You are on page 1of 18

በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን


የቅርንጫፍ ሶስት ጽ/ቤት
THE FEDERAL DEMOCRATIC REPUBLIC OF ETHIOPIA
FEDERAL HOUSING CORPORATION
BRANCH THREE OFFICE

ህዳር 30 /2013 ዓ.ም

የ2013 በጀት ዓመት የህዳር ወር

የውጤት ተኮር ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት


የ ው ጤ ት ተ ኮ ር ዕ ቅ ድ አ ፈ ጻ ጸ ም ሪአዲስፖአበባር ት

[Type text] Page 0


ክፍል አንድ

1.1. መግቢያ

በፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የ 2013 በጀት ዓመት የህዳር ወር ሪፖርት የኮርፖሬሽኑን እቅድ መነሻ ተደርጎ ከተዘጋጀው
ዓመታዊ እቅድ ተነጻጽሮ የቀረበ ነው፡፡

የሪፖርቱ ዓላማ የእቅድ አፈጻጸምን ለመገምገም ሲሆን በውስጥ የተካሄዱ የክትትልና እና ሳምንታዊ ግምገማ መሰረት
የአፈጻጸም ደረጃ ያለበትን ማወቅ፣ ችግሮችን ለይ ለቀጣይ ዓመት እንዳይደገም መፍትሄ ለመስጠት፣ ግልጽነትና
ተጠያቂነትን ለማምጣት ነው፡፡

ሪፖርቱ ሲዘጋጅ የመረጃ ምንጭ ያደረጋቸው በየሳንምቱ የተካሄደውን የሚኒ ማኔጅመንት ግምገማና አቅጣጫዎች፣
የለውጥ ስራዎች አፈጻጸም መረጃዎችን ፣ ሪፖርቶችን ከየቡድኖች የቀረቡ የአፈጻጸም ሪፖርቶች እና የመደበኛና
ድንገተኛ ሱፐርቪዥን ውጤቶችን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ ሲሆን 280 ቤቶችን ውል በማደስ፣ በውስጥ አቅም 41
ቤቶችን እና በደንበኞች 46 ቤቶችን በመጠገን እና 2,397,000. ብር ሰብስበናል፡፡

የኮሮና ቫይረስን ለመከላከልና የሰራተኞችን ደህንነት ለመጠበቅ ስራ ላይ ላሉት ሰራተኞች ግንዛቤ የማስጨበጥ፣
አገልግሎት ሲሰጥ የአንድ ሜትር ርቀት ለማስጠበቅ ተችሏል፣ ተገልጋይ ለአገልሎት ሲገቡ ማስክ እንዲጠቀሙ
እየጠየቅን ነው፣ ስራተኞቻችን በሙሉ በራሳቸው ወጭ ማስክ እዲጠቀሙ እየተደረገ ሲሆን መግቢያ ላይ የእጅ
ማስታጠብ ስራ እና የሙቀት መለካት እየተከናወነ ይገኛል፡፡

የሪፖርቱ አቀራረብና የመረጃ ትንተና በተመለከተ የኢላማ አፈጻጸም ከእቅድ ጋር በማነጻጸር ተዘጋጅቷል፡፡ በዚህም
መሰረት ሪፖርቱ ስምንት ክፍሎች ያሉት ሲሆን፤ በክፍል አንድ መግቢያ፣ በክፍል ሁለት የ 2013 በጀት ዓመት የህዳር ወር
ኦፕሬሽናል ግቦችና ዋና ዋና ተግባራት አፈጻጸም፤ በክፍል ሦስት ታቅደው ያልተከናወኑ ተግባራት ከነምክንያታቸው፣
ክፍል አራት ሳይታቀዱ የተከናወኑ ተግባራት፣ ክፍል አምስት በአፈጻጸም ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ የመፍትሄ
እርምጃዎች፣ ክፍል ስድስት የክትትልና ግምገማ ተግባራት፣ ክፍል ሰባት መደምደሚያ፣ ፈታኝ ሁኔታዎችና ወደፊት
ሊወሰዱ የሚገባቸው እርምጃዎች፤ ክፍል ስምንት ደካማና ጠንካራ ጎኖችን እና በመጨረሻም ማጠቃለያ አካትቶ የያዘ
ነው፡፡

የ ህዳር ወር Page 1
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

ክፍል ሁለት፡- ራእይ ተልእኮና ዕሴቶች

2.1. ተልዕኮ

ለኮርፖሬሽኑ ደንበኞች ደረጃቸውን የጠበቁ ቤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብና በማስተዳደር በቤት


ፍላጎትና አቅርቦት መካከል የሚታየውን የገበያ ጉድለት በማሟላት ሂደት አስተዋጽኦ በማድረግና ተወዳዳሪና
አትራፊ መሆን፡

2.2. እሴቶች

 ታማኝነት ፡ ሃላፊነታችንን በመወጣት ሂደት ወጥና ተቀባይነት ያለው አቀራረብ ይኖረናል፡፡


 ውጤታማነት ፡ የምንሰጠው አገልግሎት በእውቀት የተመሰረተና በወቅቱ በመስጠት ደንኞቻችንን
እናረካለን፡፡
 ፍትሃዊነት ፡ የምንሰጠውን አገልግሎት ያለአድሎ እናቀርባለን፡፡
 ግልጽነት ፡ ኮርፖሬሽኑ የሚሰጠውን አገልግሎት በተመለከተ ትክክለኛ ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ
እንሰጣለን፡፡
 የቡድን ስራ፡ የኮርፖሬሽኑን ግቦች ለማሳካት በቡድን እንሰራለን፡፡
 ፕሮፌሽናሊዝም፡ ስራዎቻችንን ግብረገብነት በተሞላውና ጥራትና ስታንዳርድ የጠበቀ
እንዲሆን እናደርጋለን፡፡
2.3. ራዕይ
በቤት ልማትና አስተዳደር ዘርፍ መሪ ኮርፖሬት ተቋም ሆኖ ማየት፡፡
2.4. ስትራቴጂያዊ የትኩረት መስኮች እና ውጤቶች
ቅርንጫፍ ሶስት ጽህፈት ቤት የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካትና ራዕዩን እውን ለማድረግ የሚያስችል እና ትኩረት
የሚደረግባቸውን መስኮች ለመለየት ከተቋማዊ ዳሰሳ በተለይም ተገልጋዮችና ባለድርሻ አካላት ፍላጎት ከውስጣዊ
ጥንካሬና ድክመቶች እንዲሁም ከመልካም አጋጣሚና ስጋቶች እና በስትራቴጂያዊ ትግበራ ሂደት የተገኙ
ተሞክሮዎችን መሠረት በማድረግ የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ስትራቴጂያዊ እቅድ መነሻ የሆኑ የትኩረት መስኮች እና
ከስትራቴጂያዊ የትኩረት መስኮች የሚጠበቁ ውጤቶች በቅደም ተከተል እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

ተ.ቁ. የትኩረት መስኮች ስትራቴጂያዊ ውጤቶች


1 ተቋማዊ አቅምን ማሳደግ ያደገ ተቋማዊ አቅም

2 የቤት አቅርቦትን ማሳደግ ያደገ የቤት አቅርቦት

3 የቤት አስተዳደርን ማሻሻል የተሻሻለ የቤት አገልግሎት

የ ህዳር ወር Page 1
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

2.5. ስትራቴጂያዊ ግቦች

ተ.ቁ ዕይታዎች ስትራቴጂያዊ ግቦች

1 የፋይናንስ ዕይታ (30%) 1. ትርፋማነትን ማሳገደግ (22%)


2. የፋይናንስ አስተዳደርን ማሻሻል (8%)
2 3. የደንኞችን እርካታ ማሳደግ (15%)
የተገልጋይ እይታ (15%)
4. የቤት አስተዳደር ቀልጣፋ ማድረግ (20%)
3 ውስጥ አሰራር (40%) 5. የኮርፖሬት አሰራርን ማሻሻል (15%)
6. ቅንጅታዊ ሥራዎችን ማሻሻል (5%)
መማማርና እድገት ዕይታ 7. የሰው ሃብት አቅም ግንባታና አስተዳደርን ማሻሻል (12%)
4
(15%)
8. የቴ ክ ኖ ሎ ጂ አቅ ም ና አጠ ቃ ቀ ም ማ ሳደግ (3%)

የአፈጻጸም አቅጣጫዎች

1. የተቋም አቅም ግንባታ ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመሥራትና ምቹ የሥራ አካባቢን መፍጠር፣

2. የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመሰረቱ በመፍታት እና በአገልጋይነት መንፈስ በመንቀሳቀስና

የደንበኞችን ቅሬታ በወቅቱ ለመፍታት የሚያስችል የቅሬታ አፈታት ሥርዓት ዘርግቶ መንቀሳቀስ፣

3. ለቤቶች ተገቢውን ጥበቃ በማድረግና ይዞታዎቻችን በህግ አግባቡ የተጠበቁ እንዲሆን ማድረግ፣

4. የጥገና ሥራዎችን በውስጥና በውጭ እንዲሁም በተከራዮች ተሳትፎ ለማከናወን የሚያስችል ጠንካራና

የተቀናጀ ሥርዓት መዘርጋት፣

5. የህንጻ ተቋራጮች ቅጥር የተቋራጨች ዐቅም በቂ መሆኑንና ለላስፈላጊ የጥገና ሥራ መጓትት

የማይዳርግ መሆኑን ማረጋገጥ፣

6. ተጠያቂነትና ግልጽነት የሰፈነበት የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋትና የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰቦችን

ነቅቶ መዋጋት፤

7. በባለቤትነት መንፈስ የተቋሙን ውስን ሀብትና ንብረት በአግባቡ ስራ ላይ በማዋል በአመራሩና

በሠራተኛው ውስጥ ስነ ምግባራዊ እሴቶችንና አስተሳሰቦችን በማስረጽና አገልግሎት አሰጣጦችን

ከሙስና የጸዳ እንዲሆን ማድረግ፣

8. የመረጃ አያያዝና አጠቃቀም ሥርዓታችንን በማዘመንና የተቋሙን ሥራዎች ሊደግፍ የሚችል ዘመናዊ

የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት መገንባት፤

9. ሥራዎቻችንን በህዝብ ግንኙነትና በኮሙዩኒኬሽን ስትራቴጂዎች ቀርፆ ተግባራዊ የማድረግ አሠራር

እንዲኖር ማድረግ፡

የ ህዳር ወር Page 2
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

10. በቤት አስተዳደር ዘርፍ ሚሰጡ አገልግሎቶች ሴቶችን፣ ወጣቶችን፣ ሕፃናትን፣ አዛውንቶችንና

ከኤችአይቪ ጋር የሚኖሩትን አካታች መሆናቸውንና ተጠቃሚነታቸውንም የሚያረጋግጡ እንዲሆኑ

ማድረግ፣

11. ለዘርፉ ስራ የሚጠቅሙ ምርጥ ተሞክሮዎችን መቀመርና ማስፋፋት፣

12. ከደንበኞች፣ ከባለድርሻና ከተባባሪ አካላት ጋር የተቀናጀና የደንበኞችን ተሳትፎ የሚያረጋግጥ ሥርዓት

መዘርጋት ፡፡

ክፍል ሶስት፡

የ 2013 በጀት ዓመት የህዳር ወር ዕቅድ አፈጻጸም በዕይታ መስኮች

ስትራቴጂያዊ ግቦች፣ ኦፕሬሽናል ግቦችና ዋና ዋና ተግባራት


I. የፋይናንስ ዕይታ(30%)

ስትራቴጂክ ግብ 1፡-ትርፋማነትን ማሳደግ (22%)


ኦፕ.ግብ 1፡- ገቢ የተደረገ ብር 8,812,000 ለመሰብሰብ ታቅዶ 2,397,305.41 ብር በመሰብሰብ 27.20 ፐርሰንት
ተከናውኗል፡፡ (16%)
ተግባር፡-1 መደበኛ ገቢ የሚሰበሰብባቸውን የመኖሪያ ቤት፣ የንግድና የድርጅት ቤት እንዲሁም ሽንሽኖችን
በመለየት መረጃቸውን ለመያዝ ታቅዶ 100 ፐርሰንት ተከናውኗል፤

ተግባር፡-2 ከመደበኛ ከቤቶች ኪራይ 8,633,000 ብር በመሰብሰብ ገቢ ለማድረግ

ታቅዶ 1,153,620.50 ብር በመሰብሰብ 13.36 ፐርሰንት ተከናውኗል፤

ተግባር፡-3 መደበኛ ኪራያቸውን በወቅቱ ያልከፈሉትን ደንበኞች በመለየት በወቅቱ ባልከፈሉት ላይ በመመሪያው መሰረት
እርምጃ በመውሰድ ውዝፍ 208,000 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ብር 68,798.20 በመሰብሰብ
33.076 ፐርሰንት ተከናውኗል፣

ተግባር፡-4 ቅጣትና እና ከልዩ ልዩ ገቢ 48,000 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 116,236.71 ብር

በመሰብሰብ 242.16 ፐርሰንት በላይ ተከናውኗል፡ ክንውኑ የጨመረው በጨረታ ገቢ ስለጨመረ


ነው፡፡

ተግባር፡-5 የኮርፖሬሽኑ ደንበኞች ውላቸውን በወቅቱ እንዲያድሱ በማድረግ የውል ዕድሳት አገልግሎት ክፍያ
48,000 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 58,650.00 ብር በመሰብሰብ 122.19 ፐርሰንት ተከናውኗል፡፡

የ ህዳር ወር Page 3
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

ኦፕ.ግብ 2.፡- ወጪ ቆጣቢ የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት ከደንበኞች ጋር የወጪ መጋራት አሰራርን በመዘርጋት የቀነሰ
ወጭ ብር 625,000 ብር ታቅዶ 1.62 ሚሊየን ብር በመሰብሰብ 260 ፐርሰንት ተከናወኗል፣ (4%)

ተግባር፡-.1 በጽህፈት ቤቱ ወጪ ቆጣቢ የአሰራር ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ ታቅዶ በወረቀት አጠቃቀም፣
የግንባታ ተነቃይ እቃዎችን መልሶ የመጠቀም ስራ ተከናውኗል፤

ተግባር፡-2 የጽህፈት ቤቱ የወጭ አጠቃቀምና ሃብት በመመሪያ መሰረት መፈጸሙን ማረጋገጥ

ተግባር፡-3 ደንበኞች በጥገናና በሌሎች አገልግሎቶች ላይ እንዲሳተፉ በማድረግ 625,000 ብር ለመሰብሰብ


ታቅዶ 1.62 ሚሊየን ብር ግምት ያለው ስራ በማሳተፍ ከእቅድ በላይ ተሰርቷል፡፡

ኦፕ.ግብ 3፡- ተዘጋጅቶ የቀረበ በጀትና የበጀት አጠቃቀም ሪፖርቶችና ወቅታዊ የሂሳብ መግለጫዎች፣ (2%)

ተግባር፡-.1 ዓመታዊ በጀት ማዘጋጀትና ለማስጸደቅ ታቅዶ ተከናውኗል፣

ተግባር፡-2 ወቅታዊ የበጀት አጠቃቀም ሪፖርት በየወሩ፣ በየሩብ ዓመቱና የዓመቱን በማዘጋጀት ለሚመለከተው አካል
ሪፖርት መላክ፣

ተግባር፡-3 በየወሩ የበጀት አጠቃቀምን ትክክለኛነት በማረጋገጥና በመገምገም ለሥራ ክፍሎች ግብረ-መልስ ለመስጠት
ታቅዶ ተከናውኗል፤

ተግባር፡-4 በየሩብ ዓመቱ የአጭር ጊዜ ሂሳብ መግለጫ ሪፖርት ተዘጋጅቷል፣

ስትራቴጂክ ግብ 2፡-የፋይናንስ አስተዳደርን ማሻሻል (8%)


ኦፕ.ግብ- 4 ኦዲት በተደረጉ በጽህፈት ቤቱ ሂሳብ ሪፖርቶች ላይ የተሰጡ አሉታዊ አስተያየቶችን በማረም ከ
2010 በጀት ዓመት ሂሳብ ጀምሮ የተሻለ የኦዲት አስተያየት እንዲገኝ ለማድረግ (4%)

ተግባር፡-1 ሊሰበሰቡ በማይችሉ ተሰብሳቢዎች መረጃ አደራጅቶ ለዉሳኔ እንዲሰጥ አደራጅቶ አቅርበናል፣

ተግባር፡-2 ለሌች የተሰጡ የኦዲት አስተያቶች ተቀብሎ ለማረም ታቅዶ አስተያየት ስላልቀረበ
አልተከናወነም፡፡

ኦፕ.ግብ-5፡ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ አዋጅ ቁጥር 847/2006 (Iternational


Financial Reporting Standards /IFRS/) ተግባራዊ ለማድረግታቅዶ 2009 እና የ 2010
ተሰብሳ ከሌጀር በማጥራት ለፋይናንስ ዳይሬክቶሬት አቅርበናል፡፡ (4%)

ተግባር፡-1 በአለም አቀፍ የሂሳብ ሪፖርት አዘገጃጃት ላይ ለአማካሪ ድርጅት የሚያሰፈልጉ ሰነዶችን ለማቅረብ
ታቅዶ የተጠየቅናቸውን መረጃዎች አቅርበናል፡፡

ተግባር፡-2 የ 2010 እና የ 2011 በጀት ዓመት የሂሳቦች በዓለም አቀፍ የሂሳብ ሪፖርቶች አዘገጃጀት ደረጃዎች
መሰረት የሂሳብ ሪፖርቶች ለማዘጋጀት መረጃ ለማቅረብ ታቅዶ 2009 እና የ 2010 ተሰብሳ
ከሌጀር በማጥራት ለፋይናንስ ዳይሬክቶሬት አቅርበናል፡፡

I I. የተገልጋይ ዕይታ 15%


ስትራቴጂክ ግብ 3፡- የደንበኞችን እርካታ ማሳደግ (15%)

የ ህዳር ወር Page 4
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

ኦፕ.ግብ 6 ፣ የተጠናከሩና ተሳትፎአቸው የተረጋገጠ በጽህፈት ቤቱ ያሉ 16 የአፓርታማና 1 ቁጠባ ነዋሪዎች ማህበራት


ለማጠናከር ታቅዶ ለአስራ ስድሰቱ አፓርታማ ማህበራትና ለአንድ ቁጠባ ማህበር የማጠናከር ስራዎች
ተከናውነዋል፣ (5%)

ተግባር፡-1- የ 16 አፓርታማ ነዋሪዎችን ማህበራት ለማጠናከርና ለአንድ ቁጠባ ማህበር የማጠናከር ስራዎች
ታቅዶ በ 16 ቲም ማህበራት ላይ ያሉ ነዋሪዎችን የማወያየት ሰራ ተሰርቷል

ተግባር፡-2- የአንድ የቁጠባ ማህበራትን ማጠናከር 2 የቁጠባ ማህበር የማቋቋም ሰራ ለመሰራት የታቀደ ሰሆን
አንዱን የቁጠባ ማህበር በዚህ ወር ተቋቁሟል

ኦፕ.ግብ .7፣ተግባራዊ የተደረገ የደንበኞች ማስተናገጃ ማኑዋል ስላልጸደቀ አልተከናወነም (0.5%)

ተግባር፡ 1- የተዘጋጀውን የደንበኞች ማስተናገጃ ማንዋል በብሮሸር ለማሰራጨት ታቅዶ ማኑዋል ስላልጸደቀ
አልተከናወነም ፡፡

ተግባር፡2. ማኑዋሉን ተግባራዊ ለማድረግ ታቅዶ ማኑዋል ስላልጸደቀ አልተከናወነም፡፡

ኦፐ.ግብ .8፣ የዜጎች ቻርተር ተግባራዊ ለማድረግ ታቅዶ በስተንዳርዱ መሰረት ለመስራት ጥረት ተደርጎ የውል እድሳት፣
የዘርፍ ለውጥ በስታንዳርዱ መሰረት ሲሰራ ጥገና በስታንዳርዱ መሰረት አልተከናወነም (2%).

ተግባር፡1. የዜጎች ቻርተር ለማሰራጨት ታቅዶ 175 ብሮሸሮች በማዘጋጀት ተሰራጭቷል፤

ተግባር፡3. ቻርተሩን ተግባራዊ ለማድረግ ታቅዶ 175 ብሮሸሮች በማዘጋጀት ተሰራጭቷል፣

ኦፕ.ግብ 9፣ ከደንበኞች የሚቀርቡ ቅሬታዎችንና የአገልግሎት ጥያቄዎችን በመመሪያውና በአሠራር ሥርዓቱ በወቅቱ
ምላሽ ያገኘና የተፈጠረ የደንበኞች እርካታ 75 ፐርሰንት ለማድረስ ታቅዶ በ 2012 እንደተለካው 73.05
ደርሷል፤ (4%)

ተግባር 1. በደንበኞች የሚቀርቡ ቅሬታዎችን በመቀበል በወቅቱ የጽሁፍ ምላሽ ተሰጥቷል፣

ተግባር 2. የቀረቡ ቅሬታዎችን በመቀበል አገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል ታቅዶ ከማህደር መፈለግ ጋር
የተያያዘውን ችግር ለመፍታት የመረጃ ማዘመን ስራ ሰርተናል ፣

ተግባር 3. የደንበኞችን እርካታ ከ 72 ወደ 75 ፐርሰንት ለማድረስ ታቅዶ አሁን ያለው የደንበኞች እርካታ ደረጃ
2012 መጨረሻ በተለካው መሰረት 73 ፐርሰንት ላይ ይገኛል፡፡

III. የውስጥ አሰራር ዕይታ(40%)


ስትራቴጂክ ግብ 4፡- የቤት አስተዳዳር ቀልጣፋ ማድረግ (20%)
ኦፕ.ግብ 10፡ መረጃ ወቅታዊና ዘመናዊ ማድረግ ና የአገልግሎት ጥራት አፈፃፀም ማሻሻል (1%)
ተግባር፡-1 የሚሰጡ አገልግሎቶች በስታንዳርድ መሰረት መሆናቸውን ለመከታተል ታቅዶ በአነሰ ሰዓት 3
አገልግሎቶች (አዲስ ተከራይ ውል ማዋዋል 30 ደቂቃ የነበረው በ 25 ደቂቃ፣የውል እድሳት 25
ደቂቃ የነበረው በ 20 ደቂቃ፣እና የዘርፍ ለውጥ 1 ሰዓት የነበረው በ 30 ደቂቃ) በእኩል ሰዓት
የተከናወኑ አራ አገክግሎቶች ( የንግድ ቤት ውል እድሳት፣ የመኖሪያ ቤት ቅያሬ፣ በውር፣ በፍቺ
ስም ዝውውር እን የመልካም ስም ሽያጭ)፣ ከስታንዳርዱ የበለጠ ጊዜ የወሰዱ የአገልግት ለውጥ
አድርገው ውል የሚሞሉ ናቸው በዚህ አግባብ አየተከናወነ ነው፤

የ ህዳር ወር Page 5
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

 አገልግሎት ለመስጠት ውል ፈጻሚዎችን፣ የመረጃ ባለሙያን፣ የቤቶች አስተዳር ቡድን መሪ እንደ ስራ ፍሰት
እንዲገናኙና የስራ ትእዛዝ መስጠትና መቀበል እንዲሁም ሪፖርት በቀጥታ ማየት ሚያስችል አሰራር
የወረቀት አልባ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል፡፡

ተግባር 2፡ የሚኖሩ ለውጦችን በየወሩ ወቅታዊ ለማድረግ ታቅዶ ተከናውኗል፡፡

ኦፕ.ግብ 11፡- በመመሪያው መሰረት የተለቀቁ/የተመደቡ 5 የመኖሪያ ቤቶች ታቅዶ 11 አስለቅቀናል፡፡

ተግር 1፡ በተለያየ ምክንያት በቅርንጫፉ የሚለቀቁ 5 የመኖሪያ ቤቶችን መረጃ ማደራጀትና ለማሳወቅ
ታቅዶ 11 አስለቅቀን 220 ፐርሰንት ተከናውኗል፡፡

ተግር 2፡ ቤት የተመደበላቸውን አካላት በመመሪያው መሰረት 2 ቤቶች ውል እንዲፈጽሙ ለማድረግ ታቅዶ 11


ቤቶ ውል ፈጽመው 550 ፐርሰንት የቤት ርክክብ ተደርጓል፣

ኦፕ.ግብ 12፡- በመመሪያው መሰረት በጨረታ የተከራዩ 10 የንግድ ቤቶች መረጃ ለማከራየት ታቅዶ 10 ቤቶ አሸናፊ
የቀረበባቸው ሲሆን 7 ቤቶች ውል ሞልተዋል 3 ተጠባባቂ ጠርተናል ዉል ለመፈጸም በዝግጁት ላይ እንገኛለን (100%).

ተግባር፡- 1 የተለቀቁ የንግድ ቤቶችን መረጃ በተሟላ ሁኔታ አደራጅቶ ለመያዝ ታቅዶ 3 ቤቶቸ መረጃ
አደራጅተን ይዘናል፡፡

ተግባር፡-2 በመመሪያው መሰረት ባዶ ንግድ ቤቶች ልኬት ተዘጋጅቷል፣

ተግባር.3 አሸናፊዎቹ በመመሪያው መሰረት ውል እንዲፈጽሙ በማድረግ የቤት ርክክብ ለማከናወን 10


የታቀደ ሲሆን 7 ቤቶች በጨረታ አሸናፊ አግኝተው የቅሬታ መስሚያና ውሳኔ ጊዜ ሲጠናቀቅ
ውል ሞልተዋል 3 ተጠባባቂ ጠርተናል ሲቀርቡ ሲላክልን ዉል ለመፈጸም በዝግጁት ላይ
እንገኛለን፣

ኦፕ.ግብ 13፡-በቤቶች አስተዳደር መመሪያ መሠረት ደንበኞች እየተገለገሉ መሆኑን በመስክ ክትትል በማረጋገጥ ለ 242
ቤቶች ውል ለማደስ ታቅዶ ለ 280 ቤቶች ውል በማደስ 115.70 ፐርሰንት ተከናውኗል፣ (115%)
አፈጻጸም ከፍ ያለ ምክንያት ከፍተኛ ቅሰቀሳ ሰለተደረገ ነው፡፡

ተግባር፡-1 የመስክ ክትትል ሥራ በመስራት በ 242 ቤቶች በቤቱ የሚገለገሉ ተከራዮች ህጋዊነትና በውሉ መሰረት ቤቱን
እየተጠቀሙ መሆኑን ለማጣራት ታቅዶ 280 ቤቶች ላይ ማጣራት አፈጻጸም ከፍ ያለ ምክንያት ከፍተኛ
ቅሰቀሳ ሰለተደረገ ነው፡፡

ተግባር፡-2 በመስክና በማህደር የተከራይን ህጋዊነት በማረጋገጥ የኪራይ ለ 242 ቤቶች ውል ዕድሳት
ለመፈጸም ታቅዶ ለ 280 ቤቶች ውል በማደስ 115.70 ፐርሰንት ተከናውኗል፡፡

ተግባር፡-3 ከቤቶች አስተዳደር መመሪያ ውጭ በቤት ውስጥ እየተገለገሉ የሚገኙ ደንበኞች ላይ ተገቢውን
የማስተካከያ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል ፡፡

ተግባር 4 አበል የሚከፈላቸው የቀድሞ ባለቤቶችን መረጃ ማደራጀትና ወቅታዊ በማድረግ ለክፍያ ለማስተላለፍ
ታቅዶ 100 ፐርሰንት ተከናውኗል፣

ኦፕ.ግብ 14፡- የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ያልወጣላቸው ቤቶች ካርታ ለማሰራት ታቅዶ ክትትል የተደረገ
ቢሆን በክለ ከተማው ካርታ አልተዘጋጀም፡፡(2%)
ተግባር፡-1 ካርታ ያልወጣላቸውን 17 ቤቶች መረጃ አደራጅቶ ለአዲስ አበባ አስተዳደር ተላልፏል፡፡

የ ህዳር ወር Page 6
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

ተግባር፡-2 ካርታ ያልወጣላቸውን ቤቶች ካርታ እንዲወጣላቸዉ ክትትል እየተደረገ ይገኛል፡፡

ተግባር፡-3 ካርታ ኮፒ ከማህደር ማያያዝ ታቅዶ በዚህ ወር ምንም የካርታ ኮፒ ሰላልመጣልን ኮፒ አድርገን
በየማህደሩ ያለሰርን ቢሆንም በመሰከረም ወር 26 ቤቶች ካርታ ከማህደር ተያይዟል፡፡

ተግባር፡-4 ካርታ የወጣላቸው ቤቶችን የይዞታ ምዝገባ በተጀመረበት አካባቢ የይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት
እንዲሰጣቸው ለማድረግ 5 ታቅዶ ምዝባ በከተማ አስተዳደሩ ስላልተጀመረ አልተከናነወም፣

ኦፕ.ግብ 15፡- ተጣርቶና ተረጋግጦ የተሰጠ ይዞታ ነክ እና የቴክኒክ መረጃ ፣ (1%)

ተግባር፡-1 ጥያቄ ተቀብሎ መረጃ ለማረጋገጥ ታቅዶ የአንድ ጥያቄ ቀርቦ ገንዘብ እንድያሲዙ ተደርጓል፡፡

ተግባር፡-.2 በተረጋገጠው ማስረጃ መሰረት ወቅታዊ ምላሽ መስጠት፣

ኦፕ.ግብ 16፡- ተለይተው ካሳ የተከፈለባቸዉ 6 ቤቶች፣ (1%)

ተግባር፡-1 በተለያየ ምክንያት የፈረሱ ቤቶችን መረጃ ማጥራትና ወቅታዊ ለማድረግ ታቅዶ ተከናውኗል፣

ተግባር፡-2 ካሣ ያልተከፈለባቸውን 7 ታቅዶ 13 ቤቶች በመረጃው መሰረት ክፍያው እንዲፈጸም የቅርብ ክትትል
ለማድረግ ታቅዶ ክትትል የተደረገ ነው፡፡

ኦፕሬሽናል ግብ 17፡- በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ያሉ ጉዳዮችን ክትትል ለማድረግ ታቅዶ 5 ቤቶች በፍርድ ቤት ክርክር ላይ
ይኛሉ፣ (1%)

ተግባር 1፡- ክርክር እየተደረገባቸው ያሉ 5 ጉዳዮችን መረጃ አደራጅቶ ለሚመለከተው አካል ለመላክ ታቅዶ
መረጃውን በወቅቱ ልከናል፡፡

ተግባር 2፡- የፍርድ ውሳኔ ለማስፈጸም ታቅዶ በፍርድ ቤት ውሳኔ መሰረት 1 ቤቶችን ተረክበናል፡፡

ኦፕ.ግብ 18፡- በአፓርታማ ነዋሪዎች እንዲሸፈኑ ተሳትፎና ተጠቃሚነትና በተሰጡ አገልግሎቶች የተሻሻለ የአፓርታማ
አስተዳደር፣ (1%)

ተግባር፡-1 በአፓርታማ ነዋሪዎች መተዳደሪያ እንድተገበር በዚህ አመትም ለ 2 የቁጠባ ማህበር እና ለ 16


አፓርታማ ማህበራት መተዳደሪያ ደንብ ለመፈራረም ደንብ ታትሞ እንድደርሳቸው
ተደርጎ ከ 16 አፓርታማ ማህበራት መልሰ መጥቶ የጽ/ቤት ተወካይ ፈርሞበታል፡፡

ተግባር፡-2 በአፓርታማ ነዋሪዎች ወጭ መጋራት የሚከናወኑ ዝርዝር ተግባራት የያዘ ሰነድ ማዘጋጀትና
ለመተግበር ታቅዶ 18 ሰነድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ ተገብቷል፣

ኦፕ.ግብ 19፡- የጉዳት ደረጃቸው በጥናት የተለዩ ቤቶች፣

ተግባር፡-.1 በጥናት ሰነዱ መሰረት በውስጥ ሀይል የሚጠገኑ ቤቶችን ዝርዝር የያዘ ሰነድ ለማዘጋጀት ታቅዶ ስራ
ላይ አውለናል፣

ተግባር፡-2 በውጪ ሥራ ተቋራጭና በደንበኞች የሚጠገኑ ቤቶችን ዝርዝር የያዘ ሰነድ ለማዘጋጀት ታቅዶ
ተከናውኗል፣

ኦፕ.ግብ 4.20፡- በውስጥ ዐቅም የተካሄደ 25 ቤቶች ለመጠገን ታቅዶ 41 ቤቶች ተጠግነዋል እንዲሁም በደንበኞችን
የተካሄዱ የ 30 ቤቶች ጥገናና ለማከናወን ታቅዶ 46 ቤቶች በድምሩ 87 ቤቶች ተጠግነዋል
1,911,792.31 ብር (2%)

የ ህዳር ወር Page 7
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

ተግባር፡-1 በውስጥ አቅም ጥገና የሚደረግላቸውን ቤቶችን ዝርዝር በመለየት ለማዘጋጀት ታቅዶ ተከናውኗል፤

ተግባር፡-2 በውስጥ አቅም ጥገና የሚደረግላቸውን የጥገና ፕሮግራም ለማዘጋጀት ታቅዶ ተከናውኗል፤

ተግባር፡-3 በውስጥ ዐቅም የጥገናና ዕድሳት ስራዎች ማካሄድ፣ 1,911,792.31 ብር

1. ዝቅተኛ 15 ታቅዶ 8 በመጠገን 53.33 ፐርሰንት ተከናውኗል፡፡

2. መካከለኛ 8 ታቅዶ 20 በመጠገን 250 ፐርሰንት ተከናውኗል፡፡

3. ከፍተኛ 4 ታቅዶ 13 በመጠገን 325 ፐርሰንት በላይ ተከናውኗል፡፡

ተግባር፡-4 የአፓርታማዎችን የውጭ ቀለም እድሳት መስራት 1 ታቅዶ 4 ተሰረቷል 400 ፐርሰንት ተከናውኗል፡፡

ተግባር 5፡- የተወካዮች ምክር ቤት ሙሉ እድሳት ማጠናቀቅ ግምት ዝግጅት ተጠናቅቋል፣ ፕሮግራምና እቃ
አቅርቦት ቅድመ ዝግጅ እየተደረገ ይገኛል፡፡

ተግባር 8፡ ለ 30 ደንበኞች የሚቀርቡ የጥገና ጥያቄዎች በራሳቸው ወጭ እንዲጠግኑ ፈቃድ ለመስጠት ታቅዶ 46
ደንበኞች ፈቃድ ተሰጥቷቸዋል፡፡

ተግባር 9፡ በተሰጠው የጥገና ፈቃድ መሰረት ጥገናና እድሳት መከናወኑን በመስክ ተገኝቶ 20 ፐርሰንቱን
ለማረጋገጥ ታቅዶ 89 ፐርሰንት በሱፐርቪዥን ታይቷል፡፡

ስትራቴጂክ ግብ 5፡- የኮርፖሬት አሠራርን ማሻሻል (15%)

ኦፕ.ግብ 21፡ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው አሰራር ለማስፈን መመሪያዎችን ለመተግበር ታቅዶ መመሪያና አሰራር
መሰረት ተደርጎ ተከናውኗል (2%)

ተግባር፡-1 ለመመሪያዎችና ማኑዋሎች ዝግጅት አስተያየት ለመስጠት ታቅዶ ምላሽ ተሰጥቷል፣

ተግባር፡-2 መመሪያዎችን ማኑዋሎችን ስራ ላይ ለማዋል ታቅዶ በቤት አስተዳር፣ በጥገና በፋይናስና ግዥ እና


በሰው ሃብት አስተዳደር ስራ ላይ መመሪያን መሰረት ያደረገ ስራ ተሰርቷል፡፡

ኦፕ.ግብ 22፡ ተግባራዊ የተደረጉ 3 የለውጥ መሳሪያዎች (1%)

ተግባር፡-1 የለውጥ መሳሪያዎችን (ካይዘን፣ የለውጥ ቡድንና ቢኤስሲን) ተግባራዊ ለማድረግ ታቅዶ ስራ ላይ
አውለናል፡፡

ተግባር፡-2 የአፈፃፀም ክፍተት በታየባቸው የለውጥ መሳሪያዎች ላይ ተገቢውን ማስተካከያ ለማድረግ ግብዓት
ለመስጠት ታቅዶ አስተያየት ተሰጥቷል ተከናውኗል፡፡

ተግባር፡-3 በለውጥ ሰራዊት የተከናወኑ ስራዎችን በመገምገም ግብረ መልስ ተሰጥቷል

ለመስጠት ታቅዶ ግብረ መልስ ተሰጥቷል፤

ኦፕ.ግብ 23፡- ሥራ ላይ የዋለ ዘመናዊና ጠንካራ የውስጥ ኦዲት (1%)

የ ህዳር ወር Page 8
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

ተግባር፡-1 በኦዲት ግኝቶች ላይ ማስተካከያ ለማድረግ ታቅዶ በዚህ ህዳር ወር የተሰጠ እርምት ስለሌለ
አልተከናወነም፡፡

ኦፕ.ግብ 24፡- ሥራ ላይ የዋለ የተቀናጀ የሙስና መከላከያ ስትራቴጂ (1%)

ተግባር፡-1 የስትራቴጂውን ማስፈጸሚያ ዕቅድ ተዘጋጅቷል፤

ተግባር፡-2 የተቀናጀ የሙስና መከላከያ ስትራቴጂ ስራ ላይ ለማዋል ታቅዶ አሰራርና መመሪያን መሰረት ያደረገ
ስራ ተሰርቷል እንዲሁም ሰራተኞች ሃብትን አስመዝገቧል፣

ኦፕ.ግብ 25፡- በመልካም አስተዳደር መስፈን ተጠቃሚ የሆኑ የውጪና የውስጥ ደንበኞች (2%)

ተግባር 1፡- በጽህፈት ቤት ደረጃ ከመልካም አስተዳደር መርሆዎች አኳያ ያለውን ችግር የውስጥና የውጭ
ችግሮች ለመለየት ታቅዶ ችግሮችን ለይናል፡፡

ተግባር 2፡- በጽህፈት ቤት ደረጃ ከመልካም አስተዳደር መርሆዎች አኳያ ዕቅድ ለማዘጋጀት ታቅዶ እቅድ
አዘጋጅተናል፤

ተግባር 3፡- በጥናት የተለዩትን የመልካም አስተዳደር ችግሮች መሰረት በማድረግ እያንዳንዱ የሥራ ክፍል
በፍጥነት መፍታት እንዲቻል የመረጃ አያያዝና አገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻል ስራ
ተሰርቷል፣

ተግባር 4፡- የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታትና ሪፖርት ማቅረብ፤ ከዋና ተከራዮች ጋር እየኖ ለነበሩ
ችግረኛ የድጋፍ ደብዳቤ ጽፈናል፡፡

ኦፕ.ግብ 26፡- የተዘጋጀ የፊዚካል ሥራዎች እቅድ፣አፈፃጸም ሪፖርቶችና፣ የተደረጉ የግምገማና የሱፐርቪዥን
ሥራዎች፣ (3%)

ተግባር 1፡- ወቅታዊ የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በየወሩ ማዘጋጀት በየደረጃው በጋራ በመገምገም ለሚመለከተው
ሪፖርት ተልኳል፣

ተግባር 2፡- በወሩ የተሰሩ ሥራዎችን ትክክለኛነት በሱፐርቪዥን በማረጋገጥ ግብረ-መልስ ተሰጥቷል፡፡

ኦፕ.ግብ 27፡- የግዥና ንብረት አስተዳደር ሥርዓት በመዘርጋትና ተግባራዊ በማድረግ የ 1.5 ሚሊዮን ብር ግዥ
ተፈጽሟል (1%)

ተግባር፡-1 የበጀት ዓመቱን የግዥ ዝርዝር ዕቅድና ፕሮግራም በማዘጋጀት ለማፀደቅ ታቅዶ የግዥ አቅድ አስጸድቀን
ወደ ስራ ገብተናል፡፡

ተግባር 2፡- በአቅርቦት ዕቅዱ መሰረት የተለያዩ የግዥ ዘዴዎችን በመጠቀም 1,573,140.37 ሚሊዪን ብር ግምት ያለው እቃ
ተገዝቷል

የጥገና እቃዎች 1,255,733.87 ብር

የጽዳት እቃዎች 171,087.44 ብር

የጽህፈት መሳሪያዎች 2,594.20 ብር እና ልዩ ልዩ 143,724.86 ብር፡፡

የ ህዳር ወር Page 9
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

ተግባር 3፡- የግዥ ጥያቄ አደራጅቶ ለግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ለማቅረብ ታቅዶ አቅርበናል፡፡

ተግባር 4፡- ግዢዎች በስፔስፍኬሽን መሰረት መሆናቸውን በማረጋገጥ ለመረከብ ፕሮፎርማ ሲሰበሰብና እቃ ሲገባ
የሚያረጋግጡ ባለሙያዎች መድበን እየተሰራ ይገኛል፡፡

ኦፕ.ግብ 28፡- ዉጤታማነቱ የተረጋገጠ የንብረት አያያዝና አጠቃቀም (1%)

ተግባር 1:- ቋሚና አላቂ ንብረቶችን መመዝገብና በየጊዜው ወቅታዊ ለማድረግ ታቅዶ የቋሚ ንበረት
ምዝገባ ተካነውኗል፡፡
ተግባር 2:- አገልግሎት ሰጥተው የተበላሹና ሊጠገኑ የማይችሉ ንብረቶችን በባለሙያ አረጋግጦ ወደ ዕቃ ግ/ቤት
ተመላሽ ማድረግና እንዲወገዱ ለማድረግ መረጃ ለይተን ለግዥ ዳይክቶሬት አቅርበናል፡፡
ተግባር 3፡- በግዥና በዕቃ ግ/ቤት ያሉ ንብረቶችን ለየስራ ክፍሎች ስርጭት ለማድረግ፤ ታቅዶ 1,025,569.18
ብር ግምት ያለው ንብረት ተሰራጭቷል፡፡
ኦፕ.ግብ 29 ፡- የተሻሻለ የማህደር አደረጃጀትና የመረጃ አያያዝ (1%).

ተግባር 1፡- የቤቶች ማህደር ፣ ካርታ ና ሌሎች መረጃዎች በአግባቡ ለማደራጀት ታቅዶ 3990 ማህደሮችን
የውጭ ሽፋን ቀይረን፣ ስካን አድርገን እና መረጃውን በኤሌክትሮኒክ (eDMS)
መቀባበል የሚያስችል ስራ ተሰርቶ ወረቀት አልባ አሰራር እየተተገበረ ይገኛል፣

ተግባር 2፡- ወርሃዊ ወጭና ገቢ ደብዳቤዎችና መረከብ፣ ማሰራጨትና ሪፖርት ለማቅርብ ታቅዶ ተከናውናል፣

ኦፕ. ግብ 30. ተግባራዊ የተደረገ የባለብዙ ዘርፍ ጉዳዮች (2%)

ተግባር 1፡- 1,670 ችግኞችን በጣና፣ በመስከረም አፓርትመንቶችና ገርጂ ነጫጭ ቤቶች እና ደረጃ መዳቢ ቁጠባ
ቤቶች አካባቢ እንክካቤ አደርገናል፡፡

ተግባር፡-.2 የኤድስ ፈንድ ለማጠናከር የሰራተኛ መዋጮን በየወሩ እየተዋጣ ይገኛል፣

ተግባር፡-.3 ኤች አይ ቪ በደማቸው ከሚገኙት ጋር በሚያጋጥሟቸው ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው


ዙሪያ በየቡድኑ ውይይት ተደርጓል፣

የስትራቴጂክ ግብ 6፡- ቅንጅታዊ አሰራርን ማሻሻል፤ (5%)

ኦፕ.ግብ 31- ጽህፈት ቤቱ ከባለድርሻ አካላት በተለይም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ከፍትህ አካላት፣የመሠረተ
ልማት አቅራቢዎች፣ ከሥልጠና ተቋማት ወዘተ. ጋር የሚያገናኙ ሥራዎችንና በግንኙነቱ የታዩ
ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት፤ የተፈጠረ ጠንካራ ግንኙነት ለመፍጠር ከቦሌ ና ቂርቆስ ክፍለ
ከተሞች ይዞታ አስተዳደርና ይዞታ ምዝገባ ጋር መግባቢያ ሰነድ በተፈራረምነው መሰረት
እየተተገበረ ይገኛል፡፡ (2%)

ተግባር 1፡ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካላት፣ ከፍትህ አካላት፣ ከመሰረተ ልማት አቅራቢዎች፣ ከሥልጠና ተቋማት፣
ከግንባታ አስፈጻሚ ተቋማት. ወዘተ... ጋር በቅንጅት ስራዎችን ለማከናወን ከቦሌ ና ቂርቆስ ክፍለ
ከተሞች ይዞታ አስተዳደርና ይዞታ ምዝገባ ጋር መግባቢያ ሰነድ በተፈራረምነው መሰረት እየተተገበረ
ይገኛል፡፡

የ ህዳር ወር Page 10
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

ኦፕ.ግብ 32፡- በዋናው መ/ቤት የሚገኙ የሥራ ክፍሎች ከቅርንጫፎችና ከአቻ የሥራ በረ በቅንጅት የመስራት ባህል
ከቤቶች አስተዳደር፣ ከጥገና ዳይሬክተሮችና ከቅርንጫፎች ጋር መግባቢያ ሰነድ በተፈራረምነው
መሰረት እየተተገበረ ይገኛል፡፡(3%)

ተግባር 1፡- የሥራ ክፍሎች የእርስ በእርስ ግንኙነት እና የትስስር ስምምንት ሰነድ ተግባራዊ ለማድረግ መግባቢያ
ሰነድ መሰረት በጋራ በሚያገናኙን ስራዎች ላይ በቅንጅት እየሰራን እንገኛለን፡፡

IV. የመማማርና እድገት ዕይታ (15%)

ስትራቴጂክ ግብ 7፡- የሰው ሀብት አስተዳደርን ማሻሻል፤፤ (12%)

ኦፐ.ግብ 33፣ በመዋቅሩ መሰረት የተሟላ 5 የሰው ሀይል ለማማላት ታቅዶ በዚ ወር ምንም ዓይነት ቅጥር የለም (3%)

ተግባር፡-1፡- የሰው ሀይል ዕቅድ ሰነድ በማዘጋጀት 4 ክፍት ቦታዎችን ለይተናል፣

ተግባር፡-2፡- የተለያዩ የሙሌት ዘዴዎችን በመጠቀም ክፍት የሥራ መደቦችን በሰው ኃይል ለማሟላት 5 ታቅዶ
በዚ ወር ምንም ዓይነት ቅጥር የለም ፣

ኦፕ.ግብ፡-34 የተጠናከረ የሰዉ ኃይል አስተዳደር ሥርዓት ተግባራዊ ማድረግ (6%)

ተግባር 1፡- የተለያዩ የሰው ሃብት አስተዳደር ስራዎችን መስራት 36 ህክምና አገልግሎት ፣18 ህክምና ወጪ፣ 9 ዋስትና
2 ጡረታ ማስከበር አገልግሎት ተሰጥቷል፡፡

ተግባር፡-2፡- የሰራተኞች የሞያ ደህንነትና ጤንነት ለመጠበቅ የሚያስችል አሰራር ዘርግቶ ተግባራዊ አድርገናል፡፡

ኦፕ.ግብ 35 - ለቅርንጫፉ አመራሮችና ሰራተኞች የአመለካከትና ክህሎት ማሻሻያ ስልጠና ፍላጎት ለይን አቅርበናል፡፡
(3%)

ተግባር 1፡- የስልጠና ፍላጎት በመለየት በበጀት ዓመቱ ልጠና የሚያሰፈልጋቸዉ 5 አመራሮች እና 50 ሠራተኞች በዕቅድ
ተይዟል ፡፡

ተግባር 2፡- በተዘጋጀው ስልጠና ሰራተኛውና አመራሩ አስቀድሞ እንዲያገኝ በማድረግ 10 ሠራተኞች ስልጠና
አግኝተዋል፡፡

ኦፕ.ግብ 36-. የተሸሻለ ተግባራዊ የተደረገ የማበራተቻ ስርአት ለሰራተኞችና አመራሮች የሁለት ወር ቦነስና እርከና
ጭማሪ ተተግብሯል፡፡ (3%)

ተግባር 1፡- የሠራተኞች የሥራ አፈፃፀም ምዘና በሁለተኛዉ ሩብ ዓመት የሚከናወን ነዉ፣

ተግባር 2፡- የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ አመራርና ሰራተኞች ማበረታቻ የዚህ ወር እቅድ አይደለም፡፡

ስትራቴጂግ ግብ፡- 8 የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ማሳደግ (3%)

ኦፕ.ግብ 37፡- የስራ ክፍሎችን ተጠቃሚ ያደረገ የመረጃ መረብ (1%)

የ ህዳር ወር Page 11
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

ተግባር 1፡- በስራ ክፍሎች መካከል የመረጃ ልውውጥን የሜይል ሲስተም ተጠቃሚ እንዲሆን
ለማድረግ ታቅዶ ቡድኖችና ጽህፈት ቤቱ ተጠቃሚ ናቸው፤
ኦፕ.ግብ 38 ፡ በኢኮቴ አጠቃቀም አቅሙ ያደገ የቅርንጫፍ አመራርና ፈጻሚ (2%)

ተግባር 1 የኢኮቴ ክህሎት የሚያሳድጉ ስልጠናዎች ላይ መሳተፍ ስላልተሰጠ አልተከናወነም፣


ተግባር፡-2 በሚዘረጋው የመረጃ ሲስተም በስራ ክፍሎች መካከል የመረጃ ልውውጥ ማሳለጥ እንዲቻል
ሁሉም የስራ ክፍሎች የሜይል ሲስተም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡
ተግባር፡-3 ለኢኮቴ መገልገያ መሳሪያዎች በሙሉ ወቅታዊ እና ህጋዊ አንቲ-ቫይረስ እንዲጫን ክትትል
ተደርጓል፡፡
ተግባር፡-4 ብልሽት ለሚያጋጥማቸው የኢኮቴ መሳሪያዎች የጥገናና የሰርቪስ አገልግሎት እንዲሰጥ
ክትትል ማድረግ፤

ክፍል አራት

4. ታቅደው ያልተከናወኑ ተግባራት

 የሰድሰት ቤቶች ዝቅተኛ ጥገናና ዕድሳት

ምክንያቱም፡- በወሩ ዉሰጥ የባዶ ቤቶች ማለትምመካከለኛና ከፍተኛ ጥገናዎች ከእቅድ


በላይ መብዛት

ክፍል አምስት

5. ሳይታቀዱየተከናወኑተግባራት

የለም

ክፍል ስድስት ፡- ያጋጠሙ ችግሮችና የመፍትሔ ሃሳቦች

ያጋጠሙ ችግሮች የተወሰዱ መፍትሔዎች


ያሉት ተሸከርካሪዎች ያረጁ በመሆኑ ተደጋጋሚ ብልሽት ባሉት ለመንቀሳቀስ ጥረት መደረጉ፡፡
የሚያጋጥም መሆኑ፡፡

በቤቶቻችን ላይ የሚታየውን ህገ ወጥነትን ለመከላከል በህግ ለመከታተል ጥረት እየተደረገ ቢሆንም በወቅቱ ሁኔታ
በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ ከተባባሪ አካላት መፍትሄ አልተገኘም፤ ድጋፍ ያስፈልገናል፡፡
የሚፈለገውን ያህል ድጋፍ ማግኘት ያለመቻልና ጣልቃ

የ ህዳር ወር Page 12
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

ገብነት፣ በወረዳ 18 ቀበሌ 06 የቤት ቁጥር 519 የአዲሰ


አበባ አስተዳደር በሃይል የወሰደ መሆኑና ህጋዊ አሰራር
ተከትሎ ወይ ወደ ውል አልመጣም ወይም ካሳ መከፈል
ካለበት ፈቃደኛ አለመሆናቸው፡፡
የጥገና ሥራዎችን በጥራትና ፍጥነት በጠበቀ ሁኔታ በወቅቱ የክትትል ስራ ለመስራት ጥረት መደረጉ
አጠናቅቆ ማቅረብ ያለመቻል፤
የግል ቤት ላላቸው ግለሠቦች መረጃ እያለ የፍርድ ቤት -
ዕግድ መሠጠት፤

ክፍል ሰባት- የዕቅድ አፈፃፀም ክትትል፣ ሪፖርት፣ ግምገማና ግብረ-መልስ ሥርዓት፣

7.1. የክትትል፣ የግምገማና ግብረ መልስ ሥርዓት ዓላማዎች


7.1.1. ዕቅድና ሪፖርት አቀራረብ

 ቡድኖች የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱን አመታዊ እቅድ መሰረት አድርገው ሪፖርት እስከ ፈጻሚ ድረስ
አዘጋጅተናል፡፡
 ሪፖርት ተገምግሞና ግብረ መልስ በመስጠት ቡድኖች ለቅርንጫፍ ጽ/ቤትና ቅርንጫፍ
ጽ/ቤታችን ለቤቶች አስተዳደር ዘርፍና ለስ/ፕላኒንግ እና ቢዝነስ ዴቭሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
አቅርበናል፡፡
7.1.2. ሱፐርቪዥን

 የጥገናና እድሳት ስራዎች አፈጻጸም ለመከታተል የሱፐርቪዥን ስራ ተከናውኖአል፣ በቡድን


መሪዎች እና አስፈላጊ በሆነበት በጽህፈት ቤት ደረጃ የመስክ ክትትል ተደርጓል፤
 ሕገ ወጥ የቤቶች አጠቃቀምን ለመቆጣጠር እንዲቻል፣ በመስክ ተከታታዮች፣ በደንበኞች ቡድን
መሪዎች፣ እንደ አስፈላጊነቱ በቅርንጫፍ ሀላፊ አማካኝነት በፕሮግራም የተደገፈ የመስክ
ክትትል ስራ ተከናውኖአል፤
 የቢሮ ስራዎችን አፈጻጸም ለመከታተል በቡድን መሪዎች፣ በቅርንጫፍ ሀላፊ በፕሮግራምና
ድንገተኛ የሱፐርቪዥን ስራዎች ተከናውኗል፤

የ ህዳር ወር Page 13
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

7.1.3. ክትትልና ግምገማ፣


 በክትትልና ግምገማው በአጠቃላይ ስራተኛው ስራተኛው ስራ ላይ አተኩሮ እንዲሰራ እና
አፈጻጸማችንን የተሸላ ማድረግ ተችሏል፣ ተጠያቂነት ማስፈን ተችሏል፡፡
 ከቡድኖች የሚቀርቡ የመስክ፣ የአፈፃፅም ሪፖርቶችና አስተያየቶች በማጠናቀርና በመተንተን
የዓመቱ አፈጻጸም ግምገማ በማካሄድ አቅጣጫ የሚቀመጥ ሲሆን፣ በተጨማሪም የሚያጋጥሙ
ችግሮችና ማነቆዎችን እንደአስፈላጊነቱ በማጤን መፍትሔ ለመስጠት ጥረት ተደርጓል፡፡
 በቅርንጫፍ ጽ/ቤት ደረጃ በየሳምንቱ በሚኒ ማኔጅመንት እየተገመገመ ለችግሮች መፍትሄ
ተሰጥቶአል፣
 ቡድን መሪዎችና ፈጻሚዎች የተሳተፉበት ዓመታዊ የአፈጻጸም ግምገማ ተከናውኗል፡፡
 ሰራተኞች የስዓት ፊርማ በየስራ ክፍሉ ቁጥጥር የሚደረግ ሲሆን በሚደረገው ክትትል ተደርጓል፡፡

7.1.4. ግብረ መልስ፣


 ለቡድኖች ጥንካሬዎችንና ውስንነቶችን በመለየት በየወሩ የጽሁፍ ግብረ መልስ ተሰጥቷል፡፡

ክፍል ስምንት መደምደሚያ ፈታኝ ሁኔታዎችና ለወደፊት ሊወሰዱ የሚገባቸው እርምጃዎች

8.1. መደምደሚያ
የ 2013 በጀት ዓመት እቅድ ተዘጋጅቶ እስከ ፈጻሚ ድረስ ካስኬድ የማድረግ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡ በዚህም መሰረት
በፋይናንስና ገቢ አሰባሰብ 2,397,305.41 ብር በመሰብሰብ እና 87 ቤቶችን በመጠገን ውጤታማ ሥራዎችን
አከናውነናል፡፡
8.2. ፈታኝ ሁኔታዎች

 የተሸከርካሪ እጥረት መኖሩ


 የገልባጭ መኪና አለመኖር ይህም ክብደትና ብዛት ያላቸውን የጥገና ቁሳቁሶች በወቅቱ ወደ ጥገና ቦታ
ማንቀሳቀስ አልተቻለም፡፡
 የፍርድ ቤት ዕግድ፤
 በቤት ማስለቀቅ ሂደት ከነዋሪውና ከተለያዩ አካላት ጣልቃገብነት መኖራቸው፤

8.3. . ወደፊት ሊወሰዱ የሚገባቸው የመፍትሄ እርምጃዎች


 ተሸከርካሪ በኪራይ ወይም በዝውውር ቢጨመርልን፤
 የገልባጭ መኪና ችግር ለመፍታት አንደኛው ገልባጭ መኪና በቋሚነት ቢመደብልን፡፡

የ ህዳር ወር Page 14
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

ክፍል ዘጠኝ ፡ ጠንካራን ጎን እና ውስንነቶች


9.1. ጠንካራ ጎኖች
 ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ መሻሻል ለማምጣት እየተደረገ ያለው ጥረትና የተገኙ ውጤቶች፡፡
 ለቅርንጫፉ ውጤታማነት መቆርቆርና የቡድን ስሜት መኖሩ፡፡
 በውስን ሰራተኞች ዋና ዋና አገልግሎቶች መስጠት መቻሉ፡፡
 በሰራተኞ መካከል ተነሳሽነት ስሜት መፈጠሩ፡፡
 በቡድን የመስራት ሁኔታዎች መኖራቸው፡፡
 ዘመናዊ አሰራርና የተሻለ የመረጃ አያያዝ መኖሩ፡፡

9.2. ውስንነቶች
 ህገወጥ ድርጊት በመከላከል በኩል የተሰሩ ስራዎች ቢኖሩም ከህገወጥ ግንባታ፣ ከሶስተኛ ወገን ተከራይ ጋር
በተያያዘ አሁንም ያልተሻገርናቸው ችግሮች መኖራቸው፡፡
 ጠንካራ የውስጥ አሰራር ስርዓት መዘርጋት ላይ ጅምር ስራዎች ቢኖሩም በአሰራር ላይ ክፍተቶች
መታየታቸው፡፡
 የለውጥ ስራ ውጤታማ ለማድረግ ጥረቶች ቢኖሩም በአመለካከት አልፎ አልፎ የሚያጋጥም ተግዳሮት መኖርና
ለውጡ የሚፈለገውን ያህል ውጤታማ አለመሆኑ፡፡
 ከሙስና መከላከል ጋር በተያያዘ የተከናወኑ ስራዎች እንደተጠበቁ ሆነው በሁሉም ሰራተኛ እኩል ግንዛቤ ይዞ
መንቀሰቀስ ያለመቻል፡፤
 የጥገና ጥራት ጉድለትና መዘግየቶች ማጋጠማቸው፡፡

ማጠቃለያ፡
በዚህም መሰረት ቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ በህዳር ወር ያከናወንናቸውን የግቦች አፈጻጸም ከእቅድ በማነጻጸር ሪፖርት
የተሰራ ሲሆን 280 ቤቶች ውል ለማደስ ተችሏል፡፡ እንዲሁም በነዋሪ ወጭ መጋራት 46 ቤቶች ተጠግነዋል፤ በጽ/ቤቱ

የ ህዳር ወር Page 15
የቅርንጫፍ 3 ጽ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የ ህዳር ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት

ወጭ 41 ቤቶች ተጠግነዋል፤ ለጥገና አስፈላጊ የሆኑ እቃዎች 1,255,733.87 ብር ግዥ በመፈጸም እንዲሁም


2,397,305.41 ብር ገቢ ተስብስቧል፡፡

በአጠቃላይ የስራዎች አፈጻጸም የቅርብ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ግብረ መልሶችን በመስጠት ዓመታዊ
እቅድን ለማሳካት በተደረገው ጥረት አጠቃላይ ጥሩ አፈጻፀም ላይ ደርሷል፡፡

የ ህዳር ወር Page 16

You might also like