You are on page 1of 7

1

1. ክፍል ሁለት ፡- ሪጉላሪቲ ኦዲት

1.1. የቅድመ ኦዲት ተግባራት /Pre-engagement Audit activities/


የቅድመ ኦዲት ተግባራት መከታተያ ቼክሊስት /Pre-Engagement check lists/ በመጀመሪያው
ስምሪት ወቅት ኦዲተሮች ዋና ኦዲተር መ/ቤት እንዳሉ ተሞልቶ በሚመለከታቸው ኃላፊዎች
ስምምነት ማግኘት አለባቸው፡፡ ቀጣዩ ስምሪት የሚሞላው የአንደኛው መ/ቤት የኦዲት ስራ ተጠናቆ
የመውጫ ስብሰባ ከተደረገ በኋላ ተሞልቶ በተገኘው የኦዲት ቡድን መሪ (ሱፐርቫይዘር) ስምምነት
ማግኘት አለበት፡፡
በቅድመ ኦዲት ተግባራት የሚካተቱ ቅጾች፡-

1.1.1. የሙያ ስነ-ምግባር የስራ ወረቀት (Code of ethics Declaration)


 ኦዲተሩ ኦዲት ለማድረግ ከሚሰማራበት (ከኦዲት ተደራጊው መ/ቤት)በስራው ላይ ተፅኖ
ሊፈጥር የሚችል ዘመድ ወይም ሌላ የጥቅም ግጭትን የሚፈጥር አካል ካለ ለዳይሬክቶሬቱ
በወቅቱ ማሳወቅ አለበት፣ ተፅኖው ሲታመንበት ባለሙያው እንዲቀየር ይደረጋል፡፡

 ቼክ ሊስቱ ለኦዲት በሚሰማራው የቡድን አባላት ስም ለእያንዳንዱ ተለይቶ መሞላት


አለበት፡፡

 አዲስ ወደ ኦዲት ቡድኑ የተቀላቀለ ወይም የሚቀላቀል ኦዲተር ካለ የሙያ ስነ-ምግባር የስራ
ወረቀት ሊዘጋጅለት ይገባል፡፡

 ቼክ ሊስቱ በሪጉላሪቲ ማንዋል መሰረት በትክክል ካልተሞላ እንደ ስነ-ምግባር ጥሰት


ይቆጠራል፡፡

1.1.2. የሙያ ስነ-ምግባር ማጠቃለያ/code of ethics conclusion/


 በሙያ ስነ-ምግባር የሥራ ወረቀት በእያንዳንዱ ኦዲተር ደረጃ የተለየ ስጋቶች
በማጠቀለል በሰጋቱ ላይ ሊወሰዱ የሚችሉ ውሳኔዎች ከኦዲት ቡድን ተጠቃለው
የሚቀርቡበት ሲሆን ኦዲት ቡድን መሪው የስጋቶችንና የመፍትሔ ውሳኔዎችን
በማረጋገጥ በስራው ላይ ያላቸውን ተፅዕኖ በመገምገም በኦዲት ስምሪቱ ላይ ውሳኔ
ሊያስርፍ ይገባል፡፡

2
 አዲተሩን ለሙያ ስነ-ምግባር ጥሰት የሚዳርግ አግባብ ኦዲት በሚያደርገው መ/ቤት
ከተገኘ በወቅቱ የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡ ይህን የማያደርግ ኦዲተር የስነ-ምግባር ጥሰት
እንደሰራ ተቆጥሮ ተጠያቂ ይሆናል፡፡

1.1.3. የተተመነውና ስራ ላይ የዋለው ስዓት ጋር ማነፃፀር (Budget


versus actual hours)

 ይህ የስራ ወረቀት በስራ ስምምነት የስራ ወረቀት መሰረት በተደረገው የስራ ክፍፍል መሰረት በእያንዳንዱ
ኦዲተር ተለይቶ የሰዓት እቅድ ሊያዝ እና ስራ ላይ የዋለው ሰዓትም ሊቀመጥ ይገባል፡፡
 በእያንዳንዱ ኦዲተር የተሸነሸነው ሰዓት በድምሩ በስራ ወረቀት ላይ ሊገለፅ እና ስራ ላይ ከዋለው ሰዓት ጋር
እየተነፃፀረ ልዩነቱ ሊቀመጥ እና የልዩነቱ ምክንያት ሊገለፅ ይገባል፡፡

 በኦዲቱ ክለሳ ሥራ ላይ ለሚሳተፍ ኦዲት ቡድን መሪ 24 ሰዓት እና የኦዲት ሪፖርት ለሚያወጣበት 8


ሰዓት በስሙ ተመዝግቦ ሊታቀድና ሥራ ላይ ከዋለው ሠዓት ጋር እየተነፃፀረ ሊሰራ ይገባል፡፡ይህ ሠዓት
ለመ/ቤቶች ማጠናቀቂያ ጊዜ የተመደበውን ሠዓት ሊጨምረው አይችልም፡፡

 የተተመነውን ሰዓት በትክክል በቼክ ሊስት መሙላት ያስፈልጋል፡ በስራ አመራሩ ከተተመነው ሰዓት
በላይ (በጥናት ከተቀመጠው የኦዲት ጊዜ በላይ) በተጨባጭ ምክንያት ጭማሪ ጊዜ መጠቀም
የሚያስፈልግ ሲሆን በቅደም ተከተል በኦዲት ቡድኑ፤ በኦዲት ቡድን መሪ፣ በኦዲት
ዳይሬክተር፣በምክትል ዋና ኦዲተሩና በዋና ኦዲተሩ የመጨመር ስልጣን እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
የመ/ቤቱ ደረጃ የሚጨመር ጊዜ
በኦዲት ቡድኑ በኦዲት ቡድን መሪ በኦዱት በዲይሬክተር በምክትል እና ወይም
ዋና ኦዲተሩ
በጣም ከፍተኛ 6 የሥራ ቀን ከ7 - 10 የሥራ ቀን ከ11 - 14 የሥራ ቀን ከ14 ቀን በላይ
ከፍተኛ 4 የሥራ ቀን ከ 5 - 8 የሥራ ቀን ከ9 - 12 የሥራ ቀን ከ12 ቀን በላይ
መካከለኛ 2 የሥራ ቀን ከ 3 - 5 የሥራ ቀን ከ6 - 7 የሥራ ቀን ከ7 ቀን በላይ
አነስተኛ 1 የሥራ ቀን ከ 2 - 3 የሥራ ቀን ከ4 - 5 የሥራ ቀን ከ5 ቀን በላይ
 በተላለፈው ሰርኩላር መሰረት የመስክ ኦዲተሩ ለስራው በተሰጠው ተጨማሪ ጊዜ ስራውን
ካላጠናቀቀ ስራው ባለበት ቆሞ እና በኦዲት ቡድን መሪው ማረጋገጫ ተወስዶበት ከሃላፊዎች
ጋር በመነጋገር ተጨማሪ ጊዜ ሊሰጠው ይችላል፡፡

1.1.4. የኦዲተሮች የቡድን ብቃት ስብጥር (Competency matrix)


 የኦዲት ቡድኑ ስብጥር አባላት የስራ ልምድ፤ የትምህርት ደረጃና ችሎታ ተለይቶ ሊሞላ ይገባል፡፡

 ወቅታዊ ብቃት (competency Available) ኦዲተሩ ወደ ኦዲት ተደራጊው መ/ቤት


በሚሄድበት ወቅት የብቃት መገምገሚያ ቅጹን (competency matrix) ሲሞላ ለተመደበበት
መ/ቤት የስልጠና ፍላጎት ሲያሳውቅ በትክክል የሚያስፈልጉ መሆናቸውን ተመዝኖ ሊጠየቅ
ይገባል፡፡
3
ለምሳሌ፤-

 የኦዲት ቡድን አባላት የኮምፒውተር እውቀት /ችሎታ/፤


 የኦዲት ቡድን አባላት በልዩ ኦዲት ሥራ ላይ ያላቸው ተሞክሮ ወዘተ..፤

1.1.5. የኦዲት ሥራ ስምምነቶች ደብዳቤ (Audit engagement letter)


 በ Audit engagement letter/ በአሁኑ ወቅት በመግቢያ ስብሰባ ቃለ-ጉባኤ / ተተክቶ
እየተሰራበት ቢሆንም ከምንከተለው የኦዲት አሰራር ማሻሻያ ቨርዥን 2015 አኳያ አስፈላጊ
የኦዲት የስራ ወረቀት በመሆኑ፡-

መ/ቤታችን የመንግስት መ/ቤቶችንና የልማት ድርጅቶችን ሂሳብ ኦዲት ማድረግ በአዋጅ የተሰጠው
ስልጣን እና ሃላፊነት ቢሆንም ይህ የስራ ወረቀት ከኦዲት ተደራጊ መ/ቤት ጋር እንደ ስራ ውል የሚታይ
በመሆኑ የተጠያቂነትን አሰራር የሚያጠናክር ተደርጎ ይወሰዳል፡፡

ኦዲተሮች ወደ ስራ ሲሰማሩ የስራ ስምሪት ደብዳቤው ጋር አባሪ በመሆን ለኦዲት ተደራጊ መ/ቤት የሚላክ
ሲሆን አዘገጃጀቱም አባሪ የስራ ስምምነት ደብዳቤ በሶስት ኮፒ ተዘጋጅቶ ሁለቱ ኮፒ ለኦዲት ቡድን ይሰጥ
እና ከኦዲት ተደራጊ መ/ቤት ሀላፊ ጋር ከተፈራረሙ በኋላ አንደኛው ኮፒ የኦዲት ፋይል አካል ሆኖ
የሚያዝ ሲሆን ሁለተኛው ኮፒ ለኦዲት ተደራጊ መ/ቤት የሚሰጥ ይሆናል፡፡ ሶስተኛው ኮፒ ለክትትል ይረዳ
ዘንድ ዳይሬክተሩ ላይ ፊርማ ሳይኖረው ፋይል ሆኖ ይቀመጣል፡፡

የሥራ ወረቀቱ በኦዲት ቡድን መሪው የሚዘጋጅ ሆኖ በዳይሬክተሩ የሚፈረም ሲሆን የኦዲት ቡድኑ የስራ
ስምምነት ደብዳቤውን ለኦዲት ተደራጊው መ/ቤት ከመሰጠቱ በፊት በሥራ ስምምነት ደብዳቤ ላይ በቂ
ግንዛቤ ሊያዝበት ይገባል፡፡

ኦዲት ቡድኑ የኦዲት ሥራ ስምምነት ደብዳቤ የሚፈራረመው ከኃላፊች ጋር በመሆኑ ሌሎች በኦዲት
ሥራው ላይ ወሳኝ የሆኑ አካላት ስለኦዲቱ ሥራ ስምምነት መሰረታዊ ነጥቦች መረጃ ሊኖራቸው
ስለማይችል እና ስለኦዲቱ አጠቃላይ ሂደት ግንዛቤ ለማስያዝ ይህን ደብዳቤ መነሻ በማድረግ አጭር ቃለ
ጉባኤ በማዘጋጀት በኦዲት ሥራ ስምምነት ነጥቦች ዙሪያ የመግቢያ ስብሰባ ሊደረግና ኦዲት አስደራጊ
ግለሰብ ሊወከል ይገባል፡፡

ከነጠላ ፋይናንስ ድጋፍ ሰጪ ማዕከላት ጋር ኦዲት ለሚደረጉ የገቢዎች ጽ/ቤቶች በተመለከተ ገቢዎች
ጽ/ቤት ራሱን በቻለ የጽ/ቤት ኃላፊ የሚመራ ስለሆነ ለራሱ የስራ ስምምነት ደብዳቤ ከዚህ በላይ
በተገለፀው መሰረት የሚደርሰው ይሆናል፡፡ ነገር ግን የኦዲት ስራ ሰዓትን ላለመሻማት ለገቢዎች ጽ/ቤት
የመግቢያ ስብሰባው ከነጠላ ፋይናንሱ ጋር በአንድ ላይ የሚደረግ ሲሆን ቃለ-ጉበኤው የሁለቱን መ/ቤቶች
የኦዲት ስምምነት ነጥቦችን አካቶ መዘጋጀት ይኖርበታል፡፡

4
በሥራ ስምምነት ደብዳቤ ከተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ በላይና በታች ሥራዎችን ለመፈፀም አሳማኝ የኦዲት
ሰዓት ማሻሻያ የሚያስፈልግ ከሆነ ቀደም ሲል የኦዲት ማጠናቀቂያ ሰዓትን አሰመልክቶ በወጠው መመሪያ
መሰረት ጉዳዩን ቀደም ብሎ በማሳወቅ እና በማስፈቀድ ስራውን ሊያከናውን ይችላል፡፡

በሥራ ስምምነት ደብዳቤ መካተት ያለባቸው ጉዳዩች


 የመ/ቤታችን የኦዲት የጊዜ ሰሌዳ
 2nd ኢንትሪም ኦዲት የሚደረገው ኦዲት አስደራጊዎች ሂሳባቸውን በአጭር ጊዜ ውስጥ
ዘግተው በደብዳቤ /በስልክ/ ለመ/ቤታችን እንዳሳወቁም የኦዲት ስራው እንደሚጀምር
ማስገንዘብ ቀድሞ ያሳወቀ ስራው እንደሚጀምርለት ግንዛቤ ማስያዝ የሚገባ ሆኖ
በፋይናንስ አዋጁ ከተፈቀደው የጊዜ ገደብ ዘግይቶ ሂሳብ ተዘግቶ ቢቀርብ ኦዲት
ማድረግ እንደማይችል እና ሁኔታውንም ለሚመለከተው አካል እንደምናሳውቅ ግንዛቤ
ማስያዝ፣
 የወቅቱን ሂሳብ እንደምንሰራና ለ 2nd ኢንትሪም ተመልሰን እንደምንመጣ ወዘተ በሥራ
ስምምነት ደብዳቤ በግልፅ ተጠቅሶ መፈራም ይገባል፡፡
 የወቅቱ የኦዲት ስራ መቼ ተጀምሮ መቼ እንደሚያልቅ፣ የኦዲተሩ ተግባር እና ሃላፊነት
እንዲሆን የኦዲት አስደራጊው ሃላፊነት በዝርዝር መስፈር አለባቸው ፡፡
 ለኦዲቱ የሚያስፈልጉ ሰነዶችና መዛግብቶች በወቅቱ መቅረብ እንደሚገባቸው
መገለጽ ይኖርበታል፡፡

1.1.6. የኦዲት ቡድን ሥራ ስምምነት (Team agreement)


 ከቅድመ ኦዲት ስራ እስከ ሪፖርት ድረስ ያሉትን ሁሉንም የኦዲት ስራዎች እያንዳንዱ
ኦዲተር እንደ ችሎታቸው ክፍፍል ያደርጋሉ ፡፡
ምሳሌ፤- የግንባታ ሂሳብ ከውስብስብነቱ አንጻር እንደየችሎታቸው መመደብ፤
 የቡድን አባላት በኦዲት ሃላፊው የተሰጣቸውነ ስራ ይሰራሉ ፤
 በዚህ የስራ ወረቀት በተገለፀው የስራ ክፍፍል መሰረት የሰዓት መተመኛ (Budget Vs Actual
Hours) የስራ ወረቀት ተናባቢ ሆኖ ሊዘጋጅ ይገባል፡፡
 አንዱ የሰራውን ሌላው የማረጋገጥ ስራ የመስራት ሃላፊነት አለባቸው፤
 በሁሉም የኦዲት መግለጫዎች ሁሉም የቡድኑ አባላት የመፈረም ግዴታ አለባቸው፤
ተጠያቂነትም አለባቸው፤
 ረዳት ኦዲተሮች የሚሰሩትን ስራ የመስክ ኦዲት ቡድን መሪው የሚከልሰው ሲሆን የመስክ

ኦዲት ቡድን መሪውን ስራ ደግሞ በኦዲት ቡድን መሪው ይከለሳል፤

5
2.3.1. የናሙና አመራረጥ ዘዴ እና መጠን /Sampling technique Sample size/
 በተሻሻለው የሬጉላሪቲ ኦዲት ማኑዋል በተቀመጠው የናሞና መረጣ መሠረት መስራት ይገባል፡፡ ይህም
መከናወን ያለበት በዚህ ኦዲት ጋይድ ተራ ቁጥር 2.2.1 በተቀመጠው የአሰራር ስርዓት መሰረት ሊሆን
ይገባል፡፡
 ከፍተኛ የገንዘብ መጠን ያለቸውን ሰነዶችና ከመደበኛ አሰራር ወጣ ያሉትን ቫውቸሮች
በመለየት በቀሪው የገንዘብ መጠን ላይ ናሙና አውጥቶ መስራት ይገባል፡፡
 ለኦዲት ከተመረጠ Component ውስጥ ከፍተኛ የገንዘብ መጠን /High value items/ ብቻ
ኦዲት አድርጎ ሌላዉን ማለፍ የሚቻለው ከተመረጠው Component ጠቅላላ የገንዘብ
ድምር ቢያንስ 70% የሚሸፍን ከሆነ ብቻ ነው፡፡
 ከፍተኛ የገንዘብ መጠን ያላቸው Compoment ከ 70% በታች ሆነው ከተገኙ ዝቅተኛ የገንዘብ መጠን
የያዙ Compoment 35% እስኪሞሉ ድረስ ናሙና ወጥቶላቸው ኦዲት መደረግ ይኖርባቸዋል፡፡
 ለናሙና የተመረጡ ከፍተኛ መጠን ያለው (high value items) 70% ሆኖ አንድ የወጪ
ሰነድ ብቻ ከሆነ ቀጣዩን ዋጋ ያላቸው ሌሎች ሰነዶችን በመጨመር ቢያንስ ከ10 ያላነሱ
የወጪ ቫውቸሮች ሊታዩ ይገባል፡፡
 የወጪ ሰነዶች ከ 10 በታች ቫውቸሮች ያለው ኦዲት ኮምፖነንት /component/ ሙሉ በሙሉ
(100%) በዝርዝር ይሰራል ወይም ይመረመራል፤ንሞና ሲወጣ በክፍልፋይ የሚታይ ከሆነ ወደ
ቀጣዩ ቁጥር በማጠጋጋት ሊሰራ ይገባል፡፡ ለምሳሌ፡- የንሞና መጠኑ 5.04 ቢሆን በቀጥታ 6
ቫውቸሮች መወሰድ አለበት፣
 የደመወዝ ሂሣብን በዝግ ናሙና ዘዴ ሥጋት ያለባቸውን ወሮች መርጦ መስራት ይገባል፡፡
የሚሰሩት ወሮች በየኢንትሪሙ ከሁለት ወር ማነስ የለባቸውም፡፡ ስጋት አለ ተብሎ ከታመነ
በኦዲተሩ ሙያዊ ብያኔ መሰረት ሰፍቶ ሊሰራ ይችላል፡፡
 የተራድኦ ሂሳቦች በመጀመሪያው ኢንትሪም ኦዲት ወቅት በኦዲተሩ ሙያዊ ብያኔ
(judgmental sampling) የናሙና ዘዴ በየአካውንታቸው ራሳቸውን ችለው በኮምፖነንት
ደረጃ ሳይደራጁ በየሂሳብ ቁጥር የተፈፀሙ ወጪዎችን በጥቅል ተዘርዝረው ኦዲት
የሚደረጉ ይሆናል፡፡
 የተራድኦ ሂሳቦች በሁለተኛው ኢንትሪም ኦዲት በተግባር ስራ ላይ የዋለው ወጪ ተይዞ
ከመደበኛ ሂሳብ ወጪ ጋር በየኦዲት ኮምፖነንቱ ገብተው ናሙና እየወጣላቸው ሊሰሩ
ይገባል፡፡
 በተከፋይ ሂሳብ ለምሳሌ 5028 የሚላኩ እና በወጪ ፀድቀው የሂሳብ ሰነዳቸው ከኦዲት
ተደራጊው መ/ቤት የሚያዙ ሂሳቦች እና የምግብ ዋስትና ሂሳብ በመግለጫ ደረጃ ያለውን
ጉልህነት ለመወሰን መሰረት ከሚሆነው ጥቅል ወጪ ውስጥ ሳይካተቱ ራሳቸውን ችለው

6
በኦዲተሩ ሙያዊ ብያኔ ኦዲት የሚደረጉ ሆኖ በመጀመሪያውም ሆነ በሁለተኛው ኢንትሪም
ኦዲት ወቅት ራሳቸውን ችለው ተዘርዝረው የሚሰሩ ይሆናል፡፡
 ራሳቸውን ችለው ኦዲት የሚደረጉ የተራድኦ እና የወጪ ባህሪ ያላቸው በተከፋይ የሚያዙ
ሂሳቦች ማግኘት ያለባቸው የኦዲት ሽፋን በገንዘብ መጠን 70% ያላነሰ እና በቫውቸር ብዛት
ደግሞ ከ 10 ያላነሰ ሊሆን ይገባል፡፡

3.1.1. የወጪ ሂሳብ ኦዲት


ኦዲተሮች የወጪ ሂሳብ ኦዲት ሲያደርጉ የሚከተሉትን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል፤
 ከወጪ ሌጀሮች ወደ ወጪ ሂሣብ ሪፖርት በትክክል ሪፖርት መደረጉን፣
 የወጭ ሪፖርት (መሂ/22) በትክክል ወደ ሂሳብ ሚዛን ሙከራ ሪፖርት መተላለፉን ፤
 በወጪ ሰነድ መሂ/7 የተከፈለ ክፍያ በትክክል ወደ ሂሳብ እንቅስቃሴ መዝገብ የተወራረሰ መሆኑን ፣
 የተከፈሉ ክፍያዎች የካፒታልም ሆነ የመደበኛ በጀት ርክክባቸው ለተጠናቀቁ ዕቃዎች እና አገልግሎቶች
መሆኑን እና የተያያዙ ደጋፊ ሰነዶቻቸው ትክክለኛ መሆናቸውን፣
 ግዥዎች ሁሉ በትክክለኛው የጨረታ ዘዴ ግዥ መፈጸማቸውን ፤
 ትክክለኛው የተጨማሪ እሴት ታክስ ወይም ዊዝሆልዲንግ ታክስ ሂሳብ በትክክል መቀነሱን ማረጋገጥ፤
 የእቃና አገልግሎት ግዥዎች ሁሉ መጠየቂያ የሚቀር ብላቸው መሆኑን ፣
 ክፍያዎች የሚፈጸሙት ስልጣን ባለው አካል እየተፈቀዱና እየተረጋገጡ መሆኑን፤
 ደመወዝ የሚከፈለው ሰራተኞች ለሰሩበት ቀን ብቻ መሆኑን ፤
 ሰራተኞች የውሎ አበል የሚከፈለው የመስክ ስራ ለሰሩበት መሆኑን ፤
 በውለታ የሚፈጸሙ ክፍያዎች በተገባው ውለታ መሰረት ለተሰራው ስራ ወይም ለተገኘው አገልግሎት
ከሚመለከተው ማረጋገጫ ሲቀርብ መሆኑን እና አስፈላጊ ማስረጃዎች ሁሉ ሲሟሉ መሆኑን ፤
 ክፍያዎች የተሟላ ማስረጃ ያላቸውና በተፈቀደው ልክ ብቻ የተከፈሉ መሆኑን ፣
 ግዥዎች ሁሉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ካላቸው እና የዘመኑን ግብር ከከፈሉ አቅራቢዎች መፈጸማቸውን ፤
 ግዥዎች በበጀት ዓመቱ በእቀድ ተይዘው የሚገዙ መሆኑን ፤
 የሚገዙት እቃዎች ሁሉ ንብረት ክፍል ገቢ ስለመደረጋቸው እና በተጠቃሚው ክፍል ወጪ የተደረጉ
ስለመሆኑ እንዲሁም በአካል በስራ ክፍሉ ስለ መኖራቸውን፤
 ተሰራ የተባለው የህንጻ ፤ የመንገድ ፤ የድልድይና የውሃ ግንባታዎች ስራ በአካል በመሄድ
መኖራቸውን /መሰራታቸውን/ እና የጥራት ችግር አለመኖሩን ማረጋገጥ፤
 በአጠቃላይ ከላይ የተገለጹትና ሌሎች መሰራት ያለባቸው ተግባሮች ሳይሰሩ ሲገኙ በግኝትና
በግድፈት ይዞ በሪፖርት መጻፍ፤

You might also like