You are on page 1of 52

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአነስተኛ አና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ኮርፖሬሽን

ንብረት አስተዳደር

መመሪያ ቁጥር …../2009

አዲስ አበባ
ሐምሌ/2009

1. ክፍል አንድ

1.1 ጠቅላላ

0
1.1.1 አውጪው ባለስልጣን

የኮርፖሬሽኑ ቦርድ በደንብ ቁጥር 83/2009 የተደነገጉትን ለማስፈፀም ይህን መመሪያ አውጥቷል፡፡

1.1.2 አጭር ርዕስ

ይህ መመሪያ የኮርፖሬሽኑ ንብረት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር /2009 ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡

1.1.3 ትርጓሜ

የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ ያሉ ቃላትና ሐረጎች
የሚከተሉት ትርጉም ይይዛል፡፡

1. “ቋሚ ንብረት” ማለት ዋጋቸው ከብር 1000.00 /አንድ ሺህ/ እና ከዚያ በላይ የሆኑ ንብረቶች እና
ከአንድ ዓመት በላይ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ናቸው፡፡
2. “አላቂ እቃ” ማለት የተናጠል ዋጋው ከብር 1000.00 /አንድ ሺህ/ በታች የሆነ ወይም የአገልግሎት
ዘመናቸው ከአንድ አመት በታች የሆነ ንብረት ነው፡፡
3. “ተሽከርካሪ” ማለት በመንገድ ላይ በሞተር ኃይል የሚንቀሳቀስ ወይም የሚጐተት ለሰው እና/ወይም
ለዕቃ ማጓጓዣ የሚውል ማንኛውም ተሽከርካሪ ነው፣
4. “የእርጅና ቅናሽ” ማለት ንብረቱ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ይሰጣል ተብሎ በሚገመትበት ዕድሜ ስርዓት
ባለው አኳኋን የንብረቱን ዋጋ እንደወጪ እያሰቡ መቀነስ ማለት ነው፡፡
5. “ስቶክ” ማለት በኮርፖሬሽኑ የተመረቱ ወይም የተገዙ በእርዳታ የተገኙ ንብረቶች ሆነው በመደበኛ
የስራ እንቅስቃሴ ውስጥ አገልግሎት ላይ እስከሚውሉ ድረስ በመጋዘን የተቀመጡ ቋሚ ዕቃዎች፣
መሣሪያዎችና አላቂ እቃዎች ማለት ነው፡፡ ሆኖም አገልግሎት ላይ ውለው የሚመለሱ ዕቃዎችን
አይመለከትም፡፡
6. “ኤጀንሲ” ማለት የከተማ አስተዳሩ የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ ነው፡፡

1.1.4 የመመሪያው ተፈፃሚነት ወሰን

ይህ መመሪያ ኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት እና ጽ/ቤት ተብለው በተመለከቱት ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡

1.1.5 የመመሪያው ዓላማ

1
ዘመናዊ፣ ቆጣቢ፤ ለሀብት በቂ ጥበቃ የሚያደርግና ውጤታማ የንብረት አስተዳደር ስርዓት በማስፈን፣
ኮርፖሬሽኑ በእጁ ያለውን ንብረት በጥንቃቄ የመያዝ፣ የመጠቀም፣በሂሳብ መዛግብት የመመዝገብ፤
የመቆጣጠር እና አገልግሎት ሲያበቃ ወይም አገልግሎት ላይ በማይውሉበት ጊዜ በወቅቱና በተገቢው መንገድ
እንዲያስወግድ ማስቻል ነው፡፡

ክፍል ሁለት

2.1. ስልጣንና ኃላፊነት

2.1.1. የኮርፖሬስኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ተግባርና ኃላፊነቶች

ሀ. ለንብረት ሥራ የሚመደቡ ሠራተኞች ቢቻል በሙያው ወይም ተዛማጅነት ባለው የትምህርት ዘርፍ
የሠለጠኑ መሆናቸውን ማረጋገጥ፣

ለ. ለንብረት የሥራ ክፍል በሰው ኃይልና አደረጃጀት ትኩረት መስጠት፣

ሐ. የኮርፖሬሽኑ ንብረት ኢኮኖሚያዊና ውጤታማ አገልግሎት እንዲሰጥ ከስራ ክፍሉ ጋር በመሆን የጥገና
ሥርዓት መዘርጋት፣

መ. ኮርፖሬሽኑ ንብረት ላይ ጉድለት መታየቱ በኦዲተሮች ወይም በሌላ አካል ሲረጋገጥ ንብረቱ በምርመራው
መሠረት በአይነት ወይም በገንዘብ እንዲተካ ማድረግ፣

ሠ. ዓመታዊ እና እንደአስፈላጊነቱ ድንገተኛ የንብረት ቆጠራ እና የስቶክ ምርመራ እንደ ንብረቱ አይነት የጊዜ
ገደብ በማስቀመጥ እንዲካሄድና ሪፖርት እንዲቀርብ ማድረግ፣

ረ. ኮርፖሬሽኑ ንብረት ነሽያጭ ሲያስወግድ በንብረት ሽያጭ አፈፃፀም ሂደት ቅር የተሰኘ ገዢ


የሚያቀርበውን አቤቱታ በማጣራት በጽሑፍ ምላሽ መስጠት፣

ሰ. በዚህ መመሪያ የተገለፁትን ሌሎች ተግባሮች መፈፀም በበላይነት መከታተልና ማስፈፀም፣

2.1.2. የዳሬክቶሬቱ ኃላፊነት

ሀ. በኮርፖሬሽኑ ኃላፊነት ስር የሚገኙ ቋሚ ንብረቶችን ከተገዙበት ጊዜ ጀምሮ ያሉ መረጃዎችን ለእያንዳንዱ


ንብረት የታሪክ ማህደር በመክፈት በትክክልና በተሟላ ሁኔታ በሚያዘጋጀው ቅጽ መሠረት ወይም
የኤሌክትሮኒክስ መረጃ ሥርዓት በመጠቀም መዝግቦ መያዝ አለበት፡፡

ለ. ኮርፖሬሽኑ የንብረት አስተዳደር ተግባርን የሚያከናውን የሥራ ክፍል የተጠናቀረ መረጃ የያዘ የቋሚ ንብረት
መመዝገቢያ ካርድና መዝገብ መያዙን የመከታተልና የመቆጣጠር ኃላፊነት መወጣቱን ማረጋገጥ አለበት፡፡

2
ሐ. በኮርፖሬሽኑ የንብረቱ ተጠቃሚ ሰዎችን የንብረት ምዝገባ ካርድ መያዝ ማረጋገጥ አለበት፡፡

መ. ኮርፖሬሽኑ ለእያንዳንዱ ቋሚ ንብረት የራሱ የሆነ መለያ ቁጥር መስጠት ያለበት ሲሆን፣ ይህ ቁጥር በቋሚ
ንብረቱ ላይ መለጠፍ ወይም መጻፍ ማከታተል አለበት፡፡

ሠ. የንብረት አስተዳደር ተግባርን የሚያከናውነው የሥራ ክፍል የቋሚ ንብረት ካርዶችና የቋሚ ንብረት
መዝገቦች ወቅታዊ መደረጋቸውን ማረጋገጥ አለበት፡፡

ረ. ኮርፖሬሽኑ በየዓመቱ የቋሚ ንብረቶች ቆጠራ ማካሄድ አለበት፡፡ ቋሚ ንብረቶቹ ያሉበት አቋም ወይም
የሚገኙበት ቦታ ላይ ማናቸውም ለውጥ ቢኖር ይኸው በቋሚ ንብረት ካርዱ፣ በቋሚ ንብረቱ መዝገብ
እና በጠባቂዎች የንብረት ወይም የመጋዘን ኃላፊ ዝርዝር ውስጥ እንዲመላከት መደረጉን መከታተል
አለበት፡፡

ሰ. በኮርፖሬሽኑ የማናቸውም ንብረት መጥፋት ወይም መኖሩ የማይታወቅ ሆኖ ሲገኝ ጉዳዩ ለዋና ስራ
አስኪያጁ ሪፖርት ተደርጎ ወዲያውኑ ምርመራ መካሄዱን ማረጋገጥ አለበት፡፡

ሸ. የንብረት ቆጠራ ሲደረግ ያልተገኙ ወይም መኖራቸው ያልታወቁ ቋሚ ንብረቶች ሲያጋጥሙ ለኮርፖሬሽኑ
ዋና ስራ አስኪያጅ ሪፖርት ያቀርባል፡፡ በምርመራውም ሪፖርት ጉዳይ የወንጀል ድርጊት ያለው መሆኑ
በማስረጃ ሲደገፍ ለኮርፖሬሽኑ የሕግ ተግባርን ለሚከታተል የሥራ ክፍል ሪፖርት ያደረጋል፡፡

ቀ. ዋጋቸው ከብር 1000.00 /አንድ ሺህ/ በታች ሆነው የአገልግሎት ዘመናቸው ከአንድ አመት በላይ የሆኑ
ንብረቶች ለብክነት ሊዳርጉ ስለሚችሉ ለብቻ ተመዝግበው በመያዝ የወጪና ገቢ እንቅስቃሴያቸው
ቁጥጥር እንዲኖር ያደረጋል፡፡

በ. ቋሚ ንብረት ለአንድ የሥራ ክፍል ወይም ሠራተኛ ወጪ ሆኖ ከተሰጠ በኋላ ወደ መጋዘን ሣይመለስ
በዚያው ወደ ሌላ ሠራተኛ ወይም የሥራ ክፍል በርክክብ እንዲተላለፍ ያዛል የንብረት እንቅስቃሴና
አጠቃቀምን ይወስናል የቋሚ ንብረቱ መዝገብና ካርድ ከዚህ አኳያ መስተካከሉን ማረጋገጥ አለበት፡፡

2.1.3. የንብረት የሥራ ክፍል ተግባርና ኃላፊነት

ሀ. ይህንን መመሪያ እንዲሁም የንብረት አስተዳዳር ማንዋሎችን መሠረት በማድረግ ሙያው በሚጠይቀው
ክህሎት የኮርፖሬሽኑን ንብረት ያስተዳድራል፣

ለ. የኮርፖሬሽኑ ንብረት መረጃ በመመሪያው በተደነገገው መሠረት አሟልቶ ይይዛል፣ በተጠየቀም ጊዜ


ያቀርባል፡፡

2.1.4. የኮርፖሬሽኑ ንብረቶች አወቃቀር፣ ተግባርና ኃላፊነት

3
በዚህ መመሪያ መሠረት የሚቋቋመው የንብረት አስወጋጅ/ሽያጭ ኮሚቴ፡-

1. አወቃቀርና የስብሰባ ሥርዓት


ሀ. ኮሚቴው ከሶስት ያላነሱ አባላት ይኖሩታል፡፡
ለ. የኮሚቴው አስተባባሪ፣ አባላትና ፀሐፊ በኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ይሰየማሉ፡፡
ሐ. በኮሚቴው ስብሰባ ላይ ሰብሳቢውን ጨምሮ ከግማሽ በላይ አባላት ከተገኘ ምልአተ ጉባኤ
ይሆናል፡፡
መ. የኮሚቴው ውሣኔ በድምጽ ብልጫ ይወሰናል፡፡ የኮሚቴው ድምጽ እኩል ሲሆን ሰብሳቢው
ያለበት ወገን ወሣኝ ድምጽ ይኖረዋል፡፡

ሠ. የኮሚቴው የአገልግሎት ዘመን ሁለት አመት ይሆናል፡፡ ሆኖም የኮርፖሬሽኑ የበላይ ኃላፊ አስፈላጊ
ሆኖ ሲያገኘው የኮሚቴውን የአገልግሎት ዘመን ለሁለተኛ ጊዜ ማራዘም ይችላል፡፡

2.1.5. አስወጋጅ/ሽያጭ ኮሚቴ ተግባርና ኃላፊነት፡-

ሀ. እንዲወገዱ ለተጠየቁ የኮርፖሬሽኑ ንብረቶች የሚያስፈልጉ የማስወገጃ መጠይቆች፣ መረጃዎችና ሰነዶች


ተሟልተው እንዲቀርቡ ያደርጋል፣ ያረጋግጣል፣
ለ. በኮርፖሬሽኑ የተገለጹትን የማስወገጃ መመዘኛዎችና የማስወገጃ ዘዴዎች መሠረት የቀረቡ ሰነዶችን
ይገመግማል፣
ሐ. እንዲወገዱ ጥያቄ የቀረበባቸው የኮርፖሬሽኑ ንብረቶች ባሉበት ቦታ በመገኘት ለውሳኔ የሚረዱ
ግምገማዎችን ያደርጋል፡፡
መ. በዚህ ንዑስ አንቀጽ ከሀ-ሐ በተገለጹት ግምገማዎች ላይ በመመሥረት የውሳኔ ሀሳብ ለኮርፖሬሽኑ የበላይ
ኃላፊ ይቀርባል፣
ሠ. እንዲሸጡ ውሳኔ የተሰጠባቸው የኮርፖሬሽኑ ንብረቶች የጨረታ መነሻ ዋጋ ያወጣል፣ በጨረታ ሰነድ ላይ
እንዲገለጽ ያደርጋል፣
ረ. የጨረታ ሰነድ ያዘጋጃል፣
ሰ. ማስታወቂያ ያወጣል፣ ጨረታ ይከፍታል፣ ያጫርታል፣ የጨረታውንም ውጤት ለንብረት ሽያጭ አጽዳቂ
ኮሚቴ ለኮርፖሬሽኑ የበላይ ኃላፊ ሪፖርት ያቀርባል፡፡

2.1.6. የንብረት ሽያጭ አጽዳቂው ኮሚቴ

የንብረት ሽያጭ አጽዳዊ ኮማቴ በኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስኪያጅ የሚቋቋም አምስት አባላት ያሉት ኮሚቴ ሲሆን
የሚከተሉት ተግባርና ኃላፊነት ይኖሩታል፡፡

1. የንብረት ሽያጭ ጨረታ አፈጻጸም ይህንን መመሪያ የተከተለ መሆኑን ያረጋግጣል፣


2. የንብረት ሽያጭ ጨረታ ውጤት መርምሮ ያፀድቃል፡፡

4
ክፍል ሦስት

3. የቋሚ ንብረት አመዘጋገብ


3.1. የቋሚ ንብረቶች መነሻ ዋጋ ወስኖ ስለመመዝገብ

3.1.1. የቋሚ ንብረቶች ዋጋ አተማመን

ሀ. የተገዙ ንብረቶች የመጀመሪያ ዋጋ የሚረጋገጠው በንብረት ካርዱ ላይ የተመዘገበውን የኢንቮይስ ዋጋ


መሰረት በማድረግ ነው፡፡

ለ. ያለፉት ግዥዎች ዋና ኢንቮይስ በማይገኝበት ጊዜ ኮርፖሬሽኑ የመጀመሪያውን ዋጋ የሚገምተው


ተመሣሣይ ወይም አንድ አይነት ንብረቶች በተመሳሳይ ጊዜ የተገዙበትን ዋና ኢንቮይስ መሠረት
በማድረግ ይሆናል፡፡

ሐ. ከላይ በተራ ቁጥር ሀ ወይም ለ የተጠቀሱት ሁኔታዎች ተሟልተው ካልተገኙ ዋጋው በግምት ተተምኖ
ይሰራል፡፡

3.1.2. ግንባታዎች፣

ኮርፖሬሽኑ ያከናወኑዋቸውን ወይም የተረከባቸውን የግንባታ ሥራዎች እንደ ቋሚ ንብረቶች በተለየ መዝገብ
መመዝገብ አለበት፡፡

5
ሀ. ኮርፖሬሽኑ ህንጻዎችን ለመስራት የተደረገን የቅድመ ግንባታ ቀጥተኛ ያልሆኑ ወጪዎች እና
የአስተዳደር ምክር አገልግሎት እና የመሣሰሉትን ቀጥተኛ ያልሆኑ ወጪዎችን በቋሚ ንብረት ካርድ
መመዝገብ አለበት፡፡

ለ. በግንባታ ላይ የሚገኙ ሥራዎች የሚተመኑት የተጠናቀቁትን ሥራዎች የመተመኛ ስሌት ግምታዊ


ዋጋ መሠረት በማድረግ ይሆናል፡፡

ሐ. ለሕንፃው የእርጅና ቅናሽ የሚታሰበው ሕንጻውን ለመሥራት ወይም ለመግዛት የተደረገውን ጠቅላላ
ወጪ በመነሻነት በመውሰድ ከዚሁ ሂሣብ ላይ በየዓመቱ አምስት በመቶ በመቀነስ ይሆናል፡፡
ሕንጻውን ለመሥራት ወይም ለመግዛት የተደረገው ጠቅላላ ወጪ የማይታወቅ ከሆነ የሕንጻው
ወቅታዊ የመተኪያ ዋጋ እንደመነሻ ይወስዳል፡፡

መ. ኮርፖሬሽኑ እንደቅደም ተከተላቸው የሚከተሉት ዘዴዎችን በመጠቀም የሕንፃውን ዋጋ መተመን


ይቻላል፡፡

I. የግልጽ ገበያ አተማመን ዘዴ፡- ሕንጸው በግልጽ ጨረታ ቢሸጥ የሚኖረውን የገበያ ዋጋ
መሠረት በማድረግ የሕንጻ ዋጋ ላይ መድረስ፡
II. የወቅቱ የመተኪያ ዋጋ ዘዴ፡- የሕንጻው ትክክለኛ ዋጋ የማይታወቅ ከሆነ በአሁኑ ጊዜ

የተመሣሣይ ሕንጻ አጠቃላይ የግንባታ የመተኪያ ወጪ ግምት ውስጥ በማስገባት

መገመት ይቻላል፡፡ ይህ ማለት ተመሣሣይ ሕንጻ በተመሣሣይ አካባቢና በተመሣሣይ

ዕቃዎች አሁን ለመስራት ምን ያህል ወጪ እንደሚጠይቅ በማሰብ መከናወን ይኖርበታል፡፡

III. ጉዳዩ የሚመለከተውን የመንግስት መስሪያ ቤት በየጊዜው የሚያዘጋጀውን ግምታዊ

ደረጃና የካሬ ዋጋ ማውጣት ወጪን መሠረት ባደረገ መስፈርት ተጠቅሞ የሕንጻዎቹን

ዋጋ ማውጣት ይቻላል፡፡

IV. ግምት ለሚሰሩ ባለሙያዎች ኮንትራት በመስጠት የሕንጻውን ዋጋ ማስላት ይቻላል፡፡

3.1.3. የሌሎች ቋሚ ንብረቶች ዋጋ ስለመገመት፣

ሀ. የተሽከርካሪዎች ዋጋ የሚተመነው አዲስ የመተኪያ ዋጋን መነሻ በማድረግ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ትብብር
ሚኒስቴር ያዘጋጀውንና በየዓመቱ አስር በመቶ የዋጋ ቅናሽ በማድረግ የማስላት ዘዴን በመጠቀም
ይሆናል፡፡

ለ. የቢሮ ዕቃዎች ዋጋ የሚተመነው ዕቃዎቹ ያሉበትን አቋም መሠረት ባደረገ መስፈርት ይሆናል፡፡

6
ሐ. የቢሮ መሣሪያዎች ዋጋ የሚተመነው የመሣሪያዎቹን የአገልግሎት ዘመን በመስፈርትነት በመውሰድ ሲሆን
ስሌቱ በየዓመቱ መሣሪያዎቹን አስር በመቶ የዋጋ ቅናሽ በማድረግ የሚሰላ ይሆናል፡፡

መ. የማይንቀሳቀሱ ወይም ሙሉ በሙሉ የተበላሹ ቋሚ ንብረቶች በመዝገብ ዋጋቸው (Book value) አስር
ብር ሆኖ ይመዘገባሉ፡፡

3.1.4. በትወስት ወይም በስጦታ የተገኙ ንብረቶች

3.1.4.1. የኮርፖሬሽኑ በስጦታ የሚያገኛቸውን ንብረቶች ዋጋ እና የአገልግሎት ዘመናቸውን የሚገልጽ


መረጃ ከለጋሾች ወይም ከሰጡት አካላት ለማግኘት ጥረት ማድረግ ይኖርበታል እንዲሁም
በቋሚ ንብረት መመዝገቢያ ካርዱ ላይ መመርገብና ማመልከት አለበት፡፡ መረጃው ካልተገኘ
በዚህ መመሪያ አግባብ በግምት ዋጋው መመዝገብ ይኖርበታል፡፡
3.1.4.2. በትውስት የተገኙ ንብረቶች ዋጋ እና የአገልግሎት ዘመናቸውን ከአዋሾች የተገኘውን መረጃ
መሠረት በማድረግ ከኮርፖሬሽኑ የቋሚ ንብረቶች መዝገብ በተለየ የንብረት መመዝገቢያ
ካርድ ላይ መመዝገብ አለበት፡፡ መረጃው ከአዋሾች ካልተገኘ በዚህ መመሪያ መሠረት ተፈጻሚ
ይሆናል፡፡
3.2. የቋሚ ንብረት የእርጅና ቅናሽ

በኮርፖሬሽኑ ቋሚ ንብረት ላይ የእርጅና ቅናሽ ማስላት ያስፈለገው በሀገሪቱ የገቢ ግብር ህግ እንደ
ልማት ድርጅት የሚጠበቅበትን የታስና ግብር ግዴታ ለመወጣት ሆኖ የንብረቱን ትክክለኛ ዋጋ
ለመወሰን ሣይሆን አግባብነት ካለውና ሚዛናዊ ከሆነ የሀብት ሚዛን /ዋጋ/ ላይ ለመድረስም
ጭምር ነው፡፡ የቋሚ ንብረቱ ትክከለኛ ዋጋ የሚታወቀው ሲሸጥ በሚገኝ የገበያ ዋጋ ብቻ
ይሆናል፡፡ ስለሆነም፡-

ሀ. ንብረት መዝገብ ላይ ያለ የእርጅና ቅናሽ ዋጋ ንብረትን ለማስወገድ መነሻ ግምት ሆኖ ሊወሰድ


አይችልም፣

ለ. ኮርፖሬሽኑ በየዓመቱ መጨረሻ ላይ የቋሚ ንብረት የእርጅና ቅናሽን በማስላት የንብረቱን


የመዝገብ ዋጋ መመዝገብ ይኖርበታል፡፡

ሐ. የእርጅና ቅናሽ የሚሰራው በሀገሪቱ የታክስና ግብር ህግ መሰረት ሆኖ ቀጥተኛ የእርጅና ቅናሽ
ዘዴን በመጠቀም ይሆናል፡፡ ሆኖም ከዚህ የተለየ ዘዴ መጠቀም ካስፈለገ ለቦርዱ ቀርቦ በሚሰጥ
መመሪያ መሠረት ተግባራዊ ይደረጋል፡፡
7
መ. የቋሚ ንብረት የእርጅና ቅናሽን የማስላትና በመዝገብ ላይ የመመዝገብ ኃላፊነት
የኮርፖሬሽኑ ጠቅላላ ሒሣብ እና የንብረት አስተዳደር ተግባርን የሚያከናውን የሥራ ክፍል
ይሆናል፣

ሠ. ለቋሚ ንብረቶች የእርጅና ቅናሽ የሚሰላው ንብረቱ አገልግሎት መስጠት ከጀመረበት ዕለት
አንስቶ ይሆናል፡፡

ረ. የኮርፖሬሽኑ የቋሚ ንብረት የእርጅና ቅናሽ (Depreciation) አሠራር ሥርዓት ዝርጋታ


በኮርፖሬሽኑ የፋይናንስ ተግባርን የሚያከናውነው የሥራ ክፍል የቋሚ ንብረት የእርጅና ቅናሽ
ዋጋ ሲደርሰው ሂሣቡን በሂሣብ መዝገብ ላይ ይመዘግባል፡፡

ሰ. በቋሚ ንብረቱ የመጨረሻ የእርጅና ቅናሽ ዘመን ከዓመቱ የእርጅና ቅናሽ ላይ ብር 10 /አስር/
ተቀንሶ የንብረቱ የመዝገብ ዋጋ እንዲሆን ይደረጋል፡፡

ሸ. ዋጋውን በእርጅና ቅናሽ ላይ ለጨረሰ ንብረት የእርጅና ቅናሽ አይታሰብም፡፡

ቀ. ዋጋውን በእርጅና ቅናሽ የጨረሰ ንብረት የጥገና ወጪ የዚያ ዓመት ወጪ እንጂ የንብረቱ ዋጋ
ተደርጎ አይወሰድም፡፡

8
ክፍል አራት
4. የስቶክ አስተዳደር ሥርዓት

4.1. የስቶክ ቁጥጥር ሥርዓቶች

4.1.1. የስቶክ ቁጥጥር ሥርዓት በኮርፖሬሽኑ መዘርጋት ያለበት ሲሆን በስቶክ የሚቀመጡ ዕቃዎች ለጤና
አደገኞች ወይም ባላቸው ዋጋና በቀላሉ የመንቀሳቀስ ባህርይ ምክንያት ለሥርቆት የሚጋለጡ ናቸው
ተብሎ ሲታመን ልዩ ቁጥጥር ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
4.1.2. በኮርፖሬሽኑ የሚደረገው የስቶክ ቁጥጥር ሥርዓት የሚከተሉትን የስቶክ ቁጥጥር ሥርዓት መሠረታዊ

መርሆዎች ያገናዘበ መሆን አለበት፡-


ሀ. የስቶክ ቁጥጥር አስተማማኝ፣ ተገቢና መሠረታዊ የስቶክ መዛግብቶችን መሠረት
ያደረገ መሆን አለበት፡፡ እነዚህ የስቶክ መዛግብት በተለምዶ የስቶክ ካርዶች እና ቢን
ካርዶች ስራላይ መዋል ይገባቸዋል፡፡
ለ. የዕቃዎች መቀበያ፤ ከመጋዘን ወደ መጋዘን ማስተላለፊያና ማውጫ ሰነዶች የሚገኙበት
መንገድ ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግባቸው ሆነው አስቀድመው የታተሙና ተከታታይ
ቁጥሮች ያሉዋቸው መሆን አለባቸው፡፡

ሐ.ከዚህ በላይ የተመለከቱት ቫውቸሮች ንብረት ገቢ ወይም ወጪ ከተደረገባቸው በኋላ


በተቻለ ፍጥነት በዋናው የስቶክ መዛግብቶች ላይ ማሻሻያ መደረግ አለበት፡፡

መ. የንብረት መጉደል ወይም መጭበርበር ተከስቷል የሚል ጥርጣሬ ሲኖር ንብረቱ


ከመቀበል ጀምሮ ማውጣትን፣ ጥቅም ላይ ማዋልንና አግባብ ያለው ሆኖ ሲገኝ እስከ
ማስወገድ ድረስ ያለውን እንቅስቃሴ ወደ ኋላ ሄዶ የታተሙት ሰነዶች ቁጥራቸው
ተከታታይና ይዘታቸው ያልተደለዘ ወይም ለውጥ ያልተደረገባቸው መሆኑ መረጋገጥ
አለበት፡፡

4.2. የስቶክ አስተዳደር

ኮርፖሬሽኑ ከዚህ በታች በተጠቀሱት ሁለት የሥራ መደቦች ላይ በሚገኙ ሠራተኞች መካከል በቂ የኃላፊነት
መነጣጠል መደረጉን ማረጋገጥ አለባቸው፡፡

ሀ. የስቶክ መዛግብቶች የመያዝና ስቶክ የመረከብ እንዲሁም ወጪ የማድረግ ኃላፊነቶች


ለአንድ ሠራተኛ መሰጠት የለባቸውም፡፡

9
ለ. በተመሳሳይ ስቶክ የመያዝ፣ የመረከብ፣ ክፍያን የመፍቀድና ግዥን የማከናወን ኃላፊነቶች
መለያየት አለባቸው፡፡
4.3. መሠረታዊ የስቶክ መዛግብቶች
1. የኮርፖሬሽኑ ንብረት አስተዳደር ሥራ ክፍል በተዘጋጁት ቅጾች መሠረት የስቶክ መረጃዎችን
መያዝ አለባቸው፣
2. የኮርፖሬሽኑ ንብረት አስተዳደር ሥራ ክፍል የዚህን መመሪያ ድንጋጌዎች በማይጻረር መንገድ
በሚዘጋጅ የኤሌክትሮኒክስ ዘዴ የስቶክ መረጃን መያዝና ማስተዳደር ይችላሉ፣
3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ የንብረት አስተዳደር ክፍል
የስቶክ መረጃቸውን በተለየ ሁኔታ ለመያዝ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኙት ለኮርፖሬሽኑ
ማኔጅመንት ጥያቄ በማቅረብ ሲፈቀድ መረጃውን በተለየ ፎርም መዝግበው መያዝ
ይችላሉ፡፡
4.4. ስቶክ ስለመቀበል
ኮርፖሬሽኑ አዲስ ስቶክ ሲቀበል በሚከተሉት ላይ ተገቢውን ማጣራት ማድረግ ይኖርበታል፡፡
ሀ. የዕቃ ግምጃ ቤት ኃላፊው ዕቃውን ለመረከብ የሚያስችል ከሚመለከተው የሥራ ክፍል
የተሰጠ ትዕዛዝ መኖሩን፣
ለ. የዕቃ ግምጃ ቤት ኃላፊው የዕቃውን ትክክለኛነት ከተሰጠው ትዕዛዝ የዕቃ ዝርዝር
(Specification) ጋር በማመሳከር ወይም ባለሙያ የሚፈልግ ከሆነም በባለሙያ
ስለትክክለኛነቱ ማረጋገጫ ማግኘት፣
ሐ. ስቶኩ የተገኘው ከኮርፖሬሽኑ ውስጥ ከሚገኙ ሌሎች የሥራ ክፍሎች ወይም ስቶኩን
ከሚመልሱ የኮርፖሬሽኑ አባላት ሲሆን የተገኘው ስቶክ ወጪ ከተደረገበት በሌላ
የኮርፖሬሽኑ የሥራ ክፍል ከተዘጋጀው የንብረት ወጪ ማድረጊያ ሰነድ ጋር ማመሳከር፣
መ. የስቶክ አስተዳደር ተግባርን የሚያከናውን የሥራ ክፍል ኃላፊ ከማናቸውም ምንጭ
ንብረት ሲገኝ የስቶኩን መዝገብ ንብረቱን በተቀበለበት ዕለት የማስተካከል፣

4.5. ከመጋዘን ስቶክን የማውጣት ሥርዓት


ስቶክ ከመጋዘን የሚወጣው መጀመሪያ የገባው መጀመሪያ ይወጣል የሚለውን የሂሳብ አሰራር
መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ሆኖም ከዚህ የተለየ ዘዴ መጠቀም ግዴታ ከሆነ ቦርዱን አስታውቆ
መጠቀም ይቻላል፡፡

10
ሀ. የስቶክ አስተዳደር ተግባራትን የሚያከናውን የሥራ ክፍል ኃላፊ ስቶክ ከመጋዘን ሲወጣ
በዋናው የስቶክ መዝገብ ላይ ተገቢውን ማቀናነሻ መደረጉን ለእያንዳንዱ ሠራተኛ
የስቶክ ዝርዝር ተመዝግቦ መያዙን ማረጋገጥ አለበት፡፡
ለ. የስቶክ ወጪ መጠየቂያ ተጠቃማ የሥራ ክፍሎች ወይም ሠራተኞች ለስራ
የሚያስፈልጋቸውን ንብረት በሚፈልጉበት ወቅት የዕቃ መጠየቂያ ቅጽ በተገቢው ሁኔታ
በመሙላትና በሚመለከተው ኃላፊ በማስፈረም የስቶክ አስተዳደር ተግባርን
ለሚያከናውን የሥራ ክፍል ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
ሐ. የስቶክ ወጪ ጥያቄን በማረጋገጥ የስቶክ ንብረት የሚያስተዳድረው የሥራ ክፍል
የተጠየቁት ዕቃዎች በመጋዘን ውስጥ ያሉ መሆናቸውን በማጣራት ለኃላፊው በማቅረብ
ያስወስናል፡፡
መ. የተጠየቀ የስቶክ ዕቃን ወይም ንብረትን ለመረከብ/ወጪ ለማድረግ የተጠየቀው ዕቃ ወይም
ንብረት በንብረት መረከቢያ ቅጽ ላይ በተገቢው ሁኔታ ተሞልቶ በተረካቢው ተረጋግጦ ወጪ
መደረግ አለበት፡፡
ሠ. ንብረት ከመጋዘን ወጥቶ ከኮርፖሬሽኑ ውጪ ሲሰራጭ ወይም ሲወገድ ወይም ሲሸጥ
የንብረት አስተዳደር ተግባርን በሚያከናውን የሥራ ክፍል ኃላፊ በተረጋገጠ የዕቃ ማውጫ
ቅጽ መሠረት ወይም የኤሌክትሮኒክስ የመረጃ ሥርዓት በመጠቀም በተረጋገጠው መሠረት
መሆን አለበት፡፡

4.6. የስቶክ ቆጠራ አፈጻጸም


1. ስቶክ ቆጠራ መደረግ ያለበት ከመጋዘን ወይም ከስቶክ መዛግብት ሥራ ገለልተኛ በሆኑ
ሰራተኞች ነው፡፡ የስቶክ ቆጠራው የሚደረገው የንብረትና የፋይናንስ ተግባራትን
ከሚያከናውኑ የሥራ ክፍሎች በሚቋቋም ኮሚቴ ይሆናል፡፡
2. የስቶክ ቆጠራ ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መካሄድ አለበት፡፡ ሆኖም ኮርፖሬሽኑ የስርቆት
ሪፖርት ሲቀርብለት ወይም አዲስ ሠራተኞች ሲመደቡ እና በአመት ከአንድ ጊዜ በላይ ስቶክ
ቆጠራው መካሄድ አለበት ብሎ ሲያምን ቆጠራ ከአንድ ጊዜ በላይ ሊያካሂድ ይችላል፡፡
3. የስቶክ አስተዳደር ተግባራትን የሚያከናውን የሥራ ክፍል ኃላፊ የኮሚቴው አባል ባይሆንም
የስቶክ ቆጠራ ሥራን ለማቀላጠፍ መገኘት አለበት፡፡
4. ኮሚቴው ቆጠራውን ለማካሄድ እንዲችል የሚረዱ የተሟሉ ሁኔታዎች መኖራቸውን
የንብረት አስተዳደር ተግባራትን የሚያከናውን የሥራ ክፍል ኃላፊ ማረጋገጥ አለበት፡፡
5. ከቆጠራ በኋላና በየእለቱ ስለተቆጠረው ዕቃ ወይም ንብረት ካስቆጣሪው ጋር የመተማመኛ
ፊርማ መፈራረም ያስፈልጋል፡፡

4.7. በስቶክ ቆጠራ ሪፖርት ስለማቅረብና በተገኙ ልዩነቶች ላይ ምርመራ ስለማካሄድ


11
1. የስቶክ ቆጠራውን የሚያካሂደው ኮሚቴ የቆጠራውን ዝርዝር ሪፖርት ንብረት አስተዳደር
ተግባራትን ለሚያከናውን የሥራ ክፍል ኃላፊ ማቅረብ አለበት፡፡
2. የስቶክ ቆጠራው ሪፖርት በስቶክ መዝገቡ፣ በዕቃዎች መቀበያ ሰነድ፣ በስቶክ መጠየቂያና
በስቶክ ማውጫ ሰነድ እና በትክክለኛው ቀሪ ስቶክ መካከል የታዩትን ማናቸውም ልዩነቶች
በዝርዝር መግለፅ አለበት፡፡ ልዩነቶች ከታዩም በዚህ መመሪያ መሠረት ንብረቱ እንዲተካ
ይደረጋል፡፡
4.8. የተለዩ ዕቃዎችን ስለመቆጣጠር
1. በመጋዘን የተቀመጡ አንዳንድ ዕቃዎች በጠቅላላ ለሕዝብ ጤና አደገኛ የሆኑ ወይም ጉዳትን
የሚያስከትሉ የጦር መሳሪያዎች፣ መድሐኒቶች፣ ኬሚካሎች እና የመሳሰሉት ካላቸው ልዩ
ተፈጥሮ የተነሳ ቢበዛ በየ 3 /ሶስት/ ወሩ መቆጠር አለባቸው፡፡
2. ውድ ዋጋ ያላቸው በቀላሉ ሊወሰዱ የሚችሉ ዕቃዎች እና በፍጥነት አገልግሎት ላይ የሚውሉ
ዕቃዎች ድንገተኛ ቆጠራ ሊደረግባቸው ይገባል፡፡
3. በኮርፖሬሽኑ የበላይ ኃላፊ በተጨማሪ በዓመት ሶስት ወይም አራት ጊዜ በየጊዜው የልዩ
ዕቃዎች ድንገተኛ ቆጠራ እንዲደረግ ሊያዝ ይችላል፡፡
4. ከኮርፖሬሽኑ የበላይ ኃላፊ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ይህንን ኃላፊነት ለሌላ አግባብ ላለው
የመንግስት ሠራተኛ በውክልና ሊሰጥ ይችላል፡፡
4.9. የስቶክ መጠንን ስለመቆጣጠር
የስቶክ አስተዳደር ተግባራትን የሚያከናውን የሥራ ክፍል በየጊዜው የሚያስፈልጉ ስቶኮችን
በበቂ መጠን መያዝ ይኖርበታል፡፡ ምን ያህል የስቶክ መጠን እንደሚያስፈልግ ለመወሰን
ለመደበኛ ሥራ ማስፈፀሚያ የሚያስፈልጉ የስቶክ ፍላጎቶችን፣ የታዘዙ ዕቃዎች መጋዘን
ለመድረስ የሚፈጅባቸውን ጊዜ፣ የመጋዘኑ የመያዝ አቅም እና የግዥ ትዕዛዙን ለመፈፀም
የሚያስፈልገውን ወጩ ከግምት ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል፡፡
4.10. የንብረት አጠቃቀምና ጥገና
1. የኮርፖሬሽኑ የበላይ ኃላፊ የኮርፖሬሽኑ ንብረት ኢኮኖሚያዊና ውጤታማ በሆነ መንገድ
አገልግሎት እንዲሰጥ ተገቢ የጥገና እና የእንክብካቤ ሥርዓት መዘርጋት አለበት፡፡
2. ለማሽነሪዎች /መሣሪያዎች/፣ ለተሽከርካሪዎች፣ ሕንጻዎችና ለሌሎች ንብረቶች መሠረታዊ
የሆነ ጥገና ንብረቶቹ የሚኖራቸውን የአገልግሎት ዘመን ያራዝማል ተብሎ ሲታመን ወጪው
አስቀድሞ በቋሚ ንብረት በተመዘገበው ሂሳብ ላይ ተጨምሮ መመዝገብ አለበት፡፡

12
ክፍል አምስት
5. የኮርፖሬሽኑ ንብረት አወጋገድ

5.1. ቋሚ ንብረትን የማስወገድ ስልጣን

ኮርፖሬሽኑ በዚህ መመሪያና በሌሎች ሕጎች መሠረት ቋሚ ንብረቶችን የማስወገድ ሥልጣን አለው፡፡

5.2. የኮርፖሬሽኑን ንብረት ስለማስወገድ

ኮርፖሬሽኑ በሚከተሉት ምክንያቶች ንብረትን ማስወገድ ይችላል፡፡

ሀ. ንብረቱ ለኮርፖሬሽኑ አላማዎች የማይፈለግ ሲሆን፣


ለ. ንብረቱን ይዞ መቀጠል የሚያስከትለው ወጪ ከፍተኛ በመሆኑ የማያዋጣ ሲሆን፣
ሐ. በልዩ ልዩ ምክንያት ንብረቱ የሚፈለግበትን አገልግሎት በብቃት መስጠት የማይችል
ወይም ከአገልግሎት ውጪ ሲሆን፣
መ. ኮርፖሬሽኑ ከሚኖው የመካከለኛና የረጅም ጊዜ የሥራ ዕቅድ አንጻር ትርፍ መሆኑ
ሲታመን፣
ሠ. ኮርፖሬሽኑ ለገበያ የመመሪያው ወይም ያመረተው ንብረት ሲሆን በሽያጭ ሊያስወግደው
ይችልል፡፡
5.3. ንብረት የማስወገድ ሂደትና ኃላፊነት

13
ኮርፖሬሽኑ ንብረቶችን ለማስወገድ የሚከተለውን ሂደት መከተል ይኖርበታል፣

ሀ. የኮርፖሬሽኑ ንብረቶችን በባለበትነት የመከታተል ኃላፊነት የተሰጠው የሥራ ክፍል የሚወገዱ ንብረት ዝርዝርን
በቅፅ ሞልቶ ኮርፖሬሽኑ በወቅቱ ማቅረብ ይኖርበታል፣

ለ. ኮርፖሬሽኑ የቀረበለትን መጠየቂያ ቅፅ መርምሮ ለኮርፖሬሽኑ ንብረቶች አስወጋጅ ኮሚቴ ይመራል፣

ሐ. የኮርፖሬሽኑ ንብረቶች አስወጋጅ ኮሚቴ የተመራለትን መጠየቂያ ቅፅ መርምሮ በዚህ መመሪያ መሰረት
አስፈላጊውን ይፈፅማል፡፡

መ. የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስኪያጅ የሚሰይመው ንብረት አስወጋጅ ኮሚቴ የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ ያፀድቃል፡፡
እንዲወገዱም ውሳኔ የተሰጠባቸውን የኮርፖሬሽኑ ንብረቶች በወቅቱ እንዲወገዱ ያደርጋል፡፡

5.4. ንብረት የማስወገድ ስርዓቶች


5.4.1. ኮርፖሬሽኑ ንብረቱ እንዲወገድ ለምን እንዳስፈለገ ለይቶ የማወቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ በተጨማሪም ንብረት
ሲያስወግዱ፡-

ሀ. የንብረቱ ሕጋዊ ባለቤት ማን እንደሆነ መለየትና ኮርፖሬሽኑ ንብረት እንደሆነ ማረጋገጥ፣


ለ. ሕንፃና ተመሳሳይ ግንባታዎች የባለቤትነት መብት ለመመለስ እነዚህን ንብረቶች ማስወገድ ቢፈልግ
መስተዳድሩን ማስፈቀድ እና
ሐ. የሚወገዱት ንብረቶች ልዩ ጠቀሜታ ያላቸው ወይም ጉዳት የሚያስከትሉ ሲሆኑ አግባብ ካላቸው
የመንግስት መስሪያ ቤቶች ጋር መነጋገር ይኖርበታል፡፡ የሚወገዱት ንብረቶች በባህሪያቸው ለጤና
አደገኛ የሆኑ ኬሚካሎች ወይም መድሀኒቶች ወይም የጨረር ጉዳት የሚያስከትሉ ሆነው ሲገኙ
በአወጋገዱ ላይ አስፈላጊውን እገዛ ከሚመለከተው አካል ትብብር ሊጠየቅ ይገባል፡፡
5.4.2. የሚወገደውን የኮርፖሬሽኑ ንብረት የመነሻ ዋጋ መገመት
ሀ. እንዲወገድ የተወሰነበትን የእያንዳንዱን የኮርፖሬሽኑ ንብረት የወቅቱን የመነሻ ዋጋ ንብረቱን
በሚያስተዳድረው የሥራ ክፍል/ባለሙያ ይገመታል፡፡
ለ. የሥራ ክፍሉ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ሌሎች ሙያው ያላቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶችና
ድርጅቶች የመነሻ ዋጋውን አገማመት በተመለከተ እንዲያማክሩት ሊጠይቅ ይችላል፡፡
ሐ. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 2/ለ/ መሰረት የሚጠየቀው የሙያ ምክር ከንብረቱ ልዩ ባህሪ የተነሳ
የንብረቶቹን አጠቃቀም በተመለከተ ስልጣንና ኃላፊነት የተሰጣቸውን የመንግስት ተቋማት
ወይም በዚህ ሙያ የተሰማሩ ድርጅቶችን ወይም ግለሰቦችን መሆን ይኖርበታል፡፡
መ. የመነሻ ዋጋን የገመተ ግለሰብ በሽያጭ ወይም በአወጋገድ ሥራው መሳተፍ የለበትም፡፡

5.5. የኮርፖሬሽኑን ንብረት የማስወገድ ዘዴዎች

ኮርፖሬሽኑ ንብረት ለማስወግድ የሚችሉባቸው ስድስት አማራጭ ዘዴዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡


14
ሀ. ለሌላ የመንግስት መስሪያ ቤት በማዛወር ወይም በማስተላለፍ፣
ለ. ባሉበት ሁኔታ ለሕዝብ በጨረታ ወይም በሐራጅ በመሸጥ፣
ሐ. ንብረቱን ፈታቶ በመለዋወጫነት ጥቅም ላይ በማዋል ወይም በመሸጥ፣
መ. ንብረቱን በውዳቂነት ማስወገድ፣
ሠ. ንብረቱን በስጦታ በመስጠት ማስወገድ፣
ረ. ንብረቱን በመቅበር ወይም በማቃጠል ማስወገድ፣

5.6. ንብረትን ለሌላ የመንግስት መስሪያ ቤት በማስተላለፍ ስለማስወገድ

1. ንብረትን ለሕዝብ በሐራጅ ወይም በጨረታ መሸጥ የሚያስከትለው ወጪ ከፍተኛ ሆኖ የሚታወቅ በመሆን
ኮርፖሬሽኑ ለማስወገድ የፈለገውን ንብረት ወደ ሌላ የመንግስት መስሪያ ቤት ለማዛወር ይቻል እንደሆነ
በቅድሚያ ጥረት ማድረግ አለበት፡፡
2. በመንግስት መስሪያ ቤቶች ወይም በልማት ድርጅት መካከል የሚደረገው የንብረት ዝውውር የሚፈፀመው
የወቅቱን የንብረቱን ዋጋ ግምት በመመዝገብ መሆን አለበት፡፡

5.7. ንብረቱን ባለበት ሁኔታ ለሕዝብ በጨረታ ወይም በሐራጅ መሸጥ


5.7.1. ንብረትን በጨረታ ወይም በሐራጅ ለመሸጥ መሟላት ያለባቸው ሁኔታዎች፣
ሀ. ኮርፖሬሽኑ ንብረትን በጨረታ ወይመ በሐራጅ በመሸጥ ማስወገድ ይችላሉ፡፡
ለ. ኮርፖሬሽኑ የተሻለ ዋጋ ለማግኘት፣ በፍጥነት ሽያጩን በመፈፀምና የሚያስከትሉትን ችግሮች
በመገምገም የተሻለውን የመሸጫ ዘዴን መምረዓ ይኖርባቸዋል፡፡
ሐ. የንብረት አስወጋጅ ኮሚቴ ለጨረታ ወይም ለሐራጅ የሚቀርቡትን እቃዎች የመነሻ ዋጋ
የመንግስት የኮርፖሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር እንዲያፀድቀው ማቅረብ አለበት፣
መ. ተፈታተው እንዲሸጡ የተወሰነባቸውን መለዋወጫዎች፣ እንዲሁም ውዳቂ ብረታ ብረቶች
የጨረታ ወይም የሐራጅ መነሻ ዋጋ የመለዋወጫውን ወይም የብረታ ብረቱን ዓይነት፣
የገበያውን ሁኔታና ሌሎች መረጃዎችን መሰረት በማድረግ የተገመተ መሆን አለበት፣
ሠ. ኮርፖሬሽኑ ወጪን ለመቀነስ ሲባል የሚሸጠውን ንብረት በአንድ ጊዜ በጥቅል መሸጥ አለበት፣
ረ. የጨረታ ማስታወቂያው ዘዴ የሚከተሉትን ታሳቢ ማድረግ አለበት፡-
i. የሚሸጠው የኮርፖሬሽኑ ንብረት የመነሻ ዋጋ ከብር 100000 /መቶ ሺህ/ ያነሰ ከሆነ
የኮርፖሬሽኑ ሽያጩን ቢያንስ ለ 7 ተከታታይ ቀናት በሕዝብ ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ
ለሁለት ጊዜ እንዲወጣ ማድረግ አለበት፣
ii. የሚሸጠውን የኮርፖሬሽኑ ንብረት ዋጋ ከብር 100001 /መቶ አንድ ሺህ/ በላይ
ከሆነ የኮርፖሬሽኑ በእቃውና ሰፊ ተነባቢነት ባለው ጋዜጣ ቢያንስ ለ 1 ጊዜ
ማስታወቂያው ለሕዝብ ይፋ እንዲሆን ማድረግ አለበት፡፡

15
iii. ከላይ በተራ ቁጥር i በተጠቀሰው መንገድ ሽያጩ ካልተወሰነ የንብረት አስወጋጅ/ሽያጭ
ኮሚቴ ንብረቱ የሚወገድበትን ሌላ አማራጭ ዘዴ ለዋና ስራ አስኪያጅ በማቅረብ ሲወሰን
ንብረቱ እንዲወገድ ያደርጋል፡፡
5.7.2. በጨረታ ስለሚደረግ ሽያጭ
ሀ. ኮርፖሬሽኑ የሚያወጡት የጨረታ ማስታወቂያ ኤጀንሲው ባዘጋጀው ቅፅ የተገለፁትን
ማካተት አለበት፡፡
ለ. ተጫራቾች እንዲጫረቱ በሚሰጠው ቀን ከ 15 እስከ 30 ቀናት ሆኖ በኮርፖሬሽኑ ንብረቶች
አስወጋጅ ኮሚቴ የሚወሰን ይሆናል፡፡
ሐ. ኮርፖሬሽኑ በጨረታ ማስታወቂያው እስከተመለከተው ጊዜ ድረስ ክፍት ሆኖ የሚቆይ የተለየ
የጨረታ ሳጥን ማዘጋጀት አለበት፡፡ አስወጋጅ ኮሚቴውም ጊዜው ሲደርስ ጨረታ ሳጥኑን
ማሸግ አለበት፡፡ ማናቸውም ለጨረታው ማቅረቢያ የተሰጠው ጊዜ ካለፈ በኋላ የሚቀርቡ
የጨረታ ሰነዶች ሳይከፈቱ ለተጫራቾች መመለስ አለባቸው፡፡ በጨረታ ሽያጭ በቂ ተወዳዳሪ
ካልቀረበ ወይም የቀረበው ዋጋ ተቀባይነት ካላገኘ መስሪያ ቤቱ የጨረታውን ማስታወቂያ
በድጋሚ የማውጣት ወይም ጨረታውን በመሰረዝ ሌላ የማስወገጃ አማራጭ የመጠቀም
መብት አለው፡፡
መ. ኮርፖሬሽኑ ተጫራቾች የጨረታ ማስከሪበያ እንዲያስይዙ መጠየቅ ያለበት ሲሆን፣
ለእያንዳንዱ በጨረታ መከናወን ላለበት ሽያጭ የጨረታ ማስከበሪያ ሊኖር እንደሚገባ
መወሰን አለበት፡፡ የሽያጭ ኮሚቴውም ለእያንዳንዱ ሽያጭ የሚያዘውን የጨረታ
ማስከበሪያ በጨረታው ያሸነፈው ተጫራች እንደተመረጠ ወዲያውኑ ጨረታውን ላላሸነፋ
መመለስ አለበት፡፡
ሠ. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው እና የሽያጭ ኮሚቴ አባላት ባሉበት ለሕዝብ ግልፅ
ሆኖ መከፈት አለበት፡፡ የተጫራቾች ስምና የመጫረቻው ጊዜ በሽያጭ ኮሚቴ አስተባባሪ
መነበብ አለበት፣ የሽያጭ ኮሚቴ ፀሐፊም ይህንኑ መዝግቦ መያዝ አለበት፡፡
ረ. ኮሚቴው የትኛውን የጨረታ መወዳደሪያ ሀሳብ መቀበል እንዳለበት ይወስናል፡፡ ከፍተኛው
ጨረታ በመነሻነት በተያዘው ዋጋ ወይም ከዚያ በላይ ከሆነ ኮሚቴው ከፍተኛውን የጨረታ
ዋጋ ሊቀበል ይችላል፡፡
ሰ. የንብረት አስወጋጅ/የሽያጭ ኮሚቴው በጨረታው የደረሰበትን የአፈፃፀም ሂደት
እንዲያፀድቀው ለመስሪያቤቱ የበላይ ኃላፊ ማቅረብ አለበት፡፡
5.7.3. በሀራጅ ስለሚደረግ ሽያጭ
ሀ. ኮርፖሬሽኑ የሚያወጣው የሐራጅ ማስታወቂያ ኤጀንሲዉ ባዘጋጀው ቅጽ መሠረት ተሞልቶ
መቅረብ አለበት፡፡
ለ የሐራጁ መሪ ሐራጁ ከመጀመሩ በፊት የመነሻውን ዋጋ መግለጽ አለበት፡፡ በሐራጁ የመነሻው ዋጋ
ወይም ከዚህ በላይ ንብረቱን የሚገዛ ካልተገኘ የንብረት አስወጋጅ ኮሚቴ የተሻለ ነው
የሚለውን የማስወገጃ ዘዴ መምረጥ አለበት፡፡

16
5.7.4. የተሽከርካሪዎችና መሣሪያዎች ማስወገጃ መመዘኛዎች

የኮርፖሬሽኑ ተሽከርካሪዎችንና መሣሪያዎችን ለማስወገድ ለሚከተሉት መመዘኛዎች ቢያንስ አንዱ


መማላቱን ማረጋገጥ አለባቸው፡፡

ሀ. በከፍተኛ ጉድለት ምክንያት ሊጠገን የማይችል ሲሆን፣


ለ. የመለዋወጫ ዕቃ በገበያ ላይ አለመገኘት፣
ሐ. ለማደስ የሚያስፈልገው ወጪ ከመተኪያ ዋጋው ጋር ሲነፃፀም መተካቱ የሚመረጥ ሲሆን፣
መ. በቴክኖሎጂ ኃላቀርነት ምክንያት ምርታማነቱ ዝቅተኛ ሲሆን፣
ሠ. ኮርፖሬሽኑ ከሚኖረው ወቅታዊም ሆነ የቅርብ ጊዜ የሥራ ዕቅድ አንፃር ትርፍ መሆኑ
ሲታመን፣
ረ. አገልግሎት በሰጠባቸው ጊዜያት ለጥገና የወጣው ጠቅላላ ወጪ ከሰጠው አገልግሎት ጋር
ተመጣጣኝ ሳይሆን ሲቀር፣
ሰ በእርጅና ምክንያት አገልግሎት መስጠት የማይችል ሲሆን

5.8. ቋሚ ንብረቶችን በጨረታ ሽያጭ ለማስወገድ የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት


ሀ. ቋሚ ንብረቱ በንብረትነት የተገኘበትን የሚገልጽ መረጃ ማጣራት፣
ለ. የቅድሚያ ግመታና ሽያጭ ሥራዎችን የሚያከናውኑ ሁለት ኮሚቴዎችን ማቋቋም /የገማችና
የሽያጭ ኮሚቴዎችን/፣
ሐ. የጨረታ ሰነዶችን በማዘጋጀት ጨረታ ማውጣት፣ ማጫረት፣ ጨረታውን መገምገምና
ለንብረት ሽያጭ ጨረታ አጽዳቂ ኮሚቴ ሪፖርት ማቅረብ፣
መ. የሽያጭ ገንዘቡን ወደ ኮርፖሬሽኑ ገቢ ማድረግ እና ንብረቱን ማስረከብ፣
ሠ. በሽያጭ የሚወገደው ንብረት ተሽከርካሪ ከሆነ ጨረታው ከመውጣቱ በፊት የባለቤትነት
ማስረጃ መኖሩንና የቦሎ ግብር የተከፈለ መሆኑ መረጋገጥ

5.9. የተሽከርካሪዎች፣የመሣሪያዎች እና የሌሎች ቋሚ ንብረቶች የጨረታ መነሻ ዋጋ


ሀ. ተሽከርካሪዎችና መሣሪያዎች በልዩ ልዩ ምክንያት ከአገልግሎት ውጪ ሲሆኑ ወይም በብቃት
አገልግሎት መስጠት በማይችሉበት ደረጃ ሲደርሱ በኮርፖሬሽኑ በተዘጋጀው በስሌት ዘዴ
የጨረታ መነሻ ዋጋቸውን በማስላት ማወቅና እንዲወገድ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡
ለ. ሌሎች ቋሚ ንብረቶችን በወቅቱ የገበያ ዋጋ በመገመት ማስወገድ ይኖርባቸዋል፡፡

5.10. ተሽከርካሪን ወይም መሣሪያን ባለበት ሁኔታ መሸጥ


እንዲወገድ የተወሰነበትን ተሽከርካሪ ወይም መሣሪያ ባለበት ሁኔታ ለመሸጥ ከዚህ በታች ከተመለከቱት
ውስጥ ቢያንስ አንዱ መሟላት ይኖርበታል፡፡
ሀ. ተሽከርካሪው ወይም መሣሪያው የሚሠራ ከሆነ፣
ለ. ተሽከርካሪው ወይም መሣሪያው የማይሠራ ቢሆን ሞተር፣ ትራንስሚሽን፣ ሻንሲ፣ አካሉ እና
ሃይድሮሊክ ሲስተም በሙሉ ያሉ ከሆነ፣

17
ሐ. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 7/ለ ላይ የተመለከቱት ዋና ዋና አካላቱ የተሟሉ ባይሆንም
የተሽከርካሪው ወይም የመሣሪያው ቀሪ አካል በገበያ ላይ ተፈላጊ መሆኑ ከተረጋገጠ፣

5.11. ንብረቱን ፈታቶ በመለዋወጫነት ጥቅም ላይ ማዋል ወይም መሸጥ


1. ኮርፖሬሽኑ የአንድን ንብረት አካላት ፈታተው በመለዋወጫ ዕቃነት መጠቀም ወይም መሸጥ
የሚችሉት ንብረቱን ባለበት ሁኔታ መሸጥ የማይቻል ሲሆን ወይም ባለበት ሁኔታ ከመሸጥ ይልቅ
ፈታቶ መጠቀም ወይም መሸጥ የበለጠ ጥቅም የሚያስገኝ ሲሆን ነው፡፡
2. በመለዋወጫነት ጥቅም ላይ እንዲውሉ ወይም እንዲሸጡ ከተወሰነባቸው ተሽከርካሪዎችና
መሣሪያዎች ላይ ጠቃሚ አካሎችን ፈታቶ አግባብ ባለው የዕቃ አስተዳደር አሠራር መሠረት ገቢ
እንዲሆኑና ጥቅም ላይ እንዲውሉ ወይም በጨረታ እንዲሸጡ ማድረግ ይቻላል፡፡
3. ተፈታተው እንዲሸጡ የተወሰነባቸው መለዋወጫዎች የጨረታ መነሻ ዋጋ የመለዋወጫውን ዓይነት፣
የገበያውን ሁኔታና ሌሎች መረጃዎች መሠረት በማድረግ ይገማታል፡፡

5.12. ንብረቱን በውዳቂነት ስለማስወገድ


1. ከማናቸውም የንብረት ማስወገድ ሂደት የሚገኘው ገቢ ለማስወገድ የሚደረገውን ወጪ የማይሸፍን
ነው ተብሎ ሲገመት ንብረቱ በውዳቂነት እንዲወገድ ይደረጋል፡፡ የንብረት አስወጋጅ ኮሚቴው የተሻለ
ስለሚሆነው ዘዴና ማናቸውንም ከውዳቂው ሊገኝ የሚችለውን የሽያጭ ገቢ በሚመለከት ምክር
ይሰጣል፡፡ በውዳቂነት እንዲወገዱ የሚደረጉ ሁሉ በኮርፖሬሽኑ በበላይ ኃላፊ መጽደቅ አለባቸው፡፡
2. ጠቃሚ አካሎቻቸው የተወሰዱባቸው ቀሪ ብረታ ብረቶች እና ውዳቂ ብረታ ብረቶች የመነሻ ዋጋ
የገበያውን ሁኔታና ሌሎች መረጃዎች መሠረት በማድረግ አገመት አለበት፡፡
3. በውዳቂ ብረታ ብረትነት እንዲወገዱ የተወሰነባቸውን ተሽከርካሪዎችና መሣሪያዎች እንዲሁመ
ተፈታተው ጠቃሚ አካሎቻቸው የተወሰዱባቸው ቀሪ ብረታ ብረቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉ በጨረታ
እንዲሸጡ ይደረጋል፡፡
4. ከሚመለከታቸው መንግሥታዊ አካላት ጋር በመሆን ሥነ ምህዳርን በማይጐዳ ሁኔታ ውዳቂ
ንብረቶችን በማቃጠልና በመቅበር ማስወገድ ይቻላል፡፡

5.13. ንብረትን በስጦታ በመስጠት ስለማስወገድ


1. ኮርፖሬሽኑ አንድን ንብረት ለሌላ የመንግሥት መስሪያ ቤት ወይም በማህበራዊ አገልግሎትና ልማት
ተግባራት ላይ ለተሰማሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ወይም ለክልል መንግሥታት በስጦታ ሊያስተላልፍ
የሚችለው ከሚከተሉት በአንዱ ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡
ሀ. ንብረቱ ለመስሪያ ቤቱ ሥራ የማይውል ሲሆን፣
ለ. ንብረቱ እንዲወገድ ቢደረግ የሚገኘው ገቢ ንብረቱን ለመሸጥ ወይም ለመጠበቅ ከሚወጣ
ወጪ በጣም አነስተኛ መሆኑ ሲረጋገጥ፣ ወይም
ሐ. ንብረቱ የሚተላለፍለት አካል በንብረቱ በመጠቀም ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ አገልግሎት
አሰጣዩን ለማሻሻል ያግዛል ተብሎ ኮርፖሬሽኑ ሲታመን፣
2. በዚህ አንቀጽ 1 በተገለፀው መሠረት ንብረት ለሌላ አካል በስጦታ እንዲተላለፍ የሚደረገው
የኮርፖሬሽኑ የበላይ ኃላፊ ሲፈቀድ ብቻ ነው፡፡
18
5.14. ንብረቱን በመቀበር ወይም በማቃጠል ማስወገድ
ምንም ጠቀሜታ የሌላቸው ውዳቂ ንብረቶችን ኮርፖሬሽኑ በራሣቸው ወይም የሚመለከታቸው
አካላትን በማማከር በመቅበር ወይም በማቃጠል ወይም በሌላ መንገድ ማስወገድ ይኖርበታል
1. የሚወገደው ንብረት ምንም ዓይነት የስነምህዳር ወይም የጤና ችግር የሚያስከትል ከሆነ
ኮርፖሬሽኑ በራሱ ኃላፊነት ንብረቶቹን ለይቶ በማቅበር ወይም በማቃጠል ማስወገድ ይችላል፡፡
2. የሚወገደው ንብረት ከፍተኛ የሥነምህዳር ወይም የጤና ችግር የማያስከትል ሆኖ ሲገኝ
ኮርፖሬሽኑ ስለአወጋገዱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመመካከር ንብረቱን በተገቢው መንገድ
ማስወገድ ይኖርበታል፡፡

5.14.1. ተደጋጋሚ ጨረታ የማውጣት ሂደት


1. ኮርፖሬሽኑ የሚወገዱ ንብረቶችን በጨረታ ወይም በሐራጅ ሽያጭ ከመነሻ ዋጋ ግምት ባላነስ ዋጋ
መሸጥ አለባቸው፣
2. በዚሀ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 በወጣው ግምት መሠረት በቂ ተወዳዳሪ ወይም ገዢ ካልቀረበ ለሁለተኛ
ዙር ለጨረታ ወይም ለሐራጅ ሽያጭ በድጋሚ መቅረብ አለባቸው፣
3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 በተገለፀው መሠረተ በሁለተኛ ዙር መነሻ ዋጋው ለመሸጥ ተሞክሮ በቂ
ተወዳዳሪ/ገዢ ካልተገኘ የግምት ዋጋውን በማሻሻል ለሶስተኛ ጊዜ የጨረታ/የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
በማውጣት በተገኘው ዋጋ ሽያጩ ይፈፀማል፡፡

5.14.2. ከማስወገድ ስለሚገኘው ገቢ


1. የኮርፖሬሽኑ ንብረት በሚሸጥበት ጊዜ ዋጋውን በጥሬ ገንዘብ ወይም በተረጋገጠ ቼክ ወይም በባንክ
ዲፖዚት መቀበል አለባቸው፣
2. ከሽያጭ የሚገኝ ገቢ ወጭው ተቀንሶ ለኮርፖሬሽኑ ካፒታል ኢንቨስትመንት ይውላል፡፡

5.14.3. ንብረቶችን ከመዝገብ ስለመሰረዝ


1. ከመጋዘን ወጪ የሆኑ ንብረቶች በተጠቃሚዎች እጅ እያሉ የመበላሸት፣ የመጥፋት፣ የመቃጠል ወይም
በእርጅናና በሌሎች ምክንያቶች ንብረቶችን መረከብ፣ መሰረዝ ቢያስፈልግ በኮርፖሬሽኑ የሂሳብ አያያዝ
መመሪያ ቁጥር ----- መሠረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
2. ማናቸውም የኮርፖሬሽኑ ንብረት ሲሰረዝ ንብረቱ ከመዝገብ የተሰረዘበትን ምክንያትና የንብረቱ
የመዝገብ ዋጋ በኮርፖሬሽኑ ሂሳብ ሪፖርት ውስጥ መገለጽ አለበት፡፡

5.14.4. ከቀረጥ ነጻ ስለሚገቡ ዕቃዎች


ከቀረጥ ነፃ የገቡ ዕቃዎች ለሌላ ወገን በሚተላለፉበት ጊዜ ስለ ቀረጡ አከፋፈል ሁኔታ የጉምሩክ አዋጅን
ለማስፈፀም በሚወጡ አግባብነት ያላቸው መመሪያዎች መሠረት የሚፈፀም ይሆናል፡፡

5.14.5. ስለባለቤትነት ስም ዝውውር

19
1. ሻጭ ኮርፖሬሽኑ የሸጠበትን ገንዘብ ተቀብሎ የሸጣቸውን ተሽከርካሪዎች፣ መሣሪያዎችና ሌሎችም
የስም ዝውውር የሚያስፈልጋቸው ንብረቶች በገዥው ስም ተመዝግቦ የባለቤትነት መታወቂያ
እንዲሰጠው ስልጣን የተሰጠውን አካል በደብዳቤ በመጠየቅ ማስፈፀም ይኖርበታል፣
2. ኮርፖሬሽኑ በሚሰጠው ደብዳቤ ላይ የሽያጡን ቃለ ጉባኤ፣ የገዥውን ስም፣ በጨረታ የተሸጠበትን ገንዘብ
ልክ፣ የተሸጠውን ንብረት መለያ ቁጥር፣ አይነትና ሞዴል፣ ተሽከርካሪዎችን የሻንሲና የሞተር ቁጥር
እንዲሁም የሌሎች ንብረቶችን ሌሎች መለያዎች በመዘርዘርና የጉምሩክ ቀረጥ የተከፈለበትን ሰነድ
በማያያዝ የማይከፈልበትም ከሆነ ይህንኑ በመግለጽ ማስተላለፍ አለበት፡፡
ሐ. የቀረበው አቤቱታ በኤጀንሲው ወይም በሌሎች ባለሙያዎች ዝርዝር ምርመራ ተደርጎበት ሪፖርት
እንዲቀርብለት የማድረግ፣
መ. ምስክሮችን የመጥራት፣ ምስክሮችና የንብረት ሽያጩ የሚመለከታቸው ወገኖች ቃላቸውን በመሃላ
እንዲሰጡ የማድረግ፣
ሠ. አቤቱቃ የቀረበበት የመንግስት መስሪያ ቤት ቀጣይ የአፈጻጸም እርምጃ እንዳይወስድ የማገድ፣
ረ. የመንግስት መስሪያ ቤቱ በመንግስት ግዢና ንብረት አስተዳደር አዋጅ በተደነገገው መሰረት ስራውን
እንዲያከናውን ትዕዛዝ የማስተላለጽ፣
ሰ. የመንግስት መስሪያ ቤቱ ከህግ ውጭ ያከናውነው ተግባር ወይም የሰጠው ውሳኔ በሙሉ ወይም በከፊል ቀሪ
እንዲሆን የማድረግ፣
ሸ. ተገቢ ሆኖ ካላገኘው የንብረት ገዢውን አቤቱቃ ውድቅ የማድረግ፣ ናቸው፡፡

5.14.6. በንብረት ማስወገድ ላይ ለዋና ዳይሬክተሩ ቅሬታ የሚቀርብበት አግባብና አፈታት፣

ሀ. አቤቱታ ከንብረት ገዢ መቀበል፣


ለ. አቤቱታው ለዋና ዳይሬክተሩ በዚህ መመሪያ አንቀጽ 4.11.6 ንዑስ አንቀጽ 1 መሠረት በተገቢው ጊዜ የቀረበ
መሆኑን ማጣራት፣
ሐ. አቤቱታው ለዋና ዳይሬክተሩ የቀረበው ኮርፖሬሽኑ ለአቤቱታው ምላሽ በጽሁፍ ከሰጠ በኋላ 5 /አስምት/
የስራ ቀናት ካለፈው ወይም በመጀመሪያ ለኮርፖሬሽኑ ሳይቀርብ ከሆነ ወይም ጊዜው ካለፈ የቀረበ ወይም
ለኮርፖሬሽኑ ሳይቀርብ የቀረበ ከሆነ አቤቱታውን ውድቅ ማድረግ፣
መ. አቤቱታው የቀረበው በተገቢው ጊዜ ከሆነ አቤቱታ የቀረበበት መሆኑንና ከንብረት ሽያጩ አፈጻጸም ጋር
የተያያዙ ሰነዶችንና መግለጫዎች እንዲልክ እና በጉዳዩ ላይ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ ቀጣይ እንቅስቃሴ
እንዳያደርግ የጽሁፍ ማስታወቂያ መላክ፣
ሠ. የጽሁፍ ማስታወቂያ የደረሰው የኮርፖሬሽኑ የንብረት ሽያጭ ሂደት የተከናወነባቸውን ሰነዶች፣
ማስረጃዎችና መግለጫ እንዲልክ መከታተል፣
ረ. ከኮርፖሬሽኑ ተጠናቅረው የቀረቡትን የአቤቱታውን ጭብጦች፣ ከዋና ዳይሬክተሩ የተሰጠውን ምላሽ፣
ማስረጃዎች፣ ሰነዶችና መግለጫዎች ከህጉ አኳያ በመመርመር ውሳኔ መስጠት፡፡

5.14.7. ለኮርፖሬሽኑ ቦርድ ጽህፈት ቤት የሚቀርብ አቤቱታ የሚታይበት ስርዓት፣

20
1. የንብረት ገዢ አቤቱታ የማቅረብ መብት
ጨርታውን ያወጣው ኮርፖሬሽኑ በዚህ መመሪያ የተመለከተውን በአግባቡ አልፈፀሙም በሚል ቅር
የተሰኘ ተጫራች/ገዢ ጨረታው እንደገና እንዲታይለት ወይም ሂደቱ እንዲጣራለት እንደ ጉዳዩ ሁኔታ
ለኮርፖሬሽኑ የበላይ ኃላፊ ወይም ለቦርድ ጽህፈት ቤት አቤቱታ ማቅረብ ይችላል፡፡
2. አቤቱታ ማቅረብ የማይቻልባቸው ሁኔታዎች
ሀ. ኮርፖሬሽኑ በመረጠው የንብረት ማስወገድ ዘዴ ላይ፣
ለ. በጨረታ ሰነዱ ላይ በተገለፀው የሽያጭ መነሻ ዋጋ ላይ፣
ሐ. በሚከተሉት ምክንያቶች ጨረታውን ውድቅ ለማድረግ በተሰጠ ውሳኔ፣
I. በሽያጭ አካሄዱ ላይ ውጤቱን ሊያዛባ የሚችል ስህተት መፈፀሙ ከተረጋገጠ፣
II. የኮርፖሬሽኑን ፍላጐት ለማሟላት ሌላ የተሻለ የማስወገጃ አማራጭ መገኘቱ በኮርፖሬሽኑ
ከታመነ፣
III. የቀረበው ከፍተኛ ዋጋ ኮርፖሬሽኑ ካስቀመጠው የመሸጫ መነሻ ዋጋ ያነሰ ከሆነ፣
IV. በዕጩ ተወዳዳሪዎች ወይም በሽያጭ ኮሚቴ አባላት ጨረታውን ለማዛባት የመመሳጠር ተግባር
መፈፀሙ ከተረጋገጠ፣
V. አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ተጫራቾች በመቅረባቸው ምክንያት በቂ ውድድር ባለመደረጉ
ተስማሚ የሽያጭ ዋጋ ባለመገኘቱ፡፡

5.14.8. ለኮርፖሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር የሚቀርብ አቤቱታ የሚጣራበት ስርዓት


1. ጨረታውን ያወጣው ኮርፖሬሽን የጨረታውን ወይም የአቤቱታውን ውጤት ለተጫራቹ ከገለፀበት ቀን
ጀምሮ ከሚቆጠር ሰባት የሥራ ቀናት በፊት ሽያጩን አሸናፊ ካለው ተጫራች ጋር መፈፀም የለበትም፣
2. በንብረት ሽያጭ አፈፃፀም ሂደት ቅር የተሰኘ ገዢ በአቤቱታው መሰረት የሆነውን የመጨረሻ ውሳኔ
ካወቀበት ወይም ማወቅ ይገባው ከነበረበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 5 /አምስት/ የስራ ቀናት ጊዜ ውስጥ
አቤቱታውን በመጀመሪያ ማቅረብ ያለበት ጨረታውን ላወጣው ኮርፖሬሽኑ ነው፡፡ ከዚህ ጊዜ በኋላ
ለኮርበፖሬሽኑ የሚቀርብ አቤቱታ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
3. አቤቱታውን ባቀረበው ንብረት ገዢ እና ጨረታውን ባወጣው ኮርፖሬሽን መካከል ያለው ልዩነት
በስምምነት ካልተፈታ በስተቀር የኮርፖሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር አቤቱታ ከቀረበበት ቀን አንስቶ
በ 10 /አስር/ የሥራ ቀናት ውስጥ ለቀረበው አቤቱታ ውሳኔውን በጽሁፍ መስጠት አለበት፡፡ በጽሁፍ
የተሰጠው ውሳኔ የውሳኔውን ምንነትና የሚወሰደውን እርምጃ የሚያሳይ መሆን ይኖርበታል፡፡
4. ጨረታወን ያወጣው ኮርፖሬሽን የሰጠው ውሳኔ ግልባጭ ውሳኔው በተሰጠ በ 5 /አምስት/ የስራ ቀናት
ውሰጥ አቤቱታውን ላቀረበው ንብረት ገዢ እንዲደርስ ማድረግ አለበት፡፡
5. አቤቱታ የቀረበበት ማናቸውም ንብረት ሽያጭ የሚጣራው ለጨረታው የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ፣
አዋጅና መመሪያ መሠረት በማድረግ ይሆናል፡፡

5.15. ኮርፖሬሽኑ የንብረት ሽያጭ አፈፃፀመ ሂደትን ማገድ ስለመቻሉ


ኮርፖሬሽኑ አቤቱታውን በጊዜ ገደቡ ውስጥ የቀረበ መሆኑ ካረጋገጠ አቤቱታው ውሳኔ እስከሚያገኝ ድረስ

ጨረታው ታግዶ እንዲቆይ ማድረግ ይኖርበታል፡፡

21
4.12.1 ለቦርድ ጽህፈት ቤት አቤቱታ የሚቀርብበትና የሚጣራበት ስርዓት
1. የኮርፖሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር አቤቱታው ከቀረበበት ቀን አንስቶ በሚቆጠር አስር ቀናት ውስጥ
ለአቤቱታው ውሳኔ ካልተሰጠ ወይም ውሳኔ ተሰጥቶ አቤቱታ አቅራቢው በተሰጠው ውሳኔ ያልረካ
እንደሆነ ኮርፖሬሽኑ ውሳኔ ከተገለፀበት ወይም ውሳኔ ካልሰጠ ውሳኔውን መስጠት ከነበረበት ቀን ገደብ
ማብቂያ ጀምሮ በሚቆጠር 5 /አምስት/ የስራ ቀን ጊዜ ውስጥ አቤቱታውን ለቦርድ ጽህፈት ቤት ማቅረብ
ይችላል፡፡ ከዚህ ጊዜ በኋላ በቦርድ ጽህፈት ቤት የሚቀርብ አቤቱታ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
2. ንብረት ገዢው አቤቱታውን ለቦርድ ጽህፈት ቤት ሲያቀርብ ለኮርፖሬሽኑ ያቀረበውን አቤቱታ የሚያሳይ
ደብዳቤ ኮርፖሬሽኑ ለአቤቱታው ውሳኔ ተሰጥቶ ከሆነ የውሳኔውን ቅጂ፣ የአቤቱታውን ጭብጥና፣
ተያያዥ ማስረጃዎችን በአባሪነት ማያያዝ ይኖርበታል፡፡
3. ቦርዱ አቤቱታው እንዲቀርብለት ወዲያውኑ አቤቱታ የቀረበ መሆኑን በቀረበበት አቤቱታ ላይ ያለውን
ማስረጃና መግለጫ ማስታወቂያው በደረሰው በአምስት የስራ ቀን ውስጥ እንዲያቀርብ እንዲሁም ውሳኔ
እስከሚሰጥ ድረስ ቀጣይ እንቅስቃሴ እንዲያቆም የሚገልጽ ማሰታወቂያ ለኮርፖሬሽኑ ይልካል፡፡
4. አቤቱታው የቀረበበት ኮርፖሬሽን አቤቱታውን ለማጣራት የሚያስፈልጉትን ንብረት ሽያጭ
የተፈፀመባቸው ሰነዶችና መግለጫ እንዲቀርቡለት ከቦርድ ጽህፈት ቤት ጥያቄ በቀረበለት 5 /አምስት/
የስራ ቀናት ውስጥ ማቅረብ ይኖርበታል
5. ቦርዱ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 4 የተጠየቁት ሰነዶች ከኮርፖሬሽኑ ሲቀርብለት ጉዳዩን ከአዋጅና ከዚህ
መመሪያ አኳያ በመመርመር ውሳኔውን በ 15 /አሰራ አምስት/ የስራ ቀናት ጊዜ ውስጥ በጽሁፍ መስጠት
አለበት፡፡ በጽሁፍ የተሰጠው ውሳኔ የውሳኔውን ምንነትና የሚወሰደውን እርምጃ የሚያሳይ መሆን
ይኖርበታል፡፡
6. ቦርዱ የሰጠው ውሳኔ ግልባጭ ውሳኔው በተሰጠ በ 5 /አምስት/ የስራ ቀናት ውስጥ አቤቱታውን ላቀረበው
ንብረት ገዢ አና ለመስሪያ ቤቱ እንዲደርስ ማድረግ አለበት፡፡

4.12.2 አቤቱታውን በፍርድ ቤት ስለማየት


በኮርፖሬሽኑ እና በቦርዱ ጽህፈት ቤት ውሳኔ ቅር የተሰኘ ንብረት ግዢ ጉዳዩን አግባብ ላለው ፍርድ ቤት
ሊያቀረብ ይችላል፡፡

ክፍል አምስት
5. ልዩ ድንጋጌ

22
5.1 መመሪያ ስለማሻሻል
በዚህ የንብረት አስተዳደር አፈፃፀም መመሪያ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ
ኢንዱስትሪ ክላስተር ልማት ኮርፖሬሽን ስራ አመራር ቦርድ ሲታመንበት መሻሻል ይችላል፡፡
5.1 መመሪያ የሚፀናበት ጊዜ
ይህ መመሪያ ከ ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ የፀና ይሆናል፡፡

አባተ ስጣታው
የኮርፖሬሽኑ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ

አባሪ ሰነዶች

የገቢ ዕቃ ደረሰኝ
Goods Receiving Note
የጽ/ቤት ስም____________
የእቃው ኮድ__________ ቀን _____________ የግዥ መጠየቂያ ቁጥር_________
የአቅራቢው ስም:_________________ Purchase requisition No._________
23
Supplier Name የግዥ ማዘዣ ቁጥር:_______ L/C ቁጥር ___________
Purchase Order No._____

የእቃው ምድብ____________________ የሽያጭ ደረሰኝ ቁጥር______________________ ቀን__________________________

Classification Suppliers Invoice No. Date


የውል ቁጥር_________________________

Contract No. ቀን______________


እቃው ከሌላ አካ የተላከበት ቁጥር___________
ቀን
Dispach Note No
Date

ተ.ቁ የእቃ መግለጫ የእቃ መለያ መለኪያ ብዛት የአንዱ ዋጋ ጠቅላላ ዋጋ


ቁጥር መግለጫ
I.No. Item Description Part/Serial Unit Quantity Unit Price Total Price Remark
No.

ድምር /Total
ያዘጋጀው ___________ አስረካቢ:_______ ተረካቢ:_________________
Prepared Delivered by Received by
ፊርማ/Signature_______ፊርማ/Signature_________ ፊርማ/Signature_________
ቀን/Date_________ ቀን/Date____________ ቀን/Date___________
የቅጂ ስርጭት

•ነጭ______________ፋይናንስ •አረንጎዴ_____ ለእቃ ግምጃቤት


White Finance Green Store
•ቢጫ____________ ለአቅራቢው •ሰማያዊ_________የፓድ ቀሪ
Yellow purchase/deliverer Blue Pad
•ቀይ_______ ለንብረት ምዝገባና ቁጥጥር
pink Stock record & controlling

ንብረት ማሰራጫ ቅጽ

24
ቀን/Date__________________________
የገቢ ሰነድ ቁጥር (GRN No.)_______________________
የተላካለት ጽ/ቤት __________________________________ የተረካቢ/የአሽከርካሪው ስም
Dispatched to Driver's Name
መለያ ቁጥር_____________________________________ የመታወቂያ ቁጥር
Address I.D. Number
ስልክ ሰሌዳ ቁጥር
Tel. Plate No.
የተሳቢ ሰሎዳ
Trailer
በዚህ ሰነድ የላክነው ንብረት በመልካም ሁኔታ መድረሱን እባኮ በገቢ ሰነድ ያለጋግጡልን
Please acknowledge the receipt of the following good's or items in confirmation of receiving inproper condition and send us your

የሂሳብ ኮድ የዓቃው ዓይነት መለያ ቁጥር መለኪያ/Unit of የአንዱ ዋጋ ጠቅላላ ዋጋ መግለጫ


ተ.ቁ.No /Code No. /Description P.No. Measurment ብዛት Quantity Unit Price Toltal Price Remark

አስረካቢ ያፀደቀው ተረካቢ


Dispatcher Approved by Received by
ስም_________________________ ስም_______________________ ስም_____________________________
Name Name Name
ፊርማ____________________ ፊርማ________________________ ፊርማ______________________
Signature Signature Signature
ቀን ____________________________ ቀን________________________ ቀን___________________________
Date Date Date

ስርጭት /Distribution ሰማያዊ-- በር መውጫ(1)


ነጭ- ሂሳብ Blue-gate pass
White- Finance
ቢጫ - ለንብረት ምዝገባና ቁጥጥር ቢጫ - ለንብረት ግምጃ ቤት
Yellow- stock recorded & controlling unit Yellow-store record (II)
ቀይ - የብረቱን ለተረከበው
Pink- Receiver ሮዝ - ፓድ
አረንጎዴው- ንብረቱ ለተላከለት አካል Pad
Green- Dispatching unit

የንብረት ወጪ ደረሰኝ

25
ወሳጅ /issued________________________________ ቀን /Date
የእስቶር መጠየቂያ ቁጥር/ Store Requisition No_______________________ ወጪ የሚመዘገብበት ክፍል/ስራ /cost
center_______________
የአንዱ
ዋጋ
የንብረቱ መለያ የእቃው ዓይነት
ወጪ የሚሆነው total
Code No. Description
ተቁ.S መለኪያ ብዛት Qty unit ጠቅላላ ዋጋ
/No. Unit issued price unit price መግለጫ Remark

ተረካቢ ____________________________ ፊርማ ___________________________ ቀን __________________________________


Received by Signature Date
አስረካቢ __________________________ ፊርማ________________________ ቀን____________________________
Issued By Signature Date
አፅዳቂ________________________ ፊርማ________________________ ቀን_____________________________
Approved by Signature Date
ስርጭት /Distributions
ነጭ__________________ሂሳብ ቢጫ________ ለንብረት ቁጥጥርና ምዝገባ
አረንጎዴ_________________ፓድ
white Finance Yellow Stock Record & Controlling unit
Green pad
ቀይ_______________ለተረካቢ ሰማያዊ 1 ____በር መውጫ ሰማያዊ
2_________________ፓድ
Pink Receiver Blue(I) Gate pass
Blue(II) Pad

የንብረት ወጪ መጠየቂያ (Store Requisition Form)


ጠያቂው /Requested by____________________________________Sig ________________________________

26
የስራ ክፍል ______________________________________________ SR NO._______________
ምክንያት/Purpose Of Request/_________________________________________

ቀን/Date_____________________

ተ.ቁ. የዕቃው መለያ ቁጥር መለኪያ የንብረት ኃላፊው ውሳኔ መግለጫ


ብዛት Qty.
S/No. አይነት/Description Part No. Unit Remark
የተፈቀደው ብዛት ፊርማ ቀን

ያፀደቀው ________________________ የፈቀደው _______________________


Approved By Authorized By______________________
ስርጭት/Distribution
ዋናው ቅጂ/Orignal:- ለግምጃ ቤት/Store Keeper /
አንደኛ ኮፒ /Copy/:-ፓድ/Pad/

ንብረት ማስተላለፊያ ቅጽ
Property Transfer Form
27
ከ___________________________________ ለ_____________________________
From_____________________________________________________________________________________________________________
የአስረካቢ ስራ ክፍል የተረካቢ ስራ ክፍል
የአንዱ ጠቅላላ
ገቢ የሆነው ብዛት Qty. ዋጋ ዋጋ
የንብረቱ ዓይነት Item Received Unit Total
ተ.ቀ. Description መለኪያ Unit Price Price መግለጫ Remark

Yadanoo_____________________________________________________________________________________________________________________________________________

________________________________________________________________________________________________________________________________________________________

አስተላላፊ_______________________ _________________________ ________________________________


Transferer ስም/Name ፊርማ/Signature ቀን/Date
ተረካቢ ______________________ ________________________ _________________________________
Received ስም/Name ፊርማ/Signature ቀን/Date
1.ነጭ -ሂሳብ 3.ቀይ-ለአስተላላፊ 5.ሰማያዊ-ንብረት ግምጃ ቤት
ስርጭት White -Finance Pink- Originator Blue - Warehouse

Document
Destribution 2.ቢጫ-ለተረካቢ 4. አረንጎዴ- ንብረት ቁጥጥርና ምዝገባ
Yellow-Receivers Green Record& Control

ወራዊ ንብረት የሪፖርት ቅጽ


Weekly Report Format
የአንዱ
Quantity
የዕቃው ዓይነት መለኪያ ዋጋ መግለጫ
ተ.ቁ. No.
Description Unit Unit Remark
Price የዞረ ሚዛን የወሩገቢ የወሩ የክምችት ሚዛን
28
ወጪ
BBF Supply Issue Stock Balance
d

ያዘጋጀው እቃ ግምጃ ቤት ያረጋገጠው ያፀደቀው

በንብረት መጠየቂና ማዘዣ ላይ የሚፈርሙ ኃላፊዎች ፊርማ ናሙና


ስልክ
ተ.ቁ. የኃላፊው ሙሉ ስም በኮርፖሬሽኑ የስራ ድርሻ የስራ ታ የሙሉ ፊርማ ናሙና የፓራፍ ናሙና ቁጥር
1 2 3

29
30
የቁሚ ንረት መዝገብ (Fixed Asset Registration Book )
ጽ/ቤት/ፕሮጅቸት__________________________________
ገጽ_____________
የንብረቱ ጠቅላላ መረጃ መግለጫ (General Information of Equipment)
ንብረቱ የአገልግሎ የሚዘኝ
ተ.ቁ. የንብረቱ ሰሌዳ የንብረቱ ኮድ የተገዛበት ወቅታዊ በስጦታ ት ዘመን መት ቦታ ተጨማሪ
(Ite ዓይነት ሞድል ቁጥር የኮርፖሬሽኑ ዘመን የተገዛበት ዋጋው የተገኘበት (Expecte (Current መረጃዎች ስለ
m (Item (Model (Plate ( corporation (Purchased ዋጋ(Purchas (Current ቀን/ገቢ d life Location (Additional ሞተሩ
No.) Discription ) ) No.) code NO.) Year) ed Value) Value) የሆነበት time) ) Information) (Engine)

የሻንሲ
የአምራቹ ቁጥር የተመረተ የሞተሩ ንብረቱ
መለያ (Transm በት ቁጥር የሞተር አምራች የሚገኝበት
የንብረቱ ቁጥር ission (Country ቁጥር መለያ ሁኔታ
ቀለም (Serial Serial of (Horse (Serial ሞድል( (Status of
(colour) Number) No.) Origin) Power) No.) Model) the Item)

1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17

31
ክፍል አራት

4. የኮርፖሬሽኑ ተሽከርካሪ አመዘጋገብ፣ ስምሪት፣


አጠቃቀም እና ቁጥጥር

4.1 ስለኮርፖሬሽኑ ተሽከርካሪዎች የህይወት ታሪክ ምዝገባ

4.1.1 የመንግስት መ/ቤት በግዥ፣ በስጣታ፣ በዝውውር… ወዘተ ተረክቦ ለሚጠቀምበት


ለእያንዳንዱ ተሽከርካሪ የለየ የግል ማህደር በመክፈት በማህደሩ ውስጥ ቢያንስ
የሚከተሉትን መረጃዎች መዝግቦ ይይዛል፡፡

ሀ/ የተሽርካሪውን ዓይነትና ሞዴል

ለ/ የጭነቱ ልክ በሰው፣ በኩንታል፣ በኪዩቢክ ሜትር ወይም በሊትር ተለይቶ

ሐ/ የቻሲና የሞተር ቁጥሮች

መ/ የሚጠቀመው የነዳጅ ዓይነት

ሠ/ የተገዛበት ወይም በመ/ቤቱ ባለቤትነት ሥር የዋለበት ቀንና ዓመተ ምህረት

ረ/ የተሽከርካሪው ዋጋ እና

ሰ/ የባለቤትነት መታወቂያ ደብተር ቁጥር

4.1.2 በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 የተጠቀሱት መረጃዎች በበቂ ምክንያት ተሟልተው

ያልተገኙ እንደሆነ ባሉት መረጃዎች መሰረት ርክክብ ከተፈፀመ በኋላ ኮርፖሬሽኑ

ያልተገኙትን መረጃዎች ዝርዝርና ምክንያት በተሽከርካሪው የህይወት ታሪክ ውስጥ

መዝግቦ ይይዞል፣ ያልተሟሉትን መረጃዎችም ተከታትሎ እንዲሟሉ ያደርጋል፡፡

4.1.3 የእያንዳንዱ የመንግስት ተሽከርካሪ የህይወት ታሪክ መዝገብ የተሽከርካሪው ርክክብ

ከተፈፀመበት ጊዜ ጀምሮ እስኪወገድ ድረስ በኪሎ ሜትር፣ የሚጠቀመውን የነዳጅ ዘይት

እና ቅባት ፍጆታ መጠን፣ የጥገና ወጪ፣ የተጓዘው ኪ.ሜ መጠን፣ በእነማን ይዞታ ስር

እንደነበር … ወዘተ አካቶ መያዝ አለበት፡፡

4.1.4 የተሽከርካሪው የህይወት ታሪክ መዝገብ ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ እየተፈተሸ ወቀታዊ

መደረግ ይኖርበታል፡፡

4.2. ስለኮርፖሬሽኑ ተሽከርካሪዎች ስምሪት

32
4.2.1 የዋና ስራ አስኪያጅ የኮርፖሬሽኑ ተሽርካሪዎች በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ እንዲውሉ

ማድረግ የሚያስችል የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋት አለበት፡፡

4.2.1 የዋና ስራ አስኪያጅ ለጋራ አገልግሎት፣ በልዩ የሥራ ባህሪያቸው ተሽርካሪ ለሚያስፈልጋቸው

የሥራ ኃላፊዎች፣ ለክላስተር ጽ/ቤቱ፣ ለሥራ ክፍል እና እንዲሁም ለመስክና የከተማ

አገልግሎት የሚውሉ የኮርፖሬሽኑ ተሽከርካሪዎችን ለይተው ሊመድቡ ይችላል፡፡

4.2.2 ለጋራ አገልግሎትና በሌሎች አግባቦች የሚመድባቸውን ተሽከርካሪዎች ስምሪት በዕቅድና

በፕሮግራም ለመምራትና እያንዳንዱን ስምሪት በውጤት ላይ ተመስርቶ ለመመዘን

የሚያስችለውን ዝርዝር የአፈፃፀም ሥርዓት ዘርግቶ ተግባራዊ እንዲሆን ያደርጋል፡፡

4.2.3 ለበላይ ኃላፊዎችና ኃላፊዎች ከተመደቡት በዋና ስራ አስኪያጁ ወይም ከወከለው አካል ልዩ

ፈቃድ ሳይሰጥ ወይም ለመስክ ስራ እንዲንቀሳቀሱ ከተፈቀደላቸው ተሽከርካሪዎች በስተቀር

በሥራ ቀንም ሆነ በዕረፍት ቀን የኮርፖሬሽኑ ተሽከርካሪዎችን ከከተማ ክልል ውጪ

ማሽከርከር የተከለከለ ነው፡፡

4.2.4 የኮርፖሬሽኑ ሠራተኞች ለመስክ ሥራ ሲወጡ በሥራው ባህርይ ወይም ወጪ ቆጣቢ

አማራጭ በመሆኑ ምክንያት በኮርፖሬሽኑ ተሽከርካሪ መጠቀማቸው አስፈላጊ ካልሆነ

በስተቀር የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪን ወይም የአየር ትራንስፖርትን እንዲጠቀሙ

መደረግ ይኖርበታል፡፡

4.3 ስለኮርፖሬሽኑ ተሽከርካሪዎች አጠቃቀምና ጥበቃ


4.3.1 ማንኛውም የኮርፖሬሽኑ ተሽከርካሪ ተረክቦ የሚያሽከረክር ሾፌር ወይም ኃላፊ

ተሽከርካሪውን ከማንቀሳቀሱ በፊት የተሽከርካሪው የውስጥ እና የውጭ አካላት ችግር

የሌለባቸው መሆኑን፣ በተለይም በተሽከርካሪው ላይ ያሉ ዕንከን አመልካቾችን ማለትም

የሞተር ዘይት መጠን፣ የፍሬን ሁኔታ …ወዘተ አስቀድሞ በጥንቃቄ በማየት ተሽከርካሪው

ለእንቅስቃሴ ዝግጁ መሆነን ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡

4.3.2 ማንኛውም አሽከርካሪ በሚያሽከረክረው ተሽከርካሪ ላይ ብልሽት ወይም የብልሽት ምልክት

ሲያይ ተጨማሪ ወይም የባሰ ብልሽት ከማጋጠሙ በፊት ወዲያውኑ ለኮርፖሬሽኑ

የሚመለከተው የሥራ ክፍል ማሳወቅ አለበት፡፡

4.3.3 ማንኛውም ለጋራ አልግሎት የተመደበ ተሽከርካሪ በልዩ ሁኔታ ካልተፈቀደ በስተቀር

ከመደበኛ የሥራ ሰዓት ውጪ በማንኛውም ጊዜ ከኮርፖሬሽኑ ቅጥር ግቢ ወይም


33
በኮርፖሬሽኑ ከሚታወቅ መንግስታዊ ወይም ሕዝባዊ ተቋም የማቆሚያ ሥፍራ ውጪ

እንዲያድር አይፈቀድም፡፡

4.3.4 በበላይ ኃላፊዎችና ከሚሽከረከሩ ወይም በኮርፖሬሽኑ በተፈቀደው መሠረት በተለየ ሰሌዳ

ከሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች በስተቀር ማናቸውም ተሽከርካሪ በሁለቱም ፊት በሮች ጐን

ላይ የኮርፖሬሽኑ ስም የሚያመለክት መለያ ወይም አርማ መለጠፍ አለበት፡፡

4.3.5 በሚመለከተው አካል በልዩ ሁኔታ ካልተፈቀደ በስተቀር በማንኛውም ተሽከርካሪ ላይ

ከተፈቀደለት ሰሌዳ ውጪ ሌላ ማንኛውንም ዓይነት ሰሌዳ ቀይሮ መለጠፍ አይፈቀድም፡፡

4.3.6 4.3.6 ማንኛውም ለጋራ አገልግሎት እና ለመስክ ሥራ የተመደበ ተሽከርካሪ ከተመደበበት

ሥራና የሥራ ቦታ ውጪ ሊንቀሳቀስ ወይም ለግል መጠቀሚያ ሊውል አይችልም፡፡

4.3.7 በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 3.6 አፈፃፀም በመስክ ሥራው የተሰማሩ ኃላፊዎች፣ ሠራተኞች

እና አሽከርካሪው የጋራ ኃላፊነት አለባቸው፡፡

4.3.8 ለበላይ ኃላፊዎች እና ለኃላፊዎች የተመደቡ ተሽከርካሪዎች ካልሆኑ በስተቀር በማናቸውም

ጊዜ ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ሲደረግ አገልግሎት ጠያቂው /አሽከርካሪው/ አግባብ ባለው

ኃላፊ የተፈረመ የመዘዋወሪያ ፈቃድ መያዝ ይኖርበታል፡፡

4.3.9 የኮርፖሬሽኑን ተሽከርካሪዎች እንዲያሽከረክሩ የሚፈቀድላቸው ኃላፊዎች በኮርፖሬሽኑ

የበላይ ኃላፊ ወይም በተወካዩ የተፈረመ ልዩ መታወቂያ ካርድ መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

ክፍል አምስት

ስለተሽከርካሪዎች ነዳጅ፣ ቅባት፣ ዘይት እና


መለዋወጫ ዕቃዎች አጠቃቀም፣ ቁጥጥር እና ሥርጭት

5 የኮርፖሬሽኑ ተሽከርካሪዎች ነዳጅ፣ ቅባት እና ዘይት አጠቃቀም እና ቁጥጥር

5.2 መ/ቤቶች የተሽከርካሪዎችን የነዳጅ ፍጆታ ለመከታተልና መዝግቦ ለመያዝ እንዲረዳው

የተሽከርካሪዎች የኪ/ሜ ቆጣሪ ጌጅ የተሟላና በትክክል የሚሰራ መሆኑን በየጊዜው በመከታተል

ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡

34
5.3 ለበላይ ኃላፊዎች አና ለኃላፊዎች ከሚመደቡ ተሽከርካሪዎች በስተቀር እያንዳንዱ ተሽከርካሪ

የፈጀው የነዳጅ መጠን ከሸፈነው የኪ.ሜትር መጠን ጋር እየተመዘገበ ተገቢው ሪፖርት በየወሩ

መቅረብ ይኖርበታል፡፡

5.4 የኮርፖሬሽኑ ኃላፊዎች አገልግሎት ተሽከርካሪዎች የሚውለው ነዳጅ፣ ቅባትና ዘይት የመሳሰሉት

ከውጤት ጋር በተገናዘበ መልኩ ስለሚሰራጩበት መንገድ ተጨማሪ ዝርዝር የውስጥ አሠራርና

የቁጥጥር ሥርዓት ይዘረጋሉ፡፡ በየወሩም ሪፖርት እንዲቀርብ በማድረግ ተገቢውን የአፈፃፀም

ግምገማ ያካሂዳል፡፡

6 የተሽከርካሪዎች መለዋወጫ ዕቃ አጠቃቀም እና ቁጥጥር

6.2 ማንኛውም አሽከርካሪ ወይም በራሱ እንዲያሽከረክር የተፈቀደለት ኃላፊ ያረጃ ጎማና ቸርኬን

ጨምሮ የመለዋወጫ ዕቃ በአዲስ እንዲተካለት ሲጠይቅና የጥያቄው ትክክለኛነት አግባብ ባለው

ባለሙያ ሲረጋገጥ በአዲስ እንዲተካለት የሚደረግ ሲሆን የተቀየረው መለዋወጫ ዕቃ ወደ ዕቃ

ግምጃ ቤት ተመላሽ ተደርጎ ይቀመጣል፡፡

6.3 በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 5.1 መሠረት ወደ ዕቃ ግምጃ ቤት ተመላሽ የሚደረገው የመለዋወጫ

ዕቃ መለያ ቁጥር (Serial Number) ከዕቃ ግምጃ ቤት በሚላከው መረጃ መሰረት ቀደም ሲል

ከተመዘገበበት መዝገብ ጋር ተመሳክሮ ሲረጋገጥ ያገለገሉ እቃዎች ወደሚከማቹበት ቦታ እንዲላክ

ይደረጋል፡፡ የመለዋወጫ ዕቃው መለያ ቁጥርም በተሽከርካሪው የግል ማህደር ውስጥ ተመዝግቦ

እንዲቀመጥ መደረግ አለበት፡፡

6.4 ከግምጃ ቤት ውጪ የተደረገው መለዋወጫ በተሽከርካሪው ላይ በትክክል መገጠሙ በጠቅላላ

አገልግሎት ክፍሉ ወይም አግባብነት ባለው ባለሙያ መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡

6.5 ኮርፖሬሽኑ የራሱ ጋራዥ ስለሌለው የጥገና አገልግሎት ከሚሰጠው ከተመረጠው ጋራዥ ጋር

የመለዋወጫ ዕቃ አቅርቦትንም ሲያገኝ ከሆነ የተለወጠው የመኪና ዕቃ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ

5.1 ላይ በተገለፀው መሠረት ለዕቃ ግምጃ ቤት መመለስ ይኖርበታል፡፡

ክፍል ሁለት

የኮርፖሬሽኑእና አሽከርካሪዎች ኃላፊነት

7 የኮርፖሬሽኑ ኃላፊነት

35
7.2 የኮርፖሬሽኑ ተሽከርሪዎች የህይወት ታሪክ፣ የተሽከርካሪዎችን የስምሪት ሪፖርት፣ የተሽከርካሪዎች

የነዳጅ እና የጥገና ወጪን ዝርዝር በትክክል መዝግቦ ይይዛል፡፡

7.3 ተሽከርካሪዎች ከተመደቡበት ዓላማ ውጪ ለሌላ አገልግሎት እንዳይውሉ ተገቢውን ቁጥጥርና

ክትትል ያካሂዳል፡፡

7.4 ተሽከርካሪ ተረክበው የሚያሽከረክሩ የኮርፖሬሽኑ አሽከርካሪዎችም ሆኑ የሥራ ኃላፊዎች ሥልጣን

ባለው አካል የተሰጠና አግባብነት ያለው የታደሰ የማሽከርከር ፈቃድ ያላቸው መሆኑን ያረጋግጣል፡፡

7.5 በተሽከርካሪዎቹ የግል ማህደር ውስጥ ከሚመዘገበው ሬከርድ በመነሳት ተሽከርካሪዎች ወቅታቸው

ተጠብቆ ሰርቪስ እንዲደረጉና ተገቢውን ጥገናና እንክብካቤ እንዲያገኙ ያደርጋል፡፡

7.6 ተሽከርካሪዎች የትራንስፖርት ባለሥልጣን በሚያወጣው ፕሮግራም መሠረት ዓመታዊ የቴክኒክ

ምርመራ እንዲያገኙ ያደርጋል፡፡

ተሽከርካሪዎች ወቅቱን የጠበቀ የኢንሹራንስ ሽፋን እንዲያኙ ያደርጋል፡፡

7.7 ተሽከርካሪዎች ተገቢውን የእሳት አደጋ መከላከያ፣ ክሪክ፣ መፍቻዎችና የመሳሰሉት እንዲኖሩዋቸው

ያደርጋል፡፡

7.8 በኃላፊነቱ ስር ያሉትን ተሽከርሪዎች ብዛት፣ ዓይነት፣ የሚገኙበትን ሁኔታ… መዘተ የመሳሰሉትን

መረጀዎች በማጠናቀር የበጀት ዓመቱ እንደተጠናቀቀ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለመንግስት ግዥና

ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ሪፖርት ያቀርባል፡፡

8 የኮርፖሬሽኑአሽከርካሪዎች ኃላፊነት

ማንኛውም አሽከርካሪ ወይም ተሽከርካሪ የተመደበለት ኃላፊ የሚከተሉት ኃላፊነቶች አሉበት

8.2 የትራፊክ ደህንነት ደንብና መመሪያን አክብሮ ማሽከርከርና ተሽከርካሪውን ለተመደበለት ዓላማ

ብቻ ማዋል፡፡

8.3 የትራንስፖርት ሕግና ደንብን በመተላለፍ በተሽከርካሪው ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመከላከል

እንዲቻል በኃላፊነት የተረከበው ተሽከርካሪ በጥንቃቄና በእንክብካቤ መያዝ፣

8.4 ተሽከርካሪው ለእንቅስቃሴ ዝግጁ መሆኑን ከማረጋገጥ አንፃር የሞተር ዘይት፣ የፍሬን ዘይት፣ የጎማ

ሁኔታ እና ሌሎችም ከተሽከርካሪው ደህንነት ጋር በተያያዘ መፈተሽ የሚገባቸውን ጉዳዮች

በየጊዜው መፈተሽ፣

36
8.5 በማያሽከረክረው ተሽከርካሪ ላይ ብልሽት፣ ስርቆት ወይም አደጋ ከደረሰ በአካባቢው ለሚገኝ

ፖሊስና ለመ/ቤቱ ለሚመለከተው የሥራ ክፍል ወዲያውኑ ዝርዝር ሪፖርት በስልክ ወይም በጽሁፍ

ማቅረብ፣

8.6 የተረከበውን ተሽከርካሪ በጥንቃሴ እና በእንክብካቤ መያዝ እና ተሽከርካሪው ብልሽት ካጋጠመው

ወይም ብልሽት መኖሩን የሚጠቁሙ ምልክቶችን ሲያይ ተሽርካሪውን ከነችግሩ ከማሽከርከር

መቆጠብና በወቅቱ አግባብነት ላለው የሥራ ክፍል ሪፖርት ማድረግ፣

8.7 አልኮል መጠጥ ወይም አደንዛዥ ዕፅ ወስዶ ከማሽከርከር መቆጠብ

8.8 የኮርፖሬሽኑን ተሽከርካሪ ለማሽከርከር ለተፈቀደለት አሽከርካሪ ካልሆነ በስተቀር በኃላፊነት

የተረከበውን ተሽከርካሪ በማንኛውም ሁኔታ ለሌላ አሽከርካሪ አሳልፎ አለመሰጠት፣

8.9 የትራንስፖርት ሕግና ደንብ በመተላለፍ በተሽከርካሪው ላይ ለሚደርስ ጉዳት ኃላፊና ተጠያቂ

መሆኑን በመገንዘብ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ

ክፍል አምሰት

ልዩ ልዩ

9 ሌሎች ድንጋጌዎች እና ቅፆች

9.2 በመንግሥት ንብረት አሰተዳደር መመሪያ ቁጥር 9/2003 ላይ ስለመንግሥት ንብረት አስተዳደርና

አወጋገድ የሚደነግጉ አንቀፆች፣ በሥሪ ላይ ያሉት የመንግሥት የቋሚ ንብረት አስተዳደር እና የስቶክ

37
አስተዳደር ማንዋሎች እንደአግባብነታቸው ለመንግስት ተሽከርካሪዎች አስተዳደርም ተፈፃሚነት

ይኖራቸዋል፡፡

9.3 የመንግስት መ/ቤቶች ከዚህ መመሪያ ጋር አባሪ የሆኑትን ቅፆች መጠቀም አለባቸው፡፡

10 የተሻሩ መመሪያዎች

10.2 ከመንግሥት ተሽከርካሪ አስተዳደር ጋር በተያያዘ ቀደም ሲል የወጡና በሥራ ላይ ያሉ መመሪያዎች

ከዚህ መመሪያ ጋር የሚቃረኑ እስከሆኑ ድረስ ተፈፃሚነት አይኖራቸውም፡፡

10.3 መ/ቤቶች በኃላፊነታቸው ሥር የሚገኙ ተሽከርካሪወችን ለመቆጣጠር ያወጧቸው የተሽከርካሪ

አስተዳደር የውስጥ መመሪያዎች ከዚህ መመሪያ ጋር የማይቃረኑ እስሆኑ ድረስ በተጓዳኝ

ሊሰራባቸው ይችላል፡፡

11 መመሪያው የሚፀናበት ጊዜ
ይህ መመሪያ ከ ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ የፀና ይሆናል፡፡

አባተ ስጣታው
የኮርፖሬሽኑ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ

38
አባሪዎች

ቅጽ 01

የመንግስት ተሽከርካሪዎችና ተጓዳኝ ዕቃዎች መረከቢያ

1. የመንግስት መስሪያ ቤቱ ስም

2. የተሽርካሪው፣

2.1 ሞዴል 2.2 የቻሲ ቁጥር

2.3 የሞተር ቁጥር 2.4 ሲሲ

2.5 የተገዛበት ዋጋ 2.6 የተገዛበት ቀን እና ዓ.ም

2.7 የሰሌዳ ቁጥር 2.8 የሚጠቀመው የነዳጅ ዓይነት

2.9 የመጫን ችሎታው ሰው ኩንታል ሊተር

2.10 የባለቤትነት መታወቂያ ደብተር ቁጥር

2.11 መኪናው ላይ የተነበበው ኪ.ሜትር


39
3. ከተሽከርካሪ ጋር የሚገኙ ተጓዳኝ ዕቃዎች

ተ.ቁ የዕቃው ዝርዝር ብዛት ተ.ቁ የዕቃው ዝርዝር ብዛት


3.1 3.7
3.2 3.8
3.3
3.4
3.5
3.6
4. ተሽከርካሪው አሁን የሚገኝበት ሁኔታ

የተጠቀሰውን ተሽከርካሪ ስረከብ ከላይ የተዘረዘሩትን መፍቻዎችና ዕቃዎች እንዲሁም የተሽከርካሪውን ሁኔታ

አይቼ መሆኑን አረጋግጣለሁ

የተረካቢው ስም ፊርማ ቀን

የአስረካቢው ስም ፊርማ ቀን

የአረካካቢው ስም ፊርማ ቀን

ማሳሰቢያ፡- ይህ ቅጽ በአራት ቅጅ ተሞልቶ፣ የመጀመሪያው ቅጅ ለተረካቢው፣ ሁለተኛው ቅጅ ለአስረካቢው፣ ሦስተኛ


ቅጅ ስምሪት ፍል፣ አራተኛው ቅጅ ለንብረት አስተዳደር ይሰጣል፡፡

40
ቅጽ 02
የመንግስት ተሽከርካሪ ዕለታዊ የነጃጅ፣ የዘይትና የኪ.ሜ መመዝገቢያ
የመስሪያ ቤቱ ስም የወር ዓ.ም

የሰሌዳ የነዳጅ/ዘይት ሁኔታ 1 ቀኖች 30


ቁጥር ዓይነት

ነዳጅ በኩፖን

የሞተር ዘይት

የፍሬን ዘይት

የጥራስ ጥርስ
ዘይት

ግሬስ

የሞተር ዘይት

የፍሬን ዘይት

የጥራስ ጥርስ
ዘይት

ግሬስ

የመዝጋቢው ሥም ፊሪማ ቀን

ማሳሰቢያ፡- ይህ ቅጽ የነዳጅ ማደያ ዲፖ ላላቸው የመንግስት መ/ቤቶች እንዲሁም በተለያዩ ማደያዎች ነደጅ ለሚቀዱ በካርድ ፎርም ታትሞ የየዕለቱ ፍጆታ የሚመዘገብበት ካርድ ነው፡፡

ቅጽ 03

41
የመንግስት ተሽከርካሪ ወርሀዊ የነዳጅ፣ የዘይትና የጥገና ወጪ ማጠቃለያ

የመ/ቤቱ ሥም

በወሩ በአማካ በወሩ ውስጥ የወሩ


በወሩ የተቀዳለት የተገጠመለት የጥገና የጎማ ጥገና
ውስጥ ኝ የተሞላለት የወሩ ጠቅላላ የታየ የጋራዥ
ውስጥ ጠቅላላ የነዳጅ የመለዋወጫ አገልግሎት የጎማ ዋጋ አገልግሎት ወጪ በኪ/ሜ
የሠሌዳ የጓዘው በሊትር የዘይት ዋጋ ወጪ የብልሽት ምልልስ
ተ.ቁ የተቀዳ ዋጋ ዕቃዎች ዋጋ የዕጅ ዋጋ ዋጋ ምርመራ
ቁጥር ጠቅላ የተጓዘ ዓይነት ብዛት
ነዳጅ
ላ ው ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ
በሊትር
ኪ.ሜ ኪ.ሜ

ያዘጋጀው ስም ፊርማ ቀን

ያፀደቀው ስም ፊርማ ቀን

ማሳሰቢያ ይህ ቅጽ በሦስት ተሠርቶ፣ የመጀመሪያ ቅጅ ለመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ ይቀርባል፣ ሁለተኛው ቅጅ ለመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ይላካል፣ ሦስተኛው ቅጅ
በትራንስፖርት ስምሪት ይቀመጣል፡፡

42
ቀጽ 04

የመንግስት ተሽከርሪዎች ህይወት ታሪክ መመዝገቢያ

1. የመንግስት መስሪያ ቤቱ ስም

2. የተሽከርካሪው

2.1 ሞዴል 2.2 የቻሲ ቅጥር

2.3 የሞተር ቁጥር 2.4 ሲሲ

2.5 የተገዛበት ዋጋ 2.6 የተገዛበት ቀን እና ዓ.ም

2.7 የሰሌዳ ቁጥር 2.8 የሚጠቀመው የነዳጅ ዓይነት

2.9 የመጫን ችሎታው ሰው ኩንታል

2.10 የላቤትነት መታወቂያ ደብተር ቁጥር

የመለዋወጫ የሠራተኛ የጐማ የጐማ ጥገና ውጪ የጋራዥ


የተቀዳው በሊትር የነዳጅ ዋጋ ዘይት ጠቅላላ ወጪ
ተ.ቁ ቀን ኪ.ሜ ዕቃ ዋጋ ዕጅ ዋጋ መግዣ ዋጋ ዋጋ በኪ/ሜ ምልልስ ምርመራ
ነዳጅ የተጓዘው
ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብር ሣ ብዛት

43
ማሳሰቢያ፡- ይህ ቅጽ በአንድ ኮፒ ተሠርቶ ከተሽከርካሪው የሕይወት ታሪክ ማህደር ጋር ተያይዞ መቀመጥ ይኖርበታል፡፡ በየወሩ መጨረሻ ከቅጽ 03 ጋር በማወራረስ ወርሀዊ ሪፖርት መራት

አለበት፡፡

44
ቅጽ 05

የመንግስት ተሽከርካሪዎችን ለተጠቃሚዎች መመደቢያ

የህ ቅጽ የሚሞላው አዲስ የተገዛን ወይንም ነባር ተሽከርካሪን ከአንድ የሥራ ሂደት ወደ ሌላ አዛውሮ መመደብ
ሲያስፈልግ ነው

1. የመንግስት መስሪያ ቤቱ ስም

2. የተሽርካሪው

2.1 ሞዴል 2.2 የቻነሲ ቁጥር

2.3 የተገዛበት ዋጋ 2.4 ሲሲ

2.5 የተገዛበት ዋጋ 2.6 የተገዛበት ቀን እና ዓ.ም

2.7 የሰሌዳ ቁጥር 2.8 የሚጠቀመው የነዳጅ ዓይነት

2.9 የመጫን ችሎታው ሰው ኩንታል

2.10 የባለቤትነት መታወቂያ ደብተር ቁጥር

3. ተሽከርካሪው በቋሚነት የተመደበለት

3.1 የሥራ ሂደት

3.2 የፕሮጀክት

3.3 የሥራ ጠባይ ሁኔታ ለ

3.4 ለጋራ አገልግሎት

የመሥሪያ ቤቱ ኃላፊ

ውሳኔ

ስም ፊርማ ቀን

ማሳሰቢያ፡- 1 ይህ ቀጽ የሚሞላው አዲስ የተገዛ ተሽከርካሪ ለተጠቃሚ ሲመደብ ወይም ነባር ተሽከርካሪ ከአንድ የስራ

ሂደት ወደሌላ እንዲዛወር ሲወሰን ነው፡፡


45
3. በሁለት ቅጅ ተዘጋጅቶ፣ የመጀመሪያው ቅጅ በተሽከርካሪው የግል ማህደር ውስጥ ይቀመጣል፣ ሁለተኛው ቅጅ

ለተጠሟ ይሰጣል፡፡
ቅጽ 06

የመንግስት ተሽከርካሪ አገልግሎት መጠየቂያና የመዘዋወሪያ ፈቃድ መስጫ

1. የመሥሪያ ቤቱ ሥም የሠሌዳ ቁጥር

2. የተጓዡ ሥም ሀ. ለ.

ሐ. መ.

3. የሚሄዱበት ሥፍራ

4. ምክንያት

5. አገልግሎቱ የሚፈለግበት ጊዜ ከ እስከ

የጠያቂው ስመና ፊርማ የጠያቂው ኃላፊ ስምና ፊርማ የፈቀደው ኃላፊ

ቀን የተነሳበት የተመለሰበት የጫነው ዕቃ የጫነው አተሽከርካሪው የተቆጣጣሪው ፊርማ


የሰው በአንድ ሊትር
የኪ.ሜ
የእቃው ብዘት ነዳጅ
ቦታ ኪ.ሜ ሰዓት ኪ.ሜ. ሰዓት ልዩነት ክብደት የሚሸፍነው
ዓይነት ኪ.ሜ

ከዚህ በላይ የተሰጠውን ትዕዛዝ በትክክል መፈፀሜን አረጋግጣለሁ

የሾፌሩ ስም ፊርማ ቀን

ማሳሰቢያ

1. ይህ ቅጽ በአንድ ቅጅ ከተሰራ በኃላ ከተሽከርካሪው ጋር እንዲዘዋወር ለሹፌሩ ይሰጥና፣ አገልግሎት ሲያበቃ


ለሚመለከተው ተቆጣጣሪ ስራ ክፍል ያስረክባል
2. ይህ ቅጽ ከሥራ ሰዓት ውጭ እና በበዓላት ቀናት ለሚሰጥ አገልግሎትም በተጨማሪነት ያገለግላላ፡፡
3. ይህንን በተመለከተ የመስሪያ ቤቱ የሚመለከተው ተቆጣጣሪ ስራ ክፍል ኃላፊ አለበት፡፡

46
ቅጽ 07

ልዩ መታወቂ

ስማቸው፣ ፎቶግራፋቸው እና ፊርማቸው በዚህ መታወቂያ ካርድ ላየ የሚታየው የስራ ኃላፊ ንብረትነቱ የ
………………………………….. መስሪያ ቤት የሆነውን ተሽከርካሪ እንዲያሽከረክሩ ተፈቅዶላቸዋል፡፡

ፈቃዱን የሰጠው ባለሥልጣን ስም …………………………

ፊርማ…………………………

ማሳሰቢያ፡- ይህ የፈቃድ ወረቀት ወድቆ ቢገኝ በሚከተለው አድራሻ የላኩልን፡፡

ፖስታ ሳጥን ቁጥር ………………………..

ስልክ ቁጥር ………………………………..

እናመሰግናለን

47
ቅጽ 08

የተሽከርካሪ ነዳጅ፣ ዘይት፣ ቅባትና የእጥበት አገልግሎት መጠየቂያ

ቀን
ከ ዳይሬክቶሬት

ለግዥ፣ ንብረት አስተዳደር እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት

የሰሌዳ ቁጥር የተሽከርካሪው ዓይነት ሲጠየቅ በቆጣሪው ላይ የታየ ኪ.ሜትር ንባብ

የተጠየቀበት ምክንያት

የጠየቀው የተሞላው የአሽከርካሪው


ዓይነት የማደያው ስም ምርመራ
ፊርማ
ብዛት ብር ብዛት ብር
የነዳጅ ቤንዚን

ነዳጅ ናፍጣ
የሞተር ዘይት
የፍሬን ዘይት
የጥርሳ ጥርስ ዘይት

ግሬስ
የእጥበት አገልግሎት

የጠያቂው ስም ፊርማ ቀን

በስምሪት ስራ ክፍል የሚሞላ

 ቀድሞ የተፈቀደው ነዳጅ ብዛት


 ቀድሞ ሲቀዳ የነበረው ኪ.ሜ ንባብ
 አሁን ያለው ኪ.ሜ.ንባብ
 ተሽከርካሪው በሊትር የሚጓዘው ኪ.ሜ
 በተሽከርካሪው ውስጥ የቀረው ነዳጅ በሊትር
 የተፈቀደለት ነዳጅ በሊትር
 ያዘጋጀው ስም ፊርማ ቀን

የፈቃጁ ስም ፊርማ ቀን

48
ማሳሰቢያ፡- ይህ ቅጽ በሁለት ቅጅ ከተሠራ በኋላ፣ የመጀመሪያው ቅጅ በተሽከርካሪ ስራ ክፍል ይቀመጣል፡፡ ሁለተኛው ቅጅ
በጠያቂው/በተጠቀሚው ስራ ክፍል ይያዛል፡፡

ቅጽ 09

የመንግስት ተሽከርካሪ የጥገና መጠየቂያ

የመሥሪያ ቤቱ ሥም ቀን

የሠሌዳ ቁጥር የተሽከርካሪው ዓይነት
ተሽከርካሪው የሚከተሉት ብልሽቶች ስላሉት ተመርምሮ እንዲጠገንልን እንጠይቃለን፡፡

የብልሽቱ ዓይነት

ብልሽቱን የገለፀው አሽከርካሪ ወይም ሹፌር

ሥም ፊርማ ቀን

እነድንጋይ ኳሱ

49
ቅጽ 10

የመንግስት ተሽከርካሪዎች የጥገና የሥራ ትዕዛዝ

የሰሌዳ ቁጥር የተሽከርካሪው ዓይነት የተመደበበት የስራ ክፍል የኪ.ሜትር ንባብ

የብልሽት ዓይነት ____________________________________________________


ጥገናውን ለማከናወን የተረካቢው ባለሙያ ስም ___________________ ፊርማ ___________
የተረከበበት ቀን_____________ ሰዓት ___________

የተመደበው ባለሙያ ሠራተኛ


የጥገና
ተ.ቁ የተሠራው ስራው
ቀን የባለሙያው ሥም
የወሰደው
የሰዓት ክፍያ ብር ሣ
ጊዜ

ድምር ድምር

50
ማሳሰቢያ፡- ይህ ቅጽ ጋራዥ ላላቸው የመንግስት መ/ቤቶች ወይንም ድርጅቶች የጥገና የሥራ ትዕዛዝ
የሚሞላበት ሲሆን ቅፁ በሁለት ቅጅ ተዘጋጅቶ የመጀመሪያው ቅጅ ለጥገና ክፍል ሁለተኛው ቅጅ ለጥገና
ትዕዛዝ ለሞላው ክፍል ይሰጣል፡፡

51

You might also like