Professional Documents
Culture Documents
ም
ክፍል አንድ፡
መግቢያ፣ ማኑዋሉ አስፈላጊነት፣ የማኑዋሉ ዓላማ፣ የማኑዋሉ
ይዘቶች፣ የተፈጻሚነት ወሰን፣ የማኑዋሉ አጠቃቀምና የሚጠበቁ
ውጤቶች
ክፍል ሁለት
የለውጥ ሥራ አመራር መሳሪያዎች ጽንስ ሃሳባዊ ማዕቀፍ
ክፍል ሶስት
ስትራቴጂን ወደ ፈፃሚ አካላት የማውረድ ምንነት እና የማውረጃ
ዘዴዎች
ክፍል አራት
የሚዛናዊ ስራ አመራርና ምዘና ሥርዓት የትግበራ ደረጃዎች /Steps/
እና የአተገባበር ሞዴል /Template/
2
መግቢያ
በከተማችን በየደረጃው በሚገኙ ተቋማት ተግባራዊ
ሲደረግ የቆየው የለውጥ ስራ ተስፋ ሰጪ ጅምር ዉጤት
ያስገኘ ቢሆንም በሚፈለገው ደረጃ ስር-ነቀል ተቋማዊ
ለውጥን ማረጋገጥ አልተቻለም፡፡
ስለሆነም በከተማችን ልማት እና መልካም አስተዳደርን፣
የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታን ለማጎልበት እና አገራዊ
ራዕይ እዉን ለማድረግ ስትራቴጂያዊ ጉዳዮችን በቅደም
ተከተል በማስቀመጥ እና ሁሉም ባለድርሻ አካላት
እንዲግባቡበት በማድረግ ስር ነቀል ተቋማዊ ለዉጥ
የማረጋገጥ ጥረት አጠናክሮ መቀጠል ያስፈልጋል፡፡
3
በተለይም የBSC ስርዓትን በተሟላ መልክ ለመፈጸም ከደረጃ ሰባት እስከ
ዘጠኝ ባሉት የትግበራ ደረጃዎች የአፈፃፀም ችግሮች ተስተውለዋል፡፡
• በደረጃ ሰባት የስኮር ካርዱን ዕቅድና ሪፖርት አውቶሜት አድርጎ ቀጣይነት ባለው
መልኩ ተግባራዊ ያለማድረግ፣
• በደረጃ ስምንት ስኮር ካርዱ ኬዝ ቲም ላይ ብቻ ተንጠልጥሎ መቅረቱና እስከ
ፈፃሚ ግለሰብ ካስኬድ አለመደረጉ፣
• እንዲሁም በደረጃ ዘጠኝ የምዘና ስርዓቱ በማዕከል ደረጃ እስከ ስራ ሂደት፤ በክፍለ
ከተማና በወረዳ ደረጃ እንደ ጽ/ቤትና በትምህርትና በጤና ተቋማት እንደ ተቋም
ብቻ የሚካሄድና እስከ ግለሰብ ድረስ ያልወረደ መሆኑ እና የዕውቅናና ሽልማት
ስርኣቱም ከምዘናው ውጤት ጋር በማያያዝ በመመሪያ የተደገፈ አልነበረም፡፡
በመሆኑም ይህንን የማስተግበሪያ ማኑዋል ለማዘጋጀት በሚዛናዊ ስራ አመራር
ስርዓት የተሻለ ተሞክሮ ካላቸዉ ከከተማ ልማት፣ ቤቶች እና ኮንስትራክሽን
ሚኒስቴር እንዲሁም ከፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽ/ቤት ተሞክሮ
ለመዉሰድ ተችሏል፡፡ በዚሁ መሰረትም ከከተማ ልማት፣ ቤቶች እና
ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የተገኘዉ ልምድ እንዴት ስኮር ካርዱን እስከ ግለሰብ
ድረስ ማዉረድ እንደሚቻል የተወሰደ ሲሆን ከፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና
ምዝገባ ጽ/ቤት የግለሰብን የእለት ተዕለት አፈጻጸም እንዴት ኦቶሜት ማድረግ
እንደተቻለ በተሞክሮ ተወስዷል፡፡
4
የከተማአስተዳደሩ ቀልጣፋና ውጤታማ የአሰራር
ስርዓቶችን በመዘርጋት የተለያዩ የለውጥ
መሳሪያዎችን አቀናጅቶ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡
ይህንንም ስራ ውጤታማ በሆነ መልክ ለመምራትና
ለመፈጸም እንዲሁም ግቦችንና ስትራቴጅን ወደ
ፈጻሚ አካላት የማውረዱን ስራ በተገቢው ቅደም
ተከተል ግልጽነትና ተጠያቂነት ባለው መልኩ
ለማከናወን የሚያሥችል የማስፈጸሚያ ማኑዋል
ባለመኖሩ የማኑዋሉን ዝግጅት አስፈላጊ ያደርገዋል፡፡
5
የዚህ ማኑዋል ዋና ዓላማ ከላይ እስከታች
በአስተዳደሩ ስር ያሉ ሴክተሮች በሚዛናዊ ሥራ
አመራርና ምዘና ስርዓት የተጣሉ ግቦችን በየደረጃው
ለሚገኙ ፈጻሚ አካላት በተሟላ ሁኔታ ማውረድ
የሚቻልበትን ስርዓት በመዘርጋት ለአፈጻጸም
ክትትል፤ ግምገማና ምዘና ስራ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር
ነዉ፡፡
6
ዝርዝር ዓላማዎች
ስትራቴጂን ወደ ፈጻሚ አካላት ማውረድ( cascading) ምንነት
እና በጽንሰ ሃሳቡ ዙሪያ ግንዛቤ በማዳበር የማንዋሉን አጠቃቀም
ቀላል ለማድረግ፤
ግቦችንና ስትራቴጂዎችን በየደረጃው ለሚገኙ ፈጻሚ አካላት
የማውረድ እና የምዘና ስራውን ውጤታማ በሆነ መልክ
ለመምራት/ለማካሄድ፤
የካስኬዲኒግ ስራ በተለያዩ ተቋማት ሊከናወን የሚችል በመሆኑና
እንደ ተቋሙ ግንዛቤ፤ ደረጃና የአጠናን ዘዴ የሚለያይ ስለሚሆን
ወጥ የሆነ የአሰራር ስርዓት ለመከተልና የተቀላጠፈ አሰራር
ለመፍጠር፤
የካስኬዲኒግን የአሰራር ሂደት የአንድ የስራ ሂደት ግቦች በመውሰድ
እንዴት እስከ ግለሰብ ፈጻሚ ሊወርድ እንደሚችል በምሳሌ
በማሳየት በከተማው አስተዳደር ስር በሚገኙ ተቋማት
የሚደራጀው የካስኬዲንግ ቡድን ይህን ተከትሎ ስራውን
እንዲያከናውን ለማስቻል ነው፡፡
7
የለውጥ ሥራ አመራር መሳሪያዎች (BPR እና BSC ) ላይ ያለው
ግንዛቤ ይዳብራል፤
ሰራተኞች ስለ ተቋማቸዉ ራዕይ፤ ተልዕኮ፤ እሴቶችና
ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ግንዛቤ ይኖራቸዋል፤
በአቅም ግንባታ ቢሮ በስራ ሂደት ደረጃ ከተዘጋጀው ካስኬዲንግ
ሞዴል በመነሳት ሌሎች በየደረጃው የሚገኙ ሴክተር ቢሮዎች፣
ተቋማት፣ ግቦቻቸውንና ተግባሮቻቸውን ለፈጻሚዉ ካስኬድ
የማድረጉን ስራ ያከናዉናሉ፤
ፈጻሚዎች በተቋማቸዉ እና በግለሰብ ደረጃ የተቀመጡትን
ግቦች በመረዳት ለግቦቹና ለዒላማዎች መሳካት ያላቸው
አስተዋጽኦ ያድጋል፤
ስትራቴጂ ተኮር ተቋማት (Strategy Focused
Organizations) እና ለውጤት የሚሰሩ ሰራተኞች ይፈጠራሉ፡፡
8
የተፈጻሚነት ወሰን
በዚህ ስትራቴጂን እስከ ግለሰብ የማውረጃ እና ማስተግበሪያ ማኑዋል
መሰረት የሚዛናዊ ስራ አመራር እና ምዘና ስርዓት አጥንተዉ ወደ ትግበራ
የገቡ በከተማ አስተዳደሩ ስር ያሉ ተቋማት እና ፈጻሚዎች ይጠቀሙበታል፡፡
የማኑዋሉ አጠቃቀም
ይህ ማኑዋል በሚዛናዊ ሥራ አመራርና ምዘና ስርዓት ጥናት
የተለዩትን ግቦችና ስትራቴጂዎች እንዴት ወደ ፈጻሚ አካላት
ማውረድ እንደሚቻል በምሳሌ (Template) በማስደገፍ እና
የተለያዩ የለውጥ ስራ አመራር መሳሪያዎችን አንድነትና ልዩነት
በማስቀመጥ በተገቢ ማብራሪያዎች በመደገፍ በቅደም ተከተል፤
ግልጽና ለአጠቃቀም ቀላል በሆነ መልኩ የቀረበ በመሆኑ ማንኛውም
የካስኬዲንግ ሥራ እንዲያከናውን የተመደበ ቡድን ተረድቶት
የካስኬዲንጉን ሥራ ማከናወን እንዲያስችለው ተደርጎ የተዘጋጀ ነው፡፡
9
ይህ ማኑዋል አራት ክፍሎች ያሉት ሲሆን ፤ ክፍል አንድ መግቢያ፤
ዓላማ፤ የሚጠበቁ ውጤቶች፤ የተፈጻሚነት ወሰንና የማኑዋሉ
አጠቃቀም የሚሉ ይዘቶች ሲኖሩት፤ ክፍል ሁለት የለውጥ ሥራ
አመራር መሳሪያዎች ትርጓሜና አጠር ያለ ጽንሰ ሀሳብ የያዘ
ሲሆን ይህም በስራ አመራር መሳሪያዎቹ ዙሪያ ያለውን ብዥታ
በማጥራት ግልጽነትና የጋራ ግንዛቤ እንዲኖር በማስቻል
የማኑዋሉን ዝግጅት ለመምራት ያስችላል ተብሎ የተካተተ ነው፡፡
ክፍል ሦስት የካስኬዲንግን (ግቦችንና ስትራቴጂዎችን ወደ ፈጻሚ
አካላት ማውረድ) ምንነትና የማውረጃ ዘዴዎች በንድፈ ሃሳብ
ደረጃ የሚተነትን ሲሆን ክፍል አራት ዋናው የማኑዋሉ አካል
በመሆኑ በከተማችን የሚዛናዊ ስራ አመራርና ምዘና ሥርዓት
ለመዘርጋት መከተል የሚገባንን የአሰራር ሂደት ቅደም ተከተል
በምሳሌነት አንድ የስራ ሂደት በመውሰድ የሚተነትን ነዉ፡፡
10
ሀ. መሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ /BPR/
መሠረታዊ የአስተሳሰብ ለውጥ በማምጣት ስርነቀል የአሰራርና
የአደረጃጀት ስርዓት በመዘርጋት አገልግሎቶችን በተመጣጠነ ወጪ፣
ጥራት፣ መጠንና ፍጥነት በማቅረብ እመረታዊ የአፈጻጸም ለውጥ
ለማምጣት የሚያስችል የሥራ አመራር መሳሪያ ነው፡፡
ለ. የሚዛናዊ ሥራ አመራርና ምዘና ስርዓት /BSC/
የሚዛናዊ ሥራ አመራርና ምዘና ስርዓት ማለት የተቀናጀ
የስትራቴጂያዊ እቅድ ሥራ አመራር፤ የተግባቦትና የአፈጻጸም
መለኪያ ስርዓትን አጣምሮ የያዘ የለውጥ መሳሪያ ነው፡፡ ሚዛናዊ ስራ
አመራር ስርዓት ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር፣ እነዚህን
ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ለመተግበር የሚያስችሉ ግቦችን ለይቶ
የሚያስቀምጥ፣ ግቦቹ በምክንያትና በውጤት ተሳስረው እንዴት
እሴት እንደሚፈጥሩ የሚያሳይ፣ የተቋምን ስኬት እንዲያረጋግጡ
የተቀረጹ ግቦች እንዴት እንደሚለኩ የሚያሳይና ለግቦች
የተቀመጠላቸውን ዒላማ ለማሳካት የሚያስችሉ ስትራቴጂያዊ
እርምጃዎች የሚቀረጹበትን አግባብ የሚያስቀምጥ የለውጥ
መሳሪያ ነው፡፡
11
በተለያዩ የሥራ አመራር ምሁራን እንደተገለጸው ለሁሉም ተቋማዊ የአሠራር
ችግሮቻችን ምላሽ የሚሰጥ አንድና የተዋጣለት ብቸኛ የሥራ አመራር
መሳሪያ እንደሌለ ነው፡፡ እያንዳንዱ የሥራ አመራር መሳሪያ የራሱ የሆኑ
መሠረታዊ መነሻ፣ ይዘትና ባህርይ ያለው በመሆኑ በአንድ ተቋም ውስጥ
የሚገኙትን ዘርፈ ብዙ ችግሮች በተሟላ ደረጃ ለማቃለልና ለመፍታት የራሱ
እጥረት/ውስንነት ይኖረዋል፡፡ ከዚህ እውነታ መገንዘብ የሚቻለው ብቸኛ
የሆነ የሥራ አመራር መሳሪያ ይዞ ውጤታማ መሆን እንደማይቻል ነው፡፡
በመሆኑም እንደተቋማዊ የአሠራር ችግሮቻችን ዓይነትና ብዛት እንዲሁም
ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ መሠረት በማድረግ የተለያዩ የለውጥ ሥራ አመራር
መሳሪያዎችን አቀናጅቶ መጠቀም የበለጠ ውጤታማ ሊያደርግ እንደሚችል
በግልጽ መረዳት ይቻላል፡፡
በልምድ ልውውጥ ወቅት የተመለከትናቸው ተቋማት የተጠቀሟቸው የሥራ
አመራር መሳሪያዎች እንደሚያመለክቱት መሳሪያዎቹ ዕርስ በዕርሳቸው
እንዲደጋገፉ በማድረግ ወይም በማቀናጀት መጠቀማቸው
ለውጤታማነታቸው ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳደረገ ለመረዳት ተችሏል፡፡
በተመሳሳይ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዋማት ከፍ ብሎ የተገለጹትን የለውጥ
ሥራ አመራር መሳሪያዎች ከራሱ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማጣጣም በተሟላ
መልኩ አቀናጅቶ መጠቀም ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡
12
በሚዛናዊ ስራ አመራር ሥርዓት የግንባታ ደረጃዎች ሥራ ከተጠናቀቀ
በኋላ የተዘጋጁትን ግቦችና ስትራቴጂዎች ተግባራዊ የማድረግ ሥራ ቀጣዩ
አብይ ተግባር ነው፡፡ በተለይ ደረጃ ስምንት/Cascading/ ከፍተኛ ግምት
የሚሰጠው ተግባር ይሆናል፡፡
1. ስትራቴጂን ወደ ፈጻሚ አካላት የማውረድ ምንነት
ስትራቴጂን በየደረጃው ላሉ አካላት ማውረድ ሲባል የተቋሙን
ስትራቴጂ ሁሉም ፈፃሚ አካላት ተገንዝበውት የዕለት ተዕለት ሥራቸው
እንዲያደርጉት ማስቻል ነው፡፡
በየደረጃው የሚገኙ አካላት ለስትራቴጂው ስኬታማነት የበኩላቸውን
ድርሻ ሊያበረክቱ ይችሉ ዘንድ ስለስትራቴጂው ሙሉ ግንዛቤ መፍጠርን፣
ስትራቴጂውን ሲወስዱ ስትራቴጂያዊ ትስስሩን ጠብቀው
ለስኬታማነቱም ከፍተኛ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ መሆናቸውን ማረጋገጥ
ያጠቃልላል፡፡
ስትራቴጂ በየደረጃው ላሉ አካላት የሚወርደው በስትራቴጂያዊ ግቦች
አማካይነት ነው፡፡ ስትራቴጂን የሚያወርደው አካል /የካስኬዲንግ ቡድን/
የተቋሙን ስትራቴጂያዊ ግቦች መሠረት በማድረግ ለሚያዘጋጃቸው
ግቦች መለኪያዎችን፣ ዒላማዎችንና እንዳስፈላጊነቱ ስትራቴጂያዊ
እርምጃዎችን ማዘጋጀት ይኖርበታል፡፡
13
የተቀረጹትን ስትራቴጂዎች ወደ ፈፃሚ አካላት ማውረድ
ስትራቴጂዎቹን ስኬታማ ለማድረግ ወሳኝ ነው፡፡ ይኸውም፡-
የተቋሙን ራዕይ የጋራ በማድረግ ስትራቴጂውን በየደረጃው
የሚገኙ ፈፃሚዎች የዕለት ተዕለት ተግባር እንዲያደርጉት፣
ስትራቴጂ ተኮር የሆነ የሥራ ባህል ለመገንባትና እያንዳንዱ
ፈፃሚ አካል የመጨረሻውን ተቋማዊ ውጤት እያሰበ
እንዲሰራ ለማድረግ፣
ማበረታቻና ሽልማትን ከስትራቴጂያዊ ውጤት ጋር
ለማያያዝና ሠራተኞች ውጤት ባመጣ ምን አገኛለሁ /
what is in it for me? / በማለት ለሚያነሱት ጥያቄ
ምላሽ ለመስጠት፤
የተቋሙን ስትራቴጂ በመመንዘር በየደረጃው ካሉ ግቦችና
መለኪያዎች ጋር እንዲተሳሰሩ ለማስቻል፡፡
14
በተቋም ደረጃ የተዘጋጀን ስትራቴጂ በየደረጃው ለሚገኙ ፈፃሚ
አካላት ለማውረድ በሚከተሉት ተያያዥነት ባላቸው ሶስት ዘዴዎች
መሰረት ይወርዳል፡፡ እነዚህም ስትራቴጂውን ማስረጽ /Spiritual
Cascading/፣ ግቦችን ለፈፃሚ አካላት ማውረድ /Physical
Cascading/ እና ውጤትን ከሽልማት ጋር ማያያዝ /Reward/
በመባል ይታወቃል፡፡
ሀ. ስትራቴጂውን ማስረጽ ወይም የትምህርትና ተግባቦት ሥራ
በየደረጃው የሚገኙ አካላት በሴክተሩ እና በተቋሙ ደረጃ
የተዘጋጁትን ስትራቴጂዎችንና ስለስትራቴጂዎቹ አዘገጃጀት
አስፈላጊውን መረጃና ትምህርት በመስጠት ጠለቅ ያለ ውይይት
በማካሄድ ስትራቴጂውን በእምነት፣ በዕውቀትና በባለቤትነት ስሜት
ካልተቀበሉት ሥራዎችን ቆጥረው ቢወስዱም እንኳ በተሳካ ሁኔታ
ይፈጽሙታል ለማለት ያስቸግራል፡፡ በመሆኑም የተቋሙን ራዕይና
ስትራቴጂ በሠራተኞች ዘንድ ማስረጽ የለውጥ ሃይሎችን
ለማፍራት እና ለመጠቀም የሚያስችል ስትራቴጅን ወደ ፈጻሚ
አካላት የማዉረጃ ዘዴ ነዉ፡፡
15
በሚዛናዊ ስራ አመራር ሥርዓት ትምህርትና ተግባቦት ማለት
የባህሪ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል ግንዛቤን ለመፍጠር
የሚረዱ ጭብጦችን በጹሁፍ፣ በስብሰባ እንደዚሁም በተለያዩ
የመገናኛ ዘዴዎች ማስተላለፍ ነው፡፡ የተግባቦት ሥራው ሥርዓቱ
ለምንና እንዴት እንደሚተገበር ማሳወቅን፣ በዕቅዱ የሚፈቱ
ችግሮችን፣ በሥራ አመራር ሂደትና በሠራተኛ አስተዳደር ረገድ
ዕቅድ የሚኖረውን ፋይዳ እና ተቋሙ ሊያመጣ የሚገባውን ለውጥ
ለመላው ፈፃሚ ኃይል ማሳወቅን ያጠቃልላል፡፡ በተጨማሪም
የሚከተሉትን የተግባቦት ሥራዎች በየወቅቱ ማከናወን
ያስፈልጋል፡፡
ስኬትን ማብሰር
የአፈፃፀም ውጤት ማሳወቅ
ይህንንም ለማድረግ፡-
16
i. መሰረታዊ የስትራቴጂያዊ አቅጣጫዎችን መወሰን
ተቋማት ስትራቴጂያቸውን በተቀናጀና በተጣጣመ መልኩ
ለማሳካት ይችሉ ዘንድ ከፈፃሚዎቻቸው፣ ከተገልጋዮቻቸውና
ከባለድርሻ አካላት ጋር የትምህርትና ተግባቦት ስራ
የስትራቴጂያዊ አቅጣጫዎችን ወስነው መስራት ይገባቸዋል፡፡
ለዚህም ይረዳ ዘንድ የሚከተሉትን ማከናወን ተገቢ ይሆናል፡፡
የአመለካከት ክፍተቶችን መለየትና መሙላት፣
የሠራተኛውን የስራ ተነሳሽነትና ዝግጁነት ማሻሻል፣
በለውጥ መሳሪያዎች ዙሪያ የፈፃሚዎችንና ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ
ማሳደግ ፣
የክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ አሰራርን አጠናክሮ መቀጠል፣
የመረጃ አገልግሎት ስርዓት ማሻሻል፣
የቡድን ስራ ባህል ማሻሻል፣
የICT አጠቃቀምን ማሳደግ፣
የፈፃሚውን አቅም ማሳደግ፣
17
ii. ስልቶችን መንደፍ
የተግባቦት ስልቶች የሚባሉት ፈፃሚውን
ይበልጥ ግልጽ አድርጎ ለማሳመን የሚያገለግሉ
ውጤታማዎቹ መልዕክት ማስተላለፊያ ዘዴዎች
ናቸው፡፡ በመሆኑም በዕቅድ ዝግጅት ላይ ብቁ
ስልቶች በመንደፍ በዋነኛነት ፈፃሚውን
በማሳወቅ፣ በማሳመንና ወደ ተግባር ሊያስገባ
የሚያስችል ስልት የመንደፍ ጉዳይ ነው፡፡
የውይይት መድረክ ዝግጅት
የጉብኝትና ተሞክሮ ልውውጥ ዝግጅት
ፖስተሮች
የድህረ-ገጽ አገልግሎት
መጽሔት
18
ለ. ግቦችን የማከፋፈል ሥራ (Physical Cascading)
ግቦችን ለፈጻሚ ማከፋፈል በዋናነት በሁለት ደረጃዎች
የሚከናወን ይሆናል፡፡
ለሥራ ሂደቶች እና ኬዝ ቲሞች ማውረድ
ሁለተኛው ለግለሰብ ፈፃሚዎች ማውረድ ነው፡፡
የተቀረፁ ግቦችን መሰረት በማድረግ እንደተቋሙ
ተጨባጭ ሁኔታ የሚወሰን የካስኬድንግ ቡድኖችን
ማደራጀት ያስፈልጋል፡፡ የካስኬድንግ ቡድኑ ስትራቴጂውን
የእያንዳንዱ ፈፃሚ አካል የዕለት ተዕለት ተግባር ለማድረግ
በሚያስችል መንገድ ሊደራጅና ሊሰራ ይገባል፡፡
ስትራቴጂውን ወደ ፈፃሚ አካል የማውረድ ኃላፊነት
በዋናነት የእያንዳንዱ የሥራ ሂደት ሲሆን አጠቃላይ
የማውረድ ሥራው ከተቋሙ አመራር ጋር በመሆን
የሚሰራ ነው፡፡
19
i. ለሥራ ሂደቶች እና ኬዝ ቲሞች ማውረድ
በሴክተር ቢሮ ደረጃ የተዘጋጁት ስትራቴጂያዊ ግቦች ትስስሩን /Alignment/
በጠበቀና ባጣጣመ መልኩ ለስራ ሂደቶች እና ኬዝ ቲሞች መዉረድ አለባቸዉ፡፡
በስራ ሂደት ወይም በኬዝ ቲም ደረጃ የሚቀረጹ ግቦች የተቋሙን ስትራቴጂያዊ
ግቦች የማስፈጸም ወይንም የመደገፍ ሚና ይኖራቸዋል፡፡ ይህ ስትራቴጂያዊ
ዕቅድም ወደ ዓመታዊ የአፈፃፀም ዕቅድ የሚመነዘር መሆን ይኖርበታል፡፡
i i. ለግለሰብ ፈፃሚዎች ማውረድ
ግለሰብ ፈፃሚዎች በኬዝ ቲም ደረጃ የተቀመጡትን ግቦች መነሻ በማድረግ
የራሳቸውን ዕቅድ ያዘጋጃሉ፡፡ በግለሰብ ፈፃሚ የሚዘጋጀው ዕቅድ የሚከተሉትን
ሊያካትት ይገባል፡፡
ፈፃሚ ግለሰቡ የሚሰራበት ቢሮ /የስራ ሂደት/ የቀረጻቸውን ግቦች ያሳካ
ዘንድ ከግለሰቡ የሚጠበቀውን አስተዋጽኦ፣
በቢሮ //የስራ ሂደት/ ወይም በተቋም ደረጃ የተቀመጡ ስትራቴጂያዊ
እርምጃዎች /ልዩ ኘሮጀክቶች እንዲፈጸሙ ለግለሰቡ ሊሰጥ የሚችለውን
ሃላፊነት፣
የግለሰቡን አቅም ለማሳደግ ግለሰቡ ከራሱ የሚጠበቁ የአቅም ግንባታ
ሥራዎች /Self Development Plan/ ዕቅድ ሊይዝ ይገባል፡፡ ይህም
ግለሰብ ፈፃሚዎችን የማብቃት ዕቅድ በኮምፒውተር አጠቃቀም፣ ዕቅድ
አዘገጃጀት፣ ሪፖርት አፃፃፍ፣ ወዘተ ዙሪያ ሊሆን ይችላል፡፡
20
የግለሰብ ፈፃሚዎች ዕቅድ ከተቋሙና ከስራ ሂደቱ
ስትራቴጂ ጋር ተናቦ መዘጋጅቱ የሚከተሉት
ጠቀሜታዎች ይኖሩታል፡-
ስለ ስትራቴጂው በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸውና
ለተግባራዊነቱ በተነሳሽነትና በቁርጠኝነት እንዲንቀሳቀሱ
ያስችላቸዋል፤
ግለሰቦች ዕቅዳቸውን ሲያዘጋጁ የተቋሙና የሥራ
ክፍላቸው ውጤት ተኮር ዕቅዶች ያላቸውን ትስስር
አጥርተው እንዲያዩትና እንዲፈጽሙት ይረዳቸዋል፤
እያንዳንዱ ፈፃሚ/ግለሰብ ከስትራቴጂው አንፃር እሴት
21
ሐ. ውጤትን ከእውቅናና ሽልማት ጋር ማያያዝ (Recognition and
Reward)
ማበረታቻን /እውቅናና ሽልማት/ ከውጤት ጋር ማያያዝ
የተቋሙ ስትራቴጂ በሠራተኞች ዘንድ ትኩረት
እንዲያገኝና ተግባራዊ እንዲሆን ያስችላል፡፡
የሚዛናዊ ስራ አመራር ስርዓት የአሠራር ባህልን የመቀየር
ዓላማ ያለው እንደመሆኑ መጠን ማበረታቻዎቹ ከግቦች
መሳካት ጋር መያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ የማበረታቻ ስርዓት
ሲዘረጋ በቢሮ፣ በተቋም፣ በስራ ሂደትና ግለሰብ ፈፃሚ
ደረጃ ሥርዓቱ በትክክል መዘርጋቱን ማረጋገጥና
ፍትሃዊነቱን ማየት ይጠይቃል፡፡
ለዚህም የዙሪያ መለስ ምዘናንና የሚዛናዊ ስራ አመራርና
ምዘና ሥርዓትን በጥምረት በመተግበር ሠራተኞች
ከሚሰጣቸው ግብረ መልስ በመነሳት ራሳቸውን፣ የሥራ
ባልደረቦቻቸውንና ተቋማቸውን እንዲያውቁና እንዲረዱ
ብሎም የባህሪ ለውጥን እንዲያመጡ ማገዝ ይገባል፡፡
22
በባላንስድ ስኮር ካርድ ጥናት የትግበራ ምዕራፍ
/Implementation Phase/ ሶስት ደረጃዎች
ማለትም የአውቶሜሽን ሥራ /ደረጃ ሰባት/፣
ስትራቴጂያዊ ግቦችን በየደረጃው ላሉ ፈፃሚ
አካላት /እስከ ግለሰብ ድረስ/ የማውረድ ሥራ /ደረጃ
ስምንት/ እና የአፈፃፀም የክትትል ግምገማና ምዘና
ሥራዎች /ደረጃ ዘጠኝ/ አንዳሉ ይታወቃል፡፡
የአውቶሜሽን ደረጃን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ኢኮቴል ኤጀንሲ አማካይነት ተሰርቶ የሚጠናቀቅ
ይሆናል
23
ስትራቴጂን ከተቋም እስከ ግለሰብ ፈፃሚዎች በየደረጃው
ማውረድን፣ ራስን የማብቃት እቅድን ማዘጋጀትና
የትግበራ ደረጃዎችን ያጠቃለለ ሲሆን በትግበራው
የለውጥ ሥራ አመራር መሳሪያዎች ተሳስረውና
ተመጋግበው በሥራ ላይ እንዲውሉ ለማድረግ በምሳሌ
በማስደገፍ ለማመልከት ተሞክሯል፡፡
25
የሚዛናዊ ስራ አመራርና ምዘና ሥርዓት /BSC/
ስትራቴጂያዊ ግቦችን ከስትራቴጂያዊ ዕቅድ
ኘሮግራሞችና ኘሮጀክቶች ጋር የማናበብ ሥራ ከላይ
እንደተገለጸው በስትራቴጂያዊ እርምጃዎች ደረጃ ላይ
የተከናወነ ቢሆንም በግብ ደረጃ የማናበቡ ሥራ ግን በዚህ
ደረጃ የሚሰራ ይሆናል ማለት ነው፡፡
26
1. ለየቢሮው በተለዩት ሚዛናዊ ስራ አመራርና ምዘና ሥርዓት
ትራቴጂያዊ ግቦች ሥር ሊወድቁ የሚችሉትን የቢሮውን ስትራቴጂያዊ
ዕቅድ /SPM/ ግቦች ስትራቴጂዊ እርምጃዎች ደረጃ ላይ ከተሰራው
ጋር በተናበበ ሁኔታ መለየትና በሚዛናዊ ስራ አመራርና ምዘና ሥርዓት
ስትራቴጂያዊ ግቦች ስር ማስቀመጥ ሲሆን ይህም በስትራቴጂያዊ ዕቅድ
ሰነድ ቀደም ብሎ ለግቦች የተቀመጠውን ዒላማ /Target/ እንዳለ
በመጠበቅ የሚፈጸም ይሆናል፤
2. በመቀጠልም በተቋም ደረጃ ከሚዛናዊ ስራ አመራርና ምዘና
ሥርዓት /BSC/ ግቦች ጋር የተጣጣሙት /የተናበቡት ተቋማዊ
ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ግቦች በስራቸው ላሉ የሥራ ሂደቶችና ኬዝ
ቲሞች የማከፋፈል ሥራ ይከናወናል ፡፡
27
4. በሚዛናዊ ስራ አመራርና ምዘና ሥርዓት /BSC/ ግቦች
ስር የሚወድቁት የየኘሮግራሙ የስትራቴጂዊ ዕቅድ ግቦች
የBSC የግብ አጣጣልን ሥርዓት የተከተሉ እንዲሆኑ
ማድረግ ይገባል፤ ይህም ማለት ቀጣይ ሂደትን የሚያሳዩና
ድርጊት ተኮር መሆን ይኖርባቸዋል፤
ቅፅ 001
28
የግቦችን አፈፃፀም ለመከታተልና ለመመዘን ከላይ
እንደተገለጸው በአራቱ መለኪያዎች ማለትም በመጠን፣
በጊዜ፣ በበጀት/ወጪና በጥራት ዒላማ መቀመጡን ማረጋገጥ
ይገባል፡፡ ይህን ለመስራት በቅድሚያ ሁለት ወሳኝ ጉዳዮችን
ማከናወን ያስፈልጋል፡፡
32
ይህ ደረጃ ለስራ ሂደትና ኬዝ ቲም የወረዱ ስትራቴጂያዊ ግቦች
በውጤት ተኮር ተግባራት ተመንዝረው ወደ ፈጻሚ ግለሰብ ደረጃ
እንዴት መድረስ እንዳለባቸው የምናይበት እና የግለሰብ ፈጻሚዎችን
ድርሻ በመለየት የተግባሮቹን አፈጻጸም በሚቀመጡት መለኪያዎች
መሰረት በመከታተልና በመለካት ግለሰብ ፈጻሚው ከ50 በመቶ
የሚመዘንበት ነው፡፡ ይህን ለማስፈጸም የሚከተሉትን ንዑስ
ደረጃዎች ማከናወን ያስፈልጋል፡፡
37
6.በዚህም መሰረት አንድ ግለሰብ ከአንድ ግብ ውጤት ተኮር ተግባራት 60 % ድርሻ
ቢኖረውና ከሌላ ግብ 50 % ድርሻ ቢኖረው በድምሩ 110 % ክብደት ያላቸው ውጤት
ተኮር ተግባራት ላይ ስለሚሳተፍ አፈጻጸሙ ከ110 ይመዘንና ወደ 50 በመቶ
ይለወጣል ማለት ነው፡፡
ቅፅ 005
39
ምሳሌ፡- የጥራት አለካክን በተመለከተ ለአብነት አንድ ተግባር ወስደን
ስንመለከት
ግብ 2 ተግባር 2፡ የተቀመጡ የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርዶች ከባላንስድ
ስኮር ካርድ ኢላማዎችና መለኪያዎች ጋር እንዲቃኙ ማድረግና ከላይ
እስከታች የተሳሰሩና ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ክትትልና ድጋፍ
ተግባርማድረግ፣ የጥራት አመላካች የጥራት ደረጃ
40
ለግለሰብ ፈጻሚዎች የተሰጡ ውጤት ተኮር ተግባራት
በሩብ ዓመት፤ በግማሽ ዓመት፤ በዘጠኝ ወር እና በበጀት
ዓመቱ መጨረሻ አፈጻጸማቸው ሊመዘን ይገባል፡፡ በዚህ
የሥራ አፈጻጸም ምዘና አንድ ግለሰብ ፈጻሚ ከተለያዩ
ውጤት ተኮር ተግባራት በ3ቱ መለኪያዎች የሚያገኛቸው
ውጤቶች ተጨምቀው ከ50 በመቶ ነጥብ እንዲሰጥ
ይደረጋል፡፡
41
የዙሪያ መለስ የምዘና ስርዓትን ለመተግበር
የፈፃሚውን ባህሪይ የሰራተኛው የቅርብ አለቃ፣
የሰራተኛው የቅርብ የሥራ ባልደረቦች እንዲሁም
ሰራተኛው ራሱን በፊት ለፊት ግምገማ (Face to
face evaluation/appraisal) ማድረግ
ያስፈልጋል፡፡
42
ራስን የማብቃት ዕቅድ ሰራተኞች በሥራ አፈጻጸም የራስን
ድክመትና ጥንካሬ በመለየት እንዲሁም በተቀናጀ ውጤት
ተኮር ምዘና በሚገኘው ግብረ መልስ መሠረት የተለዩ
ክፍተቶችና ድክመቶች ለማሻሻል የሚረዱ እርምጃዎችን
የማቀድና በዕቅዱ መሰረት ለመተግበር የራሳቸውን ጥረት
የሚያደርጉበት ተግባር ነው፡፡
ራስን ከማብቃት ዕቅድና አፈጻጸም ከሚገኘው ከተሻሻለ
የአፈጻጸም ደረጃ ባሻገር በራሱ ራስን የማብቃት ዕቅድ
ማዘጋጀት፣ ተግባራዊ ማድረግና ለውጥን ገምግሞ ሪፖርት
ማድረግ ሠራተኛው የሚመዘንበት መስፈርት ይሆናል፡፡
ቅፅ 007
43
44