You are on page 1of 17

በፋ/ኢ/ል/ቢሮ

የመንግስት ግዥ አስተዳደር
ዳይሬክቶሬት

የ 2012 በጀት ዓመት የ 12 ወራት


የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት

ሰኔ /2012 ዓ.ም

Page 1 of 17
መግቢያ
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በስሩ ሁለት (2) ቡድኖች ይዞ
እንደሚንቀሳቀስ ይታወቃል፡፡ በስሩ የመንግስት ግዥ አስተዳደር የግዥ አፈፃፀምና ንብረት ማስወገድ አቤቱታ
ማጣራት ቡድን እና የመንግስት ግዥ ኦዲት ቡድን የሚገኝ ሲሆን የከተማውን የመልካም አስተዳደር ስራዎችን
የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር ለመቀነስ የመንግስት ውስን ሀብት በቁጠባና ውጤታማ የልማት
እንቅስቃሴ ላይ ለማዋል ለተገልጋዩ ህ/ሰብ ቀልጣፋና ፍትሀዊ አገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር መንግስት
የነደፋቸውን የልማት ዕቅዶችና ፕሮግራሞች እንዲሁም ፖሊሲዎችና ስትራተጂዎች በብቃት ለመፈጸም
እንዲቻል በጋራ የ 2012 ዓ.ም እቅድ አውጥቶ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በመሆኑም የ 2012 በጀት ዓመት የ 12
ወራት እቅድ አፈጻጸም በግብና በተግባር ተለይቶ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

የዳይሬክቶሬቱ አጠቃላይ አላማ

በከተማችን ያለውን ውስብስብና መጠነ ሰፊ የአፈፃፀም ችግሮችን ደረጃ በደረጃ ለመቅረፍ አስተዳደሩ
ከአጭርና ከረጅም ጊዜ አኳያ የነደፋቸውን የልማት ዕቅዶችና ፕሮግራሞች ተግባራዊ እንዲሆኑ አጋዥ ሚና
የሚጫወት ሴክተር እንደመሆኑ የፀረ-ኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር ለመቀነስ ትግልን በማጠናከር
በመንግስት ግዥ አስተዳደር ላይ እስከ ክፍለ ከተማ ድረስ የተጀመረውን የማስፈፀም አቅም ግንባታ ስራ እና
የኦዲት ምርመራ አጠናክሮ በማስቀጠል ያለንን ውስን ሀብት በተገቢው ሁኔታና ስርዓትና ፍትሃዊ በሆነ
መንገድ ተግባራዊ ማድረግና ለልማት እንቅስቃሴ በማዋልና በሴክተር መ/ቤቶች ሥር ነቀል ኢኮኖሚያዊ
ለውጥ ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ጉልህ ሚና መጫዎቱና ለውጡን በሚፈለገው መልኩ ለማረጋገጥ
የሚያስችል የተደራጀ የለውጥ ሠራዊት በመገንባት፣ የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት የመንግስት ግዥ የህግ
ማእቀፎች (አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች እና ማኑዋሎች ) ተግባራዊ እንዲሆኑ ማድረግ ዋነኛ ዓላማው
ነው፡፡

የበጀት አመቱ ግቦችና ዝርዝር ተግባራት

ግብ 1. የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር መቀነስ

Page 2 of 17
ተግባር 1.1 በግዥ አፈጻጸም ሂደት የሚፈጠሩ የአሰራር ግድፈቶች በሴክተር መ/ቤቶችን የኦዲት

ምርመራ በማድረግ አሰራሩ መመሪያን የተከተለ እንዲሆን በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 4 ያቀደ ሲሆን

በ 12 ወራት ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ፡-

1. የተፋሰስ አረንጓዴ አካባቢዎች ልማት አስተዳደር ኤጀንሲ


2. የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ፋይናንስ ጽ/ቤት
3. በአራዳ ክፍለ ከተማ የካቲት 66 ከፍተኛ ደረጃ ት/ቤት
4. የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ጤና ጣቢያ
5. የትራፊክ ማናጅመንት ኤጀንሲ የጥቆማ ኦዲት
6. የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የጥቆማ ኦዲት
7. የትራፊክ ማናጅመንት ኤጀንሲ በእቅድ የተያዘ
8. የቂርቆስ ክ/ከተማ መሬት ልማት ማናጅመንት ጽ/ቤት የጥቆማ ኦዲትን ጨምሮ የኦዲት ስራው
የተከናወነ ሲሆን የ 8 ቱም ተቋማት የኦዲት ስራ 100 % ለሚመለከታቸው አካላት ተደራሽ
ተደርጓል።
ከእቅድ ውጭ የተከናወኑ የኦዲት ስራዎች
1 ኛ/ የአንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የጥቆማ ኦዲት የ 2012 ዓም የግዥ ኦዲት ተደርጎ
ስራው 100% ተጠናቋል፡፡
2 ኛ/ የትራፊክ ማኔጅመንት በኮቪድ 19 ወረርሺኝ ምክንያት የንጽህና መጠበቂያዎችን ከግዥ ስርዓት
ውጪና ያለአግባ ከተፈቀደው በላይ ግዥ ፈጽሟል በሚል የደረሰውን ጥቆማ መሰረት በማድረግ ግዥውን
ኦዲት በማድረግ ስራው 100% ተጠናቋል፡፡
3 ኛ/ የኮንስትራክሽን ቢሮ በ 2012 ዓ/ም በተለያዩ ጊዜያት ግዥ ተፈጸመባቸው የመስተንግዶ አገልግሎት
ግዥ ጥቆማ በመቅረቡ ኦዲት ተደርጎ ስራው 100% ተጠናቋል፡፡

በዚህ መሰረት በበጀት አመቱ 12 ወራት 8 የኦዲት ስራዎችን ለማከናወን ታቅዶ / ከእቅድ ውጭ
የተሰሩትን 3 የጥቆማ የኦዲት ስራዎች ጨምሮ 11 ተከናወኖ ለሚመለከተው አካል ተደራሽ የተደረገ
ሲሆን የኦዲት ክንውን አፈፃፀሙም 137.5 % ነው፡፡
 በየጊዜው የሚደረጉ የሞርኒንግ ብሪፊንግ / 1 ለ 5 / ውይይት በማጠናከር ተጨባጭ ትግል በማድረግ
በዳይሬክቶሬቱ ውስጥ የሚመጣውን ለውጥ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
 የስራ ሰዓት አክብሮ መግባትና መውጣት ፣ በስራ ሰዓት በስራ ላይ በመገኘት ተግባራዊ ተደርጓል፡፡
 በጀት ዓመቱ 12 ወራት የግዥ ፈፃሚ መ/ቤቶች ባወጡት ጨረታ ላይ ከተሳተፉ 45 አቅራቢዎች
በግዥ አፈፃፀም አካሄዱ ላይ የህግ ማቀፉን ያልተከተለ አሰራር መሆኑን ገልፀው ያቀረቡትን አቤቱታና

Page 3 of 17
ቅሬታ በመመርመር በ 16 አቤቱታና ቅሬታዎች ላይ ቅሬታው ተቀባይነት ያላገኘ መሆኑን ፣ 14 ቱ
አቤቱታና ቅሬታዎች የህግ ማቀፉን ያልተከተለ የግዥ ሂደት በመሆኑ ሙሉ ለሙሉ ጨረታው
እንዲሰረዝ መደረጉና ቀሪው 10 ሩ አቤቱታዎችና ቅሬታዎች ተቀባይነት አግኝቶ ቅሬታ አቅራቢዎቹ
በጨረታው ሂደት ተካተው ጨረታው እንዲቀጥል ውሳኔ የተሰጠበት፤ እንዲሁም 5 ቱ ደግሞ
ለቅሬታና አቤቱታ አጣሪ ኮሚቴ ቀርቦ በመታየት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ መሰረት ከአቅራቢዎች በግዥ
አፈፃፀም ዙሪያ ላይ የሚቀርቡ ቅሬታና አቤቱታ መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት በበጀት አመቱ ዘጠኝ
ወራት 55 ታቅዶ 40 የተከናወነ ሲሆን አፈፃፀሙም 72.72 ፐርሰንት ነው፡፡
 በበጀት ዓመቱ 12 ወራት ከቀረቡት የ 115 አቅራቢዎች የጥፋተኝነት ሪፖርት መካከል የ 81
አቅራቢዎች የጥፋተኝነት ሪፖርት ምርመራ ተጠናቆ ከማንኛውም የመንግስት ግዥ ላይ
እንዳይሳተፉ በ 75 ቱ ላይ ለ 6 ወራት የእገዳ ውሳኔ የተላለፈ፤ በ 5 አቅራቢዎች ለ 1 አመት እና በ 1
አቅራቢ ላይ የሁለት ዓመት እግድ የተጣለበት ሲሆን የውሳኔው ግልባጭ የ 64 ቱ አቅራቢዎች
ሰርኩለር የተላለፈ ሲሆን 17 በሂደት ላይ ያለ 25 ቱ ባለበጀት መ/ቤቶች ያቀረቡት የጥፋተኝነት ክስ
አግባብ ባለመሆኑ ውሳኔ ተሰጥቶበት ለተቋማቱ ምላሽ የተሰጠ መሆኑ በተጨማሪም 9 ከአቅራቢዎች
ማስረጃ ባለማቅረባቸው መረጃዎች እንዲሟሉ ክትትል እየተደረገበት የሚገኝ ነው።
በአጠቃላይ በበጀት አመቱ 90 ለመስራት ታቅዶ 106 የተከናወነ ሲሆን አፈፃፀሙም 117.8%
ተከናውኗል፡፡

ግብ 2 የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ሥራዎችን ማጠናከር በተመለከተ

 በ 12 ወራት መካሄድ የነበረበት የ 1 ለ 5 ውይይት

ተ.ቁ የአንድ ለአምስት ቡድን መደረግ የነበረበት የተደረገ ውይይት

የመ/ግ/ን/አስ/ዳይሬክቶሬት 48 44

 የ 12 ወራት መካሄድ የነበረበት የለውጥ ቡድን ውይይት

ተ.ቁ የለውጥ ቡድን መደረግ የነበረበት የተደረገ ምርመራ


ውይይት ውይይት
1 የመ/ግ/ን/አስ/ዳይሬክቶሬት 48 42

Page 4 of 17
 የሳምንቱን ስራዎችና ኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከት ያለበት ደረጃ በሚገባ በመገምገም ያልተሰሩ
ስራዎች ያልተሰሩበትን ምክንያቶች እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በመለየት ውይይቱን
ውጤታማና አስተማሪ የተሻለ አፈፋፀም እንዲኖር በሚያስችል መልኩ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
 የ 1 ለ 5 እና የለውጥ ቡድን እቅድ ተዘጋጅቷል፡፡

ግብ 3፡ የመረጃ ጥራትና ተደራሽነትን ማሳደግ ፡

ወቅታዊ መረጃዎችን ማደራጀትና ለተጠቃሚ ዝግጁ ማድረግ ፡

 ለተለያዩ ባለበጀት መስሪያ ቤቶች መመሪያዎች እና አዋጆች፣ደንቦች፣ ማኑዋሎች ለሚጠይቁ ባለበጀት


ተቋማት በሶፍት ኮፒና ሀርድ ኮፒ መስጠት ተችሏል፡፡
 በከተማ አስተዳደሩ እና በፌደራል በመንግስት ግዥ እንዳይሳተፉ የታገዱ አቅራቢዎችን ዝርዝር ለሁሉም ባለበጀት
መ/ቤቶች በሰርኩላር ተደራሽ ተደርጓል፡፡
 ባለበጀት መስሪያ ቤቶች መመሪያና ደንቦችን እንዲያሟሉና እንዲይዙ የማድረግ ስራ ተሰርቷል፡፡
 የበጀት ዓመቱ ዕቅድ እና የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖረት ለሚመለከተው ዓካል ተደራሽ ማድረግ ተችሏል፡፡
 በአቅራቢዎች ዝርዝር ዌብ ሳይት ለተጠቃሚዎች የማስተዋወቅ እና ብዛታቸው 65 የሚደርሱ አቅራቢዎች
በዌብሳይቱ ራሳቸውን ችለው እንዲመዘገቡ በቢሮው በኩል ሙያዊ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል፡፡
 የ 2011 በጀት አመት የ 58 ባለበጀት መ/ቤቶች የተጠቃለለ የግዥ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ
የመተንተንና የመጠመር ስራ ተሰርቶ ግብረ መልስ ለሚለካታቸው አካላት ተደራሽ ተደርጓል፡፡
 የ 2012 በጀት አመት የ 48 ባለበጀት መ/ቤቶች የተጠቃለለ የግዥ እቅድ ቀርቦ የመተንተንና
የመጠመር ስራ ተከናውኖ ግብረ መልስ ለሚመለከታቸው አካላት ተደራሽ ተደርጓል፡፡
 የ 2012 በጀት አመት የ 56 ባለበጀት መ/ቤቶች የተጠቃለለ የግዥ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ
የመተንተንና የመጠመር ስራ ተሰርቷል፡፡
 የሴክተር መ/ቤቶች እና ክፍለ ከተሞች የግዥና ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የስራ ሂደቱ መነሻ የ BSC እቅድ
/እስኳር ካርድ/ በማዘጋጀት ለሚመለከተው አካል ተደራሽ ተደርጓል፡፡
 የበጀት አመቱን የዳይሬክቶሬቱን እና የቡድኑን እቅድ ለሚመለከተው አካል ተደራሽ ተደርጓል፡፡

ግብ 4. የመፈፀምና የማስፈጸም አቅም መገንባት በተመለከተ

 በበጀት ዓመቱ 12 ወራት ከ 4 ባለበጀት መ/ቤቶች በቀረበ የስልጠና ፍላጎት ጥያቄ መሰረት ለ 130
ባለሙያዎች በመንግስት ግዥ አስተዳደር ስርዓቱ ላይ የተሻለ አቅም እንዲኖር ለማድረግ ስልጠና
ተሰጥቷል።

Page 5 of 17
በበጀት አመቱ 12 ወራት በከተማ አስተዳደሩ ስር ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች ፣ ክ/ከተሞች እና ወረዳዎች
ስር ለሚገኙ ተቋማት በመንግስት ግዥ አስተዳደር ዙሪያ ተቋማዊ ስልጠና ለ 270 ፈፃሚዎችና አመራሮች
ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ በዚህ መሰረት በበጀት አመቱ ለ 300 አመራርና ፈፃሚ ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ
ለ 270 የተሰጠ ሲሆን አፈፃፀሙም 90 ፐርሰንት ነው፡፡
 የክትትልና ድጋፍን በተመለከተ በበጀት አመቱ 12 ወራት 90 ተቋማት ላይ ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ
ታቅዶ በ 110 ተቋማት ላይ ክትትልና ድጋፍ ተደርጎ ግብረመልስ የተሰጠ ሲሆን አፈፃፈሙም 122
ፐርሰንት ነው፡፡
 ለ 10 ክፍለ ከተሞች በተጨማሪም ከእቅድ ውጪ ማእከል እና ክፍለ ከተማን ጨምሮ ለ 102 የግዥና
ንብረት የስራ ክፍሎ ላይ ምዘና በማካሄድ ምዘናው በአግባቡ ለተከናወነበት የስራ ክፍል ግብረ መልስ
የመጠመር ስራ ተሰርቷል፡፡
 በተዘጋጀው የሴክተር መ/ቤቶች እና የክፍለ ከተማ የ 2012 በጀት አመት የ BSC እቅድ /እስኳር ካርድ/ ላይ
የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለ 1 ቀን ተሰጥቷል
 በበጀት ዓመቱ ባለሙያው ራስን ለማብቃት ባቀደው እቅድ መሰረት አንድ /1 / የዳይሬክቶሬቱ ባለሙያ
በአሰልጣኞች ስልጠና ላይ ለ 8 ቀናት የፌደራል የግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጄንሲ ባዘጋጀው በከፍተኛ
ደረጃ ሙያዊ ስልጠና አቅሙን እንዲገነባ ተደርጓል፡፡

ግብ 5. የአፈፃፀም ክትትል ድጋፍ ግምገማና ግብረ መልስ ስርዓትን ማሻሻል በተመለከተ

ተግባር 1.የግዥ አስተዳደር የኦዲተር ክትትል ሥራ ማከናወን

1. ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ፋይናንስ ጽ/ቤት ፡- የጀነሬተር ግዥ ከግዥ አፈጻጸም መመሪያ
ውጪ የተፈጸመ በመሆኑ ችግሩን በፈጠሩት ላይ የማስተካከያ እርምጃ ተወስዶ እንድናውቀው
በአካልና በስልክ ከተደረገው ውጭ መጋቢት 25 ቀን 2012 ዓ/ም በተጻፈ ደብዳቤ ጭምር
አሳውቀናል፡፡

2. የተፋሰስ እና አረንጓዴ አካባቢዎች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲን ፡- የግዥ ኦዲት አድርገን


በተላከላቸው ግኝት መሰረት አብዛኛውን ችግር ለማስተካከል እንደሚችሉ ፣ የተስተካከሉ
መኖራቸውንና የባሻ ወልዴ ችሎት ፕላዛ ህንጻ ግንባታ እና የተሸከርካሪ ጥገና ግኝትን በተመለከተ
ህዳር 05 ቀን 2012 ዓ/ም በቁጥር የተ/አ/አ/ል/አስ/ኤጀ/10988/2012 በተጻፈ ደብዳቤ ምላሽ
የተሰጠ ቢሆንም አሳማኝ እና ተጨባጭ ማስረጃ የሌለው በመሆኑ በድጋሚ እንዲሰጥ
በ 15/07/2012 ዓ/ም በተጻፈ ደብዳቤ ተጠይቋል፡፡

Page 6 of 17
3. የጉለሌ ክፍለ ከተማ ፋይናንስ ጽ/ቤት የግዥ ኦዲት አድርጎ ለላከልን ግኝት በኦዲት ግኝቶቹ
መሰረት ማስተካካያ እርምጃ መወሰዱ እንዲረጋገጥ ጥቅምት 03 ቀን 2012 ዓ/ም በተጻፈ ደብዳቤ
ግብረ መልስ ተልኳል፡፡

4. ከየካ ክፍለ ከተማ ፋይናንስ ጽ/ቤት ፣ ከኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ፋይናንስ ጽ/ቤት፣ ከጉለሌ
ክ/ከተማ ፋናንስ ጽ/ቤት ፣ ከአራዳ ክፍለ ከተማ ፋናንሽ ጽ/ቤጽ እና ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ
ፋይናንስ ጽ/ቤት የተላከልንን ኦዲት ሪፖርት በመቀበል በኦዲት ሪፖርቱ ዙሪያ የታትን ጠንካራና
ደካማ ጎኖችን በመለየት እና በመገምገም ግብረ- መልስ በድብዳቤ ተሰጥቷል፡፡
5. ለንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ጤና ጣቢያ፡-
 ጤና ጣቢያው CBC Machine ለመግዛት ባወጣው ውስን ጨረታ በግዥ አፈጻጸም ሂደቱ ላይ
ችግር እዳለበት ለቢሮአችን ጥቆማ በመድረሱ ምክንያት የግዥ አፈጻጸሙን ኦዲት አድርገን
በተገኘው ግኝት መሰረት እርምጃ እንዲወሰድ መጋቢት 01 ቀን 2012 ዓ/ም በቁጥር
ፋ/ቢ 25/8/64/1481 በተጻፈ ደብዳቤ ችግሩ የተፈጠረው በጤና ጣቢያው የአሰራር ስህተት
በመሆኑ ችግሩን በፈጸሙት ላይ የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ እና የመንግስት ሃብት ያለ
አግባብ ለወጪ ከመዳረጉ በፊት መፍትሄ ተሰጥቶ ይህ ደብዳቤ በደረሰ በ 10 ቀናት ውስጥ
እንድታሳውቁን ቢጠየቅም በወቅቱ መልስ ባለመሰጠቱ በተደረገው ክትትል በድጋሚ የማስተካከያ
እርምጃ ተወስዶ እንድናውቀው መጋቢት 25 2012 ዓ/ም በተጻፈ ደብዳቤ ጠይቀናል፡፡ በተላከው
ሪፖርት መሰረት ጤና ጣቢያው ግንቦት 5 ቀን 2012 ዓ/ም በቁጥር ን/ስ/ላ/ወ 11/ጤ/ጣ/12 በተጻፈ
ደብዳቤ የማስተካከያ እርምጃ መውሰዳቸውን በግብረ መልስ አሳውቀዋል ፡፡

6. የተፋሰስ አረንጓዴ አካባቢዎች ልማት እና አስተዳደር ኤጀንሲ የባሻ ወልዴ ችሎት ፕላዛ ህንጻ
ግንባታ የኦዲት ግኝት ኮንስትራክሽን ቢሮንም ስለሚመለከት በግኘቱ ላይ ምላሽ እንዲሰጥና
መረጃ እንዲላክል ሚያዚያ 05 ቀን 2012 ዓ/ም በተጻፈ ደብዳቤ እንድናውቀው ለቀረበ ጥያቄ
ግብረ -መልስ የተሰጠ ቢሆንም በህንጻው መፍረስ ላይ ውሳኔ የሰጠው የኮንስትራክሽን ቢሮ በአስር
ቀናት ውስጥ እንዲያሳውቁን ደብዳቤ ቢጻፍም እስካሁን ምላሽ አልተሰጠም፡፡

7. የቂርቆስ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና መኔጅመንት ጽ/ቤት ፡- የክፍለ ከተማው መሬት ልማትና
ማኔጅመንት ጽ/ቤት ጥቅምት 15 ቀን 2012 ዓ/ም በጨረታ ቁጥር መ/ል/ማ/ግ/0001/2012 ዓ/ም
የተለያዩ የጽህፈት እና የጽዳት እቃዎችን ለመግዛት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ግልጽ ጨረታ
ላይ የግዥ ውል አፈጻጸሙ ችግር እንዳለበት የተሰጠውን ጥቆማ መነሻ በማድረግ ግዥው
የመንግስት የግዥ መመሪያን ፣ ህግና ደንብን ተከትሎ የተፈጸመ ስለመሆኑ በኦዲት ለማረጋገጥ

Page 7 of 17
እና የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ ለማድረግ ኦዲት አድርገን ግብረ-መልስ መስጠታችንን መነሻ
በማድረግ ጽ/ቤታችሁ በቁጥር ቂ/ክ /ከ/መ/ል/ማ/17/ን/አስ/ጠ/5799/12 በቀን ሚያዚያ 01 ቀን
2012 ዓም በተጻፈ ደብዳቤ የተላከልን ምላሽ ጽ/ቤቱ የተፈጸመውን የግዥ ጥሰት ላለመቀበል
የተሰጠ ምላሽ በመሆኑና ከችግራቸው ለመውጣት ዝግጁ መሆናቸውን ባለማሳየታቸው የችግሩ
ባለቤት በሆኑት አመራርና የጥራት ኮሚቴ ላይ የማስተካከያ እርምጃ ተወስዶ እንድናውቀው
ሚያዚያ 08 ቀን 2012 ዓ/ም በተጻፈ ደብዳቤ ተጠይቆ ጽ/ቤቱ ሚያዚያ 28 ቀን 2012 በቁጥር
ቂ/ክ/ከ/መ/ል/ማ/ጽ/ቤት/17/6026/2012 በተጻፈ ደብዳቤ በእቃው በጥራት ኮሚቴ ምዘና የተፈጠረ ስህተት
በመሆኑ ውል ሲሰጥ የገንዘብ መጠኑ ከዋናው ግዥ ጋር ልዩነት የነበረውና በመንግስት ሀብት ላይ ሊደርስ
የነበረው የብር 716,671.80 ልዩነት በኦዲት ተገኝቶ ማዳን የተቻለ ሲሆን ጽ/ቤቱ ችግሩን አምኖና
ማስተካከያ በማድረግ ለተፈፀረው ስህተት ይቅራታ ጠይቀዋል፡፡ እንዲሁም የግዥ ክፍሉና የንብረት ክፍል
ተናበው ባለመስራታቸው ለተፈጠረው ስህተት ይቅርታ በመጠየቅ ስህተቱ እንዲታረም በማድረግ ለቢሮአችን
ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

8. የጎፋ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ የጥቆማ ኦዲት ተሰጥቶ ኮሌጁ ባወጣው ጨረታ የግዥ ስርዓትን
ያልተከተለ አካሄድ የነበረ በመሆኑ ጉዳዩን ከኮሌጁ ዲን እና ከሚመለከታቸው ሃላፊዎች ጋር
በመሆን ችግሩ መፍትሄ እንዲያገኝ እና የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድ በተሰጠው አስተያየት
ኮሌጁ ግዥውን በውስጥ ኦዲት ክፍል ኦዲት እየተደረገ መሆኑንና ችግሩን በፈጸሙት ላይ
የዲሲፕሊን እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ሚያዚያ 19 ቀን 2012 በቁጥር ጎ/ኢ/ኮ/1853/25/35
በተጻፈ ደብዳቤ ያሳወቁ ቢሆንም ተጨባጭ ማስረጃ እንዲያቀርቡ በድጋሚ ተጠይቆ ምላሽ
እየተጠባበቅን ነው፡፡
 ተግባር 2. የክትትልና ድጋፍን በተመለከተ በበጀት አመቱ 12 ወራት 90 ተቋማት ላይ ክትትልና ድጋፍ
ለማድረግ ታቅዶ በ 110 ተቋማት ላይ ክትትልና ድጋፍ ተደርጎ ግብረመልስ የተሰጠ ሲሆን አፈፃፈሙም
122 ፐርሰንት ነው፡፡
 ተግባር 3. የክትትልና ድጋፍ ቼክ ሊስት በመከለስ የማዘጋጀት ስራ ተከናውኗል፡፡

ግብ 6. ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ፍትሃዊ አገልግሎት መስጠት፣

 በመንግስት ግዥ አስተዳደር አዋጅ እና መመሪያዎች ላይ በጽሁፍ ለሚቀርቡ ማብራሪያና ከተፈቀዱ የግዥ


ዘዴዎች ውጪ የቀረቡ 350 የግዥ ፍቃድ ጥያቄዎቸን ቢሮው በተሰጠው ስልጣን መሰረት የግዥ ፈቃድ
ጥያቄዎችን የመፍቀድና ሙያዊ አስተያየት በፅሁፍ ምላሽ የመስጠት ስራ ተሰርቷል።
 በበጀት ዓመቱ በ 9 ወራት ለ 65 ባለሙያዎች በግዥ አፈጻጸም ሂደት ላይ ለምክር አገልግሎት ጥያቄ ምላሽ
የመስጠት ስራ ተሰርቷል።
 በስታንዳርዱ መሰረት የዕለት ስራዎች የመመዝገብ ስራ ተሰርቷ
Page 8 of 17
የ 2011 በጀት አመት እቅድ አፈፃጸም የ 62 ተቋማት

ተ.ቁ የግዥ ዘዴ የገንዘብ መጠን በፐርሰንት

1 ግልፅ አፈፃ 6,324,828,097.76 61%

2 ሁለት ደረጃ 4,331,199.15 0%

3 በመወዳደሪያ 3,865,184.70 0%

4 ውስን ጨረታ 292,844,711.16 3%

5 ዋጋ ማቅረቢያ 141,623,254.47 1%

6 አንድ አቅራቢ 3,650,840,476.57 35%

ድምር 10,418,332,923.76 100%

የ 2011 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ያላመጡ ተቋማት ለምሳሌ


መንገዶች ባለ ስልጣን
ውሃናፍሳሽ ባለስልጣን
ንግድ ቢሮ
ትራንስፖርት ባለስልጣን
ኮንስትራክሽን ቢሮ እና ሌሎች

Page 9 of 17
የ2011 በጀት አመት የእቅድ አፈፃፀምም የ62 ተቋማት
12,000,000,000.00

10,000,000,000.00

8,000,000,000.00

Axis Title 6,000,000,000.00


10,418,332,923.76
4,000,000,000.00
6,324,828,097.76
2,000,000,000.00 3,650,840,476.57

0.00 292,844,711.16
4,331,199.153,865,184.70 141,623,254.47
ግልፅ አፈፃ ሁለት ደረጃ በመወዳደሪያ ውስን ጨረታ ዋጋ ማቅረቢያ አንድ አቅራቢ ድምር

Page 10 of 17
የ 48 ባለበጀት መ/ቤቶች የ 2012 በጀት ዓመት የግዥ ዕቅድ ማጠቃለያ

በሁሉም የግዥ መወዳደሪያ


ዘዴዎች ዓመታዊ ግልጽ ጨረታ ሁለት ደረጃ ሃሳብ ውስን ጨረታ ዋጋ አንድ አቅራቢ ጠቅላላ ድምር
የግዥ ዕቅድ ጨረታ መጠየቂያ ማቅረቢ

986,228,888.9
ዕቅድ በብር 6,581,439,073.76 0.00 0.00 180,932,331.00 0.00 4 7,748,600,293.7
0

ዕቅድ በ% 85% 0% 0% 2% 0% 13% 100%

የ48 ባለበጀት መ/ቤቶች የ2012 በጀት ዓመት የግዥ ዕቅድ ማጠቃለያ


ዕቅድ በብር ዕቅድ በ% 7748600293.70
6581439073.76

986228888.94
85% 0.00
1.00 2.00
0% 0.00180932331.00
0% 4.002% 0.00
3.00 5.00 13% 7.00
0% 6.00 100%

ያ ያ ር
ረታ ረታ የቂ ረታ ረ ቢ ራ


ጨ ጨ ጠ ጨ ቅ አ ቅ ድ
ጽ ጃ መ ስን ማ ድ ላ
ግል ደረ ብ ው ጋ አ ን ቅላ
ለት ሃሳ ዋ ጠ
ሁ ሪያ
ዳደ

ይህ የዕቅድ ማጠቃለያ የ 48 ባለበጀት መ/ቤቶች ብቻ ሲሆን የ 2012 በጀት ዓመት የግዥ ዕቅድ ካላመጡ መ/ቤቶች መካከል
ለአብነት ከፍተኛ በጀት ከሚያንቀሳቅሱ ተቋማት መካከል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን፣ መንገድ
ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ፣ ጤና ቢሮ የመሳሰሉት ይገኙበታል፤

 በህትመት ስርጭትና ቁጥጥር ክፍል በአጠቃላይ 2012 ዓ/ም የ 12 ወራት ሪፖርት በተመለከተ 856,987 የተለያዩ
ህትመቶች ተሰራጭተዋል፡፡

ግብ 7. ውጤታማ የሀብት አጠቃቀምን ማሳደግ ፣

Page 11 of 17
 የምንገለገልባቸውን ቋሚና አላቂ ንብረቶች በደንብና መመሪያ መሰረት በአግባቡ በመጠቀም፣ የዳይሬክቶሬቱን በጀት፣
ሃብትና ንብረት በቁጠባና በተገቢው ሁኔታ ለታለመለት አላማ ጥቅም ላይ ለማዋል ጥረት ተደርጓል፣
ግብ 8 የኮሚኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት አሰራርን ማጠናከርን በተመለከተ

 ዳይሬክቶሬቱ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ለማስተዋወቅ ብሮሸር ተዘጋጅቷል፡፡

በበጀት አመቱ 12 ወራት የኦዲት ግኝቶችን በተመለከተ

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፋይናንስ ጽ/ቤትን በተመለከተ፦


 የክፍለ ከተማው ፋይናንስ ጽ/ቤት ግንቦት 14 ቀን 2011 ዓ/ም በጻፈው ደብዳቤ ትእዛዝ በፕሮፎርማ ዘዴ
የተፈጸመው የጀነሬተር ግዥ ኦዲት ተደርጎ ግዥው አነስተኛ ዋጋ ካቀረበው ድርጅት ባለመፈጸሙ መንግስት ብር
74,944 (ሰባ አራት ሺህ ዘጠኝ መቶ አርባ አራት) ያለአግባብ በማስወጣት ኪሳራ ኢንዲደርስበት ተደርጓል ፡፡
 በኦዲት በተደረገውም ክትትል የጨረታ ኮሚቴው የክህሎት ክፍተት ስለነበረበት በሚል እና አሸናፊ መሆን ይገባው
የነበረው ድርጅት በአቅራቢነት አልተመዘገበም በሚል የተሰጠ ግብረ-መልስ ቢኖርም ድርጅቱ በአቅራቢነት
የተመዘገበ መሆኑን ከቀረበው ማስረጃ ተረጋግጧል ፡፡

2. የተፋሰስና አረንጓዴ ልማት አስተዳደር ኤጀንሲን በተመለከተ፦

 የባሻ ወልዴ የአረንጓዴና ፕላዛ ግንባታ ግዥ በውሉ መሰረትና በተቀመጠው የስራ ዝርዝር እና ስፔክ Quantity
(BOQ) መሰረት የተገነባ መሆኑ ተረጋግጦ ርክክብ ሳይደረግ ባልታወቀ ምክንያት ከንቲባ ጽ/ቤት አዟል በማለት
እንዲፈርስ የተደረገ በመሆኑ በተደረገው ክትትል የኮንስትራክሽን ቢሮ ባቋቋመው ኮሚቴ ህንጻው ባለበት ዲዛይን
ተስተካክሎ (As Built Design) ይሰራ ብሎ ወስኖ እያለ ህንጻው ያለበት ደረጃ ሳይታወቅ ከአሰራር ውጭ ፈርሶ
ተገኝቷል፡፡
 ኤጀንሲው በብር 260,819.18 (ሁለት መቶ ስልሳ ሺ ስምንት መቶ አስራ ዘጠኝ ከ አስራ ስምንትሳንቲም)
የተሽከርካሪ ጥገና ሲያደርግ በወቅቱ በደብዳቤ ቁጥር ው/መ/80/53/11 በቀን 11/01/2011 ዓ/ም በተጻፈ ደብዳቤ
ቢሾፍቱ ብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ከመለስ ኪዳነ ማረያም ጋራዥ በቀጥታ እንዲጠገን ተወስኗል
ተብሎ ተሽከርካሪ በቀጥታ ግዥ መጠገኑ ፤

3. የየካቲት 66 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤትን በተመለከተ፦

Page 12 of 17
 የት/ቤቱ አሸናፊ ተደርጎ የመረጠው አቅራቢ ዲ.ኤል.ኤፍ ጠቅላላ የንግድ ስራ በቀረበለት የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ
ምን አይነት ኮምፒውተር ፣ ፕሪንተር ፣ ላፕቶፕ ፣ ዲጅታል የፎቶ ኮፒ ማባዣ ማሽን ጀስትነር እና ኤል.ሲ.ዲ
(LCD Projector) እንደሚያቀርብ ግልጽ ሳያደርግ በተለይም የፍላጎት መግለጫ Specification ሳይዘጋጅ
ከቀረቡት አቅራቢዎች መካከል ዝቅተኛ ዋጋ ስላቀረበ ብቻ ከግዥ መመሪያ ደንብ እና አሰራር ውጪ እቃዎቹ
ከመገዛታቸውም በላይ በውሉ እና አቅራቢው (ዲ.ኤል.ኤፍ ጠቅላላ የንግድ ስራ ድርጅት) ለክፍያ ባቀረበው ገንዘብ
መቀበያ ደረሰኝ እና ገቢ ደረሰኝ (ሞዴል 19 ) ላይ ጭምር የእቃው ሙሉ ስፔሲፊኬሽን (Specification) ሳይገለጽ
እቃዎቹ ንብረት ክፍል ገቢ መደረጋቸው እና ክፍያ ተፈጽሞ መገኘቱ የግዥ ህግን የተከተለ አስራር አለመሆኑ እና
የመንግስትን ጥቅም ያሳጣ መሆኑ ፤

4. የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ጤና ጣቢያን በተመለከተ፡-


 ጤና ጣቢያው ከበጎ አድራጎት ድርጅቶች የገንዘብ እርዳታ አገኘሁ ቢልም የግዥ መመሪያ አፈጻጸሙን
ተግባራዊ ባለማድግ ግዥው በውስን ጨረታ እንዲፈጸም መደረጉ፣
 በተገኘው በጀት ምን ምን መገዛት እንዳለበት ከለየ በኋላ እና የግዥ ሂደቱ ከተከናወነ እና ውል ተፈጽሞ
ማሽኑ በሞዴል 19 ቁጥር 896215 ገቢ ከሆነ በኋላ ክፍያ ለመፈጸም ለማሽኑ በጀት አልተያዘም ብሎ
ክፍያ ያለመፈጸም፣
 ጤና ጣቢያው ለሚገዛቸው እቃዎች የእቃ መግለጫ በአግባቡ የማያዘጋጅ መሆኑ፣
 ጨረታው በሁለት ኤንቨሎፕ እንዲቀርብ መደረግ የነበረበት ሲሆን በ ግዥ መመሪያው አንቀጽ 15 ተራ
ቁጥር 15.18.3 መሰረት ከ (ሀ እስከ ሸ ) በተቀመጠው ዝርዝር መስፈርት መሰረት መከናወን ሲገባው
የግዥ አፈጻጸሙ መመሪያን ያልተከተለ ስለመሆኑ የጨረታ ሰነዱ በፖስታ ታሽጎ ስለመግባቱ የሚያሳይ
ኤንቨሎፕ የጨረታ ኮሚቴዎች ተፈራርመውበት ከግዥ ሰነዶቹ ጋር ተያይዘው አለመገኘቱ ፤
 የውል አፈጻጸም ችግር መኖሩ ፣ በተላከው ሪፖርት መሰረት ጤና ጣቢያው የማስተካከያ እርምጃ
ወስደዋል፡፡

5. የትራፊክ ማኔጅመንት የጥቆማ ኦዲትን በተመለከተ፡-

የተሰጠው ጥቆማ ኤጀንሲው የዋጋ ማስተካከያ በማድረግ የመንግስት ገንዘብ ያለአግባብ እንዲወጣ እና ከግዥ አፈጻጸም ውጭ
ግዥ ለመፈጸም ተሞክሯል የሚል ሲሆን ነገር ግን ኤጀንሲው በሸተው የመደበኛ ጨረታ ሰነድ ክፍል ሶስት የዋጋ ማስተካከያን

Page 13 of 17
አስመለክቶ ስህተት ሲኖር የነጠላ ዋጋ ለውጥ ሳይደረግ አጠቃላይ ወደ ጎን ብዜት እና ጠቅላላ ዋጋ ላይ ትክክለኛውን
የነጠላ ዋጋ መሰረት በማድረግ ጨረታው ይፋ ከመሆኑ በፊት ማስተካከል እንደሚቻል እና ኤጀንሲውም ለሁሉም
ተጨራቾች ተደራሽ ያደረገውን በመደበኛ ጨረታ ሰነድ ውስጥ በክፍል ሶስት ላይ በተቀመጠው ህግ መሰረት
እንዲሁም በግዥ መመሪያው
አንቀጽ 34 ተራ ቁጥር 34.1 ከ ሀ-ሐ የተገለጹትን ስለአጠራጣሪ የዋጋ ማስተካከያ አሰስመልክቶ የተጠቀሱትን ነጥቦች
ተከትሎ የተሰራ መሆኑን በኦዲት አረጋገጠናል ፡፡ እንዲሁም በመደበኛ የግዥ ኦዲት በእቅድ የተያዘው ስራ ጨረታ
የሚከፈትበትን ጊዜ ለአቅራቢዎች ሳያሳውቁ በሌሉበት በመክፈት በግኝቱ ላይ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥበት ሪፖርት
ተልኮ ምላሹን እየተጠባበቅን ነው፡፡

6. የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ በስሩ ለሚገኙ ትምህርት ቤ/ቶች
4,800 ኮምባይን ዴስኮችን ለመግዛት ባወጣው ግልጽ ጨረታ ከስፔሲፊኬሽን ውጭ ግዥ መፈጸሙን በተመለከተ እና
የወረዳ 08 ህብረተሰብ ተሳትፎ የልማት ገቢ አሰባሰብና በቼኮች ወጭ ላይ ምዝበራ ስለፈጸሙ የማራጋገጥ ስራ
ተሰርቷል። በመሆኑም 4,800 ኮምባይንድ ዴስኮች ከስፔሲፊኬሽን ውጭ መገዛታቸውንና በራሪ ቼክና ጉርድ ቼክ ላይ
የገንዘብ መጠን አበላልጦ በመጻፍ ፈራሚዎች ባዶ ቼክ ላይ በመፈረም መንግስት ላይ የብር 1,771,703.84 ኪሳራ
እንዲደርስበት ተደርጓል ይህም ፡፡

7. የትራፊክ ማኔጅመንት በእቅድ የተያዘ ኦዲት 100 % ተጠናቆ ሪፖርት ተልኮ ምላሽ
እየተጠበቀ ሲሆን፡-
 በረካታ ግዥዎች የጨረታ ሂደቶች ህጋዊ የግዥ አፈጻጸም ስርዓትን የተከተሉ ባለመሆኑ የማስተካከያ
እርምጃ እንዲወሰድ ለኤጀንቺው ሪፖርት ተልኳል፡፡
8. የቂርቆስ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንትጽ/ቤት የጥቆማ ኦዲት 100%
ተጠናቆ በድጋሚ ግብረመልስ ጭምር ተጠናቆ የተላከ ሲሆን ፡-
 ጽ/ቤቱ ሚያዚያ 28 ቀን 2012 በቁጥር ቂ/ክ/ከ/መ/ል/ማ/ጽ/ቤት/17/6026
/2012 በተጻፈ ደብዳቤ በእቃው በጥራት ኮሚቴ ምዘና የተፈጠረ ስህተት በመሆኑ ውል ሲሰጥ የገንዘብ መጠኑ ከዋናው
ግዥ ጋር ልዩነት የነበረውና በመንግስት ሀብት ላይ ሊደርስ የነበረው የብር 716671.80 ልዩነት በኦዲት ተገኝቶ ማዳን
የተቻለ ሲሆን ጽ/ቤቱ ችግሩን አምኖና ማስተካከያ በማድረግ ለተፈፀረው ስህተት ይቅራታ ጠይቀዋል፡፡ እንዲሁም የግዥ
ክፍሉና የንብረት ክፍል ተናበው ባለመስራታቸው ለተፈጠረው ስህተት ይቅርታ በመጠየቅ ስህተቱ እንዲታረም በማድረግ
ለቢሮአችን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

Page 14 of 17
9. የጎፋ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ የጥቆማ ኦዲት ተሰጥቶ ጉዳዩን ከኮሌጁ ዲን እና ከሚመለከታቸው ሃላፊዎች ጋር
በመሆን ችግሩ መፍትሄ እንዲያገኝ የማማከር ስራ ተሰርቷል ፡፡
ያጋጠሙ ችግሮች

 በወቅቱ የግዥ አፈፃፀም ሪፖርቶችን ያለማቅረብ፤ አለመሟላት


 የግብአት አቅርቦት ችግር
 የ 2012 በጀት የግዥ እቅድ ወቅቱን ጠብቆ ያለማቅረብ፤
 ባለበጀት መ/ቤቶች ለቀረበ የጥፋተኝነት ሪፖርትና እንዲሁም አቅራቢዎች በግዥ ፈፃሚ መ/ቤቶች ላይ
የሚያቀርቡት ቅሬታና አቤቱታ መረጃና ማስረጃ በወቅቱ ማቅረብ አለመቻል
 የግዥ ባለሙያዎችና ኃላፊዎች ስራ መልቀቅና ለስራው የተመደቡት ሰራተኞች አዲስ መሆን፣
 የግዥ የክፍያ ሰነዶች መረጃዎች በአግባቡ ተደራጅቶ ያለመያዝ።
 ከዕቅድ ውጪ በሌሎች ደራሽ ስራዎች ምክንያት በዕቅድ የተያዙ ስራዎችን በወቅቱ ያለመተግበር፡፡
 በአዲሱ የጂ.ኤ.ጂ ኮንቨርሽን የደረጃ መቀነስ ፣ የስያሜ ለውጥ ፣ ያልተመዘነ ባለሙያ መኖር ወዘተ
በሰራተኞች ላይ በሁሉም መዋቅር ቅሬታ ያስነሳ መሆኑ

የተወሰዱ መፍትሔዎች

 ሪፖርቶችንና እቅዱን እንዲያቀርቡ በስልክና በአካል ድጋፍ ማድረግ


 ሰራተኛ እንዲመደብ ጥረት ማድረግ
 ያለውን የግብአት ችግር በተወሰነ ደረጃ እንዲፈታ ጥረት መደረጉ
 ተቋማት ከጥፋተኝነትና ከቅሬታ አቤቱታ ጋር ተያይዞ የሚቀርቡ መረጃዎች በወቅቱ እንዲቀርቡ
ተከታታይነት ያለው ክትትል ማድረግ
 ባለው የሰው ሀይል ስራዎች እንዲሰሩ ጥረት ማድረግ
 ለአዳዲስ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በአካል በመገኘት መደገፍና ስልጠና መስጠት፣
 አዋጅ፣ መመሪያና ማኑዋል በሀርድና በሰፍት ኮፒ እንዲደርስ ተደርጓል፣
 መረጃውን በአግባቡ አደራጅተው እንዲይዙ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ ተሰርቷል።
 በየደረጃው ያለው ቅሬታ ተደራጅቶ እንደቢሮ እንዲታይ ለፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ እንዲቀርብ መደረጉ

የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ

 የለውጥ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል

Page 15 of 17
 የክትትልና ድጋፍ ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል፤
 የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር ለመቀነስ የተጀመረውን የተለያዩ የአቅም መገንቢያ
ስልጠናዎች መስጠት፣
 በአዲሱ አደረጃጀት የሰው ሀይል እንዲሟላ ከሚመለከተው አካል ጋር በመነጋገር ጥረት ማድረግ
 በጂ.ኤ.ጂ ኮንቨርሽን ላይ የተነሱት ቅሬታዎች እንዲፈቱ ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን ክትትል
ማድረግ

Page 16 of 17
Page 17 of 17

You might also like