፃፀም ክትትልና ድጋፍ ሂደት ውስጥ የህዝብ ክንፉ የሚኖረው
ሚና እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
1. የራሳቸውን የክትትልና ድጋፍ ዕቅድ ማዘጋጀት፣
2. በመንግስት ክንፉ የክትትልና ድጋፍ ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ላይ በንቃት መሳተፍና ዕቅዱ የሚዳብርበትን
ምክረ-ሃሳብ ማቅረብ፣
3. ለመልካም አስተዳደር ዕቅድ አፈፃፀም ክትትልና ድጋፍ ስራዎች ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን በመለየት ለተቋማት
አገልግሎት አሰጣጥ ቀጣይ መሻሻል በሚያግዝ መልኩ ድጋፍ ማድረግ፣
4. የመልካም አስተዳደር ዕቅዱን የአፈጻጸም አመላካቾችና ሪፖርት በየወቅቱ በመዳሰስ ጠቃሚ የማስተካከያ
ሃሳቦችን ማቅረብ፣
5. ከመንግስት ክንፉ ጋር በሚኖሩ የምክክርና የአፈፃፀም ግምገማና ግብረ-መልስ መድረኮች ላይ በንቃትና
በባለቤትነት ስሜት መሳተፍ፣
6. ከተቋማት ጋር በመሆን የድጋፍ፣ ክትትልና ግምገማ ዝክረ-ተግባር ማዘጋጀት፣
7. በሁሉም የክትትልና ድጋፍ አግባቦች የሚሰበሰቡ መረጃዎችንና የአፈፃፀም መረጃዎችን በማደራጀት፣
የአፈፃፀም ሪፖርቶችን በማጠናቀርና ግብረ መልስ በመስጠት ሂደቶች ላይ በንቃት መሳተፍ፣
47
አባሪ፡- የውስጥና የውጭ የመልካም አስተዳደር ሥራዎች እቅድ፣ ድርጊት መርሃ ግብርና አፈጻጸም ሪፖርት ማቅረቢያ ቅጾች
ቅጽ 001፤ የተለዩ የውስጥና የውጭ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍቻ እቅድ ማጠቃለያ
የተለዩ ዋና ዋና የችግሮቹ መንስኤ በችግሩ ምክኒያት ችግሮቹን ለመፍታት የተቀረፁ ግቦች የውጤት ማረጋገጫ
የመልካም የሰው ኃይል የተጣሰው የመልካም እና ግብ ተኮር ተግባራት ስልቶች
ተ.ቁ ምርመራ
አስተዳደር (ከአመለካከት፣ አደረጃጀት አሰራር አስተዳደር መርሆ የሚጠበቅ ውጤት /Means of
ግቦች ግብ ተኮር ተግባራት
ችግሮች እውቀት፣ክህሎት) Verifications/
1. የውስጥ
1.1.
1.2.
2. የውጭ
2.1.
2.2.
ቅጽ 002፡ ዓመታዊ የውስጥና የውጭ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍቻ የድርጊት መርሃ ግብር ማቅረቢ ቅጽ
ተ.ቁ ግቦችና ግብ ተኮር ተግባራት መለኪያ ክብደት መነሻ ዒላማ ዒላማ በሩብ ዓመት የሚጠበቅ ፈጻሚ አካል
48
ውጤት
1ኛ 2ኛ 3ኛ 4ኛ
የውስጥ
1. ግብ
1.1. ግብ ተኮር ተግባራት
1.1.1. ዝርዝር ተግባራት
የውጭ
1. ግብ
1.1. ግብ ተኮር ተግባራት
1.1.1. ዝርዝር ተግባራት
ቅጽ 003፤ ወርሃዊ የውስጥና የውጭ የመልካም አስተዳደር ችግሮች አፈታት አፈጻጸም ሪፖርት ማቅረቢያ ቅጽ
ተ.ቁ ግቦችና ግብ ተኮር መለኪያ ክብደት የዓመቱ የወሩ የወሩ የወሩ አፈጻጸም የስካሁኑ የስካሁኑ የስካሁን1 የተመዘገበ ምርመራ
49
ዒላማ ክንውን በመቶኛ ዒላማ አፈጻጻም
ተግባራት ዒላማ ክንውን በመቶኛ ውጤት
በመቶኛ
01 02 03 04 05 06 07 08=(07/06)*1 09 10 11=10/09)*1 12=11*04/1 13
00 00 00
የውስጥ
1 ግብ
1.1 ግብ ተኮር ተግባራት
1.1.1. ዝርዝር ተግባራት
የውጭ
1 ግብ
1.1 ግብ ተኮር ተግባራት
1.1.1. ዝርዝር ተግባራት
ቅጽ 004፤ የሩብ ዓመት የውስጥና የውጭ የመልካም አስተዳደር ችግሮች አፈታት አፈጻጸም ሪፖርት ማቅረቢያ ቅጽ
ተ.ቁ ግቦችና ግብ ተኮር መለኪያ ክብደት የዓመቱ የሩብ የሩብ የሩብ ዓመቱ ከዓመቱ አፈጻጻም የተመዘገበ ውጤት ምርመራ
ተግባራት ዒላማ ዓመቱ ዓመቱ አፈጻጻም በመቶኛ በመቶኛ
1
የስካሁን አፈጻጸም በመቶኛ የሚያለክተው የተደረሰበት ወር እና የቀደሙት መራትን ክንውን ለ ወሩን ጨምሮ ከወሩ በፊት ለተቀመጡ ዒላማዎች ተካፍሎ ከመቶ የሚገኝ አፈጻጸም ደረጃ ማለት ነው፡፡
50
ዒላማ ክንውን
01 02 03 04 05 06 07 08=(07/06)*100 09=(07/05)*100 10=08*04/100 11
የውስጥ
1 ግብ
1.1. ግብ ተኮር ተግባራት
1.1.1. ዝርዝር ተግባራት
የውጭ
1. ግብ
1.1. ግብ ተኮር ተግባራት
1.1.1. ዝርዝር ተግባራት
ቅጽ 005፤ የስድስት ወራት የውስጥና የውጭ የመልካም አስተዳደር ችግሮች አፈታት አፈጻጸም ሪፖርት ማቅረቢያ ቅጽ
ተ.ቁ ግቦችና ግብ ተኮር መለኪያ ክብደት የዓመቱ የግማሽ የግማሽ የግማሽ ዓመቱ ከዓመቱ አፈጻጻም የተመዘገበ ውጤት ምርመራ
ተግባራት ዒላማ ዓመቱ ዓመቱ አፈጻጻም በመቶኛ በመቶኛ
51
ዒላማ ክንውን
01 02 03 04 05 06 07 08=(07/06)*100 09=(07/05)*100 10=08*04/100 11
የውስጥ
1 ግብ
1.1. ግብ ተኮር ተግባራት
1.1.1. ዝርዝር ተግባራት
የውጭ
1. ግብ
1.1. ግብ ተኮር ተግባራት
1.1.1. ዝርዝር ተግባራት
ቅጽ 006፤ የዓመት የውስጥና የውጭ የመልካም አስተዳደር ችግሮች አፈታት አፈጻጸም ሪፖርት ማቅረቢያ ቅጽ
የዓመቱ የዓመቱ አፈጻጻም የተመዘገበ
ተ.ቁ ግቦችና ግብ ተኮር ተግባራት መለኪያ ክብደት የዓመቱ ክንውን ምርመራ
ዒላማ በመቶኛ ውጤት
01 02 03 04 05 06 07=(06/05)*100 08=07*04/100 9
52
የውስጥ
1 ግብ
1.1. ግብ ተኮር ተግባራት
1.1.1. ዝርዝር ተግባራት
የውጭ
1. ግብ
1.1. ግብ ተኮር ተግባራት
1.1.1. ዝርዝር ተግባራት
53
ማጣቀሻዎች /References/
54
15. Marwala, Tshilidzi (2006). Foundations for a Developmental State: A case for technical
education. Retrieved from http://arxiv.org/ftp/arxiv /papers/0907/ 0907.2019.pdf.
16. Meles Zenawi (n.d.) African Development: Dead Ends and New Beginnings. Retrieved
from www.ethioobserver.net.
17. Ndega, Stephen N. (2002). Decentralization in Africa; Astock taking survey: Working
paper series. 40(1).
18. Nicole Maldonado(2010)፡ The World Bank’s Evolving Concept of Good Governance and
Its Impact on Human Rights ፣ Doctoral Workshop on Development and International
Organizations Stockholm, Sweden, May 29-30, 2010
19. Rondinelli, D. A. (1989). Decentralization in Developing Countries: A Review of Recent
Experience. Washington D.C.: World Bank Staff Working Paper, No. 581.
20. Rondinelli, D.A. (2007). Governments Serving People: the Changing Roles of Public
Administration in Democratic Governance. 7th Global Forum on Reinventing
Government. Vienna. Austria: United Nations.
21. Samuel P. Huntington Democracy's Third Wave, Journal of Democracy Vol.2. No.2
Spring, 1991.
22. United Nations Economic and Social Council. (2013). The Developmental State: What
Options for Africa? Retrieved from http://www.uneca.org/sites/default/files/uploaded-
documents/CGPP/cgpp-3_issues-paper-english_final_160113.pdf.
23. World Bank annual report August (2007). America፡ New work.
24. World Bank Annual report December 2008 America፡ Washington.
25. World Bank (2002) Civil ServBank (eform; Strengthening World Bank and IMF
Collaboration. Washington: Library of Congress Cataloging-In-Publication Data.
26. World BANK Sub-Saharan Africa, From Crisis to Sustainable Growth, a Long Term
Perspective Study, Washington: The World Bank, 1989.
27. Yilmaz, Serdar and Venugopal, Varsha (2008). Local Government Discretion and
Accountability in Ethiopia. Georgia State University International Studies Program.
28. የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጉዳዮች በኢትዮጵያ፣ 1994፣
29. የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ትግልና አብዮታዊ ዲሞክራሲ፣ 1999፣
30. የተሀድሶዉ መስመርና የኢትዮጵያ ህዳሴ (2011).
55
31. የኢፌዴሪ የከተማ ልማት፣ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር፣ የተሻሻለዉ የከተሞች የልማታዊ
መልካም አስተዳደር ግንባታ ማዕቀፍ እና የማስፈፀሚያ ስልቶቹ፣ ሚያዝያ 2006 ዓ.ም.፣ አዲስ አበባ፡፡
32. ደሳለኝ ራህመቶ (2014) (አዳ) “በኢትዮጵያ ልማት ላይ የተሰነዘሩ አስተያየቶች/Reflections on
Development in Ethiopia/” በደሳለኝ ራህመቶ፣ ምህረት አየነው፣ አስናቀ ከፍ አለና ብርጊት
ሀበርማን አዲስ አበባ፣ ኤክሊፕስ፡፡ OPM, and CIPFA, “Good
Governance Standard for Public Services,” 2004.
56