Professional Documents
Culture Documents
ድርጅት
የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ (ረቂቅ)
ማውጫ ገጽ
ክፍል አንድ
1.1 መግቢያ ……………………………………….……………….………
ክፍል አምስት
1.1 መግቢያ
የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በዋናነት የፖስታ መልዕክቶችን በመቀበል፣ በማስተላለፍ እና በማደል እንዲሁም የገንዘብ
ማስተላለፍ ስራ ላይ የተሰማራ ሲሆን ከነዚህ አገልግሎቶች በተጨማሪ የተለያዩ የኮሚሽንና የውክልና ስራዎችን ያከናውናል፡፡ ድርጅቱ
ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ለአገሪቱ ዘላቂ ልማት የላቀ ሚና የሚጫወት መሆን እንዲችል
ደንበኛ ተኮር የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት የአስር ዓመቱን ዕቅድ አቅዶ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡
የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ደግሞ በስትራቴጂ የሚመራ የኮሙኒኬሽን ስርዓት መተግበር ከበላይ አመራሩ የሚጠበቅ ወሳኝ ሚና
ነው፡፡
ተቋሙን የሚመለከቱ መረጃዎችን በወቅቱና ቀጣይነት ባለው መልኩ በአግባቡ ለማሰራጨት አስፈላጊ ከሆኑ የኮሙኒኬሽን የአሰራር
ስርዓቶች መካከል አንዱ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ነው፡፡ በቀላል አገላለጽ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ አንድን ጉዳይ ወይም ሁነት የተመለከቱ
መረጃዎችን ወደተለያዩ ተደራሲያን ለማሰራጨት የሚያገለግል የኮሙኒክሽን ዕቅድ ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ
ከማህበረሰብ፣ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ተደራሲያን ጋር ለመገናኘት የሚያገለግል ንድፍ ነው ማለት ይቻላል፡፡
ኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ፡-
- ባለድርሻዎችን መለየት፣
ከነዚህ ሐሳቦች በመነሳት የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ለምን መረጃ ማሰራጨት እንዳለብን ወይም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ግንኙነት
ማድረግ ያለብን ለምን እንደሆነ ከወዲሁ አውቀን እንድንነሣ ምቹ ሁኔታ ይፈጥርልናል፡፡
ከእነዚህ ሃሳቦች በመነሣት የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ለምን መረጃ ማሰራጨት እንዳለብን ወይም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር
ግንኙነት ማድረግ ያለብን ለምን እንደሆነ ከወዲሁ አውቀን እንድንነሣ ምቹ ሁኔታ ይፈጥርልናል፡፡ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ኮሙኒኬሽን
ለምን? የሚለውን በግልጽ የሚመልስ ከመሆኑ በተጨማሪ ሊሳኩ የሚታሰቡ ዓላማዎችን በግልጽ በማመላከትም ምቹ የኮሙኒኬሽን
ድባብ ይፈጥራል፡፡
የድርጅቱ ዓላማ፣ ርዕይና ተልዕኮ እንዲሁም ዕቅድች በተገቢው መንገድ እንዲተዋወቁና የባለድርሻ
አካላት ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግ፣
የኮሙዩኒኬሽን ስራዎች በተቀናጀ መንገድ የድርጅቱ የስራ ማዕከል እንዲሆን ማድረግ ፤
እንደተቋም ጠንካራና ወጥ የሆነ መልዕክት እንዲተላለፍ ማድረግ ፤
ድርጅቱ የሚያስተላልፋቸው ቁልፍ መልእክቶች ግልጽና ሚዛናዊ በሆነ መንገድ እንዲተላለፍ ማድረግ ፤
የባለድርሻ አካላት አመለካከትና ባህርይ ለመለወጥና ለድርጅቱ ተልዕኮ ስኬት አጋር እንዲሆኑ ድጋፍ
ማድረግ፣
ደረጃውን የጠበቀና የተቀናጀ የኮሙዩኒኬሽንና የህዝብ ግኝኙነት ስራ ማከናወን፣
በኮሙዩኒኬሽን ስራዎች ላይ የምክር ድጋፍ፣ አመራርና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ በመስራት ተቋማዊ
የገጽታ ግንባታ ስራ ማከናወን፣
1.4 የኮሙኒዩኬሽን ስትራቴጂ ጠቀሜታ
የተሳካና የተዋጣለት የስራ አፈፃፀም እንዲኖር ለማስቻልና ሁሉን አሳታፊ የሚያደርግ ስርዓት ለመፍጠር
በድርጅቱ የሚታዩ የመረጃ ክፍተት (information gap) ሊያጠቡ የሚችሉ መንገዶችን ማሰብ የግድ የሚል ነው፡፡
በመሆኑም ሁሉም የድርጅቱ ማህበረሰብ እንደ ባህል ሊከተላቸውና ዕለት ተዕለት የህይወቱ መመሪያ
ሊያደርጋቸው የሚገቡ የኮሙኒኬሽን ባህሎች ሊኖሩት ይገባል፡፡
በዚህም መሰረት የተያዘውን ለውጥ የተሳካ ለማድረግ፣ በአመለካከቱ የተቀየረ እና ለለውጥ ዝግጁ የሆነ የሰው
ሀይል ለመፍጠር፣ በቀላሉ ችግሮችን ለመፈተሽና ለመቅረፍ እንዲሁም መልካም አስተዳደርን ለማስፈን
የሚያስችሉ ከታች የተቀመጡትን የኮሙኒኬሽን ባህልና እምነቶችን ለማዳበርና ለማጎልበት ርብርብ ማድረግ
ይገባል፡፡
ወቅታዊ መረጃዎችን የሚመለከተው ደንበኛ/ሰራተኛ እንዲያውቅ ማድረግ
መረጃን የማካፈል ልምድን ማዳበር፣
የተሟላ፣ ግልፅና ተአማኒነት ያለው የመረጃ ልውውጥ ሳይቆራረጥ በተከታታይ መስጠት፣
በኮሙኒኬሽን ክፍተት ይሁን በሌላ የሚፈጠሩ ያለመጣጣምን በሂሳዊ መንገድ የሚሻሻሉበትን
መንገድ ማመቻቸት፣
የምንሰጣቸው (የምናስተላልፋቸው) መረጃዎች (ውይይቶች) አዎንታዊ ምላሽን የሚቀሰቅሱ
እንዲሆኑ ማድረግ፣
ሁልጊዜ በመልዕክት ላይ መሆን የሚለውን መሰረት ያደረጉ የመረጃ ባህሎችና እምነቶች
ማዳበር፣
ትክክለኛ እና ጥራት ያለው መረጃ ለደንበኛ እና ለሰራተኛ በመስጠት ግንኙነትን ማሻሻል የሚሉ
ናቸው፡፡
2.3 የድርጅቱ ተልዕኮ፣ ርዕይ እና እሴቶች
ተልዕኮ
ጥራቱን በጠበቀ እና ኢኮኖሚያዊ በሆነ የፖስታ አገልግሎት ዜጎች እና ተቋማትን እርስ በእርሳቸውና ከሌላው
ዓለም ጋር ማስተሳሰር
ርዕይ
በ 2022 ዓ.ም በአፍሪካ ተወዳዳሪ የሆነ እና ለሀገራችን ዘላቂ ልማት የላቀ ሚና የሚጫወት የኢትዮጵያ ፖስታ
ተፈጥሮ ማየት
እሴት
ደንበኛ ተኮር አገልግሎት፤
ልናገለግላቸው ይገባል፤
እንሰጣለን፡፡
ታማኝነት፤
ተጠያቂነት፤
ፈጠራን ማበረታታት
የሪፎርም ስራው ለሰራተኛው ተደራሽ የሚሆንበትን መንገድ ማመቻቸት ፡- ድርጅቱ አዲስ የጀመረውን
የሪፎርም ስራ ተከታታይነት ባለው መንገድ ለሰራተኛው እና ለደንበኛው ለማሳወቅ ፍላጎት እና ጥረት
መኖሩ
የፖስታ ክበባት ፡- የፖስታ ክበባትን በመላው ሀገሪቱ ለማጠናከር እና የፊላቴሊ ተግባራት ለተማሪዎች
ለማስተዋወቅ በድርጅቱ ያለው ፍላጎት እየሰፋ መምጣት
የደንበኞች ዳሰሣዊ ጥናት መሰራቱ፡- በመላው ሀገሪቱ ከደንበኞች ጋር በሚኖሩ መድረኮች ተሳታፊ
ለሚሆኑ ደንበኞች መጠይቆችን በመበተን የደንበኞች ዳሰሳዊ ጥናት መሰራቱ እና የደንበኞችን ፍላጎት
በየጊዜው ለማወቅ ጥረት መደረጉ
በውስን የሰው ሀይል ስራዎችን ለመስራት ተነሳሽነት መኖሩ፡- የድርጅቱ አመራሮች ከተገልጋዩ
ህብረተሰብ ፊት ለፊት የሚገናኙበት ሁኔታ መፈጠሩ እና የደንበኞችን ችግሮች ለመፍታት የረጅም እና
የአጭር ጊዜ እቅዶች በማስቀመጥ መፍትሄ ለመፈለግ ጥረት መደረጉ
ከሚዲያዎች ተቀራርቦ ከመስራት አንፃር፡- ሚዲያዎች መረጃ ፈልገው በሚመጡበት ወቅት በፍጥነት
መረጃውን በመስጠት ከሚዲያዎች ጋር ጥሩ ግንኙነት መፍጠር መቻሉ፤ የሚወጡ ዘገባዎች አብዛኛዎቹ
አዎንታዊ እንደሆኑ በሚዲያ ሞኒተሪነግ ማረጋገጥ መቻሉ፡፡ በድርጅቱ የሚዘጋጁ መድረኮችም ለሁሉም
ሚዲያዎች ክፍት በማድረግና በመጋበዝ ተገቢውን የሚዲያ ሽፋን እንዲያገኝ መቻሉ፡፡
የሰራተኞች የስራ ተነሳሽነት መኖር፡- የዲፓርትመንቱ ሰራተኞች ድርጅቱን ወደተሻለ ደረጃ ለመለወጥ
የሚቀርብላቸውን ስራ በተገቢው መንገድ ለመስራት፣ደንበኞችን በተገቢው መንገድ ለማስተናገድ፣
ትእዛዝን ሳይጠብቁ ስራዎችን ለመስራት ተነሳሽነት መኖር እና ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ
ተነሳሽነት መኖር፡፡
2.4.2 ደካማ ጎን
ተልዕኮ ለመወጣት እንዲያስችለው የሪፎርም ስራዎችን ማከናወን ጀምሯል፡፡ በዚህ መሰረት ሰራተኞች
የትምህርት ዝግጅታቸውና የስራ ልምዳቸው ታይቶ የሚመጥኗቸው ቦታዎች እንዲመደቡ መደረግ
ይገባዋል፡፡ ከዚህ አንፃር የኮሙኒኬሽን እና አለም አቀፍ ግንኙነት ዲፓርትመንት ኮሙኒኬሽን እና አለም
አቀፍ ግኝኙነት በሚሉ ሁለት ቡድኖች ተዋቅሯል፡፡ በእነዚህ ቡድኖች ውስጥ ስራው በሚፈልገው ዕውቀት
እና ክህሎትሰራተኞች አልተሟሉም፡፡
ለኮሙኒኬሽን ስራ የሚውሉ የግብዓት አቅርቦቶች አለመሻሻል ፡- ለኮሙኒኬሽን ስራ የሚውሉ ግብዓቶች
አቅርቦት በተገቢው መንገድ እየቀረቡ ባለመሆኑ ስራዎች ላይ ጫና እያደረሰ ይገኛል፡፡ በተለይ ከቴክኒካዊ
ቋት እንዳይኖር አድርጓል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በዲፓርትመንቱ ለሚሰሩ ስራዎች ከጥራት ይልቅ ለአነስተኛ
ገንዘብ ትኩረት መሰጠቱ ስራው ላይ ከፍተት እንዲፈጠር አድርጓል፡፡
ከቅርንጫፍ ፖስታ ቤቶች እና ከዲፓርትመንቶች ጋር ያለው የመረጃ ልውውጥ ደካማ መሆን ፡- ከተለያዩ
አነስተኛ መሆን፣ በየዕለቱ አዳዲስ መረጃዎች አለመጫን፤ የገጹ ተከታዮች ቁጥርም አነስተኛ መሆን እና
መረጃዎችንም ቡስት ለማድረግ አለመሞከሩ፡፡ ድረ-ገፁ ሙሉ በሙሉ አለመስራቱ እና ሳቢ አለመሆኑ፣
ዩቲውብ ቻናል እና ትዊተር ገጽ እና ሌሎች የማህበራዊ ድረ-ገጾች ከመጠቀም አንፃር ከፍተኛ ክፍተቶች
መኖራቸው፡፡
በወቅታዊ ጉዳዮች መጠመድ፡- የተግባቦት ስራዎቻችንን ስትራቴጂክ ከሆኑ ጉዳዮች ይልቅ በወቅታዊ
ጉዳዮች ማተኮር፡፡ ይህም ለከፍተኛ አመራሩ በኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዙሪያ የማማከር ስራ ላይ ትኩረት
እንዳይደረግ አድርጓል፡፡
2.4.3 መልካም አጋጣሚዎች
አማራጭ የሆኑ የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን መገኘታቸው
የአለም ፖስታ ህብረት ለኮሙኒኬሽን ስራ ትኩረት መስጠት
የትምህርት ቤት ፖስታ ክበባትን ለማጠናከር በጎ ፈቃደኝነት መኖር
የገፅታ ገንባታው ሥራው እየተጠናከረ መምጣት
የማህበራዊ ድረ-ገፅ አጠቃቀም እየተጠናከረ መምጣት ፡- ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም
ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነው፡፡ የደንበኞችንና የሰራተኞችን ጥቆማዎች በቀላሉ ማግኘት ማስቻሉ
እንዲሁም በቀላሉ ብዙ ሰዎች መረጃው እንዲደርሳቸው ጥረት መደረጉ እና የተከታዮች ቁጥርም
ጭማሪ እያሳየ መምጣቱ፡፡
2.4.4 ስጋቶች
አሉታዊ ገጽታ በፍጥነት አለመቀየር ፡- ከዚህ ቀደም ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ደንበኛው
የነበረው አመለካከት አሉታዊ ጎን የሚያመዝን ነው፡፡ ምንም እንኳን በአሁኑ ወቅት የሪፎርም ስራ
በመስራት በለውጥ ሂደት ላይ የሚገኝ ተቋም ቢሆንም ቀደም ሲል የነበረውን ስም ለመቀየር የራሱ ጊዜ
መወሰዱ የማይቀር ነው፡፡ አመለካከት የረጅም ጊዜ ሂደት በመሆኑ ቀደም ሲል የነበረው የተቋሙ ገጽታ
አሁን የምንሰራው ስራ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር ግልፅ ነው፡፡ ደንበኛ ለውጦችን እያየ
በሂደት ድርጅቱ የሚሰራቸውን አበረታች ስራዎች ይደግፋል የሚል ፅኑ እምነት አለን፡፡ ይህን ዕውን
እንዲሆን ግን ሁሉም የድርጅቱ ሰራተኛ ቁርጠኝነትና ቀጣይነት ያለው ተሳትፎ አስፈላጊ ነው፡፡
የብልሹ አሰራሮች መኖር፡- በድርጅቱ የተለያዩ ዲፓርትመንቶች ከብልሹ አሰራር ጋር በተያያዘ የሚወጡ
መረጃዎች አሉ፡፡ መሰል ተግባር ላይ የተሰማሩ ህገወጥ ስራቸው እንዳይታወቅባቸው እና የገንዘብ
ምንጫቸው እንዳይደርቅ የተለያዩ ፕሮፓጋንዳዎችን ሊያሰራጩ ይችላሉ፡፡ ለውጡን ለመደገፍ ፍላጎት
ያለውን ሰራተኛ እንዲሁም ደንበኛን አፍራሽ መረጃዎች እያሰራጩ ብዥታ ሊፈጥሩበት ይችላሉ፡፡
የበጀት እጥረት ፡- ከሚዲያ ተቋማት፣ ከአማካሪ ድርጅቶችና ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት
ለሚሰሩ የኮሙኒኬሽን ስራዎች የበጀት እጥረት ሊያጋጥም ይችላል የሚል ስጋት አለ፡፡ የሚተላለፉ
መልዕክቶች ተቀባይነት እንዲያገኙ የተመረጡ የተግባቦት ስራዎችን ፕሮፌሽናል በሆኑ ተቋማት
ማሰራት አስፈሊጊ ነው፡፡ ስለሆነም ይህንን ለማሳካት ለስራው በቂ በጀት ይዞ መንቀሳቀስ ያስፈልጋል፡፡
ለክፍሉ የሚገባውን ትኩረት አለመስጠት፡ - በድርጅቱ የውስጥ እና የውጭ ኮሙኒኬሽን ስራው በጥሩ
ሁኔታ እንዲሰራ መሻት ቢኖርም ክፍሉን ለማጠናከር ፍላጎት አለመኖር፡፡
ክፍል ሦስት
አተገባበር
የኮሙዩኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት ስትራቴጂውን ዕለት ተዕለት የመተግበርና አተገባበሩን የመከታተል
ኃላፊነት የኮሙዩኒኬሽን እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዲፓርትመንት ቺፍ ኦፊሰሩ ነው፡፡ ውጤታማ የሆነ
እንዲሆኑ መልዕክቶቹ የሚተላለፉበትን መንገድ መምረጥና መወሰን ተገቢ ይሆናል፡፡ ይህም ስትራቴጂካዊ
አዘጋጅቶ ለተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የመስጠትና የተቋሙን ስራዎች ማስተዋወቅ፣ በስብሰባዎች እና አውደ
መረጃ ለመስጠት፣ የተቋሙ ይፋዊ እንቅስቃሴዎች ለማስተዋወቅ፣ ምልመላና መረጣ ለማከናወን፣ ለባለ ድርሻ
ለማስተላለፊያነት የሚያገለግል ነው፡፡ ለምሳሌ፡- በየወሩ የሚታተመው ፖስታ ጋዜጣ፣ በዓመት ሁለት ጊዜ
የሚታተመው ዜና ፖስታ መጽሔት፤
3.1.5 ኦን ላየን ሚዲያ/ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ
ኦን ላየን ሚዲያ ድረ-ገጽ እና ማህበራዊ ሚዲያዎችን የሚያካትት ሲሆን በይነ መረብ /Internet/ በመጠቀም
በተቋሙ ዌብሳይትና ማህበራዊ ሚዲያ አማካይነት መረጃ ለማስተላለፍ ጥቅም ላይ የሚውል ነው፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ በብሮድካስት ሚዲያው (ቴሌቪዥንና ሬዲዮ) በአየር ሰዓት ኪራይ እና ተመርጠው ስፓንሰር
የድርጅቱን እንቅስቃሴ የተመለከተ ዜና እና መረጃ በተገቢው ሁኔታ ለማስተላለፍ ውጤታማ የሆኑ የዜና
ተቋማት /የመገናኛ ብዙሃን ግንኙነት ሊኖር ይገባል፡፡ ይህ ግንኙነት ከድርጅቱ የኮሙኒኬሽን ቺፍ ኦፊሰር ባሻገር
የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ሊመሩትና ሲኒየር ባለሙያዎች ሊሳተፉበት ይገባል፡፡ ከዚሁ ጎን ለጎን የድርጅቱ ዋና
ዋና እንቅስቃሴዎች የዜና ሽፋን በሚያገኙበት ጊዜ ሚዲያዎች መረጃዎቹና ባላቸው የዜና ፋይዳ (News
Value) ለይተው ትኩረት ለሚሰጧቸው ጉዳዮች ተገቢውን ትኩረት እንዲሰጡ አዎንታዊ ግፊት ማሳደሩ
አስፈላጊ ይሆናል፡፡
የድርጅቱ ሰራተኞች ለመገናኛ ብዙሃን መረጃ/ቃለመጠይቅ በሚሰጡበት ጊዜ እርስ በእርሱም ሆነ ጉዳዩ
ተገቢው ክትትልና ጥንቃቄ መደረግ ይኖርበታል፡፡ ለመረጃ ግልፅነትና ቅልጥፍና መረጃ የሚሰጡ አካላትን
መለየትና ተገቢውን የመገናኛ ብዙሃን አጠቃቀም ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ለድርጅቱ
በሌላ በኩል የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች መደበኛ ያልሆኑና ከተቋማዊ ስራዎች ጋር ቀጥተኛ
የተቋም ገፅታ ከመገንባት ባሻገር ከመገናኛ ብዙሃን ጋር መልካም ግንኙነት ለመፍጠር ያግዛል፡፡
ክፍል አራት
የኮሙኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት ስትራቴጂ
4.1 ቁልፍ መልዕክቶች
ድርጅቱ በአዋጅ ከተሰጠው ተልዕኮ በመነሳት ማስተለለፍ የሚፈልጋቸው ቁልፍ መልዕክቶች ከተልዕኮው
በመነጩ ምሰሶዎች (Pillars) ላይ የተመሰረቱ እንዲሆኑ ከፍተኛ ጥረት ያደርጋል፡፡ በእነዚህ ምሰሶዎች ላይ
ተመስርቶ የሚቀረፀውን መልዕክት ወጥ በሆነ መንገድ በአግባቡ እንዲተላለፍ ማድረግም መሰረታዊ ጉዳይ
ነው፡፡ ስለሆነም ቀጥሎ የተመለከቱት ቁልፍ መልዕክቶች የተቋሙን ተልዕኮ የሚያሳኩ ናቸው ተብለው
ተለይተዋል፡፡
በድርጅቱ ቁልፍ ተግባራት ላይ የደንበኞችና ባለድርሻ አካላት ድምፅ እንዲሰማና እንዲሳተፉ ለማድረግ
በትጋት ይሰራል፡፡
ለድርጅቱ ተልዕኮ ስኬት የተቋሙ ሰራተኞች የጎላ ድርሻ አላቸው፡፡
በመልካም ስነምግባርና ቅልጥፍና የታገዘ አገልግሎት በመስጠት የድርጅታችንን ስምና ዝና እንገነባለን፡፡
የድርጅቱን ገቢ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥተን መስራት ይኖርብናል፡፡
የመረጃ አስተዲደር ሰርዓታችንን የሚያሻሽሉ ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥተን እንሰራለን፡፡
የአገልግሎት አሰጣጥን እና የደንበኛ አገልግሎት አፈጻጸምን ለማሻሻል የሚያግዙ ምቹ ሁኔታዎችን
እንፈጥራለን፡፡
4.2 ስትራቴጂያዊ አጋሮች
የኮሙኒኬሽን ባለስልጣን
ኢትዮቴል ኮም
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
የዓለም ፖስታ ህብረት
የተለያዩ አየር መንገዶች
የተለያዩ የየብስ የህዝብ ትራንስፖርት ማህበራት
የአፍሪካ ፖስታ ህብረት
ጉሙሩክ ኮሚሽን
የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ
ዲኤች ኤል
ግብርና ሚኒስቴር
መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን
የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፓሬሽን
የቡድን ገለፃው መልዕክት ለዲፓርትመንቱ በተሰጠው ዋንኛ ተግባር ላይ የሚተኩር ይሆናል፡፡ የሚመረጠው
መልዕክትም እንደአስፈሊጊነቱ ለዲፓርትመንት መሪዎች በቃል/በስልክ፣ በኢሜይል፣ ወይም በሌላ ተመራጭ
በሆነ አመቺ መንገድ እንዲደርስ እና ለየቡድኖቹ ካስኬድ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በዚህ መነሻነት መልዕክቱ
በየቡድኑ ገለጻ እና ውይይት የሚደረግበት ነው፡፡
4.4.2 ኮሙዩኒኬተሮችን መጠቀም
በዲፓርትመንቶች የሚከናወኑ ስራዎችን ታሳቢ ያደረጉ መልዕክቶችን ለመቅረፅና በተገቢው መንገድ
ለማስተላለፍ እንዲሁም የኮሙዩኒኬሽን ስትራቴጂውን ለመተግበር ለዲፓርተመንቱ ቋሚ ኮሙዩኒኬተሮችን
(Focal communicator/person) መመደብ አስፈሊጊ ይሆናል፡፡ ይህ አሰራር ኮሙኒኬተሮቹ
የዲፓርትመንቶችን ስራዎች በቅርበት ተረድቶ የሚፈለገውን መልዕክት ለማስተላለፍ ያስችላቸዋል ተብሎ
ይታመናል፡፡ ኮሙዩኒኬተሮቹ በኮሙኒኬሽን እና አለም አቀፍ ግኝኙነት ዲፓርትመንት ውስጥ ሆነው
የተመደቡበትን የስራ ሂደት ስራዎች በአግባቡ እንዲተዋወቁ የሚሰሩ ይሆናል፡፡
4.4.1.1 የኮሙዩኒኬተሮች ሚና ፡-
በስራ ክፍሎች ውስጥ የኮሙኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት ስትራቴጂውን አፈፃፀምን ማገዝ፣
ለስራ ክፍልቹ የኮሙዩኒኬሽን ወኪል (Laison) ሆኖ ማገልገል፣
ስራ ክፍልቹ የኮሙኒኬሽን ፍላጎቶችን በመለየት ለኮሙኒኬሽን እና አለም አቀፍ ግኝኙነት ቺፍ ኦፊሰር
ማቅረብ፣
የስራ ክፍልቹን መረጃዎችን በመለየት በመገናኛ ብዙሃን ተገቢው ሽፋን የሚያገኙበትን ዘዴ በመቀየስ
የገፅታ ግንባታ ስራ እንዲሰራ ለዲፓርትመንቱ ግብአቶችን አደራጅቶ ማቅረብ፣
የመገናኛ ብዙሃን ስራ ክፍልቹን የተመለከተ መረጃ ወይም ምላሽ ሲፈልጉ መረጃ ማደራጀት
የኮሙዩኒኬተሮቹ ሚና ይሆናል፡፡
4.4.3 የውስጥ ህትመቶች
በድርጅቱ አሰራሮች ላይ በማተኮር በሚታተመው ፖስታ ጋዜጣ ላይ የተቋሙን ርዕይ፣ ተልዕኮ፣ አፈፃፀም፣
የሞዴል ሠራተኞች/ፈጻሚዎች ድርሻ፣ አርአያነት ያለው ተግባር የፈጸሙ ሰራኞችን በማቅረብ ሌሎች
ሰራተኞችን ለተቋሙ ተልዕኮ ስኬት ለማነሳሳት ሊያግዝ ይችላል፡፡
የውስጥ ህትመቶች የጋዜጣና መጽሔት፣ ዜና መጽሔት፣ብሮሸር ህትመት፣ ፍላየር ጊዜ፣ ብሮሸር በአመት ሁለት ጊዜ፣ ፍላየር
በአመት አንድ ጊዜ
የፕሬስ ኮንፈረንስ የተመረጠው ርእሰ ጉዳይ መልዕክት በማን መተላለፍ አለበት የሚለውን
መግለጫ መወሰን፣
መግለጫውን መስጠት
የተቀናጀ የኮሙዩኒኬሽን በግራፊክስ፣ በህትመት፣ በፐብሊሲቲ እንዲሁም በህዝብ ግንኙነት የሚሰራ
ስራ የገጽታ ግንባታ ስራዎች መለየትና መተግበር፣
የማማከር ስራ ለድርጅቱ የሚመጡ ሰነዶች፣ መረጃዎች እና ሌሎች ጉዳዮችን በቀረቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ
አስመልክቶ ለዋና ስራ አስፈጻሚ ምክር የማቅረብ እና ፕሮፖዛል
የማዘጋጀት ስራ ይሰራል፡፡
የውስጥ ህትመቶች የጋዜጣና መጽሔት፣ ዜና መጽሔት፣ብሮሸር ህትመት፣ የጊዜ ሰሌዳ
ክፍል አምስት
5.1 የክትትልና ግምገማ ዕቅድ እና በጀት
የኮሙኒኬሽን ሥራችን ያመጣውን ውጤት የምንከታተለበትና የምንለካባት ሥርዓት መፍጠር አስፈላጊ ነው፡፡
ክትትል ምን እየሆነ ነው የሚለውን ሂደት ቀጣይነት ባለው መልኩ የምንከታተልበት ሲሆን፤ ግምገማ አጠቃላይ
የኮሙኒኬሽን ተግባራት ፕሮግራሙን ከማሣካት አኳያ ያላቸውን ሚና የምናይበት ነው፡፡ በዚህ ሂደት የሚከተሉት
ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ማተኮር ያስፈልጋል፡፡
የምንመዝነው ውጤትን እንጂ የተከናወኑ ተግባራትን መሆን የለበትም፤
በዚህም መሠረት በኮሙኒኬሽን ግቦች የተከናወኑ የኮሙኒኬሽን ተግባራት፣ የኮሙኒኬሽን ውጤቶችና
ኮሚዩኒኬሽን የፈጠረው ተፅዕኖ ነው፡፡
በግቦቹ ላይ የተመሠረቱ የውጤት አመልካቾች መቀመጥ ይኖርባቸዋል፤
በኮሚዩኒኬሽን ስትራቴጂ ዝግጅት ወቅት ሙሉ የክትትል ዕቅድ ከማውጣት ይልቅ በሂደት ማዘጋጀት የተሻለ
ይሆናል፤
5.2 በጀት
የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ በሚዘጋጅበት ወቅት አንዱ አስፈላጊ የፕሮግራሙ አካል በጀትና የበጀት ምንጭ የመለየት
ሥራ ነው፡፡ በስትራቴጂው የመጀመሪያ ክፍል ላይ የተሰራው ትንታኔ በጀቱ ምን ላይ? በምን ያህል መጠን? መዋል
እንዳለበት ለመለየት ያስችላል፡፡ በኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ በጀት የሚመደብላቸው ሰባት ጉዳዮች አሉ፡፡ እነዚህም፦
1. የኮሙኒኬሽን ምርምር
2. ክትትልና ግምገማ
3. የፕሬስ ሥራዎች ዝግጅትና ሕትመት
4. የብሮድካስት ውጤቶች ዝግጅት
5. ልዩ ልዩ ሁነቶች
6. የዕቅድ ዝግጅትና ቅንጅታዊ ትስስር መፍጠሪያ ስብሰባዎች
7. ለውስጥ ኮሙኒኬሽን
ከዚህ ውጭ ዝርዝር የበጀት መጠን በኮሙኒኬሽን ስትራቴጂው ላይ እንዲቀመጥ አይጠበቅም፡፡ ይህም ሆኖ
ስትራቴጂው ፈጽሞ ሊገኝ/ሊሟላ/ የማይችል የበጀት መጠን ታሣቢ ተደርጎ መዘጋጀት የለበትም፡፡
የኮሙኒኬሽን እና አለም አቀፍ ግኝኙነት ዲፓርትመንት የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ በጀት
የጊዜ ሰሌዳ የሀብት ፍላጎት
ተ.ቁ ተግባራት መለኪያ መጠን አስተያየት
2013 2014 2015 2016 2017 ገንዘብ ምንጭ
4 የግድግዳ ካላንደር በቁጥር 15000 3000 3000 3000 3000 3000 2,500,000 ከድርጅቱ
5 የጠረጼዛ ካላንደር በቁጥር 15000 3000 3000 3000 3000 3000 3,000,000 ከድርጅቱ
7 የግድግዳ ዜና በቁጥር 2600 520 520 520 520 520 7,500 ከድርጅቱ