You are on page 1of 24

/

የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ ቤት የትምህርትና ሥልጠና መመሪያ

Kaleab Pawlos (MA)

ሰኔ 2009 ዓ.ም

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 1


መግቢያ

የትምህርትና ሥልጠና የአንድን ተቋም የማስፈጸም አቅም ግንባታ መሳሪያዎች አካል ከመሆናቸውም በላይ በተቋሙ ውስጥ የሚታየውን የሥራ
አፈጻጸም ችግር ለመፍታት የሚጠቀሙበት መሳሪያ ነው። ሰራተኞች ሙያዊ ዕውቀታቸውንና ክህሎታቸውን በመገንባት የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት
ለመወጣት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። በፈጣን የዕድገት ጉዞ ላይ ከሚገኘው ሳይንስና ቴክኖሎጂ ጋር ተጣጥሞ ለመጓዝና በዘርፉ ዕድገት የሙያተኛውን
ዕውቀትና ችሎታ በትምህርትና ስልጠና በመገንባት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ አስተዋጽኦው ትልቅ ነው።

ትምህርትና ስልጠና የሰውን ልጅ የእውቀት፣ የክህሎት፣ የባህርይና የአመለካከት ደረጃ ለማሳደግ እንደ ትልቅ መሳሪያ የሚያገለግል ስለሆነ በተቋሙ
ውስጥ በየደረጃው የሚገኙ የስራ ሃላፊዎች፣ ባለሙያዎችና ሌሎች ሰራተኞች የተጣለባቸውን ተግባርና ሃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ ለማስቻል
ከወቅቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር እንዲራመዱ እና የመ/ቤታቸውን አላማና ግብ በአግባቡ ተረድተው ወጤታማ በሆነ መልኩ እንዲያሳኩ
ለማድረግ የትምህርትና ሥልጠና ዕድል ማግኘት አለባቸው።

በፌደራል የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 515/1999 አንቀጽ 12/2 ላይ “ማንኛውም የመንግስት መ/ቤት ስትራቴጂክ እቅዱን መሰረት በማድረግ
የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ የሰው ሀይል ዕቅዱን አጥንቶ ተግባራዊ ማድረግ አለበት።” ይላል። አንቀጽ 58 ንዑስ አንቀጽ 1 ላይም “እያንዳንዱ
የመንግስት መ/ቤት ለመ/ቤቱና ለሰራተኛው የሚያሰፈልገውን ሥልጠና በማጥናት፣ ዕቅድ በማውጣትና በጀት በማስፈቀድ ሰራተኞቹ አስፈላጊውን
ሥልጠና እንዲያገኙ የማድረግና ለፌደራል የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚ/ር የማሳወቅ ሃላፊነት አለበት።” በማለት በመንግስት መ/ቤቶች
ላይ ሃላፊነት ጥሏል።

ከዚህ ሌላ የመግስት ኮሙየኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የጥናት፣ ምርምርና አቅም ግንባታ ጄኔራል ዳይሬክቶሬት ተግባርና ሃላፊነት አስመልክቶ ሰኔ 27/2006
ዓ.ም በቁጥር ኮ/ሠሀ-19/9098 ባስተላለፈው ሰርኩላር “1 ኛ).ተቋሙን በማገልገል ያለውን የሰው ሃብት አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ የአገር ውስጥና
የውጭ አገር የትምህርትና ስልጠና ዕድሎችን በማፈላለግ ተግበራዊ ያደርጋል፣ 2 ኛ). በፌዴራል እና በክልል ያሉ ኮሙዩኬተሮችንና በተቋሙ ውስጥ
የሚገኘውን የሰው ሃብት አቅም ክፍተት ፍላጎት ዳሰሳ በማድረግ እንዲለይ ያደርጋል፣ የአቅም ክፍተቶች የሚሞሉበትን የትምህርትና ስልጠና
ፕሮግራሞች በመቅረጽ ተግባራዊ ያደርጋል፣ ከስልጠና በኋላ የተገኘውን የስራ ላይ ለውጥ በመገምገም ከሙያዊ ትንተና ጋር ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ
ያደርጋል፣ 3 ኛ).ስልጠናዎች የሚመሩበትን ዝክረ ተግባር ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ ያደርጋል፣ የስልጠና ርዕሰ ጉዳዮችንም በመለየትና በማፅደቅ ሞጅሎች
እንዲዘጋጁና ተፈፃሚ እንዲሆኑ ይሠራል፣ 4 ኛ). በኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን፣ በማህበረሰብ ሚዲያ እና በህዝብ ግንኙነት የስራ መስክ ተሰማርተው
እየሰሩ ያሉና አዲስ የሚቀጠሩ ባለሙያዎችን አቅም ለመገንባት /ለማብቃት/ የሚያስችል የስልጠና ማዕከል እንዲደራጅ ያደርጋል፣ ስራውን በባለቤትነት
ይመራል” የሚባሉ ተግባርና ሃላፊነቶች ግምት ውስጥ በማስገባት የትምህርትና ስልጠና መመሪያው አሻሽሎ ማዘጋጀቱ ታምኖበታል።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 2
በዚሁ መሰረት የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት በተቋቋመበት አዋጅ፣ በተሰጠው ስልጣንና ሃላፊነት መሰረት በኮሙዩኒኬሽን፣ ኢንፎርሜሽንና
በሚዲያ ልማት ዘርፍ ሁለገብ አቅም መገንባት እንዲሁም ህዝቡ በዋና ዋና አገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት እንዲፈጠር በዘርፉ ስትራቴጂካዊ
የመሪነት ሚና መጫወት እንዲችል እንዲሁም በጽ/ቤቱ ማቋቋሚያ ደንብ ቁጥር 158/2001 በ 5.3 ላይ የፌደራል የመንግስት መ/ቤቶችን የህዝብ
ግንኙነት ሰራተኞች አቅም ያለበትን ደረጃ እያጠናና እየፈተሸ አቅማቸውን የመገንባት ተግባራትን ከወቅቱ ሁኔታ ጋር እያጣጣመ የመንግስትን ተልዕኮ
እና አላማውን ለማሳካት በሚየስችል መልኩ የፌደራልና የክልል ኮሙዩኒኬተሮች በብቃትና በጥራት አሟልቶ የሰው ሃይሉን የሚፈለገውን ውጤት
ማምጣት እንዲቻል በትኩረት መሰራትን ዘመኑ ከሚጠይቀው የሚዲያ፣ ኮሙዩኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን አንጻር በትምህርትና ስልጠና እንዲገነባ ማድረግ
ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው።

በመሆኑም ይህ መመሪያ የፌደራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 515/1999 ክፍል ስድስት አንቀጽ 58 ፣የመንግስት ሠራተኞችን የማሰልጠን
ኃላፊነትን አስመልክቶ በንዑስ አንቀፅ 1 እና 2 የተገለጸውን መነሻ በማድረግና ቀደም ሲል በነበረው የጽ/ቤቱ የትምህርትና ስልጠና መመሪያ ላይ የታየውን
ክፍተት ሊሞላ በሚችል መልኩ አስተካክሎና መተግበር በሚያስችል ሁኔታ እንደገና ማሻሻያ በማድረግ ተዘጋጅቷል።

ስለሆነም የሰው ሃብት አቅምን ለመገንባት በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚሰጥ የትምህርትና ሥልጠና መመሪያ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ
በቀድሞው የሥልጠና መመሪያ ላይ በአፈጻጸም የተከሰቱ ክፍተቶችን መዝጋት በሚያስችል መልኩ ማሻሻያ የተደረገበት ይህ የትምህርትና ሥልጠና
መመሪያ ተሻሽሎ እንዲወጣ ተደርጓል።

ክፍል አንድ
ጠቅላላ
1.1) አጭር ርዕስ “ይህ መመሪያ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ሥልጠና መመሪያ ቁጥር ---/2008” ተብሎ ሊጠቀስ
ይችላል።
1.2) ትርጓሜ
የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በሰተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ:-

1.2.1. “ጽ/ቤት” ማለት በሚኒስትሮች ም/ቤት ማቋቋሚያ ደንብ ቁጥር 158/2001 የተቋቋመ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።
1.2.2. “የበላይ ሃላፊ” ማለት ጽ/ቤቱን በበላይነት የሚመራ ሚኒስትር ወይም ሚኒስትር ዴኤታ ማለት ነው።
1.2.3. “ትምህርት” ማለት የመ/ቤቱ ሰራተኞች በስራ ላይ እንዳሉ ወይም ለተወሰነ ጊዜ ስራቸውን አቋርጠው ደረጃቸውን ከፍ ለማድረግ በአገር ውስጥ
ወይም በውጭ አገር ዕውቀት የሚቀስሙበት ሥርዓት ነው።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 3


1.2.4. የጥናት፣ ምርምርና አቅም ግንባታ ጄ/ዳይሬክቶሬት ማለት የጽ/ቤቱን እንዲሁም በፌዴራልና በክልል የሚገኙ የሚዲያና የኮሙዩኒኬሽን
ሃላፊዎችና ባለሙያዎች አቅማቸው እንዲገነባ የሚሰራና በመስኩ ጥናትና ምርምር በማድረግ በመንግስት ፖሊሲዎዎችና ስትራቴጂዎች ግባት
የሚያቀርብ ነው።
1.2.5. “ሥልጠና” ማለት ሠራተኛው የተሰማራበትን የስራ ድርሻ በቅልጥፍና እና በጥራት ለማከናወን እንዲችል በታቀደ፣ በተደራጀና በተመቻቸ መልኩ
በዕውቀት፣ በክህሎት፣ በአመለካከትና ሙያ ላይ ተመስርቶ የሚሰጥ ነው።
1.2.6. ‘’የትምህርትና ሥልጠና ወጪዎች’’ ማለት በአገር ውስጥ ወይም በውጭ አገር ለትምህርትና ሥልጠና በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የዋሉ
አጠቃላይ ወጪዎች ሲሆኑ መደበኛ ደመወዝንም ይጨምራል።
1.2.7. “የአጭር ጊዜ ሥልጠና” ማለት ለሶስት ወርና ከዚያ በታች ለሆነ ጊዜ በአገር ውስጥ ወይም በውጭ አገር የሚሰጥ ማንኛውም ስልጠና ነው።
1.2.8. “የመካከለኛ ጊዜ ሥልጠና” ማለት ከሶስት እሰከ ስድስት ወራት ለሆነ ጊዜ በአገር ውስጥ ወይም በውጭ አገር የሚሰጥ ማንኛውም ስልጠና ነው።
1.2.9. “የረጅም ጊዜ ሥልጠና” ለስድስት ወርና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ በአገር ውስጥ ወይም በውጭ አገር የሚሰጥ ማንኛውም ስልጠና ነው።
1.2.10. “የአገር ውስጥ ሥልጠና” ማለት በአገር ውስጥ የሚሰጥ ማናቸውም የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ሥልጠና ነው።
1.2.11. “የውጭ አገር ሥልጠና” ማለት ከኢትዮጵያ ውጭ በመንግስት መ/ቤቶች በጀት ወይም በእርዳታ የሚሰጥ የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ
ሥልጠና ነው።
1.2.12. “ወርክሾፕ ወይም አውደ- ጥናት ወይም ስብሰባ“ማለት ከስልጠና ውጪ የሆኑ የተለያዩ ውይይቶች፣ ጥናታዊ ጽሁፎች፣ ሪፖርቶች ወዘተ…
የሚቀርቡበትና ተሳታፊዎች የሚጋበዙበት ነው።
1.2.13. “ስኮላርሺፕ” ማለት በአገር ውስጥና በውጭ አገር ከሚገኙ ልዩ ልዩ የት/ት ተቋማት፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ መ/ቤቶች እና አገሮች
የሚገኝ ነፃ የትምህርት ወይም ሥልጠና እድል ነው።
1.2.14. ‘’የስልጠና ፍላጎት” ማለት የኮሙዩኒኬሽን፣ ኢንፎርሜሽንና የሚዲያ ዘርፍን ተልዕኮ ከማሳካት አኳያ በሚጠበቀውና በተጨባጭ ባለው
የሰራተኛው የአመለካከት፣ የዕውቀት፣ ክህሎት ደረጃ መካከል ያለውን ክፍተት የሚያመለክት መረጃ ነው።
1.2.15. ‘’የትምህርትና ስልጠና መስፈርት’’ ማለት ለማንኛውም ዓይነት ትምህርትና ስልጠና የሚላኩ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመምረጥ በዚህ
አፈጻጸም መመሪያ ውስጥ የተዘረዘሩት የማወዳደሪያ መስፈርቶች ናቸው።
1.2.16. ‘’የትምህርትና ስልጠና ውል’’ ማለት አንድ ሰራተኛ ለማንኛውም ዓይነት ትምህርትና ስልጠና ከተመረጠ ከጽ/ቤቱ ጋር የሚፈርመው የግዴታ
ሰነድ ነው።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 4


1.2.17. ‘’ የጥናት፣ ምርምርና አቅም ግንባታ ጄ/ዳይሬክቶሬት “ማለት የጽ/ቤቱን እንዲሁም በፌዴራል እና በክልል የሚገኙ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን
ኃላፊዎችንና ባለሙያዎችን አቅማቸው እንዲገነባ የሚሰራ እና በመስኩ ጥናትና ምርምር በማድረግ ለመንግስት ፖሊሲና ስትራቴጂ ግብዓት
የሚያቀርብ ጄ/ዳይሬክቶሬት ነው።
1.2.18. “ዕጩ ተወዳዳሪ” ማለት የተገኘውን የትምህርትና ስልጠና ዕድል ለማግኘት ለውድድር የቀረበ ሰራተኛ ነው።
1.2.19. “ሰራተኛ” ማለት በፌደራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ መሰረት በመ/ቤቱ ውስጥ በቋሚ ሰራተኝነት ተቀጥሮ በማገልገል ላይ የሚገኝ ሰራተኛ
ወይም የስራ ሃላፊ ነው።
1.2.20. “የትምህርትና ሥልጠና መራጭ ኮሚቴ” ማለት በጽ/ቤቱ ውስጥ የሚቋቋም የሚመጡ የስልጠና እና የትምህርት እድሎች ላይ በተቀመጡ
መስፈርቶች መሰረት ዕጩ ተወዳዳሪዎችን አወዳድሮ የሚመርጥና ለመ/ቤቱ የበላይ ሃላፊ ለውሳኔ የሚያቀርብ ማለት ነው።
1.2.21. በዚህ መመሪያ በወንድ ፆታ የተገለፀው ለሴት ፆታም ያገለግላል።
1.2.22. በዚህ መመሪያ ጋር የተያያዙት ውሎች የመመሪያው አካል ናቸው።
1.3) የመመሪያው የተፈጻሚነት ወሰን
በዚህ መመሪያ ውስጥ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ሚኒስቴር መመሪያ ጋር የሚቃረኑ ጉዳዮች ካጋጠሙ ተፈጻሚነት
እይኖራቸውም። ስለሆነም የዚህ መመሪያ ተፈፃሚነት በመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ብቻ ይሆናል።

1.4) የመመሪያው አስፈላጊነት


የጽ/ቤቱን ራዕይ እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ሰራተኞች በሚያደርጉት የተግባር እንቅስቃሴ የአቅም ውስንነት ችግር እንዳይገጥማቸው
ከሚሰሩት ስራ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባለውና ወደፊት በሚሰማሩበት የስራ መስክና ለሚቀበሉት ሃላፊነት የሚያሰፈልጋቸውን ሥልጠና/ትምህርት
ማግኘት እንዳለባቸው የማያጠያይቅ እውነታ ነው። የዚህ የትምህርትና ስልጠና መመሪያ አስፈላጊነት የሚመነጨው ጽ/ቤቱ የሰራተኞቹን አቅም
ለማጎልበት በሚያካሂዳቸው ትምህርትና ስልጠናዎች በተያዩ ጊዜያት የሚከሰቱትንና ጎልተው የታዩ የእውቀት፣ የክህሎትና የአመለካከት ችግሮችን
ለመቅረፍ በቡድን የመሰራት ባህልን ያዳበረ ሁለገብና ውጤታማ ሰራተኛ ለመፍጠር የሰራተኛውንና የስራ ሂደቱን ብሎም የጽ/ቤቱን የስራ አፈጻጸም
ውጤት ለማሳደግ የትምህርትና ስልጠና እድሎች መስፈርቱን የሚያሟሉ ሆነው የተገኙ ሰራተኞች ግልጽና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ተወዳድረው
እንዲመረጡ ለማስቻል ጭምር ነው።
1.4. የትምህርትና ስልጠና አላማዎች
1.4.1. በጽ/ቤቱ ውስጥ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ ሃላፊዎችና ሰራተኞች ሙያቸውንና እውቀታቸውን በማሻሻል የተመደቡበትን ስራ በጥራትና
በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዲያከናውኑ ለማድረግ፣

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 5


1.4.2. ሰራተኛው ከሳይንሰና ቴክኖሎጂ እድገት ጋር የሚፈጠሩ አዳዲስ እውቀትና የአሰራር ስልቶችን አውቆ ተግባራዊ እንዲያደርግ፣
1.4.3. የሰራተኞች መሰልጠን /መማር ለጽ/ቤቱ አላማ መሳካት፣ ለሰራው ጥራትና የተሻለ አሰራር ለመቀየስ እንዲያግዝ ለማድረግ፣
1.4.4. የሰራተኛውን ደካማ የስራ አፈጻጸም አስወግዶ በጥራትና በተቀላጠፈ ሁኔታ ስራውን እንዲያከናውንና ሰራተኛውን ለማበረታታትና የተሻለ
አፈጻጸም ደረጃ ላይ ለማድረስ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር፣
1.4.5. የሰራተኞችን ፍልሰት ለመቀነስና ሰራተኞቹ በጽ/ቤቱ ውስጥ ለረጅም ጊዜያት እንዲቆዩ ለማበረታታት፣
1.4.6. የጽ/ቤቱን የስራ ውጤት ለማሻሻል፣ ሰራተኞቹን ለማበረታታት፣ በችሎታ ላይ የተመሰረተ በሀገር ውስጥና በውጭ አገር የሚሰጡ
ትምህርትና ስልጠናዎችን ከአድሎ ነፃ የሆነ የውድድር ስርዓት ለማስፈን ናቸው።
1.4.7. የሚሰጡ የትምህርትና ስልጠና ዕድሎች የጽ/ቤቱን ራዕይና ተልኮ የሚያሳኩ መሆናቸውን ለማረጋገጥ።

1.5.2. የአገር ውስጥና የውጭ አገር ትምህርት እድል ምንጮችና ባህሪያት


1.5.3. ምንጮች
1.4.7.1. አገር ውስጥ ባሉ ተቋማት በመደበኛ፣ በርቀትና በተከታታይ በተለያዩ የትምህርት ደረጃዎች የሚሰጡ የትምህርትና ስልጠና እድሎች፣
1.4.7.2. ከፌደራል መንግስት ለጽ/ቤቱ የሚደለደሉ ወይም የሚሰጡ የውጭ አገር የትምህርትና ስልጠና እድሎች፣
1.4.7.3. በጽ/ቤቱ በሚቀረፁ ፕሮግራሞች አማካኝነት ከተለያዩ አካላት የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና እድሎች ናቸው።

1.5.4. ባህርያት
1.5.4.1. በቀጥታ ለጽ/ቤቱ የሚደለደሉ እድሎች:- መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶችና ተቋማት በቀጥታ ለጽ/ቤቱ ተወስነው የሚደለደሉ
ሲሆኑ የሀገር ውስጥ ወይም የውጪ ሀገር ትምህርትና ስልጠና ዕድሎችን ሊያካትቱ ይችላሉ፡፡
1.5.4.2. ተጨማሪ የውድድር ጠባይ ያላቸው እድሎች:- መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶችና ተቋማት በሚገኙ ዕድሎች የጽ/ቤቱ እጩ
ተወዳዳሪዎች
1.5.4.3. ከሌሎች መስሪያ ቤቶች፤ድርጅቶችና ሀገሮች ዕጩ ተወዳዳሪዎች ጋር የሚወዳደሩበት የትምህርትና ስልጠና ዕድሎችን ሊያካትቱ ይችላሉ፡፡

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 6


ክፍል ሁለት
2. ለትምህርትና ሥልጠና ውድድር የሚያበቁ ሁኔታዎችና ልዩ ትኩረት የሚሹ አካላት አመራረጥ
2.1. ለትምህርትና ሥልጠና ዕድል የሚያበቁ መስፈርቶች

በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር በሚሰጡ የአጭር፣ የመካከለኛና የረዥም ጊዜ የትምህርትና የሥልጠና ዕድሎች የሚወዳደሩ ሰራተኞች:-

2.1.1. በጽ/ቤቱ ቋሚ ሰራተኞች የሆነ፣ በጽ/ቤቱ ወይም በማንኛውም የመንግስት ተቋም ቢያንስ ሁለት አመት ያገለገለ፣
2.1.2. ዕድሉን በሰጠው አካል የተቀመጡ መስፈርቶችን የሚያሟሉ፣
2.1.3. በሌሎች የትምህርትና ስልጠና እድሎች ተመዝግበውና ተወዳድረው ያልተመረጡ፣
2.1.4. ቀደም ሲል በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር የአጭር፣ የመካከለኛና የረዥም ጊዜ ትምህርትና ሥልጠናዎች ላይ የተሳተፉ ከሆነ ለሌላ
የትምህርት ወይም የስልጠና ዕድል ለመወዳደር ቀድሞ የገቡትን የውል ግዴታ ያጠናቀቁ መሆን አለባቸው፣
2.1.5. የከፍተኛ ትምህርት ዕድል ተጠቃሚ የሆነ ሠራተኛ ትምህርቱ ለሚወስደው ጊዜ እጥፍ አመት አገልግሎት ለመስጠት ተመጣጣኝ ዋስትና
ማቅረብ አለበት፣
2.1.6. ለጽ/ቤቱ በቀጥታ የተደለደሉ የስልጠና ዕድሎች የተወዳደረ ዕጩ በውድድሩ ማለፉ እስካልተረጋገጠ ድረስ በሌላ ትምህርት/ስልጠና መወዳደር
አይችልም።
2.1.7. ማንኛውም እጩ ተወዳዳሪ በአገር ውስጥ ወይም በውጭ አገር በማንኛውም የትምህርት/ስልጠና ፕሮግራም ላይ ያለ መሆን የለበትም፣
2.1.8. ከአገር ውስጥና ከውጭ አገር በሚገኙ የትምህርት ዕድሎች በተመሳሳይ የትምህርት ደረጃ በድጋሚ መወዳደር አይችልም፣
2.1.9. የስራ አፈጻጸም ምዘና የሁለት ጊዜ አማካኝ ነጥብ 60% እና ከዚያ በላይ የስራ አፈጻጸም ደረጃ ያገኘ መሆን አለበት፣
2.1.10. ለሁለተኛ እና ለሶስተኛ ዲግሪ የትምህርት ዕድል ለመወዳደር ለወንድ 50 ለሴት 52 መብለጥ የለበትም።
2.1.11. የትምህርት ደረጃቸው ከመጀመሪያ ዲግሪ በታች ያሉ ሠራተኞች በጽ/ቤቱ የበላይ ሃላፊ በልዩ ሁኔታ ሲፈቀድ ብቻ እንዲማሩ ይደረጋል።
2.1.12. ለአጫጭር ጊዜ ስልጠናዎች የሚቀርቡ ዕጩዎች እድሜ እድሉን በሰጡ ወገኖች መስፈርት መሰረት ሊፈፀም ይችላል።
2.2. ልዩ ትኩረት የሚሹ ዕጩዎች አመራረጥ፣

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 7


2.2.1. ተመሳሳይ ፆታ ያላቸው ዕጩ ተወዳዳሪዎች እኩል ነጥብ ካገኙ በአገልግሎት ቅድሚያ ያለው ዕድሉን እንዲያገኝ ይደረጋል፣
2.2.2. በማወዳደሪያ መስፈርቱ ተወዳድረው እኩል ወይም እስከ ሶስት በመቶ የሚደርስ ተቀራራቢ ውጤት ላመጡ አካል ጉዳተኛ፣ ሴቶችና
በመ/ቤቱ ውስጥ በአንጻራዊነት አነስተኛ የብሄር ተዋፅኦ ላላቸው ብሄር ብሄረሰቦች ቅድሚያ ይሰጣል፣
2.2.3. በውድድሩ አንድ ሴትና አንድ ወንድ እኩል ነጥብ ካገኙ ለሴቷ ተወዳዳሪ ቅድሚያ ይሰጣል፣

2.3. የምርጫ ማወዳደሪያ መስፈርቶችና የነጥብ አሰጣጥ


በመመሪያው የተጠቀሱት ቅድመ ሁኔታዎች እንደተጠበቁ ሆነው ለትምህርትና ስልጠናው የሚመዘገቡ እጩዎች የሚመረጡባቸው መስፈርቶች፣
ተ.ቁ የመስፈርቱ አይነት በመቶኛ
1. ለውጤት ተኮር የስራ አፈጻጸም የተሰጠ ነጥብ፣ 70%
2. ለትምህርት አማካይ ውጤት የተሰጠ አጠቃላይ ነጥብ፣ 10%
3. ለስራ ልምድ የተሰጠ አጠቃላይ ነጥብ፣ 10%
4. ለማህደር ጥራት የተሰጠ አጠቃላይ ነጥብ፣ 10%
ጠቅላላ ድምር 100%

የስራ አፈጻጸም ምዘና ውጤት በተቋሙ በሚመለከተው የስራ ሂደት መሪ ተሰጥቶ በበላይ ሃላፊ /በተወካዩ የተረጋገጠ መሆን ይኖርበታል፣
ለማወዳደር እንዲያመች ከ 100% የተገኘውን የቅርብ ጊዜ ሁለት የውጤት ተኮር የስራ አፈጻጸም ውጤታቸው ወደ 70% በማስላት ይቀየራል።
በተለያዩ ምክንያቶች የስራ አፈጻጸም በተከታታይ ያልተሞላ ከሆነ በ 2 ተከታታይ የስራ አፈጻጸም ውጤት ማወዳደር ይቻላል። ይህም ካልተሟላ
እና በቂ ምክንያት ያለው ከሆነ በአንድ ጊዜ የስራ አፈጻጸም መወዳደር ይቻላል፣
ቀጥታ አግባብነት ያለው የትምህርት ደረጃ 10%፣በተዘዋዋሪ ግኑኙነት ያለው የትምህርት ደረጃ 5% እና ግኑኙነት የሌለው የትምህርት ደረጃ 2.5%
የሚሰጥ ይሆናል።

2.3.1. ለስራ ልምድ የተሰጠ አጠቃላይ ነጥብ፣

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 8


ከማወዳደሪያ መስፈርቶች መካከል ሰራተኛው ያለው የአገልግሎት ዘመን ያስገኘው የስራ ልምድ አንዱ ነው። ሰራተኛው በስራ ዘመኑ በተለያየ የስራ
መደብ ላይ በቀጥታ፣ በተዘዋዋሪ እና አግባብ በሌለው በመስራት ያበረከተው አስተዋጽኦ 10% ተሰጥቶታል። ከ 15 ዓመት በላይ የስራ ልምድ
ተጨማሪ ነጥብ አያስገኝም።
ሀ) ለረዥም ጊዜ ትምህርትና ስልጠና በአገልግሎት ብዛት የተሰጠ ነጥብ

አገልግሎት በአመት የሚያስገኘው ውጤት


ቀጥታ አግባብነት ያለው ተዘዋዋሪ አግባብ ያለው አግባብ የሌለው 25%
100% 50%
2 1.3 0.65 0.3
3 2 1 0.5
4 2.67 1.3 0.65
5 3.3 1.65 0.8
6 4 2 1
7 4.67 2.3 1.15
8 5.3 2.65 1.3
9 6 3 1.5
10 6.67 3.3 1.65
11 7.3 3.65 1.8
12 8 4 2
13 8.67 4.3 2.15
14 9.3 4.65 2.3
15 እና ከ 15 ዓመት በላይ 10 5 2.5

ለ) የመካከለኛ ጊዜ ትምህርትና ስልጠና/አገልግሎት ብዛት የተሰጠ ነጥብ


አገልግሎት በአመት የሚያስገኘው ውጤት
6 ወር 0.33
1 ዓመት 0.67
2 ዓመት 1.33
3 ዓመት 2
4 ዓመት 2.67
5 ዓመት 3.33
6 ዓመት 4
7 ዓመት 4.67
8 ዓመት 5.33
9 ዓመት 6
የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 9
10 ዓመት 6.67
11 ዓመት 7.33
12 ዓመት 8
13 ዓመት 8.67
14 ዓመት 9.33
15 እና ከ 15 ዓመት በላይ 10

2.3.2. የትምህርት አማካይ ውጤት አመዳደብ


ለአማካይ ውጤት የሚሰጠው ውጤት ነጥብ 10% ሲሆን ነጥብ አሰጣጡም የሚከተለው ነው፦
አማካይ ውጤት የሚሰጥ ነጥብ
ተ.ቁ
1 2.00-2.39 ወይም 50-59% 5
2 2.40-2.79 ወይም 60-69% 6
3 2.80-3.19 ወይም 70-79% 7
4 3.30-3.59 ወይም 80-89% 8.25
5 3.60-3.99 ወይም 90-99% 9
6 4.00 ወይም 100%
10

2.3.3. የማህደር ጥራት

የማህደር ጥራት አንዱ የማወዳደሪያ መስፈርት ሲሆን ውድድር ከመደረጉ ቀደም ብሎ ቀላል የዲሲፕሊን ቅጣት እስከ 2 አመት፣ ከባድ የዲሲፕሊን
ቅጣት እስከ 5 አመት በሪከርድነት በሰራተኛው ማህደር ውስጥ የሚያዝ በመሆኑ የሥነ-ምግባር ችግሮች ያሉበትን ሰራተኛ ተጠቃሚ የመሆን መብት
ከቅጣት ዘመኑ በፊት እንዳይጠቀምበት ለማድረግ የማህደር ጥራት ያላቸውን ሰራተኞች ለማበረታታት ለማህደር ጥራት የሚሰጠው አጠቃላይ ነጥብም
10% ሆኖ ዝርዝር የነጥብ አሰጣጡም እንደሚከተለው ይሆናል።
ተ.ቁ የማህደር ጥራት የሚቀነስ ነጥብ የሚሰጥ ነጥብ
1 አንድ ወር ደመወዝና በላይ ቅጣት 4 6
2 የሁለት ጊዜ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ 3 7
3 የመጀመሪያ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ 2 8

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 10


4 የቃል ማስጠንቀቂያ በጽሁፍ የተረጋገጠ 1 9
5 ምንም የቅጣት ሪከርድ የሌለበት 0 10

ክፍል ሦስት
3. በአገር ውስጥና በውጭ አገር ሥልጠና/ትምህርት ስለሚከፈል ደመወዝ እና ድጋፍ፦

ሀ) ሠራተኛው የተላከበትን ወይም ሠራተኛው እንዲሰለጥን ከተላከበት ደረጃ በላይ ለመቀጠል የሚያስችል ዕድል ቢያገኝ በቅድሚያ የጽ/ቤቱን ኃላፊ
ስምምነት እስካላገኘ ድረስ ያገኘውን ዕድል መቀጠል አይችልም። ሆኖም ሠልጣኙ ለስልጠና የተላከበትን የሙያ መስክ ያለጽ/ቤቱ ፍቃድ ቢለውጥ
ወይም ያልተፈቀደለትን የትምህርት ደረጃ ቢማር፤

1. ለስልጠናው ጊዜ የደመወዝ ክፍያ አይከፈለውም።


2. ጽ/ቤቱ በሥልጠናው ምክንያት ያወጣውን ወጪ ሰልጣኙ ለመ/ቤቱ ይመልሳል፣

ለ) በውጭ ሃገር ስልጠና እንዲከታተል የተመረጠ ሠራተኛ ለጤና ምርመራ፣ ለክትባት፣ ለኮቴ፣ ለፓስፖርት፣ ለቢዛና ለመሳሰሉት የሚያስፈልገው ወጪ
በጽ/ቤቱ የሚሸፈን ይሆናል።

ሐ) ትምህርት ወይም ስልጠና በመከታተል ላይ የሚገኝ ሠራተኛ በስራ ላይ ሊያገኝ ይችል የነበረውን ለተመሳሳይ የስራ መደብ ባልደረቦቹ የተሰጠ
ጥቅም በመመሪያ የተከለከለ እስካልሆነ ድረሰ በውጭ አገር ትምህርት ወይም ሥልጠና በመከታተል ላይ በመሆኑ ምክንያት የሚሰጠው ጥቅም
አይነፈግም። ሆኖም በስራ ፀባይ ምክንያት ለስራ ማከናወኛ ተብሎ ይከፈል የነበረው የትራንስፖርት የኃላፊነትና ሌሎች አበሎች አይሰጡም።

መ). በውጭ ሃገር ነፃ የትምህርት ዕድል አግኝተው ለሚሄዱ የጽ/ቤቱ ሠራተኞች ለትምህርት ላይ ለሚቆዩበት ሙሉ ጊዜ ግመሽ ደመወዝ
ይከፈላቸዋል።

3.1. ለሀገር ውስጥ የትምህርት ዕድል የሚደረግ ድጋፍ


3.1.1. ሠራተኛው በአገር ውስጥ የትምህርት ተቋማት በመደበኛነት እንዲማር መ/ቤቱ ከፈቀደ ሙሉ ደመወዝ ይከፈለዋል። ይሁንና በሠራተኛው
ምክንያት በሆነ በማንኛውም ጥፋት የትምህርት ወይም የስልጠናው ጊዜ ቢራዘም ለተራዘመው ጊዜ ጽ/ቤቱ ክፍያ አይፈፅምም።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 11


3.1.2. በጽ/ቤቱ ፍቃድ እንዲማር የተደረገ ሠራተኛ የመመረቂያ ጹሁፍ በሚያዘጋጅበት ወቅት ለጽሑፉ ማጠናከሪያ የሚሆን የገንዘብ ድጋፍ
ማኔጅመንቱ በሚወስነው መሰረት ክፍያ ይደረግለታል። ሁኖም ጥናቱ ሲያጠናቅቅ የጸደቀውን የመመረቂያ ጽሑፍ ለጽ/ቤቱ ስልጠና ክፍል
ማቅረብ አለበት።
3.2. የትምህርት ሥልጠና ጊዜ የማራዘም ጥያቄ
የተሰጠውን የትምህርት ዕድል በተወሰነው የጊዜ ገደብ በበቂ ምክንያት ማጠናቀቅ ካልቻለና ልዩ ሁኔታዎች ማለትም ሕመም፣ የቤተሰብ ችግር፣
በትምህርት መውደቅ ወይም መዘገየትና ሌሎች አሳማኝ ምክንያቶች ካጋጠሙ የሚከተሉት መረጃዎች ከተሟላ የትምህርት ጊዜ የማስረዘም ጥያቄ
ሊያቀርብ ይችላል።

ለዚህም የማራዘም ጥያቄው ተቀባይነት የሚኖረው፤


፩) ከተማሪው አማካሪ ጥያቄ ሲቀርብ፣
፪) ከትምህርት ተቋሙ የድጋፍ ማስረጃ ሲያቀርብ፣

፫) ሥልጠናውን ለማራዘም የሚያስችል ሌላ ተጨማሪ ማስረጃ ሲቀርብ፣

ጉዳዩ የሚመለከተው የቀረበለትን የማራዘም ጥያቄ በስልጠና ኮሚቴው ማስረጃዎች እንዲታዩ እና ኮሚቴው የደረሰበትን የውሳኔ ሃሳብ በበላይ ኃላፊ
ተቀባይነት ሲያገኝ ሊፈቀድ ይችላል፣

3.3. የሰልጣኞች ግዴታ


መንግስት በአገር አቀፍ ደረጃ የሚያወጠው የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ እንደተጠበቀ ሁኖ ለስልጠናው የተመረጡ ሠራተኞች የሚከተሉትን ግዴታዎች
እንዲያሟሉ ይጠበቅባቸዋል።
3.3.1. ሠልጣኙ የሰጠነበትን የሙያ መስክ አጠናቆ ሲመለስ ጽ/ቤቱ በሚመድበው የስራ ቦታ የመስራት፣
3.3.2. በውጭ ሃገር እና በሃገር ውስጥ ለትምህርትና ለስልጠና የተመረጡ ሠራተኞች ስልጠናውንና ትምህርቱን ለመከታተል የወሰደበትን ጊዜ እጥፍ
ማገልገልና መ/ቤቱ በሚያዘጋጀው ውል መፈፀም ይኖርባቸዋል፣
3.3.3. በማታው ክፍለ ጊዜ ጽ/ቤቱ እየከፈለላቸው በመማር ለሚያጠናቅቁ ሠራተኞች በትምህርት ቆይታቸው የነበረውን ጊዜ ያህል ጽ/ቤቱን
እንዲያገለግሉ ይደረጋል፣

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 12


3.3.4. ለሥልጠና የሚሄዱ ሠራተኞች ስልጠና ከመሄዳቸው በፊት ለትምህርትና ለስልጠና ከሚወጣው ወጪ ጋር የሚመጣጠን የነጠላና የአንድነት
ዋስ በመጥራት የውል ግዴታ መፈረም ይኖርባቸዋል፣
3.3.5. በአንድ የትምህርት ወይም ስልጠና መስክ ዕድል ከተሰጣቸው በኋላ ወደ ሌላ የትምህርት ወይም ሥልጠና መስክ በራሰቸው ፈቃድ ብቻ
መቀየር አይችሉም፣
3.3.6. የረጅም ጊዜ የአገር ውስጥ ወይም የውጭ አገር ት/ትና ስልጠና ተጠቃሚዎች ትምህርታቸውን ወይም ስልጠናቸውን በፈፀሙ ከአንድ ወር ባልበለጠ ጊዜ
ውስጥ ለአቅም ግንባታ ጄኔራል ዳይሬክቶሬት እና ለሰው ሃብት ሪከርድና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ሪፖርት ማድረግ አለባቸው።
3.3.7. የአገር ውስጥ ሰልጣኞች ከትምህርት ተቋሙ የሚያቀርቡበት የትምህርት የጊዜ ሠሌዳ መሰረት ት/ት ከሚሰጥባቸው ጊዚያት ውጭ ባሉት ሰዓትና ዕረፍት
ምክንያት ትምህርት በማይኖርበት ጊዜ በመደበኛ ስራቸው ላይ በመገኘት አገልግሎት የመስጠት ግዴታ አለባቸው፣
3.3.8. በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር ለትምህርትና ስልጠና የተመረጠ ሠራተኛ ለትምህርትና ስልጠና ከሜሄዱ በፊት ፎርማሊቲዎችን ማለትም ክሊራንስ፣
የውል ግዴታና የደመወዝ ውል ማሟላት አለበት፣
3.3.9. ሠራተኛው ስልጠናውን ጨርሶ ሲመለስ የማገልገል ግዴታውን የማይወጣ ከሆነ ለስልጠናው የወጣበትን ማንኛውም ወጪና የተከፈለውን ደመወዝ ህጋዊ
ወለድ 9% ጨምሮ ይከፍላል።
3.3.10. ሠራተኛው የማገልገል ጌዴታውን ሙሉ ለሙሉ ሳያጠናቅቅ ቢለቅ ለስልጠና ወይም ለትምህርት የወጣለትን ማንኛውም ወጪና የተከፈለውን ደመወዝ
ለማገልገል ግዴታ ለገባባቸው ወራት ተከፍሎ ለቀረው ጊዜ የሚጠበቅበትን ገንዘብ ህጋዊ 9% ወለዱን ጨምሮ የመክፈል ግዴታ አለበት፣
3.4. የጽ/ቤቱ ግዴታዎች
3.4.1. በአገር ውስጥ ወይም በውጭ አገር የአጭር፣ የመካከለኛ እና የረጅም ጊዜ ስልጠና የሚከታተሉ ሠራተኞች የውል ግዴታና የደመወዝ ውክልና
ፎርማሊቲዎች ማረጋገጥ፣
3.4.2. በትምህርትና ስልጠና ላይ ለሚገኙ ሠራተኛ ደመወዝ የመክፈልና መመሪያው በሚፈቅደው መሰረት ልዩ ልዩ ወጪዎችን መሸፈን፣
3.4.3. በአገር ውስጥ ወይም በውጭ አገር ለትምህርትና ስልጠና የተላከ ሠራተኛ በተላከበት ሙያ እና ቦታ በየጊዜው መከታተልና በጊዜ ገደቡ መመለሱን
የማረጋገጥ፣
3.4.4. ሰራተኛው የገባውን የውል ግዴታ በማንኛውም መልኩ ካላከበረ በየደረጃው አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ማድረግ፣
3.4.5. በመንግስት ውሳኔ በዝውውር ወይም በሹመት ወደ ሌላ መ/ቤት ቀድሞ የገበውን የውል ግዴታ ያላጠናቀቀ ከሆነ የቀረበትን የቆይታ ግዴታ የሚያመለክት መረጃ ለሄደበት
መ/ቤት ያሳውቃል፣

ክፍል አራት
4. የትምህርትና ስልጠና ኮሚቴ ስለመቋቋም

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 13


1. ጽ/ቤቱ ለተቋሙ ከተለያዩ አገራትና ትምህርት ተቋማት የሚገኙትን የትምህርትና ስልጠና እድሎች በግልጽነት፣ በፍትሃዊነትና በተጠያቂነት
አግባብ ለመጠቀም ዕጩ ሰልጣኞችን የሚመርጥ ኮሚቴ ያቋቁማል።
2. የትምህርትና ስልጠና መራጭ ኮሚቴ አምስት/5/ አባላት የሚኖሩት ሲሆን ስብጥሩም በሚከተለው አይነት ይሆናል።
ሀ) በጥናት፣ ምርምርና አቅም ግንባታ ጄ/ዳይሬክቶሬት የስልጠና አሰራር ስርዓት ቡድን መሪ
------------------------------------------------------------------ሰብሳቢ
ለ) የሰው ሀብትና ሪከርድ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር---------አባል
ሐ) የሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር----------------አባል
መ) በሰራተኞች የሚመረጡ ሁለት የሰራተኞች ተወካዮች (አንድ ወንድና አንድ ሴት) አባል
ሠ) ከሰው ሀብትና ሪከርድ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የሚወከል አንድ ከፍተኛ ባለሙያ--ፀሃፊ ይኖሩታል።
4.1. የመራጭ ኮሚቴው ተግባራትና ሃላፊነቶች
1. የትምህርትና ስልጠና እድሉን የሰጠው አካልና ጽ/ቤቱ ያስቀመጣቸውን መመዘኛዎች መሰረት በማድረግ ዕጩዎች በውድድሩ እንዲሳተፉ
መጋበዛቸውን ያረጋግጣል፣
2. በሰው ሀብትና ሪከርድ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በኩል የዕጩዎች ምዝገባ በመመሪያው መሰረት መከናወኑን ያረጋግጣል፣
3. ለትምህርትና ስልጠና እድሉ የተመዘገቡ ዕጩዎችን የግል ማህደርና ሌሎች ከሰው ሀብትና ሪከርድ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የሚቀርቡትን
በመቀበልና በመመርመር የቀረቡትን ዕጩ ተወዳዳሪዎች የግል ዝርዝር መረጃዎች ትክክለኛነት በማረጋገጥ ያወዳድራል፣
4. በውድድሩ አሸናፊ የሆኑትን በመለየት በዚህ መመሪያ ላይ የዕጩዎች ማወዳደሪያና የሰልጣኞች መራጭ ኮሚቴ የውሳኔ አስተያየት ማቅረቢያ ቅጽ
ላይ 1 ላይ በመሙላትና በመፈረም ውጤቱን ከተወዳዳሪዎቹ ጋር ለመ/ቤቱ የበላይ አመራር አቅርቦ ያፀድቃል፣
5. ስለ አጠቃላይ የትምህርትና ስልጠና የስራ አፈጻጸም በየስድስት ወሩ ሪፖርት በማዘጋጀት ለበላይ አመራር ያቀርባል።
4.2. በመራጭ ኮሚቴ አባልነት የሚመደቡና የሚመረጡ
4.2.1. በሥነ-ምግባራቸውና በስራ አፈጻጸማቸው የተመሰገኑ፣
4.2.2. በሥነ-ስርዓት አክባሪነታቸው፣ በታማኝነታቸው የታወቁና ሁሉንም በእኩልነት ሊመለከቱ ይችላሉ ተብለው የሚገመቱ፣
4.2.3. ባለፉት ሁለት አመታት ውስጥ በከባድ የዲሲፕሊን ግድፈት ያልተቀጡ፣
4.2.4. በጽ/ቤቱ ውስጥ ከሶስት አመት ያላነሰ አገልገሎት ያላቸው እና
4.2.5. ቢቻል በጽ/ቤቱ ውስጥ በልዩ ልዩ የስራ ክፍሎች ተዘዋውረው የሰሩ መሆን አለባቸው።
4.3. የኮሚቴው የአገልግሎት ዘመን
ሀ) የኮሚቴው አባላት የሚያገለግሉት ለሁለት አመት ይሆናል።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 14
ለ) የኮሚቴው አባላት የአገልግሎት ዘመናቸውን ከጨረሱ በኋላ በስራ አፈጻጸማቸው ሲታመንባቸውና እንዲቀጥሉ ከተፈለገ በድጋሚ ለሁለት አመት ሊመረጡ
ይችላሉ።
4.4. ከሰብሳቢነት ወይም ከአባልነት ስለመነሳት
1. የኮሚቴው ሰብሳቢ ወይም ማንኛውም አባል ፀሃፊውን ጨምሮ ለትምህርት/ስልጠና እድል ተወዳዳሪ ሆኖ በዕጩነት በቀረበ ጊዜ፣
2. ለስልጠናው በዕጩነት ከቀረበ ሰራተኛ ጋር ፀብ ወይም የስጋ፣ የጋብቻ ዝምድና ያለው መሆኑ በማስረጃ ሲረጋገጥ ለዚያ ጉዳይ ብቻ ከአባልነቱ ሊነሳ ይችላል፣
3. የኮሚቴውን ተግባርና ሃላፊነት የሚጎዳ በስራው ጥንቃቄ እና ትጋት የጎደለው ተግባር ወይም አድሏዊነት ያለው ተግባር መፈጸሙ ሲረጋገጥ፣
4. የተጣለበትን ተግባርና ሃላፊነት በመዘንጋት ምስጢር ሲያወጣ እንዲሁም የሥነ-ምግባር ጉድለት ሲፈጽም የተገኘ ከኮሚቴው ወይም ከአባልነት ያለተጨማሪ
ሥነ-ስርዓት በጽ/ቤቱ የበላይ ሃላፊ ከአባልነት ይሰረዛል። በተጨማሪም ቢዲሲፕሊን አፈጻጸም መመሪያ መሰረት የሥነ-ስርዓት እርምጃ ሊወሰድበት ይችላል።
4.5. የኮሚቴው አሰራር
1. የትምህርትና ሥልጠና ኮሚቴ አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ ይሰበሰባል።
2. በኮሚቴው ስብሰባ ላይ ከአባላቱ ግማሽ ከተገኙ ምልዓተ-ጉባኤ ይሆናል። ሆኖም ከተገኙት አባላት አንዱ የሰራተኛ ተወካይ መሆን አለበት።
3. የኮሚቴው ሰብሳቢ በማይኖርበት ጊዜ እንደሁኔታው ከአባላቱ መካከል ጊዜያዊ ሰብሳቢ ይመረጣል።
4. አከራካሪ ሁኔታ ሲያጋጥም በድምጽ ብልጫ ይወሰናል። አባላቱ በሀሳብ እኩል የተከፈሉ እንደሆነ ሰብሳቢው ያለበት ወገን ያቀረበው ሀሳብ ያልፋል።
5. ማንኛውም አባል አስቀድሞ ከሰብሳቢው ሳያስፈቅድ ከስብሰባው ቢዘገይ ወይም ቢቀር ሰብሳቢው በሚያቀርበው ማሰረጃ መሰረት ተገቢው የዲሲፕሊን
እርምጃ እንዲወሰድበት ይደረጋል።
ክፍል አምስት
5. የትምህርትና ስልጠና እድሎችን በበላይ አመራር ስለማስወሰን፣ማሰታወቂያ አወጣጥ፣ እና የእጩዎች አመዘጋገብ
5.1. የትምህርትና ስልጠና እድሎችን በበላይ አመራር ስለማስወሰን
5.1.1. በጽ/ቤቱ እቅድ የተያዙትም ሆነ ከእቅዱ ውጭ ከአገር ውስጥ እና በውጭ አገር መንግስታት የትምህርት ተቋማት የሚሰጡ እድሎች
በቅድሚያ ለመ/ቤቱ የበላይ አመራር ቀርበው እንዲታዩና እንዲፈቀዱ መደረግ ይኖርባቸዋል።
5.1.2. በቀጥታ ለተቋሙ ከተሰጡት ተልዕኮዎችና ተግባራት ጋር ተያይዞ ስልጠናው ለሚመለከታቸው ዳይሬክቶሬቶች የሚመጡ የአገር ውስጥም
ሆነ የውጭ አገር የትምህርትና ስልጠና እድሎች በበላይ አመራሩ የሚመለከተው ሰልጣኝ በቀጥታ እንዲመረጥ ወይም እንዲሳተፍ ይደረጋል።
5.2. የትምህርትና ሥልጠና እድሎች ማስታወቂያ አወጣጥ፣
5.2.1. የማስታወቂያ አስፈላጊነት

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 15


ሀ) የሥልጠና ማስታወቂያው እንዲወጣ የሚደረገው ተፈላጊውን የመመዘኛ መስፈርት የሚያሟሉ የጽ/ቤቱ ሰራተኞች እድሉን እንዲጠቀሙ
ለማሳወቅ፣

ለ) ለትምህርትና ሥልጠና እድሉ ተገቢው እና ብቁ የሆኑ ሰራተኞች እንዳይዘነጉ ለማድረግ፣

ሐ) ተወዳዳሪዎች የትምህርትና ስልጠና እድሉን አስመልክተው እንዲያውቁና ያላቀረቧቸውን ማስረጃዎች በወቅቱ ለማቅረብ እንዲችሉ ለማድረግ፣

መ) የግልጽነትና የፍትሃዊነት እንዲሁም የተጠያቂነት አሰራር እንዲኖር ለማድረግ ነው።

5.2.2. ማስታወቂያው ይዘት


ለትምህርትና ስልጠና እድሎች የሚወጣው ማስታወቂያ በመ/ቤቱ በተለያዩ የስራ ቦታዎች በጽ/ቤቱ የማስታወቂያ ሰሌዳ ሁሉም ሰራተኞች በግልጽ
ሊመለከቱት በሚችሉበት ቦታ የሚለጠፍ ሆኖ የሚወጣው የትምህርትና ስልጠና ማስታወቂያ የሚከተሉትን ማካተት ይኖርበታል።

5.2.2.1. የትምህርቱ /የስልጠናው አይነት የአጭር ፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ መሆኑን፣


5.2.2.2. ትምህርቱ /ስልጠናው የሚሰጥበት ቦታ፣
5.2.2.3. ትምህርቱ /ስልጠናው የሚፈጀው ጊዜ፣
5.2.2.4. የሚፈለጉ የሰልጣኞች ብዛት፣
5.2.2.5. ትምህርቱ /ስልጠናው የሚጀመርበት ጊዜ፣
5.2.2.6. የሚፈለገው የትምህርት ዓይነት፣ ደረጃ፣ ልዩ ሙያ፣ የስራ ልምድ፣ ፆታ፣ እድሜ ወዘተ…፣
5.2.2.7. ትምህርቱን /ስልጠናውን የሚሰጠው አካል የሚጠይቃቸው መስፈርቶች፣
5.2.2.8. የመመዝገቢያ ቀን፣ ሰዓትና የቢሮ ቁጥር ተገልፆ በሰው ሀብትና ሪከርድ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት አማካይነት የሃላፊው ስም፣ የጽ/ቤቱ
ማህተም፣ ማስታወቂያው የወጣበት ቀን፣ ወርና ዓመተ ምህረት የያዘ መሆን ይኖርበታል።
5.2.3. ማስታወቂያውና ምዝገባው የሚቆይበት ጊዜ

1) የጊዜ መጣበብ ከሌለ በስተቀር ማስታወቂያው ለአምስት/5/ ተከታታይ የስራ ቀናት በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ተለጥፎ የሚቆይ ሲሆን በዚሁ ጊዜ
ውስጥ የተወዳዳሪዎች ምዝገባ ጎን ለጎን በሰው ሃብትና ሪከርድ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት አማካኝነት ይካሄዳል። ሆኖም የስልጠናው እድል ውድድር በጣም
አስቸኳይና የተጣበበ ጊዜ ያለው ከሆነ የተገኘው እድል እንዳይመክን ማስታወቂያው አምስት የስራ ቀናትን ላይጠብቅ ይችላል።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 16


2) ተወዳዳሪዎች ለምዝገባ በሚቀርቡበት ጊዜ በማስታወቂያው የተገለጹትን ለመመዝገብ የሚያበቁ መስፈርቶችንና ማስረጃዎችን አሟልተው መቅረብ
አለባቸው። ሆኖም በስራ ምክንያት እና በአመት እረፍት ፈቃድ በቦታው ባለመኖራቸው በሰው ሃብትና ሪከርድ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት፣ በስራ ባልደረባ
ወይም በቅርብ ሃላፊ የሚመዘገቡ ሰራተኞች ቢኖሩ የተጠየቀውን መረጃ አሟልተው የማቅረብ ግዴታ አለባቸው። ማስታወቂያው በወጣበት ወቅት በስራ
ምክንያት በአካል ተገኝተው መመዝገብ ያልቻሉ ሰራተኞች ያላቸውን ማስረጃ አሟልተው ማቅረብ እንዲችሉ በአማራጭነት የኤሌክትሮኒክ
ሚዲያዎችን መጠቀም ይችላሉ።

5.2.4. ማስታወቂያ ማውጣት የማያስፈልጋቸው ትምህርትና ስልጠናዎች፦


ሀ) ከአንድ ወር (30 ቀናት) በታች በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር ለሚሰጡ አውደ ጥናቶች፣ ሴሚናሮች፣ ስብሰባዎች፣ ወርክሾፖች፣ የልምድ
ልውውጦችና እርስ በርስ የመማማሪያ መድረኮች ማስታወቂያ ማውጣት ሳያስፈልግ ሰራተኞችን የመመልመል ሃላፊነት በጥናት፣ ምርምርና አቅም
ግንባታ ጄ/ዳይሬክቶሬት አማካኝነት ሆኖ በበላይ ኃላፊዎች የሚወሰን ይሆናል።

ለ) ለአጭርም ሆነ ለረዥም ጊዜ ከውጭ አገር የተገኘ ስኮላርሺፕ ማስታወቂያውና ምዝገባው የሚቆይበት ጊዜ በሚለው መመሪያ ቁጥር 2.2.3 “1”
መሰረት መፈፀም የማይቻል ከሆነና ቀነ ገደቡ በማጠሩ ምክንያት ማሰታወቂያ አውጥቶ ዕጩዎች ተመዝግበው ውድድር ተካሂዶ ዕጩ ለመምረጥ
የማይቻል ሆኖ ሲገኝ በበላይ አካል ውሳኔ የመጣውን መስፈርት አሟልቶ የተገኘ ሰራተኛ በዕድሉ እንዲጠቀም ይደረጋል።

ክፍል ስድስት
6. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
6.1. የቅሬታ አቀራረብና ውሳኔ አሰጣጥ
6.1.1. በዚህ መመሪያ መሰረት በሚከናወን የዕጪዎች ምዝገባ፣ ውድድርና መረጣ እንድሁም በሌሎች አፈጻጸሞች ላይ ቅሬታ ያላቸው ሠራተኞች
ለበላይ ኃላፊው አቤቱታቸውን ማቅረብ ይችላሉ፣
6.1.2. የመ/ቤቱ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ቅሬታው በደረሰው ከ 5(በአምስት) ቀናት ባልበለጠ ጊዜ ምላሽ መስጠት አለበት፣
6.1.3. ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴው የደረሰበትን የውሳኔ ሃሳብ/አስተያየት ወዲያውኑ ለበላይ ሃላፊው ያቀርባል፣
6.1.4. የጽ/ቤቱ የበላይ ሃላፊ ቅሬታው በቀረበ በሦስት ቀን ጊዜ ውስጥ ተገቢውን ውሳኔ ለአቤቱታ አቅራቢው ያሳውቃል፣
6.1.5. የበላይ ሃላፊው ውሳኔ የመጨረሻ ይሆናል፣
6.2. በመመሪያው ያልተሸፈኑ ጉዳዮች

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 17


በዘህ መመሪያ ውስጥ ያልተሸፈኑ ጉዳዮች ቢያጋጥሙ በጥናት፣ ምርምርና አቅም ግንባታ ጄኔራል ዳይሬክቶሬት በኩል ለጽ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ እየቀረቡ
ውሳኔ የሚያገኙ ይሆናል።
6.3. ተጠያቂነት
ማንኛውም የትምህርትና ስልጠና ኮሚቴ አባል፣ የስራ ሂደት መሪ ወይም ሠራተኛ ባለው ስልጣን ወይም የስራ ድርሻ በመጠቀም ከዚህ መመሪያ ውጭ
ለሚፈፅማቸው ተገቢ ያልሆነ የምርጫ አፈጻጸም ተግባራት በዲስፒሊን ተጠያቂ ይሆናል፣ መመሪያውን ስለማሻሻል ጽ/ቤቱ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው
ይህን መመሪያ ሊያሻሽለው ወይም ሊለውጠው ይችላል፣ መመሪያው የሚፀናበት ጊዜ ይህ መመሪያ ከ…2008 ዓ.ም.ጀምሮ የፀና ይሆናል፣
የትምህርትና የስልጠና ዕድል አጠቃቀም ስምምነት ውል

ይህ የስምምነት ውል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት (ከዚህ በኋላ ውል ሰጪ እየተባለ በሚጠራው) አድራሻ፦ አዲስ አበባ ቂርቆስ ክ/ከተማ
ወረዳ፦….የቤት ቁጥር፦..……..ስልክ ቁጥር፦……….የፖስታ ሳጥን ቀጥር፦ …………..ፖስታ ሣጥን እና

በ……………(ከዚህ በኋላ ውል ተቀባይ እየተባለ በሚጠራው)

አድራሻ፦አዲስ አበባ፦……………...ክ/ከተማ ወረዳ፦……….የቤት ቁጥር፦..……..ስልክ ቁጥር፦……….የፖስታ ሳጥን ቁጥር፦……………መካከል


ከዚህ ቀጥሎ በዝርዝር በተመለከተው ሁኔታ ዛሬ ………………..ቀን 200…..ዓ.ም. በውል ሰጪ መ/ቤት ተፈፅሟል።

አንቀፅ 1

የውሉ አላማ

የዚህ ውል ዓላማ የመ/ቤቱን ቋሚ ሠራተኞች የትምህርት ወይም የስልጠና ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል መብትና ግዴታን በውል ሰጪ እና
በውል ተቀባይ መካከል ለመፈፀም ነው።

አንቀፅ 2

የውል ተቀባይ ሁኔታ

የትምህርት ወይም ስልጠና ዕድሉ በተሰጠበት ወቅት ውል ተቀባይ በ………ዳይሬክቶሬት ተመድቦ ይሰራ የነበረ ሲሆን፦

 የስራ መደቡ መጠሪያ፦………………………………….


 የስራ መደቡ ደረጃ፦………………………………………..

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 18


 የመደብ መታወቂያ ቁጥሩ፦……………………………….
 የደመወዝ መጠን/በግሮስ/፦………………………………..
 የቤተሰብ ሁኔታ ያገባ…….. ያላገባ ……………………

ሰልጣኙ/ኟ ያገባ/ች ከሆነ/ች

አድራሻ፦አዲስ አበባ፦……………...ክ/ከተማ ወረዳ፦……….የቤት ቁጥር፦..……..ስልክ ቁጥር፦……….የፖስታ ሳጥን ቀጥር፦………የሆነ


ባለቤቴ………………..ከውል ሰጪ ጋር ያደረጉትን ይህን ውል የማወቅና የተስማማሁበትም መሆኑን በፊርማዬ አረጋግጣለሁ።

አንቀጽ 3

ስለትምህርቱ/ ሥልጠናው

የትምህርቱ/የስልጠናው ዕድል የተገኘው በውል ሰጪ ሲሆን፣

ወጪውን የሚሸፍነው ኣካል፦…………………………..

የቆይታው ጊዜ፦………………………………………..

የስልጠናው ዘርፍ፦……………………………………

ውል ሰጪ የሚሸፍነው የገቢ ዓይነት፦…………………..

የፈቀደው ኋላፊ፦………………………………………..

አንቀፅ 4
የውል ተቀ ባይ ግዴታ
ውል ተቀባይ
በገባው ግዴታ መሠረት ሣይፈጽም ቢቀር እሱን ተክቶ ሃላፊነቱን የሚወስድ ዋስ የመጥራት፣
የተላከበትን ትምህርት ወይም ስልጠና በአግባቡ የመከታተልና ውጤት የማስገኘት ፣
በቅድሚያ ለውል ሰጪ አስታውቆ ካልተፈቀደለት በስተቀር የተላከበትን የትምህርት/የስልጠና መስክ ያለመለወጥ፣
ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ካላጋጠመ በስተቀር ትምህርቱን/ስልጠናውን ለማቋረጥ ቢገደድ አመች በሆነ የመገናኛ ዘዴ ተጠቅሞ ለውል ሠጪ
ማሳወቅ፣

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 19


በተለየ ሁኔታ የተፈቀደለት ካልሆነ በስተቀር በትምህርት/በስልጠናው ቆይታ ወቅት አጋዥና አስፈላጊ የሆኑ የትምህርት መሳሪዎችንና
ለትምህርት/ለስልጠና ተቋሙ የሚያስፈልጉ ማናቸውም ወጪዎች ራሱ መሸፈን አለበት፣
የትምህርት/የስልጠና ተቋሙን ደንብና ሥርዓት ማከበርና ይህን ካለመፈፀም የተነሳ የሚያስጠይቅ ድርጊት ፈጽሞ ቢገኝ ሃላፊነቱን የመውሰድ፣
የትምህርት ወይም የስልጠና ቆይታቸውን ጊዜ ከውል ሰጪ ፍቃድ ውጭ እንዲራዘም ያለማድረግ፣
ለአገር ውስጥ ስልጠና የሚገባ ትምህርቱን ወይም ስልጥና ከሚሰጣቸው ጊዚያት ውጪ ባሉት ቀናት በማይኖርበት ጊዜ በመደበኛ ስራ ገበታው
ተገኝቶ አገልግሎት የመስጠት፣
የትምህርት ወይም የስልጠና አጠናቆ ሲመለስ ስለ ትምህርቱ/ሥልጠናው በጽሑፍ ሪፖርት የማቅረብ፣
ከትምህርት ወይም ከስልጠናው በኋላ ቀደም ሲል ይከፈለው የነበረው የስራ መደብ ደረጃና ደመወዝ አገልግሎት የመስጠት፣
የትምህርት ወይም ስልጠናውን የፈጀውን ጊዜ እጥፍ አገልግሎት ለመ/ቤቱ የመስጠት፣
ከውል ሰጪ እውቅና ፍቃድ ውጪ የትምህርት ወይም የስልጠና ቆይታ ጊዜውን ቢያራዝም፣ ውል ሰጪ ለዚሁ ተጨማሪ ጊዜ የከፈላውን ደመወዝ
ሆነ ሌላ ወጪ ካለ ከነህጋዊ ወለዱ የመመለስ፣

ከነዚህም በተጨማሪ

ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ሳያጋጥመው ትምህርቱን/ስልጠና ቢያቋርጥ፣


የትምህርት/የስልጠና ተቋሙን ደንብና ሥርዓት ሳያከብር ቀርቶ ከተቋሙ ቢባረር፣
ከትምህርት ወይም ስልጠናው መጠናቀቅ በኋላ በውል ሰጪ መ/ቤት ለማገልገል ፈቃደኛ ሣይሆን ቀርቶ ስራውን ቢለቅ፣ ውል ሰጪ
በትምህርቱ/በስልጠናው ጊዜ የከፈለውን ደመወዝ እና ሌችም ወጪዎች ካሉ ከህጋዊ ወለዱ የመመለስ ግዴታ አለበት፣
አንቀጽ 5
የውል ሰጪ ግዴታ
ውል ሰጪ
 የትምህርት/ስልጠናው ማስፈፀሚያ ያዋለውን የገንዘብ ወጪ ማስረጃ በአግባቡ መያዝ፣
 የትምህርት/የስልጠና ዕድሉን ለሠጠው ተቋም የውል ተቀባይነት ስም፣ የትምህርት፣ የስራ ልምድና ሌሎች ማስረጃዎችን አሟልቶ
የማስተላለፍ፤
 ውል ተቀባይ በትምህርቱ/ስልጠናው ላይ ለቆዩበት ጊዜ ሕግ በሚፈቅደው መሰረት ደመወዙን የመክፈልና ሌሎች መብቶችንና ጥቅማጥቅሞችን
የመጠበቅ፣

አንቀጽ 6

ውሉ ስለሚቆዩበት ጊዜ

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 20


ይህ ውል ትምህርቱ/ስልጠናው ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ፀንቶ ይቆያል

አንቀፅ 7

ውሉ ስለሚቋረጥበት ሁኔታ

ለትምህርቱ/ለስልጠናው የተመደበው ጊዜ ሲያልቅ/ሲያበቃ፣

እንደውሉ ሲፈፀም፣

በሁለቱ ተዋዋይ ወገኖች ስምምነት፣

ውል ተቀባይ በገባው ግዴታ መሰረት ሳይፈፅም ቢቀር ዉሉ ይቋረጣል፣

አንቀጽ 8

የዋስ ግዴታ

እኔ………………….አድራሻዬ……………..ክ/ከተማ…………………..ቀበሌ……የቤት ቆጥር………….ስ.ቁ……………ፖስታ ሳጥን


ቁጥር…… የሆነ ውል ተቀባይ በዚህ ውል አንቀፅ 4 በገባው ግዴታ መሰረት ሳይፈፀም ቢቀር በስልጠናው ወቅት የተከፈለውን ደመወዝና ሌሎችም
ወጪዎች ካሉ እነዚህንም ጨምሮ ለውል ሰጪ ለመመለስ የነጠላና የአንድነት ዋስ መሆኔን አምኜ በመቀበል ፈርሜአለሁ።
ዋሱ ለገባው የዋስትና ግዴታ የሚያስዘው የንግድ ፈቃድ ወይም የማይቀሳቀስ ንብረት በዘመኑ ግብር የተከፈለበትና የንግድ ድርጅት ወይም የማይቀሳቀስ
ንብረት ከማንኛውም ዕዳ እና እገዳ ነፃ መሆኑን የሚያረጋግጥ፣ የመንግስት ሠራተኛ ከሆነም ከሚሰራበት መ/ቤት የወር ደመወዙን የሚገልጽና ሠራተኛው
በማንኛውም ምክንያት ስራውን ቢለቅ ለውል ሰጪ የሚያስውቅ ለውል ሰጪ የሚያስውቅ መሆኑን የሚገልፅ ደብዳቤ ማቅረብ ግዴታ አለበት።
ዋሱ ባለትዳር ከሆነ/ች
እኔ………………….አድራሻዬ……………..ክ/ከተማ…………………..ቀበሌ……የቤት ቆጥር………….ስ.ቁ……………ፖስታ ሳጥን
ቁጥር…… የሆነ ውል ተቀባይ የሰጡትን ዋስትና አውቄ የተቀበልኩ መሆኔን በፊርማዬ አረጋጣለሁ።

አንቀጽ 9

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 21


ይህ በኢትጵያ ፍትሐቤር ሕግ ቁጥር 1731 መሠረት በሁለት ተዋዋይ ወገኖች መካካል እንደ ሕግ ሆኖ ያገለግላል።

ስለውል ሰጪ ውል ተቀባይ
ስም…………………………… ስም……………………………
ፊርማ………………………… ፊርማ……………………………
ቀን……………………………… ቀን……………………………
የውል ተቀይ ባለቤት
ስም………………………
ፊርማ…………………………
ቀን…………………………
ዋስ የዋስ ባለቤት
ስም……………………… ስም…………………….
ፊርማ……………………… ፊርማ…………………..
ቀን………………………… ቀን…………………………

ምስክሮች
ስም ፊርማ ቀን
1………………………….. ……………….. ………………….
2…………………………… ………………... ………………….
3…………………………… ………………… ………………….
4…………………………… ………………… …………………..
ይህ ስምምነት ………………ቀን…………………ወር……….ዓ.ም. ተፈርሟል።

የሰልጣኞች መራጭ ኮሚቴ የውሳኔ አስተያየት ማቅረቢያ ቅጽ

በኮሚቴው ስብሰባ ላይ የተገኙ አባላት

የአባላት ስም የስራ መደቡ መጠሪያ


…………………ሰብሳቢ …………………
…………………የሰው ሃብት ልማትና ሪከርድ ዳይሬክተር …………………
…………………የሴቶችና ወጣቶች ዳይሬክተር …………………
የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 22
………………….የኮሚቴው ፀሃፊ ………………..
የሰራተኛ ተወካይ
1………………………. አባል ……………..
2………………………….አባል ……………..
የስልጠናው አይነት……………………..

የሚፈጀው ጊዜ …………………………

ትምህርቱ/ስልጠናው የሚሰጥበት ጊዜ………………

ትምህርቱ/ስልጠናው የሚሰጥበት አገር………………

የኮሚቴው የውሳኔ አስተያየት

ከዚህ ጋር ተያይዞ በሚገኘው የእጩዎች ማወዳደሪያ ቅፅ ላይ በስም የተጠቀሱትን ካወዳደረ በኋላ አቶ/ወ/ሮ/ወ/ሪት………………………ን መርጦ
አቅርቧል።

ተመራጩ ብልጫ ያገኘባቸው ዋና ዋና ነጥቦች

………………………………………………………………………………………………………………………………………………
……………………………………………………………………………………………………
በምርጫው ያልተስማማ አባል ቢኖር በሃሳብ የተለየበት ምክንያት…
………………………………………………………………………………………………………………
በምርጫው ያልተስማማው አባል ስም ……………………..ፊርማ……………………………
ኮሚቴው የውሳኔ አስተያየቱን ያቀረበበት ቀን……………ወር……………ዓ.ም…………….
የኮሚቴው ሰብሳቢና የአባላት ስም
ስም ፊርማ
……………………………….. ………………………..
………………………………. ………………………..
……………………………… …………………………
………………………………. ……………………………
የመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ ውሳኔ

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 23


………………………………………………………………………………………………………………………………………………
…………………………………………………………
የበላይ ኃላፊው ኮሚቴ ባቀረበው የውሳኔ አስተያየት የማይስማማ ቢሆን የኮሚቴው አስተያየት ያልተቀበለበት ምክንያት
………………………………………………………………………………………………………………………………………………
…………………………………………………………………………………………………
የበላይ ኃላፊ
ስም ……………………………. ማዕረግ…………………….
ፊርማ………………………….. ቀን……………………..ወር…………….ዓ.ም.
የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

የትምህርትና ስልጠና ማወዳደሪያ ቅፅ

የስልጠናው ርዕስ…………………………የስልጠናው ጊዜ………………የስልጠናው አገር…………...

ተ.ቁ የተወዳዳሪ ስም የትውልድ የት/ት አመካይ የስራ ልምድ 10% ለውጤት ተኮር የማህደር ጥራት 10% ጠቅላላ የነጥብ ደረጃ መግለጫ

ዘመን ውጤት(GPA) 70% ድምር

ቀጥታ ግኑኙነት በተዘዋዋሪ ግኑኙነት የሌለው

ያለው ግኑኙነት ያለው

የስልጠና ኮሚቴ ስምና ፊርማ

1. …………………………………………
2. ………………………………………..
3. …………………………………………
4. ………………………………………..
5. ………………………………………..
6. ……………………………………….

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና የውስጥ መመሪያ Page 24

You might also like