Professional Documents
Culture Documents
1
ማውጪያ
1. መግቢያ 3
2. የክትትልና ግምገማ ዓላማ 3
3.ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች 5
3.1 የገንዘብ አቅርቦትን ለማሻሻል የበለጠ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት፣ 5
2
1. መግቢያ
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ዘርፉ አሁንም ወደፊትም ለሚያከናውናቸው
ተግባራት ስኬታማነት የክትትልና ግምገማ ስርዓት መገንባት ትልቅ ድርሻ አለው፡፡ የክትትልና ግምገማ ዘዴዎች ወቅቱን የጠበቀ
የአፈጻጸም ሪፖርት ማቅረብ፣ ውጤትን በመገምገም፣ የግምገማ መድረኮች /ስብሰባዎች/ በማካሄድ፣ የአካል ምልከታ ማድረግን
ያካትታሉ፡፡ በመሆኑም ማንኛውንም የስራ እንቅስቃሴ በተያዘላቸው ዕቅድ መሰረት በተፈለገው አግባብ፣ወጪ እና ጊዜ
እየተተገበረ እና መተግበራቸውን የሚጠቁም ቀጣይነት ያለው የክትትል እና ግምገማ ስትራቴጅ ለመዘርጋት ታስቦ የተዘጋጀ
ነው፡፡
ክትትልና ግምገማ ከማኔጅመንት ወይንም አስተዳደር መሳሪያዎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ለትክክለኛ ፕሮጀክት አስተዳደር
ክትትልና ግምገማ በምንም አይነት መልኩ ሊተኩ ወይንም ሊቀየሩ አይችሉም፡፡
የተቀመጡ ግቦች በስትራቴጂያዊና ዓመታዊ ዕቅድ ዝግጅት ሂደት የተለዩ ክፍተቶችን እየሞሉና
ችግሮችን እየፈቱ መሆኑን ለማረጋገጥ፣
የታቀዱ ሥራዎች በተያዘላቸው መርሃ ግብር መሠረት እየተከናወኑ ስለመሆናቸው ለመገምገምና ቀጣይ
አቅጣጫ ለማስቀመጥ፣
በዕቅድ ተይዘው የሚከናወኑ ሥራዎች የተቋሙን ተልዕኮና ራዕይ ከማሳካት አንጻር ያሉበትን ደረጃ
ለመገምገም፣
በትግበራ ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመለየት ትክክለኛና ወቅታዊ ድጋፍ ለመስጠት ናቸው፡፡
አግባብነት ያለው የግብዓት አጠቃቀም፣ ግብዓት ወደ ምርት መቀየራቸውን ማረጋገጥ፣ የዕቅድ ትግበራ ጊዜንና እና
በጀት አጠቃቀም ላይ ማስተካከያ ለማድረግ፣ የስራ ክፍሎችን/ፕሮጀክቶችን አቅም እና ያሉበትን ሁኔታ
በማገናዘብ የዕቅድ አፈፃፀማቸውን መፈተሽ እንዲሁም የተከናወኑ ስራዎችን መከለስ እና ተፅዕኖዎችን
መገምገም የሚሉት ይገኙበታል፡፡
3
የፕሮጀክቶችን
እንቅስቃሴ ይዳስሳል
ትግበራው በተያዘለት
የፕሮጀክቶችን ጊዜ መከናወኑን
አላማና ግብ ማረጋገጥ
ይዳስሳል
ምርትን እና
ውጤትን ይዳስሳል
የገባኛል ባዮችንና
ባለድሻዎችን
የመሳብና በቡድን
የመስራት ልምድን
ያዳብራል የክትትልና የታዩ ለውጦችንና
ግምገማ መሻሻሎችን
አላማዎች ይዳስሳል
መነሻ ሃሳብ
የመውሰድ ልምድ
ያዳብራል
በአጠቃላይ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ የክትትልና ግምገማ ሥራዎች የዘርፉን ዕቅድ ውጤታማነት ለማረጋገጥ
እንዲቻል ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች እንደሚከተለው ተለይተው ቀርበዋል፡፡
4
3.1 የገንዘብ አቅርቦትን ለማሻሻል የበለጠ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት፣
የቀጥተኛ ወጪዎችን ቁጥጥር “cost accounting”ን መሠረት በማድረግ የምንገመግም ሲሆን ቀጥተኛ
ያልሆኑትን ወጪዎች(Indirect costs)ደግሞ አስቀድሞ በታቀደላቸው በጀት እና እስትራቴጅክ ግቦችን
መሠረት በማድረግ እየተገመገሙ ግብረ-መልስ በመስጠትና በቀጣይ ያሉ ለውጦችን የመከታተል ሥራ
ይሰራል፡፡
በተለይ የፕሮጀክቶች ዋና ዋና ወጪዎች ማለትም እንደ ነዳጅ ፣የኪራይ መሣርያ፣የትርፍ ሰዓትና ሌሎች
ክፍያዎችንና የኮንስትራክሽን ማቴሪያሎች አጠቃቀም ጥብቅ ክትትል በማድረግ በተቀመጠው የአሰራር
ስርዓትና ስታንዳርድ መሠረት እንደፈጸም እናደርጋለን፡፡
5
3.4 ፕሮጀክቶችንና ዲስትሪክቶችን ከመደገፍ አንፃር
በማኔጅመንት ደረጃ በየወሩ የአፈጻጸም ግምገማ ይደረጋል፣ ያጋጠሙ ውስጣዊና ውጫዊ ችግሮችን
ይለያሉ የመፍትሔ እርምጃዎችም ይወሰዳሉ፣
በማኔጅመንት ደረጃ በየወሩ፣ በመምሪያ ደረጃ በየ 15 ቀን፣ በቡድን ደረጃ በየሳምንትና በዩኒት/በክሩ
ደረጃ በየቀኑ ሥራን የማቀድ አፈጻጸምን የመገምገም ሥራ ይሰራል፤
በየሩብ አመቱ ሪፖርት ለሰራተኛው እየቀረበ ግብረ-መልስ ይወሰዳል፡፡ ለምሳሌም የበጀት አመቱ
የስድስት ወር ሪፖርት ለሰራተኛው ቀርቦ ተገምግሟል፡፡ ጠቃሚ ግብዓቶችም ተገኝተዋል፣
የአፈፃፀም ደረጃቸው በጣም አሳሳቢ ሁኔታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ለምሳሌ፡- ጅንካ፣ጉባ እና ዱለቻ በየወሩ
ከዕቅድ እስከ አፈፃፀም ድረስ በመምሪያ፣ በዋና መምሪያ እና በዘርፍ ደረጃ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር ከማድረግ
በተጨማሪ በየጊዜው የመስክ ግምገማ በማድረግ በአፋጣኝ አፈፃፀማቸው የሚሻሻልበትን መንገድ የመፍትሄ ሃሳብ
በማስቀመጥ ተግባራዊነቱም ክትትል ይደረጋል፡፡
በአጠቃላይ የፕሮጀክቶቹ አፈፃፀም በኮርፖሬሽኑ ተቋማዊ ብቃት ላይ በተለያየ አቅጣጫ ያስገኘውን ውጤት መገምገም ዘርፉ
በኮርፖሬሽኑ እንዲሁም በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ ያለው ወሳኝ ሚና በምን ደረጃ ላይ እንዳለ ለማወቅ ይረዳል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በክትትልና ግምገማው በዘርፉ የታዩ ድክመቶችን እና ሊወሰዱ የሚገባቸውን እርምጃዎች በመጠቆም በቀጣይ
ዓመታዊ ዕቅድ ላይ እንደ ግብዓት ለመውሰድ አስተዋጽዖ ሊያበረክት ይችላል፡፡ ይህንንም በማድረግ የኮርፖሬሽኑን ዕቅድ አፈፃፀም
በማሻሻል ዘርፉ የበኩሉን ድርሻ እንዲያበረክት ያግዘዋል፡፡