You are on page 1of 40

የ 2015 ዓ.

ም የስልጤ ዞን የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የአስር ወር የተግባራት አፈጻጸም ሪፖርት

የስልጤ ዞን ብ/ፓ/ቅ/ ፅ/ቤት

ግንቦት/2015 ዓ.ም

ወራቤ

0
መግቢያ

ፓርቲያችን ብልጽግና ባለፉት የለውጥ ዓመታት የኢትዮጵያን ከፍታ ለማሳደግና ብልጽግናን ለማረጋገጥ በኢኮኖሚያዊ፣
በማህበራዊና በፓለቲካዊ ጉዳዮች በርካታ ተግባራትን ማከናወን የቻለ ፓርቲ ነው፡፡ የሀገራችን ወቅታዊ ሁኔታ
እንደሚታወቀው በውጫዊና ውስጣዊ ተግዳሮቶች ውስጥ ሆነን ፓርቲው ለቀጣይ ሥራችን መሠረት የሚሆኑ ስኬቶችን
ማስመዝገብ ተችሏል፡፡

የፓርቲያችንን ጉባኤ ተከትሎ በየደረጃው ህዝቡ ያነሳቸውን የመልማት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የሰላምና ደህንነት፣ ሥራ አጥነትና
ኑሮ ውድነት እንዲሁም በአግልግሎት አሰጣጥ ያሉ ጉድለቶችን ለማረምና የህዝብ እርካታ ከፍ ለማድረግ የተነሱ ጉዳዮች
በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ምላሽ እንዲያገኙ ለማድረግ ትግል እየተደረገ ይገኛል፡፡ በዋናነት ፓርቲን የማጠናከርና
ተቋማዊ አሰራርን መትከል አንኳር ተደርጎ ተወስዷል፡፡

ያለፈውን ዓመት የፓርቲና የመንግስት ዋና ዋና ግቦች አፈፃፀም ግምገማ እንደ መነሻ በመውሰድ የ 2015 ዓ/ም ዕቅድ በማቀድ
ከዞን እስከ ታችኛው መዋቅር ፈፃሚን የማዘጋጀት ስራ ተሰርቶ ወደ ተግባር ተገብቷል፡፡ የፓርቲ አመራርና አባላት
የማጥራት፣ የበቅቶ ማብቃት፣ ጠንካራ ተቋማዊ አደረጃጀት በመፍጠርና በማጠናከር ላይ ትኩረት ያደረገ እቅድ በማቀድ በሁሉም
ተቋማት ደረጃ አደረጃጀቶችን እየፈተሹና እያጠናከሩ ወደ ተግባር ማስገባት፣ፓርቲውን ወደ ፊት ሊያራምዱ የሚችሉ
ወይም ለፓርቲው እሴት የሚጨምሩ ወጣቶች፣ ሴቶችና ምሁራን ላይ ትኩረት በማድረግ አዳዲስ አባላት ምልመላ አሰራርን
በጠበቀ መልኩ መተግበር፤ የፓርቲ ተግባራት በህገ ደንቡ መሰረት እንዲፈጸም ትግል በማድረግ፣ ወደ መረጃ ቋት ያልገቡ አባላትን
ወደ መረጃ ቋት የማስገባት ተግባራት ሁሉንም ተግባራት በጊዜ የለንም መንፈስ የመፈፀም ተግባር ተጠናክሮ እንዲቀጥል
ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ተደርጓል፡፡

በንቅናቄ መፈፀም ያለባቸውን ተግባራት ለይቶ ርብርብ በማድረግ አመራራችንና አባሉ በፓርቲ የሚቀመጡ አቅጣጫዎችን
በመቀበል ዘርፈ ብዙ ስኬቶችን ጠብቆ በማስቀጠልና ጉድለቶችን ያለምህረት በማረም በህዝብ የተነሱ አንገብጋቢ ጥያቄዎችን
መመለስ በሚያስችል ሁኔታ ጠንካራ የፓርቲ አደረጃጀት በመፍጠር የአስተሳሰብና የተግባር አንድነትን በመገንባት ተግባራት
የመፈጸም አቅማችን በማሳደግ ብልፅግናችንን እውን ለማድረግ ከመቼውም ጊዜ በላይ ወሳኝ ወቅት ላይ እንገኛለን፡፡

በዚህ ዓመት እንደ ሀገር የተጋረጡብንን ፈተናዎች በጽናትና በብስለት ተቋቁመን በአዲስ መልክ በፓርቲያችን እየመነጩ
የሚቀርቡና የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ሊያረጋግጡ የሚችሉ አዳዲስ እሳቤዎችን አረንገዴ አሻራ፣ የሌማት
ትሩፋት፣‹‹በደም የተከበረ በላብ የታሰረ›› ወዘተ ከፍተኛ ሀገራዊ ንቅናቄዎች የመምራት፤ የዞናችን ህዝብ የጠየቀውን የአደረጃጀት
ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በዲሲፕሊን በመምራት ውጤታማ ለማድረግና ተቆጥሮ በተሰጠው ተግባር ልክ በአዲሱ የአመራር ምዘና
መመርያ መሰረት የመመዘን ስራ ያለ ጠንካራ ፓርቲና ተቋማዊ አሰራር ሊሳካ የማይቻል በመሆኑ በየደረጃው ያለውን የፓርቲ
መዋቅር በሱፐርቪዥን የማጠናከር ተግባራት ተከናውኗል፡፡

1
በሂደቱ በየደረጃው ተጨባጭ ውጤቶች የታዩ ቢሆንም ከተግባር ተግባር እና ከመዋቅር መዋቅር የአፈፃፀም ልዩነቶች
ተስተውሏል፡፡ በመሆኑም ያለፈው የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈፃፀም እና የፈዴራል እና የዞን ሱፐርቪዥን ቡድን ምልከታ ሪፖርት
በማመጋገብ ጥንካሬዎችን ይበልጥ በማጠናከር እና ጉድለቶችን ፈጥኖ በማረም ፓርቲን በየደረጃው ለመትከል በሚያስችል

መልኩ እንደሚከተለው ቀርቧል::

በፖለቲካና ርዕዮተዓለም ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት

1. የነባራዊ ሁኔታ ግምገማ


ሀ/ የከፍተኛ አመራሩ

 በጥንካሬ

 ከፍተኛ አመራሩ የተግባርና የአስተሳሰብ አንድነቱ ይበልጥ ተጠናክሮ በመሔዱ በሀገራዊ፣በክልላዊና በዞናዊ የተለያዩ
አጀንዳዎች ላይ የጋራ አቋም በመያዝ በቀላሉ እያሳካን የመጣንበት

 በየደረጀው የሚገኘውን የአመራራችን ጤናማነት ነባራዊ ሁኔታ በየወቅቱ እገመገሙ በመሄድና በተለዩ ጉድለቶች
የተመሰረተ የተሻለ ድጋፍ ለታችኛው መዋቅር የተደረገበት

 በየደረጃው የፓርቲና የመንግስት ሥራዎች ተቀናጅተው እንዲመሩ በማድረግ በተለያዩ የማታገያ አጀንዳዎች
በተለይም በመደበኛና በበጋ መስኖ ስንዴ፣በሌማት ቱርፋት፣በምርት አሰባሰብ፣በመከላከያ ሠራዊት ድጋፍ፣ በስራ ዕድል
ፈጠራ፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በትምህርት ሥራዎች፣ በከተማ ንቅናቄ ሥራዎች፣ በአደረጃጀት እና በሌሎች ተግባራትም
እያደረገ ያለው ጥረት፣

 የህዝባችንን የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የገጠሩንና የከተማውን ህዝባችንን በማነቃነቅ
በትምህርት፣ በጤና፣ በመንገድ፣ በውሀ፣ በማብራት፣ በሀገር-ህልውና፣ በስፖርትና በሌሎችም መስኮች በበርካታ መዋቅርች
ለተሞክሮ የሚሆኑ ስራዎች የተሰራበትና ተግባሩን በቅርብ ርቀት ድጋፍ የተደረገበት

 በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ አጠቃላይ የፓርቲና የመንግስት ዋና ዋና ተግባራት ዕቅድ አፈፃፀም በመገምገምና በ2015 በጀት
ዓመት መከናወን ያለባቸውን የፓርቲና የመንግስት ዋና ዋና አቅጣጫዎችን በተደራጀና በተቀናጀ መልኩ የፈጻሚ ዝግጅት
መድረኮች እስከታችኛው መዋቅር ድረስ በትግል ማሳካት የተቻለበት፣

 በጉድለት
 በየወቅቱ በተለያየ መንገድ የሚነሱ ጉድለቶችን ለአብነት የገጠመንን ሀገራዊ የግብዓት እጥረት፣ በሸገር

2
ከተማ የቤቶች መፍረስ ዙሪያ እና የዞኑ ሚና፣ የፕሮጀክቶች አፈፃፀም እና እየገጠመን ያለው ሀገራዊ
ሁኔታ አለማቀፋዊ ይዘት ያለው የኑሮ ውድነት ችግር ወዘተ… ሰነድ እያዘጋጁ በየደረጃው ካለው
አመራር፣ አባል እና ሕዝብ እየተግባቡ የመሄድ ውስንነት መኖሩ፤

 ለስራ አጥ ወጣቱ ፋይናንስ ለማቅረብ ምንጭ የሆነውን ቁጠባና ብድር የማስመለስ ስራው ላይ
እንደመሪ በመራነው ያክል የሚፈለገውን ለውጥ ማምጣት አለመቻሉን

 ሁሉ-አቀፍ ድጋፍ ከመስጠትና ፈጣንና ቀልጠፋ አገልግሎት ከመስጠት አንፃር መሻሻሎች ያሉ ቢሆንም አሁንም
አመራሩ ከችግር ሙሉ በሙሉ ያልወጣ መሆኑን፣

 የሴክተርና የንቅናቄ ተግባራትን እንዲሁም ወቅታዊና መደበኛ የፓርቲና የመንግስት ስራዎችን አደራጅቶና አቀናጅቶ
ከመምራት ይልቅ አሁንም በወቅታዊ ተግባራት ላይ ብቻ የመንጠልጠል ድክመት፣

 አመራሩ ባለቤት ሆኖ ሌብነትን እና ብልሹ አሰራርን ከመታገል አንፃር በከተማ መሬት፣በገጠር የወል
መሬት፣ በተለያዩ መዋጮዎች በደረሰኝ አሰባሰብ፣ በገቢ ፣በፋይናንስ ግዢ እና ኮን/ት አስተዳደር እና
በአገልግሎት አሰጣጥ ጉድለት ወዘተ እየተስተዋሉ ያሉ ጉድለቶች መታየታቸው፣/ሁሉም መዋቅር
 ከስነ ምግባር አንፃር በሶሻል ሚዲያ በዩቲዩብ እና ቲክቶክ በተደራጁና አፍራሽ ኃይሎች በፓርቲያችን
በሚነዙት ፕሮፖጋንዳ እና በሚራገቡ አሉባልታዎች ላይ ብዥታ ውስጥ የመግባት፣ ስልክ የመዝጋት፣

ስልክ ያለማንሳት፣ስብሰባ ላይ አርፍዶ የመገኘት፣ስብሰባ ሳያልቅ ወጥቶ የመጥፋት፣የውጤታማነት


ችግር፣ቢሮና ወረዳ/ከተማ አርፍዶ የመግባትና ፈጥኖ የመመለስ፣እንደ የመዋቅሩ ነባራዊ ሁኔታ ችግር
ፋቺ ድጋፍ አለማድረግ፣አብዛኛው መዋቅር

 ከማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም አንፃር ቀጣይነት ያለው ጠንካራ የማጥቃትና የመመከት ሥራ አሁንም የቤት ሥራ
ሆኖ መቆየቱ፣ሁሉም መዋቅር

 የተጀማመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች በተለይም ገበያን ለማረጋጋት በሁሉም ከተሞች
የተጀመረውን የቅዳሜ፣የእህድ፣የሰኞ በሁሉም መዋቅር ተመሳሳይ ደረጃ አለማድረስና ከማጠናከር አንፃር
አሁንም ጉድለት ያለ መሆኑ፣

 ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በቋሚነት የሚታዩ ችግሮችን እየፈቱ
የመሄድ እጥረቶች መኖር፤

ለ/ የመካካለኛ አመራሩ የሁኔታ ግምገማ

3
 በጥንካሬ

 በዚህ ደረጃ የሚገኘው አመራር የአስተሳሰብና የተግባር አንድነቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ


የመጣ፣ፓርቲያዊ ዲሲፕልን ጠብቆ የተሰጠውን ተልዕኮ በመወጣት ረገድ የተሻለ መሆኑ

 ከላይ በሚወርድ ዕቅድና አቅጣጫ መሠረት መከናወን ያለባቸውን አንኳር የፓርቲና የመንግስት ተግባራትን በመለየት
አቅዶ ለማሳካት መካከለኛ አመራሩ እያደረገ ያለው ጥረት፣

 በዋና ዋና የፓርቲና ንቅናቄ ተግባራት በተለይም በመደበኛና በበጋ መስኖ ስንዴ፣በሌማት ቱርፋት፣በተቀነጀ
ተፋሰስ ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በጤናና ትምህርት ሥራዎች እንዲሁም በከተማ ንቅናቄ
ሥራዎች እና በሌሎች ተግባራት የመካከለኛ አመራሩ ሚና ከፍተኛ የሆነበት፣

 አመራሩ የህዝብ የልማት ጥያቄን ለመመለስ በገጠርም ሆነ በከተማ የሚገኘውን ማህበረሰብ


አስተባብሮ በዓይነትም ሆነ በጥሬ ገንዘብ በማሰባሰብ በርካታ የልማት ስራዎችን እየሰራ መምጣቱ፣

 ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የሚደረጉ በተለያዩ ወቅታዊ አጀንዳዎች ላይ መድረኮችንና ውይይቶችን


በሚቀመጡ ማስፈፀሚያ ዕቅዶችና ስልቶች መሠረት ውጤታማ አድርጎ ለመፈፀም እያደረገ ያለው ጥረት
የተሻለ መሆኑ፣

 በአጠቃላይ ሲታይ ግን የታቀዱ የመንግስትና የፓርቲ ሥራዎችን ለማሳካት የሚደረገው የአመራሩ ዝግጁነት ከጊዜ ወደ
ጊዜ እየተሻሻለና እያደገ የመጣበት ሁኔታ መኖሩ፣

 በጉድለት

 ቁጥሩ ቀላል ያልሆነ አመራር አሁንም የልምድና የተሞክሮ እንዲሁም የውጤታማነት እጥረት የሚታይበት መሆኑ፣

 የፓርቲውን መርሆዎችና እሴቶች በሚገባ ጨብጦ ዕለት ተለት ለተግባራዊነቱ ርብርብ በማድረግ የተዛቡ
አመለካከቶችን ታግሎ ከማስተካከል አንፃር አሁንም የተጠናከረ የግንባታ ሥራ የሚያስፈልገው መሆኑ፣

 በወቅታዊ ሶሻል ሚዲያ በሚረገቡ አሉባልታዎች ላይ ብዥታ ውስጥ የመግባትና የመወሰድ፣የእርስ


በርስ መጠራጠር ችግር ውስጥ የመግባት፣በሶሻል ሚዲያ የመፃፍና የማፃፍ ችግር ውስጥ የመግባት
 መካከለኛ አመራራችን የፓርቲ እና የመንግስት ተግባራትን አቀናጅቶ ከመምራት ይልቅ አሁንም በወቅታዊ ተግባራት
ላይ የመንጠልጠል ሁኔታ መኖሩ፣

 የሴክተርና የዘመቻ ሥራን አቀናጅቶ ውጤታማ አድርጎ ከመምራትም አንፃር ጉድለት ያለበት መሆኑ፣

 የሚመራዉን መዋቅር ነባራዊ ሁኔታ በዝርዝር ገምግሞ የተደራጀና የተገመገመ ሪፖርት በወቅቱ ከማቅረብ አንፃር
ውስንነት ያለበት መሆኑ፣

4
 በየተቋማቱ ያለውን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለይቶ በአጭር፣ በመካከለኛና በረዥም ጊዜ አቅዶ በለውጥ
አመራር ማዕቀፍ ውስጥ በመሆን ለላቀ ውጤታማነት ተቀናጅቶ ከመስራት አንፃርም ጉድለት እንዳለበት
ተገምግሟል፡፡

 የስነ-ምግባር ችግር ለአብነት ስልክ የመዝጋት፣ስልክ ያለማንሳት፣ስብሰባ ላይ አርፍዶ


የመገኘት፣ስብሰባ ሳያልቅ ወጥቶ የመጥፋት፣የውጤታማነት ችግር፣ቀበሌ አርፍዶ የመግባትና ፈጥኖ
የመመለስ፣ሲገመገም የማኩረፍ ወዘተ

 ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት አንፃር አሁንም የሚፈለገውን ቁመና በሚገባ ያለመላበስ፣ በትንሽ ውጤት
የመርካት፣
ሐ/ የመሠረታዊ ድርጅትና የህዋስ አመራር ሁኔታ

 በጥንካሬ

 የሚሰጡ ተልዕኮዎችን ተቀብሎ ለማሳካት እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ የተሻለ መሆኑ፣

 በሚሰጠው አቅጣጫና ድጋፍ መሰረት ወቅታዊና መደበኛ ተግባራትን ወደ መሬት ለማው


የሚያደርገው ጥረት በአዎንታ የሚወሰድ መሆኑ፣በአብዘኛው መዋቅሮች

 ሁሉም መሠረታዊ ድርጅት የዓመቱን ዕቅድ አዘጋጅተው እየተንቀሳቀሱ ያሉ መሆኑ፣

 በማህበረሰብ አቀፍ በሚደረጉ በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ ገንዘብ በማዋጣትና በማነቃነቅ

ከፍተኛውን ሚና የሚጫወት መሆኑ፣

 አብዛኛው መሠረታዊ ድርጅት በተቀመጠዉ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ዉይይት እያደረገ መሆኑ፣

 በጉድለት

 መሠ/ድርጀትና ህዋሳት የነባራዊ ሁኔታ ግማገማ ምንጭ መሆን አለመቻላቸው፣

 የታችኛው አመራራችን የትምህርትና የግንዛቤ ደረጃዉ ከሌላዉ የአመራር እርከን በአንፃራዊነት ዝቅተኛ ከመሆኑ ጋር
ተያይዞ ወቅታዊ መረጃዎችን በሚገባ አደራጅቶ መዋቅሩን በሚገባው ልክ ከማንቀሳቀስ አንፃር ጉድለት መታየቱ፣

 በአንዳንድ በከተሞች ሆነ በወረዳዎች የሚስተዋለውን የህገ-ወጥ ግንባታና መሬት ወረራ ከመከላከል ይልቅ
የጉዳዩ ተባባሪ ሆኖ የመገኘት፣/በአብዘኛው መዋቅሮች/

 ምን አለፋኝ በሚል አስተሳሰብ ኃላፊነት ያለመወጣትና ከኃላፊነት የመሸሽ፣ተስፋ የመቁረጥ/በደጋማ ወረዳዎች


ይሰፋል/

5
 የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ሙሉ በሙሉ በላይኛው መዋቅር ብቻ እንደሚፈታ መጠበቅ፣አልፎ አልፎ
ከህዝበኝነት አባዜ ያለመላቀቅ ሁኔታ መታየት፣

 በሁሉም መዋቅር በሚባል ደረጃ መሠረታዊ የጠባቂነት ችግሮች በስፋት መታየታቸው፣

 በመደበኛነት መሠረታዊ ድርጅቶችና ህዋሳት በተግባር አፈፃፀም መነሻ ለመሠረታዊ ድርጅትና ህዋስ አመራሮች
እንዲሁም ለአባላት የደረጃ ምዘና በየወቅቱ እየሰጡ አለመሄድና የማሳወቅ ድክመት፣
መ/ የአባላችን ሁኔታ

 በጥንካሬ

 በፓርቲና መንግስት የሚወርዱና የሚቀመጡ ዕቅዶችንና አቅጣጫዎችን መሬት ለማውረድ የሚያደርገው ጥረት ጠንካራ
መሆኑ፣

 በየወቅቱ በሚፈጠሩ ድርጅታዊ፣ መንግስታዊና ህዝባዊ መድረኮች ላይ አባሉ በግንባር ቀደምትነት


እያደረገ ያለው ትግልና ተሳትፎ፣

 እንደ ሀገር የገጠመንን የሠላም፣ የፅንፈኝነት፣ የአክራሪነት፣ የኑሮ ውድነትና የገበያ አለመረጋጋት ፈተናዎች ተቋቁሞ
ከፓርቲና መንግስት ጎን ሆኖ አሁንም በተለያየ መንገድ እያደረገ ያለው ድጋፍ፣

 በ 2015 በጀት ዓመት የታቀዱ የፓርቲና የመንግስት ሥራዎችን ለመፈፀም በፈፃሚ ማዘጋጃ መድረኮች ላይ ባሳዩት
ቁርጠኝነት ልክ እየተንቀሳቀሱ መሆኑ፣

 በሠላም፣ በልማት፣ በመልካም አስተዳደርና በዴሞክራሲ ግንባታ እና በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ በሚፈጠሩ መድረኮች
ቀድሞ ተሳታፊ በመሆን እና ገንቢ ሀሳቦችን በመስጠት ለመድረክ ስኬት አዎንታዊ ሚና እያበረከተ መሆኑ፣

 የክልል አደረጃጀት ጥያቄን ፓርቲና መንግስት ምላሽ ለመስጠት እያደረገ ያለውን ጥረት በመደገፍ የቆመበት
አግባብ የተሻላ መሆኑ፣
 በጉድለት

 ጥቂት የማይባል አባላችን ድርጅታዊ፣ መንግስታዊና ህዝባዊ ዉይይቶች ላይ ወጥነት ባለው መልኩ በግንባር
ቀደምትነት የመሳተፍ ድክመት፣

 በተለያዩ በሶሻል ሚዲያ በኤፍቢ፣በቱዩበሮች፣በቱዩተሮች በሚለቀቁ አሉባልታዎች የሚዋዥቅ አባላት


የሚታይበት

6
 እርስ በእርስ ከመተጋገል ይልቅ በአመራር ጉድለት ላይ ብቻ ማነጣጠር፣

 ጥቂት የማይባል የፐብሊክ ሰርቫንት አባል ትክክለኛ የአባል ስብዕና ተላብሶ ለብልፅግና ዕሳቤና ግብ ከመታገል
አንፃር ጉድለት ያለበት መሆኑ፣

 መርህ ላይ ቆሞ ከመታገል ይልቅ ቅራኔዎችን ብቻ መነሻ አድርገው የሚንቀሳቀሱ አባላት መኖራቸው፣ጉድለቶችን


ውጫዊ ማድረግና ዉስጣዊ አድርጎ ያለመቀበል፣

 ዉይይቶች ላይ ወጥነት ባለው መልኩ አለመሳተፍ፣ የአቋም መዋዥቅና የጥራት ችግር መስተዋሉ፣

 ከኑሮ ውድነትና ከአንዳንድ የመልካም አስተዳደር እጦት ጋር ተያይዞ አልፎ አልፎ በፓርቲና
በመንግስት ላይ የምሬት ድምፆችን ማስተጋባት፣

 በተሰማራበት ቦታ የህዝብ አገልጋይነት መንፈስ ተላብሶ ባለጉዳይን ከማስተናገድ አኳያ ግንባር ቀደም ያለመሆኑ፣

ሠ/ የህዝብ

የገጠር ህዝብ ሁኔታ

 በጥንካሬ

 እንደ ሀገር የገጠመንን የሠላም፣ የፅንፈኝነት፣ የአክራሪነት፣ የኑሮ ውድነትና የገበያ አለመረጋጋት ፈተናዎችን ተቋቁሞ
ከፓርቲና መንግስት ጎን ሆኖ አቋሙን ሳያሸራርፍ አሁንም በተለያየ መንገድ እያደረገ ያለው ድጋፍ የሚደነቅ መሆኑ፣

 በ 2015 በጀት ዓመት የታቀዱ የፓርቲና የመንግስት ሥራዎችን ለመፈፀም የሚያደርጉት እንቅስቃሴ፣በፓርቲና መንግስት
የሚቀመጡ ዕቅዶችንና አቅጣጫዎችን መሬት ለማውረድ የሚያደርገው ጥረት፣

 በየወቅቱ በሚፈጠሩ መንግስታዊና ህዝባዊ መድረኮች ላይ የገጠሩ ማህበረሰብ እያደረገ ያለው ተሳትፎና ትግል፣
በሠላም፣ በልማት፣ በመልካም አስተዳደርና በዴሞክራሲ ግንባታ የላቀ ሚና መጫወታቸው

 የክልል አደረጃጀት ጥያቄን ፓርቲና መንግስት ምላሽ ለመስጠት እያደረገ ያለውን ጥረት በመደገፍ ያሳዩት ቁርጠኝነት፣
 በጉድለት

 አ/አደሩ ራሱ የሚያመርተውን ምርት በውድ ዋጋ እየሸጠ ባለበት ሂደት የማደበሪያ ዋጋ የሚቀመስ አልሆነም የማለት፣

 ወቅታዊ የዓለምዐቀፍ ሁኔታን ግንዛቤ ውስጥ ያለማስገባት ሁኔታ መታየቱ፣

 አለምዐቀፍ ሁኔታ የወለደው የማደበሪያ ዋጋ መናርና የአቅርቦት ዕጥረቱን እንደመልካም አስተዳደር እጦት ጋር ተያይዞ
የምሬት ድምፆችን ማሰማት፣

 ለኑሮ-ውድነት በስፋት የመንግስት ችግር ብቻ አድርጎ የመመልከትና የሚዛናዊነት ችግር የሚታይ መሆኑ፣
7
ረ/ የከተማ ነዋሪ ሁኔታ

 በጥንካሬ

 የከተማው ማህበረሰብ የፅንፈኛ ፖለቲከኞች ሰለባ የመሆን እድል ያለው ቢሆንም መንግስት የሚያደርጋቸውን
የፖለቲካና የልማት እንቅስቃሴዎች እየደገፈ መሆኑ፣

 አቋሙን ሳያሸራርፍ ከአመራር ጎን በመሆን በየወቅቱ እያጋጠመን ያለው አስቸጋሪ ሁኔታ እንዲቀየር
እያደረገ ያለው ድጋፍ፣

 መንግስታዊና ህዝባዊ የውይይት መድረኮች ላይ እያደረገ ያለው ተሳትፎና እየሰጠ ያለው ገንቢ አስተያየት፣የልማትና
የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ፊት ለፊት የመታገልበት ሁኔታ፣

 የፀረ-ሠላምና ፀረ-ልማት ኃይሎችን ከማጋለጥ፣ ከመታገልና ከማክሸፍ አንፃር የበኩሉን ሚና በግንባር ቀደምትነት
እየተወጣ መሆኑ፣

 ህዝባዊ አደረጃጀትን በማጠናከር የማታ ሮንድ ጥበቃ ላይ በመሳተፍ የአካባቢ ሠላምንና ፀጥታን ለማረጋገጥ
እያደረጉት ያለው እንቅስቃሴ የተሸለ መሆኑ፣

 በአከባቢ ልማትም እያደረገ ያለው ተሳትፎና እንቅስቃሴ እየተሻሻለ የመጣ መሆኑ፣


 በጉድለት

 እስካሁን በከተሞች የተከማቹና ሲንከባለሉ የቆዩ የልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮች ሁሉም በአንዴ መንግስት
እንዲፈታለት የመጠበቅ ዝንባሌ፣
 የተለያዩ የአካባቢ መሠረተ ልማቶች እንዲሰሩ የተወሰኑ አካላት በመንግስትና ፓርቲ ላይ ጫና ለማሳደር መሞከር፣
 ባልተመለሱ የልማትና የመልካም መልካም አስተዳደር ችግሮች ምክንያት በተለይም ከገበያ አለመረጋጋት ጋር ተያይዞ
ተስፋ የመቁረጥና በፓርቲና መንግስት ላይ የማማረር ሁኔታ፤
 ጥቂት የማይባል የከተማ ነዋሪ መንግስታዊና ህዝባዊ ዉይይቶች ላይ የመሳተፍ ፍላጎት ዝቅተኛ መሆን፣
ሸ/ የወጣቶች ሁኔታ

 በጥንካሬ

 ወጣት ከፀጥታ አካላት ጎን ሆኖ የአካባቢውን ሠላም ለማስጠበቅ በየአካባቢው እያደረገ ያለው ተሳትፎና
እንቅስቃሴ የተሻላ መሆኑ፣

 በክረምትና በበጋ በጎ ፈቃድ ሥራዎች ላይ አብዛኛው ወጣት ያደረገው ተሳትፎና እንቅስቃሴም እጅግ የተሻለና ተስፋ

8
ሰጪ መሆኑ፣

 በየወቅቱ የሚያደርገውን ሀገራዊ ጥሪ ተቀብሎ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ረገድ የወጣት አደረጃጀቶችና አጠቃላይ
ወጣቶች እያሳዩት ያለው እንቅስቃሴ፣

 በየወቅቱ በሚፈጠሩ ሀገራዊ፣ ክልላዊና ካባቢያዊ መድረኮች በተለይም በፀጥታ፣ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች፣ በተለያዩ
የፓርቲና መንግስት የንቅናቄ መድረኮች፣ በበጎ ተግባራት እና በሌሎችም ወቅታዊ መድረኮች ወጣቶች በንቃትና በስፋት
በመሳተፍ ከፓርቲና መንግስት የሚወርዱ አቅጣጫዎችንና ተልዕኮዎችን ተቀብሎ ለተግባራዊነቱም እያሳዩት ያለው
አዎንታዊ ምላሽ፣

 በጉድለት

 አጋጣሚ ቢያገኙ በፀረ-ሠላም ቡድኖች ተታለው በአፍራሽ ተልዕኮ ዉስጥ ለመሰለፍ ወደ ኋላ የማይሉ ወጣቶች

መኖራቸው፣

 ከሥራ ዕድል አለመፈጠርና ኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ ባሉ ጉዳዮች በማማረር መርህ ላይ ቆሞ ከመታገል ይልቅ ጭፍን

ትችትና ጥላቻ የማንፀባረቅ ሁኔታ፣

 ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንፃር መንግስት በሚያመቻቸዉ ማንኛዉም የሥራ አማራጭ ተደራጅቶ ከመስራት ይልቅ ሥራ
ማማረጥና የተቀጣሪነት አዝማሚያ መታየቱ፣

 በሥራ-አጥነት ችግር ሳቢያ ቁጥሩ ቀላል ያልሆነ ወጣት የተሟላ ሥነ-ምግባር ይዞ በአገር ወዳድ ስሜት ምክንያታዊ ትወልድ ሆኖ

ከመውጣት አንጻር ያለ ጉድለት፣

 በተለያዩ ኢሞራላዊ ድርጊቶች ውስጥ መዘፈቅ፣ በተለያዩ ሱሶች መጠመድ እና በመሳሰሉት ችግሮች ሰለባ የሆነ ወጣት

ቁጥር የሚናቅ አለመሆኑ፣

 የጠባቂነትና የሥራ ባህል አለማሻሻል፣ሁሉንም ነገር መንግስት እንዲፈታ የመፈለግ ዝንባሌ አሁንም ያለ መሆኑ፣
ቀ/ የሴቶች ሁኔታ

 በጥንካሬ

 ሴቶች በአደረጃጀቶቻቸው በመጠርነፍ የሚሰጣቸውን ተልዕኮ ከራሳቸው ሁኔታ ጋር አጣጥመው እቅድ በማውጣት፣
በወጣው እቅድ ላይ በመግባባትና በጋራ በማቀድ የሚያደርጉት እንቅስቃሴና እያስመዘገቡት ያለው ተጨባጭ ውጤት፣

 ቁልፍ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ሴቶችን ለመተካትና ለማብቃት እየተደረገ ያለው ጥረት በሴቶች ዘንድ ከፍተኛ
መነሳሳት የፈጠረ መሆኑ፣

9
 በሠላሙ፣ በልማቱና መልካም አስተዳደር ሥራዎች ላይ ሴቶች እያበረከቱ ያሉት እንቅስቃሴ የተሻላ መሆኑ

 በጉድለት

 በየደረጃው አጠቃላይ ሴቶችን በጋራ ዓላማ ዙሪያ በማነቃነቅ ህብረተሰባዊ ለውጡን በማፋጠን ሴቶች በፖለቲካዊ፣
ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፉ ያላቸውን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚደረገው ትግል አሁንም ሰፊ ጉድለት
የሚታይበት ነው፡

 በታችኛዉ መዋቅር አሁንም የሴቶች ተዋፅዖ የሚፈለገውን ያህል አለመሆን፣ በተለይ በትምህርት ዘርፍ አመራርነት ማለትም
በርዕሰ-መምህርነትና በሱፐርቫይዘር ደረጃ ላይ የሴቶች ቁጥር ማነሱ መስተካከል ያለበት እንደሆነ ተገምግሟል፡፡

በ/ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ሁኔታ

 በጥንካሬ

 አሁን ባለው ሁኔታ አብዛኞቹ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወሳኝ በሆኑ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የተቀራረበና
ተመሳሳይ ሀሳብና አዎንታዊ አቋም ያላቸው መሆኑ፣

 እንደዞን የጋራ ም/ቤቱን በየወቅቱ በተለያዩ ሀገራዊና ክልላዊ አጀንዳዎች በመወያየት የጋራ ም/ቤቱ አዎንታዊ
ሚና እንዲጫወት መደረጉ፣

 ለአንድ ለተፎካካሪ ም/ቤት አባላት በዳሎቻ ከተማ አስተዳዳርና በዞን ታርቲ ድጋፍ በማድረግ ቤት እንዲሰራ
የተደረገበት፣

 ጦርነቱ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ድቀት በማስከተሉ መንግስት የኢትዮጵያን ጥቅም በሚያረጋግጥ
መልኩ ድርድር ማድረጉ እና ከድርድሩ በኋላም መንግስት በፍጥነት እያደረጋቸው ያለውን ሥራዎች በተለይም መልሶ
የማደራጀት ሥራዎችን አብዛኞቹ የተፎካካሪ አባላት ማድነቃቸው፣

 የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ አቅም ለማዳከም ከተለያዩ አቅጣጫዎች ብዙ ጫናዎች እንዲደርስ ታቅዶ እየተሰራ
ቢቆይም ያንን በመቋቋም ሉዓላዊነቷ ተረጋግጦ እንዲቀጥል መንግስት እያደረገ ያለው መሪነት እጅግ የሚያስመሰግን
መሆኑን መናገራቸው፣
 በጉድለት

 ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከተ የመጣውን የሥራ-አጥነት ችግር፣ የገበያ አለመረጋጋትና የዋጋ ግሽበት በወለደው የኑሮ

10
ውድነት፤በሸገር ሲቲ ስለተፈናቀሉ ዜጎቻችን፣በዞናችን እየተሰሩ ባሉ የልማት ፕሮጀክቶች ዲሊያንስ፣በስልጤ የልማት
ማህባር፣በክልል አደረጃጀት ጉዳዮች ላይ ወዘተ...የማስጮህ ሁኔታ መኖራቸው፣

 ዓላማቸውን ለማስፈፀም ደግሞ ወጣቶችን የመጠቀም ፍላጎት፣ በተላይም በወጣቶች የበጎ ስራዎች አመካይነት ወጣቱን
ለመያዝ የመፈለግ ፍላጎት የሚታይ አዝማሚያ መታየቱ፣

 ከአልቾ ዊሪሮ ወረዳ ውጪ ሌሎቹ አምስቱ የተፎካካሪ ታርቲዎች የጋራ ም/ቤት ወቅታቸውን ጠብቀው መወያየት
አለመቻለቸው፣

በህዝባችን የተነሱ ጉዳዮች

 በጥንካሬ
 የብልጽግና ፓርቲ የሚያቅዳቸው እቅዶች የሚያማልሉ ናቸው የመደመር ፍልስፍና የሰው ተኮር መሆኑ
ህብረተሰቡ በነጻነት የመናገር እና የህብረተሰቡ ተሳትፎ ስራዎች እንዲጠናከሩ የማድረግ ስራ ሊቀጥል

እንደሚገባ/ሁሉም መዋቅር/

 ብልጽግና ማለት ከስሙም መሊቅ/እድገት ማለት ነው ይህን እድገት አሁን ላይ በአጭር ግዜ ማየት
ያልቻልነው በሃገሪቷ ውስጥ ከውጭም ከውስጥ ጠላቶች በመብዛታቸው የህዝቡ ሁለንተናዊ ልማቱ
እንዳይረጋገጥ በመሆኑ ነው እንጂ ከብልጽግና ዓላው አንጻር ወደ ፊት ጥሩ ነገር ይመጣል የሚል ተስፋና

እምነት እንዳላቸው ይገልጻሉ /ሳንኩራ ፣ዓለምገበያ

 ስለፓርቲችን ቅቡልነት ለዚህ የሚያነሷቸው ምክንያቶች፤ ሀገራዊ አንድነትንና ሉዋላዊነትን


ለማረጋገጥ የተሰረው ስራ፤ የፖሎቲካ ምህዳሩን ለማስፋት የተሰረው
ስራ፤ ሜጋ ፕሮጄክቶችን ለማጠናቀቅ የተደረገው ጥረት፤ /በሁሉም መዋቅር/

 እንደ ዓለም ገበያ ከተማ ከተማ አ/ሩ ራሱ የብልጽግና ውጤት መሆኑ ብልጽግና እንደፈለግን የመናገርና

የሃሳብ በነጻነት ማራመድ፣ እኩልነት የሰጠ ፓርቲ ነው የቀድሞው አፈናና ውሽት ቀርቷል፡/ሳንኩራ
፣ዓለምገበያ
 ህዝቡ ከለውጡ በኃላ የመጡ ለውጦችና በሂደቱ የገጠሙ ችግሮችን የሚፈታበት አግባብ በጥንካሬ
የሚያነሳ ሲሆን በተለይም የህዳሴ ግድብ ለማጠናቀቅ የተደረገውን ጥረት ፣የሠላም ስምምነት፣

11
የህዝብ ድጋፍና ቁርጠኝነት፣ ገበታ ለሀገር፣ አረንጓዴ አሻራና የሌማት ትሩፋት፣

 የማህበረሰቡ ሚና የጎላ መሆኑንና በወረዳ/ከተማው የሚያወርደውን እቅድ ለማሳካት ቁርጠኛ

መሆኑንና ከብልፅግና ጎን እንደቆመ የሚገልፁበት ሁኔታ በጥንካሬ የሚወሰድ መሆኑ፣ አብዛኛው


መዋቅር
 በጉድለት
 አዲስ አበባ ላይ ህገ-ወጥ ቤት በሚል የሚፈርሰው ትክክል አይደለም ከፓርቲው መርሆችና እሴቶች

አብሮ የሚሄድ አይደለም/ድግሪው ይለያይ እንጂ ሁሉም

 የተረኝነት አስተሳሰብ በኦሮሚያ በግልጽ እየተንጸባረቀ ነው/ሦስቱ ደጋማ ወረዳዎች የተነሳበት/


 ከቤት ፈረሳ አንጻር የተከሰተውን ችግር ለመፍታት ሌሎች ዞኖች እየተንቀሳቀሱ እና የተፈናቀሉትን

ሲያመጡ የኛ ዞን እያመጣ አይደለም ምንም ድጋፍ እያደረገ አይደለም/ሦስቱ ደጋማ ወረዳዎች


 የማዳበሪያና የምርጥ ዘር አቅርቦት ችግር ፤መንግስት ለነጋዴ አሳልፎ ሰጥቶናል፣የኑሮ ውድነት ፍጹም
የሚቀመስ አልሆነም ፤የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች በወቅቱ እየተጠናቀቁ አይደለም በሚል በስፋት

የተነሳበት/ሁሉም ጋ/
 ወረዳ ላይ የህግ የበላይነት እየተከበረ አይደለም፤ ለአብነት ሌባ ታስሮ ያለአግባብ ይለቀቃል፤

እንደሀገርም የህግ በላይነት እየተከበረ አይደለም ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡/ምዕ/አዘ/በ


 በአጠቃላይ ከአዲስ አበባ ቤት መፍረስ ጋር አጡዘው የሚያነሱበት እንዲያውም በዚህ ሳዓት ምርጫ

ቢኖር ተፎካካሪ ፓርቲ አያሸንፍም ነበር ወይ በሚል የሚያነሱበት ምዕ/አዘ/በ የሌራ ከተማ

መሠ/ድርጅት አመራሮች የሚያነሱበት መንገድ ከመጠን ያለፈና የስነ-ምግባር ችግር፣


 ከኑሮ ውድነት ጋር በተያያዘ የኑሮ ውድነትን ለመቅረፍ የሚሰራው ስራ በተለይም መንግስት ሰራተኛ
ትኩረት የነፈገ ነው በዚህም የተነሳ የአባላት ስሜት መሸርሸር ጀምሯል ፓርቲው ችግሮችን ከላይ
ጀምሮ ህገወጥነትን እያረሙ ከመሄድ አንጻር ያላየው ነው፡፡ ለመንግስት ሰራተኛው ክብር እንደሌለው
የሚሳየው ደሞዝ ማሻሻያ ያለማድረጉ ነው፡፡ ነጋዴን የሚቆጣጠርበት ህግ ቢኖርም ያለመቆጣጠር

ችግር አለ ፓርቲው ታች ወርዶ ያለውን የህዝብ ሁኔታ ማየት አለበት፡፡ምስ/አዘ/


 ዝነኝነትና ተቀባይነት በአጋጣሚም በስራም ሊገኝ ይችላል፡፡ ከባዱ ዝነኝነትና ተቀባይነትን ማዝለቅ
ነው፣ብልጽግና በሃይማኖቶችና በህዝብ አያያዝ ስህተት ተቀባይነቱን እንዳያጣ እየሰጋን ነው፣ሰፋ ያለ

የህዝብ ቅሬታ መኖሩን፣/ ወራቤ ከተማ


 የህገ ወጥ ሰዎች ዝውውር ያለ መሆኑ ወጣቶች በደላላዎች እየተታለሉ ወደ ሌላ ሀገር እየሄዱ ያሉ

መሆኑ በቀጣይም ተከታትሎ ህጋዊና አስተማሪ ቅጣት መወሰድ እንዳለበት/ዓለምገበያ ከተማ

12
 ከተማው ላይ ሌብነት/ስርቆት የሞተር፣ባጃጅ፣ ስልክ፣ሱቅ …..ወዘተ እንደሚሰረቅ በቀጣይ የከተማ

ፓሊስ የተለከየ ትኩረት ሰጥቶ ማ/ቡን አሳትፎ በጋራ መሰራት እንዳለበትና በሌቦቹም ላይ ተገቢው

ውሳኔ መሰጠት እንዳለበት/ዓለምገበያ ከተማ


 ሁለቱም ከተማ ላይ የወጣቶች መዝናኛ አለመኖሩ ወጣቶች ለሱስና ለአልባሌ ቦታ ብሎም ለስድት

እየተዳረጉ መሆኑ/ሳንኩራ፣ዓለምገበያ ከተማ


 ሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ላይ የፌክ አካውንት እየተከፈተ የከተማውን ወጣት ለማደናበር የሚሰሩ

አካላት መኖራቸው ይሕም በብዛት በአመራሩና በሴክተር ሰራተኛው አማካይነት መሆኑ/ዓለምገበያ


ከተማ
 ዓምና ለምርጥ ዘር በሚል የከፈልነው ብር ዘሩንም ሳንወስድ ብሩ እስከ አሁንም

አለመመለሱን፣ከንግድና ገቢ ስረዓት ጋራ በተያያዘ አርብ እለት ገበያ ቀን እንዲቀየር በተደጋጋሚ

ተጠይቆ ምላሽ አላገኘንም፣የወረዳው መቀመጫ ትሆናለች ተብሎ ነበር በሚል የተሳሳተ ትርክት

የማንሳት ሁኔታ ያለ መሆኑ /ሳንኩራ ማዞሪያ ከተማ

2. በዝግጅት ምዕራፍ የተከናወኑ


2.1 የፈጻሚ ዝግጅት
 በጥንካሬ

 በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ዞናል በስልጢ ወረዳ በተዘጋጀው መድረክ በየዘርፉ የተከናወኑትን ተግባራት
በመገምገም፣የነበሩ ጥንካሬዎች እና ጉድለቶች በተገቢው ተለይተው በጥንካሬው ልምድ በመውሰድ፣ የነበሩ ጉድለቶች

የ 2015 በጀት ዓመት እቅድ ውስጥ በማካተት ወደ ተሻላ ትግበራ መገባቱ፣

 የዞን ቅድመ-ዝግጅት ተከትሎ የወረዳ/ በከተማ አስተዳደር፣ የቀበሌ፤ የመሰረታዊ ድርጅት ፤ የህዋስ እንዲሁም
በግለሰብ ደረጃ እቅድ በማዘጋጀት እና ተገቢውን ተግባቦት በመፍጠር ወደ ትግበራ መገባቱ፣
 በየደረጃው የታቀዱ እቅዶችን ከራሳቸው አካባቢያዊ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማጣጣም ተዘጋጅቶ ከፈጻሚ

አካላት/አመራርና አባላት/ ጋር በቂ ተግባቦት የተፈጠረ ሲሆን ሁሉም እንደየ ማህበራዊ መሰረቱ በዕቅዱ አፈፃጸም ዙርያ
የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ተደርጓል፡፡

 በየደረጃው የሚታቀደው እቅድ ከዋናው እቅድ የተናበበ እንዲሆን ጥራት ያለው እቅድ ለማቀድ ጥረቶች ተደርጓል፡፡

 ከዞን ጀምሮ እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ አደረጃጀቶች የሚወያዩበት ወጥ አሰራር በማዘጋጀት ወደ ውይይት
የተገባ መሆኑ፣

13
 በጉድለት

 አንዳንድ መዋቅሮች እቅድ ያላጠናቀቁ መሰረታዊ ድርጅትና ህዋሳትና መዋቅሮች መኖራቸው በ 9 ወር አፈጻጸም
በጉድለት ተገምግሞ የተቀለሰ እቅድ በማቀድ ሁሉም በእቅድ እንዲመሩ የማድረግ ስራ ቢሠራም ተግባሩ
አለመጠናቀቁ ፡፡

 በየደረጃው የታቀዱ እቅዶች የእቅድ ጥራት ውስንነቶች የሚታይባቸው፣የነባራዊ ሁኔታ ግምገማ የሌለው፣ኮፒ-
ፔስት፣የተሟላ ዕቅድ ያልያዘ በተለይም እንደፓርቲ የሚሰሩ ስራዎችን ያልያዘ ዕቅድ

የተገኘበት/ቅበት፣ጦራ፣አልቾዊሪሮ፣ምዕ/አዘ/በ፣ሳንኩራ፣ዳሎቻ

 የዓመቱ የፓርቲ ዕቅዶች እስከ ግለሰብ ድረስ ስለመታቀዱ እንዲሁም ሁሉም አደረጃጀቶችና አባላት በዕቅድ

እየተመሩ ስለመሆናቸው ማግኘት ያልተቻለባቸው መሠ/ድርጅቶችና ህዋሳት መኖራቸው፣የውሸት መረጃ


ከማስተላለፍ አባዜ መውጣት ያልቻልንበት፣
2.2 ሁሉም አደረጃጀቶች የተሟላ ዕቅድ እንዲኖራቸው የተደረገበት መንገድ

 በጥንካሬ

 የ 2015 ዓ.ም የፈጻሚ ማዘጋጃ መድረኮች በአብዛኛው መዋቅሮች በቂ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ በተገቢው
መፈጸማቸው፤
 ከጥቂት መዋቅሮች ውጪ በመ/ድርጅትና በህዋሳት ደረጃ ዕቅድ እንዲኖራቸው መደረጉና በአሰራርና አደረጃጀት

መመሪያው ላይ በተቀመጠው መሠረት ዕቅዶቹ በመ/ድርጅቶች ኮንፍራንስ የጸደቁ መሆኑ፣

 ዕቅዶች በፎርማቱ መሰረት የተዘጋጁ መሆኑ፣ በተዘጋጀው እቅድ ላይ ውይይት የተደረገበት መሆኑና

 ሞደል የአደረጃጀቶችና የግለሰብ ዕቅድ በአብዛኛው ተደራሽ መደረጉ አንዲሁም እስከ ግለሰብ ድረስ የታቀዱ ዕቅዶች

መኖራቸው፤ በአብዛኛው መዋቅር መ/ድርጅትና ህዋስ አደረጃጀቶች የአባልነት መዋጮ ዕቅድ በአግባቡ ተካትቶ የታቀደ
መሆኑ፣
 በጉድለት፡-
 የህዋስና መሰረታዊ ድርጅት ዕቅድ ዝግጅት በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ተግባራዊ ከማድረግ አንጻር ሰፊ ጉድለት
መኖሩ፤
 የዕቅድ ዝግጅት የጥራትና ይዘት ጉድለት ያለበት (ነባራዊ ሁኔታ የማይተነትን፣ የድርጊት መርሃ ግብር የሌለው፣ የዕቅድ
መጠን የማይገልጽ፣ የአባላት መዋጭ ፣አባላት ምልመላ አደረጃጀቶች በአብዛኛው የመዋጮ ዕቅድ የሌላቸው
መሆኑ፣
 ነባራዊ ሁኔታ የተነተነና አደረጃጀቶቹን የሚመሰል ዕቅድ አለማቀድ፤ የወረዳውን መነሻ ዕቅድን እንደ ራስ ዕቅድ

14
ወስደው ከራስ ተጨባጭ ዕቅድ ያላቀዱ መ/ድርጅቶች፣ ህዋሳት መኖራቸው፣
 የመሰረታዊ ድርጅት ንዑሳን ኮሚቴዎች ዕቅድ ተዘጋጅቶላቸው ያለመመራቱ፣
 የአባላት የግል ዕቅድ የተንጠባጠና በአግባቡ ያልታቀደ መሆኑ፣በስተቀር የአባላት የግል እቅድ አለመኖሩ፡፡
 አባላት በውይይት ወቅት የግል ዕቅድ እንዳላቸው በቃል ደረጃ የተናገሩ ቢሆንም በተደረገው የዶክመንት

ፍተሸ ያልተገኘ መሆኑ፣ ወራቤ ከተማ 01 ቀበሌ/


 በአብዛኛው መዋቅር በህዋሳት እና በግለሰብ ዕቅድ ፣እንደፓርቲ በዓመቱ የሚሰሩ ዝርዝር ተግባራት፣
የድርጊት መረሃ ግብር የሌለው መሆኑ፤

 የግለሰብ ዕቅድ በተደራጀና በተሟላ መልኩ ያልታቀደ መሆኑ(ማስፈጸሚያ ድርጊት መርሃ

ግብር፣የአባላት የመዋጮ ፣የግንኙነት አግባብ የማይገልጽ መሆኑ) የሁሉም ህዋሳት ዓመታዊ ዕቅድ

በመ/ድርጅት ዘንድ ያለመደራጀት መሆኑ፣

2 . 3 የአመራሩና አባሉን የአቅም ግንባታ ተግባራትን ከማከናወን አኳያ

 የወቅታዊ የፖለቲካ፣ የልማት፣ የፀጥታና የመልካም አስተዳደር የሁኔታ ግምገማ ሰነዶችን በማዘጋጀት በየደረጃው
ከሚገኘው አመራር ጋር በተገቢው በመግባባት፣ በተዋረድ ለመላው አባላት እና ደጋፊዎች በማውረድ የተግባር
እንቅስቃሴ መደረጉ፣
 በየደረጃው በተለያዩ ወቅታዊ ሀገራዊና ዞናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ማለትም

ከወጣቶች፣ ሴቶች፣ ምሁራን፣ የሀይማኖት መሪዎች፣ አ/አደሮች፣ የከተማ ነዋሪዎች ጋር ገንቢ ውይይቶች
መደረጋቸው፣

 የ2015 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ሥራዎች አፈፃፀም መነሻ ያደረገ የአመራርና አባል የማጥራት መድረክን
እንደ ቁልፍ መገንቢያ መሣሪያ አድርጎ በመውሰድ በየደረጃው የሚገኝ የአመራሩንና አባሉን አቅም ለማጎልበት ታቅዶ
መሰራቱ፣
 የአባላት ፖለቲካዊ አቅም ለመገንባት እንዲሁም የተግባርና አስተሳሰብ አንድነት ለመፍጠር የመሠረታዊ ድርጅትና
የሕዋስ ውይይቶች የማይተካ ሚና ያላቸው ሲሆን ሰፊ የፖለቲካ ሥራዎች በመስራትና ያሉንን አባላት በማጥራት
በአዲስ መልክ እንዲደራጁ በማድረግ ለአቅም ግንባታና ተልዕኮ ሥምሪት የተሻለ ሁኔታ ለመፍጠር ተችሏል።

 አሁን ባለው ሁኔታ ፓርቲን ለማጠናከር በየማህበራዊ መሠረት የሕዋሳት ውይይቶች በየ 15 ቀናት እየተደረገ ይገኛል፡፡
የተግባር አንድነት ለማረጋገጥ በያንዳንዱ ተልዕኮ አፈፃፀም ሂደት የሚፈጠሩ ግድፈቶችንና የተዛቡ አስተሳሰቦችን ጊዜ
ሳይሰጠዉ ከማረም አንፃርም በርካታ መሻሻሎች ተመዝግበዋል፡፡

 “የልሳነ ብልፅግና” መፅሄት ቅፅ 1 ቁጥር 3 ፈጥኖ ለአባላት ተደራሽ በማድረግ በመ/ድርጅትና በህዋስ ውይይት በማድረግ

15
ለፓርቲው አመራርና አባላት አቅም መገንብያ እንዲሆን መደረጉ፣
 ሁሉም መሠረታዊ ድርጅቶች የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት፣ የቀጣይ ዕቅድ እና የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ
ላይ ተጨማሪ ግንዛቤ እንድይዙ ወጥ በሆነ ሁኔታ አቅም የመገንባት ሥራ መሰራቱ፣

2.4 በየደረጃው ተዘጋጅተው ውይይት የተደረገባቸው ሰነዶችን በተመለከተ

 ልሳነ-ብልፅግና 2 ኛ ዓመት ቅፅ 1 ቁጥር 3 መጽሄት ላይ ውይይት ተደርጎዋል፣

 ክልል በተነሱ የአደረጃጀት ጥያቄዎች ዙሪያ የተዘጋጀ ክልላዊ የዉይይት ሰነድ፣

 በደ/አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተደረሰውን የሰላም ስምምነት አስመልክቶ በተዘጋጀው ሰነድ፣

 ጥቅምት 24 ሰሜን እዝ ላይ በህወሃት የተፈፀመዉ ጥቃት የመታሰቢያ መነሻ ሠነድ፣

 በደም የተከበረ በላብ የታሰረ በሚለው ሰነድ፣

 ዘላቂ ሰላምና ቀጣይነት ያለው ዕድገት የማረጋገጥ ውጥኖች በሚለው ሰነድ፣

 የአመራር እና አባላት ማጥራት መድረክ /በወቅታዊ የፖለቲካ ፤ የሰላም እና የልማት ተግባራት ሁኔታ ግምገማ
ሰነድ፣

 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እና የ 2 ኛ ምዕራፍ የአደረጃጀት ጉዳይ ሰነድ፣

 ዐቅምን በውጤት፤ ፈተናን በስኬት በሚል ለብልጽግና አመራርና አባላት የተዘጋጀ የስልጠና ሠነድ፣

 ለፀረ ሙስና ቀን በዓል አከባበር ፓናል ዉይይት የቀረበ ክልላዊ መነሻ ሰነድ፣

 በፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ክልላዊ የመ/ድርጅት ግንዛቤ ማሳደጊያ መድረክ፣

 በቅርቡ በፓርቲው በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ድሎችን ጠብቆ ሳናሳንስና ሳናንኳስስ በመቀበል
ወቅታዊ ፈተናዎችን በብቃት መመከት የሚያስችል አቅም መገንቢያ መድረክ እና ሌሎችም የውይይት
ሰነዶች ላይ አባሉ ውይይት አድርጎባቸዋል፡፡

በየወቅቱ ከማዕከል በሚወርዱ ሰነዶች የአመራርና የአባለት ሰልጠና መድረክ የተመራበት አግባብ ‹‹በደም የተከበረ በላብ
የታሰረ››፤ ‹‹ዐቅምን በውጤት፤ ፈተናን በስኬት››፤ ከፈተና ወደ ልዕልና፤ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ወዘተ አፈፃፀም
በሱፐርቪዥን ምልከታ ግኝቶች፡-

 በጥንካሬ
 በየወቅቱ አባላት እንዲወያዩባቸው የወረዱ ወቅታዊ አጀንዳዎች በቂ ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ የተፈጠሩ መሆኑን
የተገኘባቸው መዋቅሮችና የሱፐርቭዥን ቡድኑ በገባባቸው ህዋሳትና መሰረታዊ ድርጅቶች ዘንድ ማየት መቻሉ፣
 በስልጠናው መድረኮችም የተፈጠረው ቁጭትና መነሳሳት ወደ ተግባር እየተለወጡ መሆኑ መልካም እንደሆነ፣

16
በመድረኩም በየመዋቅሩ በስልጠናው ማለፍ ያለባቸው አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች መሳተፋቸውን ማረጋገጥ
መቻሉን፣
 ከውስን አካላት በስተቀር በስልጠናው መድረክ ማለፍ ያለባቸው አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች የስልጠናዎቹን
መድረክ ያለፉ መሆኑ፤

 በጉድለት
 የስልጠናም ሆነ የውይይት መድረኮች ወደ ታች እየወረዱ በሄዱ ቁጥር የተሟላ ቅድመ ዝግጅት
ግድፈት የሚታይበት፣የተበታተና የአባላት ተሳትፎ የሚታይበት፣
 በሰነዶቹ ይዘትና መሰረታዊ ጭብጥ አባላት በተገቢው እንዲጨብጡ እየተደረገ ያለበት አግባብ መሠረታዊ ጉድለት

መታየቱ፣ሰለጠኑ/ተወያይረተዋል የተባሉ አባላት አብዘኛው ሲጠየቅ መናገር የማይችልበት ሁኔታ በሁሉም መዋቅር
ያጋጠመ መሆኑ፣
 በአባላት ዘንድ ውይይት የተደረገባቸውን ርዕሰ-ጉዳዮች እና መሰረታዊ ጭብጦችን ያለማስታወስ ሁኔታ በስፋት
መኖሩን፣የመድረኮቹ ጥራት ችግር እንደሆነ ምልከታ በተደረገባቸው አደረጃጀቶች በሙሉ መታየቱ፣
 ሰነዶቹ የተደራጁበትን ሁኔታ ምልከታ ሲደረግ ከውስን ሰነዶች በስተቀር ብዙሃኑን ማግኘት
አለመቻሉን፣በአብዛኛው መዋቅር

2.5 የአስተሳሰብና የተግባር አንድነትን ለማጠናክር እየተሰራ ያለው የፖለቲካ ስራ አፈፃፀም ያለበትን ደረጃ

 በጥንካሬ
 የአመራሩ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ያለ በመሆኑ ከክልል አደረጃጀት ጋር ተያያዥ በነበሩ አጀንዳዎች
በቀላሉ እየተግባቡ የጋራ አቋም የተያዘበት፣እንደዞን ደማቅ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ማድረግ የተቻለበት፣
በሁሉም መዋቅር
 በየደረጃው ተግባርን ማእከል ያደረገ የፖለቲካና የአደረጃጀት ተግባራት እንቀስቃሴ ለማሳካት ከሚደረገው ጥረት መነሻ
የፓርቲው አመራር የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በአብዛኛው መዋቅር መኖሩን መመልከት መቻሉ፣

 የአመራርና አባላት ማጥራት መድረኮችንና ሌሎች የግንባታ መድረኮች በመጠቀም በተከታታይ የማረም ሥራዎችን
እየሰሩ መሆናቸው፣

 በህዋሳት እየተደረጉ ባሉ ውይይቶች የአመለካከት ችግሮችን ለማራም ት ል ቅ ዕድል መሆናቸው፣

 የአ/አደር መሰረታዊ ድርጅትና ህዋሳት በወቅታዊ የግብርና ልማትና የመልካም አስተዳደር አጀንዳዎች ላይ
እንደሚወያዩና ከሞላ ጎደል በአብዛኛው መዋቅር ተመሳሳይ ግንዛቤ መኖሩ መረጋገጡ፣
 በየደረጃው ጤናማ መተማመንና መናበብ እንዳለ በውይይት በተነሱ ሀሳቦችና በተግባር የተሰሩ ስራዎች
ያስረዳሉ፣ምስራቅ ስልጢ ወረዳ አመራሩ

17
 በአመራሩ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በመኖሩ ሁሉንም የህበረተስብ ክፍል በተደራጀ አግባብ ወደ ልማት

ስራ ማስገባት መቻሉ፣ስኬታማ የአመራር ተሞክሮዎችን ተ ከ ታ ታ ይ ነ ት ባ ለ ው መ ል ኩ ማስፋት፣ምስ/ስልጢ


 በአብዛኛው መዋቅር የአመራሩን የአስተሳሰብና ተግባር አንድነትን ለማጠናከር ተልዕኮ እየሰጡ እና እየገመገሙ
እንዲሁም በተግባር ሂደት ግድፈት የታየባቸውን አመራሮች እየገመገሙና እያረሙ መሄዳቸው

ምስ/ስልጢ፣ሁልባራግ፣ስልጢ፣ምስ/አዘ፣
 በጉድለት

 የተሟላና ወጥ ቁመና ያለው የፓርቲ አመራርና አባላት ከመፍጠር አንጻር ጉድለት መኖሩ፤ የፐ/ሰርቫንት

አባላት፣የኢን/ዝ መ/ድርጅትና በተለይም በፐብልክ ሰርቪስ መ/ድርጅት)፤

 ከወረዳ/ከተማ ከጠቅላላ አመራሩ እስከ አባል ድረስ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ለማጠናክር የሚሰራው የፖለቲካ
ስራ አሁንም ብዙ መስራት የሚጠይቅ መሆኑን፣

 በመሠ/ድርጅትና በህዋስ አመራሩ በሁሉም አካባቢ ወጥና ተቀራራቢ የሆነ የአመራር የአስተሳሰብና የተግባር
አንድነት ያለመፈጠሩ፣
 ለህበረተሰብ ጥያቄዎች ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ሰበቦችን የማብዛት፣የህዝብ መድረኮች የመሸሽ አዝማሚያዎች

መኖራቸው፣/ ወራቤ ከተማ/

 ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ጉድለቶች ፈጥኖ ያለማረም፣የተሳሳተ ሪፖርትና እይታ እንዲኖር

ጥረት የማድረግ፣/ ወራቤ 01 ቀበሌ፣ሳንኩራ ማዞሪያ

 በአፍራሽ አጀንዳዎች የመጠለፍ አዝማሚያ መታየቱ (በሸገር ሲቲ ጋር የተፈጠረ አጀንዳን በፓርቲው ስርዓት
ከሚያገኘው መረጃ ይልቅ የማህበራዊ ሚዲያን የመረጃ ምንጭ አድርጎ

የመጠቀም/ምዕ/አዘ/በ፣አልቾዊሪሮ፣ምስ/አዘ/በ ከመካከለኛ-የበታች አመራሩ ድረስ/

 ሁሉም አመራር በእኩል ደረጃ የተግባር ተሳትፎ ከማድረግ አንጻር ውስንነት መኖሩ፤የተጀመሩ ውይይቶች ጥሩ
ቢሆኑም እስከ ታች ድረስ ባለመውረዱ የተነሳ አሁንም ልዪነቶች በስፋት የሚንጸባረቁ መሆኑን፣

 የመሠ/ድርጅት አመራሩ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ላይ የሚፈለገውን ደረጀ የደረሰ አለመሆኑን፣የውጤታማነት

ችግር፣ የአቅም ውስንነት እና በግልጽ በሚታይ የሥነ-ምግባር መጓደሎች የሚገለጽ መሆኑ፤ምዕ/አዘ፣ወራቤ፣አልቾ


2.6 የአመራርና የአባላት የማጥራት እንዲሁም የአመራር ምዘና ስራ ስለመከናወኑ

 በጥንካሬ
 የፓርቲያችን አመራርና አባላት የማጥራት ስራ ከዞን ማዕከል እስከ ታች ቀበሌ ድረስ ሳይጠባጠብ መከናወኑ፣

በመድረኮቹ በስራ አፈጻጸም ድክመት፣ በስነ-ምግባር ብልሽት እንዲሁም በአመለካከት ጥራት ግድፈት የሚታይባቸው
18
አመራርና አባላትን በሚገባ በመለየት የማረምና የመገንባት ሥራ መሰራቱ፣በሁሉም መዋቅር
 በማጥራት መድረኮች የየደረጃው አመራር እና አባላት ሁኔታ ግምገማ ሰነድ ላይ የበሰለ ውይይት በማድረግ ተገቢ
ግንዛቤ መያዙ፣ በአካል ግምገማ ነጥሮ የውጡ ጉዳዮች በሂስ ግለ ሂስ እና በማጥራት መድረክ ባለቤት
ማግኘታቸው፣
 በሂስ ግለ ሂስ ሂደቱ በአመራርና አባላት መካከል ተገቢ መማማር የተፈጠረበት፤ ክፍተቶች በትግል እንዲታረሙ
መልካም ዕድል የተፈጠረበት፣ የማጥራት ሂደት በጣም አስተማሪ የነበረበት፣
 የፓርቲያችንን ውስጠ ዴሞክራሲ የሚያጠናክር፣ አመራርና አባላትን ለቀጣይ ተልዕኮ ያነሳሳ እና የውስጥ አቅም
የሚፈጥር እንደሆነ
 በአጠቃላይ በየማህበራዊ መሰረቱ የተፈጠሩ የማጥራት መድረኮች የተሻለ ግንዛቤ የተፈጠረበት፣ ተሳታፊው ሃሳቡን
በዴሞክራሲያዊነት፣ በነፃነት እና በግልፅኝነት ያራመደበት፣ ብዥታ የሚፈጥሩ ጉዳዮች ላይ በግልፅ በመነጋገር እና
በመከራከር የተሻለ ተግባቦት የተፈጠረበት እና ለቀጣይ ተግባር ተነሳሽነትን የጫረ መድረክ እንደነበር የሁሉም መዋቅር
ሪፖርት ያሳያል፣
 የማጥራት መድረኮችን ተከትሎ በፓርቲው ውስጥ የገዘፈ ችግር የሚታይባቸው አመራርና አባላት ላይ ተገቢው
ፓለቲካል እርምጃ መወሰዱ፣
 በአመራር ምዘና መመሪያ ላይ በሁሉም ደረጃ ላለው አመራር ግንዛቤ እንዲይዝ ከተደረገ በኋላ የግማሽ ኣመት አፈፃፀም
መነሻ ባደረገ ሁኔታ ሁሉም የፓርቲ አመራሮች እንዲመዘኑ የተደረገበት፣
 በጉድለት
 በቀበሌያት ለአ/ አደር አባላት የሚሰጠው የምዘና ውጤት አባላት እምብዛም የማይታወቅ መሆኑ፤
 በአንዳንድ አመራሮችና አባላት በማጥራት መድረኩ የተወሰደው እርምጃ አስተማሪ አለመሆኑ ግምገማዉ
የአደርባይነት ችግሮች የሚታይበት መሆኑ፣ከመጠን በላይ የማስታመም ሁኔታ መኖሩንና አባሉ ግን ከችግር
የማይጠራበት፣
 ቀበሌ መ/ድርጅትና ህዋስ በዝቅተኛ ደረጃ የተፈረጁ አመራርን በግንባር ቀደም የመተካት ሥራው
የ ጥ ራ ት ጉድለት ሚታይበት መሆኑ፤

 በ ቀ በ ሌ ደ ረ ጃ የአመራርና አባላት የማጥራት መድረኮች በተገቢው ሁኔታ የተፈፀሙ አለመሆናቸው፣


የአመራር ዲሲፕሊን እና እርምጃ አወሳሰድ አካባቢ የራሱ የሆነ ልልነት የሚታይበት መሆኑ፤
 የኢንተርፕራይዝና የትምህርት ማህባራዊ መሠረት አካባቢ የአባላት ማጥራት ስራው የተሳካ የማይመስል ነገሮች
መኖራቸው፣
 በየመሠ/ድርጅቱ የሚገኘው የኢንስፔክሽንና ቁጥጥር ኮሚቴ ነጻና ህይወት ኖሮት ተግባራትን ከመምራት አንጻር
ሁሉም መዋቅር በሚባልበት ደረጃ ፋንክሽናል ያልሆነ ፤በማጥራት ሂዳት ችግር የሚገጥማቸውን አባላት

19
ቅሬታ አለመፍታት፣

በአደረጃጀት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት

1. የዝግጅት ምዕራፍ አፈጻጸም በተመለከተ

1.1. በ 2014 ዓ.ም በጀት ዓመት ሳይከናወኑ የቀሩ ስራዎችን የ 2015 ዕቅድ ከማዘጋጀት አኳየ (ዕቅድ

ዝግጅት)

በጥንካሬ

 እንደዞናችን በ 2014 በጉድለት የተለዩ እና በ 2015 የእቅድ ዘመን የትኩረት አቅጣጫ የነበሩ ዋና ዋና

ጉዳዮች፡-

 አደረጃጀት አልተጠናቀቀም፤አመራር አካላትና አባላት በፓርቲ የአደረጃጀት መመሪየ

አልተደራጁም፤ መመሪያ አለመገንዘብ ፤ተግባር እና ሀላፊነቱን የለማወቅ ክፍተት፤ ሁሉም

ተግባራት በአደረጃጀቶች አይፈፀሙም፤

 በመሆኑም የ 2015 ዓ.ም ዕቅድ በ 2014 የልተሳኩ፤በከፊል የተሳኩና ዝቅተኛ ክንዉን የላቸዉ

ተግባራት እስከ ህዋስ የዕቅድ አካል ሆነዋል፡፡

 ከዞን እስከ ህዋስ የዕቅዶቻችን ይዘት ከላይ የ10 አመት ስትራቴጂክ/ጠቋሚ አቅታጫ/ ከታች የ2014

ግምገማ መነሻ መድረግ እንዳለብን ተግባብተናል፤ሞዴል እቅድ ለሁሉም ማህ/መሠረት መሠ/ድና ህዋሳት

አዉርደናል፡፡

 እስከ 10ኛ ወር ሪፖርት የመሠ/ድ 100%፤የህዋሳት 100%ና የግለሰብ ዕቅድ (85 - 95%) ፤በሩብ አመት

የመስክ ምልከተ የን/ኮ ዕቅድ እና የግለሰብ ዕቅዶች እንዲሟሉ አቅጣጫ ተቀመጠ የተህሳስ ቀጥሎ

ይቀርበል፡፡

በኢንስፔክሽን የተዩ ጥንካሬዎች

 የወረዳ/ከተማ አስተዳደሮች ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ደረጃ ሁሉም መዋቅሮች የዘርፍ ዕቅዶችን

ጨምሮ ከወትሮ በተሸለ ጥራት አዘጋጅተዉ ወደ ተግባር ምዕራፍ መገባቱን የኢንስፔክስን ቡድኑ

አረጋግጧል፡፡የሚቶ ወረዳ ፓ/ፅ/ቤት አልተየም፡፡

20
 በመሠ/ድና ህዋስ ደረጃ በሁሉም መዋቅር የሚገኙ መሠረታዊ ድርጅቶችና ህዋሳት ዕቅድ እንዳላቸው

የሚያሳይ መረጃዎች እንደተደራጀ በኢንስፔክሽን ቲሙ የተረጋገጠ ቢሆንም ከመሠ/ድ እስከ ግለሰብ

ዕቅድ ተቀራረቢ ተግባር የተየባቸዉ ለአብነት ኡልባራግ (ደመቄ፤ኬራቴና አስተዳደራዊ ዘርፍ

መ/ድርጅቶችና ህዋሳት)፤ስልጢ(በአጀራ 2 መሠ/ድና አሰተዳደር ዘርፍ መ/ድና ህዋሳት፤የፈደራል

ሱ/ቡድን ምሰ/ስልጢ( -------------------------------) የተሸሉ መሆናቸዉን አረጋግጧል፡፡

 ከአባላት እቅድ አንፃር፦ በየደረጃው የዕቅድ መረጃዎች በተህሳስም ሆነ በዚህ ዙር የመስክ ምልከተ

ተረጋግጧል ሆኖም ግን አብዛኛዉ የአመራርና አባላት እቅድ የጥራት ችግር ያለበት ነዉ፡፡

በኢንስፔክሺን የተለዩ ጉድለቶች፡-

 የመሠ/ድና ህዋስ ዕቅዶች የጥራት ችግር፤ከወረዳ/ከ/አስተዳደር የተላኩ ሞዴል እቅድ ኮፒ፤ ሁሉም

ተመሳሰይ/ኮፒ ፔስት/፣የዘርፉን ማታገያ ያላከተተ፤ የአደረጃጀቶችን ተልዕኮ የለያዘ፤ ነባራዊ ሁኔታ

ያለገናዘበ ፣ ሊመዘን የማይችል፤እና ዉስን መዋቅር ቢሆንም ዕቅድ የሌላቸዉ አደረጃጀት እንዳሉ

መመልከት ተችሏል ለአብነት፡-

 ሚቶ የአ/አደር ፤የከተማ ኗሪ እና የፓብሊክ ሰርቪስ ግንባር መሠ/ድና ፐ/ሰርቪስ መሠ/ድና

ህዋሳት(አብዘኛዉ ዕቅድ የለም)

 ሳንኩራ የአ/አደር ግንባር ቦነሻ (የጥራትና ግንዛቤ)

 ዳሎቻ ወረዳ የአ/አድር( ዋንጃ ሾላ (የግንዘቤና የጥራት)

 ምዕራብ የከተማ ኗሪ ግንባር(የጥራት ችግር)

 አሊቾ አብዛና መ/ድ(የግነዛቤ ችግር) ስልጢ ወረዳ(ኩኖ የጥራት ችግር)

 ላንፉሮ የኗሪ ግንባር አለም ጨፌ(የግንዛቤ ክፍተት)

 ምንም ዕቅድ የልተገኘበት ጦራ ት/ት ግንባር፤ አ/ገበያና ደ/ከተማ የኢንተርፕራይዝ

ግንበር፤መሠ/ድ፤ቅበት የት/ትና ኢነተርፕረይዝ ገንባር መ/ድ ፤ሚቶ የከተማ ኗሪና ፐ/ሰርቪስ

 አብዛኛዉ መዋቅር የ 60 ቀን እቅድ አልተገኛም፤

 የን/ኮሚቴዎችና የግል እቅድ ፦ ከነጥራት ችግሩም በየደረጃው የግል ዕቅድ የዘጋጁ አመራሮችና አባለት

ቢኖሩም አሁንም በርካተ አመራርና አባል እቅድ የሌለዉ ነዉ፡፡

2.2. በየደረጃው ላለው አመራርና አባል የእቅድ ኦረንቴሽን በተመለከተ፡-

21
 በየደረጃዉ ፈፃሚ አካላት ማለትም አመራርና አባላት በተጀጋጀዉ እቅድ ላይ ተከታተይ መድረኮችን

በመፍጠር መግባበት ተችሏል፡፡(ቀበሌ፤መሰ/ድ፤ህዋስ )በዕቅድ ተግባቦት፤ በመመሪያ ግንዘቤ ተፈጥሯል፡፡

3.አደረጃጀቶችን በመፈተሸ በአድሱ አሰራርና አደረጃጀት መመሪያ መሠረት የማደራጀትና ግንዛቤ

የመፍጠፈር ስራዎችን በተመለከተ ፤-

3.1. የፓርቲ አደረጃጀቶች በአደረጃጀት መመሪያ መሠረት መደራጀት፤ በግንባር ቀደም አመራር መመራት፣
ሁሉም አባላት አሰራር መመሪያዉን፤ፕሮግራም፤ህገደንቦች ስለመገንዘባቸዉ በጥንካሬና በጉድለት፡-

በጥንካሬ፡-

 በ 2015 ሁሉም የፓርቲ አደረጃጀቶች የአደረጃጀት አሰራር መሰረት እንዲደራጁ በማድረግ ክፍተት
የአደረጃጀት ክፍተቶች ለማረጥበብ የሞከረዋል፡፡
 የ 135869 አባለት መረጃ በኦርኔል ተደራጅቶ በመሠ/ድና ህዋስ በመዝገብ፤ወረዳ/ከተማ በኤከስ

ኤልና ፎቶ፤ በዞን በመረጃ ቋት ለማደራጀት አቅደን በመጃ ቋት 99%፤ ፎቶ 90% ተፈፅሟል፡፡

 በአድሱ አደረጃጀት መሠ/ድርጅት 105 በመጨመር ከ 635 ወደ 740 ሲሆኑ 514 ህዋስ

በመቀነስ ከ 4281 ወደ 4795 ሃዋሳት አደራጅተናል፡፡


 የአሰራር መመሪያዉና ሌሎች ድንቦች ለአባለት ስልጠና ተሰጥቷል እስከ 11 የፓርቲ ደንቦች
ወርዷል
 አሁንም በአሰራር መመሪያ ዉጭ የተደራጁ መሠ/ድና ህዋሳት አሉ

 ግ/ቀደም አመራሮች የሚመሩ ቢሆንም የግንዘቤ ክፍተቶች ሰፊ ናቸዉ

በጉድለት፡-

የኢንስፔክሽን የተለዩ፡

በፌደራል የሱፐርቪዢን ቡድን የተለዩ ጉድለቶች፡-

 የፌድራል ሱፐርቪዢን ቡድን የማዕከል ፐብሊክ ሰርቪስ አባላት ወይይት ወቅት 300 አባል በአንድ

መሠ/ድርጅት መኖሩን አንስቷል ፡፡

በዞን የኢንስፔክሺን ቡድን የተለዩ ጉድለቶች፡-

22
ሚያዝያ 2015 በ 9 ወረዳና 4 ከ/አስተዳደሮች በተደረገ ኢንስፔክሺን የተዩ ጉድለቶች፡-

 አባላት በፓርቲው የአሰራርና አደረጃጀት መመሪያ መሰረት ከማደራጀት አንፃር አብዛኛዉ መዋቅር የመ/ድ

ና ህዋስ አመራሮች ሰፊ የግንዛቤ ክፍተት በመኖሩ መሠ/ደ ከ 210 በላይ ህዋስ ከ 35 በላይ አባላት

የተደራጁ መሆኑን ማረጋገጥ ተችለዋል፡፡

 ለአብነት ጦራ ከ/አስ ኗሪ ግንባር(363 በመ/ድ)፤ ዳሎቻ ከተማ ፐ/ስርቪስ( 280 በመ/ድ)


፤ሚቶ አ/አደር (52 በህዋስ)፤ ላንፉሮ አ/አደር (311 በመ;ድ)፤ምዕራብ የኗሪ የምበሪማ (420
በመ/ድ)፤ዓለም ገበያ የኗሪ ግንባር (415 በመ/ድ)፤ዳሎቻ ወረዳ አ/አደር ከ 6 ሀዋስ በላይ
መደረጀቱን መጥቀስ ይቻላል፡፡
 የአመረር ግነዛቤ ከተሰጠዉ ስልጠና የተራራቀ መሆኑን አብዛኛዉ የተዩ መዋቅሮች መመልከት
ተችሏል፡፡

3.2.በአደረጃጀትና አሰራር መመሪያ መሰረት የአስተባባሪ ኮሚቴ ፤ የፓርቲ አመራር ኮሚቴዎ፤


የመሠ/ድርጅቶችና ህዋሳት እንድሁም ን/ኮሚቴዎች አመራሮች በተቀመጠው አሰራር መሰረት ተግባር
መገምገም፤የሪፖርት ቅብብሎሽ እና ግብረ መልስ ከመስጠት አኳያ በጥንካሬ ና በጉድለት

በጥንካሬ

 በወረዳ/ከተማ አስተዳደር ደረጃ ፤ሁሉም መዋቅር ሊባል በሚችል ደረጃ የአስተባባሪ ኮሚቴ፤ የፓርቲ

አመራር ኮሚቴ አሰራሩን ጠብቆ በመደበኛነት ተግባር መገምገም፤ግ/መልስ መስጠት፤አረጃጀቶችን ጠጋ

ብሎ የሚደግፉበት ሂደት በአብዛኛዉ መዋቅሮች የተሸለ እንደሆነ ተወስዷል፡

 በመሠ/ድርጅትና ህዋሳት ደረጃ፤ ወቅቱን ጠብቆ የፓርቲና የመንግስት ተግባራትን በመደበኛነት

የመገምገም፤ግ/መልስ የመስጠት፤አረጃጀቶችን በተግባር መፈረጅ በአብዛኛዉ መዋቅር ከግዜ ወደ ግዜ

ለዉጥ የለዉ ቢሆንም ሂደቱን ወደ ዉጤት የቀየሩ መዋቅሮች ቁጥር ዉስን መሆናቸዉን መየት ተችሏል፡፡

በተለይም አመራሩ ዕቅዱንና አሰራር ግንዘቤ አስጨብጦ ወደ ተገባር ከማስገባት አንፀር የተሸሉ

፤ሁልባራግ፤-ም/ስልጢ ፤ስልጢ ሲሆን ከነበረባቸዉ ጉድለት የወጡ ቅበት ከተማ ፤ምዕራብ ተጠቀሽ
ናቸዉ፡፡ በአንድ ወይም ሁለት ዘርፍ የሚገለፅ ጥንካሬ የላቸዉ አ/ገበያ፤ምስራቅ አዘርነት፤ላንፉሮ
፤ምዕራብ አዘርነት፤ አሊቾ ፤ዳሎቻ ወረዳ የሚጠቀሱ ናቸዉ

በጉድለት

23
 መሠ/ድርጅትና ህዋሳት ወቅቱን ጠብቆ የፓርቲና የመንግስት ተግባራትን በመደበኛነት

ከመገምገም/ዉይይት/;፤ግ/መልስ ከመስጠት፤ሪፖርት ከመለዋወጥነ ከመመዘን አኳያ ሰፊ ጉድለት

የተየባቸዉ መዋቅሮች ለአብነት

 ሚቶ ወረደ በተዩ 3 ቱም ግንባሮች የመሠ/ድ አመራር ግንዘቤ ዕጥረት፤የተገባር ክፍተቶችና

የመረጃ ጉድለቶች ሰፈ የሚል ሲሆን

 ጦራና ቅበት ከ/አስ ት/ት ግንባር እንዲሁም አ/ገበያ ከ/አስ ኢንተርፕራይዝ መሠ/ድ

የአደረጃጀት ስራ እለተጠነቀቀም፡ ፡ቅበት ከ/አስ ኢንተርፕራይዝ ግንባር፤ ዳ/ከተማ

የኢንተርፕራይዝ እና የት/ት ግምባር የሀዉይይት፤የመረጃ አደረጃጃት ጉድለት የለባቸዉ

ናቸዉ፡፡

 ሲጠቃለል የት/ት ግንባር በተቋማዊ ነፃነት ስም ተዘንግቷል፤የኢንተርፕራይ ግንባር ጉድለቶች

ምክኒያት የላቸዉም፡፡

 የአርሶ አደር እና ከተማ ኗሪ ግንባር አብዛኛዉ የመሠ/ድርጅት/የህዋስ ዉይይቶች ቀለጉበኤና ሪፖርት

በተፈሰስ ወቅት የተካሄዱ መሀናቸዉ አሊቾ ፤ምስ/አዘርነት፤ዳሎቻ ወረዳ፤ለንፈሮ፤ምዕራብ

አዘርነት፤ሳንኩራ .. በታዩ የገጠርና የከተማ ኗሪ አደረጃጀቶች መረጃ መመልከት ተቸሏል፡፡

 በሁሉም ዘርፍ/ግንባር/ እና አብዛኛዉ መዋቅር የህዋሳትና መሠ/ድርጅት ዕቅድ የጥራጥ፤ነባረዊ የልየዘ

መደበኛ ውይይት፤ሪፖርት አላለክ፤ግ/መልስ፤ እንዱሁም መ/ድርጅት አመራሮች ህዋሳት ከመደረፍ አንፃር

በመዋቅሮች መካከል፤በአንድ መ/ር ዘርፎች/ግንባሮች/ መካከል፤ በአንድ መሠ/ድርጅት ህዋሳት መካከል

የተራረቀ ልዩነት መኖሩን አሊቾ፤ስልጢ ፤ዳሎቻ ወረዳ ፤ምስ/አዘርነት፤አ/ገበያ ከ/አስ፤ ጦራ ከ/አስ …

መጥቀስ ይቻላል፡፡

 በቀበሌ ከአንድ በላይ መሠ/ድ በሚገኝባቸዉ ቀበሌዎች የቀበሌ የመሠ/ድርጅት አስተባባሪ ኮሚቴ ሁሉም

መሠ/ድርጅቶች እንደ ቀበሌ ስራቸዉን ገምግመዉ፤ግ/መልስ የሚሰጡበትና ደረጃ የሚፈርጁበት አሰራር

ከኡልባራግ(ደመቄ) ዉጭ በአብዛኛዉ መዋቅር የግንዛቤ ክፍተት መኖሩን ምስ/አዘርነት

መ/አዳዘር፤ላንፉሮ(ጎቤ) ፤አሊቾ(አብዛና)፤አ/ገበያ (01 ቀበሌ ቁ 1 ና ቁ 2) ሳንኩራ፤ ወዘተ መዋቅሮች

ተግባራዊ አልሆነም፡፡

4.በየደረጃው መሰረታዊ ድርጅቶች ኮንፍራንስ የካሄደ ስለመሆኑ፡-

በጥንካሬ
24
 በሦስቱም ዙር በቂ የቅድመ ዝግጅት ተደርጎ ኮንፈረንስ ተካሄዷል፡፡ በክልል፤ በዞን ፤ወረዳ/ከ/አስደረጃ

የተዘጋጁ ሠነዶች፤የኮ/ንስ ቁልፍ አጀንዳዎች፤ማስፈፀሚያ ዕቅዶች፤ሌሎች ወወቅተዊ አጀንደዎችን

በማዉረድ የተካሄዱ ናቸዉ፡፡

 በ 3 ቱም ዙር የኮንፍራንስ መድረኮች በአደረጃጀትና አሰራር መመሪያ መሰረት ወቅቱን የሚመጥኑ

የተለየዩና በርካታ አጀንዳዎች ቀርበዋል ለምሰሌ-

 በአንደኛ ሩብ አመት ኮንፈረንስ(ፈፃሚ ዝግጅት)

 የ 3 ወር አፈፃፀም ሪፖርት መገምገም፤

 የ 2015 እቅድ ገምግሞ ማፅደቅ፣

 በአሠራር አደረጃጀት መመርያው መሠረት አደረጃጀቶችን መልሶ ማደራጀት እና አደረጃጀቶች

ግንባር ቀደም አመራር መሰየም፤

 የዕጩ አባላት ወደ ሙሉ አባላት ማሸጋገር፣

 የተጓደለ አመራር የመተካትና ሌሎች አጀንዳዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

 በየካቲት 2015 ለኮንፈረንስ የቀርቡ አጀንዳዎች፡-

 በአሠራርና አደረጃጀት ጊዜያዊ መመርያ አጭር ስልጠና/ግንዛቤ ማስጨበጥ/

 የ 6 ወር የፓርቲ አፈፃፀም ሪፖርት ፡፡

 የቀሪ ግማሽ አመት የተከለሰ እቅድ ማፅደቅ፡፡

 የእጩ ጊዜያቸው የጨረሱትን በሙሉ አባልነት ማፅደቅ፡፡

 አመራር ጉድለት ባለበት አደረጃጀት መሟለት፡፡

 የመ/ድርቷ፣ የህዋሳትና የአባላት የምዘና ውጤት በዝርዝር አቅርቦ ማፀደቅ ፤

 ሦስተኛ ሩብ አመት (ሚያዝያ) ተመሳሰይ አጀንዳዎች ቀርበዋል

 ጥቅመት በልሳና ብልፅግና አባላት ተወየይተዋል፤

በእንስፔክሽን ምልከተ ወቅት የተዩ ጉድለቶች፡-

 በኮንፈረንሶች መድረከሎች የአሰራር መመሪየዉ ስልጠና የተሰጠ ቢሆንም አመራሩ የግነዛቤ ጉድለቶች

የስራ ድርሻ አለማወቅ፤የምዘና ደረጃ፤ የግንኙነት አግባብ ፤የዕቅድ ግልፅ አለመሆንና የጥራት ችግር

፤የሪፖርት ግዜ ፤የአባላት ተሰትፎ ክፍተት በተለይም የተሳተፉ አመራሮችና አባላት አጀንዳዉን በአግባቡ

የለመጨበጥ መሠረታዊ ጉድለት ተይቷል ፡፡


25
 ለአብነት ሚቶ ኤደነባ አጋ፤አሊቾ አብዛና ፤ምስ/አዘርነት ፐ/ሰርቪስ ግንባር ፤ጦራ ከ/አስ አምቼ

መሠ/ድ፤ምዕራብ አዘርነት የኗሪ ግንባር ፤ላንፉሮ አለም ጨፌ 01 ፤ዓለም ገበያ የኗሪ ግንባር፤ሳንኩራ

ማዞሪያ 01፤ዳ/ከተማ ፓ/ሰርቪስ ግንባር፤ዳ/ወረዳ አ/አደር ግንባር መየት ተችሏል፡፡

 ት/ት ግንባር በአመዛኙ መቀዛቀዝ/መዘንጋት/ የተየበት መሆኑ፤

5.ተግባርን ማእከል ያደረገ የአደረጃጀት የአባላት ምዘና አፈጻጸም

በጥንካሬ፡-

 ሁሉም መዋቅሮች አደረጃጀቶችና አባላትን ወደ ምዘና ስርአት ማስገባታቸዉ

 ፊት የሚወጡ አደረጃጀቶችና አባላት ቁጥር ከፍ እንዲል ሁሉንም አደረጃጀቶችና አባላት በሙሉ ወደ


ምዘና ለማስገባት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑ

በጉድለት፡-

 አብዛኛዉ መዋቅር የአደረጃጀቶችንም ሆና የአባላት ምዘና በቁጥር ከመግለፅ ባለፈ ምዘናዉ የስገኛዉን
ፈይዳ የለመግለፅ ችግር መኖሩ፤

 በተለያየ ወቅት በታየ የመስክ ምልከተ አደረጃጀቶች ተመዝነዉ የተፈረጁበትን ደረጃ የለመወቅ ችግር፤

 በአንዳንድ መዋቅሮች በየወቅቱ ከመመዘን አንጻር ሰፊ ክፍተቶች መኖራችው

 የማይመዘኑ መሰረታዊ ድርጅት ህዋስና አባላት መኖራቸዉ

4. የአደረጃጀቶች የውይይት ቦታና ጽ/ቤት ስለማዘጋጀት

በጥንካሬ

 ተግባሩ በ 2015 የትኩረት አቅጣጨ ተይዞበት የሚሰራ ሲሆን እንደ ዞን ካሉን 740 መሰረታዊ ድርጅቶች

ዉስጥ አባሎቻቸዉን አስተባብረዉ የራሳቸዉን ቢሮ የገነቡና ከግለሰቦች በክረይ ቢሮ ያላቸው

መሠ/ድርጅቶች ብዛት 352 ሲሆኑ ቀሪዎቹ በሂደት ለይ የሉ ናቸዉ፡፡

26
 ከፅ/ቤት አኳ መዋቅሮችን ስንመለከት አሊቾ ከ 104 ለ 104 ፤ኡልባራግ ከ 44 ለ 44፤ ቅበት ከ 24

ለ 22፤ወራቤ ከ 31 ለ 17፤አለም ገበያ ከ 21 ለ 6፤ጦራ ከ 16 ለ 8፤ ላንፉሮ ከ 68 ለ 68፤ሲልጢ ከ 99

ለ 7፤ ሳንኩራ ከ 66 ለ 54፤‹ምስራቅ ስልጢ ከ 58 ምንም ያለዉ የለም፤ምስራቅ አዘርነት ከ 46 ለ 34፤

ምዕራብ አዘርነት ከ 27 ለ 9 ፤ ደሎቻ ከ/አስ ከ 16 ለ 12፤ሌሎች በዚህ መካከል የሉ ናቸዉ፡፡

 ከ 4795 ህዋሳት ዉስጥ በተለየ አማራጭ የመወያያ ቦታ ያላቸው ህዋሳት ብዛት 1806 ሲሆኑ ቀሪዎቹ

በሂደት ላይ ናቸዉ፡፡
5. በሁሉም ተቋማት ደረጃ ተግባራትን በአደረጃጀት ከመፈፀም አንፃር፡-

5.1 ስራዎች በአደረጃጀቶች ስለመሰራታቸውና የተሰሩ ዋና ዋና ስራዎች

በጥንካሬ፤

 ከዞን እስከ ቀበሌ መሠ/ድርጅትና ህዋሳት ድረስ ተግባራት በፓርቲ አደረጀጀት መሠረት በተገበዉ
እየተከናወነ ያለ መሆኑ፡፡

 ከመሠረታዊ ድርጅት ፣ህዋሳ ፣አባል ግለሰብ ድረስ በፓርቲ አሠራርንና አደረጃጅት መመሪያ በተከተለ
መልኩ ተደርጀቷል፡፡

 በፓርቲያችን አሠራርንና ሥራዓት ዙሪያ አባላት ጋር ወይይት ተደርጎ ወደ ተግባር በመግባት በፓርቲያችን
የሚከናዉኑ ተግባራት በሙሉ አሠራር ተጠብቶ ይተገበራል፡፡ ተቋማዊ

 የፖርቲና የመንግስት ሥራዎች ተቀናጅተው እንዲተገበሩ በማድረግ

መዋቅሮችን ስንመለከት
 ሁሉም የዞናችን መዋቅሮች እንደ አግሮኢኮሎጂያቸዉ ተጨባጭ የማህ/ሰቡን ኢኮኖሚያዊ ብልፅግና

ለማረጋገጥ አመራሩንና አባሉን በዋና ዋና የልማትና የመ/አስተዳደር አጀንዳዎች በማሳተፍ እስከ ግለሰብ

እየመዘነ ይገኛል፡

 ለአብነት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ፤ የሙዝና ፍራፍሬ ክላስተር በመፍጠር፤ በሌማት ትሩፋት የወተት ልማት

፤ዶሮ ልማት ፤የማር ሀብት ልማት ፤በክርምትና በጋ የበጎ ፈቀድ ስራዎች ፤ የት/ቤቶችን ስታንደርድ

በማሻሸል፡ በከተማ ልማት ስራዎች ወዘተ አደረጃጀቶችና አባላት በደረጃ እየተፈረጁ ይገኛሉ፡፡

በጉድለት

 ምዘነዉን ሁለም አደረጃጀትና አመራር ፤አባል አየቀዉም፡፡የምዘና መረጃ ፈይል አይደረግም፡፡

27
 ሁሉንም ተግባር በዘመቻ ለመፈጸም የመፈለግና ሁልግዜ ጉትጎታን የመጠበቅ ችግሮች ያለባቸው
አደረጃጀቶች መኖራቸዉን በአባላት ፎቶ አሰባሰብ፤

 የመሠ/ድ አመራር አጀንዳዎችን ለህዋሳት አከፋፍሎ በመስጠት ህዋሳትን ተከፋፍለው ድጋፍ የለ ችግር፡፡

 የፓርቲ አደረጃጀት አመራር ሆነዉ በመንግስ ተግባር ላይ ማትኮር፤

5.2 አደረጃጀቶች ብቃት ባላቸው አመራሮች እየተመሩ ስለመሆናቸው

በጥንካሬ፡-

 በነሀሴ ወር የአመራር ና የአባል ማጥራት ግምገማ መድረኮችን ተከትሎ በተለያየ ምክኒያት የልተሟሉ
የአደረጃጀት አመራሮችን ጨምሮ የተግባር አፈፃፀም ችግር የተየባቸዉ በርካታ ቁጥር ያላቸዉ አመርሮችን
በግምባር ቀደሞች የመተካት ስራ ተሰርቷል፡፡
 ግ/ቀደም አመራሮች የሚመሩ ቢሆንም የግንዘቤ ክፍተቶች ሰፊ ናቸዉ

 በአባለት መረጃ ማዘመን ተግባር ጎን ለጎን በርካተ ጉድለት የነበረባቸውን የአደረጃጀት አመራሮችን

ብቃት ባለቸዉ እንዲተኩ ማድረግ ተችሏል፡፡

 በ 3 ቱም ዙር ኮንፈረንስ አመራር የማስተካከልና የማፅደቅ ስራ ተከናዉኗል፡፡

28
6. ተግባራት በህገ -ደንብ መሰረት እየተመራ ስለመሆኑ
 በአሰራር መመሪያዉ በተለየየ ወቅት ለአባለት የአጫጭር ግዜ ስልጠናዎች ተሰጥተዋል፡፡
 በወረዳ/ከተማ አስተዳደር ደረጃ ፤ሁሉም መዋቅር ሊባል በሚችል ደረጃ የአስተባባሪ ኮሚቴ፤ የፓርቲ
አመራር ኮሚቴ አሰራሩን ጠብቆ በመደበኛነት ተግባር መገምገም፤ግ/መልስ መስጠት፤አረጃጀቶችን ጠጋ
ብሎ የሚደግፉበት ሂደት በአብዛኛዉ መዋቅሮች የተሸለ እንደሆነ ተወስዷል፡
 በመሠ/ድርጅትና ህዋሳት ደረጃ፤ ወቅቱን ጠብቆ የፓርቲና የመንግስት ተግባራትን በመደበኛነት
የመገምገም፤ግ/መልስ የመስጠት፤አረጃጀቶችን በተግባር መፈረጅ በአብዛኛዉ መዋቅር ከግዜ ወደ ግዜ
ለዉጥ የለዉ ቢሆንም ሂደቱን ወደ ዉጤት የቀየሩ መዋቅሮች ቁጥር ዉስን መሆናቸዉን መየት ተችሏል፡፡
 በ 2015 ሁሉም የፓርቲ አደረጃጀቶች የአደረጃጀት አሰራር መሰረት እንዲደራጁ በማድረግ ክፍተት
የአደረጃጀት ክፍተቶች ለማረጥበብ የሞከረዋል፡፡
 የ 135869 አባለት መረጃ በኦርኔል ተደራጅቶ በመሠ/ድና ህዋስ በመዝገብ፤ወረዳ/ከተማ

በኤከስ ኤልና ፎቶ፤በዞን በመረጃ ቋት ለማደራጀት አቅደን በመጃ ቋት 99%፤ ፎቶ 90%


ተፈፅሟል፡፡
 በአድሱ አደረጃጀት መሠ/ድርጅት 105 በመጨመር ከ 635 ወደ 740 ሲሆኑ 514 ህዋስ

በመቀነስ ከ 4281 ወደ 4795 ሃዋሳት አደራጅተናል፡፡


 የአሰራር መመሪያዉና ሌሎች ድንቦች ለአባለት ስልጠና ተሰጥቷል እስከ 11 የፓርቲ ደንቦች ወርዷል፡፡

8. አዳዲስ አባላት ማፍራት ስራን በተመለከተ፡-

በጥንካሬ

 ትኩረት በተሰጣቸው ማህበራዊ መሰረቶች ማለትም ሴቶች ፣ ወጣቶች፣ ምሁራን፣ ላይ ትኩረተረ የደረገ

ስራ ለመስራት ተችሏል፡፡

 እንደ ዞን በ 2014 ዓ.ም. መጨረሸ ከነበረን 135604 አባል ዉስጥ 10%(13560) ለመመልመል ተቅዶ

1744(1.3%) ዕጩዎችን ወደ ሙሉ አባልነት ማሸጋገር ተችሏል፤ 3009 ደግሞ በዕጩነት ላይ ያሉ ናቸዉ፡፡

 መዋቅርችን ስንመለከት፡- አ/ገበያ 42(1.2% ሆኖ 14 ከሙህራን) ፤ቅበት 38(0.9% ሆኖ 7

ከሙህራን)፤አሊቾ 250(2%ሆኖ ሙህራን የሉም)፤ላንፉሮ 122( 0.9% 17 ከሙህራን)

29
 የአድስ አባል ምልመላችን በፓርቲው አሰራር መሠረት መመልከቻ አስገብቶ፤በፕሮግራሙ አሰልጥኖ፤በቂ
ድጋፍ እየገኛ 6 ወር የዕጩነት ግዜ አጠናቆ በኮንፈረንስ የፀደቀበት መረጀ በአግባቡ አለማደረት ጉድለት፡፡

 ወደ ሙሉ አባልነት የመጡት ላይ የብልፅግና ዓላማ፤መርሆ፤ እሴት ከማስጨበጥ የህዋስና መሰረታዊ


ድርጅት አመራሮች ተከታጠይ የለማድግ ክፍተት መኖሩ፡፡

 በት/ት፤እንተርፕራይዝ፡ፐብሊክ ሰርቪስ፤ሌሎችም ግንባሮች ብዙ አባል ያልሆኑ መኖራቸዉ፡፡

 የአዳድስ አባላት ቁጥር መጨመር ከመዋጮ ጋር በማስተሳሰር ብዙ ዕጩዎች እያሉ ግዜየቸዉ አልፎም
የለማፅደቅ ችግር፡፡

 በመሠ/ድርጅትና ህዋሳት ደረጃ በ 2015 ወደ ሙሉ አባልነት የመጡትና በዕጩነት ደረጃ የሉትን መረጃ
በስም ዝርዝር ፈይል የለማድግ ችግር፡፡

9. በየደረጃ ኮር አመራር ማፍራት ስራን በተመለከተ

 ኮር አመራር ማለት በቁጥር ጥቂት ሆኖ በአመራር ልምድና ብስለት፣ ስትራቴጂክ ጉዳዮችን በቁልፍነት
ለይቶ አመራር ከመስጠትና ከፍ ያለ ሀሳብ በማፍለቅ አመራር የሚሰጥ ሀይል ሲሆን አብዛኛዉ መዋቅር ኮር
አመራር የአስተባበሪ ኮሚቴ አካትን መረጀ ብቻ የደረጃሉ፡

10.በየደረጃ ግንባር ቀደም አመራና አባላት ማፍራት ስራን በተመለከተ

 ተተኪ አመራር ማለት አሁን በየመዋቅሩ ያለውን ፑል አመራር እና ግንባር ቀደም አባላትን ያካተተ ስለሆነ
ከህዋስ ጀምሮ ከቁጥር መረጃ ባለፈ በስም ተለይቶ ድጋፍ የመደገፍና የማብቀት እና በየግዜዉ ብቃቱንም
እየመዘኑ የለመሄድ ጉደለት ይተየል፡፡
11.መረጃና ዶክመንቴሽን በተመለከተ

ሁሉንም አይነት መረጃዎችና ዶከመንቶች ዘመናዊ በሆነ መልኩ(soft and hard copy) ከማደራጀት

ወረዳ/ከተማ ፓ/ፅ/ቤቶች መሠ/ድርጅቶችን ስንመለከት

በጥንካሬ የተለዩ፡-

30
 በዞን፤ወረዳ/ከ/አስተዳደር ፓርቲ ፅ/ቤቶች ደረጃ በሁሉም ዘርፎች ሁሉም አይነት መረጃዎች በሶፍት

ኮፒ ዶክመንት ኖራቸዉን ማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን ዉስን መረጃዎችን በሀርድ ኮፒ የላደረጁ መዋቅሮች

መኖረቸዉን በመገምገም እንዲታረሙ ተደርጓል፡፡

 የመረጃ አደረጃጀት ለማዘመን በ 2015 ዓ.ም ከሌላው ግዜ በተለየ መልኩ ትኩረት በመስጠት የአባላትና

አመራሮችን መረጃ ማደራጀት የተቻለበት ነዉ

 በአጠቀለይ ወ 692 ሴ 110 ድ 802 አመራሮችን በተሻሻለው ኤክስ ኤል ፎርማት ለማደራጀት ተቅዶ

ወ 692 ሴ 110 ድ 802 (100% ) በማደራጀት ወደ መረጃ ቋት መስገባት የተቸለ ሲሆን

ሁሉንም (foto,) ተሟልቶ ወደ መረጀ ቋት ማስገባት ተችሏል ፡፡ ሌላዉ ወ 91851 ሴ 44018 ድ

135869 አባለትን በተሻሻለው ኤክስ ኤል ፎርማት ለማደራጀት ተቅዶ ወ 91171 ሴ 43599

ድ 134770 (99%) አባላትን በማደራጀት ወደ መረጃ ቋት መስገባት የተቸለ ሲሆን ከዚህ ዉስጥ ወ

84639 ሴ 37743 ድ 122382 (90%) አባላተ (foto,) ተሟልቶ ተደራጅቷል፡፡

 ከአባላት ማጥራት ስራዉ ተየያዥ መረጃዎች ከህዋስ ጀምሮ በኦርኔል የተደደረጀበት መንገድ የተሸለ

መሆኑን መገምገም ተችሏል፡፡

 በመሠ/ድርጅትና ህዋሳት ደረጀ የመረጃ ና ዶክመነቴሺን ስራአቱ በተሸለ ሁኔታ ማደረጀት የተቸለ

ቢኖሩም ቀሪ ስራዎች አሁንም እንዳሉ ተገምግሟል፡፡

በዞን ኢንስፔክሽን የታዩ ጉድለቶች ፡-


 ኢንስፔክሺን በየቸዉ 13 መዋቅሮች በመሠ/ድርጅቶችና ህዋሳት አይነቱና ጥርቱ ቢለያይም መሠረተዊ

መረጃዎች መኖራቸዉን ማየት የተቸለ ቢሆንም ቁጥራቸዉ ቀላል የልሆኑ አደረጃጀቶች የተጓደለና

የጥራት ችግር የለዉ መሆኑ ፤ አንዳንዶቹ ደግሞ ምንም አይነት መረጃ የሌላቸዉ መሆኑን በመስከ

ምልከታ ወቅት ማረጋገጥ ተችሏል፡፡

ክፍል ሁለት ሀብት ልማት እና አስተዳደር ዘርፍ የአስር ወራት የዕቅድ አፈፃፀም እና የሱፐርቪዥን ሪፖርት

31
1. የመዋጮ አቆራረጥ መመሪያዉን ተግባራዊ ከማድረግ አንጻር

በትክክል መመሪያውን ተከትሎ እየቆረጡ ያሉ ዳሎቻ ከተማ፣ጦራ

ከተማ፣ምስ/ስልጢ፣ሁለባራግ፣ሳነኩራ፣አለምገበያ፣ምዕ/አዘርነት እና ምስ/አዘርነት ሲሆኑ በከፊል መመሪያውን

እየተገበሩ ያሉ ስልጢ ወረዳ፣ቅበትና ላንፍሮ ሲሆኑ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ያላደረጉ ዳሎቻ ወረዳ ፣ሚቶ

ወረዳ፣ወራቤ ከተማ እና አሊቾ ውሪሮ ወረዳዎች ናቸው፡፡

2. ደረሰኝ ለአባሉ በወቅቱ እየደረሰ ስለመሆኑ ማረጋገጥ

ደረሰኝ በወቅቱ ከመስጠት አንጻር እስከ መጋቢት ወር ድረስ ደረሰኝ የሰጡ ዳሎቻና ምስ/ስልጢ ወረዳ፤ እስከ

የካቲት ወር የሰጡ ጦራ ከተማ፣ወራቤ ከተማና ሁለባራግ፤ እስከ ጥር ወር የሰጡ ዳሎቻ ከተማ ና ሳንኩራ፤

እስከ ታህሳስ ወር የሰጡ ስልጢ ወረዳ ና ቅበት ከተማ እስከ ጥቅምት ወር የሰጡ ሚቶና ላንፉሮ ወረዳ በዘጠኝ

ወሩ አንድ ግዜ ብቻ (የሀምሌና የነሃሴ) ደረሰኝ የሰጡ ምዕ/አዘርነትና አለምገበያ ከተማ ናቸው፡፡

ደረሰኝ ቆርጠው ለህዋስ አመራ ወይም ለሰውሃብት እያስፈረሙ የሚሰጡ ዳሎቻ ወረዳ፣ጦራ

ከተማ፣ሳንኩራና አሊቾ ሲሆኑ ሌሎች መዋቅሮች ሳያስፈርሙ የሚሰጡ ናቸው፡፡

3. በ 2013 እና 2014 ዓ.ም ለቀበሌ ተሰራጭተው ያልተመለሱ ደረሰኞችን ከማስመለስ አንጻር

በ 2013/14 ዓ.ም ለቀበሌ ተሰራጭተው ያልተመለሱ ደረሰኞች ያላስመለሱ መዋቅሮችን ስንመለከት ዳሎች

ወረዳ 6 ደረሰኝ፣ ሚቶ 2 ደረሰኝ፣ ላንፉሮ ወረዳ 7 ደረሰኝ፣ ምዕ/አዘርነት 1 ደረሰኝ፣ ምስ/አዘርነት 3 ደረሰኝ

አሊቾ 1 ደረሰኝ ያላስመለሱ ናቸው፡፡

4. የ 10 ወር የገቢ አሰባሰብ

ተ.ቁ ወረዳ/ከተማ የ 2015 ዓ.ም የ 10 ወራት የ 10 ወራት አፈጻጸም

32
አስተዳደር ገቢ ዕቅድ ዕቅድ የገቢ አፈፃጸም በፐረሰንት
1 ስልጢ 870,282 725,235 745,000 103%
2 አልቾ 734,868 612,390 607,989 99%
3 ሁልባራግ 604,797 503,997 607,017 120%
4 ሳንኩራ 600,180 500,150 566,925 113%
5 ወራቤ 545,138 454,281 409,569 90%
6 ምዕ/አዘርነት 480,744 400,620 289,622 72%
7 ላንፍሮ 470,404 392,003 411,555 105%
8 ዳሎቻ ወረዳ 456,315 380,262 386,077 102%
9 ምስ/አዘርነት 433,413 361,177 336,548 93%
10 ሚቶ 328,356 273,630 269,287 98%
11 ምስ/ስልጢ 305,535 254,612 217,025 85%
12 ቅበት 297,481 247,900 224,401 91%
13 ጦራ 297,362 247,801 239,645 97%
14 አለምገበያ 170,928 142,440 193,831 136%
15 ዳሎቻ ከተማ 175,816 146,513 146,071 100%
16 ዞን ማዕከል 460,000 383,333 349,500 91%
ድምር 7,083,754 5,903,128 5,898,379 99.9%

5. የልሳነ-በልጽግና መጽሔት ዕዳ

5.1 ቅጽ 01 ቁጥር 02 (የአንድ መጽሔት ዋጋ አስር ብር)

ተ.ቁ ወረዳ/ከተማ የተላከ የተላከው ገቢ የተደረገ ቀሪ ዕዳ ብር

አስተዳደር መጽሔት መጽሔት በብር ብር

የመጽሔት ስቀየር

ብዛት
1 ስልጢ 400 4,000 4,000 0
2 አልቾ 400 4,000 4,000 0
33
3 ሁልባራግ 350 3,500 3,500 0
4 ሳንኩራ 350 3,500 3,500 0
5 ወራቤ 300 3,000 3,000 0
6 ምዕ/አዘርነት 350 3,500 3,500 0
7 ላንፍሮ 300 3,000 3,000 0
8 ዳሎቻ ወረዳ 350 3,500 3,500 0
9 ምስ/አዘርነት 300 3,000 3,000 0
10 ሚቶ 300 3,000 3,000 0
11 ምስ/ስልጢ 300 3,000 3,000 0
12 ቅበት 300 3,000 3,000 0
13 ጦራ 300 3,000 3,000 0
14 አለምገበያ 200 2,000 2,000 0
15 ዳሎቻ ከተማ 200 2,000 2,000 0
16 ዞን ማዕከል 300 3,000 3,000 0
ድምር 5,000 50,000 50,000 0

5.2 ቅጽ 01 ቁጥር 03 (የአንድ መጽሔት ዋጋ ሃያ ብር))

ልሳነ-ብልጽግና መጽሔት ቅጽ 01 ቁጥር 03 ስርጭትና ሽያጭ መረጃ እስከ (2/09/2015 ዓ/ም)

ተ.ቁ ወረዳ/ከተማ የተላከ የተላከው ገቢ የተደረገ ቀሪ ዕዳ ብር

አስተዳደር መጽሔት መጽሔት በብር ብር

የመጽሔት ስቀየር

ብዛት
1 ስልጢ 400 8,000 0 8,000
2 አልቾ 400 8,000 0 8,000
3 ሁልባራግ 350 7,000 7,000 0

34
4 ሳንኩራ 350 7,000 7,000 0
5 ወራቤ 300 6,000 6,000 0
6 ምዕ/አዘርነት 350 7,000 0 7,000
7 ላንፍሮ 300 6,000 0 6,000
8 ዳሎቻ ወረዳ 350 7,000 0 7,000
9 ምስ/አዘርነት 300 6,000 3,000 3,000
10 ሚቶ 300 6,000 0 6,000
11 ምስ/ስልጢ 300 6,000 0 6,000
12 ቅበት 300 6,000 0 6,000
13 ጦራ 300 6,000 0 6,000
14 አለምገበያ 200 4,000 0 4,000
15 ዳሎቻ ከተማ 200 4,000 0 4,000
16 ዞን ማዕከል 300 6,000 6,000 0
ድምር 5,000 100,000 29,000 71,000

35
የሱፐር ቪዥኑ አካሄድ

የፌደራሉን መነሻ ያደረገ እና ዞናዊ ጉዳዮችን ያካተተ ቼክ ሊስት ተዘጋጅቶ ዝርዝር ኦረንቴዬሽን ተሰጥቱዋል።

ለ 13 ቱ መዋቅሮች 6 ቡድን ተመድቡዋል።

ከአንድ ቡድን 3 መዋቅር ከመያዝ ውጪ 2 መዋቅር ነው የያዙት።

መምሪያ እና ጽ/ቤት 4 ቱም መ/ድርጅቶች እና 8 ህዋሳት በ 4 የሱፐርቪዥን ቡድን ታይቱዋል።

መመሪያዎች ስለ መደራጀታቸው የመዋጮ አቆራረጥ በመመሪያው ስለመሆኑ ደረሰኝ እየደረሰ ስለመሆኑ እና


የእንስፔክሽን እና ሱፐር ቪዥን ስራዎችን ቼክ የሚያደርግ 1 ቡድን ናስር፣ዘይኔ እና ሽኩር ሁሉንም መዋቅር ዞረው
አይተዋል።

በተጨማሪ ከፌደራል ተቋም ዩኒቨርሲቲው በተመሳሳይ ታይቱዋል።

የክልል ተቋማት ተዘለው ነበር ዛሬ ማስተካከያ ተሰጥቶበት ፖሊ እና ግ/ምርምር ተገብቱዋል።

ከመረጃ ፍተሸ በተጨማሪ በያንዳንዱ መዋቅር 6 መድረኮች ተፈጥሩዋል የፓርቲ ኮሚቴ፤የህዋስ እና መ/ድርጅት
አመራር፤ የቀበሌ አመራር ፤የተመረጠች ህዋስ አባላት፤ የተውጣጣ የህዝብ ክፍል እስከ 30 የሚደርስ እና አስተባባሪ
ኮሚቴ፤የፓርቲ ኮሚቴ እና የካብኔ አባላት መድረክ ተፈጥሩዋል፡

በማዕከልም የተቋም አመራር የህዋስ እና የመ/ድርጅት አመራር እና አጠቃላይ አባላት ጋር ውይይት ተደርጉዋል፡፡

ሆስፒታሎች በሚገኙበት ከተማ /ወረዳ ፓርቲ ይታያሉ ይላል አስታንዳርድ አልተቀመጠም በቀጣይ ፈትሸን ማረም
ማብራሪያም መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡

እያንዳንዱ መዋቅር ሁለት ቀን የፈጀ ፍተሸ እና ምልከታ ተደርጎ ሶስት ቀን የሪፖርት ዝግጅት በመስጠት ሁለት ቀን
የፈጀ ዝርዝር ግምገማ ከሱፐር ቪዥን ቲሙ ጋር አድርገናል፡፡

ሁሉም መዋቅር በቀጣይ 60 ቀናት ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራባቸው እና ሊፈትሻቸው የሚገቡ ጉዳዮች

1 አደረጃጀቶችን የማዋቀር ስራችን ገና አላለቀም

 በመመሪያው መሰረት አደረጃጀቶችን ከማደራጀት አንፃር ጉድለቶች ታይተዋል። መ/ድርጅት አባላት ከ 22 እስከ
210 መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል ይህ ችግር አሁንም አልተፈታም በአንድ መሰረታዊ ድርጅት ከተባለው በላይ
አባል እና የ ታቀፉ ህዋሳት መኖራቸውን አይተናል ። ህዋሳት ብዛት ትንሹ 2 ትልቁ 6 መሆን እያለበት በዚያ መንገድ
አይደለም፤ የህዋስ አባልም ከ 11 እስከ 35 ቢልም ከተቀመጠው ቁጥር በላይ እስከ 47 የተደራጀበት ሁኔታ
አይተናል።
 የቀበሌ አስተባባሪ ኮሚቴ የቀበሌ አደረጃጀቱ ላይ ያለ የግልፀኝነት ችግር መፈታት ይኖርበታል።
 ውይይት በአደረጃጀትና አሰራር መመሪያው መሰረት እየሄደ አይደለም።
 የሪፖርት ቅብብሎሹ ችግር ያለበት ነው ህዋስ ለመ/ድርጅት መ/ድርጅት ለፓርቲ ጽ/ቤት
 የግ/መልስ፤ የደረጃ አሰጣጥ፤ የኮንፍረንስ አካሄድ፤ አባል ማድረግ ሂደቱ ወዘተ ችግር ያለበት ነው። ቀጣይ ፈትሾ
ማረም ያስፈልጋል።
 ሶስቱ ንኡስ ኮሚቴዎችን አደራጅቶ ወደ ስራ ከማስገባት አንፃር ጉድለት ያለበት ነው።

36 | P a g e
 መሰረታዊ የሆነ የዕቅድ ችግር ዕቅዱ ኮፒ ነው፤ የግለሰብ ዕቅድ የለም፤ ዕቅዱ የፓርቲ ስራወችን በተገቢው
አልያዘም፤ ዕቅዱን አባሉ አያውቀውም፤ ዕቅዱ የድርጊት መርሃ ግብር የለውም ፤ ጭራሽ ዕቅድ የሌለበትም አለ
 በሁሉም ማህበራዊ መሰረት ያሉ አደረጃጀቶችን እኩል ያለመደገፍ፣ ያለ ማደራጀት፣ ያለ መከታተል፣ የሚቀለው
ቦታ የማዘንበል ችግሮች የታዩ ሲሆን በተለየ መንገድ የት/ት ግንባር እና የእንተርፕራይዝ ግንባር የተተወ ነው።
 የከተማ ነዋሪ አደረጃትም በቂ ትኩረት አላገኘም።
 የመረጃ አደረጃጀት እና ዶክመንቴሽን በአብዛኛው በማዕከል ጽ/ቤት ደረጃ በተሸለ መንገድ ያለ ቢሆንም በህዋስ እና
መ/ድርጅት ደረጃ ችግር ያለበት ነው። የተለያዩ መ/ደርጅቶች በአንድ መዝገብ በአንድ ፋይል አመራራቸውን ያለ
ማወቅ መመሪያዎች ያለ መኖር ዕቅዶች ሪፖርቶች ቼክ ሊስቶ ሚዘና የአመራር ባንክ ወዘተ ፋይል ተሟልቶ እና
ተደረጅቶ አልተያዘም።

2 የፖለቲካ ስራ ላይ

 የውይይት አጀንዳ ያለመቅረጽ፤ ተጨማሪ ሰነድ ያለማዘጋጀት፤ የተዘጋጁ የፓርቲ ዕሳቤ ላይ፤ የአደራጃጀት እና
የአሰራር መመሪያ፤ ፕሮግራም ላይ፤ ልሳነ ብልጽግና፤ በየ ወቅቱ የሚወርዱ አጀንዳዎች ላይ በወቅታዊ የንቅናቄ
አጀንዳ እና በተቋም ስራ ላይ በወጥነት ውይይት እየተካሄደ አይደለም።
 የፖለቲካ ስርፀት ስራችን ከችግር የተላቀቀ አይደለም አሁንም ቀላል የማይባል አመራር በፖርቲው የነገበውን
አላማ፣ ለማሳካት የወጠናቸው ግቦችን፣ የፖርቲው ዕሴት፣ ስለ ፖርቲው ፕሮግራም ፣ መተዳደሪያ ደንብ፣ ስለ
አደረጃጀት እና አሰራር መመሪያ፣ ዋናዋና ጉዳዮችን እና ሜጀር ሺፍቶችን ከማወቅ እና ከመተንተን አንፃር ጉድለት
አለ።
 ህዋስ እና መ/ድርጅት የነባራዊ ሁኔታ ምንጭ እና የአመለካከት ቀረፃ እና የተግባር ማሳለጫ ቱልስ እየሆኑ
አይደሉም።
 ተገቢ የሆነ ምዘና የመመዘን እና ምዘናውን መነሻ ያደረገ የፖለቲካ የቅጣት ውሳኔ ያለ ማሳረፍ፣ የአመራር እና
የአባላት የግናባታ እና የአያዝ እንዲሁም እርምጃ አወሳሰድ ስራችን ችግር ያለበት እና በመረጃ የተደገፈ
አይደለም።
 ኮር አመራር የማፍራት አመራር ሊሆኑ የሚችሉ አባላትን ለይቶ የአመራር ባንክ የለ ማዘጋጀት ወዘተ ችግር አለ።
 በየ ወቅቱ የሚፈጠሩ አጀንዳዎችን ምንጭ ፤መንስኤ እና አሁናዊ ነባራዊ ሁኔታን ተረድቶ እና ተንትኖ እሱን
የሚመጥን ሰነድ አዘጋጅቶ የፖለቲካ ስራ ከመስራት አንፃር የጠባቂነት እና የአላካኪነት ችግር ይስተዋላል። ለምሳሌ
እንደ ዞናችን በሱፐር ቪዥኑ የተለዩ እና በስፍት የሚነሱ አጀንዳዎች

1 የግብአት እጥረት/ምርጥ ዘር እና ማዳበሪያ/

2 የኑሮ ውድነት

3 በሸገር ከተማ ዙሪያ በሚደረገው የቤት ማፍረስ የዞኑ ሚና እና ያልተገቡ ትርክቶች

4 በየ ደረጃው ያሉ ፕሮጀክቶች እና የመሰረተ ልማት ጉዳዮች

5 ሀገራዊ፤ክልላዊ፤ዞናዊ፣ ወረዳዊ እና ከተማ አስተዳደራዊ ነባራዊ ሁኔታ ላይ በየ ደረጃው ካለው አመራር ፤ አባል እና
ህዝቡ ጋር የምናደርገው ውይይት ጥራት ያለው እና የተግባባንበት ነው ብሎ መውሰድ አይቻልም።

6 በአጠቃላይ እንደ ሀገር፤ክልል፤ዞን እና ወረዳ/ከተማ አስተዳደር ላይ በሚፈጠሩ ሰው ሰራሽ ፣ ተፈጥሮዋዊ ፈተናዎች


እና ተግዳሮቶች እንዲሁም በሚዲያዎች እና በአፍራሽ ሀይሎች ፕሮፖጋንዳ በሚለቀቁ አሉ ባልታዎች ወዘተ ውስጣዊ
እና ውጫዊ የፓርቲውን ፈተናዎች በውል ተረድቶ ችግሮችን በሙሉ ውጫዊ ሳያደርጉ እና ሳያላክኩ ብልጽግና ሆኖ
በመርህ ላይ ቆሞ የማስረዳት እና የመፍታት ጉድለትን ማረም ያስፈልጋል፡፡

37 | P a g e
3 ከሰው ሀብት እና የፋይናንስ አስተዳደር ስራችን

 የመዋጮ አቆራረጡ መመሪያነ ደንቡን ተከትለው የማይቆርጡ 4 መዋቅሮች ዳሎቻ ወረዳ፣ሚቶ ወረዳ፣አልቾ ወረዳ
እና ወራቤ ከተማ አስተዳደር ሲሆኑ አቆራረጥ ላይ የወጥነት ችግር ያለባቸው እና ቡራቡሬ መዋቅሮች ስልጢ፣ ቅበት
እና ላንፉር ሲሆኑ ሌሎች ቀሪ 8 መዋቅሮች በአሰራሩ መሰረት የሚቆርጡ ናቸው። ሁሉም መዋቅር መፈተሽ እና
ማጥራት ያለበት በየ ግዜው አብዴት እየተደረገ እየተስተካከለ አለመሆኑን በአባላት ቅሬታም ይነሳል የኛ ምልከታም
ተመሳሳይ ደሞዝ ኖሮት 75 ብር 16 ብር የሚቆረጥበት ሁኔታ ማየት ተችሉዋል።
 አልቾ ደግሞ ከ ግሮስ ነው የሚቆረጠው
 ለአባላት ደረሰኝ እንዲደርስ ከማድረግ አንፃር ከመዋቅር መዋቅር የሚለያይ ቢሆንም ችግር ውስጥ ያሉ እና 1 ብቻ
የሰጡ ምዕራብ አዘርነት እና አለም ገበያ ናቸው
 የተቆረጠ ገንዘብ በየ ወሩ ተቆርጦ ከመላክ አንፃር የ 9 ኝ ወሩን ስናይ የ 5 ወር ባለ ማስገባት መሪው ምዕራብ አዘርነት
ሲሆን ሚቶ የ 3 ወር ባለ ማስገባት ይከተላል ሳንኩራ የ 2 ወር አላስገባም የአንድ ወር ያላስገቡ አልቾ፣ ጦራ፣
ላንፉሮ፣አለም ገበያ እና ዳሎቻ ከተማ ናቸው።
 የአምና ካርኒ ያላስመለሱ መዋቅሮች ዳሎቻ ወረዳ 6 ሚቶ 2 ላንፉሮ 7 ምስ/አዘርነት 3 ምዕ/አዘርነት 1 እና አልቾ
1 ናቸው።
 የልሳነ ብልጽግና መጽሄት ሁለተኛ ዙር ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ገቢ ያደረጉ ሶስት መዋቅሮች ሁልባራግ፣ሳንኩራ እና
ወራቤ ሲሆኑ ምስ /አዘርነት ግማሽ ገንዘብ አስገብተዋል ሌላው መዋቅር በሙሉ ያላስገቡ ናቸው።
4 የፓርቲ ስራዎች ላይ ያለ የድጋፍና ክትትል ስራን በተመለከተ

 ወጥ በሆነ መንገድ ፓርቲ ተክሎ አንድም አባል እና አደረጃጀት ከዕቅድ፤ ከውይይት ፤ ከሪፖርት ፤ከግ/መልስ ፤
ከደረጃ፤ ከመዋጮ መቁረጥ ፤ ከአባላት ማፍራት እና ከኮንፍረንስ ውጪ መሆን የለበትም ብሎ ተተክሎ ከመስራት
አንጻር ጉድለት ያለበት ነው
 ሶስቱን መስተጋብሮችን ዕቅድና ሪፖርት፤ ግምገማ እና ግ/መልስ፤ ምዘና እና ደረጃን ተክሎ ያለመሄድ ጉድለት አለ
 የፓርቲ የበላይነት እና መሪነትን ያለ ማረጋገጥ ተግባራትን በአደረጃጀት ያለ መምራት የሚሰሩ ሁሉም የልማት
ስራዎች ከፓርቲያችን ዕሳቤ አንጻር ምን ማለት እንደሆነ ያለመረዳት እና ከዕሳቤያችን አስተሳስሮ ያለ ማንሳት
አንዳንድ መዋቀሮች የፓርቲን ስራ በሙሉ ወደ ጎን በመተው የመንግስት ስራዎች ላይ ስምጥ ብሎ የመግባት እና
በድጋፍና ክትትል ያለ ማውጣት ችግር
 ጠንካራ የኮ/ፖስት ስርአት ያለመትከል
 የውሸት ሪፖርት ቀምሞ የመስጠት እና እሄን በድጋፍና ክትትል ያለ ማጋለጥ

በመምሪያና ጽ/ቤት

ከአደረጃጀት አንጻር የህዋስ ብዛትን ማየት ያስፈልጋል 11 9

የዕቅድ ችግር አለ ኮፒ ፔስት ነው የግለሰብ ዕቅድ በተሙላ መንገድ የለም

የተሙላ ውይይት እና ሪፖርት የለም

የአባላት የፖለቲካ ስራ ላይ፤ ፕሮግራሙን ከማወቅ ዕሳቤዎችን ከማስረጽ አንጻር ጉድለቶች አሉ

የመረጃ ችግር ፤የድጋፍ ችግር፤ የአመለካካት ችግር በተለይ ት/ት ቴክኒክ

38 | P a g e
ችግሮችን ውጫዊ የማድረግ፤ ፓርቲውን የመተቸት፤ አልቻለም ይልቀቅ የኑሮ ውድነት ተረኝነት አለ ጦርነቱ ትክክል
አልነበረም ኤሄ ሁሉ ሰው አልቆ ለምን በዚህ መንገድ ተፈታ፤የኑሮ ውድነት እያለ እንዴት ላወያይ ወዘተ

አመራሩ ተገኝቶ ያለ ማወያየት እና አመለካከት ያለ መስበር ጉድለት መኖሩ

 በታየው እንስፔክሽን የ መዋቅሮች ሁኔታ

የተሸሉ፡- ስልጢ፤ሁልባረግ ላንፉሮ፤ አለም ገበያ ፤ምስራቅ አዘርነት፤ ምስራቅ ስልጢ

መሀከለኛ፡-ምዕራብ አዘርነት ፤ዳሎቻ ወረዳ፤ ዳሎቻ ከተማ፤አልቾ፤ቅበት፤ ጦራ

ዝቅተኛ፡- ሚቶ

ከመምሪ እና ጽ/ቤት

 ማህበራዊ መሰረታዊ ድርጅት ዝቅተኛ ነው


 አስተዳደራው መሰረታዊ ድርጅት መሀከለኛ
 ኢኮኖሚያወ መ/ድረጅት 1 እና ሁለት የተሸሉ ናቸው

ችግር ውስጥ የገቡ ህዋሳት

 ት/ት
 ቴክኒክና ሞያ
 ውሃ እና ሚሊሻ ሲሆኑ
 መሀከለኛ ያሉ
 አስተዳደር እና እንቨስትመንት
 የተሸሉ ህዋሳት
 ፋይናንስ እና
 ንግድ ናቸው

 ከሸገር ከተማው ቤት ማፍረስ ሁሉም ጋ ቢኖርም በደንብ መወያየት የሚያስፈልገው አልቾ/ከጉራጌ/፤


ምስራቅ/የድንበር እሹ ከሁልባራግ ከሀዲያ እና ከጉራጌ/፤ምዕራብ ስፋት አለው
 ከመሰረተ ልማት ምስራቅ በተለይ ዩሮ አፕ ላይ አልቾ ከቦዠባር ሳንኩራ ረግዲና ማዞሪያ የሚነሱ ጉዳዮች
 ሁሉም መዋቅር ግን መወያየት እና መግባባት ያለበት በግብአት አቅርቦት ዙሪያ፤ በሸገር ከተማ ቤት መፍረስ ላይ፤
በኑሮ ውድነት ዙሪያ በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ በፕሮጀክቶች ዙሪያ፤ በስርቆት እና ሌብነት ዙሪያ

39 | P a g e

You might also like