Professional Documents
Culture Documents
መግቢያ
ሪከርዶችን በማስተዳደር ሂደት የሚፈጠሩ አላስፈላጊ ወጪዎችን እንዲሁም የቦታና የጊዜ ብክነት ሊያስቀር የሚችል
ዘመናዊ የሪከርድ ሥራ አመራር ሥርዓት በመዘርጋት ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፣
ከማይንቀሳቀሱ ሪከርዶች ውስጥ ለዘለቄታዊ ፋይዳ እና ለጥናትና ምርምር ከፍተኛ ዋጋ ያላቸውን ለይቶ በመጠበቅ
ለመጪው ትውልድ እንዲተላለፍ ማድረግና አገልግሎት ላይ ማዋል በማስፈለጉ፣
የሪከርዶች ምዘና፣ ዝውውርና አወጋገድ በተመለከተ ማንኛውም የመንግስት አካል የሚመራበት አንድ ወጥ የሆነ ሥርዓት
መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣
በወጣቶች የስፖርትና የባህል ሚኒስቴር የወጣውን የሪከርዶች ምዘና፣ ዝውውርና አወጋገድ መመሪያ ቁጥር 2/1997 ን
ማሻሻል በማስፈለጉ፣
በአዋጅ ቁጥር -------------/2006 አንቀፅ 38 ንዑስ አንቀፅ 2 መሠረት ይህ የሪከርዶች ምዘና ዝውውርና አወጋገድ
መመሪያ ወጥቷል።
ክፍል አንድ
ጠቅላላ
1. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ “የሪከርዶች ምዘና፣ ዝውውርና አወጋገድ መመሪያ ቁጥር--------/2006” ተብሎ ሊጠቀስ
ይችላል።
2. ትርጓሜ
የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በቀር በዚሀ መመሪያ ውስጥ:-
3. “ዝውውር” ማለት በምዘና መርሆ እና መስፈርት መሠረት ዘለቄታዊ ፋይዳ አላቸው ተብሎ የተመረጡትን
ሪከርዶች ወደ ባለሥልጣኑ ማዛወር ማለት ነው።
1
6. “የመረጃ ሰጪነት ፋይዳ ያለው ሪከርድ” ማለት የህብረተሰቡን ዕምነት ፣ ልማድ አቤቱታ ፣ አመለካከት ፣
ባህል፣ ኢኮኖሚያዊ ፣ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ትምህርታዊ ሁኔታዎች የሚያንፀባርቁ ክንዋኔዎችን ያካተቱ
ሪከርዶች ማለት ነው።
7. “የሪከርድ መራጭ ኮሚቴ” ማለት በሪከርድ አመንጪው ተቋም የሪከርዶችን ምዘናና መረጣ ሥራ
የሚያከናውን በደንብ ቁጥር---------/2006 አንቀፅ 20 ንዑስ አንቀፅ 1 መሠረት የሚቋቋም ኮሚቴ
ማለት ነው።
8. “ዘላቂ ፋይዳ” ማለት ሪከርዱ ከተፈጠረበት ጉዳይ ባሻገር ለጥናትና ምርምር እንዲሁም ባለው ታሪካዊ
ፋይዳ ለትውልድ እንዲተላለፍ በቋሚነት መጠበቅ ማለት ነው።
9. “ቀጣይ ፋይዳ” ማለት ጠቀሜታው በጊዜ የተገደበ እና ለሪከርድ አመንጪው የዕለት ተዕለት አስተዳደራዊ
እንቅስቃሴ አስፈላጊ ሆኖ በማስረጃነት እና በማረጋገጫነት የሚያገለግል ሪከርድ ማለት ነው።
10. “ባለሥልጣን” ማለት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመፃሕፍት ባለሥልጣን
ነው።
11. “ሠው” ማለት ማንኛውም የተፈጥሮ ወይም በህግ የሰውነት መብት የተሰጠው ሰው ነው።
3. የተፈፃሚነት ወሰን
ክፍል ሁለት
ማንኛውም መንግስታዊ አካል የሪከርዶች ምዘናና መረጣ ሲያከናውን የሪከርዶችን የማያቋርጥ ጠቀሜታ እና
የሪከርዶችን ዘላቂ ፋይዳ የሚሉትን መርሆዎች መሰረት ያደረገ ይሆናል።
መ. ስትራቴጂክ ዕቅዶች
ሠ. ፎቶ ግራፎች
2
ሸ. መጻጻፎች
የዘገቡ፡፡
ውክልና የዘገቡ፡፡
5. ጋዜጣዊ መግለጫዎች፡፡
2. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ አንድ መሠረት የምዘናና መረጣ ስራ ሲያከናውን ከዚህ በታች ለተመለከቱት የግል
ማህደሮች ልዩ ትኩረት መስጠት አለበት።
ሀ. በአርአያነታቸው ተጠቃሽ የሆኑ የቋሚ እና የጊዜያዊ ሠራተኞች እና የበጎ ፈቃድ አገልጋዮች ምደባ እና ሥራ
አፈፃፀም የተጠናቀሩበት መረጃ የያዘ፣
1. በመደበኛ ፍ/ቤቶች ፣ በሸሪዓ ፍ/ቤቶች ፣ በአስተዳደራዊ ፍ/ቤቶች እና በልዩ ፍ/ቤቶች ታይተው ብይን ወይም
ውሳኔ የተሰጠባቸው ሪከርዶች፣
2. ጠቅላይ ፍ/ቤት በሰበር ችሎት ውሳኔ የሰጠባቸው ሪከርዶች እና
3. በፍትህ እና በፖሊስ ጽ/ቤቶች የሚገኙ በማናቸውም ሁኔታ ከእንቅስቃሴ ውጭ የሆኑ ሪከርዶች የመረጣ ሥራ
ይከናወንላቸዋል።
4
4. የክልል መደበኛ ፣ ሸሪዓ ፣ አስተዳደራዊ እና ልዩ ፍ /ቤቶች እንዲሁም በፍትህና በፖሊስ ጽ/ቤቶች ታይተው
ብይን ወይም ውሳኔ የተሰጠባቸው ሆነው በማናቸውም ሁኔታ ከእንቅስቃሴ ውጭ የሆኑ ሪከርዶችን
በተመለከተ ባለሥልጣኑ ከክልሎች ጋር በሚያደርገው ግንኙነት የሚፈፀም ይሆናል።
5. በዚህ አንቀፅ ከንዑስ አንቀፅ አንድ እስከ አንቀፅ ሦስት የተመለከተው እንደተጠበቀ ሆኖ:-
ሀ. ሽብርተኝነትን፣
መ. የሙስና ወንጀሎችን፣
ሠ. የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን፣
ረ. የሞግዚት አስተዳደርን፣
ክፍል ሦስት
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አዋጅ ቁጥር --------/2006 አንቀፅ 15 ንዑስ አንቀፅ 5 ድንጋጌ
መሠረት አመንጪ ተቋማት ለተቋሙ የበላይ ሃላፊ ተጠሪ የሆነ የሪከርድ መራጭ ኮሚቴ ያቋቁማሉ።
1 የሪከርድ መራጭ ኮሚቴ አባላት ከዓላማ ፈፃሚ የሥራ ዘርፎች ፣ ከህግ፣ ከፋይናንስ፣ ከእንፎርሜሽን
ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ እና የሪከርድና ማህደር ኃላፊውን ያካተተ መሆን አለበት።
2 የሪከርድ መራጭ ኮሚቴ አባላት ብዛት በተቋሙ ሥራ ስፋትና ጥበት ላይ የሚወሰን ሆኖ ከአምስት ማነስና
ከዘጠኝ መብለጥ የለበትም።
3 የሪከርድ መራጭ ኮሚቴ አባላት በተቻለ መጠን የተቋሙን ታሪክ፣ ሥልጣንና ተግባራት የሚያውቁ ፣
የረዥም ጊዜ የሥራ ልምድና ብቃት ያላቸው ሊሆኑ ይገባል።
4 የሪከርድ መራጭ ኮሚቴው መርሃ ግብሩን በማዘጋጀት የአፈፃፀም ሪፖርቱን ለተቋሙ የበላይ ሃላፊ በየሩብ
ዓመቱ ሪፖርት ማድረግ አለበት።
5 አመንጪ ተቋማት ለሪከርድ መራጭ ኮሚቴ ሥራ ልዩ ትኩረት በመስጠት አመቺ ሁኔታዎችን የመፍጠር፣
በተለያዩ ምክንያቶች በተጓደሉ አባላት ምትክ በወቅቱ የመተካት ኃላፊነት አለባቸው።
6 የኮሚቴው የሥራ ዘመን ሶስት ዓመት ይሆናል። ሆኖም ተቋሙ ሲያምንበት አባላቱ ለተጨማሪ የሥራ
ዘመን በዲጋሚ ሊመረጡ ይችላሉ።
5
7 የኮሚቴው አባላት 2/3 እና ከዚያ በላይ ካልተገኙ ምልዓተ ጉባኤ አይኖርም።
8 የሪከርድ ምዘናና መረጣ ወሳኝና ጥንቃቄ የሚያስፈልገው በመሆኑ የኮሚቴው ውሳኔ በውይይትና ክርክር
በሚደረስ ስምምነት ይሆናል። ስምምነት በማይኖርበት ሁኔታ በድምፅ ብልጫ ይወሰናል። አስፈላጊ ሆኖ
ሲገኝ ባለስልጣኑን ያማክራሉ።
1. ማንኛውም የሪከርድ መራጭ ኮሚቴ የሚከተሉትን የቅድመ መረጣ ተግባራት ማከናወን አለበት።
ሀ. ለአስተዳደራዊ ሥራ የማይፈለጉና ከእንቅስቃሴ ውጪ የሆኑ ሪከርዶችን የድጋፍ ሰጪ ፣ የዓላማ ፈፃሚ ዘርፍ ወይም
በጉዳያቸው ወይም በሥራ ክፍላቸው የአፈጣጠር ሥርዓታቸውን በመጠበቅ የመለየት ሥራ ማከናወን አለበት።
ለ. የአፈጣጠር ሥርዓታቸው ተጠብቆ የተለዩ ሪከርዶችን እንዲደራጁ ፣ እንዲፀዱ ፣ እንዲናፈሱ የማድረግ ተግባራትን
ያስተባብራል።
ሐ. ሪከርዶችን በፋይል ለመመዝገብ የሚቀጠሩ ሠራተኞች ቢቻል 12 ኛ ክፍል እና በሶሻል ሳይንስ ትምህርታቸውን
ያጠናቀቁ እንዲሆኑ ያደርግሉ፡፡ በምዘናና መረጣ ዙሪያ ገለፃ እንዲሰጣቸውም ያስተባብራል።
ያካሂዳሉ።
3. የሪከርድ መራጭ ኮሚቴ አባላት ወደ ሥራ ከመግባታቸው በፊት በቋሚነት የምዘናና መረጣ ሥራውን ለማከናወን
የሚያስችል መርሃ ግብር መቅረፅ አለባቸው።
4. ከእንቅስቃሴ ውጪ የሆኑ ሪከርዶችን በዚሀ መመሪያ አንቀፅ------ መሠረት በመመዘን በሪከርድ ማዕከል ለተወሰነ ጊዜ
የሚጠበቁትንና ለቋሚ ጥበቃ ወደ ብሔራዊ ቤተመዛግብት የሚዘዋወሩትን እና የሚወገዱትን ይለያሉ።
5. በሪከርዶች የማቆያ እና የማስወገጃ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የተለዩ ርከርዶች ላይ የሪከርድ መራጭ ኮሚቴው ውሳኔ
ይሰጣል።
6. በምዘናና መረጣ ሂደት ያለፉትን ወይም በሪከርዶች የማቆያና የማስወገጃ የጊዜ ሰሌዳ
መሠረት የተለዩ ሪከርዶች ላይ ውሳኔ ያረፈበት ዝርዝር የያዘ 4 ቅጂ በቃለ-ጉባኤ
6
7. የተቋሙ የበላይ ኃላፊም ቃለ-ጉባኤው እንደደረሰው ሪከርዶቹ ከዝውውር ሊስታቸው ጋር
ለባለሥልጣኑ በመላክ የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥበት ያደርጋል።
8. የሚሰሩባቸውን ዶክሜንቶች በአግባቡና በሥርዓት በመያዝ ስለሥራው እንቅስቃሴና ውሳኔ አጠቃላይ ገላጭ ሪፖርት
ማዘጋጀት አለበት።
ክፍል አራት
ስለሪከርዶች ዝውውር
1. በዝገት ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉ እንደ እስፒል ፣ አግራፍ ፣ ፋስትነር የመሳሰሉትን ብረት ነክ ቁሶች
በፕላስቲክ ወይም በሲባጎ ክር የመቀየር፣
2. ለዘለቄታና ለተወሰነ ጊዜ እንዲጠበቁ የተመረጡ ሪከርዶች ያረጁና የተጎዱ ክላሰሮችንና አቃፊዎችን በአዲስ
የመተካት፣
3. ሪከርዶችን በምዝገባ ቅደም ተከተላቸው መሠረት ከባለሥልጣኑ ጋር በሚደረስ ስምምነት ለማጓጓዝ አመቺ
በሆነ ካርቶን ወይም ሳጥን ለእያንዳንዱ ጊዜያዊ መለያ ቁጥር በመስጠት የማዘጋጀት፣
4. የሚዛወሩ ሪከርዶችን ዝርዝር የዝውውር ሊስት በአራት ኮፒ አዘጋጅቶ አንዱን ለመሥሪያ ቤቱ በማስቀረት
ሦስቱን ለባለሥልጣኑ የመላክ፣
5. ሚስጢራዊና ልዩ ጥበቃ ሊደረግላቸው የሚገባ ሪከርዶችን በመለየት ለሕዝብ ክፍት የሚሆኑበትን ጊዜ
የማስቀመጥ ፣ እንዲሁም ወደ ባለሥልጣኑ ሊዛወሩ የሚገባቸው በልዩ ምክንያት ያልተዛወሩ ሪከርዶች ሲኖሩ
የማሳወቅ፣
6. ሪከርዶቹን በጥንቃቄ በሽፍን መኪና አጓጉዞ ለባለሥልጣኑ የማስረከብ ግዴታ አለበት።
7. በዚህ አንቀጽ ከንዑስ አንቀጽ 1 እስከ 6 የተመለከተው እንደተጠበቀ ሆኖ አመንጪ ተቋማት ወደ ባለሥልጣኑ
የተዛወሩ ሪከርዶቻቸውን የመጠቀም ወይም የመዋስ መብት አላቸው።
1. አዋጁ ተፈፃሚ የሚሆንባቸው አመንጪ ተቋማት ዘላቂ ፋይዳ ያላቸውን ሪከርዶች ወደ ባለሥልጣኑ
የሚያዛወሩት ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ከሌለ በቀር በሪከርድ ማዕከል በኩል ይሆናል።
7
2. ከግለሰቦች ወይም ከግል ተቋማት በስጦታ ወይም በሽያጭ መዛግብትን ወደ ባለሥልጣኑ ለማዘዋወር ሲፈለግ
በብሔራዊ መዝገብ የተመዘገቡ ፣ ሀገራዊና ዘላቂ ጠቀሜታ ያላቸው ብቻ ተመርጠው ይሆናል።
3. በአዋጁ አንቀፅ 7 ንዑስ አንቀፅ 10 በተደነገገው መሠረት ወይም ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ከሌለ በቀር
የግለሰብም ሆነ የግል ተቋማት መዛግብት የምዘናና መረጣ ሥራ ሳይከናወን ወደ ባለሥልጣኑ አያዛወሩም።
4. ግለሰቦች ወይም የግል ተቋማት መዛግብታቸውን ለባለሥልጣኑ በስጦታ ለማስተላለፍ ጥያቄ ሲያቀርቡ
የምዘናና መረጣ ውሳኔውን ለመቀበልና ያልተመረጡትን ኃላፊነት በመውሰድ መስማማታቸውን ፣ ከዝውውር
በኋላ የመዛግብቱ ባለቤትነት መብት የማን እንደሚሆን ፣ ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት ሊሆኑና የሚችሉበትን
ሁኔታ በፅሁፍ ግልፅ ማድረግና ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል።
ክፍል አምስት
ስለሪከርዶች አወጋገድ
ማንኛውም መንግስታዊ አካል እንዲወገዱ ውሳኔ የሰጠባቸውን ሪከርዶች ከዚሀ በታች ከተመለከቱት ውስጥ
በአንዱ ሊያስወግድ ይችላል።
ህጋዊነት ያረጋግጣል።
ይኖርበታል።
ይገባል።
መከናወን አለበት።
ሀ. ቃለ-ጉባኤዎች
ክፍል ስድስት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
1. ስለ ሪከርዶች አወጋገድ በተመለከተ በወጣው አዋጅ ፣ ደንብና በዚህ መመሪያ ከተቀመጡ ድንጋጌዎች ውጭ
ሪከርዶችን ማስወገድ አይችልም።
2. እንዲወገድ የተወሰነበትን ሪከርድ በማናቸውም ሁኔታ ለሦስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠትም ሆነ ጥቅም ላይ
ማዋል አይችልም።
9
3. በዚህ መመሪያ ውስጥ ለማስወገድ ከተመረጡት ዘዴዎች ውጪ ሪከርዶችን ማስወገድ አይችልም።
1. ባለሥልጣኑ በመዛግብትነት የተረከባቸውን ሪከርዶች የመዛግብትነት ፋይዳ የላቸውም ብሎ ሲያምን አመንጪ ተቋማትን
በማሳተፍ ዳግም መረጣ ሊያከናውን ይችላል፡፡
2.
አብርሃም ጮሻ
10
የብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻህፍት ባለስልጣን
ዋና ዳይሬክተር
11