You are on page 1of 14

የስራ ዕቅድ

በሰላም ማስከበር ዋና መምሪያ የኮንቲጀንት ማሰ/ት/ቤት

የ 1 ኛ ሩብ ዓመት የስራ እቅድ መግቢያ

የሰላም ማስከበር ዋና መምሪያ የኮንቲጀንት ማሰ/ት/ቤት በመከላከያ የተያዘውን የለውጥ ጉዞ በብቃትና


በንቃት እንዲሁም በድል ለመወጣት የተሟላ የአእምሮ እና አካላዊ ሰነ-ልቦና ጤንነት የተጠበቀ ሰራዊት
ለማድረግ የ 1 ኛ ሩብ ዓመት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እና ተላላፊ የሆኑ በሽታዎች የመከላከልና
የታመሙትን የማከም እቅድ በማዘጋጀት ሰልጠኝ እና አሰልጣኝ እንዲሁም የት/ቤታችንን ማህበረሰብ
ደስተኛና ጤናማ እንዲሆን ተደርጓል፡፡

ሰላዚህ በሬጅመንቶች (ሠልጣኞች) ጠንካራ በሽታ የመከላከል ስራዎች ቀጣይና ተከታታይነት እንዲኖረው
በማዕከሉ እስታፍ እና ማሕበረሰብ እንዲሁም የባለጓዝ መኖሪያ ሰፈር ልክ እንደሬጅመንቶች ጠንካራ
በሽታ የመከላከል ስራ ለመስራት የሚታዩ አደናቃፊና ደካማ አስተሳሰብ ለመቅረፍ የተጀመረው የፅዳት
ዘመቻ ተጠናክሮ እና ውጤታማ ሆኖ እንዲቀጥል የእስታፍ አመራርና የጤና ባለሙያ ቅንጅት አጠናክረን
መስራት ይጠበቅብናል፡፡

 ተላላፊ የሆኑ በሽታዎች ከመከላከል አንፃር የአካባቢያችን ሁኔታ


በአካባቢያችን ከሚገኙ የሲቪል ጤና ተቋማት ጋር በመደራጀትና የጋራ ጥምር ሃይል በማቋቋም
ከሚመለከተው ባለ ድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር ለወደፊት ሊከሰት የሚችሉ ተላላፊ በሽታዎች
በመተንበይና እንደ አተት፤ወባ፤TB HIV፤ የአባዘር በሽታዎች እና ሌሎች የደምተቅማጦች
የመሳሰሉት ከሰው ወደ ሰው በቀላሉ የሚተላለፍ ለመከላከል አጠናክረን የምንቀጥልበት ይሆናል፡፡
 ይህ እንዲህ እንዳለ ሆኖ የት/ቤታችን የውስጥ በሽታ የመከላከል ስራ አጠናክረን በመቀጠል በድንገት
በወረርሽኝ መልኩ ሊከሰቱ የሚችሉ እንደአተት፤ ወባ የመሰሳሉትን በሽታዎች ለስልጠና ስጋት
በማይሆንበት ደረጃ የማድረግ ግዴታ አለብን፡፡
 ተላላፊ በሽታዎች ለመከላከል ውስጣዊ ሁኔታ
የት/ቤታችን አስልጣኞች ሠልጣኝና ጠቅላላ ማሕበረሰብ ጤንነቱ የተጠበቀ በአእምሮውና በአካል
ብቁና አስተማማኝ የተሰጠውን ተልእኮ ያለምንም የጤና እንከን ሳይኖረው ጠንካራ ሃይል እንዲሆን
በሬጅመንቶች አካባቢ የዳበረና ጠንካራ የመከላከል ስራዎች እየተሰራ ይገኛል፡፡
በዚህ መሰረት የትምህረት ቤታችን ኮማንድና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ድጋፍና በሽታ የመከላከል
ስራዎችን እንደግብአት በመጠቀም በማእከሉ እስታፍ እና በሲቪል ሰራተኞች ሰፈር
እንዲሁም ባለጓዝ ሰፈሮች (አካባቢዎች) የሚታዩ የበሽታ የመከላከል ድክመት ለመቅረፍ
በየደረጃው ያለው የእስታፍ አመራሮችና የጤና ሙያተኞች በጋራ በመነጋገርና በመግባባት
ላይ ተደርሰዋል፡፡
በቀጣይም ተጠናክሮ የተጀመረው የፅዳት ዘመቻ እንዲቀጥል ይደርጋል፡፡
የትምህርት ቤቱ አሰልጣኞችና የትምህርት ቤቱ አጠቃላይ ማሕበረሰብ የዳበረና ጠንካራ
በሽታ የመከላከል ልምድ ያለው መሆኑን ይታወቃል ይህ ልምድ አዳብሮና አጠናክሮ ሳይዘናጉ
ለማሰቀጠል ከፍተኛ ጥረት ይሻል፡፡
 በጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል አንፃር የሚታዩ እጥረቶች
 ወደ ሠላም ማስከበር የሚሰማሩ ሠልጣኝ ክፍሎችና ግለሰቦች አካባቢ ተላላፊ የሆኑ በሽታዎች
ከመከላከል አንፃር የሚታዩ ዋና ዋና እጥረቶች፤
 ጠንካራ የአከባቢ ፅዳት አለማድረግ
 ከመፀዳጃ ውጪ መፀዳዳት በየቦታው የመሽናት ችግር
 የምግብ ቤትና የመመገቢያ ዕቃ ንፅህና አያያዝ ችግር
 የመጠጥ ውሃ ንፅህና ቁጥጥር አለመጠበቅ
 በየሳምንቱ የመኝታ አልባሳት በፀሐይ ላይ አለማውጣት
 ጫማና ካልሲ በየቦታው መጣል
 የውሃ ሃይላንድ ፕላስቲክ በየቦታው መጣል
 የአባላዘር በሽታዎች ችላ ማለትና ለህይወት ዋጋ አለመስጠት
 በአጠቃላይ ነባር ወታደር ነው በማዕረግም ሆነ በዕድሜ ከኔ በላይ ነው ያውቃል በማለት ችላ
በማለትና የቁጥጥር ማነስ የሚታዩ እጥረቶች ናቸው፡፡

2. በማዕከሉ እስታፍና ባለጓዝ አጠቃላይ በሲቪል ሰራተኞች አካባቢ የሚታዩ እጥረት

 በመዝናኛ ክበብ አከባቢ ያሉ እጥረቶች


በመዝናኛ ክበብ ዙርያ የሚታዩ ችግሮች በተለይም በቁጥር አንድ የፈሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ትቦዎች
ያረጁ በመሆናቸው ሰራተኞች የተሟላ የስራ ልብስ አለመልበስ አዳዲስ ሰራተኞች ሲቀጠሩ
አለማስመርመር (ሳይመርመር)ስራ ማስጀመር ነባሮቹም ቢሆኑ በፕሮግራሙ መሰረት አለማስመርመር
ናቸው፡፡
 በቄራ አከባቢ ተላላፊ የሆኑት በሽታዎች ከመከላከል አንፃር ያሉ እጥረቶች
በቄራ አባቢ የሚታዩ እጥረቶች በቂ የሆነ ውሃ አለመኖር በየወቅቱ ፅዳቱን የሚከታተል ቋሚ ስራተኛ
የሌለው መሆኑ፤ ከብት ከታረደ በኋላ በወቅቱ አለማጠብ ጥገኛ የሆድ ትላትሎችና የተቅማጥ በሽታ
ሊያስከትል ይችላል፡፡
 የጤና ማበልፀግና በሽታ ከመከላከል አንፃር የተወሰዱ ድምዳሜዎች
የጤና ማበልፀግና በሽታ ከመከላከል አንፃር እሰካሁን የሄድነው ጉዞ አበረታች ሲሆን ቀጣይ በሽታ
ከመከላከል አንፃር እንደ ጥንካሬ መውስድ ያለብን የትምህርት ቤቱ ኮማንድ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እና
የአሠልጣኞች ጠንካራ በሽታ የመከላከል ስራ መስራት እና እንደግብአት ተጠቅመን የነበረን ጠንካራ
በሽታን የመከላከል ስራ አጠናክረን የጤና ሙያተኞች ክትትልና ድጋፍ ታክሎበት ቀጣይ በያዝነው ሩብ
ዓመት የተሻለና ውጤታማ በሽታን የመከላከል ስራዎች አጠናክረን መቀጠል ይኖርብናል፡፡
የእቅዱ አጠቃላይ አላማ
ወደ ተለያዩ አገሮች ለሚሰማራ የሰራዊት አባላት አካላዊና ስነ-ልቦናዊ ጥንካሬ እንዲኖረው
ጤንነቱን የተጠበቀ አስተማማኝ ሃይል ለማድረግ ነው፡፡
 ግቦች
1. የጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማድረግ
2. ተላላፊ የሆኑ በሽታዎች ሊያስከትሉ የሚችሉ ሁኔታዎች መለየት
3. ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን የመከላከል ስራ መስራት
4. የጤና ትምህርት በፕሮግራሙ መሰረት በመሰጠት የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖር ማድረግ
5. በሆስፒታልየሚሰራየፈውስና እንክብካቤ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እና ተገልጋይ ደስተኛ
እንዲሆን ማድረግ
6. በሆስፒታል እና በሁለቱ ክሊኒኮች ያሉ የመንግስት ንብረትና መድሃኒት ተገቢ ክትትልና
ቁጥጥር ማድረግ
7. የጤና ሙያተኞች አቅም ለማሳደግ የተለያዩ አጫጭር ስልጠናዎችን እንዲያገኙ ማድረግ
8. ለህሙማን የተመደበው በጀት በመመሪያው መሰረት እንዲጠቀሙ ማድረግ
9. በመመሪያና አሰራር በተከተለ ለሰራዊቱና ለሲቪል ሰራተኞች መልካም አስተዳደር ማስፈን

10.የተለያዩ የህትመት ውጤቶችን ለግንባታ መጠቀም

1. ግቦችን ለማሰካት የሚሰሩ ስራዎች


1.1 የቅድመ በሽታ መከላከል ስራዎች
 የአየር ንብረት መዛባት ተከትሎ የተለያዩ በሽታዎች እንደወረርሽኝ መልክ ሊከሰቱ ስለሚችሉ
የቅድመ ትንበያና የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥ
 ወደ ሰላም ማስከበር ለሚሰመራ ሰልጣኞችና ለትምህርት ቤታችን ማህበረሰብ የሚሰጡ የጤና
ትምህርት ወቅቱን የጠበቀና የአካባቢው ነባራዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ ማስገባትና በተከታታይ
የጤና ትምህርት ማስተማር ይሆናል፡፡
 በወር አንድ ጊዜ የእስታፍና የሰልጣኝ እንዲሁም የት/ቤታችን ማህበረሰብ በጋራ የፅዳት ዘመቻ
ፕሮግራም በማውጣት ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን የመከላከል ስራ በመሰራት የብዙሃኑ ተሳትፎ
ማሳደግ፡፡
 የመኝታ ቤት በፕሮግራም እንዲፀዱ እና እንዲናፈሱ ማድረግና ክትትል ማድረግ ፡፡
 የሰልጣኝ ፕሮግራም ሲወጣ የጤና ት/ት ፕሮግራም አብሮ እንዲካተት ማድረግ
 የመኝታ ቤት የግልና አካባቢ ንፅህና አጠባበቅ ስራ በቅርብ አመራሮች እንዲመራ የጤና
ሙያተኞች ድጋፍና ክትትል እንዲኖር ማድረግ፡፡
 ወደ ሠላም ማስከበር ግዳጅ የሚሰማራ ሠልጣኝ የጤና ሙያተኞች ከሰልጣኝ ጎን ለጎን በሽታ
የመከላከል ስራ እንዲሰሩ ማድረግ፡፡
 የሠላም ማሰከበር ሰልጣኞች ከጋንታ ጀምሮ እስከ ሬ/ት ድረስ የጤና ኮሚቴ ማዋቀርና በጤና
ሙያተኞች ምን መሰራት እንዳለበት ኦረንቴሽን መስጠት እንዲሁም ኮሚቴዎች ጋር ግምገማ
ማድረግ ናቸው፡፡
 ፕሮጀክቶቹ እንዳይፈራርሱና ጥገና የሚያሰፈልጋቸው ጥገና እንዲደረግላቸው ክትትል ማድረግ
ግብአት የሚያሰፈልጋቸው ግብአት ማፈላለግ፡፡
 ከተጓዳኝ የሲቪል ጤና ተቋማት ጋር በጋራ መሰራት፡፡

1.2 የወባ በሽታ ስርጭት መግታት


 የወባ ትንኝ መራቢያ ቋሚና ጊዜያዊ ቦታዎችን መለየት
 የግል የወባ በሽታ መከላከያ ዘዴ መጠቀም እንደ ባዝ ኦፍ ፤የአልጋ አጎበርና ሌሎችም ዘዴዎች
መጠቀም
 ከወቅቱ ተለዋዋጭ ሁኔታ ጋር የሚጣጣም ዕቅድ ማቀድ እንዲሁም የአካባቢው ጤና ተቋማት
ጋር አብሮ መስራትና አፈፃፀሙን መከታተል ናቸው፡፡

1.3 የውሃና የምግብ ወለድ በሽታዎች መከላከል


 የመጠጥ ውሃ በአመት ሁለት ጊዜ ውሃ እንዲመረመር ማድረግ እንዲሁም የውሃ መያዣ
ሮቶዎችን እንደየሁኔታው እንዲታጠብና የመጠጥ ውሃ አያያዝ ክትትል ማድረግ
 የሚንስ ቤት ቋሚ ሰራተኞች በየወር የጤና ምርመራ እንዲያደረጉ የኮንትራት ሰራተኞች
ወደ ስራ ከመግባታቸው በፊት የጤና ምርመራ ማድረግ ፤ የግል ንፅህና ቁጥጥር ማድረግ
 የመመገቢያ ዕቃዎችና አዳራሽ ንፅህናቸውን መከታተል
 የዳቦ መያዣ ካሳ ፤ የማስቀመጫ ቦታ እና የዳቦ መጓጓዣ ተሸከርካሪዎች ፅዳታቸውን
መከታተል ፡፡
 የማዕከሉ ቄራና መዝናኛ ክበብ የውስጥና የውጭ ፅዳት ክትትል ማድረግ ፡፡
 ሁሉም የክበብ ሰራተኛ ስራ ከመጀመራቸው በፊት የጤና ምርመራ እንዲያደርጉ ክትትልና
ቁጥጥር ማድረግ
 የመዝናኛ ክበብ የወጥ ቤት ፤ ስጋ ቤት እና አስተናጋጆች የስራ ልብስ እንዲዘጋጅ
ከሚመለከተው አካል ጋር መነጋገርና ተግባራዊነቱ ክትትል ማድረግ፤ ጤና ትምህርት ማስተማር
 በክበብ ዙሪያ የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓት ክትትል ማድረግ
 መዝናኛ ክበብ የሻይ፤ የቡናና የእንጀራ ማቅረቢያ ዕቃዎች ንፅህና መከታተል
 የመዝናኛ ክበብ ለተጠቃሚው ምቹና ደስታን የሚሰጥ እንዲሆን ከሚመለከተው አካል ጋር
መነጋገር
1.4 ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ትኩረት ማድረግ
 ተላላፊ ያልሆኑ በሽታ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ማስተማር
 ተላላፊ ያልሆኑ በሽታ ተጠቂ ለሆኑት የቅርብ ድጋፍና ክትትል ማድረግ
 ለከፍተኛ መኮንኖች ሜዲካል ቼክ -አፕ በአመት ሁለት ጊዜ ማድረግ
ለምሳሌ ፡- የደም ግፊት
- ስኳር በሽታ
1.5 የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ /HIV/AIDS/ እና ሌሎች የአባላዘር በሽታዎች ላይ የግንዛቤ ስራዎች
መስራት
 በማሰልጠኛ ትምህርት ቤታችን አሁን እየታየ ያለውን የኤች.አይ.ቪ/ኤድስና ሌሎች የአባላዘር
በሽታዎች በስፋት የመከሰት ሁኔታ አብዛኛውን ሰው የግንዛቤ ማነስ ነው ባይባልም የግድየለሽነት
ሁኔታ የፈጠረውና በጊዜው ችግር መገፋት ቁጥሩ ቀላል በማይባል የግንዛቤ ችግሩን ለመፍታት
መስራት ያለብን ስራዎች እንዳሉ ግን የማያሻማ ጉዳይ ነው ስለሆነም መሰራት ያለባቸው ጉዳዩች
1. ስለ ኤች.አይ.ቪ/ኤድስና ሌሎች የአባላዘር በሽታዎች በተመለከተ ጠንካራ የጤና ትምህርት
መስጠት ማስተማር
2. ኤች.አይ.ቪ /ኤድስ ክበቦች ከሰልጣኙ ከራሱ የተውጣጡ ሰዎች ማጠናከር
3. የአቻ ለአቻ ውይይት እንዲቀጥልና ፕሮግራም እንዲወጣለት ከኮማንድ ጋር በመነጋገር የአባላዘር
በሽታ እንዲቀንስ ማድረግ
4. የኮንዶም ጥቅምና አጠቃቀም በፅንሰ ሃሳብና በተግባር ማስተማር በዋና ዋና ቦታዎች ላይ ኮንዶም
ማስቀመጥ
5. ከአጎራባች የጤና ተቋማት ጋር ግንኙነት መፍጠር
ሚኒ-ሚዲያ ለማደረጃት ከሚመለከታቸው አባላት ጋር መነጋገር በስምምነቱ መሰረት መስራት

የአባላዘር በሽታ መከላከልና መቆጣጠር


 ተጋላጭነትን ማስወገድ ኮንዶም በአግባቡ መጠቀምና የግንዛቤ ስራ መስራት
 የተጋለጡትን ማከምና ምክር መስጠት
 የተሟላ ዳታ መያዝና ሪፖርት ለሚመለከተው ማቅረብ

1.6 የእስክሪን ስራ
የሰላም ማስከበር እስክሪን በተመለከተ

 ከዚህ በፊት እየሰራነው የመጣን ስራ ቢሆንም ቀላል የማይባሉ ግድፈቶች ሲያጋጥሙ እንደነበር
የቅርብ ትዝታችን ነው፡፡ስለሆነም ግድፈቶቹ የሚከሰቱት ከሞያተኛ እስከ አመራር እና አጠቃላይ
አባሉ የየራሱ ስራ ባለመስራትና የቅድመ ዝግጅት ባለማድረግ እንደ ሬጅመንት በአንድ ላይ ግር ብሎ
በመምጣትን አመራርም የሞያተኛ ስራ ነው ብሎ ችላ በማለት እና ትኩረት አለማድረግ በመጣደፍ
ወይም በሩጫ ሩጫ ሲሰራ ስለነበር የዶክመንት መጥፋትና ውጤት የመዛባት ሁኔታ አጋጥሞናል፡፡
ስለዚህ ሁሉም ሰው የየራሱ ስራ በመስራት ችግሮች እንዳይከሰቱ በታቀደ እና በፕሮግራም ብቻ
በመሄድ ችግሮች
 በዚህ መሰረት ወደ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤታችን የሚገቡ የሰራዊት አባላት የሰላም ማስከበር
መምሪያ መሰረት ከክፍላቸው እስክሪን የተደረገላቸው የማረጋገጥ ስራ መስራት
የማረጋገጥ ስራ መስራት
የእስክሪን ስራ አጭር ዕቅድ ማውጣት
የእስክሪን ስራ እና የክትባት ስራ በአግባቡ መስራት
የእስክሪን ስራ በሚኖርበት ጊዜ ጊዜያዊ አደረጃጀት ማበጀት ማን ምን መሰራት
እንዳለበት በግልፅ ማስቀመጥ
ለሰላም ማስከበር ግዳጅ የሚሰማራው ብቁ የሆኑትና ብቁ ያልሆኑ የተሟላ ዳታ መያዝ
ስለ እስክሪን ስራ እና እስክሪን የተሰራላቸው ሰዎች የማረጋገጥ ስራ በመስራት ለጤና
ባለሞያዎች ግልፅ ኦረንቴሽን መስጠት
1.7 በሆስፒታል የሚሰጠው ሰርቪስ በተመለከተ
1.7.1 በተመላላሽ ህክምና በተመለከተ
በተመላላሽ የሚታከሙት ሳይጉላሉ በጊዜ ታክሞ ወደ ስልጠና እንዲመላለሱ ማድረግ
የሚሰጠው አገልግሎት በፍጥነት እንዲያገኙ ማድረግ
መሰረታዊ የስራ ሂደት በተቻለ ሁኔታ ማስቀጠል
የምርመራ ሁኔታ ዝግጁ ማድረግ
ለምርመራ አጋዥ የሆኑ ማቴሪያሎች መጠየቅና ማሟላት
ምሳሌ፡- በላቦራቶሪ
መድሃኒትና የማቴሪል እጥረት እንዳያጋጥም ጥንቃቄ ማድረግ

1.7.2 አስተኝቶ ህክምና በተመለከተ

ተኝተው ለሚታከሙ ሆስፒታሉን ምቹ ማድረግ


ለምሳሌ፡- - በአቀባበል
- በማረፊያ ቦታ ንፁህና
- በኑሮ ፤በአጠቃላይ በሆ/ሉ በሚሰጠው ግልጋሎት ደስተኛ እንዲሆን ማድረግ
የታዘዘው መድሃኒት በአግባቡ መስጠት
ተኝቶ የሚታከሙት ስለግልጋሎት አስተያየት እንዲሰጡና እንደግብዓት መጠቀም
አስተኝቶ የህክምና ሪፖርት በየቀን በመከላከያ ስልጠና መምሪያ ለጤና ቡድን ሪፖርት ማድረግ

2. ፈውስና እንክባኬ በተመለከተ


2.1 የመድሃኒት የህክምና ማቴሪያል አቅርቦት
መድሃኒት መከላከያ ባስቀመጠው መመሪያ መሰረት መጠየቅ እና የተጠየቀው መድሃኒት
ሲፈቀድ በጊዜ እንዲመጣ ግፊት ማድረግ
የመጣው መድሃኒት ሲረከብ በቴራፕትክ ኮሚቴ ማረጋገጥ
የመድሃኒት ብክነት እንዳይኖር ማድረግ
ወጪና ገቢ ክትትል ማድረግና የመድሃኒት አወጣጥ ሲስተም መከተል
ወቅቱን ጠብቆ ለሚከሰተው በሽታ መከላከያ ክትባት መጠየቅ
የመድሃኒት ስቶር ንፅህና ክትትል ማድረግ
የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው መድሃኒቶች ለሚመለከተው አካል ሪፖርት ማድረግ
ሲፈቀድ በመምሪያ መሰረት ማስወገድ
የጎደለውን የህክምና ማቴሪያል ጥያቄ ማቅረብ
የሚሰራና የማይሰራ የህክምና ማቴሪያል መለየትና የማይሰራ እንዲጠገን ማድረግ
ለመጀመሪያ ህክምና ርዳታ የሚያስፈልጉ ማቴሪያል መጠየቅ
መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሚገኘው መድሃኒትና ማቴሪያል ሲገኝ ወደ መንግስታዊ
ሲስተም ማስገባትና በመምሪያው መሰረት መጠቀም
አምፑላንስ መምሪያ በሚፈቅደው መሰረት መጠቀም፤ሳይጉላላ ከሬ/ቶች ወደ ሆ/ል እንዲሁም
ከታከሙ በኋላ ወደ ሬ/ቶች ማድረስ
ወቅታዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ ኪቶችን ማሟላት
የሰላም ማስከበር ሰልጣኞች የተከተቡና ያልተከተቡ መለየት

4. መልካም አስተዳደርና ማስፈን ዲሞክራሲያዊና ደስተኛ የሆነ አሃድ መፍጠር


መልካም አስተዳደር ማስፈን ማለት አድሎ ማስወገድ ሁሉም በደንብና በመመሪያ መሰረት
እኩል የሚስተናገድበት ሁሉም የሚገባውና የማይገባው የሚያውቅ የሚገባውን እንደሚያገኝ
እርግጠኛ የሆነ አባል መፍጠር ማለት ነው፡፡
በመሆኑም ለግንባታ የተመቸ ሁኔታ መፍጠር ፤ የመተሳሰብና የመደጋገፍ ባህልን ማሳደግ ፤ የህግ
የበላይነት ማረጋገጥ ግልፀኝነትና ተጠያቂነት አሳታፊነትን ማስፋትና ማሳደግ
መልካም አስተዳደር ማስፈን ማለት ዲሞክራሲያዊ አመራር ማረጋገጥ ቋሚ መመሪያዎችን
አሰራሮችን በፅናት መተግበር መልካም አስተዳደር በማስፈን አሳታፊነትን ማረጋገጥ ናቸው፡፡
ስለዚህ በየደረጃቸው ያለው የጤና ሙያተኛ አመራር መልካም አስተዳደር ለማስፈን
የሚከተሉትን ነጥቦች በቀጣይነት መስራት አለበት፡፡
ማንኛውም ምልመላ ሁሉም አባል ባለበት እንዲመለመል ማድረግ
አባሉ ስለምልመላው አስተያየት እንዲሰጥ ማድረግ
ሁሉም ውሳኔዎች ዕቅዶችን ኮሚቴያዊ አሰራርን መከተል ተጠያቂነት ግልፀኝነት እንዲኖር
ማድረግ
አስተዳደራዊ መብቶችን ግዴታዎችን እኩል ትኩረት መስጠት
አባሉ በግልም ሆነ በጋራ የሚያስነሳቸው ችግሮችና ጥያቄዎች በአግባቡ ማስተናገድና
በመፍትሄውም የአባሉን ተሳትፎ ማረጋገጥ
መመሪያዎችና አሰራሮች ያለምንም መሸራረፍ ሙሉ በሙሉ ሲተገበሩ ሁሉም አባላት
ተጠቃሚ እንደሚሆኑ በየጊዜው የማስገንዘብ ስራ በመስራት እንዲሁም በእምነት እንዲይዙት
ማድረግ
የጤና ሙያተኞች የመንግስት ሲቪል ሰራተኞች የሻይ ቡና ፕሮግራም ማጠናከር
ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮች
ከዘህ በፊት በሰራናቸው ውጠታማ የጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል ስራዎች ጤናማ
አሰልጣኝና ሰልጣኝ እንዲሁም የግቢው ማህበረሰብ መፍጠር ተችሏል፡፡ ነገር ግን በሽታ
የመከላከል ፤የታመሙትን የማከምና የመንከባከብ ጥንካሬ ላይ ሆነን የሚታዩ ክፍተቶችን
ጠንክረን ካላስወገድናቸው እንቅፋት ለሆኑ የሚችሉ
በመመሪያዎችና ደንቦች ላይ ትኩረት አለማድረግ ፤ አሰራርን አለመከተል ሊያጋጥመን ይችላል
በሚፈጠሩ ችግሮች አንድ አይነት አስተሳሰብና አመለካከት በሜዝ በቁርጠኝነት ያለመታገልና
ተቻችሎ የመሄድ ሁኔታ ሊያጋጥመን ይችላል፡፡
ለህሙማን በሚሰጠው ግልጋሎት የበሽታ መከላከል ስራ መሰላቸት ሊገጥመን ይችላል፡፡
የመድሃኒትና የህክምና ማቴሪያል እጥረት ሊያጋጥመን ይችላል፡፡
በአጫጭር ስልጠና ምክንያት ስራን መሰረት አለማድረግ በሚደረገው ምልመላ ግለኝነት
ሊታይ ይችላል፡፡
በእስታፍ አባላት ስራን ምክንያት በማድረግ በፅዳት ዘመቻ የማንጠባጠብ ሁኔታ ሊገጥመን
ይችላል፡፡

የመፍትሄ አቅጣጫ

 በታቸለ መጠን መመሪያዎችና ደንቦች እንዲከበሩ ፤ በመመሪያ መሰረት እንዲሰሩ ድጋፍና


የቅርብ ክትትል ማድረግ እንዲሁም ከመመሪያና አሰራር ውጭ የሚሄዱትን እርምጃ
በመውሰድ ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ
 በሚፈጠሩት ችግሮች አንድ ዓይነት አስተሳሰብ እንዲኖር የጋራ መግባባት መፍጠር ፤ የግል
ምክር መስጠት ፤ ከችግሩ የሚላቀቅበት አቅጣጫ ማሳየት
 ለህሙማን የሚሰጠው ሰርቪስ ላይ መሰላቸት እንዳይኖር በሚደረገው የጠዋት ጠዋት
ሚቲንግ ላይና በሚደረገው የስራ ግምገማ ግልፅ ውይይት ማድረግ
 በሚደረገው ማንኛውም ዓይነት ምልመላ ስራንና ክራይቴሪያ መሰረት ተግባራዊ ማድረግና
የጤና ባለሙያ ስነ-ምግባር መከተል
 ሁሉም የእሰታፍ አባላት በተቀመጠው ፕሮግራም የፅዳት ዘመቻ እንዲሳተፍ ከቅርብ አመራር
ጋር በመነጋገር መሰራት ናቸው፡፡
አመራር ቁጥጥር ክትትል
አመራር የተቀመጡት ዝርዘር ስራዎችን በላቀ ተነሳሽነት በሙሉ ፍላጎት እንዲፈፀሙ ሁሉም
በየደረጃው ያለው ጤና ሙያተኛ እርስ በእርስ በመማማር አቅም በማሳደግ ሙያዊ ግዴታውን
መወጣት
ለጤና ቡድን የተሰጠው ተልዕኮ መሰረት በማደረግ ቀጣይ ልንሰራቸው የሚቻለውን የኮሚቴ ስራ
መስራት
ግምገማ
የጤና አገልግሎት አመራር በየስራ ድርሻ ማክሰኞ እለት ሳምንታዊ የኢንፎርሜሽን ልውውጥ
ማድረግ
አርብ እለት በ 15 ቀን አንድ ጊዜ አጠቃላይ አባሉ ስራ ግምገማ ማድረግ
በየዕለቱ ጠዋት ጠዋት ሁል ጊዜ የአዳሪ ኢንፎርሜሽን ልውውጥ ማድረግ
የ 2 ኛ ሩብ ዓመት የነበሩን የስራ አፈፃፀም ከዕቅዱ በመነሳት ሁሉም ጤና ሙያተኛ ባሉበት
ግምገማ ይደረጋል፡፡

የሪፖርት ስርዓት
ለት/ቤቱ ሎጀስቲክሲ በየሳምንቱ ያለው የጤና ሁኔታ በአካል ወይም በስልክ ሪፖርት ይደረጋል
የእለት አስተኝቶ የህክምና ሪፖርት በየቀኑ 3-4 ባለው ሰዓት በመከላከያ ስልጠና ዋና መምሪያ ለጤና
አገልግሎት ሪፖርት ይደረጋል፡፡
ሃሙስ እለት በየሳምንቱ ሪፖርት ለሎጀስቲክሲ ፅ/ቤት ይላካል፡፡
ወርሃዊ ሪፖርት ሎጀስቲክሲ ፅ/ቤት ወር በገባ በ 20 ኛው ቀን ለስልጠና መምሪያ ወር በገባ በ 25 ቀን
ይደረጋል
ወር ሪፖርት ወር በገባ 15-20 ም/አዛዥ ሎጀስቲክስ ፅ/ቤት እና 15-20 በስልጠና ዋና መምሪያ
ለጤና አገልግሎት ሪፖርት ይላካል
የማሰልጠኛ የጤና አገልግሎት በተቀመጠለት ፕሮግራም መሰረት የተለያዩ የጤና ማበልጸግና በሽታ
የመከላከል ስራዎችን በፎርማቱ መሰረት የወር ሪፖርት የሚላክ ይሆናል፡፡
የኮንቲንጀንት ማ/ት/ቤት 2013 በጀት ዓመት የ 1 ኛ ሩብ ዓመት ዝርዝር ስራዎች

የጊዜ ሰሌዳ

ተ/ቁ የሚከናወኑ ተግባራት የአፈጻፀም አቅጣጫ ዝርዘር ተግባራት ፈፃሚ አካላት ሀም


1 የቅድመ በሽታ  ተከታታይነት ያለው የጤና ት/ት መስጠት  በሽታ
መከላከል ስራዎችን  የሜንሲ ቤት ሰራተኞች የጤና ምርመራ ማድረግ የመከላከል
መከናወን  የአካባቢ የፅዳጽ ዘመቻ ማድረግ ኃላፊ
 የጤና ኮሚቴዎችን ማደራጀት  በየደረጃ
 የፕሮጀክት ስራዎችን ማስቀጠል ያለው ጤና
 የቄራ ቁጥጥር ክትትል ማድረግ ሙያተኞች
 የወረርሽኝን ስጋት ሲኖር አስቀድሞ ለሚመለከተው
ሪፖርት ማድረግ
2 የወባ በሽታ መከላከል  የወባ በሽታ መነሻ ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮች ላይ ቅኝት በጤና
ማድረግ ባለሙያተኞች
 የወባ ትንኝ መራቢያ አመቺ ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮችን ና በሁሉም
ማስወገድ አባልናማ/ሰብ
 የተለያዩ የመከላከል ዘዴዎችን መጠቀም
3 የምግብና የውሃ እና ምግብ በተመለከተ፡-የምግብ መዘጋጃና የመመገቢያ ቤቱና በጤና
ኤር ወለድ በሽታ የምግብ ቤት ሰራተኞች ንፅህና መከታተል ባለሙያተኞች
የመከላከል ስራዎችን  የምግብ ዕቃዎች አጠባ ሶስት ደረጃዎች በአግባቡ ክትትል ሁሉም
መስራት መጠቀም አባልና
 ሁል ጊዜ ከሽንት ቤት መልስ እጅ በሳሙና መታጠብ ማህ/ሰብ
ይተገበራል
ወሃን በተመለከተ  በሽታ
 የመጠጥ ውሃ ንፅህና መከታተል መከላከል
 የውሃ መያዣ እቃዎችን ንፅህና መከታተል ኃላፊ
 ወቅቱ ጠብቆ ውሃን ማስመርመር  በየደረጃው
ያለው
ሙያተኛ
4 የሰላም ማስከበር  ለእስክሪን ስራ ቅድሚያ መዘጋጀት
የእስክሪን ስራ  የሰው ሃይልና ማቴሪያል ማሟላት ሁሉም ጤና
በተጠናከረ መንገድ እን
ማከናወን  ለስራው የተመደቡ ሙያተኞች በተመደቡበት ስራ ሙያተኞች
በጥራት መሰረት ተገቢውን ሙያዊ ምርመራ ማድረግ
 አንፊት የተባሉትን የተሟላ ዳታ መያዝና ሪፖርት
5
የተሟላ የህክምና ማድረግ
አገልግሎት መስጠት ሆስፒታል
 ሆ/ሉና ክሊኒኮች ለ 24 ሰዓት አገልግሎት መስጠት አዛዥና
የህክምና አገልግሎት አጠቃላይ
ሙያተኞች
በተመላላሽ የሚታከሙ
ተኝቶ የሚታከሙ
ከአቅም በላይ የሆኑትን ወደ ከፍተኛ ህክምና ሪፈራል
መላክ
የእናቶችና የህፃናት የምንሰጣቸው አገልግሎቶች
በተጠናከረ መንገድ ማስኬድ
6 የጤና ሙያተኞች የሙያተኞች አቅም ለማጎልበት በስራ ላይ የእርስ በረስ  በሲነር
አቅም ማሳደግ  በሞርኒግ ሚቲንግ በየ 15 ቀን በተመረጡ ርዕስ እርስ በርስ ሙያተኛና
መማማር በአጋር
 በአጋር ድርጅቶች የሚሰጡ በስራ ቦታና ከስራ ውጭ ድርጅቶች
ስልጠናዎችን ስራን ማዕከል ባደረገ መልኩ የአቅም
ማሳደግ ስራ መስራት
7 የህሙማን በጀት  የተመደበልን የህሙማን አልጋ በጀት በሚኖ መጠቀም የሆ/ል
በአግባቡ መጠቀም  ተኝተው ለሚታከሙ ታካሚዎች ሎጅስቲክስ
 ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት ቶሎ ድነው ወደ
ስልጠናቸው እንዲገቡ ጥረት ማድረግ
8 በኤች አይ ቪ ኤድስና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች በተጠናከረ መንገድ በየደረጃው ባለው
ሌሎች አባላዘር ማስኬድ ጤና ሙያተኞች
በሽታዎች መከላከልና  የጤና ት/ት ማስተማር
መቆጣጠር
 የኮንዶም ስርጭት 100% ማዳረስ

9 የአባላዘር በሽታ ለመከላከል፡- የግንዛቤ ማስጨበጫ ክሊኒካል


 ተጋላጭነትን ማስወገድ ስለ ኮንዶም አጠቃቀም ኦፊሰር
ማስተማር በሲንድሮሚክ አፕሮች ማከም
 ደንበኞች ሳይጎልበት ጥረቱን የጠበቀ ዳታ መያዝና ከቦታ
ቦታ ሲንቀሳቀሱ የትራንስፈር አውት እና ትራንስፈር
ኢን የተሟላ ኢንፎርሜሽን መያዝና
መመለት ይጠበቅብናል፡፡
10 የመድሃኒትና የህክምና  የፋርማሲ ስራዎችን ህግና ደንብ የተከተለ ማድረግ  ሜዲካል
መገልገያ መሳሪያዎች  የመድሃኒት አቅርቦት ማረጋገጥ ወቅቱን የጠበቀ መጠየቅ ሎጀስቲክስ
የአቅርቦትና ማዘጋጀት  የፋርማሲ
አገልግሎት ስራ  የመድሃኒትና የህክምና መሳሪያዎች ክምችት ደህንነት ሰራተኞች
በአግባቡ ማከናወን ማድረግ
 የመጠቀሚያ ጊዜያቸው የደረሱ መድሃኒቶችና
መሳሪያዎችን መቆጣጠር
 የቢን ካርድና የስቶክ ካርድ እንዲሁም የመዝገብ አያያዝ
ቼክ ማድረግ
 ከአጎራባች ጤና ተቋማትና በአጋር ድርጅቶች ጋር
የተቀናጀ የስራ ትስስር መፍጠር
 መድሃኒት ስንጤቅ በስቶር ያለው ይዘት መሰረት ያደረገ
ብክነትን ማስወገድ መሆን አለበት፡፡
11 አሰተዳደራዊ ስራዎች  በሆ/ል ውስት ያለ የሰው ሃይል ዳታ መረጃና ንኡስ አርኔል  ጤና
በትረት መያዝ አገልግሎት
 የሚደረጉ የተለያዩ ምልመላዎች ግልፅነትና ፍትሃዊነት ጠቅላላ
ማረጋገጥ አገልግሎት
 ለአባሉ የሚሰጡ ተልዕኮዎች ግልፅ ማድረግ በጋራ
 የተሰሩ ስራዎች በአፈፃፀማቸው ላይ የነበረውን ጠንካራና
ደካማ ጎኖች በመገምገም ለግንባታ መጠቀም
12 መልካም አስተዳደር  በመልካም አስተዳደር ዙሪያ የሚሰሩ ስራዎች ማከናወን ፤  ሁሉም
ማስፈን መብትና ግዴታን ማሳወቅ አመራር
 ከመከላከያ የሚወርዱ መመሪያዎች አመራሩ አውቆ
አባሉ በትክከል እንዲያውቃቸው ማድረግ
 ስራዎች ሁሉ የአባሉ ተሳትፎን ያረጋገጠ መሆኑን
ማረጋገጥ
 በተቋማችን የሚሰሩ በጎ ተግባራት አባላት እንዲያውቁት
በማድረግ በተቋሙ ያላቸውን እምነትና ፍቅር ማሳደግ
 በአመራሩ በአባላት መካከል ያለው ግንኙነት
ዲሞክራሲያዊ ማዕከልነት ያደረገ እንዲሆን ማድረግ፡፡

You might also like