You are on page 1of 54

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ

ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ የሰው ሃይል አስተዳደር መመርያ

መስከረም, 2013

ዓዲግራት, ትግራይ, ኢትዮዽያ

Table of Contents
መግቢያ....................................................................................................................................................3

ክፍል አንድ ጠቅላላ....................................................................................................................................3

አንቀጽ 1 አጭር ርእስ.............................................................................................................................3

አንቀፅ 2 ትርጓሜ...................................................................................................................................3

አንቀጽ 3 አላማ.....................................................................................................................................5

አንቀጽ 4 የመመሪያው ተፈፃሚነት ወሰን..................................................................................................5

ክፍል ሁለት በቅጥር ላይ የተመሰረተ የስራ ግንኙነት........................................................................................6

1
አንቀጽ 5 ቅጥር.....................................................................................................................................6

አንቀጽ 6 የቅጥርና የደራጃ እድገት ኮሚቴ አባላት.......................................................................................8

አንቀጽ 7 የቅጥርና ደረጃ እድገት ኮሚቴ ተግባርና ሀላፊነት..........................................................................8

አንቀጽ 8 የመወዳደሪያ መስፈርት............................................................................................................9

አንቀጽ 9 በተወዳዳሪዎች ስለሚቀርቡ መስረጃዎች..................................................................................11

አንቀጽ 10 የሙከራ ጊዜ ቅጥር...............................................................................................................12

አንቀጽ 11 የስራ ውል...........................................................................................................................13

አንቀጽ 12 የሥራ ውል አመሰራረት........................................................................................................13

አንቀጽ 13 የስራ ውል የሚቆይበት ጊዜ...................................................................................................13

አንቀጽ 14 የሥራ ግንኙነቶች.................................................................................................................13

አንቀጽ 15 የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ መብቶች........................................................................................14

አንቀጽ 16 የሰራተኞች መብቶች...........................................................................................................14

አንቀጽ 17 የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ግዴታዎች.......................................................................................14

አንቀጽ 18 የሠራተኞች ግዴታዎች.........................................................................................................15

አንቀጽ 19 የስራ ውል የሚሻሻልበት ሁኔታ...............................................................................................17

አንቀጽ 20 ከስራ ውል የሚመነጩ መብትና ግዴታዎችን ለጊዜው ስለማገድ.................................................17

አንቀጽ 21 ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ከሰራተኛው ጋር ያደረገው የስራ ውል ስለሚቋረጥበት ሁኔታ....................17

አንቀጽ 22 የስራ ውል ከመቋረጡ በፊት ስለሚሰጥ ማስጠንቀቂያ ስነ-ስርዓት...............................................17

አንቀጽ 23 የስራ ስንብት እና የካሳ ክፍያ..................................................................................................17

አንቀጽ 24 ዝውውር............................................................................................................................18

አንቀጽ 25 የደረጃ ዕድገት......................................................................................................................18

አንቀጽ 26 የስራ አፈፃፀም ምዘና...........................................................................................................23

ክፍል ሶስት ደመወዝና ጥቅማጥቅም...........................................................................................................24

የደመወዝ አወሳሰንና ይዘት........................................................................................................................24

አንቀጽ 27 ጠቅላላ...............................................................................................................................24

አንቀጽ 28 የአከፋፈል ዘዴ እና የክፍያ አፈፃፀም........................................................................................25

አንቀጽ 29 የደመወዝ ጭማሪ................................................................................................................25

አንቀጽ 30 የውሎ አበል........................................................................................................................26

አንቀጽ 31 የህክምና አገልግሎት.............................................................................................................27

2
አንቀጽ 32 የመጓጓዣ ሰርቪስ አገልግሎት.................................................................................................27

አንቀጽ 33 የጡረታ መዋጮ...................................................................................................................28

አንቀጽ 34 የኢንሹራንስ ሽፋን...............................................................................................................28

አንቀፅ 35 ለስራ የሚያስፈልጉ የአደጋ መከላከያ የስራ እና ደንብ ልብስ.........................................................28


ሰንጠረዥ 1፡ የደንብ ልብስ ዓይነት ማጠቃለያ.................................................................................................30
ክፍል አራት የስራ ሰዓት.............................................................................................................................31

አንቀፅ 36 የስራ ሰዓት...........................................................................................................................31

አንቀጽ 37 የሻይ እረፍት.......................................................................................................................31

አንቀጽ 38 የሳምንት የእረፍት ጊዜ.........................................................................................................32

አንቀጽ 39 የህዝብ በዓላት.....................................................................................................................32

አንቀጽ 40 የትርፍ ሰዓት ስራ ክፍያና የትርፍ ስራ ሰዓት ሁኔታዎች..............................................................32

አንቀጽ 41 የትርፍ ስራ ሰዓት አከፋፈል...................................................................................................32

ክፍል አምስት ፈቃድ................................................................................................................................33

አንቀጽ 42 ጠቅላላ...............................................................................................................................33

አንቀጽ 43 ልዩ ፈቃድ...........................................................................................................................34

አንቀጽ 44 ልዩ ልዩ ተግባሮችን ለማከናወን ለሰራተኞች የሚሰጥ ፈቃድ.......................................................34

አንቀጽ 45 ለግል ጉዳይ የሚሰጥ ፈቃድ...................................................................................................34

አንቀጽ 46 የህመም ፈቃድ....................................................................................................................35

አንቀጽ 47 የህመም ፈቃድ ክፍያ............................................................................................................35

አንቀጽ 48 የወሊድ ፈቃድ.....................................................................................................................35

ክፍል ስድስት የመረጃ አያያዝና አጠቃቀም..................................................................................................35

አንቀፅ 49 መዝገብ ቤት........................................................................................................................35

ክፍል ሰባት የስነ ሥርዓት አከባበርና የሚወሰዱ የማስተካከያ እርምጃዎች........................................................36

አንቀፅ 50 ጠቅላላ................................................................................................................................36

አንቀጽ 51 የስነ - ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃዎች አወሳሰድ..........................................................37

አንቀጽ 52 የስነ-ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃዎች አወሳሰድ ኃላፊነት...............................................37

አንቀጽ 53 የስነ - ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃዎች የተፃፈ ደብዳቤ ስለመቀበል.................................37

አንቀጽ 54 የተወሰደ የስነ-ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃ ስለመሻር....................................................52

ክፍል ስምንት ልዩ ልዩ ጉዳዮች..................................................................................................................52

3
አንቀፅ 55 የሰራተኛ የአገልግሎት የእድሜ ጣሪያ.......................................................................................52

አንቀጽ 56 የሴቶችና የወጣት ሠራተኞች የሥራ ሁኔታ.............................................................................52

አንቀጽ 57 የሙያ ደኅንነት ፣ጤንነትና የሥራ አካባቢ.................................................................................52

አንቀጽ 58 በሥራ ምክንያት ስለሚመጡ ጉዳቶች....................................................................................52

አንቀፅ 59 የሰራተኛ ማህበር እና የህብረት ስምምነት................................................................................53

አንቀጽ 60 የሥራ ምስክር ወረቀት ስለመስጠት........................................................................................53

አንቀፅ 61 የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ማህተም..........................................................................................53

አንቀጽ 62 መመሪያው የሚፀናበት ጊዜ...................................................................................................53

ቅፃቅፆች................................................................................................................................................54

4
መግቢያ
የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ የኢፌዴሪ አሠሪና ሠራተኛ ህግ አዋጁን በአገናዘበ ሁኔታ
ይህንን የሰው ሃብት አስተዳደር መመሪያ አዘጋጅቷል። የዚህ መመሪያ ዋና ዓላማ ቢዝነስ እንተርፕራይዙ
በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴው ላይ የሚያጋጥሙ አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ተቀባይነት ያለው ውሳኔ
ለመወሰን ማገዝና ሠራተኛው ጥቅሙን፣ መብቱንና ግዴታውን እንዲያውቅ ማስቻል ነው።ይህ መመሪያ
በሠራተኛ አስተዳደር፣በሥራ ቀናት፣ በሥነ ሥርዓት አከባበር፣ በንብረት አያያዝና አጠቃቀም፣ በደመወዝና
ጥቅማጥቅም፣ በመረጃ አያያዝና አጠቃቀም፣ በልዩ ልዩ አበል አከፋፈልና ሌሎች ጉዳዮች ላይ
የኢንተርፕራይዙን ደንቦች እንዲይዝ ተደርጓል።

ክፍል አንድ ጠቅላላ


አንቀጽ 1 አጭር ርእስ
ይህ መመርያ የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ የሰው ሃይል አስተዳደር መመርያ ቁጥር
001/2012 ዓ.ም ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል።

አንቀፅ 2 ትርጓሜ
በዚህ መመሪያ ውስጥ
1. “አዋጅ” ማለት የአሰሪ እና ሰራተኛ አዋጅ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ማለት ነው።
2. “ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ” ማለት ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ቢዝነሰ ኢንተርፕራይዝ ማለት ነው።
3. “ሠራተኛ” ማለት በአዋጅ ቁጥር 1156/11 አንቀፅ 2/3 መሰረት ከኢንተርፕራይዙ ጋር በቅጥር ላይ
የተመሰረተ የስራ ግንኙነት ያለው ግለሰብ ነው።
4. “የስራ ሁኔታ” ማለት በአሰሪ እና ሰራተኛ መካከል ያለ ጠቅላላ ግንኙነት ሲሆን ይህም የስራ
ስዓትን፣ ደመወዝን፣ ፈቃዶችን፣ ሰራተኛ ከስራ በሚሰናበቱበት ጊዜ የሚገባቸውን ክፍያዎች፣
ጤንነትና ደህንነት፣ በስራ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ሠራተኞች የሚከፈል ካሳ፣ ሰራተኖች
ከስራ የሚቀነሱበትን ሁኔታ፣ የቅሬታ አቀራረብ ስርዓቶችንና የመሳሰሉትን ያጠቃላል።
5. “የሰራተኛ ቅነሳ” ማለት የአሰሪ እና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/11 በአንቀፅ 29 መሰረት
የተሰጠ ትርጉም ነው።
6. “ፈቃድ” ማለት በአዋጅ ቁጥር 1156/11 እና በዚህ መመሪያ መሰረት ሠራተኛው በመደበኛ የስራ
ጊዜ ደመወዝ እየተከፈለው ወይም ሳይከፈለው ከመደበኛ ስራው ለመቅረት የሚሰጥ ፈቃድ ነው።
7. “ላልተወሰነ ጊዜ የሚደረግ የስራ ውል” ማለት በአዋጁ አንቀፅ 9 መሰረት በቋሚ የስራ መደብ ላይ
የሚደረግ የስራ ውል ማለት ነው።
8. “ለተወሰነ ጊዜ ወይም ለተወሰነ ስራ የሚደረግ የስራ ውል” ማለት በአዋጁ አንቀፅ 10
መሰረት የሚፈፀም የስራ ውል ነው።
9. “ደመወዝ” ማለት በአዋጁ አንቀፅ 53 ንዑስ አንቀፅ 1 መሰረት አንድ የኢንተርፕራይዙ
ሠራተኛ በስራ ውል መሰረት ለሚያከናውነው ስራ የሚከፈለው መደበኛ ክፍያ ነው።
ሆኖም ደመወዝ በአዋጁ አንቀፅ 53 ንዑስ አንቀፅ 2 ከ ሀ-ረ የተጠቀሱትንና የቢዝነሰ
ኢንተርፕራየዙን ጡረታ መዋጮ ድርሻ አይጨምርም።
10. “የሙከራ ጊዜ” ማለት አንድ ሠራተኛ የቢዝነሰ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ በስራ ውሉ
መሠረት ሊቀጠርበት ለታቀደው ቦታ ተስማሚ መሆኑን ለመመዘን ሚሰጥ ጊዜ ነው።

5
11. “የስራ ስንብት ካሳ” ማለት በአዋጁ 1156/11 አንቀጽ 39 ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረት የሙከራ
ጊዜውን የጨረሰና የስራ ውሉ የተቋረጠበት ሰራተኛ ከቢዝነሰ ኢንተርፕራየዙ የሚከፈለው
የስራ ስንብት ክፍያ ነው።
12. “መደበኛ የስራ ሰዓት” ማለት በአዋጁ አንቀጽ 61 ንዑስ አንቀጽ 2 መሰረት ሰራተኛው
ስራውን የያከናውንበት ወይም ለስራ የሚገኝበት ጊዜ ነው።
13. “ትርፍ የስራ ሰዓት” ማለት በአዋጁ አንቀጽ 66 ንዑስ አንቀጽ 1 ላይ በተጠቀሰውና በዚህ
ደንብ መሰረት ከተወሰነው የቀኑ መደበኛ የስራ ሰዓት በላይ የሚሰራ የስራ ሰዓት ማለት
ነው።
14. “የወሊድ ፈቃድ” ማለት ነፍሰ ጡር የሆነች የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ ከእርግዝናዋ
ጋር በተያያዘ ለምርመራ ከወሊድ በፊትና በኋላ በአዋጁ አንቀፅ 88 መሰረት ቢዝነሰ
ኢንተርፕራይዙ የሚሰጣት ፈቃድ ሆኖ ሰራተኛዋ ከምርመራ በኋላ የሀኪም ማስረጃ
የምታቀርብበት ነው።
15. “በስራ ላይ የሚደርስ ጉዳት” ማለት ስራ ላይ የሚደርስ አደጋ ወይም በስራ ምክንያት
የሚመጣ በሽታ ማለት ነው።
16. “በስራ ምክንያት የሚመጣ በሽታ” ማለትበአዋጁ በአንቀፅ 98 በተቀመጠው መሰረት
ሰራተኛው ከሚሰራው የስራ አይነት ወይም ከሚያከናውናቸው የስራ አካባቢ የተነሳ
ሰራተኛው ላይ የሚደርስ የጤና መታወክ ማለት ነው።
17. “የአካል ጉዳት” ማለት በኣዋጁ አንቀፅ 99 በተቀመጠው መሰረት የመስራት ችሎታ መቀነስ
ወይም ማጣትን የሚያስከትል ሁኔታ በስራ ላይ የሚደርስ ጉዳት ነው፡
18. “የደንብ ልብስ” ማለት አንድ ሰራተኛ በተመደበበት የስራ ፀባይ ምክንያትና በቢዝነስ
ኢንተርፕራይዙ አሰራር መመሪያ መሰረት በስራ ጊዜ ሁሉ የሚለበስ ልብስ ማለት ነው።
19. “የሙያ ደህንነት” ማለት በአዋጁ አንቀፅ 92 መሰረት የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙን ሰራተኞች
ደህንነትና ጤንነት በሚገባ ለመጠበቅ የጤና መታወከና የአካል ጉዳት እንዳይደርስባቸው
መከላከል የሚያስችል እርምጃዎችን መውሰድ ነው።
20. “ዝውውር” ማለት አንድ የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ በቅጥር ከተመደበበት የስራ
መደብ ወይም አካባቢ ወደሌላ የስራ መደብ ወይም አካባቢ የሚፈፀም የሰራተኛ ዝውውር
ነው።
21. “የደረጃ እድገት” ማለት ከአንድ የስራ መደብና ደመወዝ ወደ ከፍተኛ የስራ መደብና
ደመወዝ የሚደረግ የደረጃ ለውጥ ማለት ነው።
22. “የዲሲፒሊን እርምጃ” ማለት የበቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ የተጣለበትን ግዴታና
ሃላፊነት ባለመወጣቱ ወይም ደንቡንና መመሪያዎችን ባለማክበሩ በሚፈፅማቸው ጥፋቶች
ምክንያት በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ በስነስርአት እርምጃ አወሳሰድ ሰንጠረዥ መሰረት የፍርድ
ቤት ውሳኔ ሳይጠብቅ በመመሪያው መሰረት በተቀመጠው የቅጣት ሰንጠረዥ ሰራተኛውን
ከጥፋቱ ለመመለስና ለማስተካከል የሚወስዳቸው የዲሲፒሊን እርምጃዎች ማለት ነው።
23. “የጉዳት ካሳ” ማለት በአዋጅ አንቀፅ 109 መሰረት በስራ ላይ በሰራተኛው ጥፋት
ምክንያት ላልተከሰተ ጉዳት ለሰራተኛው የሚከፈል ካሳ ማለት ነው።
24. “በስራ ላይ የደረሰ አደጋ” ማለት ማንኛውም የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሠራተኛ ስራውን
በማከናወን ላይ ሳለ ወይም ከስራው ጋር ግንኙነት ባለው ሁኔታ አደጋ ከደረሰበት ሠራተኛ
ውጭ በሆነ ምክንያት ወይም ሰራተኛው ስራውን ለማከናወን ባደረገው ጥረት ምክንያት
በሰራተኛው አካል ወይም በአካሉ በማንኛውም ክፍል ተፈጥሮአዊ እንቅስቃሴ ላይ በድንገት
የደረሰበት ጉዳት ማለት ነው።
25. “ኮሚቴ” በዚህ ደንብ መሰረት የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ የስራ መሪዎች የሚወክሏቸው
አካላት የሚገኙበት ኮሚቴ ማለት ነው።

6
26. “የአስተዳደር ስራ መመሪያ” ማለት አዋጁንና በመንግስት የሚወጡትን የአሰሪ እና
ሠራተኛ ጉዳይ የሚመለከት ደንቦችና መመሪያዎችን ሳይቃረን ቢዝነሰ ኢንተርፕራየዙ
ሚያወወጣው የስራ ደንብ ነው፡

አንቀጽ 3 አላማ
ይህ መመሪያ የሚከተሉት ዓላማዎች አሉት፡-

1. የኢንተርፕራይዙንና የሠራተኛዉን ጥቅም በህጉ መሰረት ማስጠበቅ


2. የሚመለከታቸው ጉዳዮችን በሚመለከት የአሠራር ወጥነትና ፍትኃዊነት እንዲኖር ማረጋገጥ
3. መመሪያውን ለሠራተኛው ተደራሽ በማድረግ ተቋማዊ መግባባት መፍጠር
4. በየደረጃው የሚገኝ የሥራ ኃላፊ ተዘውታሪ (routine) ተግባራት ላይ የሚያጠፋውን ጊዜ
መቆጠብ

አንቀጽ 4 የመመሪያው ተፈፃሚነት ወሰን


1. ይህ መመርያ በአዋጅ አንቀፅ 3 ንዑስ አንቀፅ 2 “ለ” የተገለፀውን እና በአንቀፅ “10“
መሠረት ለተወሰነ ጊዜ ወይም ለተወሰነ ስራ የሚቀጠሩ ሠራተኞችን አይመለከትም። ከዛ
ውጭ ቋሚ ሠራተኞች ብሎ ድርጅቱ የተቀበላቸው ሰራተኞች በሙሉ ይመለከታል።
2. በዚህ መመርያ ውስጥ ያልተመለከቱ ጉዳዮች በኢንተርፕራይዙ ደንብና መመሪያ ወይም
በአሰሪና ሠራተኛ በወጡ እና በሚወጡ የመንግስት ደንቦችና መመሪያዎች መሰረት ፍፃሜ
ያገኛሉ።
3. ይህ መመሪያ ለወንድ እና ሴት ፆታ እኩል ያገለግላል።

ክፍል ሁለት በቅጥር ላይ የተመሰረተ የስራ ግንኙነት


አንቀጽ 5 ቅጥር
1. የቅጥር አፈፃፀም
1.1 በኢንተርራይዞቹ ለሚፈፀም ቋሚ ቅጥር ከመፈፀሙ በፊት

ሀ/ ክፍት የስራ ቦታ መኖሩን


ለ/ ለስራ መደቡ በጀት የተፈቀደለት መሆኑን
ሐ/ ለስራው ሰራተኛ የሚያስፈልግ መሆኑ ሲታመንበት

1.2 በማንኛውም የስራ ደረጃ የሚወጣ ክፍት የስራ መደብ ማስታወቂያ የሚከተሉትን
መረጃዎች ማካተት ይኖርበታል፡-

ሀ/ የስራ መደብ መጠሪያ


ለ/ የስራ መደቡ ደረጃና ደመወዝ
ሐ/ የስራ ቦታ
መ/ ለስራ መደቡ የሚያስፈልገው የትምህርት አይነትና ደረጃ

7
ሠ/ ለሰራ መደቡ የሚያስፈልገው የስራ ልምድ
ረ/ የክፍት ስራ መደቡ ብዛት
ሰ/ የመመዝገቢያ ቦታ፣ ቀንና ስዓት
ሸ/ ፆታ ፣ እድሜ እንደ አስፈላጊነቱ
ቀ/ የቅጥር ሁኔታ /ቋሚ ወይም ኮንትራት/
በ/ የፈተና ቀኑ ወደፊት በውጥ ማስታወቂያ ይገለፃል
ተ/ ተያዥ
ቸ/ የስራ መደቡ ጥቅማ ጥቅም ካለው
ነ/ እንደ አስፈላጊነቱ የብቃት ማረጋገጫ
ኘ/ የስራ መደቡ የሚጠይቀው ልዩ እውቀት፣ ችሎታና ክህሎት ካለ

1.3 የቅጥር ማስታወቂያ በጋዜጣ ወይም ስራ ፈላጊ ያየዋል ተብሎ በሚታሰቡ የማስታወቂያ
ቦታዎች ለ 5 ተከታታይ የስራ ቀናት ተለጥፎ ምዝገባ ይካሄዳል።
1.4 ዲፕሎማ፣ ዲግሪ፣ ማስተርስ ለሚጠይቁ የስራ መደቦች የስራ መደቡ የስራ ልምድ
የማያስፈልግ ከሆነ እንደ አስፈላጊነቱ ፈተና መስጠት ሳያስፈልግ በ G.P.A ውጤት በመለየት
ቅጥር ይፈፀማል። ይህም በሰው ሀብት አስተዳደርና በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ አስተባባሪ
ቀርቦ ሲወሰን ተግባራዊ ይሆናል።
1.5 አንድ ሰራተኛ ሲቀጠር ቢያንስ የሚከተሉትን መረጃዎች ማሟላት ይኖርበታል፡-

ሀ/ የትምህርት ማስረጃ
ለ/ የስራ ልምድ /አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ/
ሐ/ የጤንነት ምርመራ ማረጋገጫ የሀኪም የምስክር ወረቀት
መ/ የሂወት ታሪክ ቅጽ መሙላት
ሠ/ የፖሊስ እጣት አሻራ መርመራ ውጤት
ረ/ ተያዥ ማቅረብ /አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ/
ሰ/ ቃለ ማሀላ መፈፀም፣ ሆኖም ከስራ ላይ ለሚቀጠሩ ሰራተኞች በ ሐ እና ሠ
የተጠቀሱት ግዴታ አይሆኑም።

1.6 የጣት አሻራና የጤንነት ምርመራ ውጤት ለማቅረብ የማይቻልበት ሁኔታ በጊዜያዊነት
ሲያጋጥም የሰው ሀብት አስተዳደርና የገቢ ማመንጫ ዋና አስተባባሪ ውሳኔ ይሰጡበታል።
1.7 ለአንድ ክፍት የስራ ቦታ ቢያንስ ሦስት ተወዳዳሪዎች ያልተገኙ እንደሆነ ለሁለተኛ ጊዜ
ማስታወቂያ በድጋሚ እንዲወጣ ተደርጎ በመጨረሻ የተገኙትን በማወዳደር ቅጥሩ
በኢንተርፕራይዙ ዋና አስተባባሪ ሲፀድቅ ቅጥሩ ይፈፀማል። የስራ መደቡ አስቸኳይነት
በድጋሚ ቢወጣም የመገኘት እድሉ ግምት ውስጥ ገብቶና ቅጥሩ የሚፈፀምለት የስራ ክፍል

8
አስተያየት ተጠይቆ መስፈርቱን አሟልተው ለውድድር የቀረቡ ቁጥራቸው ከሦስት በታች
ቢሆን በሰው ሀብት አስተዳደር ቅጥር እንዲከናወን በመስፈርቱ መሰረት የውሳኔ ሀሳብ
ከቀረበና በኢንተርፕራዙ ዋና አስተባባሪ ፀድቆ የተገኙትን ተወዳዳሪዎች በማወዳደር ቅጥሩ
ይፈፀማል።
1.8 በቢዝነስ ኢንተርፕራዙ ውስጥ በኮንትራት ተቀጥረው በማገልገል ላይ የሚገኙ ሰራተኞች
ለቦታው የተጠቀሰውን መስፈርት አሟልተው ከተገኙ በቋሚ የስራ መደብ ላይ ተመዝግበው
ሊወዳደሩ ይችላሉ።
1.9 በቢዝነስ ኢንተርፕራዙ በዲሲፕሊን የተሰናበተ ሰራተኛ በድጋሚ መቀጠር አይችልም።
1.10 በተመሳሳይ ቀንና ቁጥር ከወጡ የተለያዩ ማስታወቂያዎች መካከል አንድ
አመልካች መመዝገብ የሚችለው በአንድ ክፍት የስራ መደብ ብቻ ይሆናል።
1.11 አዲስ ሰራተኛ ሲቀጠር አመልካቹ ለስራው ተፈላጊ ችሎታ ያለው መሆኑን
ለማረጋገጥ እንደ አስፈላጊነቱ የፅሁፍና የቃል ወይም የተግባር ፈተና ይሰጣል።
1.12 አንድ ሰራተኛ የሙከራ ጊዜውን ፈፅሞ በውሉ መሰረት ሲቀጠር ደብዳቤ
እንዲሰጠው ይደረጋል፣ በልዩ ልዩ ምክኒያት ደብዳቤ ሳይደርሰው ቢቀር በውሉ ጊዜ
እንደተቀጠረ ይቆጠራል።
1.13 በአጠቃላይ ውጤት የነጥብ ብልጫ አግኝቶ/ታ የተመረጠ/ች ተወዳዳሪ የጥሪ
ማስታወቂያ ለ 3 ተከታታይ የስራ ቀናት በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ እንዲለጠፍ ይደረጋል፣
በ 3 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ቀርቦ ሪፖርት ካላደረገ አንደኛ ተጠባባቂ በተመሳሳይ
መንገድ እንዲቀጠር ይደረጋል። አንደኛ ተጠባባቂ ካልቀረበ በውጤታቸው መሰረት
በተከታታይ ጥሪ በማድረግ እንዲቀጠሩ ይደረጋል።

አንቀጽ 6 የቅጥርና የደራጃ እድገት ኮሚቴ አባላት

የኮሚቴው አባለት
ሀ. የሰው ኃይል አስተዳደር (ፐርሶኔል)……………………………….. ሰብሳቢ
ለ. በስራ አስከያጁ የሚመረጡ 2 የማኔጅመንት አባላት……………… አባል
ሐ. ቅጥር የሚፈፀምለት መምሪያ አስተባባሪ ……………..……..…… ፀሃፊ
መ. 2 የሰራተኞች ተወካዮች ………………..…………………...…… አባል

አንቀጽ 7 የቅጥርና ደረጃ እድገት ኮሚቴ ተግባርና ሀላፊነት


ሀ/ የአመልካቾችን መረጃ ማጣራት
ለ/ በወጣው ማስታወቂያ መሰረት የስራ መደቡ የሚጠይቀው የትምህርት ደረጃና የስራ
ልምድ ተሟልቶ መገኘቱን ማረጋገጥ፣
ሐ/ የተግባር ፈተና መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በመመዘኛ የፈተና አሰጣጥ ስርአት
ይፈፀማል
መ/ የቅጥርና ደረጃ እድገት ባለሙያዎች ቡድን ውሳኔ የሚሰጠው በድምፅ ብልጫ
ቢሆንም በሀሳብ የሚለይ ካለ ግን የተለየበት ምክኒያት በግልፅ በፅሁፍ ይቀርባል።

9
ሠ/ የቅጥርና ደረጃ እድገት የደመወዝና የደረጃ ሁኔታ በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ቦርድ
በሚሰጠው ደረጃና መጠን የሚወሰን ይሆናል።

አንቀጽ 8 የመወዳደሪያ መስፈርት


1. እንደሚወጡት የስራ መደቦች ማስታወቂያ የተወዳዳሪ መመዘኛ የተግባር፣ የፅሁፍ፣ የቃል
ወይም በነዚህ ጥምረት ፈተናው መሰጠት ያለበት ስለመሆኑ በሰው ሀብት አስተዳደር ቅጥሩ
ለሚፈፀምለት ክፍል ያሳውቃል።
2. የተወዳዳሪዎች መመዘኛ ነጥብ አመዳደብ

ሀ/ የተግባር ፈተና ለሚጠይቁ የስራ መደቦች


 ለተግባር ፈተና 70%
 ለፅሁፍ ፈተና 20%
 ለቃል ፈተነሰ 10%
 ለጽሁፍ ፈተና የሚቀርበው የተግባር ፈተና ከግማሽ በላይ ያመጣ
ሲሆን ነው፣ ይሁን እንጅ የጽሁፍና የቃል ፈተና መስጠት አስፈላጊ ሆኖ
በማይገኝበት ጊዜ 100% የተግባር ፈተና ይወስዳል።
ለ/ የተግባር ፈተና የማይጠይቁ የስራ መደቦች፡-

 ለፅሁፍ ፈተና 70%


 ለቃል ፈተነሰ 30% ይሆናል
ሐ/ የቃልና የተግባር ፈተና መስጠት በማያስፈልግበት የስራ መደብ ላይ የጽሁፍ
ፈተና 100% ይይዛል።

መ/ ለሴቶች 3% በተጨማሪነት የተግባር ፈተና ለሚጠይቅም ለማይጠይቅም


ውድድሮች ነጥብ ይሰጣል።

ሠ/ አሸናፊው በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ለመቀጠር 50% እና ከዛ በላይ ማግኘት


አለበት።

ረ/ ለቅጥር በሚደረገው ውድድር የስራ አፈፃፀም የምዘና ውጤት ለተወዳዳሪዎች


አያገለግልም።

ሰ/ አካል ጉዳተኞችን ሊያሳትፍ የሚችል የስራ መደብ ላይ አካል ጉዳተኛ ተወዳዳሪ


የፈተናውን ማለፊያ ውጤት ካገኘ ቅድሚያ ይሰጠዋል።

10
3. 12 ኛ ክፍል ያጠናቀቀ ወይም ከ 1992 ዓ.ም በኋላ 10 ኛ ክፍል ያጠናቀቀና ከዚያ በታች
የትምህርት ዝግጅት ያላቸውን ለሚጋብዙ የስራ መደቦች ተወዳዳሪዎች የሚያቀርቡት
ያገልግሎት ማስረጃ ከሚወዳደሩበት መደብ ጋር ያለውን ተዛማጅነት በቀጥታና በተዘዋዋሪ
ይዛመዳል ወይም አይዛመድም ብሎ መፈረጅ ሳያስፈልገው እንዲወዳደሩበት ይደረጋል።
ይህም ማለት ፈተናውን ማለፍ እስከቻሉ ድረስ የስራ ልምዳቸው በሁለገብነት
ያገለግላቸዋል።
4. በተለያየ ሙያ ስልጠና ሰርፍትኬት ፣ ዲፕሎማ በሚጠይቁ የስራ መደቦች ላይ 12 ኛ ክፍል
ያጠናቀቁና ከ 1992 ዓ.ም በኋላ 10 ኛ ክፍል ያጠናቀቁና ከዛ በታች የሆኑ የትምህርት
ዝግጅት ያላቸው አብረው የሚጋበዙበት ሁኔታ ሲኖር የሚያቀርቡት ማስረጃ ለስራ መደቡ
አግባብ ያለው ሊሆን ይገባል። የስራ መደቡ የሚጠይቀውን የሙያ መስፈርት ፣ የትምህርት
ዝግጅት ወይም በልምድ /በሁሉም/ አሟልተው ያልቀረቡ መወዳደር አይችሉም። ይሁን
እንጅ ኢንተርፕራይዙ የተሻለ ብቃት ያለው ሰራተኛ በተለየ ሁኔታ ሊቀጥር ይችላል።
5. ለአንድ ስራ መደብ ለመወዳደር ከሚጠይቁት ተፈላጊ ችሎታዎች በላይ ማስረጃ ይዘው
የሚቀርቡ ቢኖሩ ማስረጃው ተጨማሪ ነጥብ አያስገኝም፣
6. ለአንድ የስራ መደብ በርካታ አመልካቾች በሚቀርቡበት ጊዜ በቅጥርና በደረጃ እድገት
ኮሚቴው አማካኝነት የማጣሪያ ምርጫ በማድረግ ተመራጭ ችሎታና ብቃት ያላቸውን
እጩዎች ብቻ መርጦ ለውድድር ሊያቀርብ ይችላል። በእጩነት የሚቀርቡ ተወዳዳሪዎች
እስካሉ ድረስ ቢያንስ ለአንድ መደብ ከሦስት ያላነሱ ተወዳዳሪዎች ቢሆኑ ይመረጣል፣
ካልሆነ ግን አንድም ተወዳዳሪ ቢሆን ከተቋሙ ጥቅም አንፃር ተመዝኖ ቅጥር ሊፈፀም
ይችላል።
7. ተፈላጊው ሰራተኛ ለመቅጠር ተፈላጊ ችሎታውን የሚያሟላ ካላገኘ የሚከተሉትን
ሁኔታዎች በማሟላት ሰራተኛ በታሳቢ ሊቀጥር ይችላል። ክፍት ለሆኑ ዲግሪና ከዚያ በላይ
ለሚጠይቁ የስራ መደቦች ተወዳዳሪ በዝውውርም ሆነ በደረጃ እድገት በማይገኝበት ጊዜ
የኢንተርፕራይዙ የስራ አመራር ቦርድ በወሰነው ደረጃና ደመወዝ በታሳቢነት ቅጥር
እንዲፈፀምለት ያደርጋል።

ሀ/ የታሳቢ ቅጥር አፈፃፀም ከመደበኛ ቅጥር ስርአት የተለየ ሂደት አይኖረውም።

ለ/ ታሳቢ ቅጥር የሚፈፀመው የመጀመሪያ ዲግሪና ከዚያ በላይ የትምህርት ዝግጅት


ያለው ባለሙያ ለማግኘት አንድ ጊዜ የቅጥር ማስታወቂያ ወጥቶ አሟልቶ

11
የሚቅርብ ሳይኖር ሲቀር ወይም በቂ ባለሙያዎች ቀርበውም ዝቅተኛውን
የማለፊያ ነጥብ ሳያሟሉ ሲቀሩ ነው።

ሐ/ በታሳቢ የሚቀጠሩ ሰራተኞች ወደፊት የስራ መደቡን ሊይዙ የሚችሉት ደረጃ


እድገት ስርአትን ተከትሎ ከኢንትርፕራይዙ ነባር ሰራተኞች ጋር በመወዳደር
ብልጫ ነጥብ ያገኘ እንደሆነ ብቻ መሆን ይኖርበታል። ሆኖም ከአንድ አመት
በታች የሚጠይቅ አገልግሎት ከሆነ የአገልግሎት ጊዜውን ሲያሟላ ያለ
ውድድር ይሰጣል።

አንቀጽ 9 በተወዳዳሪዎች ስለሚቀርቡ መስረጃዎች


1. የትምህርት ማስረጃ ተቀባይነት የሚኖረው፡-

ሀ/ በትምህርት ሚኒስቴር እውቅና ከተሰጠው ት/ት ቤት ሆኖ የሚቀርበው ማስረጃ


ወይም ትራንስክቢት ስርዝ ድልዝ የሌለው የት/ቤቱ ርዕሰ መምህር /ስልጣን
የተሰጠው ሀላፊ/ የፈረመበት፣ የፈራሚወው ስምና ማእረግ፣ ማስረጃ የተሰጠበት
ቀንና ዓመተ ምህረት እንዲሁም የት/ቤቱ ማህተምና የባለ ማስረጃው ፎቶ ግራፍ
ያለበት ሆኖ ሲገኝ፣

ለ/ ከዩኒቨርሲቲ /ኮሌጅ/ የተሰጡ የትምህርት ማስረጃና ትራንስክርኒት ለሪጅስትረሩ


ወይም በትምህርት ቤቱ ማህትም ሲረጋገጥና ከተቻለም የባለ ማስረጃው ፎቶ
ግራፍ ያለበት ሲሆን፣

ሐ/ የኮሌጅ /ዩኒቨርሲቲ/ ትምህርት ከሆነ በፈፀመው የትምህርት ዓመት የተወሰነው


የትምህርት ስዓት ወይም ክሬዲት ሀወር ማጠናቀቁ ከደረጃ ጋር አጣጥሞ የሚገልፅ
መሆኑ ሲረጋገጥ፣

መ/ የብቃት ማረጋገጫ ሙያ ላይ የተሟላ ማስረጃ ሲቀርብ፣

2. ማንኛውም ከውጭ የተገኘ ዲግሪ/ዲፕሎማ/ ደረጃው ያልተወሰነ የትምህርት ማስረጃ


ሲያገኝም አስቀድሞ ለትምህርት ሚኒስቴር እየቀረበ የአቻ ግምት ሊሰጠው ይገባል።
3. የስራ ልምድ የሚባለው የመንግስት መ/ቤቶች ወይም መንግስታዊ ባልሆኑ እና አለማቀፋዊ
ድርጅቶች ህጋዊ አቋምና የተሟላ አደረጃጀት ኖሮቸው ተገቢውን የስራ አፈፃፀም ውጤት
በየወቅቱ ክትትልና ቁጥጥር በሚያደርጉ የግል ድርጅቶች ውስጥ ቋሚ ደመወዝ

12
እየተከፈላቸው በመደበኛ የስራ ስዓት የተወሰነ ስራን ለማከናወን ሊቀስም የሚችለውን
የስራ ችሎታን የሚገልፅ ማስረጃ ሲሆን ማስረጃውም የተሟላ ነው የሚባለው፡-

ሀ/ የመ/ቤቱ አርማ ወይም መጠሪያ

ለ/ ወጭ የሆነበት ቀንና ቁጥር

ሐ/ የሰራበትን ሙያ ፣ የስራ መደቡ መጠሪያ ፣ ደመወዝና የአገልግሎት ዘመን

መ/ የራስጌ እና የግርጌ ማህተም ኖሮት የሀላፊው ስም ፣ የስራ ደረጃና ፊርማ


ሊይዝ ይገባል፣

ሠ/ በሰሩበት ዓመታት የስራ ግብር መክፈላቸውን የሚገልፅ መረጃ ሲቀርብ ነው።

4. ፈተናውን ያለፉት ተወዳዳሪዎች ዝርዝር የኮሚቴውን የውሳኔ ሀሳብ የያዘ የመረጣ ሂደቱ ቃለ
ጉባኤ ጋር በውጤታቸው ቅደም ተከተል ተደራጅቶ ስራ አስከያጁ ቀርቦ የመጨረሻ ውሳኔ
እንዲሰጥበት ይደረጋል። ዳይሬክተሩ በማይገኝበት በተወካይ ውሳኔ እነዲሰጥበት ይደረጋል።

አንቀጽ 10 የሙከራ ጊዜ ቅጥር


በአዋጁ 1156/11 አንቀጽ 11 ንዑስ አንቀጽ 1-7 በተመለከተው እና በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ የሥራ
ደንብ መሠረት አዲስ የሚቀጠር ሰራተኛ የሙከራ ጊዜን በተመለከተ እንደሚከተለው ይሆናል።
10.1 ሙከራ ላይ የሚገኝ ሰራተኛ የሙከራ ጊዜውን የጨረሰ ሌላ ሰራተኛ ያለውን መብትና
ግዴታ ይኖረዋል።
10.2 የሙከራ የቅጥር ጊዜ ሰራተኛዉ ከተቀጠረበት ጊዜ ጀምሮ ለ 60 የስራ ቀናት ይሆናል፣
10.3 በሙከራ ላይ የሚገኝ ሰራተኛ በገባው ውል እና በተሰጠው የሥራ መዘርዘር መሰረት
የሙከራ ጊዜውን ከመፈፀሙ ከ 15 ቀን አስቀድሞ የቅርብ ኃላፊው ለቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ
እሴት የሚያመጡ አስቀድመው በተሰጡት መመዘኛዎች መሰረት የሙከራ ጊዜ የሥራ
አፈፃፀም ምዘና ሪፖርት ሞልቶ ለሰው ኃይል አስተዳደር ሃላፊ እንዲደርስ ያደርጋል።
10.4 ሰራተኛው በሙከራ ጊዜው የሥራ አፈፃፀም ምዘና ሪፖርት መሰረት አፈፃፀሙ ከ 3 በታች
ካገኘ ሰራተኛው ተስማሚ ስለማይሆን ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ያለ ማስጠንቀቂያ እና የሥራ
ስንብት ክፍያ እና ካሳ ሳይከፍል የስራ ውሉን ሊያቋርጥ ይችላል።
10.5 ሰራተኛውን በሙከራ ጊዜ የስራ አፈፃፀም ምዘና ሪፖርት መሰረት የሙከራ ጊዜውን
ከመጨረሱ በፊት የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ ሆኖ መቀጠል ወይም ያለመቀጠሉን
የሚገልጽ ደብዳቤ እንዲደርሰው ይደረጋል።
10.6 በሙከራ ላይ ያለ ሠራተኛ በሙከራ ጊዜው ስራውን ያለ ማስጠንቀቂያ ሊለቅ ይችላል
ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙም ሰራተኛውን ያለማስጠንቀቂያ ሊያሰናብተው ይችላል።
10.7 የሙከራ ጊዜውን የጨረሰ ሰራተኛ በቋሚነት እንዲቀጠር ሲደረግ በቋሚነት ቅጥሩ
ለሙከራ ከተቀጠረበት ጀምሮ ይቆጠርለታል።
10.8 የሙከራ ጊዜውን የጨረሰ ሰራተኛ በውሉ መሠረት የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ
መሆኑን የሚያረጋግጥ ደብዳቤ ይሰጠዋል ሆኖም የጽሁፍ ማረጋገጫ ሳይሰጠው ቢቀር
እንደቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ቋሚ ሰራተኛ ይቆጠራል።

13
አንቀጽ 11 የስራ ውል
በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ መዋቅር እና የረጅም ጊዜ የሰው ኃይል ዕቅድ መሰረት ክፍት የስራ መደብ
በሚኖርበት ጊዜ ኢንተርፕራይዙ ውስጥ ካሉ ሰራተኞች መካከል በዝውውር ወይም በዕድገት
በክፍት ቦታው ላይ ሰራተኛ መመደብ ሳይችል ሲቀር በአዋጁ እና በዚህ መመሪያ መሰረት ሰራተኛ
ቅጥር ይፈጽማል። የሰራተኛ ቅጥር እና የሥራ ውል ይዘት በአዋጁ መሰረት ይሆናል

አንቀጽ 12 የሥራ ውል አመሰራረት


1. ማንኛውም በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ እና ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ የሚቀጥረው ሰራተኛ መካከል የሚኖር የስራ
ውል በአዋጁ አንቀጽ 4 መሰረት ይሆናል።
2. በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ከሰራተኛው ጋር ለሚያደርገው የስራ ውል በአግባቡ የተዘጋጀ ፎርም ይኖረዋል።

አንቀጽ 13 የስራ ውል የሚቆይበት ጊዜ


በአዋጁ በአንቀጽ 10 ከተመለከቱት በቀር ማንኛውም የሥራ ውል ላልተወሰነ ጊዜ እንደተደረገ
ይቆጠራል።

አንቀጽ 14 የሥራ ግንኙነቶች


የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ የሥራ ግንኙነቶች ከላይ ወደታች ለሥራ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች
ለሠራተኛው በየደረጃው ተደራሽ የሚሆኑበት፣ ከታች ወደ ላይ የሠራተኛው ሀሳቦች
የሚስተናገዱበት እና አሳታፊ አሠራር የሚጠናከርበት ሲሆን በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙና ሠራተኛው
የሚኖሩ መብቶችና ግዴታዎች በዚህ መመርያና በአዋጁ መሰረት ይወሰናል።

አንቀጽ 15 የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ መብቶች

1. የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ አሳማኝ ስትራቴጅና ፖሊሲ እንዲሁም የአሰራር ስርዓት፣ የአሰራር


ማንዋሎችና የአሰራር ዘዴዎችን የመዘርጋት፣ ተግባራዊ የማድረግና የመለወጥ።
2. የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ የመቅጠር፣ ዕድገት የመስጠት፣ የማዛወር፣ የማስተዳደር፣
የእርከንና የደመወዝ ጭማሪ የማድረግ እና ሰራተኛውን የመቆጣጠር።
3. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ የሰራተኛ አዋጁን ሳይፃረር ለሰራተኛ ኃላፊነት የመስጠት፣ ከኃላፊነት
የማውረድ፣ የመቅጣት፣ የፍርድ ቤትን ውሳኔ ሳይጠብቅ እና ሳያግደው ከስራ የማገድ ወይም
የማሰናበት።
4. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ በአዋጁ የማይካተቱ እንደ ቅጥር፣ ስልጠና ወዘተ… ያሉ ጉዳዮችን
በሚመለከት የራሱ ፖሊሲዎች፣ ደንቦች እና የሥራ መመሪያዎች የማውጣትና የማስፈፀም።
5. ሌሎች በአዋጁ የተደነገጉ መብቶችን የመፈፀም መብት ይኖረዋል።

አንቀጽ 16 የሰራተኞች መብቶች


1. ማንኛውም ሰራተኛ ምንም አድልዎ ሳይደረግበት ከአዋጁ እና በ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ
መመሪያ መሰረት ሊያገኝ የሚገባው መብቶችና ጥቅማጥቅሞች የማግኘት መብት
አለው።
2. አንድ ሰራተኛ ከአዋጁ እና ከሥራ ደንቡ ውጭ ከሥራ መሰናበት፣ መታገድ ወይም
ከቦታ ቦታ መዛወር አይፈፀምበትም።
3. በአዋጁ አንቀጽ 54 ንዑስ አንቀጽ 2 መሰረት ሰራተኛው ለሥራ ዝግጁ ሆኖ
በሰራተኛው ጉድለት ባልሆነ ምክንያት ሳይሰራ ቢውልም ደመወዙን የማግኘት መብት
አለው።
4. ሌሎች በአዋጁ የተገለፁ መብቶች ይኖሩታል።

14
አንቀጽ 17 የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ግዴታዎች
ቢዝነስ ኢንተርፕራየይዙ የሚከተሉት ግዴታዎች ይኖሩታል፡-
1. በአዋጁ ወደፊት መንግስት የሚያወጣቸው ህጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎችን የማክበር።
2. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ የተቋቋመበትን ዓላማና ስትራቴጂ፣ ራዕይ፣ ተልዕኮና እንዲሁም
አሰራር ስርዓትና የሥራ ዕቅድ የማሳወቅ።
3. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ለሥራ መሪዎች እና ለሰራተኞች የአዋጁን ትርጉም፣ መንፈስና
አፈፃፀም በሚገባ እንዲረዱ አስፈላጊውን ሁሉ ማድረግ።
4. በአዋጁ አንቀጽ 92 ስለ ሙያ ደህንነት፣ ጤንነት እና የሥራ አካባቢ የተዘረዘሩትን የስራ
ግዴታዎች መወጣት፣ በሥራ ላይ ሊደርሱ ለሚችሉ የአደጋ መከላከያዎችና የሥራ እና የደንብ
ልብስ የማቅረብ እንዲሁም አግባብ ያላቸው መ/ቤቶች የሚሰጡትን መመሪያዎች የመከታተል
እና የመተግበር።
5. ለእያንዳንዱ ሰራተኛ የስራ ኃላፊነቱንና ገደብ የሚገልጽ የሥራ መዘርዝር የመስጠት፣
6. በስራ ውሉ መሰረት ሰራተኛው ስራውን በሚፈልገው ጊዜና ጥራት እንዲያከናውን እንደ
አስፈላጊነቱ ለሥራ የሚያስፈልገውን የሰው ኃይል፣ ማቴሪያልና መሳሪያ ማቅረብ።
7. የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ መሆኑን የሚያረጋግጥ መታወቂያ ለሰራተኛው ያለምንም
ክፍያ የመስጠት ግዴታ ሲኖረው ነገር ግን ሰራተኛው የተሰጠው መታወቂያውን ካጠፋ ላጠፋው
መታወቂያ ወረቀት ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ በሚያወጣው የክፍያ ስርዓት መሰረት ክፍያ
በመፈፀም ተለዋጭ መታወቂያ ይሰጣል።
8. ሰራተኛው በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ የስራ ደንብና በአዋጁ ማግኘት የሚገባውን ጥቅማጥቅም
በወቅቱ እንዲያገኝ ማድረግ።
9. በማንኛውም ሁኔታ የሰራተኛውን መብትና ክብር፣ ህሊና የሚነኩ ተገቢ ያልሆኑ አሰራሮችና
ተግባሮች ከመፈፀም መቆጠብ።
10. በአዋጅ አንቀጽ 12 ንዑስ አንቀጽ 2 መሰረት ለሰራተኛው ደመወዝና ሌሎች ተገቢ
ክፍያዎች የመክፈል።
11. በአዋጅ አንቀጽ 12 ንዑስ አንቀጽ 6 የሰራተኛው ጤንነት እነዲመረመር በህግ ወይም አግባብ
ባለው አካል ግዴታ በሚጣልበት ጊዜ ለምርመራው የሚያስፈልገው ወጪ ይሸፍናል።
12. በአዋጅ አንቀጽ 12 ንዑስ አንቀጽ 8 በተጠቀሰው መሰረት የስራ ውል በሚቋረጥበት ጊዜ
ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛው የነበረውን የሥራ ዓይነት፣ የአገልግሎት ዘመኑን፣ ሲከፈለው
የነበረውን ደመወዝ የሚያሳይ የምስክር ወረቀት ለሰራተኛው ያለክፍያ ይሰጣል።
13. ከአንድ የስራ ቦታ ወደ ሌላ የስራ ቦታ ለሚዛወር ሰራተኛ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ በቦታው
ሊያገኙ የሚገባውን ጥቅማጥቅሞች ይሰጣል።

አንቀጽ 18 የሠራተኞች ግዴታዎች


1. በአዋጁ አንቀጽ 13 ንዑስ አንቀጽ 1 እስከ 7 የተጠቀሱትን ግዴታዎች ማክበርና ከህገ ወጥ
ድርጊት መቆጠብ።
2. ቢዝነስ ኢንተርፕራየዙ የሚያወጣቸውን ስትራቴጂዎች፣ ከአዋጅ ጋር የማይቃረኑ ፖሊሲዎች፣
የአሰራር ስርዓቶች፣ ማንዋሎች ህጐችና ደንቦች ማክበርና መፈፀም።
3. የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ዓመታዊ ዕቅድ ግቡን እንዲመታ የስራ ውጤት ለማምጣት ሙሉ
ችሎታውንና ጊዜውን ስራ ላይ ማዋል። አዳዲስ ሃሳቦችን ማፍለቅ፣ ስራውን በተነሳሽነትና
በጥራት መስራት ይኖሩበታል።
4. በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ተቀጣሪ ሆኖ እስካለ ድረስ የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙን ጥቅም
የሚጐዳ ስራና ከቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ውልና ስምምነት ውጭ አለመስራት።

15
5. ለሥራው ሲባል የተሰጡትን ማቴሪያሎችና ንብረቶች ወጪ ቆጣቢ በሆነ፣ ወጪን መቀነስ
በሚያስችል አግባብ ረጅም የአገልግሎት ዘመን መስጠት በሚያስችል አግባብ መያዝና
መጠቀም።
6. አደጋ የሚያስከትሉ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ በቀጥታ ቢመለከተውም ባይመለከተውም አደጋው
ከመድረሱ በፊት ለሚመለከተው አካል አስቀድሞ ማሳወቅ፣ በሥራ ቦታ ወይም በሰራተኛው
ላይ አደጋ ሲደርስ ግንባር ቀደም ሆኖ መቆም፤መርዳትና መተባበር።
7. ለራሱ እና ለሥራ ጓደኞቹ እንዲሁም ለሌሎች ሰዎች ደህንነትና ለ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ
ሥራ ጐጂ የሆኑና አሉታዊ ተጽዕኖ የሚያመጡ ድርጊቶችን አለመፈፀም፣ ሌሎችም ሲፈዕሙ
ሲመለከት ለሚመለከተው ኋላፊ ማሳወቅ።,
8. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ በሚያቀርብለት የሰው ኃይል፣ ማቴሪያልና የሥራ መሣሪያ ተጠቅሞ
ውጤታማ ሥራ የመስራት ግዴታ አለበት።
9. በሚመለከተው ባለስልጣን ፈቃድ ካልተሰጠ በስተቀር በሥራ ምክንያት በእጁ የገባውን ሰነድ
እና ሚስጥር፣ ማናቸውም የድርጅቱን ንብረት መሳሪያ ወይም ቁሳቁስ ለግል ጥቅሙ መውሰድ
ወይም ለ 3 ኛ ወገን አሳልፎ መስጠት ወይም ከድርጅቱ ሥራ ጋር ላልተያያዙ ተግባር
አለማዋል። ሌሎችም እንዳይፈፀሙ የመቆጣጠር ሲያጋጥመውም ለሚመለከተው ኃላፊ
ማሳወቅ።
10. በአዋጁና በዚህ የአስተዳደር መመሪያ የተጠቀሱትን የስነ - ስርዓትና ዲሲፕሊን ደንቦች
ማክበር ሌሎችም እንዲያከብሩ ማድረግ፣ የማያከብሩ ሲያጋጥሙ ለሚመለከተው ኃላፊ ሪፖርት
ማድረግ።
11. ሰራተኛው ለሕይወቱ ወይም በሥራ ባልደረባው ወይም በሌሎች ሰዎች ወይም በስራ ሁኔታ
አደጋ ከሚያስከትል ከማናቸውም ድርጊት መራቅ።
12. ሰራተኛው በስራ ውሉና በስራ ደንቡ መሰረት በቅርብ ኃላፊ የሚሰጡትን የስራ ትዕዛዝና
መመሪያ መፈፀም።
13. ማንኛውም ሰራተኛ በስራ ሰዓትና በስራ ላይ የተሰጡትን የአደጋ መከላከያ መሳሪያዎችን
መጠቀም፣ የራሱን ንጽህና መጠበቅ እና የተሰተካከለ አልባሳት መልበስ አለበት።
14. ማንኛውም ሰራተኛ በራሱ ፈቃድ ስራ በሚለቅበት ጊዜ ለኢንተርፕራይዙ ከአንድ ወር
በፊት የማሳወቅ ግዴታ አለበት።
15. የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙን አንድነት፣ ሰላም የሚያናጋ የሀሰት ወሬና አልቧልታ ከመንዛት
መቆጠብ፣ የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙን ጥቅም የሚፃረር ስራ በወሬም ይሁን በተግባር
አለመፈፀም፣ ሌሎችም እንዳይፈጽሙ መቆጣጠርና ሲያጋጥመዎ ለሚመለከተው የቢዝነስ
ኢንተርፕራይዙ ኃላፊ ማሳወቅ /ሪፖርት/ ማድረግ።
16. በምርት ላይ የተሰማሩ ሰራተኛ ለምርት ሂደት ፈርሞ የተረከባቸውንና የተሰጡትን ጥሬ
ዕቃዎችና ሌሎች ማቴሪያሎች በአግባቡ በተቀበለበት ስታንዳርድ መሰረት ተጠቅሞ የምርት
ሂደቱን ሪፖርት እና የእጅ ቀሪ ጥሬ ዕቃና ማቴሪያል ከተቀበለው ጋር አገናዝቦ የባከነውን
በሪፖርት መልክ አስቀምጦ በሰነድ የማስረከብ።
17. በተጨማሪም ኃላፊው የሚያዘውን ተጨማሪ ሥራዎች የመስራት ግዴታ አለበት።

አንቀጽ 19 የስራ ውል የሚሻሻልበት ሁኔታ


በአዋጁ መሰረት በሚወጡ የሰራ ደንቦች መመሪያዎች እና በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ በሚያወጣቸው የስራ
ደንቦች መሰረት ይሆናል።

አንቀጽ 20 ከስራ ውል የሚመነጩ መብትና ግዴታዎችን ለጊዜው ስለማገድ


1. ከስራ ውል የሚመነጩ መብትና ግዴታዎችን ለጊዜው ማገድን በተመለከተ በአዋጁ ከአንቀጽ
17-22 በተገለፀው መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል።

16
2. ሰራተኛው ፈፀመ የተባለው ጥፋት እስከሚጣራ ድረስ ሰራተኛውን ከስራ ደህንነት በተያያዘ
ጉዳይ ማገድ አስፈላጊ ሁኖ ሲገኝ ወድያው ለተወሰነ ጊዜ ያለ ደመወዝ ከስራው ማገድ ይቻላል።

አንቀጽ 21 ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ከሰራተኛው ጋር ያደረገው የስራ ውል ስለሚቋረጥበት ሁኔታ


1. በአዋጁ በአንቀጽ 23 እና ቀጥለው በተዘረዘሩት አንቀፆች መሰረት ባሉት ሁኔታዎች የስራ ውል
ይቋረጣል።
2. በዚህ መመሪያ አንቀጽ 12.1 መሰረት የስራ ውል ሲቋረጥ ደመወዝና ከደመወዝ ጋር የተያያዙ
ክፍያዎች ድርጅቱ በአዋጁ አንቀጽ 36-38 በተጠቀሰው መሰረት ይፈፀማል።

አንቀጽ 22 የስራ ውል ከመቋረጡ በፊት ስለሚሰጥ ማስጠንቀቂያ ስነ-ስርዓት


1. በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙና በሰራተኛው የስራ ውል ከመቋረጡ በፊት የሚሰጥ ማስጠንቀቂያ
በአዋጁ አንቀጽ 31፣34 እና 35 መሰረት የሚፈፀም ይሆናል።
2. በአዋጁ አንቀጽ 34 መሰረት በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ወይም በሰራተኛው የሚሰጥ
ማስጠንቀቂያ ውሉ የሚቋረጥባቸውን ምክንያቶች እና ውሉ የሚቋረጥበትን ቀን የሚገልፅ ሆኖ
በፅሁፍ መሆን አለበት፣ በፅሁፍ ያልተሰጠ ማስጠንቀቂያ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል።
3. በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ወይም በወኪሉ የሚሰጥ ማስጠንቀቂያ ለሰራተኛው በእጅ መስጠት
አለበት።
4. ሰራተኛውን ማግኘት ካልቻለ ወይም ሰራተኛው ማስጠንቀቂያውን ለመቀበል ፈቃደኛ ካልሆነ
ማስጠንቀቂያው ሰራተኛው በሚገኝበት የስራ ቦታ ለ 1 ዐ ተከታታይ ቀናት ግልፅ በሆነ
የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ይለጠፋል።

አንቀጽ 23 የስራ ስንብት እና የካሳ ክፍያ


የሙከራ ጊዜውን የጨረሰ ሰራተኛ እና በአዋጁ ቁጥር 1156/11 መሰረት የስራ ውሉ ለተቋረጠበት ሰራተኛ
ከቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ የስራ ስንብት ክፍያ በአዋጁ አንቀጽ 39 እና 40 መሰረት የማግኘት መብት
አለው።

አንቀጽ 24 ዝውውር
አንድ ሰራተኛ በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ውስጥ ከአንድ የሥራ መደብ ወደ ሌላ ተመሳሳይ የሥራ
መደብ የማዛወር አላማ ስራ እና ሰራተኛውን በማገናኘት የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ የሥራ
እንቅስቃሴ ውጤታማ ለማድረግ የሚሰራ ስራ እንደተጠበቀ ሁኖ:-

1. በኢንተርፕራይዙ ውስጥ ዝውውር የሚፈፀመው የሰራተኛውን እውቀት እና ችሎታ በበለጠ


ለመጠቀም እና ሰራተኛው በሚዛወርበት ተመሳሳይ የሥራ መደብ፣ ቦታ የተከሰቱ ችግሮችን
ለመፍታት የሚያስችልና ተጨማሪ እሴት የሚፈጥር ሲሆን ነው።
2. ሰራተኛው በራሱ ማህበራዊ ችግር ምክንያት ዝውውር ሲጠይቅ እና በዝውውር
በሚመደብበት ተመሳሳይ ሥራ ወይም የሚመደብበት ቦታ ሙሉ አቅሙን እና ችሎታውን
መጠቀም የሚያስችል ሁኔታ እና የሥራ መደብ ሲኖር ዝውውር ሊፈጽም ይችላል።
3. ሰራተኛው የተመደበበትን ስራ ለማከናወን ችሎታው ቀንሶ ሲገኝ የሰራተኛው የስራ ደረጃ ቀንሶ
ወደ ሌላ የስራ መደብ ተዛውሮ ሊሰራ ይችላል።
4. ሰራተኛው በሀኪሞች ቦርድ በተረጋገጠ የህክምና ማስረጃ በጤናው ምክንያት ወደ ሌላ ተመጣጣኝ
የስራ መደብ ወይም የስራ ቦታ ዝውውር ሲጠይቅና በጠየቀው ቦታ ሙሉ አቅሙን ተጠቅሞ
ውጤታማ ስራ መስራት የሚያስችል ተመጣጣኝ የሆነ ክፍት የስራ መደብ መኖሩ በኢንተርፕራይዙ
ሲረጋገጥ ይሆናል።

17
5. በልዩ ልዩ ምክንያት ጊዜያዊ ክፍት የስራ መስክ ስልጠና የወሰደ ሰራተኛ መመደብ ሲያስፈልግ
በኢንተርፕራይዙ በተመሳሳይ የስራ መስክ ስልጠና ከወሰደ ሰራተኛ መካከል በቋሚነት ወይም
በጊዜያዊነት አዘዋውሮ ሊያሰራ ይችላል።
6. ነፍሰ ጡር ሴት የምትሰራበት የስራ መደብ ለጤናዋ የማይመች መሆኑ በህክምና ቦርድ ሲረጋገጥ
የምታገኘው ጥቅም ሳይነካ የሚመጥናት ክፍት የስራ መደብ ከተገኘ ኢንተርፕራይዙ ለጤንነትዋ
ወደሚያመች ሌላ የስራ መደብ አና ቦታ ያዛውራታል፤
7. አንድ ሰራተኛ የተፈፀመበት ዝውውር አግባብነት የለውም ብሎ ሲያምን አቤቱታውን በቅሬታ
አቀራረብ ስነ-ስርዓት መሰረት የማቅረብ መብቱ የተጠበቀ ነው፤
8. አንድ ስራተኛ የጊዜያዊ ዝውውር ከ 6 ወራት ለበለጠ ጊዜ እንዲቆይ አይደረግም፤

አንቀጽ 25 የደረጃ ዕድገት

1. የደረጃ እድገት አፈፃፀም፡-


1.1 ክፍት የስራ መደቡ በመዋቅር የተጠናና በሰው ሀይል እንዲሟላ ጥያቄ ቀርቦ
በውስጥ ዝውውር ማሟላት የማይቻል መሆኑ ሲታወቅ የደረጃ እድገቱ ማስታወቂያ
ይወጣል።
1.2 የደረጃ እድገት ማስታወቂያ በሰው ሀብት አስተዳደር የሚወጣ ይሆናል።
1.3 የደረጃ እድገት ማስታወቂያ በኢንተርፕራይዙ ዋና ክፍል በርና በሌሎች ሰራተኛው
በግልፅ ሊያሳይ በሚችልበት ቦታ መለጠፍ አለበት፣ የደረጃ እድገት ማስታወቂያ
ከተለጠፈበት ቀን ጀምሮ ለ 5 ተከታታይ የስራ ቀናት እንዲቆይ ይደረጋል፣
1.4 በውክልና የሰራ ሰራተኛ በውክልና ሲሰራ በነበረበት የስራ መደብ ላይ የደረጃ እድገት
ወጥቶ ሲወዳደር ከሌሎች ተወዳዳሪዎች ጋር እኩል ነጥብ ካገኘ ቅድሚያ ይሰጣል፤
1.5 የደረጃ ዕድገት በኮሚቴው ከታዬ በኋላ ከውሳኔ ሃሳብ ጋር ለኢንተርፕራይዙ ስራ
አስከያጅ ቀርቦ የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥበት ይደረጋል። ስራ አስከያጁ
በኮሚቴው ውሳኔ ሀሳብ ካልተስማማ ያልተስማማበትን ምክንያት በመግለጽ ጉዳዩ
በኮሚቴ እንደገና እንዲታይ ያደርጋል። በኮሚቴው በቀረበው አስተያየት ላይ ስራ
አስከያጁ የሚሰጠው ውሳኔ የሚጸና ሆኖ እድገቱ በስራ አስከያጁ ካፀደቀበት ቀን
ጀምሮ ይሰጠዋል።
1.6 እድገት ለተሰጠው ሰራተኛ ስለ አዲሱ ስራው አስፈላጊውን መመሪያ በፅሁፍና በቃል
ሰራተኛው ስራውን ከመጀመሩ በፊት ይሰጠዋል።
1.7 የደረጃ እድገቱን የሰው ሀብት አስተዳደር ከሰራ እና ከጨረሰ በኋላ በኢንተርፕራይዙ
ስራ አስከያጅ በማቅረብ ያፀድቃል።

18
1.8 የኢንተርፕራይዙ ስራ አስከያጅ ያላፀደቀው እንደሆነ የደረጃ እድገቱ እንደገና
እንዲታይ ለሰው ሀብት አስተዳደር ይመለሳል፣ የሰው ሀብት አስተዳደርም
አስፈላጊውን ማስተካከያ ይሰራል።
1.9 የደረጃ እድገቱ የሚሰጠው እድገቱ በደብዳቤ ወጭ ከተደረገበት ቀን ጀምሮ ሲሆን
ክፍያውም በዚህ መሰረት ይፈፀማል።
1.10 ለደረጃ እድገት ብቸኛ ተወዳዳሪ ቢቀርብ መስፈርቱን ተፈትኖ ማለፊያ ውጤት
ካገኘ እድገቱን ሊያገኝ ይችላል።
1.11 እድገት ያገኘው ሰራተኛ የሙከራ ጊዜ አይኖረውም።
1.12 ደረጃ እድገት ያገኘ ሰራተኛ ለሌላ እድገት የሚወዳደረው እድገቱን ካገኘ ከ 9 ወር
በኋላ ይሆናል።
1.13 አንድ የደረጃ እድገት ያገኘ ሰራተኛ የደመወዝ መጠን ከስራ መደቡ ጋር እኩል
ወይም ከዚያ በላይ ከሆነ ያንድ እርከን ደመወዝ ይጨመረዋል።
1.14 የደረጃ እድገት ያገኘ ሰራተኛ ደመወዝ ከአዲሱ የስራ መደብ ደረጃ ጣሪያ እኩል
ወይም ከዚያ በላይ ሆኖ ከተገኘ ደመወዙ ያው የድሮው ይሆናል።
2. ለደረጃ እድገት ብቁ ስለመሆን፡-

ሀ/ ለክፍት የስራ መደቡ የሚጠየቀውን የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ የሚያሟላ፣


ለ/ የደረጃ እድገት ከዚህ በፊት ተሰጥቶት ከሆነ ከደረጃ እድገቱ በኋላ ቢያንስ 9 ወር
ያገለገለ፣
ሐ/ በኢንተርፕራይዙ ቢያንስ 9 ወር ያገለገለ፣
መ/ በውድድሩ ወቅት በዲስፕሊን አፈፃፀም መመሪያ ከስራ ያልታገደ እንዲሁም ከደረጃው
ዝቅ ብሎ እንዲሰራ ተወስኖበት የጊዜ ገደቡን ያልጨረሰ ፣ በወቅቱ የደመወዝ ጭማሪ
እገዳ ቅጣት የተቀጡ ለውድድር ብቁ አይሆኑም፣
ሠ/ የስራ አፈፃፀም ነጥቡ አማካኝ ውጤት 60% እና ከዚያ በላይ የሆነ፣
ረ/ የደረጃ እድገት የሚያስከለክል በማስረጃ ተደገፈ ምክኒያት የሌለበት፣
ሰ/ በእድሜው ምክኒያት ጡረታ ሊወጣ ከ 3 ወራት የበለጠ ጊዜ የሚቀረው ለደረጃ እድገት
በእጩነት ሊወዳደር ብቁ ሊሆን ይችላል፣
ሸ/ እድገት በሚሰጥበት ወቅት በመደበኛ /በቀን/ ትምህርት ላይ ያልሆነ መሆን አለበት፣
ቀ/ ለጡረታ እስከ 3 ወራት የቀራቸው ሰራተኞች ለደረጃ እድገት ሊወዳደሩ አይችሉም፣

19
በ/ የኮንትረት ስራ መደብ ሲኖር የኮንትራት ሰራተኞች ተወዳድረው እድገት ሊሰጣቸው
ይችላል፣ በዚህ መመሪያ የተቀመጡ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው፣

3. ለደረጃ እድገት የሚወዳደሩባቸው ርዕሶች፡-


1. እውቀጥና ክህሎት ለመመዘን የሚመዝን ፈተና፣
2. የስራ አፈፃፀም ውጤት፣
3. የማህደር ጥራት፣
4. ለደረጃ እድገት የሚቀርበው የትምህርት ማስረጃ ተቀባይነት የሚኖረው በዚህ መመሪያ
በአንቀጽ 9/1/ሀ በተገለፀው መሰረት ይሆናል፣
5. ለደረጃ እድገት የሚቀርቡ ደረጃቸው ያልተወሰኑ የትምህርት ማስረጃዎች በዚህ መመሪያ
አንቀጽ 1/9/ለ በተገለፀው ይፈፀማል፣
6. ለደረጃ እድገት የሚያዘው የስራ ልምድ በዚህ መመሪያ አንቀጽ 1/9/ሐ በተገለፀው መሰረት
ይፈፀማል፣
7. በደረጃ እድገት የሚያዘው የስራ መደብ የስራ ልምድ የሚጠይቅ ከሆነ የስራ መደቡ
የሚጠይቀውን የስራ ልምድ አሟልቶ ለመወዳደር ለመመዝገብ የሚያዝለት፡-

ሀ/ የባችለር ዲግሪና የስራ ልምድ ለሚጠይቅ የስራ መደብ ሰራተኛው ዲግሪውን ከማግኘቱ
በፊት ዲፕሎማውን ይዞ የሰራው አገልግሎት ከስራው ጋር በቀጥታ አግባብነት ያለው
አንድ ዓመት እንደ አንድ ዓመት ይያዝለታል፣

ለ/ ዲፕሎማና የስራ ልምድ ለሚጠይቅ የስራ መደብ ሰራተኛው ዲፕሎማውን ከማግኘቱ


በፊት የሰጠው አገልግሎት ከስራው ጋር በቀጥታ አግባብ ያለው የሁለት ዓመት የስራ
ልምድ እንደ አንድ ዓመት የስራ ልምድ ይያዝለታል፣

ሐ/ ማስተርስ በሚጠይቅ የስራ መደብ ላይ የመጀመሪያ ዲግሪ ይዞ ያገኘው የስራ ልምድ


የአንድ ዓመት የስራ ልምድ እንደ አንድ ዓመት የስራ ልምድ ይያዛል፣

መ/ በአሁኑ 10 ኛ ክፍል በድሮው 12 ኛ ክፍል በላይ ከዲፕሎማ በታች የትምህርት ዝግጅት


ለሚጠይቁ የስራ መደቦች አግባብ ያለው የስራ ልመድ አንድ ዓመት የስራ ልምድ እንደ
አንድ ዓመት ይያዛል፣

ሠ/ የተለያዩ የትምህርት ዝግጅት /ደረጃ/ ለሚጠይቁ የስራ መደቦች ዝቅተኛውን የትምህርት


ዝግጅት በመያዝ ልምድ ይመነዘራል / የልምድ አያያዝ ይወሰዳል/

8. 12 ኛ ክፍል ያጠናቀቀ ወይም ከ 1992 ዓ.ም በኋላ 10 ኛ ክፍልን ያጠናቀቀ /ከዚህ በታች
የትምህርት ዝግጅት ያላቸውን በደረጃ እድገት የሚጋበዙ የስራ መደቦች ተወዳዳሪዎች
የሚያቀርቡት የአገልግሎት ማስረጃ በተመለከተ በዚህ መመሪያ መሰረት የሚፈፀም ይሆናል፣

20
9. ለደረጃ እድገት የትምህርት ዝግጅትና የስራ ልምድ የሚያገለግለው ነጥብ በመስጠት
ለማበላለጥ ሳይሆን በደረጃ እድገት የወጣው ክፍት የስራ መደብ የሚጠይቀውን ተፈላጊ
ችሎታ መስፈርት በማሟላትና ለውድድር ለመመዝገብ ብቻ ይሆናል፣
10. በአንድ ደረጃ እድገት በወጣ ክፍት የስራ መደብ ለመወዳደር ከሚጠይቁ ዝቅተኛ ተፈላጊ
ችሎታዎች በላይ ማስረጃ ይዘው የሚቀርቡ ቢኖሩ ማስረጃው በተለየ ሁኔታ ታይቶ
ተጨማሪ ነጥብ አያስገኝላቸውም፣
11. የሰራተኛው የስራ አፈፃፀም መመዘኛ ቅጽ በየ 6 ወር አንድ ጊዜ ሚሞላ ቢሆንም ለደረጃ
እድገት ውድድር ግን የሚወሰደው ለተወዳዳሪው የሚሞላው 3 ቱ የመጨረሻ አማካኝ
ውጤት ነው። ቢያንስ በ 2 ቱ የስራ አፈፃፀም 50% እና በላይ መሆን አለበት፣
12. አዲስ ሰራተኛ ከሆነ የሁለት ጊዜ የስራ አፈፃፀም ይወሰድለታል፣
13. የደረጃ እድገት ማስታወቂያ ከወጣ በኋላ የሚሞላ የስራ አፈፃፀም በወቅቱ ለወጣው
ማስታወቂያ አይወሰድም፣
14. የዲስፕሊን ቅጣት ወይም አፈፃፀም በሰራተኛው ማህደር ውስጥ በሪከርድነት ተይዞ
ከሰራተኛው ላይ ሊጠቀስ ወይም የደረጃ እድገት ነጥብ ለማስቀነስ የሚችለው ከዚህ በታች
በመለከተው ሰንጠረዥ መሰረት ይሆናል፡-

 ተ.ቁ  የቅጣት አይነት  በአማካኝ የሚቆይበት


ጊዜ
 1  የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ  3 ወር
 2  ከ 1 – 5 ቀናት የደመወዝ ቅጣት  6 ወር
የተፃፈበት
 3  ከ 6 – 15 ቀናት የደመወዝ ቅጣት  9 ወር
የተፃፈበት
 4  ከ 15 ቀናት በላይ የደመወዝ ቅጣት  1 ዓመት
የተፃፈበት
 5  ከደረጃ ዝቅ የተደረገ  2 ዓመት

4. የደረጃ እድገት ነጥብ አሰጣጥ፡-


1. ለፈተና ------------ 60%
2. ለስራ አፈፃፀም -----30%
3. ለማህደር ጥራት --- 10%
4. ለደረጃ እድገት እውቀትና ክህሎት ለመመዘን የሚያስችል ፈተና 60% የሚይዝ
ሲሆን በእያንዳንዱ እድገት በሰው ሀብት አስተዳደር አቅራቢነት የፈተናው
አይነት ጥምረት ለገቢ ማመንጫ ዋና ክፍል ቀርቦ ይወሰናል፣ ፈተናው
የሚሰጡበት አማራጮች፡-

4.1 ለተግባር ፈተና ለሚጠይቁ መደቦች፡-


 ለተግባር ፈተና ------------ 60%

21
 ለፅሁፍ ፈተና ------------- 30%
 ለቃል ፈተና ---------------- 10%
4.2 የፅሁፍና የተግባር ፈተና መስጠት በማያስፈልግበት የስራ መደቦች ላይ የቃል ፈተና
ከ 100% ይወሰዳል፣

5. በደረጃ እድገት ለማህደር ጥራት 10% የሚይዝ ሲሆን ዝርዝር አፈፃፀሙም፡-

 ተ.ቁ  የተወሰደው የዲስፕሊን እርምጃ  የሚሰጥ


ነጥብ
 1  ምንም የቅጣት ሪኮርድ የሌለበት  10
 2  የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው  8
 3  ከ 1 – 5 ቀናት የደመወዝ ቅጣት የተፃፈበት  6
 4  ከ 6 – 15 ቀናት የደመወዝ ቅጣት የተፃፈበት  4
 5  ከ 15 ቀናት በላይ የደመወዝ ቅጣት  2
የተፃፈበት
 6  ከላይ ከተራ ቁጥር 5 ከተጠቀሰው ቅጣት  0
በላይ ያሉ ቅጣቶች

አንቀጽ 26 የስራ አፈፃፀም ምዘና


1. የስራ አፈፃፀም ምዘና ሪፖርት በአመት 2 ጊዜ ማለትም በሀምሌ መጀመሪያ እና በታህሳስ ወር
መጨረሻ ይሞላል፤
2. የሰራተኛው የስራ አፈፃፀም ምዘና ፍትሃዊነት፣ ግልፅነትንና የተጠያቂነት ባህልን በሚያዳብር አግባብ
እና አድርጐ መሞላት አለበት፤
3. የስራ አፈፃፀም ምዘና ሪፖርት የተሞላለት ሰራተኛ በስራ መመዘኛ ሪፖርቱ ቅፅ ላይ የሰራተኛው
አስተያየት በሚለው አስተያየቱን ሰጥቶ እንዲፈርም ያደርጋል፤
4. የስራ አፈፃፀም ምዘና ሪፖርት በአንድ ኦሪጅናል ብቻ ተሞልቶ ከሰራተኛው የግል ማህደር ይያያዛል፤
5. በስራ ምዘና ሪፖርት ላይ በተሞላው ጉዳይ ሪፖርቱን የሞላው ኃላፊ እና ሪፖርቱ የተሞላበት ሰራተኛ
መካከል አለመግባባት ቢፈጠር ቅሬታ አቅራቢው በግንባር ቀርቦ ቅሬታውን ይገልጻል። በሚቀጥለው
የበላይ ኃላፊ የሚሰጠው ውጤት የመጨረሻ ውሳኔ ይሆናል።
6. የስራ አፈፃፀም ምዘና ከ 3፡00 (የአፈፃፀም መለክያ ክ 5 ከሆነ) በታች የሚያመጣ ሰራተኛ በአሠሪና
ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/11 መሰረት እና በድርጅቱ አስተዳደር መመሪያ መሰረት ክህሎቱን
የሚያሻሽል ስልጠና ይሰጠዋል።
7. ሰራተኛው በተሰጠው ግምገማ መሰረት የስራ አፈፃፀምን ማሻሻል አለበት ፣ ሰራተኛው በቀጣዩ የስራ
አፈጻጸም ግምገማ ሥልጠናና ድጋፍ ተሰጥቶት ውጤቱ ከ 3፡00 ነጥብ በታች ከሆነ በአዋጁ አንቀጽ 34
መሰረት ውሉ ይቋረጣል።

22
ክፍል ሶስት ደመወዝና ጥቅማጥቅም

የደመወዝ አወሳሰንና ይዘት


አንቀጽ 27 ጠቅላላ
1. በአዋጁ አንቀጽ 53 ንዑስ አንቀጽ 1 እና 2 እንዲሁም አንቀጽ 54 ንዑስ አንቀጽ 1 እና 2
የተዘረዘረው እንደተጠበቀ ሆኖ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ደመወዝ የሚከፈለው በሥራ
ውሉ መሰረት ሰራተኛው ለሚያከናውነው መደበኛ ስራ እና ለተሰራ ስራ ብቻ ይሆናል።
2. በአዋጁ አንቀጽ 53 መሰረት በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ የሚፈፀሙ የሚከተሉት ክፍያዎች
እንደ ደመወዝ አይቆጠሩም።
 የትርፍ ሰዓት ስራ፣
 የውሎ አበል፣ የቤት አበል፣ የበረሃ አበልና የመጓጓዣ አበል፣ የዝውውር ወጪና
ሠራተኛው በሚጓጓዝበት ወይም የመኖርያ ቦታውን በሚለውጥበት ወቅት
የሚከፈል ተመሳሳይ አበል፣
 ከአሰሪ የሚሰጥ ጉርሻ /ቦነስ/፣
 ኮሚሽን፣
 ተጨማሪ የሥራ ውጤት የሚከፈሉ ሌሎች ማትጊያ ክፍያዎች ፣
 ከደንበኞች የሚሰበሰብ የአገልግሎት ክፍያ።
3. የእረፍት ቀናትና የህዝብ በዓል ደመወዝ የሚከፈልባቸው ስለሆኑ የሰራተኛ ደመወዝ
የሚሰራው በ 30 ቀናት ይሆናል፣ ለደመወዝ ስሌትም ሲባል አንድ ወር በ 30 ቀናት ብቻ
ይሰላል።
4. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ አመች በሆኑ የሥራ መደቦች የሰራተኛውን የወር ደመወዝ እና
ተጨማሪ የስራ ውጤት ክፍያ በስራ አፈፃፀም ላይ እንዲመሰረት የማድረግ መብት
ይኖረዋል።

አንቀጽ 28 የአከፋፈል ዘዴ እና የክፍያ አፈፃፀም


1. በአዋጁ አንቀጽ 55 መሰረት ደመወዝ በጥሬ ገንዘብ ወይም ሰራተኛውና
ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ በሚስማሙበት ዘዴ ይፈፀማል።
2. በአዋጁ አንቀጽ 57 መሰረት በህግ ወይም በሰራተኛው በራሱ ፈቃድ ህጋዊ
በሆነ አግባብ የወከለው ሰው ከሌለ ደመወዝ የሚከፈለው በቀጥታ
ለሰራተኛው ይሆናል።
3. በተለያየ ምክንያት በሰራተኛው ላይ የህግ አካላት ከሰራተኛው ደመወዝ ላይ
ተቆርጦ ለ 3 ኛ ወገን እንዲከፈል ኢንተርፕራይዙ የህግ ውሳኔ ሲደርሰው በህግ
ውሳኔው መሠረት ከሰራተኛው የተጣራ ደመወዝ ላይ ቆርጦ የህግ ውሳኔ
ለተወሰነለት ህጋዊ አካል የመክፈል ግዴታ አለበት።
4. በአዋጅ አንቀጽ 59 መሰረት ሰራተኛው የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ እዳ ካለበት
እና በየወሩ ከደመወዙ እየተቆረጠ በኢንተርፕራይዙ ገቢ እንዲያደርግ
የመስማማት ግዴታ አለበት።
5. በአንድ ጊዜ ከአንድ ሰራተኛ ደመወዝ ላይ በአጠቃላይ ሊቆረጥ የሚችለው
የገንዘብ መጠን በምንም እኳኋን ከወር ደመወዙ አንድ ሦስተኛ መብለጥ
የለበትም።

23
አንቀጽ 29 የደመወዝ ጭማሪ
1. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የገቢ ተቋሙ ከሚያገኘው የተጣራ ትርፍ
የመንግስት ገቢ ግብር፣ የንግድ ፈቃድ ግብር ተከፍሎ ለዩኒቨርሲቲው ፈሰስ በቦርዱ
በሚወሰነው መሰረት ሆኖ ቀሪውን ለኢንተርፕራይዙ ማስፋፊያ እና ለሰራተኛ ማበረታቻ
ክፍያና ደመወዝ ጭማሪ ያደርጋል።
2. በዓመቱ ደመወዝ ጭማሪ የተዘጋጀውን ገንዘብ ለሰራተኞች ለማደላደል ገቢ ማመንጫ
ተቋማቱ በጋራ በሚስማሙበት መሰረት ይፈፀማል።
3. ኢንተርፕራይዙ የደመወዝ ጭማሪ ሲያደርግ ሰራተኛው ጭማሪ የሚያገኘው ፡-

ሀ/ በዲስፕሊን ቅጣት ምክንያት የደመወዝ ጭማሪ እገዳ ያልተደረገበትና ከሶስት ወር በላይ


የእስራት ፍርድ ያልተፈደረበት ሲሆን፣

ለ/ የደመወዝ ጭማሪ የኢንተርፕራይዙ ቦርድ ትርፋማነቱን ሲያረጋግጥ በራሱ መስፈርት


የሰራተኞችን ጥቅማ ጥቅም በመወሰን በፕሬዚዳንቱ አፀድቆ ስራ ላይ ያውላል፣

ሐ/ የደመወዝ ጭማሪ በየ 5 ዓመቱ ሲሆን ጥቅማ ጥቅም ግን በየ ዓመቱ የሚከናወን ይሆናል።

መ/ የቦነስ ክፍያ በሚፈፀምበት ጊዜ የስራ ውላቸው ተቋርጦ ለተሰናበቱ ሰራተኞች የቦነስ


ክፍያው ተፋፃሚ አይፈፅምም። ይሁን እንጅ በሞት ምክንያት የስራ ውላቸው ለተቋረጠ
ለህጋዊ ወራሾቻቸው የቦነስ ክፍያው ይፈፀማል።

4. በተለያዩ ምክኒያቶች የደመወዝ ጭማሪ መስፈርቶችን ባለማሟላቱ የደመወዝ ጭማሪ


የታለፈው ሰራተኛ የታለፈውን የደመወዝ ጭማሪ በማንኛውም ጊዜ መጠየቅ አይችልም፣
5. መንግስት በማናቸውም ጊዜ የሚያደርገው ልዩ የደመወዝ ማሻሻያ ሲኖር ኢንተርፕራይዙ
ተጠይቆ ሲፈቀድ ሰራተኞች ደመወዝ ላይ የማስተካከያ ጭማሪ ሊደረግ ይችላል፣
6. ከላይ በተገለፀው አግባብ ለሰራተኛ ደመወዝ በሚጨመርበት ጊዜ ሰራተኛው ጣራ ደርሷል
ሳይባል ቀጥሎ ያለውን እርከን ይሰጠዋል። ጣሪያ የሚያገለግለው በደረጃ እድገት ጊዜ
ይሆናል።

አንቀጽ 30 የውሎ አበል


1. የውሎ አበል የሚከፈለው ሰራተኛው ከተመደበበት አካባቢ ወይም ከተማ ለቢዝነስ
ኢንተርፕራይዙ ስራ ወደ ሌላ ቦታ ወይም ከተማ ሲንቀሳቀስ ነው፤
2. ጉዞ ከመደረጉ በፊት ከተዘጋጀ ቅፅ የጉዞ አስፈላጊነት፣ በጉዞው መነሻና የውሎ አበል
የሚከፈልበት ቀን ተጠቅሶ ይሞላል። በሚመለከተው ኃላፊ ይፀድቃል።

24
3. ጉዞው እንደተከናወነ ተልኮውን የፈፀመ ሰራተኛ የጉዞ ሂሳቡን ከማወራረዱ በፊት ስለ ተልዕኮው
የስራ ክንውን ሪፖርት ተልዕኮውን ለሰጠው ኃላፊ ማቅረብ አለበት።
4. ማንኛውም ሰራተኛ አስቀድሞ የተሰጠውን አበል ከማወራረዱ በፊት ሌላ ተልዕኮ እና አበል
አይሰጠውም።
5. የውሎ አበል ክፍያ ከአንድ ወር በላይ አይፈቀድም ሆኖም አስገዳጅ ሁኔታ ሲፈጠር እና የውሎ
አበል ክፍያ የሚፈፀምበት ጉዞ በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ዋና ስራ አስኪያጅ ወይም እሱ
በወከለው አካል ሲፀድቅ ለአንድ ተጨማሪ ወር ብቻ ሊራዘም ይችላል።
6. ለጉዞ ከተፈቀዱት የጉዞ ቀናት በላይ የአበል መጠን ከፍ አድርጐ መስጠት አይፈቀድም።
7. አንድ ሰራተኛ የውሎ አበል የሚከፈለው በቋሚነት ከተመደበበት ከተማ 25 ኪሎ ሜትር እርቀት
ሲንቀሳቀስ ብቻ ነው።
8. የውሎ አበል አከፋፈል በመንግስት የአበል አከፋፈል መጠን መሰረት ተፈፃሚ ይደረጋል።

አንቀጽ 31 የህክምና አገልግሎት


1. የህክምና አገልግሎት ሠራተኛው ከመቀጠሩ በፊት ስለ ጤንነቱ በቂ በህክምና ማረጋገጫ
እንዲያቀርብ መደረግ አለበት።
2. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ከሥራ ጋር በተያያዙ እና ባልተያያዘ ምክንያት ሠራተኛው
ለሚያጋጥመው ህመም የህክምና ወጪ በዓመት እስከ 2500 ብር (ሁለት ሺህ አምስት መቶ
ብር) ይሸፈናል። ነገር ግን ራስን ለመከላከል ካልሆነ በስተቀር ከሌሎች ሰዎች ጋር በሚደረግ
ድብድብ የሚፈጠር አደጋን የጦር መሳሪያዎችን በባለቤትነት በመያዙ ምክንያት በራስ ላይ
የደረሰ አደጋን እና ኢንተርፕራይዙ ለህክምና ውል የገባበት የህክምና ተቋም ሆኖ በአግባቡ
ፈቃድ የተሰጠው የህክምና ዶክተር ትዕዛዝ ሳይሰጥበት የተፈፀመ ውርጃን የሕክምና ወጪ
አይሸፍንም።
3. በህክምና ልድን አልቻልኩም በፀበል እና በወጌሻ እታከማለሁ ለሚል ሠራተኛ በቢዝነስ
ኢንተርፕራይዙ የዓመት ፈቃዱን እንዲወስድ ይፈቅድለታል። የዓመት ፈቃድ ከሌለው ከ 15
ቀን ያልበለጠ ያለክፍያ ፈቃድ ይሰጠዋል። ሆኖም ሰራተኛው የዓመት ፈቃዱን ጨርሶ
በአምስት ቀን ውስጥ ካልተመለሰ ኢንተርፕራይዙ ሠራተኛውን ከሥራ ያሠናብተዋል።

አንቀጽ 32 የመጓጓዣ ሰርቪስ አገልግሎት


1. ለቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ የስራ ቅልጥፍናና ምርታማነት ያመች ዘንድ ቢዝነስ
ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ ወደ ስራ ሲገባና ሲወጣ የትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣል ።
የሚሰጠው የሰርቪስ መኪና አገልግሎት በድርጅቱ አቅም ላይ ይመሰረታል።
2. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ለሰርቪስ የሚመድባቸው የትራንስፖርት መኪኖች ሰራተኛው
በሚኖርበት አካባቢ በዋናዋና መንገዶች የማቆሚያ ፌርማታ እና የሚደርሱበት ሰዓት
ይኖራቸዋል። ሰራተኛውም የትራንስፖርት መኪኖች ከሚደርሱበት ሰዓት 10 ደቂቃ
ቀድሞ መገኘት አለበት።
3. ማንኛውም የሰርቪስ መኪና አገልግሎት ከሰጠ በኋላ ተመልሶ በድርጅቱ ቅጥር ግቢ
መገኘትና ማደር አለበት።
4. ለሰራተኛ የተመደቡ የሰርቪስ መኪኖች ከሰራተኛ ውጭ ሌላ ሰው መጫን የለባቸውም።

አንቀጽ 33 የጡረታ መዋጮ

25
በግል ድርጅቶች ሠራተኛ ጡሮታ አዋጅ ቁጥር 715/2003 መሠረት ላልተወሰነ ጊዜ የተቀጠሩ የቢዝነስ
ኢንተርፕራይዙ ሠራተኞች ከደመወዛቸው እና ከድርጅቱ እየተቆረጠ የጡረታ ዋስትና ይቀመጥላቸዋል።

አንቀጽ 34 የኢንሹራንስ ሽፋን

ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ለቋሚ ሠራተኞች በሥራ ሰዓት የ 24 ሰዓት የአደጋ ዋስትና ይገባል።

አንቀፅ 35 ለስራ የሚያስፈልጉ የአደጋ መከላከያ የስራ እና ደንብ ልብስ


1. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ አደጋ በሚያሰከትሉ የሥራ መደባች ላይ ለተመደበ ሰራተኛ ተገቢውን
የአደጋ መከላከያ መሣሪያ ይሰጣል።
2. የአደጋ መከላከያ መሣሪያዎች እና መከላከያዎች የእድሜ ዘመን እና የሚቀየሩበት ጊዜ እንደየ
አደጋ መከላከያ መሣሪያው ስለሚለያይ የአገልግሎት ዘመናቸው በዚህ መመርያ መሰረት
ይሆናል።
3. አዲስ ተቀጣሪ ሠራተኛ እንደተቀጠረ ወዲያውኑ የሥራ ልብስና የአደጋ መከላከያ
ይሰጠዋል።ነገር ግን ለአዲስ ሠራተኛም ሆነ የሥራ መደቡን ለሚቀይር ነባር ሠራተኛ የ 6 ወር
አገልግሎት ዘመን ያላቸው የሥራ ልብስና የአደጋ መከላከያ በድጋሜ የሚሰጠው ከሁለት ወር
በታች በሆነ ጊዜ ከሆነ ሊታሰብ የሚችለው ለተቃረበው መደበኛ የልብስና የአደጋ መከላከያ
መስጫ ጊዜ ነው።ከስድስት ወር በላይ አገልግሎት ላላቸው የሥራ ልብስና የአደጋ መከላከያ
በድጋሜ የሚሰጠው የአገልግሎት ዘመናቸውን በማገናዘብ የሚታሰብ ይሆናል።
4. ማንኛውም በስራ መደቡ ምከንያት የስራ ልብስ የተሰጠው ሰራተኛ በስራ ሰዓት የተሰጠውን
የሥራ ልብስ በሚፈለገው ደረጃ ንፅህናውን ጠብቆ መልበስ አለበት።
5. ማንኛውም የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሠራተኛ የተሰጠውን የደንብ ወይም የሥራ ልብስ መሸጥ
ወይም ለሦስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት የለበትም።
6. በሥራና በደንብ ልብስ ዝርዝር የአሰጣጥ ሠንጠረዥ መሠረት በዓመት ሁለት ጊዜ የሚሰጥ ከሆነ
አሰጣጡ በሀምሌ እና በጥር ወር ይሆናል።
7. ለሠራተኛው የሚሰጠውን የደንብ/የሥራ ልብስ፣ ጫማ እና ሌሎች የአደጋ መከላከያዎች 2 ከሆነ
በየ 6 ወሩ አንድ አንድ ይሰጠዋል።
8. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ከዚህ በታች በተመለከቱት የሥራ መደቦች የሥራ አደጋ መከላከያ፣
የሥራና የደንብ ልብስ ያቀርባል፡

26
ተ.ቁ የስራ መደብ መጠሪያ ምርመራ
የደንብ ልብስ/ የስራ ልብስ ዓይነት
1. የጥበቃ ሰራተኛ በአመት 1 ቴትሮን ኮትና ሱሪ፣1 የተዘጋጀ ሸሚዝ፣ 1 ቆዳ ጫማ፣ 1 ኮፍያ
እንዲሁም በ 2 አመት 1 የዝናብ ልብስ እና በ 3 አመት 1 ካፖርት።
2. ጽዳትና ተላላኪ በአመት 2 ቴትሮን ጋወን፣ 2 ቆዳ ጫማ፣2 ባለ ሸምቆቆ ኮፍያ እንዲሁም
በአመት 1 ጃንጥላ እና ፕላስቲክ ጓንት እንዳለቀ።
3. የትራንስፖርት አገልግሎት አስተባባሪ፣ የህትመት ስራዋች አስተባባሪ፣ በ 1 አመት 1 ቴትሮን ጋዎን።
ለረዳት ንብረት ሰራተኛ፣ ለዋና ገንዘብ ያዥ እና ለረዳት ገንዘብ
ያዥ
4. የእነዳስትሪ ወርክሾፕ አስተባባሪ፣ የኮነስትራክሽን ና ህንጻ ግንባታ በአመት 1 የደህንነት ጫማ 2 ቴትሮን እስከ ደረቱ ኪስ ያለው ቱታ
ዲዛይን መምርያ ስ/አስከያጅ ዲዛይን ክፍል ሃላፊ ፣ ኮንስትራክሽን
ሱፐርቫዘር ክፍል ሃላፊ
5. በያጅ፣ ረዳት በያጅ፣ የእንጨት ስራዋች ባለሞያ ፣ ረዳት የእንጨት በአመት 2 የደህንነት ጫማ፣ 2 ቴትሮን እስከ ደረቱ ኪስ ያለው ቱታ ፣የአይን
ስራዋች ባለሞያ ፣ አውቶመካኒክ ፣ ረዳት አውቶመከኒክ መከላከያ መነፅር (እንዳለቀ) ፣የእጅ ጓንት(እንዳለቀ)
6. የእንስሳት ሃብትና የእርሻ ልማት አስተባባሪ በአመት 1 የፕላስቲክ ጫማ፣ 1 ቴትሮን እስከ ደረቱ ኪስ ያለው ሱሪና
ሸሚዝ
7. የዳልጋ ከብት ተንከባካቢ ሰራተኛ ፣ የበግና ፍየል ተንከባካቢ ሰራተኛ ፣ በአመት 2 የላስቲክ ጫማ፣ 2 ቴትሮን እስከ ደረቱ ኪስ ያለው ሱሪና ሸሚዝ
የደሮ አርቢና መጋቢ ሰራተኛ ፣ እና በ 2 አመት 1 የብርድ መከላከያ ካፖርት፣ የእጅ ፕላስቲክ
ጋንተ(እንዳለቀ)።
8. የእንስሳት ጤና ባለሞያ ፣ የእርሻ ልማት ባለሞያ ፣ የግምት ባለሞያ ፣
የጥረዛ ባለሞያ ፣ የህትመት በለሞያ በአመት 1 ቴትሮን ጋዎን።
9. የደረቅ ጭነት ሽፌር፣ የህዝብ ማመላለሻ ሹፌር ፣ የትነሽ መኪና ሽፌር
፣ ረዳት ሽፌር 2 ካኪ ቱታ በዓመት
10. ስትራክቹራል ኢንጂነር፣ ሳኒተሪ እነጂነር፣ ኤለክትሪካል ኢንጂነር፣
አርክቴክት ኢንጂነር፣ ረዚደንት ኢንጂነር፣ ሳይት ኢንጂነር፣ በአመት 2 የደህንነት ጫማ፣ 1 ቴትሮን ጋወን
መካኒካል ዲዛይን እንጅነር፣ ፣ ሰርቨየር

ሰንጠረዥ 1፡ የደንብ ልብስ ዓይነት ማጠቃለያ

27
9. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ በሥራው ባህሪ ምክንያት የሥራ ልብስ ለሚሰጣቸው ሠራተኞች በወር
አንድ ባለ 250 ግራም የልብስ ሳሙና ይሰጣል። ለጋራዥ ለወርክ ሾኘ ለማምረቻ መሳሪያዎች
መካኒኮች ለሥራው ኦሞ ያቀርባል። ለእያንዳንዱ ሠራተኛ አንድ ጥቅል የመፀዳጃ ወረቀት እና
ባለ 145 ግራም አንድ የገላ ሳሙና በወር አንድ ጊዜ ይሠጣል።

ክፍል አራት የስራ ሰዓት


አንቀፅ 36 የስራ ሰዓት
1. የቀን ወይም የሳምንት የስራ ሰዓት ጣሪያ በአዋጁ አንቀፅ 61 በንዑስ አንቀፅ 1 እና 2 የተቀመጠው
የስራ ሰዓት በቀን 8 ሰዓት ወይም በሳምንት ከ 48 ሰዓት የማይበልጥ ሆኖ በዚህ መሰረት የቢዝነስ
ኢንተርፕራይዙ የስራ ሰዓት በቀን 8 ሰዓት የማይበልጥ ሆኖ በዚህ መሰረት የቢዝነስ
ኢንተርፕራይዙ የስራ ቀናት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ይሆናል።
2. ለቢሮ/ለመደበኛ የስራ ሰዓት/ሰራተኞች
ሀ/ ከሰኞ እስከ አርብ
 ጠዋት ከ 2፡00 – 6፡00 ሰዓት
 ከሰዓት በኋላ ከ 7፡00 – 11፡00 ሰዓት
ለ/ ቅዳሜ
 ጠዋት 2፡00 -6፡00 ሰዓት
3. የቢሮ/የመደበኛ ስራ ሰዓት/ ሰራተኞች ከሽፍት ሰራተኞች ውጭ የሚሰሩትን ያጠቃልላል።
4. ለሽፍት ሰራተኞች
ሀ/ ጠዋት ከ 12፡30 -8፡30 ሰዓት
ለ/ ከሰዓት ከ 8፡30 - ምሽቱ 4፡30 ሰዓት
5. ለጥበቃ ሰራተኞችና ለጥበቃ ፈረቃዎች
ሀ/ ከጥዋት 1፡00 - ማታ 1፡00 ሰዓት
ለ/ ከማታ 1፡00 -ጠዋት 1፡00 ሰዓት
አንድ ቀን/24 ስዓት/ ጠብቆ ሁለት የእረፍት ቀን ይሰጠዋል በሳምንት የሰራው ከ 48 ሰዓት ከበለጠ
ለሰራው የትርፍ ስዓት ክፍያ ይፈፀምለታል።

አንቀጽ 37 የሻይ እረፍት


በፈረቃ ለማይሰሩ የሻይ ዕረፍት ጠዋት ከ 4፡00 -4፡15 እንዲሁም ከሰዓት ከ 9፡00 – 9፡15 የ 15 ደቂቃ የሻይ
እረፍት ይሰጣል ።

አንቀጽ 38 የሳምንት የእረፍት ጊዜ


1. በአዋጁ አንቀፅ 69 ንዑስ አንቀፅ 1-3፣ አንቀፅ 7 ዐ ንዑስ አንቀፅ 1 እና 2 መሰረት
ማንኛውም ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ ከሰባት ቀናት ጊዜ ውስጥ ያልተቆራረጠ
ከ 24 ሰዓት የማያንስ የሳምንት እረፍት ያገኛል።
2. በአዋጁ አንቀፅ 69 ንዑስ አንቀፅ 2 መሰረት የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ የሳምንቱ
እረፍት በተቻለ መጠን እሁድ ቀን እንዲውል ማድረግ ካልተቻለ በምትኩ ሌላ ቀን
የሳምንት እረፍት ቀን ሊሰጥ ይችላል።

28
3. ስለ ትርፍ ሰዓት ክፍያ አንድ ሰራተኛ በሳምንት የእረፍት ቀኑ ከሰራ በአዋጁ አንቀፅ 68 ንዑስ
አንቀፅ 1 ባለው መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል።
4. ማንኛውም የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ በመደበኛ የስራ ቀናት ትርፍ ሰዓት እንዲሰራ
ከተገደደ ለሰራባቸው ትርፍ ሰዓት የትርፍ ሰዓት ክፍያ ይፈፀምለታል።

አንቀጽ 39 የህዝብ በዓላት


1. በአዋጁ አንቀፅ 73 እና አግባብ ባለው ህግ መሰረት የሚከበሩ የህዝብ በዓላት ተብለው
የታወጁ እና በተጨማሪ በልዩ ልዩ ምክንያቶች በዓል ሆነው እንዲከበሩ የሚወሰኑ ቀናት
ደመወዝ የሚከፈልባቸው ይሆናሉ።
2. በአዋጁ አንቀፅ 73 መሰረት የወር ደመወዝ የሚከፈላቸው የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ
ሰራተኞች የወር ደመወዛቸው የሚታሰበው ባአላትን እና የሳምንት የእረፍት ቀናትን
ጨምሮ ስለሆነ በህዝብ በአላት ባለመስራታቸው ምክንያት ደመወዛቸው አይቆረጥም።

አንቀጽ 40 የትርፍ ሰዓት ስራ ክፍያና የትርፍ ስራ ሰዓት ሁኔታዎች


1. በአዋጅ አንቀፅ 67 ንዑስ አንቀፅ 1 መሰረት ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ለስራ ካቀደው ስራ
አንፃር የተሻለ አማራጭ መንገድ ሳይኖረው ቀርቶ ስራው በትርፍ ስራ እንዲሰራ የቢዝነስ
ኢንተርፕራይዙ ማነጅንግ ዳይሬክተር ወይም በፅሁፍ የወከለው ኃላፊ የትርፍ ሰዓቱ ቀርቦ
መፈቀድ አለበት። የቅርብ ኃላፊው ካዘዘ ሰራተኛው የታዘዘውን የትርፍ ሰዓት ስራ
የመስራት ግዴታ አለበት።
2. በወቅቱ መሰራት ያለበት ስራ ሆኖ ሰራተኛው በቅርብ ኃላፊው ከታዘዘ የትርፍ ሰዓቱ
በሚቀጥለው የስራ ቀን እንዲፈቀድ ይደረጋል።
3. ነፍሰ ጡር ሴቶች የትርፍ ሰዓት እንዲሰሩ አይገደዱም።
4. የስራ መሪዎች የትርፍ ሰዓት ስራ ቢሰሩ የትርፍ ሰዓት ክፍያ አይከፈላቸውም ከዓመት
እረፍታቸው ግን ሊታሰብላቸው ይችላል።

አንቀጽ 41 የትርፍ ስራ ሰዓት አከፋፈል


1. የትርፍ ሰዓት ስራ ክፍያ በመስክ ስራ ላይ በአበል የተሰማሩ ሰራተኞችን አይመለከትም።
2. የትርፍ ሰዓት ስራ አከፋፈል የሰራተኛው ያልተጣራ የወር ደመወዝ ለ 208 ሰዓታት ተከፍሎ
በሚገኘው ውጤት ላይ የተመሰረተ ይሆናል።

ክፍል አምስት ፈቃድ


አንቀጽ 42 ጠቅላላ
1. የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ ማግኘት የሚገባው ፈቃድ በቅድሚያ ተሰልቶ የቢዝነስ
ኢንተርፕራይዙ የስራ እንቅስቃሴ እና የሰራተኛውን ጥቅም በማይጐዳ አግባብ ተስማሚ ጊዜ
በመምረጥ እና የአመት እረፍት ኘሮግራም በማውጣት የአመት እረፍቱን እንዲወስድ ያደርጋል
ይህም በአዋጁ አንቀጽ 78 ንዑስ አንቀጽ 3 መሰረት የሚፈፀም ይሆናል።
2. የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኞች የአመት ፈቃዳቸውን የአመት ፈቃዱን ባገኙበት ቀጣይ
አመት መውሰድ አለባቸው
3. የአንድ ሰራተኛ የአመት ፈቃድ ከአንድ ዓመት በላይ ሊጠራቀም የሚችለው የሚመለከተው
በቅርብ ኃላፊው በህጋዊ መንገድ አውቆት ሰራተኛው በስራው ላይ ባይገኝ ችግር የሚፈጠር

29
መሆኑ ሲረጋገጥ እና የአመት እረፍት ፈቃዱ ወደ ሚቀጥለው የበጀት አመት እንዲተላለፍ
የሰው ኃይል አስተዳደር መምሪያ ስራ አስኪያጅ በደብዳቤ ሲያጸድቀው ይሆናል።
4. አንድ የቢዝነስኢንተርፕራይዙሰራተኛ በአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/11 አንቀፅ 77
መሰረት ላገለገለበት የመጀመሪያ አንድ ዓመት 16 የስራ ቀናት የአመት ፈቃድ ይሰጠዋል።
ከአንድ አመት በላይ የተበረከተ አገልግሎት ለእያንዳንዱ ሁለት የአገልግሎት አመታት አንድ
የስራ ቀን እየተጨመረ ይሰጣል።
5. አንድ ሰራተኛ የአመት ፈቃዱን በሚወስድበት ጊዜ በስራ ላይ ቢሆን ኖሮ ሊከፈለው ከሚገባው
ጋር እኩል የሆነ በእረፍት ላይ ለሚቆይበት ጊዜ ደመወዝ በቅድሚያ መውሰድ ይችላል።
6. በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ጠያቂነት ሰራተኛው የአመት እረፍት እንዲወጣ ከተደረገ እረፍቱን
የሚወስድበት ጊዜ ከ 15 ቀናት በፊት ይነገረዋል። ሆኖም ይህ አባባል ውሉ የሚቋረጥበትን
ሰራተኛ አይመለከትም።
7. የአመት እረፍት ፈቃድን በገንዘብ ለውጦ ክፍያ ማድረግ አይፈቀድም። ሆኖም የአመት እረፍት
ተጠናቆ ከመውሰዱ በፊት የስራ ውሉ የተቋረጠ ሰራተኛ ፈቃድ ወደ ገንዘብ ተለውጦ
ይሰጠዋል።

30
አንቀጽ 43 ልዩ ፈቃድ
1. ለቤተሰብ ጉዳይ የሚሰጥ ፈቃድ ሆኖ ሰራተኛው
ሀ/ ለአንድ ጊዜ ህጋዊ ጋብቻ ሲፈፅም ወይም
ለ/ የትዳር ጓደኛው፣ ወላጅ፣ ተወላጅ ወይም እስከ ሁለተኛ ዘር ግንድ ድረስ የሚቆጠር
የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመድ ሲሞትበት ከክፍያ ጋር ለሦስት የስራ ቀናት ፈቃድ
ይሰጠዋል።
2. አንድ የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ቋሚ ሰራተኛ ከዚህ አለም በሞት ሲለይ የሰው ኃይል አስተዳደር
መምሪያ በሚሰጠው መመሪያ መሰረት ቢዝነስ ኢንተርፕራየዙን ወክለው የሚሄዱ ሰራተኞች
በቀብር ስርዓት ላይ እንዲገኙ ይደረጋል።

አንቀጽ 44 ልዩ ልዩ ተግባሮችን ለማከናወን ለሰራተኞች የሚሰጥ ፈቃድ


1. በአዋጁ አንቀጽ 83/1 መሰረት አንድ ሰራተኛ የስራ ክርክር ለማሰማት ወይም አሰሪና ሰራተኛ ጉዳዮችን
ለማስፈፀም ህጋዊ ስልጣን ያላቸው አካሎች ዘንድ ለማስፈፀም ለጠፋው ጊዜ ብቻ ከክፍያ ጋር ፈቃድ ይሰጠዋል።

2. በአዋጅ አንቀፅ 83/2 መሰረት አንድ ሰራተኛ የሲቪል መብቱን ሊያስጠብቅ ወይም የሲቪል
ግዴታውን ሲፈፅም ለዚሁ አላማ ላጠፋው ጊዜ ብቻ ከክፈያ ጋር ፈቃድ ይሰጠዋል።

3. አንድ የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ በፍርድ ቤት ወይም ፖሊስ ለተለያዩ ጥያቄዎች ሲፈለግ
እና ጥያቄውም በፖሊስ ወይም በፍርድ ቤት ሲረጋገጥ በፍርድ ቤት ወይም በፖሊስ የተፈለገበትን
ጉዳይ በመደበኛ የስራ ሰአት ከሆነ ለጥያቄው ለተፈገበት ወቅት ደመወዝ የሚከፈልበት ፈቃድ
ይሰጠዋል።

4. ሰራተኛው ለፍርድ ቤት ወይም በፖሊስ የተፈለገው በራሱ ጥፋት መሆኑን ቢዝነስ


ኢንተርፕራይዙ ካረጋገጠ የሚሰጠው ፈቀድ ከአመት እረፍት ፈቃድ ላይ ይቀነሳል።

አንቀጽ 45 ለግል ጉዳይ የሚሰጥ ፈቃድ


1. ማንኛውም የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ በድንገት ለሚገጥመው ችግር የአመት ፈቃድ
ከሌለው በአመት ከ 15 ቀን ያልበለጠ ደመወዝ የማይከፈልበት ፈቃድ ይሰጠዋል።
2. ስራተኛው የዚህ አይነት ፈቃድ እንዲሰጠው በቂ ምክንያት ሲኖረው የቅርብ ኃለፊው የቢዝነስ
ኢንተርፕራይዙ የስራ ሁኔታ ከግምት አስገብቶ በአንድ ጊዜ እስከ ግማሽ ቀን ከአመት ፈቃድ
የሚቀነስ ወይም ያለ ክፍያ ፈቃድ ሊሰጠው ይችላል።

አንቀጽ 46 የህመም ፈቃድ


1. ማንኛውም የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ በህመም ወይም በሌላ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት
ሥራ መግባት የማያስችል ሁኔታ ሲያጋጥመው ቢያንስ ሥራ ከመገባቱ በፊት ከሁለት ስዓት አስቀድሞ
በሚያመቸው የመገናኛ ዘዴ ለቅርብ ኃላፊው ወይም ለሰው ኃይል አስተዳደር መምሪያ ማሳወቅ
አለበት።
2. ለቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ለተወሰነ ጊዜ ወይም ለተወሰነ ስራ የተቀጠረ ሰራተኛ በህመም ፈቃድ ላይ
እያለ የስራ ጊዜው በመድረሱ ወይም ስራው በማለቁ አላስፈላጊ ከሆነ ውሉ በስምምነቱ መሰረት
ይቋረጣል።

31
3. ማንኛውም ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ የህመም ፈቃድ የሚያገኘው በመንግስት ከታወቀ
የህክምና ድርጅት ወይም ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ውል ከወሰደበት የህክምና ተቋም የህክምና ምስክር
ወረቀት እና ፈቃድ ሲያገኝ ብቻ ይሆናል።
4. የህመም ፈቃድ ከማለቁ በፊት የስራ ውሉ ዘመን ካለቀ የህመም ፈቃድ አብሮ ይቋረጣል።

አንቀጽ 47 የህመም ፈቃድ ክፍያ


የህመም ፈቃድ ክፍያ በአዋጅ አንቀፅ 86 መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል።

አንቀጽ 48 የወሊድ ፈቃድ


1. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ነፍሰጡር የሆነች ሰራተኛ ከእርግዝናዋ ጋር የተያያዘ ምርመራ ለማድረግ
ከደመወዝ ጋር ፈቃድ ይሰጣታል። ሆኖም ሰራተኛዋ ከምርመራው በኋላ ለምርመራ ከደመወዝ ጋር
ለተሰጣት ፈቃድ የሃኪም ማስረጃ ማቅረብ አለባት።
2. ነፍሰጡር የሆነች ሰራተኛ ከመውለዷ በፊት ሃኪም እንድታርፍ ካዘዘላት ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ
ከደመወዝ ጋር እረፍት ይሰጣታል።
3. ነፍሰጡር የሆነች ሰራተኛ እወልዳለሁ ብላ ከገመተችበት ቀን በፊት መውለጃዋ እስኪደርስ የ 3 ዐ
ተከታታይ ቀን የቅድመ ወሊድ ፈቃድ እንዲሁም ከወለደች በኋላ ከወደለችበት ቀን ጀምሮ 90
ተከታታይ ቀናት የወሊድ ፈቃድ ከክፍያ ጋር ይሰጣታል።
4. ሰራተኛዋ ከመውለዷ በፊት የወሰደችው የ 3 ዐ ቀን ፈቃድ ሲያልቅ ካልወለደች እረፍት ልታገኝ
ትችላለች የምታገኘውም እረፍት እንደ መደበኛ የህክምና ፈቃድ ይቆጠራል።

ክፍል ስድስት የመረጃ አያያዝና አጠቃቀም


አንቀፅ 49 መዝገብ ቤት
1. መዝገብ ቤት የሰራተኛ ፋይል እና ሌሎች የስራ እንቅስቃሴ ፋይሎች የሚቀመጡበት ቤት ማለት
ነው።
2. የመዝገብ ቤት አላማ ፡-
ሀ. የሚመጡ ደብዳቤዎችን መመዝገብ ፣ ፋይል ማድረግ ለሚመለከታቸው የስራ
ክፍሎች እና ሠራተኛ ማሰራጨት እና መቀበል ነው።
ለ. መረጃዎችን በሲስተምና በጥንቃቄ በሚፈለጉበት ጊዜ ተሎ እንዲገኙ አድርጎ
ማስቀመጥ ነው።
3. የሰራተኛ ፋይል፡- የሠራተኛው ፕሮፋይል በማኅደሩ የሚገኙ ጠቃሚ መረጃዎችን ማለትም፡-
 የስራ ውል
 የስራ ልምድ
 የት/ት ደረጃ
 የስራ አፈፃፀም
 ግልፅ የህይወት ታሪክ መረጃ ወ.ዘ.ተን ይይዛል።
4. የሰራተኛ ፋይል ፐርሶኔል ዋና ክፍል ይቀመጣል
5. ሌሎች የስራ እንቅስቃሴ ፋይሎች ማለትም ማንኛውም በፅሁፍ የሚደረግ እንቅስቃሴ በኢንተርፕራይዙ
መዝገብ ቤት መቀመጥ አለበት። መዝገብ ቤት መአከላዊ ወይም ማእከላዊ ባልሆነ መንገድ
እንደስራው ስፋት እየታየ የሚደራጀ ይሆናል።
6. ሌሎች የስራ እንቅስቃሴ ፋይሎች በፋይል ሽፋናቸው የሚከተሉት ሊኖሩ ይገባል።

32
 ስም እና የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ምልክት
 የፋይል ቁጥር
 የተከፈተበት ቀን
 በውስጡ የያዘው ፋይል ብዛት
7. ደብዳቤዎች ከቢሮ ውስጥ በውስጥ ማስታወሻ ደብዳቤ የቢሮ ውስጥ ማስታወሻ ተብሎ በራስጌው
ተፅፎ ሊፃፃፉ ይችላሉ።

ክፍል ሰባት የስነ ሥርዓት አከባበርና የሚወሰዱ የማስተካከያ እርምጃዎች


አንቀፅ 50 ጠቅላላ
1. የስነ-ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃ ዋነኛ አላማው ሰራተኛው በምክር፣ በተግሳፅ እና ለጥፋቱ
ተመጣጣኝ ቅጣት በመስጠቱ ከጥፋቱ እና ከድክመቱ ታርሞ ጠንካራ ዲሲኘሊንና የስራ ፍቅር
ያለው ሰራተኛ መፍጠር ነው።
2. አንድ ሰራተኛ ላይ የስነ- ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃ የሚወስደው ሰራተኛው በተደጋጋሚ
ጥፋቶች እንዲታረም እና በሰራተኛው እና በአሰሪው መካከል መልካም ግንኙነት ተፈጥሮ
በቢዝነስኢንተርፕራይዙ የኢንዱስትሪ ሰላም እንዲነግስ ለማድረግ ነው
3. የስነ-ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃ ጠንካራ ጐኖችን የበለጠ ለማጐልበት ደካማ ጐኖችን
አስወግዶ ጥንካሬዎችን ለማምጣት የሚፈፀም በመሆኑ እዚያው እንዳለ የሰው ኃይል ግንባታ
ማስፈፀሚያ አንድ አካል ሆኖ መታየት አለበት።

አንቀጽ 51 የስነ - ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃዎች አወሳሰድ

1. የስነ-ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ በሚመለከት ስንብትን የሚያስከትል ጥፋት ተፈፅሞ ሲገኝ


እና አስፈላጊነቱ በማነጅንግ ዳይረክተሩ ሲታመንበት።
2. በስነ-ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃ አወሳሰድ ሰንጠረዥ መሰረት በተፈፀሙ ጉድለቶች
የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ማኔጅመንት የድሲኘሊን ኮሚቴ ውሳኔ ሳይጠብቅ እርምጃ
መውሰድ ይችላል።
3. ሰራተኛው ከስራ ስንብት በፊት ባለው የመጨረሻ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እርምጃ ላይ ቅሬታ
ካለው ቅሬታውን ለማነጅንግ ዳይረክተሩ ያቀርባል።ማነጅንግ ዳይረክተሩ ቅሬታውን ጉዳዩ
እንዲታይ ወደ ዲሲኘሊን ኮሚቴ ሊመራለት ይችላል፡
4. የዲሲኘሊን ኮሚቴ ኢንተርፕራይዙ የስነ- ስርዓት ጉድለቶች፣ ማረሚያ እርምጃዎችን፣
ጥፋቶችንና ድክመቶችን አጣርቶ የውሳኔ ሃሳብ የሚያቀርብ የዲሲኘሊን ኮሚቴ ይኖረዋል።

አንቀጽ 52 የስነ-ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃዎች አወሳሰድ ኃላፊነት


1. የቃል ማስጠንቀቂያ እና የመጀመሪያ ደረጃ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ የሚሰጠው በቅርብ ኃላፊ ይሆናል።

2. እስከ 7 ቀን የሚደርስ የደመወዝ ቅጣት በመምሪያ ሥራ አስኪያጅ የሚሰጥ ቅጣት ይሆናል።


3. የመጨረሻ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እና የደመወዝ ቅጣት በሰው ኃይል አስተዳደር ይሰጣል።
4. ከኃላፊነት ማውረድ፣ ለተወሰነ ጊዜ የስራ እና ከደመወዝ ማገድ እንዲሁም ከስራ ማሰናበት
በማነጅንግ ዳይሬክተር ወይም እሱ በሚወክለው ይሆናል።

33
አንቀጽ 53 የስነ - ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃዎች የተፃፈ ደብዳቤ ስለመቀበል
1. ጥፋት የፈፀመ ማንኛውም ሰራተኛ የስነ-ስርዓት ጉድለት ማረሚያ ፎርም ወይም ደብዳቤ
አልቀበልም ማለት አይችልም። ሆኖም ቅሬታ ካለው ፎርሙን ወይም ደብዳቤውን ተቀብሎ
በቅሬታ አቀራረብ ስነ-ስርዓት መሰረት ቅሬታውን ማቅረብ ይችላል።
2. በቃል ማስጠንቀቂያ ፎርም ላይ አልፈርምም ማለት እና ደብዳቤ አልቀበልም ማለት እንደ የስነ-
ስርዓት ጉድለቶች ተቆጥሮ በስነ-ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃ ሰንጠረዥ መሰረት
ያስቀጣል።
3. የስነ ስርአት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃ ሰንጠረዥ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን የተከለከሉ ድርጊቶች
መፈጸም ወይም የታዘዘውንና እንዲፈጽም ግዴታው የሆኑትን አለመፈጸም ለዲሲፕሊን
ግድፈቶች በቂ ምክንያቶች እንደሆኑ በመቁጠር በአጥፊው ላይ የዲስፕሊን እርምጃ ይወሰዳል
የጥፋቶቹ አይነቶችና ደረጃ በደረጃ የሚወሰዱት የዲስፒሊን እርምጃዎች እንደሚከተለው
ተዘርዝረዋል

34
የጥፋት ዓይነት ለ 1 ኛ ጊዜ ለ 2 ኛ ጊዜ ለ 3 ኛ ጊዜ ለ 4 ኛ ጊዜ ለ 5 ኛ ጊዜ
ያለ በቂ ምክንያት ማርፈድ መዘግየት የጽሁፍ የመጨረሻ
ወይም ቀደም ብሎ መውጣት ወይም ማንቀጠንቀቂያና የ 5 የጽሁፍ
መቅረት የቃል ማስጠንቀቂያ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ቀን ደመወዝ ቅጣት ማስጠንቀቂያና ስንብት
ሀ/ እስከ ግማሽ ሰዓት መዘግየት ወይም የ 15 ቀናት
ቀደም ብሎ መውጣት ደመወዝ ቅጣት
የመጨረሻ የጽሁፍ
ለ/ግማሽ ቀን መቅረት ያልሰራበት የጽሁፍ ማንቀጠንቀቂያና የ 7
የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ማስጠንቀቂያ የ 15 ስንብት
ደመወዝ ተቆርጦ ቀን ደመወዝ ቅጣት
ቀናት ደመወዝ ቅጣት
ሐ/ አንድ ቀን መቅረት ያልሰራበት የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የ 7 የመጨረሻ የጽሁፍ
ደመወዝ ተቆርጦ ቀናት ደመወዝ ቅጣት ማስጠንቀቂያ የ 15 ስንብት
ቀናት ደመወዝ ቅጣት
መ/ ከአንድ ቀን በላይ መደዳውን እስከ 3 የመጨረሻ የጽሁፍ
የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
ቀን የቀረ ያልሰራበት ደመወዝ ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
የ 5 ቀናት ደመወዝ ቅጣት
ተቆርጦ ደመወዝ ቅጣት
የመጨረሻ የጽሁፍ
ሠ/ መደዳውን አራት ቀን የቀረ የቀረበት የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የ 10
ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ቀን ደመወዝ ተቆርጦ ቀናት ደመወዝ ቅጣት
ደመወዝ ቅጣት
ረ/ መደዳውነ አምስት ቀን የቀረ ስንብት
የመጨረሻ የጽሁፍ
ሰ/ አልፎ አልፎ በአንድ ወር ውስጥ 1 ዐ
ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ቀን የቀረ
ደመወዝ ቅጣት
የመጨረሻ የጽሁፍ
ሸ/ ለሚቀጥለው ተረኛ ሳያስረክብ የሄደ
ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ሰራተኛ
ደመወዝ ቅጣት
የመጨረሻ
29.4.5.2 መዘዋወር/መታጣት
የ 10 ቀን ደመወዝ የጽሁፍ
ሀ/ ከምድብ ስራው መታጣት በሥራ ጊዜ የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና 2 ኛ
የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ቅጣትና 2 ኛ ደረጃ ማስጠንቀቂያና ስንብት
ስራውን ትቶ ያለፍቃድ ሲዘዋወር ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የ 15 ቀናት
የተገኘ
ደመወዝ ቅጣት
ለ/ በሥራ ሰዓት ከድርጅቱ ቅጥር ግቢ የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የ 7 ቀን ደመወዝ ቅጣትና 2 ኛ የመጨረሻ የጽሁፍ ስንብት
ያለፈቃድ የወጣ ያልሰራበት 2 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ማስጠንቀቂያና የ 15

35
ደመወዝ ተቆርጦ ማስጠንቀቂያ ቀናት ደመወዝ ቅጣት
ሐ/ ስራ መስራት ባለበት ሰዓት
ከተፈቀደው ጊዜ ቀድሞ ወይም የመጨረሻ
ከተፈቀደው ጊዜ በላይ ካፍቴሪ ተቀምጦ የጽሁፍ
የ 7 ቀናት ደመወዝ
የተገኘ ሰራተኛ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የ 2 ቀናት ደመወዝ ቅጣት ማስጠንቀቂያና ስንብት
ቅጣት
የ 15 ቀናት
ደመወዝ ቅጣት

29.4.5.3 የስራ ሀላፊነትን አለመወጣት


ሀ/የተቀጠረበትን ተግባር እንዲያከናውን የ 15 ቀናት ደመወዝ
የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና 2 ኛ
ከተወሰነው የሥራ ጊዜ ሳያሰፈቅድ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ቅጣትና የመጨረሻ ስንብት
ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
ለግል ጥቅም ያዋለ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ

ለ/ የተመደበበትን ስራ በቸልተኝነት
የመጨረሻ የጽሁፍ
ወይም በግድየሌሽነት ሳያከናውን የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 7
ማስጠንቀቂያ የ 15 ቀናት ስንብት
መቅረቱ በማስረጃ ከተረጋገጠ ቀን ደመወዝ ቅጣት
ደመወዝ ቅጣት
ለሚደርሰው ጥፋት ተጠያቂ ሆኖ
ሐ/ እንዲጠበቅ በተሰጠው ሥፍራ
ተገቢውን ጥበቃ ሳያደርግ ቀርቶ
ስንብት
ንብረት እንዲጠፋ ያደረገ
ለሚደርሰው ጉድለት ተጠያቂ ሆኖ
መ/ በኃላፊነት በተመደበበት የሥራ ክፍል
ተገቢውን ቁጥጥር ባለማድረጉ
ሁለተኛ ደረጃ የጽሁፍ
በሚመራቸው ሰራተኞችም ሆነ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 5 ከደመወዝና ከሥራ
ማስጠንቀቂያና የ 1 ዐ ቀናት ስንብት
በሌላ ወገን ወይም በድርጅቱ ላይ ቀናት ደመወዝ ቅጣት ደረጃ ዝቅ ማድረግ
ደመወዝ ቅጣት
ጉዳት የሚያደርስ ጥፋት ቢፈጽም
ለደረሰው ጉዳት ኃላፊ ሆኖ

ሠ/ በኃላፊነት ወይም በተመደበበት 2 ኛ ደረጃ የጽሁፍ የመጨረሻ የጽሁፍ ስንብት


የሥራ ፀባይ ወይም የሥራ ቦታ ማስጠንቀቂያና የ 5 ቀናት ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት
የተነሳ ከሌላ ስራ ክፍል ጋር በስራ ደመወዝ ቅጣት ደመወዝ ቅጣት
ትብብር እንዲደረግ ተጠይቆ

36
ሊተባበር ሲገባው ለመተባበር
ፈቃደኛ ሆኖ ያለመገኘቱ ሲረጋገጥ
29.4.5.4. ካርድ መምታት/መፈረም
የመጨረሻ የጽሁፍ
ሀ/የሌላውን ሰራተኛ ካርድ የመታ ወይም
ማስጠንቀቂያ የ 15 ቀናት ስንብት
አስመስሎ የፈረመ
ደመወዝ ቅጣት
ለ/ ያለበቂ ምክንያት የሰዓት የመጨረሻ
መቆጣጠሪያ ካርድ ሲወጣና ሲገባ የጽሁፍ የጽሁፍ
ያልመታ ወይም የቃል ማስጠንቀቂያ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ማንቀጠንቀቂያና የ 5 ማስጠንቀቂያና ስንብት
ያልፈረመ/ያልፈረመበት ደመወዝ ቀን ደመወዝ ቅጣት የ 15 ቀናት
ተቆርጦ ደመወዝ ቅጣት
ሐ/ በሰዓት መቆጣጠሪያ መዝገብ ላይ
የመጨረሻ የጽሁፍ
ፈረሞ ወይም ካርድ መትቶ ከስራው
ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ያልተገኘ በስራ ላይ ያለነበረበት ጊዜ
ደመወዝ ቅጣት
ከደመወዙ ተቀናሽ ተደርጎ
የ 3 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የ 15 ቀናት ደመወዝ ቅጣትና
36.8.5.5 መተኛት
2 ኛ ደረጃ የጽሁፍ የመጨረሻ የጽሁፍ ስንብት
ሀ/ በስራ ጊዜ ተኝቶ የተገኘ ሰራተኛ
ማስጠንቀቂያ ማስጠንቀቂያ
የመጨረሻ የጽሁፍ
ለ/ በስራ ጊዜው ተኝቶ የተገኘ የጥበቃ
ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ሰራተኛ
ደመወዝ ቅጣት
የመጨረሻ
29.845.6 በስራ ሰዓት መላፋት
የ 5 ቀን ደመወዝ የጽሁፍ
ሀ/ በሥራ ሰዓትና በስራ ላይ ሆኖ ሲላፋ የ 3 ቀን ደመወዝ ቅጣትና 2 ኛ
የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ቅጣትና 3 ኛ ደረጃ ማስጠንቀቂያና ስንብት
የተገኘ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የ 15 ቀናት
ደመወዝ ቅጣት
የመጨረሻ የጽሁፍ
ለ/ በኢንተርፕራይዙ ቅጥር ግቢ ውስጥ
ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
የግብረ ስጋ ግንኙነት መፈፀም
ደመወዝ ቅጣት
29.845.7 በሥራ ሰዓት ፣ የሥራ፣የደንብ
ልብስና የአደጋ መከላከያ አለመጠቀም

37
የመጨረሻ
ሀ/ ለሥራ የተሰጠውን ልብስ፣ጫማ፣ የ 2 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የ 7 ቀን ደመወዝ የጽሁፍ
የአደጋ መከላከያና የመሳሰሉትን የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ 21 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ቅጣትና 3 ኛ ደረጃ ማስጠንቀቂያና ስንብት
አለመጠቀም እና በንፅህና አለመያዝ ማስጠንቀቂያ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የ 15 ቀናት
ደመወዝ ቅጣት
ለ/ የተሰጠውን የስራ ልብስ፣ጫማ የአደጋ የ 4 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
መከላከያ ባለመጠቀም አደጋ 1 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ቢደርስበት ማስጠንቀቂያ ደመወዝ ቅጣት
ሐ/ ቀበቶ ያላቸውን ተሽከርካሪ የ 3 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና 3 ኛ
ለሚያሽከረክሩ ሾፌር የአደጋ 2 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ስንብት
ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
መከላከያ ቀበቶ አለማሰር ማስጠንቀቂያ ቀናት ደመወዝ ቅጣት
29.4.5.8 በንብረት ላይ ወይም በስራ ቦታ
ሆን ብሎ አደጋ ስለማድረስ የመጨረሻ የጽሁፍ
የ 3 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የ 7 ቀን ደመወዝ ቅጣትና 3 ኛ
ሀ/ የሚሰራባቸውን መሳሪያዎች የጣለ፣ ማስጠንቀቂያና የ 15 ስንብት
የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
መሳሪያውን ተክቶ ወይም ዋጋውን ቀናት ደመወዝ ቅጣት
ከፍሎ
ለ/ ለሥራ አስፈላጊ ሳይሆን መርዛማ
በህግ ተጠያቂ ሆኖ ስንብት
ኬሚካል ይዞ የተገኘ
የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
ሐ/ጉዳት ሊያደርስ የሚችል
3 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ያልተመደበበትን ሥራ ሲሰራ የተገኘ
ማስጠንቀቂያ ደመወዝ ቅጣት
መ/ ያተመደበበትን ስራ /በተለየ ሁኔታ
የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
ሳይታዘዝ/ በመስራት ጉዳት ያደረሰ
3 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ላደረሰው ጉዳት/ጉድለት/ተጠያቂ
ማስጠንቀቂያ ደመወዝ ቅጣት
ሆኖ
ሠ/ የድርጅቱ ንብረት በሆኑና
በሚሰራባቸው መሳሪያዎች ሆን ብሎ
ወይም በከባድ ቸልተኝነት ጉዳት ስንብት
ማድረሱ በማስረጃ ሲረጋገጥ
የንብረቱን ዋና ክፍሎ
29.4.5.9 ሳይፈቀድለት ስንብት
ኢንተርፕራይዙን ንብረት ወይም

38
ገንዘብ ለግል ጥቅም ያዋለየንብረቱን
ዋጋ ከፍሎ እና በሕግ ተጠያቂ ሆኖ
29.4.5.10 ንብረት አሳልፎ መስጠት
ሀ/ በኃላፊነት የተረከበውን ንብረት
የመጨረሻ የጽሁፍ
ያለትዕዛዝ አሳልፎ የሰጠ ወይም
ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ያከራየ የንብረቱን ዋጋና ኪራይ
ደመወዝ ቅጣት
በወቅቱ የገበያ ዋጋ ተገምቶ
እንዲከፍል ተደርጎ
29.4.5.11 የኢንተርፕራይዙን ተሽከርካሪ
የመጨረሻ የጽሁፍ
ማሽከርከር
ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ሀ/ ከሚመለከተው ክፍል ሳይፈቀድለት
ደመወዝ ቅጣት
የኢንተርፕራይዙን ተሽከርካሪ ያሽከረከረ
ለ/ ማንኛውም የኢንተርፕራይዙን
ተሽከርካሪ ያለ ኢንተርፕራይዙ
ፈቃድ ወይም ያለ ደረጃ ያሽከረከረና ስንብት
ጉዳት ያደረሰ ለደረሰው ጉዳት
ተጠያቂ ሆኖ
ሐ/ ጥንቃቄ ባለማድረግ
የ 10 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
በሚያሽከረክረው ተሽከርካሪ ላይ
3 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ጉዳት ያደረሰ ለደረሰው ጉዳት
ማስጠንቀቂያ ደመወዝ ቅጣት
ተጠያቂ ሆኖ
መ/ የግል ጥቅም ሊያስገኝ በሚችል
የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
አኳኋን ዕቃም ሆነ ሰው የጫነ፣
3 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ለጫነው እቃ ወይም ሰው በወቅቱ
ማስጠንቀቂያ ደመወዝ ቅጣት
የገበያ ዋጋ ሂሳብ መሰረት ክፍሎ
ሠ/ በመደበኛ የስራ ስዓት
የመጨረሻ የጽሁፍ
የኢንተርፕራይዙንሰራተኛ አላግባብ የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና 2 ኛ
የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ማስጠንቀቂያና የ 15 ስንብት
አላሳፍርም ያለ ወይም ትቶ የሄደ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
ቀናት ደመወዝ ቅጣት
አሽከርካሪ
ረ/ ኢንተርፕራይዙ ቋሚ የመኪና የመጨረሻ የጽሁፍ ስንብት
መሳደሪያ ቦታ ባዘጋጀለት ቦታ ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት
ማሳደር ሲገባው ያለፈቃድ ደመወዝ ቅጣት

39
መኪናውን ከኢንተርፕራይዙ ወይም
ከቅርንጫፉ ውጭ ያሳደረ ሾፌር
ሰ/ የሰርቪስ አገልግሎት ከሰጠ በኋላ
የ 7 ቀናት ደመወዝ ቅጣት የመጨረሻ የጽሁፍ
ከሚመለከተው ኃላፊ የተለየ ፈቃድ
የመጨረሻ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ሳይሰጠው መኪና ይዞ ወደ ግቢ
ማስጠንቀቂያ ደመወዝ ቅጣት
በሰዓቱ ያልተመለሰ ሾፌር
ሸ/ ከሚመለከተው አካል ለመኪና ለስራ የመጨረሻ የጽሁፍ
የበር መውጫ ፈቃድ ሳይኖረው ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
መኪና ከግቢ ይዞ የወጣ ሾፌር ደመወዝ ቅጣት
29.4.5.12 ብክነት
የመጨረሻ የጽሁፍ
ሀ/ ለሥራ የተሰጡትን ዕቃዎች፣ የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና 2 ኛ
የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ማስጠንቀቂያና የ 15 ስንብት
መሳሪያዎችና ሰነዶች ያለአግባብ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
ቀናት ደመወዝ ቅጣት
ያባከነ ወይም ያበላሸ
ለ/ በኢንተርፕራይዙ ስልክ በሥራ የ 10 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
ሳይሆን ለግል ጉዳይ አገር ውስጥ 2 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
የደወለ ማስጠንቀቂያ ደመወዝ ቅጣት
29.4.5.13 እምቢተኝነት
የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና
ሀ/ በስሙ የተፃፈ ደብዳቤ አልቀበልም ከደመወዝ ማገድና እስከ 5 ቀን
3 ኛ ደረጃ የጽሁፍ
ያለ የተሞላለትን የሰራ አፈፃፀም ላይ ካልተቀበለ ስንብት
ማስጠንቀቂያ
አልፈርምም ያለ
የመጨረሻ የጽሁፍ
ለ/ ለአደጋ መከላከል እንዲተባበር
ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ሲጠየቅ ያልተባበረ
ደመወዝ ቅጣት

40
ሐ/በአዋጁ ከተቀመጠው ውጭ ሥራ አንዳይሰራ የመጨረሻ የጽሁፍ
ሠራተኛውን የገፋፋ ወይም ያነሳሳ ወይም ተፃራሪ ማስጠንቀቂያና የ 15 ስንብት
ቅስቀሳ ያደረገ ወይም ያሳደመ ቀናት ደመወዝ ቅጣት
መ/ በዚህ መመሪያ አንቀጽ 3 ንዑስ አንቀጽ 3.2.4 የመጨረሻ የጽሁፍ
የ 3 ቀን ደመወዝ ቅጣትና
መሰረት ሥራውን እንዲሰራ በበላይ ኃላፊው ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
ሲታዘዝ አልሰራም ያለ ደመወዝ ቅጣት
29.4.5.14 ጠበኛነት
የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
ሀ/ በሥራ ላይ የበላይን ወይም የበታችን ወይም
3 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ማንኛውንም የሥራ ባልደረባ መሳደብ
ማስጠንቀቂያ ደመወዝ ቅጣት
በማስረጃ ሲረጋገጥ
የ 7 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
ለ/ በሥራ ጊዜ ጠብ መጫርን ማስፈራራት ወይም
የመጀመሪያ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
ሥራ ማወክ በማስረጃ ሲረጋገጥ
ማስጠንቀቂያ ደመወዝ ቅጣት
ሐ/ በኢንተርፕራይዙ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሰው
የመጨረሻ የጽሁፍ
የደበደበ፣ የደበደበውን ሰው የህክምና ወጪ
ማስጠንቀቂያና የ 15 ስንብት
ሸፍኖ በድብደባው ወቅት በንብረት ላይ ጉዳት
ቀናት ደመወዝ ቅጣት
ከደረሰ የንብረቱን ዋጋ ከፍሎ
መ/ በኢንተርፕራይዙ ውስጥም ሆነ ውጭ በሥራ
በህግ መጠየቁ
ላይ ተሰማርቶ በሚገኘው ሰራተኛ ላይ ሆነ
እንደተጠበቀ ሆኖ ስንብት
ብሎና አውቆ አስቦ አደጋ ያደረሰ
ሠ/ ደንበኞችና ወኪሎችን ማጉላላት፣ የ 3 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የ 7 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
ለደንበኞችና ለወኪሎች ተገቢውን አገልግሎት 1 ኛ ደረጃ የጽሁፍ 3 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ስንብት
አለመስጠት ማስጠንቀቂያ ማስጠንቀቂያ ቀናት ደመወዝ ቅጣት
ረ/ የኢንተርፕራይዙን ደንበኞች የዘለፈ በማስረጃ የመጨረሻ የጽሁፍ
ሲረጋገጥ የ 10 ቀን ደመወዝ ቅጣትና
ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
ደመወዝ ቅጣት
29.4.5.15 እምነት ማጉደል
ሀ/ ስርቆት፣ በኢንተርፕራይዙ ውስጥ በህግ መጠየቁ
የኢንተርፕራይዙ ሆነ የሌላ ሰራተኛ ንብረት እንደተጠበቀ ሆኖ ስንብት
ወይም ገንዘብ መውሰዱ በማስረጃ ሲረጋገጥ
ለ/ ለመውሰድ ወይም ለመስረቅ የሞከረ በማስረጃ የመጨረሻ የጽሁፍ ስንብት

41
ሲረጋገጥ ማስጠንቀቂያና የ 15
ቀናት ደመወዝ ቅጣት
ሐ/ በግዢ አሰራር ላይ የኢንተርፕራይዙን ጥቅም
ሳይጠብቅ ለግል ጥቅም ለማግኘት ጥረት
ያደረገ ወይም በግዥ ሥራ ወቅት
በህግ መጠየቁ
የኢንተርፕራይዙን ጥቅም ያላስከበረ
እንደተጠበቀ ሆኖ ስንብት
በኢንተርፕራይዙ ላይ የደረሰውን ኪሳራና
ኢንተርፕራይዙ ሊያገኝ የነበረውን በገንዘብ
ከፍሎ
መ/ ለማጭበርበር የሃሰት ሰነዶችንም ሆነ
ማስረጃዎችን ያቀረበ በኢንተርፕራይዙ
በህግ መጠየቁ
ማህተም ወይም አርማ በያዙ እትሞች
እንደተጠበቀ ሆኖ ስንብት
በመጠቀም ያጭበረበረ ወይም አስመስሎ
የፈረመ
ሠ/ የግዥ ዋጋ ማወዳደሪያ ሰነዶችን
በህግ መጠየቁ
ሚስጥራዊነት ያልጠበቀ ወይም የአንዱን ዋጋ
እንደተጠበቀ ሆኖ ስንብት
ተመን ለሌላ ሰው /ወገን/ ያሳየ
ረ/ ከደንበኞች ገንዘብ፣ ወይም ሌላ ነገር በህግ መጠየቁ
ያጭበረበረ መሆኑ ሲረጋገጥ እንደተጠበቀ ሆኖ ስንብት
የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
ሰ/ የኢንተርፕራይዙ ማስታወቂያ ያለፈቃድ
2 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ቀናት ስንብት
የቀደደ፣ ያበላሸ ወይም ያነሳ
ማስጠንቀቂያ ደመወዝ ቅጣት
ሸ/ የኢንተርፕራይዙን ዕድገት፣ ህልውናና ጥቅም
የመጎዳ ምስጢር ለሌላ ሰው አሳልፎ የሰጠ፣ በህግ መጠየቁ
ያሳወቀ በኢንተርፕራይዙ ላይ ለሚደርሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ስንብት
ጉዳት ተጠየቂ ሆኖ
ቀ/ ከኢንተርፕራይዙ ገንዘብ/ንብረት ተረክቦ እስከ 5 ቀን ገቢ ካላደረገ እስከ 10 ቀን ገቢ ካላደረገ
ያለበቂ ምክንያት ገቢ ያላደረገ ለንብረቱና የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የ 15 ቀን ደመወዝ ቅጣትና እስከ 15 ቀን ገቢ
ለገንዘቡ ተጠያቂ ሆኖ 2 ኛ ደረጃ የጽሁፍ የመጨረሻ የጽሁፍ ካላደረገ ስንብት
ማስጠንቀቂያ ማስጠንቀቂያ

42
በ/ ራሱን ወይም ሌላውን ለመጥቀም ሲል የሃሳት
ሰነዶችን በማስረጃነት ያቀረበ ወይም በህግ መጠየቁ
የኢንተርፕራይዙን የሚጎዳ የሃሰት የምስክር እንደተጠበቀ ሆኖ ስንብት
ወረቀት የሰጠ በማስረጃ ሲረጋገጥ
ተ/ የራሱን ወይም የሌላውን ሰው ብልጽግና
በመሻት ማንኛውንም የኢንተርፕራይዙን
ንብረት ወይም ሰነድ ወይም ገንዘብ ለግል በህግ መጠየቁ
ጥቅሙ ያዋለ ወይም ያለፈቃድ የወሰደ እንደተጠበቀ ሆኖ ስንብት
ወይም ለ 3 ኛ ወገን አሳልፎ የሰጠ መሆኑ
በማስረጃ ሲረጋገጥ
29.4.5.16 በአሰሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር የ 5 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
የ 3 ቀን ደመወዝ ቅጣትና
377/96 እና በዚህ መመሪያ መሠረት የትርፍ 3 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ስንብት
2 ኛ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
ሰዓት ሥራ ትዕዛዝ አለመቀበል ማስጠንቀቂያ ቀናት ደመወዝ ቅጣት
29.4.5.17 ማጥፋት
ሀ/ በኃላፊነት የተረከበውን መሣሪያ፣ ንብረትና
የ 7 ቀን ደመወዝ ቅጣትና የመጨረሻ የጽሁፍ
ገንዘብ ካለመጠንቀቅ የተነሳ በሦስተኛ ወገን የ 3 ቀን ደመወዝ ቅጣትና
2 ኛ ደረጃ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የ 15 ስንብት
ያስወሰደ ወይም ያሰረቀ በሦስተኛ ወገን የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
ማስጠንቀቂያ ቀናት ደመወዝ ቅጣት
ስለመወሰዱ ሲረጋገጥ ለጠፋው ንብረት
ተጠያቂ ሆኖ
ለ/ በኃላፊነት የተረከበውን መሣሪያ የጣለ፣ ወይም
ለሦስተኛ ወገን ያስወሰደ ወይም ያሰረቀ በህግ ስንብት
ተጠያቂ ሆኖ
29.4.5.18 አሳልፎ መስጠት
በኃላፊነት የተረከበውን መሣሪያ /መኪና/ የመጨረሻ የጽሁፍ
ላልተፈቀደለት ማንኛውም ሰው ማስጠንቀቂያና የ 15 ስንብት
እንዲጠቀምበት ወይም እንዲነዳ አሳልፎ የሰጠ ቀናት ደመወዝ ቅጣት
በማስረጃ ሲረጋገጥ
29.4.5.18 ማጭበርበር
በማስመሰል በባለስልጣን ፊርማ የተጠቀመ
በህግ መጠየቁ
ወይም የኢንተርፕራይዙ ማኀተም ለግሉ
እንደተጠበቀ ሆኖ ስንብት
ወይም ለሌላ ወገን ጥቅም ላይ ያዋለ

43
29.4.5.19 አንድ ሠራተኛ አንድ ወይም ከአንድ በላይ ጥፋት አጥፍቶ ከተቀጣ በኋላ ቅጣቱ ከሚነሳበት ጊዜ በፊት ሌላ ጥፋት ቢያጠፋ የሚቀጣው ለመጨረሻ ጊዜ
ላጠፋው ጥፋት/ጥፋቶች ለከፍተኛው በስነ ስርዓት እርምጃ አወሳሰድ ሠንጠረዥ ሊቀጣ የሚገባውን በሁለተኛ ደረጃ ያለውን ቅጣት ይሆናል።
29.4.5.20 በዚህ የቅጣት ሠንጠረዥ ውስጥ ያልተሸፈኑ የሥነ ሥርዓት ጉድለቶች ባጋጠሙ ጊዜ ኢንተርፕራይዙ ከተመሳሳይ የስነ ስርዓት ጉድለቶች ጋር
በማዛመድ የቅጣት እርምጃ ይወስዳል።

a.

44
አንቀጽ 54 የተወሰደ የስነ-ስርዓት ጉድለቶች ማረሚያ እርምጃ ስለመሻር
1. አንድ ሰራተኛ ከመጨረሻ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እና የደመወዝ ቅጣት በታች የሚያስቀጣ ጥፋት አጥፍቶ
እርምጃ ከተወሰደበት በኋላ የተቀጣበትን ቅጣት ወይም ሌላ ጥፋት በሚቀጥሉት 6 ወራት ውስጥ ካልፈፀመ
እና ከጥፋቱ የታረመ መሆኑ በኢንተርፕራይዙ ሲረጋገጥ የጥፋት መሻሪያ ደብዳቤ ይጻፍለታል።

2. አንድ ሰራተኛ የመጨረሻ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እና የደመወዝ ቅጣት የሚያስቀጣ ጥፋት አጥፍቶ እርምጃ
ከተወሰደበት በኋላ የተጣለበትን ቅጣት ወይም ሌላ ጥፋት በሚቀጥለው አንድ አመት ውስጥ ካልፈፀመ እና
ጥፋቱ የታረመ መሆኑ በኢንተርፕራይዙ ሲረጋገጥ የጥፋት መሻሪያ ደብዳቤ ይፃፍለታል።

3. ሰራተኛው በግል ማህደር ውስጥ ስለሚያዙ መረጃዎች ለማወቅ በሚፈልግበት ጊዜ የሚመለከተውን ኃላፊ
ጥይቆ ማህደሩን ሊያይ ይችላል።

ክፍል ስምንት ልዩ ልዩ ጉዳዮች


አንቀፅ 55 የሰራተኛ የአገልግሎት የእድሜ ጣሪያ
1. ማንኛውም ሰራተኛ የእድሜ ጣሪያ 60 ዓመት ይሆናል። የሰራተኛው ዕድሜ የሚወሰደው ሲቀጠር ከያዘው
የትምህርት ማስረጃ ነው።
2. ሰራተኛው ዕድሜው 60 ዓመት ሲሞላው በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/11 መሰረት ማግኘት
የሚገባው ክፍያ ተፈፅሞለት ከኢንተርፕራይዙ ጋር ያለው የስራ ውል እንዲቋረጥ ይደረጋል።
3. ሆኖም የሰራተኛው ልምድ እና የትምህርት ዝግጅት ከገበያ ሊገኝ የማይችል ሲሆን ማነጂንግ ዳይሬክተሩ
የሰራተኛውን የእድሜ ጣሪያ ከ 5 ዓመት ላልበለጠ ጊዜ ሊያራዝመው ይችላል።

አንቀጽ 56 የሴቶችና የወጣት ሠራተኞች የሥራ ሁኔታ


በአዋጁ አንቀጽ 87-91 በተመለከተው መሠረት የሚፈፀም ይሆናል።

አንቀጽ 57 የሙያ ደኅንነት ፣ጤንነትና የሥራ አካባቢ


የሙያ ደኅንነት፣ ጤንነትና የሥራ አካባቢን በተመለከተ በአዋጅ ቁጥር 1156/11 አንቀጽ 92-94 በተጠቀሱትና
በዚሁ ደንብ በተካተቱት መሠረት ይሆናል።

አንቀጽ 58 በሥራ ምክንያት ስለሚመጡ ጉዳቶች


ኢንተርፕራይዙ በሚገባው የኢንሹራንስ ሽፋን መሠረት ተፈፃሚ ይሆናል።

አንቀፅ 59 የሰራተኛ ማህበር እና የህብረት ስምምነት


1. ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ ማህበር እንዲቋቋም አስፈላውጊን ድጋፍ ያደርጋል፣ ማህበሩም የሚቋቋመው በአዋጅ
ቁጥር 1156/2011 አንቀፅ 113 መሰረት ይሆናል።
2. የሚቋቋመሙ የሰራተኛ ማህበር ከኢንተርፕራይዙ የማኔጅመንት አባላት ጋር የጋራ ስምምነት ሊፈፅም
ይችላል። ይህም በአዋጅ ቁጥር 1156/2011 መሰረት ይሆናል።

45
አንቀጽ 60 የሥራ ምስክር ወረቀት ስለመስጠት
ሰራተኛው በስራ ላይ እያለ የምስክር ወረቀት በሚጠይቅበት ጊዜ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሰራተኛው
የምስክር ወረቀት እንዲሰጠው ካመለከተበት ቀን ጀምሮ በ 3 ቀናት ባልበለጠ ጊዜ በቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ
ሰራተኛው የጠየቀውን የምስክር ወረቀት ይሰጠዋል።

አንቀፅ 61 የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ማህተም


1. ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ማህተም አደረጃጀቱ ካለ የመዝገብ ቤት ኃላፊ እጅ፣ መዝገብ ቤት ከሌለ
በዳይሬክተሩ ፀሐፊ እጅ ይቀመጣል፣
2. መዝገብ ቤት ኃላፊው በዚህ መመረያ እና በሚሰጥ ውክልና መሠረት ደብዳቤ ፈርሞ ማውጣት የሚችል
ኃላፊ ወይም ተወካይ ፊርማ እና ቲተር ተቀምጦበት የሚደርሰውን ደብዳቤ ማኅተም አትሞ ወጪ
ያደርጋል፣
3. ማንኛውም ወጪ ደብዳቤም ሆነ መረጃ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ማህተም ሊደረግበት ይገባል። ማነጅንግ
ዳይሬክተሩ ማነኛውም ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙን የሚመለከቱ ጉዳዮችን በሚመለከት ወደ ላይ፣ወደ ጎንና
ወደ ታች፣ የመምሪያ ሥራ አስኪያጆች ዘርፋቸውን በሚመለከት ደብዳቤ ወጪ ያደርጋሉ።

አንቀጽ 62 መመሪያው የሚፀናበት ጊዜ


ይህ መመሪያ በኢንተረፕራይዙ ቦርድ ታይቶ ከፀደቀበት ___ቀን መስከረም 2013 ዓ.ም ጀምሮ የፀና
ይሆናል።

ቅፃቅፆች
 በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ የርክክብ
ማስረጃ ቅጽ /ክሊራንስ/

1. የሠራተኛው ስም ---------------------------------- የስራ መደብ --------------------------------------


2. የርክክብ ቅጽ የሚዞርበት ምክንያት -------------------------------------------------------

46
ተ.ቁ የስራ ዘርፍ አስተያየት/ዕዳ ካለ ይጠቀስ ፊርማ ቀን
1 የሚሰሩበት ክፍል
2
3
4
5
6
7
8
9

3. ፊርማ ____________

ማሳሰቢያ፡ ሠራተኛው ከለቀቀ ወይም ከተዛወረ በኋላ ዘግይቶ የሚገኝ የኢንተርፕራይዙ ንብረት /ገንዘብ/
በግለሰቡ ላይ ከተገኘ ይህ ቅጽ ከመጠየቅ አያድንም።

 በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲት ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ ለተወሰነ ስራ ወይም


ጊዜ የሚቆይ የቅጥር ውል
መግቢያ

ይህ የቅጥር ውል ከዚህ በታች የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ እየተባለ የሚጠቀሰው እና


ሰራተኛ እየተባለ በሚጠቀሰው በአቶ/ወ/ሮ /ወ/ሪት ------------------------ መካከል በአዋጅ ቁጥር 1156/11
አንቀጽ 10 ሀ፣ ሐ እና ሠ መሰረት የተፈፀመ ለተወሰነ ስራ ወይም ጊዜ የሚቆይ የስራ ውል ነው።

አንቀጽ 1 ውሉ የሚፀናበት ጊዜ

47
ይህ ውል ፀንቶ የሚቆየው በአሁኑ ስዓት የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ እያከናወነ ባለው
የ-------------------------- ተቋም ምክንያት የተፈጠረ የስራ ጫና እስከ ሚቃለል ይህ ውል ከተፈረመበበት
ከ---------------- ቀን -------------------- ዓ.ም ጀምሮ አስከ --------------------

ቀን ---------------------- ዓ.ም ነው። ሆኖም የሙከራ ጊዜ ከማለቁ በፊት ማናቸውም ወገን ውሉን
መሰረዝ ይችላል።

አንቀጽ 2 የስራ አይነት

ሰራተኛው የተቀጠረበት የስራ መደብ ወይም አይነት ----------------- ሆኖ ከዚህ ጋር የተዛመዱትንና ከዚሁ
ተግባር የሚመነጩትን ስራዎች የማከናወን ግዴታን ያጠቃልላል።

አንቀጽ 3 የስራ ቦታ

ሰራተኛው አሁን የተቀጠረበት የስራ ቦታ ---------------------- ቢሆንም የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ደመወዝና


ደረጃውን ጠብቆ ሰራተኛውን በኢንተርፕራይዙ ውስጥ በሚገኙት ተቋማት አዛውሮ ማሰራት ይችላል።

አንቀጽ 4 ደመወዝ

ቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ለሰራተኛው በየወሩ ብር ------------------- የወር ደመወዝ ይከፍላል። ከዚህም ላይ


የስራ ግብር፣ ሌሎች ህጋዊ ክፍያዎች ይቀነሳሉ።

አንቀጽ 5 የሕጎች ተፈፃሚነት

አዋጅ ቁጥር 1156/11 ፣ የህብረት ስምምነትና ሌሎች ድንጋጌዎች በሰራተኛውና በኢንተርፕራይዙ መካከል
በተፈፀመው በዚህ ውል ላይ በተመሰረተው የስራ ግንኙነት ላይ ተፈፃሚ ይሆናል።

አንቀጽ 6 ውሉን ስለመሰረዝ ወይም ስለ ማደስ

6.1 በውሉ ጊዜ ውስጥ ሰራተኛው የገባበትን ግዴታ መወጣት ያልቻለ እንደሆነ ወይም የዲሲፕሊን ጉድለት
የፈፀመ እንደሆነ ወይም ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ የቢዝነስ ኢንተርፕራይዙ ሲያጋጥመው ወይም
የተወሰነው ስራ /ጊዜ/ ሲያልቅ ኢንተርፕራይዙ ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ መስጠት ሳያስፈልገው የስራ
ውሉን መሰረዝ ይችላል።

48
6.2 በውል አንቀጽ 6.1 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ በውል አንቀጽ 1 የተጠቀሰው ጊዜ ገደብ ሲያልቅ
ይህ ውል ቀሪ ይሆናል። ሆኖም ሁለቱ ወገኖች ውሉ እንዲራዘም ስምምነት ላይ ከደረሱ በደረሱበት
ስምምነት መጠን አሰሪው ውሉ የተራዘመ መሆኑን ጠቅሶ ለሰራተኛው በፅሁፍ ሲያሳውቅ ውሉ እንደ
ታደሰ ይቆጠራል።

አንቀጽ 7 ውሉ ስለሚፀናበት ጊዜ

ይህ ውል ከ-------------------------------- እስከ ------------------------------- ድረስ የፀና ይሆናል

አንቀጽ 8 ውሉ የተፈረመበት ቀን

ይህ ውል ዛሬ ------------------------------- 200---------- ዓ.ም በሁለቱም ወገኖች ተፈረመ

የአሰሪው ስምና ፊርማ የሠራተኛው ሙሉ ስምና ፊርማ

--------------------------- -------------------------------

ምስክሮች፡ ስም ፊርማ

1. ---------------------------------- -------------
2. ---------------------------------- -------------
3. --------------------------------- -------------
 በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ የሠራተኞች
የህይወት ታሪክ ቅጽ
1. የግል ሁኔታ መግለጫ
ሀ/ የሰራተኛው/ዋ ስም ---------------------------------- የአባት ስም --------------------------------------

የአያት ስም ----------------------------------- የእናት ሙሉ ስም -------------------------------------

ለ/ ልደት -------------------- ቀን ------------------- ዓ.ም ---------------------- ክልል -----------------


ዞን----------- ከተማ---------------- ቀበሌ ------------------- ስልክ ቁጥር -----------------------

ሐ/ ዜግነት ---------------------------------

መ/ ፆታ ---------------

2. የቤተሰብ ሁኔታ፡
ሀ/ የጋብቻ ሁኔታ ያገባ ያላገባ በፍች የተለየ

49
ለ/ የሚስት /የባል ሙሉ ስም ----------------------------------- ስልክ ቁጥር ---------------------------

ሐ/ የልጆች ብዛት ------------ ወንዶች ------------- ሴቶች -------------

ተ.ቁ ወንዶች ልደት ተ.ቁ ሴቶች ልደት


1 1
2 2
3 3

3. የትምህርት ደረጃ፡

የትምህርት ደረጃ የትምህርት ቤቱ የትምህር ዘመን ትምህርቱን የትምህርት ደረጃ


/የተቋሙ መጠሪያ/ አጠናቋል
ከ እስከ
1 ኛ ደረጃ
መለስተኛ ደረጃ
2 ኛ ደረጃ
ኮሌጅ
ዩኒቨርሲቲ
ልዩ ት/ቤት /ተቋም

 የመኪና መንጃ ፈቃድ አለዎት------------- ደረጃው------------ የታደሰበት ጊዜ ----------- ክልል


-------------- ዞን ----------- ከተማ ----------- ክፍለ ከተማ ------------ ቀበሌ -------- የቤት ቁጥር
------------
4. የቋንቋ ችሎታ /የሀገር ውስጥ ወይም የውጪ ሀገር ቋንቋዎች

ተ.ቁ የቋንቋው ስም መስማት መናገር ማንበብ መፃፍ


1
2
3
5. የስራ ሁኔታ
ሀ/ አሁን የያዙት የስራ መደብ መጠሪያ --------------------------------------------------------------
ለ/ ከዚህ በፊት በመንግስት መ/ቤት ሰርተዋል? -----------------------------------------------------

ከ------ አስከ ------ የቀጣሪው መ/ቤት የስራው አይነት ደመወዝ የለቀቁበት


ስም ምክኒያት
1
2
3
6. በአደጋ ጊዜ ተጠሪ

50
ተ.ቁ ስም ከነ ክልል ከተማ ክ.ከተማ ቀበሌ የቤት የስልክ
አያት ቁጥር ቁጥር

7. ዘመድ ያልሆኑ ስለ እርስዎ የሚያውቁ የሁለት ሰዎች ስም ይስጡ

ተ.ቁ ስም ከነ ክልል ከተማ ከ.ከተማ ቀበሌ የቤት የስልክ


አያት ቁጥር ቁጥር

8. ማረጋገጫ
ከአሁን ቀድም የሞላሁት የሒወት ታሪክ ቅጽ ተመሳሳይና ያልተለየ መሆኑን እያረጋገጥኩ የተለየ ቢሆን ለምሳሌ፡
እንደ ልደት ዘመን የመሳሰሉት የተለያዩ ቢሆን /ከሚመለከተው ክፍል ጥያቄ ቢነሳ ዋስ ሆኘ አመልሳለሁ።

የሠራተኛው ስምና ፊርማ -------------------------------------------- ቀን----------------------------------------

51
 በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ ተቋማት የሠራተኞች
የስዓት መቆጣጠሪያ
የስራ ክፍል ------------------------------------
ከ-------------------------------------------- ቀን እስከ -------------------------------------- ቀን 201------------------------------ ዓ.ም

ተ.ቁ ሙሉ ስም ሰኞ ማክሰኞ ረቡዕ ሀሙስ ዓርብ ቅዳሜ


ጧት ከሰዓት ጧት ከሰዓት ጧት ከሰዓት ጧት ከሰዓት ጧት ከሰዓት ጧት ከሰዓት
1
2
3
4
5
6
7
8
9
10

መግለጫ፡ የክፍል ሀላፊ ስም ---------------------------------- ፊርማ ----------------- ቀን--------------


የሰው ሀብት ባለሙያ ስም ------------------------------ ፊርማ -------------- ቀን ----------------

 ዓፈ = የዓመት ፈቃድ
 ሕፈ = የህመም ፈቃድ
 ወፈ = የወሊድ ፈቃድ
 መስ = መስክ ስራ
 ሐ = የሐዘን ፈቃድ
 እፍ = የእክል ፈቃድ
 ቀ = ቀሪ
 ዘ = የዘገየ

52
 በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ
የደመወዝ ውክልና መስጫ ቅጽ

1. እኔ ---------------------------------------------------- የመለያ ቁጥር ----------------------------------

ከ----------------------- 201--------- ዓ.ም ጀምሮ አቶ/ወ/ሮ ---------------------------------- ስለኔ

ሆነው ደመወዜንና ጥቅማ ጥቅሜን እንዲቀበሉልኝ መወከሌን በፊርማየ አረጋግጣለሁ።

2. የወካይ ስምና ፊርማ -------------------------------------------------------------------------------

3. የተወካይ ስምና ፊርማ -----------------------------------------------------------------------------

4. ምስክሮች፡-

ስም ፊርማ

1 ኛ. -------------------------------------------------------- ----------------------

2 ኛ. ------------------------------------------------------- ----------------------

3 ኛ.-------------------------------------------------------- ----------------------

ውክልና የተሰጠበት ቀን --------------------------------------------------

53
 በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ
የፈቃድ መጠየቂያ ቅጽ

ቀን---------------------------
የሠራተኛው ስም ---------------------------------------- መለያ ቁጥር --------------------

የስራ መደቡ መጠሪያ --------------------------- የሚሰራበት ክፍል -------------------

የአገልግሎት ጊዜ -------------------------------------- ፈቃድ ወስዶ የሚገኝበት አድራሻ -----------------------

ቀበሌ ----------------- የቤት ቁጥር --------------- ስልክ ቁጥር -------------------------

የተጠየቀው የፈቃድ አይነት

1. የዓመት ፈቃድ የተጠየቀው ፈቃድ ----------- ቀናት


2. የሕመም ፈቃድ ከ----------- አስከ ---------------
3. የሐዘን ፈቃድ ፈቃድ የተጠየቀበት ምክንያት --------------
4. የወሊድ ፈቃድ -----------------------------------------------
5. ሌላ ------------------------------------------------------
------------------------------------- የጠያቂው ሠራተኛ ፊርማ ---------------------------------
የተተኪ ሰራተኛ ስም ------------------------------------- የተፈቀደው ጊዜ --------------- ቀን -----------

የክፍሉ ኃላፊ አስተያየት ----------------------------------------------------------------------------------------

የክፍሉ ኃላፊ ስም ----------------------------------------------- ፊርማ -------------- ቀን ------------------

በሰው ሀብት አስተዳደር ክፍል ብቻ የሚሞላ

ሳይጠቀሙበት ቀርቶ ካለፈው ዓመታት የዞረ ፈቃድ /የተመዘገበ

20---------------------------- ------------------------------------------- ቀናት

20---------------------------- ------------------------------------------- ቀናት

20---------------------------- ------------------------------------------ ቀናት

ድምር ------------------------------------ ቀናት የተፈቀደ ------------------------- --------ቀናት

ከዚህ በኋላ የሚተርፈው ፈቃድ ------------------ ቀናት

ፈቃዱን ያዘጋጀው ስምና ፊርማ -----------------------------------------------------------------

54

You might also like