Professional Documents
Culture Documents
1.1 መግቢያ
የፌዴራል ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ በአገር አቀፍ ደረጃ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓት በመዘርጋት የኩነቶች
ምዝገባ ወጥና ቀጣይነት ባለው የአሰራር ስርዓት ላይ እንዲመሰረት ተግባሩን በበላይነት የማስተባበር፣ በአገር
ደረጃ ከኩነቶች ምዝገባ የተገኘውን መረጃ በማእከል አደራጅቶ በመያዝ ለአገሪቱ ፖሊሲ ቀረጻ፣ ስትራቴጂክ
እቅድ አቅጣጫ፣ ለማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ለተለያዩ ፕሮግራሞች እቅድ ብቁና ጥራቱን የጠበቀ መረጃ
ኤጀንሲዉ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ በመላ አገሪቱ ተግባራዊ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ በህግ የተሰጠውን ተግባርና
ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት በምዝገባ ቅድመ ዝግጅት ወቅት አመታዊ እቅዱን በማዘጋጀትና ፈጻሚ ፣
ባለድርሻና ተባባሪ አካላት በእቅዱ ዙሪያ የጋራ መግባባት እንዲፈጥሩ በማድረግ የምዝገባ ስራዉ በመላ አገሪቱ
እንዲጀምር ተደርጓል፡፡
የምዝገባ ስራዉ ከተጀመረ በኋላም በምዝገባ ሂደት ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት እና ከመዝጋቢ እና
ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመስራት የአዋጅ ማሻሻያ ጨምሮ በርካታ ማስተካከያዎች የተደረጉ ሲሆን
በየደረጃዉ የሚገኘዉን መዝጋቢ አካል አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ስልጠናዎችን በስፋት በመስጠት
እንዲሁም ህብረተሰቡ በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ዙሪያ ግንዛቤ በመፍጠር ተሳትፎዉን ሊያሳድጉ የሚችሉ የግንዛቤ
ማሥጨበጫ መድረኮችን በማዘጋጀት የምዝገባ ስራዉ ዉጤታማ እንዲሆን ለማድረግ ሰፊ ርብርብ ሲደረግ
ቆይቷል፡፡
በመላ አገሪቱ የተጀመረዉን የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራ ቀጣይነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ስራዎች አበረታች
ቢሆኑም የምዝገባ ስራዉን በሚፈለገዉ ፍጥነት እና የጥራት ደረጃ በማከናወን ረገድ ፈታኝ ሁኔታዎች
ያጋጠሙ ሲሆን በተለይም በየደረጃዉ የሚገኘዉ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ መዋቅር የምዝገባ ስራዉን የተሟላ
እዉቀት እና ክህሎት ይዞ በመምራት ረገድ ዉስንነት ያለበት መሆኑ ፣ የምዝገባ ስራዉን ተግባራዊ በማድረግ
ረገድ ወሳኝ ድርሻ ያለዉ የቀበሌ ስራ አስኪያጅ ለስራዉ ተገቢዉን ትኩረት በመስጠትና ባለቤት ሆኖ
1
በመፈጸም ረገድ ክፍተት ያለበት በመሆኑ በምዝገባዉ ጥራት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳደረ መሆኑ ፣ በየደረጃዉ
የሚገኙ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ስርአቱን በመደገፍ ረገድ የሚጠበቅባቸዉን ሚና በሚፈለገዉ ደረጃ እየተወጡ
አለመሆኑ ፣ የምዘገባ ስራዉ በሁሉም የምዝገባ ጽ/ቤቶች አለመጀመር እንዲሁም የወሳኝ ኩነት ምዝገባ
ስራዉን ዉጤታማ በማድረግ ረገድ ወሳኝ ሚና ያለዉ የጤናዉ ዘርፍ ሃላፊነቱን በሚፈለገዉ ደረጃ
በመሆኑም የምዝገባዉን ቀጣይነት ለማረጋገጥ እንዲቻል በምዝገባዉ አፈጻጸም ላይ የታዩ ጠንካራ አፈጻጸሞችን የበለጠ
ተጠናክረዉ እንዲቀጥሉ ለማድረግ እንዲሁም ከምዝገባ ፍጥነት ፣ ተደራሽነትና ጥራት ጋር ተያይዞ በተለዩ ቁልፍ ችግሮችና
በቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ዙሪያ በየደረጃዉ ከሚገኘዉ መዝጋቢ እና ባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ መግባባት በመፍጠር
የምዝገባ ስራዉ አስተማማኝ መሰረት ላይ እንዲያርፍ ለማድረግ እንዲቻል በኤጀንሲ ደረጃ የኤጀንሲዉን የ 2009-
2012 ስትራቴጅክ እቅድ ፣ የኤጀንሲዉን የ 2009 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም ፣ የተገልጋይ እና ባለድርሻ
አካላት ፍላጎት መነሻ በማድረግ በ 2010 በጀት አመት ሊከናወኑ የሚገባቸዉን ግቦች፣ ዋና እና ዝርዝር
ተግባራት ፣ በእቅድ አፈጻጸም ወቅት ተግባራዊ የሚደረግ የድጋፍና ክትትል ስርአት እንዲሁም በአፈጻጸም ወቅት
በ 2017 የኩነቶች ምዝገባ ለዜጐች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ተጠቃሚነት፣ ለሕግ የበላይነት እና
ስለ ኩነት ምዝገባ አገራዊ ፋይዳ ህብረተሰቡ ያለውን ግንዛቤ በማሳደግ፤ የኩነት መረጃ በመልካም
ዘመናዊ የአሰራር ስርዓትን በመጠቀም ደህንነቱ የተረጋገጠ የኩነት መረጃ በብቃትና በጥራት
እንዲውል ማድረግ፣
በጥናትና ምርምር አዳዲስ የአሰራር ስልት በመቀየስ በአገር አቀፍ ደረጃ ወጥ እና ዘመናዊ የመረጃ
የኤጀንሲው ዕሴቶች
ግልጸኝነትና ተጠያቂነት፣
ምስጢር ጠባቂነት፣
የከተማ አስተዳደሮች ፣ የወሳኝ ኩነቶችን የሚመዘግቡ የፌዴራል ተቋማት እና የባለድርሻና ተባባሪ አካላት ስርአቱን
በመደገፍ ረገድ የነበራቸዉን ሚና በጥንካሬና በድክመት የተዳሰሰ ሲሆን በዉስጣዊ ሁኔታ ዳሰሳ ላይም የኤጀንሲዊ
የመሰረታዊ የስራ ሂደት (BPR) ጥናት ሰነድ ፣ የኤጀንሲው ሚዛናዊ ውጤት ተኮር (BSC) 2009 - 2012 ዓ.ም
ጥናት ሰነድ እንዲሁም አገራዊ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ምክር ቤት ፣ የኤጀንሲው የስራ አመራር ቦርድ እና የኤጀንሲዉ
3
አመራር እና ፈጻሚ ስርአቱን በመደገፍ ረገድ የነበራቸዉን ሚና በጥንካሬና በድክመት በመዳሰስ ለእቅዱ እንደ መነሻ
በአመለካከት ረገድ
ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የምዝገባ ስራዉ ለህዝቡ ቀጣይ እድገት ጠቃሚ መሆኑን በእምነት በመያዝ
እና መረጃዉ ለተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እንዳለዉ በአመለካከት በመዉሰድ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ
አሰራር ስርአቱን ተግባራዊ በማድረግ ሂደት ፈታኝ ሁኔታዎች ቢኖሩም ማሳካት ይቻላል የሚል እምነት እና
አመለካከት በመያዝ ምዝገባዉን በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች እውን እንዲሆን
በክልል እና ከተማ አስተዳደር ደረጃ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን እዉን ለማድረግ እንዲቻል የተደረገዉ
ጥረት አበረታች ቢሆንም የምዝገባ ስራዉን ዉጤታማ ለማድረግ በሚደረገዉ ጥረት በየደረጃዉ ከሚገኙ ወሳኝ
ባለድርሻ አካላት ጋር ጠንካራ ቅንጅት በመፍጠር በጋራ መስራት ወሳኝ ተግባር መሆኑን በእምነት በመያዝ እና
ለተግባራዊነቱ በሚፈለገዉ ደረጃ በመንቀሳቀስ ረገድ ክፍተት የነበረ ሲሆን የምዝገባ ስርአቱን ተግባራዊ
በማድረግ ሂደት የሚያስፈልጉ ግብአቶችን በራስ ተነሳሽነት በማሟላት ረገድ በአመለካከት ደረጃ ችግሮች
ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የምዝገባ ስርአቱን እዉን በማድረግ ረገድ ያሳዩት አበረታች ጥረት እንዳለ ሆኖ
የምዝገባ ስራዉ ከጀመረ በኋላ የምዝገባ ጥራት እና ሽፋን በሚፈለገዉ ደረጃ እንዲደርስ ከማድረግ አንጻር
ክፍተት የታየ ሲሆን በክልል እና ከተማ አስተዳደር ደረጃ ከአመለካከት አንጻር የታዩ ክፍተቶችን በቀጣይ እቅድ
በክህሎት ረገድ
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራዉን ተግባራዊ በማድረግ ሂደት ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች በፌዴራል ደረጃ
የተሰጡ ስልጠናዎችን መነሻ በማድረግ በራስ አቅም ስልጠና በመስጠት እና የምዝገባ መመሪያዉን የማስተግበር
አቅማቸዉ እየተሻሻለ የመጣ መሆኑ እንዲሁም በምዝገባ አፈጻጸም ሂደት ላይ የታዩ የአፈጻጸም ችግሮችን
በራስ አቅም በመፍታት ረገድ ያሳዩት እንቅስቃሴ አበረታች መሆኑን የምዝገባ አፈጻጸሙ ያሳያል፡፡
4
ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራዉን በራስ አቅም ለመምራት የሚያደርጉት ጥረት
አበረታች ቢሆንም ምዝገባዉን በፌዴራል እና በክልል የስራ ቋንቋ ተጠቅሞ በማከናወን ፣ ምዝገባዉን
በሚፈለገዉ የጥራት ደረጃ እና የሚፈለጉ መሰረታዊ መረጃዎችን በሚያሟላ ሁኔታ ተግባራዊ በማድረግ ፣
በየደረጃዉ ያለ ፈጻሚ አካል መረጃን በሚፈለገዉ ደረጃ በማጣራት ረገድ ክፍተት ያለበት መሆኑ እንዲሁም
መረጃ አደራጅቶ በመያዝ እና ለአገልግሎት ዝግጁ በማደረግ ረገድ ክፍተት ያለ መሆኑ የምዝገባ አፈጻጸሙ
የሚያሳይ ሲሆን በክልል እና ከተማ አስተዳደር ደረጃ በክህሎት ረገድ የታዩ ክፍተቶችን በቀጣይ እቅድ በማካተት
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን ተግባራዊ ለማድረግ እንዲቻል ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ተቋማዊ
ስራ ነዉ፡፡ በዚህ መሰረት ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን ተግባራዊ ለማድረግ
በፌዴራል ደረጃ የወጣዉን የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አዋጅ መሰረት በማድረግ የምዘገባ ደንብ በማዘጋጀት እና
በማስገባት ረገድ የተሻለ እንቅስቃሴ በማድረግ ምዝገባዉ እንዲጀምር ያደረጉ መሆኑ በጥንካሬ የሚወሰድ
ነዉ፡፡
በሌላ በኩል የምዝገባ ስራዉን ቀጣይነት ለማረጋገጥ እንዲቻል ከክልል ጀምሮ እስከ ታችኛዉ የአስተዳደር
መዋቅር ድረስ ተቋማዊ አደረጃጀቱን ከመመለስ ባሻገር የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን ከማጠናከር አንጻር
ወሳኝ ድርሻ ያላቸዉን የህዝብ አደረጃጀቶችን በመጠቀም ወደ ስራ እንዲገቡ በማድረግ ረገድ አበረታች
እንቅስቃሴ ያደረጉ ሲሆን ይህም የምዝገባ ስርአቱን በማስቀጠል ረገድ በጎ አሰተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡
የምዝገባ ስራዉን እዉን በማድረግ ረገድ የሰሩት ስራ አበረታች ቢሆንም በክልል እና በከተማ አስተዳደር ደረጃ
የሚገኙ ሁሉንም የምዝገባ አደረጃጀቶች በተሟላ ደረጃ የምዝገባ ስራዉን እንዲጀምሩ በማድረግ ረገድ
ክፍተት ያለ ሲሆን በተለይም የምዝገባ ስራዉን በማከናወን ረገድ ወሳኝ ድርሻ ያለዉ የቀበሌ መዋቅር
5
ተጠሪነቱ ለሌላ አካል መሆኑ ምዝገባዉን ዉጤታማ በማድረግ ረገድ ተግዳሮት መሆኑን የምዝገባዉ አፈጻጸም
ያሳያል፡፡
በሌላ በኩል በምዝገባዉ ሂደት ዉስጥ ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር ጠንካራ እና ዉጤታማ
መረጃ ላይ ተመስርቶ በመላክ ረገድ ክፍተት ያለ በመሆኑ በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ እንዲፈታ ማድረግ ይገባል፡፡
በግብአት ረገድ
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራን ተግባራዊ በማድረግ ሂደት በየደረጃዉ የሚገኙ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ መዋቅር
ተቋማዊ የሰዉ ሃይሉን እና የምዝገባ ግብአቶችን በወቅቱ እና በሚፈለገዉ መጠን እንዲያሟሉ የማድረግ ስራ
ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ለምዝገባ ስራዉ አስፈላጊ የሆኑ የሰዉ ሃይል እና የምዝገባ ግብአቶችን
በማሟላት ረገድ አበረታች እንቅስቃሴ ያደረጉ ሲሆን በዚህ ረገድ ከክልል ጀምሮ እስከ ወረዳ ባለዉ መዋቅር
አስፈላጊዉ የሰዉ ሃይል በአይነት እና በመጠን በማሟላት ወደ ስራ እንዲገባ በማድረግ ረገድ አበረታች
እንቅስቃሴ ያደረጉ ሲሆን በሌላ በኩል ምዝገባዉን ለማከናወን የሚያስችል የክብር መዝገብ እና የምስክር
ወረቀት እንዲሟላ እንዲሁም ለምዝገባ ስራዉ አስፈላጊ የሆኑ ሌሎች ግብአቶች እንዲሟላ በማድረግ ረገድ
በክልል እና ከተማ አስተዳደር ደረጃ የምዝገባ ስራዉን ለማስጀመር የሚያስችል ግብአት በማሟላት ረገድ
የሚገኘዉን መዝጋቢ አካል ለመደገፍ የሚያስችል ተሽከርካሪ በመመደብ ረገድ ክፍተት ያለ በመሆኑ
በየደረጃዉ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት እንዲሰሩ በእቅድ በማካተት መስራት ይገባል፡፡
6
ከድጋፍና ክትትል አንፃር
መዝጋቢ አካል በምዝገባ ወቅት የሚያጋጥመዉን ችግር ሊፈታ የሚችል የድጋፍ እና ክትትል
አድርገዋል፡፡
በሌላ በኩል በበድጋፍ እና ክትትል ወቅት የተለዩ ችግሮችን በራስ አቅም በመፍታት እንዲሁም
ከአቅም በላይ የሆኑ ችግሮችን ከፌዴራል ጋር በጋራ ተቀናጅቶ እንዲፈታ በማድረግ ረገድ
የምዝገባ ስርአቱን ቀጣይነት ለማረጋገጥ እንዲቻል በክልል እና ከተማ አስተዳደር ደረጃ የተሰሩ ስራዎች ያሉ
ቢሆንም የድጋፍና ክትትል ስራዉ ክፍተትን የለየ እና በእቅድ እንዲመራ በማድረግ እንዲሁም ዉጤት ላይ
መሰረት ያደረገ የድጋፍ እና ክትትል ስራ በመስራት ረገድ ክፍተት ያለ ሲሆን የምዝገባ ስራዉን ዉጤታማነት
ለማረጋገጥ የሚያስችል የድጋፍና ክትትል ስርአት እንዲዘረጋ ለማድረግ ትኩረት በመስጠት የሚሰራ ይሆናል፡፡
በፌዴራል ደረጃ ኩነቶችን እንዲመዘግቡ በህግ ኃላፊነት የተጣለባቸው ተቋማት የአገር መከላከያ
7
ሚኒስቴር እና በብሄራዊ የመረጃ እና ደህንነት አገልግሎት የስደተኞችና ከስደት ተመላሽ ጉዳይ
አስተዳደር ናቸዉ ::
የፌዴራል ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ የወሳኝ ኩነቶችን የሚመዘግቡ የፌዴራል ተቋማት የምዝገባ
ስራዉን ለመጀመር እንዲችሉ ለእያንዳንዳቸዉ የሚያገለግሉ የክብር መዝገብ ቅጽ፣ ምስክር ወረቀትና
የተጠቃለለ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ፣ የመረጃ አደረጃጀት፣ ቅብብሎሽ፣ አያያዝና አቅርቦት አፈፃፀም
መመሪያ እንደ ተቋማቱ ተጨባጭ ሁኔታ የማዘጋጀት ስራ የተሰራ መሆኑ እንዲሁም ተቋማቱ ቀድሞ
መሆኑ በቀጣይ ተቋማቱ ለሚያከናዉኑት የምዝገባ ስራ ወሳኝ ግብአት በመሆን የሚጠቅም መሆኑን
ያሳያል፡፡
የምዝገባ ስራዉን ለማከናወን ከኤጀንሲዉ ጋር በተፈጠረዉ የጋራ መግባባት መሰረት በቅድመ ዝግጅት
ደረጃ የሚከናወኑ ተግባራትን ትኩረት ሰጥቶ በማከናወን፣ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን አገራዊ
በማድረግ ረገድ ዉስንነት ያለባቸዉ ሲሆን የተጣለባቸውን የስራ ሃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ
ለማድረግ የጋራ እቅድ በማዉጣትና አፈጻጸሙን በታቀደ የጋራ ምክክር መድረክ በመገምገም የምዝገባ
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአት የባለ ብዙ ዘርፍ ባህሪ ያለዉ እና በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች በወጥነት ተግባራዊ የሚሆን
በመሆኑ ከወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአት ጋር ተያያዥነትና ትስስር ያለዉ ተልእኮ የተሰጣቸዉ ተቋማት ጋር በጠንካራ ግንኙነት
ላይ የተመሰረተ ቅንጅት መፍጠር ወሳኝ ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰድ ነዉ፡፡ በመሆኑም ስርአቱን ከመደገፍ አንጻር ከቁልፍ
ባለድርሻ አካላት ጋር ለወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ መነሻ የሚሆኑ የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡
ለአብነት ለመጥቀስ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራዉን ከመደገፍ አንጻር አፈጻጸሙን በየጊዜዉ
በመገምገም እና ድጋፍ በመስጠት እንዲሁም የምዝገባ ስራዉ ያለበትን የአፈጻጸም ደረጃ ሊያሳይ የሚችል ዳሰሳ በማድረግ
ግብረ መልስ በመስጠት ድጋፍ እያደረገ መሆኑ ፣ የፍትህ ዘርፉ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን በመምራት እና በመደገፍ
8
ረገድ እያበረከተ ያለዉ አስተዋጽኦ አበረታች መሆኑ ፤ በጤና ተቋማት የሚከሰቱ ውልደትና ሞትን ለመመዝገብ
እንዲቻል ከጤናው ዘርፍ ጋር የጋራ መግባቢያ ሰነድ መፈራረም መቻሉ በቀጣይ ስርአቱን በመገንባት ሂደት ምቹ
በሌላ በኩል በትምህርት ዘርፍ በኩል እድሜያቸዉ ለትምህርት የደረሱ ህጻናትን መረጃ መሰረት በማድረግ
የትምህርት ተሳትፎ እና ተደራሽነት ለማሻሻል ከልደት ምዝገባ የሚገኘውን መረጃ ለመጠቀም ተቋሙ ጋር
በጋራ ተቀናጅቶ ለመስራት ፍላጎት ያለ መሆኑ፣ የሴቶችና ሕፃናትን ሕጋዊና አስተዳደራዊ መብት ለማረጋገጥ
የኩነቶች መረጃ ያለዉን ፋይዳ በመገንዘብ በጋራ ተቀናጅቶ ለመስራት ፍላጎት ያለ መሆኑ ስርአቱን በቀጣይነት
በተመሳሳይ በመገናኛ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከቴክኖሎጂ ልማት አንፃር ያለዉ ልምድ፣ በማእከላዊ
ስታስቲክስ በኩል በህዝብና ቤቶች ቆጠራ እና በዳሰሳ ጥናት ላይ ተመስርቶ ስታትስቲክሶችን የማዉጣት ልምድ
ለቀጣይ ለወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ የአሰራር ስርአት ዝርጋታ ምቹ ሁኔታ መኖሩን የሚያመላክት ከመሆኑም በላይ
ከላይ ቁልፍ ባለድርሻ አካላት የተቋማቸዉን ግብ በአስተማማኝ መረጃ ላይ ተመስርቶ ከማሳካት አንጻር የወሳኝ
ኩነት ምዝገባ ስርአት ያለዉን ቁልፍ ድርሻ በመረዳት ስርአቱ እንዲገነባ ከፍተኛ ፍላጎት ያላቸዉ መሆኑ ለወሳኝ
ሌላዉ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን ዉጤታማ ከማድረግ አንጻር በሃይማኖት ተቋማት ልደትን፣ ሞት፣
ጋብቻና ፍች በመመዝገብ እንዲሁም ከወሳኝ ኩነት ምዝገባ መዋቅር ጋር በቅንጅት በመስራት ረገድ ያላቸዉ
ከላይ የተጠቀሱ ጉዳዮች የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን አስተማማኝ መሰረት ላይ ለመጣል እንደ መልካም
አጋጣሚ የሚወሰዱ ቢሆንም በሁሉም ባለድርሻ አካላትና በኤጀንሲው መካከል ሊኖር የሚገባው
የጋራና የተናጠል ተግባር ተለይቶ በጠንካራ ቅንጅታዊ የአሰራር ስርአት እንዲደገፍ አለመደረጉ
፣በወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ተሳታፊ የሆኑ ተቋማት የምዝገባ ስራዉን አጠናክሮ ለማስቀጠል
የጤናዉ ዘርፍ የጋራ መግባቢያ ሰነድ ከመፈራረም በዘለለ የልደት እና ሞት ማሳወቂያ ቅጽ አዘጋጅቶ
እንዲሆን በማድረግ ረገድ ተገቢ ትኩረት ሰጥቶ አለመፈጸም በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቷቸዉ ሊፈቱ
9
2.1.4 የተባባሪ አካላት ሁኔታ
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ለወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራዉ ትኩረት በመስጠት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነ
ቢሆንም የምዝገባ ስርአቱ አዲስ፣ ሰፊና ሁሉን አቀፍ ባህሪ ያለዉ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ስርአቱን በተሟላ ደረጃ
ለመዘርጋት የሚያስፈልገዉን ሰፊ ሀብት ለማሰባሰብ የሚያስችል ስልት ነድፎ ተግባራዊ ማድረግ ወሳኝ ጉዳይ
ነዉ::
ይህን ሰፊ የበጀት ክፍተት ለመሙላት ዘርፉን ለመደገፍ ፍላጎት ያላቸዉን ተባባሪ አካላት በመለየት እና ቀጣይነት
ያለዉ ግንኙነት በማድረግ በሚዘጋጁ የጋራ ምክክር መድረኮች አማካይነት ስርአቱን ለመገንባት ያለዉን ቴክኒካል
እና ፋይናንሻል ክፍተት በግልጽ በማሳየት ተባባሪ አካላት ድጋፍ ሊሰጡ የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር
በአገር ውስጥ የሚገኙ ተባባሪ አካላት ጋር የጋራ ፎረም በማቋቋም ድጋፍ ለማግኘት እየተደረገ ያለዉ
የተጀመሩ ግንኙነቶችን ተከትሎ የተወሰኑ ተባባሪ አካላት በተለይም ዩኒሴፍ እና የአለም ባንክ
በቴክኒክ በመደገፍ ረገድ አበረታች እንቅስቃሴ እያደረጉ ሲሆን ይህም በአገር አቀፍ ደረጃ
በተባባሪ አካላት የተጀመረዉ የድጋፍ ስራ አበረታች ቢሆንም በተፈጠረዉ የጋራ መግባባት መሰረት
ሁሉም ተባባሪ አካላት ድጋፍ በመስጠት ረገድ ፈጥነዉ ወደ ስራ የገቡ አለመሆኑ ፣ የትብብር መስኩ
በአንድ ማዕከል የተቀናጀ አለመሆን ½ የተወሰኑ ክልሎችን ብቻ በተናጥል የመደገፍ ፍላጎት የሚታይ
መሆኑ እና የተደረገዉ ድጋፍ ከሚጠበቀዉ አንጻር ሲታይ በጣም አነስተኛ መሆኑ የምዝገባ ስራዉን
በተሟላ በጀትና የማስፈጸም አቅም ለማስቀጠል አሉታዊ ተፅእኖ የሚፈጥር ስለሆነ ይህን ሁኔታ
በተመሳሳይ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን ዉጤታማ ለማድረግ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚገኙ እና
የወሳኝ ኩነት መረጃን በመጠቀም የጥናት እና ምርምር ስራዎችን የሚሰሩ የሙያ ማህበራት እና ልዩ
ጥቅም በግልጽ በማሳየት ያላቸዉን ሙያዊ እዉቀት እንዲያበረክቱ ማድረግ ጠቃሚ ተደርጎ የሚወሰድ
ጉዳይ ነዉ::
10
በዚህ መሰረት አደረጃጀቶቹ ከስርአቱ የሚያገኙትን ጥቅም ከወዲሁ ታሳቢ በማድረግ በትብብር
ለመስራት እያሳዩ ያለዉ ፍላጎት አበረታች ሲሆን ይህን ፍላጎት እንደ ምቹ ሁኔታ በመዉሰድ በእቅዱ
ላይ በግልጽ አካቶ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ተገቢ እና ወሳኝ ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰድ ይሆናል ::
ኤጀንሲዉ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን በመላ አገሪቱ ተግባራዊ ለማድረግ እንዲችል ተቋማዊ
መዋቅሩን እና አደረጃጀቱን ሊመልስ የሚችል የመሰረታዊ የሥራ ሂደት ለዉጥ (BPR) ጥናት
በኤጀንሲ ደረጃ ቀደም ሲል ተጠንቶ ወደ ስራ እንዲገባ የተደረገዉ የመሰረታዊ የሥራ ሂደት ለዉጥ
ያመላከተ እና ኤጀንሲዉ ስራዉን እንዲጀምር በማድረግ ረገድ ወሳኝ ድርሻ የነበረዉ ሲሆን ኤጀንሲዉ
የምዝገባ ስራዉን ሲጀምር ቀደም ሲል የተጠናዉ ተቋማዊ የመሰረታዊ የስራ ሂደት ለዉጥ ጥናት
ተቋማዊ ተልእኮዉን የሚሸከም አለመሆኑን በመረዳት ጥናቱን የመከለስ ስራ የሰራ መሆኑ በጥንካሬ
የሚወሰድ ነዉ ፡፡
ኤጀንሲዉ ተቋማዊ የመሰረታዊ የስራ ሂደት ለዉጥ ጥናቱን በማስጠናት ወደ ስራ እንዲገባ በማድረግ
ረገድ አበረታች ተግባራትን ያከናወነ ቢሆንም ጥናቱ በኤጀንሲ ደረጃ መከናወን የሚገባቸዉን
ተግባራትን በተሟላ ሁኔታ በመለየት እና ተቋማዊ የሰዉ ሃይሉን በሚፈለገዉ ደረጃ በመመለስ ረገድ
ክፍተት ያለበት ሲሆን በዚህ ረገድ የታዩ ክፍተቶችን ለመቅረፍ እንዲቻል የተከለሰዉን የመሰረታዊ
የስራ ሂደት ለዉጥ ጥናት ፈጥኖ ወደ ተግባር እንዲገባ በማድረግ ረገድ ዉስንነት ያለ መሆኑን
አፈጻጸሙ ያሳያል ፡፡
የሥራ ሂደት ለዉጥ ጸድቆ ወደ ተግባር እንዲገባ በቀጣይ ትኩረት በመስጠት መስራት ይገባል፡፡
11
2.2.2 የኤጀንሲው ሚዛናዊ ውጤት ተኮር (BSC) 2009 - 2012 ዓ.ም ጥናት ሰነድ፣
የኤጀንሲዉ ሚዛናዊ ውጤት ተኮር ሰነድ የተቋሙን ባለድርሻ እና ተገልጋይ ፍላጎት መነሻ በማድረግ
የተዘጋጀ መሆኑ፣ በኤጀንሲ ደረጃ ትኩረት ሊደረግባቸዉ የሚገቡ ስትራቴጅክ ጉዳዮችን የለየ መሆኑ ፣
ስትራቴጅክ ጉዳዮችን መነሻ በማድረግ ተቋማዊ የትኩረት መስኮችን ያመላከተ መሆኑ ፣ በኤጀንሲ
ደረጃ በስትራቴጅክ ዘመኑ መከናወን የሚገባቸዉን ግቦች እና ተግባራትን ያካተተ መሆኑ ፣ ተቋማዊ
እቅዱን የሚደገፉ ስትራቴጅክ እርምጃዎችን የለየ መሆኑ በስትራቴጅክ እቅድ ደረጃ በጥንካሬ
የኤጀንሲዉ የሚዛናዊ ውጤት ተኮር ሰነድ ከላይ የተጠቀሱ ጥንካሬዎች ያሉት ቢሆንም በስትራቴጅክ
ዘመኑ የተለዩ ግቦችን እና ተግባራትን ለማከናወን የሚያስችል በጀት የመለሰ አለመሆኑ፣ በኤጀንሲ
ደረጃ የሚዛናዊ ውጤት ተኮር ስርአቱን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ በቂ የሰዉ ሃይል የተሟላ አለመሆኑ፣
የሚዛናዊ ውጤት ተኮር ስርአቱን በተሟላ ደረጃ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የምዘና ስርአት
አለመኖር የሚዛናዊ ዉጤት ተኮር ስርአቱን በመተግበር ሂደት ያጋጠሙ ችግሮች ሲሆኑ በቀጣይ
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አገራዊ ምክር ቤት አገራዊ የምዝገባ ስርአቱን የሚመራ የኤጀንሲዉ ከፍተኛ
የስልጣን አካል ነዉ፡፡ ምክር ቤቱ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ድጋፍና ዉሳኔ በሚሹ ጉዳዮች ላይ
ዉሳኔዎችን በማሳለፍ፣ የምዝገባ ስራዉን በተሟላ ሁኔታ ለማስቀጠል በመዝጋቢ ተቋማት የሚታዩ
የአፈጻጸም ክፍተቶችን በመገምገምና አቅጣጫ በመስጠት በውሱን ደረጃም ቢሆን የበኩሉን አስተዋጽኦ
እያበረከተ የሚገኝ ሲሆን ምክር ቤቱ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አጀማመር ማብሰሪያ ፕሮግራም ላይ
በመገኘት በአገር አቀፍ ደረጃ የምዝገባ ስራዉን ለመጀመር የተከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አገራዊ ምክር ቤት የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን ለመገንባት ካለዉ ወሳኝ ሚና
አንጻር የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ሂደቱን ለማጠናከር የሚያስችል ወቅቱን የጠበቀ አቅጣጫ እና ዉሳኔ
12
ቤት ስብሰባ ላይ በተሟላ ሁኔታ በመገኘት ረገድ ክፍተት ያለ ሲሆን ምክር ቤቱ ለስርአት ዝርጋታዉ
ያለዉን ወሳኝ ድርሻ በመገንዘብ አደረጃጀቱን በላቀ ደረጃ ለመጠቀም በአፈጻጸም ወቅት የታዩ
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ የስራ አመራር ቦርድ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን በመምራት ረገድ
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ስራ አመራር ቦርድ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን በመምራት ረገድ
በምዝገባ ቅድመ ዝግጅት ወቅት የሚከናወኑ ተግባራትን በተሳካ ሁኔታ እንዲፈጻሙ ከመደገፍ እና
ተግባራትን እያከናወነ መሆኑ ኤጀንሲዉ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን ተግባራዊ በሚያደርግበት
የኤጀንሲዉ የስራ አመራር ቦርድ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራዉን በመምራትና በመደገፍ ረገድ
ያከናወናቸዉ ተግባራት አበረታች ቢሆኑም በስራ አመራር ቦርዱ የጋራ መድረክ ላይ የኤጀንሲዉ ቁልፍ
ባለድርሻ አካላት በተሟላ ደረጃ በመገኘት ሚናቸዉን በመወጣት እንዲሁም የቁልፍ ባለድርሻ
ተቋማትን በተለይም የጤና ጥበቃ ሚኒስቴርን አፈጻጸም ገምግሞ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድ
በማድረግ ፣ በተቀመጠዉ መርሃ ግብር መሰረት ተገኝቶ የቅርብ ድጋፍ በማድረግ በኩል ክፍተት ያለ
በመሆኑ በቀጣይ በጀት ዓመት የስራ አመራር ቦርዱን አቅም በመጠቀም ረገድ ትኩረት ተሰጥቶት
የሚሰራ ይሆናል::
13
2.2.5 የኤጀንሲዉ አመራርና ፈጻሚ ሁኔታ
በአመለካከት ረገድ
የኤጀንሲዉ አመራር አካል በ 2009 በጀት አመት በተቋም ደረጃ በእቅድ የተያዙ ተግባራትን
ለማስፈጸም እና የምዝገባ ስራዉን በብቃት ተግባራዊ ለማድረግ እንዲቻል የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓቱን
በመዘርጋት ረገድ የሚከናወኑ ወሳኝ ተግባራትን በውስጥ አቅም ማከናወን ይቻላል የሚል እምነት በመያዝ ወደ
ስራ የገባ መሆኑ ምዝገባዉን ለማስቀጠል ወሳኝ እና ለሌሎች ስኬቶች መነሻ የነበረ አመለካከት ነዉ ብሎ መዉሰድ
ይቻላል፡፡
የኤጀንሲዉ አመራር የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራዉን ለማስጀመር የነበረዉ ፍላጎት እና ተነሳሽነት
የምዝገባ ስራዉም ከተጀመረ ጀምሮ በዉስን የሰዉ ሃይል ነገር ግን በላቀ ቅንጅት እና ጥረት ተልኮዉን
ማሳካት እንደሚቻል በማመን ለተፈጻሚነቱ ርብርብ እያደረገ መሆኑ ለቀጣይ ተቋማዊ ስኬት
የኤጀንሲዉ አመራር አካል ተቋማዊ ለዉጡን አጠናክሮ ለመቀጠል እንዲቻል በአመለካከት በመዉሰድ
ያከናወናቸዉ አበረታች ተግባራት ያሉ ቢሆንም በተቋም ደረጃ የተጀመረዉን የለውጥ ሰራዊት ግንባታ ለዕቅድ
አፈፃፀምን ውጤታማነት ያለውን ፋይዳ በመረዳት በዕምነት ወስዶ በላቀ ደረጃ ተግባራዊ በማድረግ
፣መልካም አስተዳደርን በማስፈን ረገድ የተለዩ ክፍተቶችን አንደ ቁልፍ ችግር ወስዶ በተሟላ ደረጃ
ለመፍታት ተገቢውን ጥረት በማድረግ ረገድ ዉስንነት የነበረበት ሲሆን በእቅድ የተያዙ ተግባራት
በተያዘላቸዉ መርሃ ግብር ከመፈጸም ይልቅ የጠባቂነት ችግር የነበረበት መሆኑን አፈጻጸሙ ያሳያል፡፡
14
በሌላ በኩል የኤጀንሲዉ አመራር አካል የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር ያለውን አደጋ ተረድቶ
ከአድርባይነት በፀዳ መንፈስ የተሟላ ትግል በማድረግ፣ የለውጥ መሳሪያዎች ትግበራ ለዕቅድ
አፈፃፀምን ውጤታማነት ያላቸውን ፋይዳ በመረዳት በዕምነት ወስዶ በተሟላ ደረጃ በመተግበር
እንዲሁም በእቅድ የተያዙ ተግባራትን በእቅዱ መሰረት በተሟላ ደረጃ በመፈጸም ረገድ ክፍተት
ያለበት ሲሆን ስርአቱን ከመገንባት አንጻር በጅምር ደረጃ የታዩ ለዉጦችን ለማስቀጠል እንዲቻል
በክህሎት ረገድ
ሌላዉ ከወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓት ግንባታ ጋር ተያይዞ ትኩረት የሚሰጠዉ ጉዳይ የአመራሩን
የመፈጸም አቅም የማሳደግ ጉዳይ ነዉ ፡፡ በመሆኑም የተቋሙ አመራር አካል የወሳኝ ኩነት ምዝገባ
ጥረት አበረታች ከመሆኑም ባሻገር በምዝገባ ቅድመ ዝግጅት ወቅት የተፈጠረዉን አቅም የምዝገባ
የሚወሰድ ነዉ፡፡
በሌላ በኩል የኤጀንሲዉ አመራር አካል የምዝገባ ስራውን ቀጣይነት ለማረጋገጥ በሚደረገዉ ጥረት
መዝጋቢ አካላትን ለማብቃት እንዲቻል የስልጠና ሰነዶችን በውስጥ አቅም በማዘጋጀት እና ስልጠና
እንዲሰጥ በማድረግ ፣ የተሰጡ ስልጠናዎች ያስገኙትን ዉጤት ለማወቅ የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት
የተደረገ ሲሆን ይህም በቀጣይ ተቋማዊ አቅም በመፍጠር የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን ለማሳካት
የተቋሙን አመራር የመፈጸም አቅም በማሳደግ ረገድ የተከናወኑ አበረታች ተግባራት ያሉ ቢሆንም ዕቅዶችን
በሚፈለገው የጥራት ደረጃ በማዘጋጀት፣ ሊከናወኑ የሚችሉ ተግባራትን ብቻ ለይቶ በማቀድ እና በተቀመጡ
መርሃ ግብሮች መሰረት በመፈጸም እንዲሁም ስራዎችን ጎን ለጎን አቀናጅቶ በመምራት ረገድ ክፍተቶች ያሉ
15
በሌላ በኩል አመራሩ ስትራቴጅክ ጉዳዮች ላይ በማትኮርና ስራን በኮሙኒኬሽን በመምራት ፣ የፈጻሚዉን
የአቅም ክፍተት በመለየት በሚፈለገው ደረጃ የማብቃት ስራ በመስራት እንዲሁም እቅድን መሠረት ያደረገና
ጥራቱንና ወቅቱን የጠበቀ ሪፖርት አዘጋጅቶ በማቅረብ ረገድ የክህሎት ክፍተት ያለበት ሲሆን የክህሎት
ክፍተቱን ለመሙላት በቀጣይ በእቅድ አካቶ መስራት ትኩረት የሚሰጠዉ ተግባር ይሆናል፡፡
ተቋማዊ አሰራርና አደረጃጀቱን ከማጠናከር አንጻር የኤጀንሲዉ አመራር ከምዝገባ ቅድመ ዝግጅት ወቅት አንስቶ
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራዉን ለማስጀመር የሚያስችሉ መመሪያዎች እና የምዝገባ ሰነዶችን እንዲዘጋጁ በማድረግ
፣ አዋጁን እንዲሻሻል በማድረግ ፣ የአዋጁን መሻሻል መሰረት በማድረግ የአፈጻጸም መመሪያዎች እንዲሻሻሉ
በማድረግ እንዲሁም ለፌዴራል መዝጋቢ ተቋማት የምዝገባ ቁሳቁስ በማዘጋጀት እና ምዝገባ እንዲጀምሩ
በተመሳሳይ አመራሩ ተቋማዊ ስራዎች ከልማዳዊ አሰራር ተላቀዉ በለውጥ ሥራ አመራር ስርዓት ለመምራት
የሚያስችል የመሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ጥናት ተግባራዊ በማድረግ ረገድ አበረታች እንቅስቃሴ ያደረገ ሲሆን
የምዝገባ ስራዉም ከተጀመረ በኋላ ተቋማዊ ዕቅዱን በሚዛናዊ የውጤት ተኮር አስተቃቀድ ስልት እንዲዘጋጅ
አደረጃጀቶችን ፈጥሮ ወደ ስራ በማስገባት ረገድ አበረታች ጥረት ያደረገ ሲሆን ይህም ለቀጣይ እቅድ
አጣጥሞ በመምራት ረገድ ክፍተት ያለበት ሲሆን ክፍተቱን መሰረት ያደረገ ቀጣይነት ያለዉ
በሌላ በኩል በስራ ላይ ያለው የኤጀንሲው አደረጃጀት ተቋማዊ ተልዕኮውን በተሟላ ደረጃ እንዲሸከም
ለማድረግ እንዲቻል የተጀመረዉ የመሰረታዊ የስራ ሂደት ለዉጥ ጥናት ተጠናቆ ወደ ተግባር እንዲገባ
16
በማድረግ ፣ በሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የጉዲፈቻ ኩነት ምዝገባ እንዲጀመር ተገቢዉን
ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም በእቅድ የተያዙ ተግባራትን በውጤት እየቃኙ በመምራት ረገድ ክፍተት
ታይቶበታል ፡፡
በመፈፀም ረገድ ክፍተት ያለበት ሲሆን ክፍተቱን ለመሙላት በቀጣይ ትኩረት በመስጠት መስራት
ይገባል፡፡
የኤጀንሲዉ አመራር የግብአት አቅርቦት ስርአትን ከማጠናከር አንጻር የምዝገባ ስራዉን ለማስጀመር
የምዝገባ ስራዉም ከተጀመረ በኋላ ለፌዴራል መዝጋቢ ተቋማት የሚያገለግል መመሪያ ፣ የክብር
መዝገብ እና የምስክር ወረቀት በማዘጋጀት እና ለስርጭት ዝግጁ በማድረግ ፣ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ
ስራዉን ቀጣይነት በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝ ሚና ያላቸዉ ግብአቶችን ለማሟላት የሚያስችል የበጀት
ድጋፍ በተባባሪ አካላት እንዲደረግ ጥረት በማድረግ ረገድ የተሻለ ስራ መስራት ችሏል፡፡
በሌላ በኩል ኤጀንሲዉ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን በተሻለ ሁኔታ ለመምራት የሚያስችለዉ ቢሮ
ከመንግስት በመረከብ እና ቢሮዉን በማደስ እንዲሁም ተቋማዊ ግብአቶችን በመጠቀም ረገድ የሚታዩ
ሲሆን ከግብአት አቅርቦት ጋር ተያይዞ የተከናወኑ ተግባራት የምዝገባ ስራዉ ዉጤታማ እንዲሆን
17
የኤጀንሲዉ አመራር የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ግብአቶችን በማሟላት
ተልእኮ ለማሳካት ወሳኝ ግብአት የሆነዉን የሰዉ ሃይል በሚፈለገዉ ደረጃ በማሟላት እና የተገኙ
ግብአቶችን የተቋሙን ተልዕኮ በሚያሳካ መንገድ አሟጦ በመጠቀም ፣ በተቋም ደረጃ በግብአት
አጠቃቀም ዙሪያ የሚታዩ ችግሮችን በቀጣይነት በመገምገም እና ችግሩ በተሟላ ደረጃ እንዲፈታ
በማድረግ ረገድ ክፍተት ያለበት ሲሆን ክፍተቱን ለመሙላት በቀጣይ ትኩረት በመስጠት የሚሰራ ይሆናል፡፡
የኤጀንሲዉ አመራር የድጋፍና ክትትል ስራዎችን ዉጤታማ ለማድረግ የወሳኝ ኩነት መዝጋቢ አካላት ምዝገባውን ከመጀመር
አንፃር ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ ለማወቅ የሚያስችል ዳሰሳ በማድረግ በተገኙ መረጃዎች ላይ ተመስርቶ ክፍተቶችን
በሌላ በኩል ኤጀንሲዉ በምዝገባ አፈጻጸም ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን በድጋፍና ክትትል በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫ
እንዲቀመጥ በማድረግ ረገድ ያከናወነዉ ተግባር የምዝገባ ስራዉን ዉጤታማነት ከማረጋገጥ አንጻር የሚኖረዉ አስተዋጥኦ
የጎላ ነዉ፡፡
የኤጀንሲዉ አመራር ተቋማዊ የድጋፍ እና ክትትል ተግባሩን ዉጤታማ ለማደረግ ያከናወናቸዉ ተግባራት
አበረታች ቢሆኑም በእቅድ የሚመራ የድጋፍና ክትትል ስርአት ዘርግቶ ተግባራዊ በማድረግ እንዲሁም ቀጣይነት
ያለዉና ችግር ፈቺ የሆነ የክትትልና ድጋፍ ስርአት ዘርግቶ በመፈጸም ረገድ ክፍተቶች ታይተዉበታል፡፡
በተመሳሳይ እቅድ አፈጻጸም ላይ ተመስርቶ ጠንካራ እና ቀጣይነት ያለዉ የእቅድ አፈፃፀም ግምገማና ግብረ -
መልስ ስርዓት ዘርግቶ ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ዉስንነት ያለበት ሲሆን በዚህ ረገድ የታዩ ክፍተቶችን
በመቅረፍ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን በጠንካራ የድጋፍና ክትትል ስርአት አማካይነት ዉጤታማ ለማድረግ
18
2.2.5.2 የኤጀንሲዉ ፈጻሚ
በአመለካከት ረገድ
የኤጀንሲዉ ፈጻሚ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓቱን በመዘርጋት ረገድ የሚከናወኑ ተግባራትን በውስጥ አቅም
ማከናወን ይቻላል የሚል እምነት በመያዝ ወደ ስራ የገባ መሆኑ ምዝገባዉን ለማስቀጠል ወሳኝ እና ለሌሎች ስኬቶች
መነሻ የነበረ አመለካከት ነዉ ብሎ መዉሰድ የሚቻል ሲሆን በተመሳሳይ የምዝገባ ስራዉም ከተጀመረ በኋላም
በዉስን የሰዉ ሃይል ነገር ግን በላቀ ቅንጅት እና ጥረት ተልኮዉን ማሳካት እንደሚቻል በማመን
ለተፈጻሚነቱ ርብርብ እያደረገ መሆኑ ለቀጣይ ተቋማዊ ስኬት መሰረት ነዉ ብሎ መዉሰድ ይቻላል፡፡
የኤጀንሲዉ ፈጻሚ አካል ተቋማዊ ለዉጡን አጠናክሮ ለመቀጠል እንዲቻል በአመለካከት በመዉሰድ ያከናወናቸዉ
አበረታች ተግባራት ያሉ ቢሆንም በተቋም ደረጃ የተጀመረዉን የለውጥ ሰራዊት ግንባታ ለዕቅድ አፈፃፀምን
ውጤታማነት ያለውን ፋይዳ በመረዳት በዕምነት ወስዶ በላቀ ደረጃ ተግባራዊ በማድረግ ፣መልካም
አስተዳደርን በማስፈን ረገድ የተለዩ ክፍተቶችን እንደ ቁልፍ ችግር ወስዶ ለመፍትሄዎቹ በጋራ
የኤጀንሲዉ ፈጻሚ የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር ያለውን አደጋ ተረድቶ ከአድርባይነት በፀዳ
መንፈስ የተሟላ ትግል በማድረግ፣ የለውጥ መሳሪያዎች ትግበራ ለዕቅድ አፈፃፀምን ውጤታማነት
ያላቸውን ፋይዳ በመረዳት በዕምነት ወስዶ በተሟላ ደረጃ በመተግበር እንዲሁም በእቅድ የተያዙ
ተግባራትን በእቅዱ መሰረት በተሟላ ደረጃ በመፈጸም ረገድ ክፍተት ያለበት ሲሆን ስርአቱን ከመገንባት
አንጻር በጅምር ደረጃ የታዩ ለዉጦችን ለማስቀጠል እንዲቻል አመለካከቱ የተስተካከለ እና የተሟላ
የለዉጥ ሰራዊት ገንብቶ መንቀሳቀስ እንዲቻል የተለዩ ክፍተቶችን ትኩረት ሰጥቶ መፍታት ይገባል፡፡
በክህሎት ረገድ
የኤጀንሲዉ ፈጻሚ አካል የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓት ግንባታ ዓለማቀፋዊ መርሆዎችን ፣
በምዝገባ ቅድመ ዝግጅት ወቅት የተፈጠረዉን አቅም የምዝገባ ስራዉን ለማስጀመር በግብአትነት
በመጠቀም ምዝገባዉን እንዲጀመር ያደረገ መሆኑ በጥንካሬ የሚወሰድ ሲሆን ፈፃሚዉ በተቋሙ
19
በተፈጠሩ የተለያዩ መድረኮች አማካይነት አቅሙን ለማሳግ እና የዕውቀትና ክህሎት ልውውጥና
ሽግግር መደረጉ በቀጣይ ተቋማዊ አቅም በመፍጠር የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን ለማሳካት
የተቋሙ ፈጻሚ የመፈጸም አቅም በማሳደግ ረገድ የተከናወኑ አበረታች ተግባራት ያሉ ቢሆንም በእቅድ የተያዙ
ተግባራት አፈጻጸም ላይ የተሟላ ግንዛቤ በመያዝ ፣ የክህሎት ክፍተቱን በመለየት እና ለመሙላት በሚፈለገዉ
ደረጃ በመንቀሳቀስ እንዲሁም እቅድን መሠረት ያደረገና ጥራቱንና ወቅቱን የጠበቀ ሪፖርት አዘጋጅቶ በማቅረብ
የኤጀንሲዉ ፈጻሚ አካል ተቋማዊ አሰራርና አደረጃጀቱን ከማጠናከር አንጻር ከምዝገባ ቅድመ ዝግጅት ወቅት
አንስቶ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራዉን ለማስጀመር የሚያስችሉ መመሪያዎች እና የምዝገባ ሰነዶችን እንዲዘጋጁ
በማድረግ ሂደት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ አበረታች ስራዎችን የሰራ ሲሆን በተቋማዊ የመሠረታዊ የሥራ ሂደት
ለውጥ ጥናት ዝግጅት እና ትግበራ ላይ እንዲሁም በተቋማዊ የሚዛናዊ ውጤት ተኮር እቅድ ዝግጅት እና
የኤጀንሲዉ ፈጻሚ ከአሰራር እና ከአደረጃጀት አኳያ ከላይ የተጠቀሱ ጥንካሬዎች ያሉት ቢሆንም
በእቅድ የተያዙ ተግባራትን በጠንካራ ቅንጅታዊ አሰራር ላይ ተመስርቶ በመፈጸም እና በዕቅድ የተያዙ
ተግባራትን በውጤት እየቃኙ በመፈጸም ረገድ ክፍተት ያለበት ሲሆን ክፍተቱን ለመሙላት በቀጣይ
20
የኤጀንሲዉ ፈጻሚ ግብአቶችን በማሟላት እና ጥቅም ላይ እንዲዉሉ ለማድረግ ረገድ
አሟጦ በመጠቀም ረገድ ክፍተት የነበረበት በመሆኑ በቀጣይ በትኩረት ሊፈታ ይገባዋል፡፡
የኤጀንሲዉ ፈጻሚ አካል በድጋፍና ክትትል ስራዎች ላይ በመሳተፍ እና በመዝጋቢ አካላት ረገድ በአፈጻጸም ወቅት የሚታዩ
ችግችን ለመፍታት ያደረገዉ ጥረት የሚበረታታ ሲሆን የድጋፍ እና ክትትል ስራዎችን ችግር ፈቺ በሆነ ሁኔታ
ኤጀንሲዉ ተቋማዊ ስትራቴጅክ እቅዱን መነሻ በማድረግ በ 2009 በጀት አመት ለመፈጸም በእቅድ የተያዙ
ግቦችን እና ተግባራትን አፈጻጸም በመገምገም በእቅድ አፈጻጸም ወቅት የተለዩ ጠንካራ አፈጻጸሞችን በቀጣይ
በጀት አመት የበለጠ ተጠናክረዉ እንዲቀጥሉ ለማድረግ እንዲሁም በሚፈለገዉ ደረጃ ያልተፈጸሙ ግቦች እና
ተግባራትን በመለየት እና በምን ምክንያት ሳይፈጸሙ እንደቀሩ በማወቅ በ 2010 በጀት አመት እቅድ ላይ
በመሆኑም በክፍል ሶሰት በ 2009 በጀት አመት በዝግጅት ምእራፍ ፣ በተግባር ምእራፍ እና በማጠቃለያ
3.1.1.1 ጥንካሬዎች
21
የኤጀንሲዉን አመራር እና ፈፃሚ አቅም በማሳደግ ረገድ ፣
የኤጀንሲዉን አመራር እና ፈጻሚ አካል የአፈጻጸም ክፍተት ለመለየት የሚያስችል የግምገማ መድረክ
የጥልቅ ተሃድሶ መድረክ በማዘጋጀት እቅዱን በመፈጸም ረገድ በአመራር እና በፈጻሚ ደረጃ የነበሩ
ጥንካሬዎችን እና ክፍተቶችን በመለየት ተቋማዊ አፈጻጸሙን የተሻለ ለማደረግ የሚያስችል የጋራ መግባባት
ኤጀንሲዉ በ 2009 በጀት አመት በእቅድ የያዛቸዉን ተግባራት አፈጻጸም በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫ
ለማስቀመጥ እንዲቻል ከክልል እና ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲዎችን አፈጻጸም
ለመገምገም የሚያስችል ያጋራ ምክክር መድረክ በማዘጋጀት በእቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረኩ የታዩ
የተሰራ መሆኑ፣
በኤጀንሲዉ የ 2009-12 ስትራቴጅክ እቅድ እና የ 2009 ዓ.ም አመታዊ እቅድ ዙሪያ ለፌዴራል ፣
ለክልል እና ከተማ አስተዳደር ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ አመራርና ፈጻሚዎች ስልጠና ነክ
መደረጉ፣
የኤጀንሲዉን የሰዉ ሃይል አቅም በማሳደግ ተቋማዊ ተልእኮዉን ለማሳካት እንዲቻል ለኤጀንሲዉ
የኤጀንሲዉን ሰራተኞች የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዙሪያ የሚታዩ ክፍተቶችን በዳሰሳ ጥናት በመለየት
22
የግብአት አጠቃቀም አቅም በማሳደግ ረገድ ½
በክልልና በከተማ አስተዳደር ደረጃ የምዝገባ ስራዉን ለማከናወን የሚያስችሉ የክብር መዝገብ እና
በኤጀንሲ ደረጃ የሰው ኃይል ስምሪትና አያያዝ የውስጥ አሰራር ማኑዋል እንዲዘጋጅ መደረጉ ፣
ተቋማዊ የሥራ ደረጃ ምዘና ጥናት መሰረት በማድረግ በተቋም ደረጃ የሚገኙ ሰራተኞች በተላከዉ መመሪያ መሰረት ፍትሃዊ
ኤጀንሲዉ ከመንግስት የተረከበዉን ቢሮ በኤጀንሲዉ ፍላጎት እና ለስራ ምቹ ሊሆን በሚችል አግባብ በማደስና
በአስፈላጊ የቢሮ ግብአቶችን በማደራጀት ሰራተኛዉ ለስራ ምቹ በሆነ ሁኔታ በአዲስ ቢሮ ስራ እንዲጀምር
የኤጀንሲዉን ሰራተኛ በህግ የተፈቀደለትን ጥቅማ ጥቅም በወቅቱ እንዲያገኝ የማድረግ ስራ የተሰራ መሆኑ ፣
በኤጀንሲ ደረጃ የሚገኙ ሴቶችንና አካል ጉዳተኞችን ከእቅድ ዝግጅት ጀምሮ በትግበራ እና በአፈጻጸም ግምገማ ላይ
ከተባባሪ አካላት ጋር የጋራ መግባባት በመፍጠር ተቋማዊ ተልእኮዉን ለማሳካት የሚያስችል የበጀት ድጋፍ
የ 2009 በጀት አመት የኤጀንሲዉ የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም ከ 2008 በጀት አመት ተመሳሳይ ወቅት
3.1.1.2 ድክመቶች
23
የኤጀንሲዉን አመራር እና ፈጻሚ አቅም ለማጠናር የሚያስችል የተሟላ ስልጠና በመስጠት እና የራስ ማብቂያ
በበጀት አመቱ ክፍት መደቦችን በሰዉ ሃይል ለማሟላት በእቅድ የተያዙ ተግባራት በተሟላ ደረጃ የተፈጸመ አለመሆኑ፣
የኤጀንሲውን ሰራተኞች የእውቀትና ክህሎት ክፍተት በዳሰሳ ጥናት ለመለየት በእቅድ የተያዘዉ ተግባር የተፈጸመ አለመሆኑ ፣
ለኤጀንሲዉ ሰራተኞች በአካባቢ ጥበቃ፣ በኤች .አይ.ቪ፣ በአካል ጉዳተኞች፣ በሰብዓዊ መብት፣ በህፃናት መብት ዙሪያ
3.1.2.1 ጥንካሬዎች
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራ አመራር ቦርድ የኤጀንሲዉን አፈጻጸም በመገምገም እና በአፈጻጸም ወቅት
የተሰራ መሆኑ ፣
የኤጀንሲዉን የለዉጥ ሰራዊት አደረጃጀት ለማጠናከር እንዲቻል የለዉጥ ሰራዊት አደረጃጀት ለመፍጠር
ተቋማዊ ተልእኮዉን ለማሳካት እንዲቻል በሚዛናዊ ዉጤት ተኮር ምዘና ስርአት የተቃኘ
መሆኑ ፣
24
በአመራሩ እና በፈጻሚ ደረጃ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር እና የኪራይ ሰብሳቢነት ችግሮችን በግምገማ በመለየት
ከአማካሪ ድርጅት ጋር ተያይዞ የአሰራር ክፍተቱን የፈጠሩ የኤጀንሲዉ አካላት እና አማካሪ ደርጅቱ በህግ ተጠያቂ
በኤጀንሲዉ የፋይናንስ እና የንብረት አጠቃቀም ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በመለየት በቀጣይ እንዲስተካከሉ ለፈጻሚ አካላት የምክር
የኤጀንሲዉን የበጀት አጠቃቀም አቅም ለማሳደግ እንዲቻል ከገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር ጋር
በመቀናጀት የኤጀንሲዉ ባለሙያዎች በፕሮግራም በጀት ዙሪያ ስልጠና እንዲያገኙ የማድረግ ስራ የተሰራ መሆኑ ፣
ረገድ፣
ቅጽ፣ምስክር ወረቀትና የተጠቃለለ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ፣ የመረጃ አደረጃጀት፣ ቅብብሎሽ፣ አያያዝና
አዋጁን ለማሻሻል እንዲቻል ከፌዴራል ዋና አቃቤ ህግ ጋር በጋራ ጥናት በማድረግ የአዋጅ ማሻሻያዉ
ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የወሳኝ ኩነት መረጃዎችን ለፌዴራል ኤጀንሲዉ እንዲልኩ በማድረግ መረጃዎችን የመቀበል ፣ የማጥራት
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አጀማመር ማብሰሪያ መድረክ ሰፊ የህዝብ ንቅናቄ ሊፈጥር በሚችል መልኩ በማክበር
መሆኑ፣
25
የመረጃ አመዘጋገብ፣ አደረጃጀትና አያያዝ ደህንነትን በማሻሻል ረገድ ½
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ መረጃ ደህንነቱ ተጠብቆ እንዲደራጅ ለማድረግ ኤጀንሲዉ ከመንግስት
የተሰጠዉን አሮጌ ህንጻ በርካታ በጀት በመመደብ ህንጻዉ መረጃ ለመያዝ አመች በሆነ ሁኔታ በማደስ
በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ዙሪያ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የክፍተት ዳሰሳ በማድረግ ስልጠና
ሁሉንም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ያሳተፈ እና የወረዳ መዋቅሩን ማእከል ያደረገ ስልጠና
የተሰጠ መሆኑ ፣
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን በመገንባት ሂደት ወሳኝ ድርሻ ላላቸዉ ቁልፍ ባለድርሻ አካላት
የግንዛቤ ማሥጨበጫ መድረክ በማዘጋጀት የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን በመገንባት ሂደት
ከኤጀንሲዉ ቁልፍ ባለድርሻ ተቋም ከሆነዉ ከማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ጋር በቅንጅት የሚሰሩ ስራዎችን
በተጠናከረ አግባብ ለመስራት የሚያስችል የጋራ መግባቢያ ሰነድ በማዘጋጀት የመፈራረም ስራ የተሰራ መሆኑ ፣
26
በኤጀንሲዉ ስራ አመራር ቦርድ ስብሰባ ላይ ወሳኝ ባለድርሻ አካላት ኤጀንሲዉን በመደገፍ ረገድ ያላቸዉ
አፈጻጸም በሪፖርት እንዲቀርብ በማድረግ ቦርዱ በቅንጅታዊ አሰራሩ ላይ በታዩ ክፍተቶች ዙሪያ አቅጣጫ
3.1.2.2 ድክመቶች
ተቋማዊ የለዉጥ ሰራዊት ግንባታ ስራዉ በተጠናከረ አግባብ በመምራት እና የኪራይ ሰብሳቢነት እና የመልካም አስተዳደር
ለህብረተሰቡ በስርአቱ ዙሪያ በቂ ግንዛቤ በመፍጠር ተሳትፎዉ በሚፈለገዉ ደረጃ ማሳደግ አለመቻሉ፣
3.1.3.1 ጥንካሬዎች
በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚነሱ ቅሬታዎችን በመለየት ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል ቅሬታ እና አቤቱታዎችን ተቀብሎ
በምዝገባ ሂደቱ ላይ በአገልግሎት አሠጣጥ ረገድ የቅሬታ መንስኤ የሚሆኑ ጉዳዮችን በመለየት ችግሩን የአሰራር ስርአቱን
27
በኤጀንሲ ደረጃ ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካላትን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከማጠናከር አንጻር በኤጀንሲዉ ደረጃ ልዩ
ድጋፍ የሚሹ አካላትን ፍላጎት መሰረት የደረገ እቅድ በማዘጋጀት ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት የተደረገ መሆኑ፣
የአገልግሎት ተደራሽነትና ተጠቃሚነትን በማሳደግ ረገድ ተቋማዊ አፈጻጸሙ ያለበትን የአፈጻጸም ደረጃ ለማወቅ
እንዲቻል ከህግ ማእቀፍ ፣ ከአደረጃጀት ፣ ከአቅም ግንባት ስራዎች አፈጻጸም እንዲሁም ከሪፖርት እና መረጃ ቅብብሎሽ
ስርአት አንጻር የዳሰሳ ጥናት ለማድረግ የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ ጥናቱ እንዲጀመር የተደረገ መሆኑ፣
በኤጀንሲ ደረጃ የድጋፍና ክትትል ተግባራትን በመፈጸም ሂደት የሚታዩ የድጋፍና ክትትል ክፍተቶችን በዳሰሳ ጥናት የመለየት ስራ የተሰራ
መሆኑ ፣
መሆኑ፣
3.1.3.2 ድክመቶች
የተገልጋዮችን ቅሬታ ለመቀነስ የሚያስችሉ ስልቶችን በተሟላ ደረጃ ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ክፍተት ያለ መሆኑ፣
በየደረጃዉ ለሚገኙ 13,694 የወሳኝ ኩነት መዝጋቢ አካላት በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ጽንሰ ሃሳብ እና አተገባባር
በየደረጃዉ ለሚገኙ 5,515,751 ለሚሆኑ ባለድርሻ አካላትና የህብረተሰብ ክፍል በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ጽንሰ
ሃሳብ ዙሪያ ግንዛቤ በመፍጠር በምዝገባ ስራዉ ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ የተፈጠረ መሆኑ፣
በአገር አቀፍ ደረጃ ለምዝገባ ስራ አስፈለጊ የሆኑ ግብአቶች እንዲሟሉ በማድረግ ምዝገባ መጀመር
ከሚገባቸዉ 18,616 ቀበሌዎች በ 15,527 /83.5%/ የምዝገባ ማእከላት የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራ
እንዲጀመር መደረጉ ፣
28
በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ምዝገባዉን በጀመሩ የምዝገባ ማእከላት አማካይነት በአራቱም የኩነት አይነቶች
በእቅድ ከተያዘዉ 1,488,231 ኩነት መካከል 631,854 /42%/ ያህል ኩነት ምዝገባ በማከናወንና መረጃዉን
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአት ግንባታ ያለበትን የአፈጻጸም ደረጃ በዳሰሳ ጥናት በመለየት ስርአቱን በመገንባት
በፌዴራል ደረጃ የወሳኝ ኩነት እንዲመዘግቡ በህግ ሃላፊነት የተሰጣቸዉ ተቋማት የምዝገባ ስራዉን
በሚፈለገዉ ደረጃ ባይሆንም ህብረተሰቡ በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ጠቀሜታ ላይ ግንዛቤ የፈጠረ መሆኑ ፣
በሚፈለገዉ ደረጃ ባይሆንም በየደረጃዉ የሚገኘዉ የፖለቲካ አመራር የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን በመደገፍ
በሚፈለገዉ ደረጃ ባይሆንም የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱ ለመገንባት የሚያስፈልጉ ግብአቶችና ለማሟላት
እንዲቻል ከተባባሪ አካላት ጋር በተፈጠረ ግንኙነት አማካይነት ተባባሪ አካላት ስርአቱን በበጀትና በቴክኒክ
እንዲደግፉ መደረጉ ፣
የኤጀንሲዉ አመራር እና ፈጻሚ በተለያየ ጊዜ በተሰጠዉ ስልጠና ፣ ልምድ ልዉዉጥ አማካይነት ስርአቱን
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ መዋቅሩን በማጠናከር ረገድ ወሳኝ ሚና ያለዉ የሰዉ ሃይል በማሟላት ወደ ስምሪት
ገብቶ ተቋማዊ እቅዱን በመፈጻም ረገድ የበኩሉን ድረሻ እንዲወጣ የተደረገ መሆኑ፣ / ከፌዴራል እስከ ወረዳ
29
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን በመደገፍ ረገድ ወሳኝ ሚና ያላቸዉ በየደረጃዉ የሚገኙ የዘርፉ
አለመሆኑ በተለይም የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራዉን ዉጤታማ በማድረግ ረገድ ወሳኝ ሚና ያለዉ
በየደረጃዉ የሚገኙ የወሳኝ ኩነት መዝጋቢ አካላት ምዝገባዉን በሚፈለገዉ የጥራት ደረጃ ለማከናወን
በፌዴራል ደረጃ የወሳኝ ኩነት እንዲመዘግቡ በህግ ግዴታ የተጣለባቸዉ መዝጋቢ አካላት የምዝገባ
የምዝገባ ስራዉን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ወሳኝ ድርሻ ያለዉ የቀበሌ ስራ አስኪያጅ ተጠሪነቱ ለሌላ
አካል በመሆኑ ለክትትልና ድጋፍ ስራ አስቸጋሪ በመሆኑ ለስራዉ ተገቢዉን ትኩረት በመስጠትና
ባለቤት ሆኖ በመፈጸም ረገድ ክፍተት የፈጠረ እና በምዝገባዉ ጥራት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳደረ
መሆኑ ፣
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአት ግንባታ ላይ ህብረተሰቡ ያለዉን ተሳትፎ ለማጠናከር እንዲቻል
ህብረተሰቡ በስርአቱ ዙሪያ በቂ ግንዛቤ ያለዉ ባለመሆኑ ኩነቶችን የማስመዝገብ ተሳትፎዉ አነስተኛ
መሆኑ፣
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አላማ የዜጎችን መረጃ በወቅቱና በጥራት በመመዝገብ መረጃዉ ለህግ፣
ወቅታዊ የኩነት ምዝገባ ላይ ከማተኮር ይልቅ ጊዜዉ ያለፈበት ኩነት የማስመዝገብ ችግር ያለ መሆኑ፣
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ መረጃ በሚፈለገዉ የጥራት ደረጃ በመመዝገብ እና የመረጃዉን ደህንነት
በመንግስት እና በተባባሪ አካላት ድጋፍ ግብአቶችን ለማሟላት የተደረገ ጥረት ያለ ቢሆንም የበጀት
ፍላጎቱ ሰፊ በመሆኑ ይህን የበጀት ክፍተት ለመሙላት አስተማማኝ የበጀት ምንጭ አለመኖር፣
30
የመረጃ ቅብብሎሽ ስርአቱ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ የተደገፈ ባለመሆኑ ምክንያት በአመዘጋገብ ፣
መረጃን ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ፌዴራል ባለዉ መዋቅር ተደራሽ በማድረግ እንዲሁም መረጃዎችን
ስለሆነም በ 2009 በጀት አመት በእቅድ ተይዘዉ የተከናወኑ ተግባራት ያስገኙትን ዉጤት የበለጠ አጠናክሮ
ለመቀጠል እና እቅዱን በመፈጸም ረገድ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመፍታት በ 2010 በጀት አመት የተሻለ
ክፍል አራት፡- የፌዴራል ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ የ 2010 በጀት አመት
ዕቅድ
በተቋሙ የ 2010 በጀት አመት ፊዚካል እቅድ ዙሪያ ለክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች
ኦረንቴሽን መስጠት ፣
የኤጀንሲዉ ዳይሬክቶሬቶች የተቋሙን እቅድ መነሻ በማድረግ የ 2010 ዓ.ም እቅድ እንዲያዘጋጁ
ማድረግ ፣
የኤጀንሲዉ ዳይሬክቶሬቶች የ 2010 ዓ.ም እቅድ ለስራ ሂደቱ ፈጻሚዎች እንዲያወርዱ ማድረግ
፣
የኤጀንሲዉን የ 2010 እቅድ ለማሳካት ወሳኝ ድርሻ ያላቸዉን ሌሎች እቅዶች ማዘጋጀት፣
የኤጀንሲዉን የ 2010 በጀት አመት የሰብአዊ መብት ድርጊት መርሃ ግብር እቅድ ማዘጋጀት፣
የኤጀንሲዉን የ 2010 ዓ.ም የመልካም አስተዳደር እና የለዉጥ ስራዎች እቅድ ማዘጋጀት፣
31
ተቋሙ የሥራ ሂደቶች የፈፃሚዉን የዕውቀትና የክህሎት ክፍተትን ለማሳደግ የሚያስችል የራስ ማብቂያ ዕቅድ
እንዲያዘጋጁ ማድረግ ፣
የኤጀንሲው አመራር የመምራት አቅም ሊያጎለብት የሚችል ስልጠና መስጠት፣
ለኤጀንሲዉ አመራር በሚዛናዊ ዉጤት ተኮር / BSC / ጽንሰ ሃሳብ እና አተገባበር ዙሪያ ስልጠና መስጠት ፣
ለኤጀንሲዉ አመራር በፕሮግራም በጀት አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና መስጠት፣
ለኤጀንሲዉ አመራር በትራንስፎርሜሽናል ሊደር ሽፕ ዙሪያ ስልጠና መስጠት ፣
በተዘጋጀዉ የልምድ ልዉዉጥ ማኑዋል ዙሪያ በኤጀንሲ ደረጃ የጋራ መግባባት መፍጠር ፣
የኤጀንሲዉ ዳይሬክቶሬቶች የእርስ በእርስ የልምድ ልዉዉጥ የሚያደርጉበት አሰራር ተግባራዊ ማድረግ ፣
የኤጀንሲዉ ስራ አመራር ቦርድ አባላት ፣ የኤጀንሲዉ ማኔጅመንት አባላት እና የቡድን መሪዎች የወሳኝ ኩነት ምዝገባ
አተገባበር ዙሪያ የዉጭ አገር ልምድ እንዲያገኙ ማድረግ፣
በልምድ ልዉዉጥ ወቅት የተለዩ ምርጥ ልምዶችን መቀመር እና ማሰራጨት፣
የኤጀንሲዉን ዳይሬክቶሬቶች በለዉጥ ስራዎች አተገባበር ፣ በእቅድ ፣ ሪፖርትና በጀት ዝግጅት ድጋፍ መስጠት፣
የግቡ ውጤት፡ የመፈፀም አቅማቸው ያደገ አመራርና ፈፃሚ ½
ግብ 2 :- ተቋማዊ የለዉጥ ስራ አመራር ዉጤታማትን ማሻሻል
32
የለውጥ ሥራ አመራር ስርዓትን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ የለውጥ መሳሪያዎችን ማዘጋጀት፣
የኤጀንሲዉን የዜጎች ቻርተር ማዘጋጀት፣
በኤጀንሲ ደረጃ የፈጣን ለዉጥ አምጭ ተግባራትን / አቅጣጫ ጠቋሚ ፣ የቢሮ መግለጫ ፣ ባጅ ፣ የጠረንጴዛ መግለጫ
/ እንዲሟላ ማድረግ ፣
ተቋማዊ ተግባራትን በተደራጀ የለዉጥ ሰራዊት እንዲመራ ማድረግ፣
33
የኤጀንሲዉን አመራር እና ፈጻሚ የኢ/ቴክኖሎጅ አጠቃቀም ክፍተት ለመሙላት የሚያስችል ስልጠና
መስጠት፣
ለኤጀንሲዉ ሰራተኞች የመሰረታዊ ኮምፒዉተር ስልጠና መስጠት፣
ለኤጀንሲዉ ሰራተኞች የዳታ ኢንትሪና ቫሊዴሽን ስልጠና መስጠት ፣
ለኤጀንሲዉ ሰራተኞች በኤስ ፒ ኤስ ኤስ ዘሪያ ስልጠና መስጠት፣
ለኤጀንሲዉ የኢን/ ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በአድቫንስድ ኔት ወርክ ዙሪያ ስልጠና መስጠት፣
ለኤጀንሲዉ የኢን/ ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በፕሮግራሚንግ ዙሪያ ስልጠና መስጠት፣
ለኤጀንሲዉ የህዝብ ግንኙነት ባለሙዎች በፊልም እና ፎቶ ኢዲቲንግ ዙሪያ ስልጠና መስጠት፣
ለኤጀንሲዉ የህዝብ ግንኙነት ባለሙዎች በግራፊክስ ዙሪያ ስልጠና መስጠት፣
ለኤጀንሲዉ የጥናት ምርምርና አሰራር ስርአት ባለሙያዎች በክብር መዝገብ እና የምስክር
ወረቀት ዲዛይን ዙሪያ ስልጠና መስጠት፣
ሰራተኞች የአመት ፈቃዳቸዉን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የፈቃድ አሰጣጡ በእቅድ እንዲመራ ማደረግ ፣
34
በተቋም ደረጃ የግንቦት 20 በአል ማክበር ፣
35
በተዘጋጀዉ የድጋፍና ክትትል ማኑዋል ዙሪያ በኤጀንሲ ደረጃ የጋራ መግባባት መፍጠር ፣
የድጋፍና ክትትል ተግባራትን ማከናወን ፣
ድጋፍና ክትትል ለማድረግ የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማከናወን፣
ለክልል እና ከተማ አስተዳደር ድጋፍና ክትትል ማድረግ፣
የኤጀንሲዉን የሰብአዊ መብት የድርጊት መርሃ ግብር አፈጻጸም በመገምገምና ሪፖርት በማዘጋጀት
ለሚመከተዉ አካል ሪፖርት መላክ ፣
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ማሰልጠኛ ሰነድ በማዘጋጀት ከመዝጋቢ አካላት የጋራ ማድረግ ፣
የስልጠና አዘጋጃጀት እና አሰጣጥ ጋይድላይን ማዘጋጀት፣
ለፌዴራል መዝጋቢ ተቋማት ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የስልጠና ሰነድ ማዘጋጀት፣
ለክልሎች እና ከ/አስተዳደሮች ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የአዋጁን ማሻሻያና የዳሰሳ ጥናት
ግኝቶችን ያካተተ የስልጠና ማኑዋል ማዘጋጀት፣
በተዘገጀዉ የስልጠና እቅድ እና የሥልጠና አተገባበር ዙሪያ ከመዝጋቢ አካላት ጋር የጋራ መግባባት
መፍጠር፣
36
ለክልል ፣ ለከተማ አስተዳደር እና ለፌዴራል መዝጋቢ ተቋማት አመራር እና ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት፣
ለአራቱ የፌዴራል መዝጋቢ ተቋማት በምዝገባ አፈጻጸም መመሪያ ላይ ስልጠና መስጠት፣
ለክልል እና ከተማ አስተዳደር አመራሮችና ባለሙያዎች በተሻሻለዉ የምዝገባ አፈጻጸም መመሪያ
ዙሪያ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት፣
ለክልልና ከተማ አስተዳደር ወ/ኩ/ም/ኤ/ አመራርና ባለሙያዎች በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ
አጠቃቀም ዙሪያ ቴክኒካዊ ስልጠና መስጠት ½
በዳታ ኢንኮዲንግ፣ በዳታ ቬሪፊኬሽን ፣ ኢንትሪ እና ቫሊዴሽን ዙሪያ ለመረጃ ቅበላ ባለሙያዎች
ቴክኒካዊ ስልጠና መስጠት ½
ለክልልና ከ/አስተዳደር የጥናትና ምርምር ባለሙያዎች በጥናትና ምርምር ክህሎት ዙሪያ ስልጠና
መስጠት፣
ልዩ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸዉ ክልሎች / አፋር፣ ጋምቤላ፣ ቤኒሻንጉል፣ ሶማሌ፣ ድሬዳዋ ፣ ሃረር /
አመራሮች እና ባለሙያዎች በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ትግበራ ዙሪያ ስልጠና መስጠት፣
በክልል እና ከተማ አስተዳደር ደረጃ ለሚገኙ የትምህርት እና ስልጠና ባለሙያዎች በስልጠና አሰጣጥ
ክህሎት ላይ ስልጠና መስጠት፣
በድረ-ገፅ እና ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ ለክልልና ከተማ አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች
ስልጠና መስጠት ፣
በየደረጃዉ የተሰጡ ስልጠናዎችን አፈፃፀም ደረጃ ከክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ጋር በመገምገም
የቀጣይ አቅጣጫ ላይ መግባባት መፍጠር ½
ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ጽንሰ ሃሳብ እና አተገባበር ዙሪያ ስልጠና እንዲሰጡ ማድረግ፣
በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ደረጃ በሚሰጡ ስልጠናዎች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር፣
ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በወሳኝ ኩነት ምዝገባ አፈጻጸም መመሪያ እና በሌሎች መሰረታዊ ርእሰ ጉዳዮች
ዙሪያ በየደረጃዉ ለሚገኙ አመራርና ፈጻሚ አካላት ስልጠና እንዲሰጡ ማድረግ፣
በየደረጃው ለሚገኙ የዘርፉ አመራርና ፈፃሚ የልምድ ልውውጥ መድረክ ማዘጋጀት
በክልል እና ከተማ አስተዳደር ደረጃ ተግባራዊ የሚደረገዉን የልምድ ልውውጥ ማስፈጸሚያ እቅድ ማዘጋጀት፣
በፌዴራል አስተባባሪነት በክልሎች መካከል የልምድ ልዉዉጥ መድረክ በማዘጋጀት ተግባራዊ ማድረግ ፣
የክልል እና ከተማ አስተዳደር አመራሮች እና የስራ ሂደት መሪዎች የዉጭ አገር ልምድ እንዲያገኙ ማድረግ፣
የልምድ ልዉዉጥ መድረኩን ፋይዳ መገምገም ፣
የግቡ ውጤት፡- የማስፈፀምና የመፈፀም አቅማቸው ያደገ አመራርና ፈፃሚ
37
በኤጀንሲ ደረጃ የተዘጋጀዉን ድረ-ገጽ በየጊዜዉ እየተከታተሉ የተሟላ ይዘት እንዲኖረዉ ማድረግ ፣
በፌዴራል እና በክልል ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ደረጃ ኔትዎርክ መዘርጋት፣
የኤጀንሲዉን ሰርቨር ለስራ ዝግጁ ማድረግ ፣
የኢ-ለርኒንግ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የዌብሳይት ፔጅ ማዘጋጀት ፣
በኤጀንሲ ደረጃ የዳታ ሪከቨሪ ክፍል ማዘጋጀት ፣
ከሃይማኖት ተቋማት፣ ከጠቅላይ ፍ/ቤት ፣ ከትም/ት ሚ/ር ፣ ከሴቶችና ህ/ጉ/ ሚ/ር ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል
መግባቢያ ሰነድ ማዘጋጀት፣
የተባባሪ አካላትን የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርአቱን በመደገፍ ረገድ የነበራቸዉን ሚና መገምገም ፣
ኤጀንሲዉን በቴክኒካል ጉዳዮች ዙሪያ የሚያማክር ከባለድርሻና ተባባሪ አካላት የተዉጣጣ የቴክኒክ ቡድን ማቋቋም፣
የቴክኒክ ቡድኑ በጋራ ያከናወናቸዉን ጉዳዮች ለኤጀንሲዉ በየጊዜዉ በሪፖርት እንዲያቀርብ ማድረግ፣
38
በሥራ ላይ ያሉ ቅንጅታዊ አሠራሮችን አፈጻጸም መገምገም፣
39
በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ጽንሰ ሃሳብ እና አስፈላጊነት ዙሪያ ለክልል እና ከተማ አስተዳደር ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ምክር
ቤት/ ቦርድ አባላት ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ማዘጋጀት፣
በወረዳ ደረጃ ለሚገኙ አስተዳዳሪዎች ፣ አደረጃጀት ፣ የፍትህ ጽ /ቤት እና የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ጽ /ቤት ሃላፊዎች
በወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና አተገባበር ዙሪያ ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ማዘጋጀት፣
በክልል እና በከተማ አስተዳደር ደረጃ ለሚገኙ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ዙሪያ ግንዛቤ
መፍጠሪያ መድረክ ማዘጋጀት፣
በተዘጋጁ አገራዊ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ የጥራትና ሽፋን አመልካቾች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር
የጋራ ስምምነት መፍጠር፣
በተዘጋጁ ስታንዳርዶችና አመልካቾች መሠረት የወሳኝ ኩነት መረጃ ምዝገባ ጥራትና ሽፋንን መለካት፣
የወሳኝ ኩነት መረጃ ምዝገባ ጥራትና ሽፋን የደረሰበትን ደረጃ አስመልክቶ ለመዝጋቢ አካላት ዉጤቱን
መግለጽ ፣
በወሳኝ ኩነት ምዝገባ አተገባበር ዙሪያ ጥናት ማካሄድ፣
በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ትግበራ ዙሪያ የዳሰሳ ጥናት ማካሄድ ፣
በአገር አቀፍ ደረጃ የወሳኝ ኩነት የመከሰት መጠን በተመለከተ ጥናት ማድረግ ፣
40
በአፋር ፣ ትግራይና አማራ ክልሎች በቤት ዉስጥ የሚከሰት ልደትና ሞት ምዝገባን በተመለከተ ጥናት
ማድረግ፣
በቤት ዉስጥ የሚከሰት ልደትና ሞት ጥናት መሰረት በማድረግ የአሰራር ማኑዋል ማዘጋጀት፣
ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የወሳኝ ኩነት እንዲመዘግቡ ማድረግ፣
ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የልደት ኩነት እንዲመዘግቡ ማድረግ፣
ከክልል እና ከተማ አስተዳደር ጋር በመረጃ አላላክ አመታዊ መርሃ ግብር ዙሪያ የጋራ መግባባት ላይ መድረስ ፣
በኤጀንሲ ደረጃ ያለዉን የበጀት ክፍተት ለመሙላት እንዲቻል ከተባባሪ አካላት ጋር ቀጣይነት ያለዉ ግንኙነት
መፍጠር፣
41
በተባባሪ አካላት ተቀባይነት ያገኙ የበጀት ድጋፎችና ለማስፈጸም የሚያስችል ጋር የጋራ ስምምነት ሰነድ
ማዘጋጀት ½
በኤጀንሲ ደረጃ ከተባባሪ አካላት የተገኙ የበጀት ድጋፎች ወደ ትግበራ እንዲገቡ ቀጣይነት ያለዉ ክትትል
ማድረግ ፣
የወጭ አጠቃቀም ሪፖርት በየወሩ ለስራ ሂደቶች እና ለሚመለታቸዉ አካላት በየበጀት ኮዱ እና የወጭ ርእስ ማሳወቅ፣
በዋና ኦዲተር እና በዉስጥ ኦዲት ለሚሰጡ የኦዲት ግኝቶች ላይ ወቅታዊ ምላሽ መስጠት፣
በተቋም ደረጃ የተከናወኑ ግዥዎችን አፈጻጸም በተመለከተ የተደራጀ ሪፖርት ለማኔጅመንት ማቅረብ ፣
የኤጀንሲዉን የፋይናንስ፣ የንብረት፣ የበጀትና የሰዉ ሃይል ስምሪት አጠቃቀም ኦዲት ማድረግ፣
የተቋሙን የሰዉ ሃይል ስምሪት ኦዲት ማድረግ ፣
የተቋሙን የመደበኛና የፕሮጀክት ሂሳቦችን አጠቃቀም ኦዲት ማድረግ ፣
የተቋሙን የንብረት አጠቃቀም ኦዲት ማድረግ ፣
የተቋሙን የግዥ አፈፃፀም ኦዲት ማድረግ ፣
ለኤጀንሲዉ አመራር እና የማኔጅመንት አባላት የምክር አገልግሎት መስጠት፣
በተገኙ የኦዲት ግኝቶች ላይ ማስተካከያ መደረጉን ክትትል በማድረግ ለማኔጅመንት ሪፖርት
ማቅረብ ፣
የግቡ ውጤት፡- ውጤታማ የፋይናንስ አጠቃቀም ½
42
5.4 የተገልጋይ እይታ
ግብ 15፡- የአገልግሎት ተደራሽነትና ተጠቃሚነት ማሳደግ ½
የአገልግሎት ተደራሽነትና ተጠቃሚነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን፣
ተገልጋዩ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ሰርትፍኬት እንዲወስድ ማድረግ፣
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አገልግሎት መስጠት ያልጀመሩ የምዝገባ ጽ/ቤቶችን ምዝገባ እንዲጀምሩ ማድረግ፣
በየደረጃዉ የሚሰጡ የአቅም ግንባታ ተግባራት የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ ሁኔታ
እንዲፈጸም ማድረግ፣
ተገልጋዮች ማወቅ የሚገባቸዉን መረጃዎች ማህበራዊ ድረ-ገጽ በመጠቀም ተደራሽ እንዲሆን ማድረግ ፣
የኤጀንሲዉን ተገልጋይና ባለድርሻ አካላት በኤጀንሲዉ እቅድ ዝግጅትና አፈጻጸም ሂደት ላይ ማሳተፍ ፣
ተገልጋይና ባለድርሻ አካላት የኤጀንሲዉን እቅድ አፈጻጸም የሚገመግሙበትን መድረክ ማዘጋጀት፣
በመድረኩ የተሰጡ ግብአቶችን ተግባራዊ በማድረግ አፈጻጸሙን ለተገልጋይና ባለድርሻ አካላት በሪፖርት
ማሳወቅ፣
43
የተዘጋጁ የአስተያየት መስጫ መሳሪያዎችን በመጠቀም ተገልጋዩ አስተያየት እንዲሰጥ
ማድረግ፣
የኤጀንሲዉን ተገልጋይና ባለድርሻ አካላት የእርካታ ደረጃ መለካት፣
የግቡ ዉጤት ፡- ያደገ የተገልጋይና ባለድርሻ አካላት ዕርካታና አመኔታ፣
ለመፈጸም እንዲቻል በየደረጃዉ የሚገኘዉ አመራርና ፈጻሚ አካል የመፈጸም አቅሙ በቀጣይነት
ለመገንባት የሚያስችል በእቅድ አፈጻጸም ላይ መሰረት ያደረገ ችግር ፈች የድጋፍና ክትትል ስርአት
በመሆኑም ኤጀንሲዉ የ 2010 በጀት አመት እቅዱን በስኬት ለማጠናቀቅ በዝግጅት ምእራፍ ፣ በተግባር
በስራ ሂደትና በቡድን ደረጃ ሊከናወኑ የሚገባቸዉ ተግባራት ከዚህ በታች ቀርበዋል፡፡
የማድረግ ስራ ይሰራል፡፡
44
5.1.2 በማኔጅመንት ደረጃ ፡-
ወሳኝ ድርሻ ላላቸዉ የኤጀንሲዉ ባለድርሻ አካላት ዝርዝር ኦረንቴሽን በመስጠት በእቅዱ ላይ
ይሰራል፡፡
ሌላዉ በዝግጅት ምእራፍ ወቅት ትኩረት የሚሰጠዉ ጉዳይ በእቅድ የተያዙ ተግባራት
የኤጀንሲዉ ዳይሬክቶሬቶች በተቋም ደረጃ በበጀት አመቱ በእቅድ የተያዙ ተግባራትን ዉጤታማ
በማድረግ እና በተዘጋጀዉ እቅድ ዙሪያ በየደረጃዉ የሚገኙ የዳይሬክቶሬቱ ፈጻሚ አካላት ዝርዝር
45
ኦረንቴሽን በመስጠት በእቅዱ ላይ የጋራ መግባባት እንዲፈጥሩ የማድረግ ስራ ትኩረት በመስጠት
የሚሰሩ ሲሆን በእቅድ ኦረንቴሽን መድረኩ ላይ የተገኙ ግብአቶችን በተደራጀ አግባብ በእቅዱ
በእቅድ አፈጻጸም ወቅት የነበሩ ጠንካራ አፈጻጸሞችን ፣ ደካማ አፈጻጸሞችን እና በአፈጻጸም ወቅት
ያደርጋል፡፡
ዳይሬክቶሬቶች በእቅድ የተያዙ ተግባራት አፈጻጸም የሚያሳይ ወቅታዊ ሪፖርት ከለዉጥ ቡድኖች
የሚሰራ ይሆናል፡፡
በዳይሬክቶሬት ደረጃ የሚገኙ ቡድኖች በስራ ሂደቱ በእቅድ የተያዙ ተግባራትን ለማሳካት
እንዲቻል በዝግጅት ምእራፍ ወቅት የቡድኑን እቅድ እንዲዘጋጅ በማድረግ እና በተዘጋጀዉ እቅድ
ይኖርባቸዋል፡፡
ቡድኑ በእቅድ አፈጻጸም ወቅት የነበሩ ጠንካራ አፈጻጸሞችን ፣ ደካማ አፈጻጸሞችን እና በአፈጻጸም
46
ቡድኖች በእቅድ የተያዙ ተግባራት አፈጻጸም የሚያሳይ ወቅታዊ ሪፖርት ከ 1 ለ 5 አደረጃጀቶች
የሚሰራ ይሆናል፡፡
በክልል፣ በማኔጅመንት ፣ በስራ ሂደት እና በቡድን ደረጃ የሚከናወኑ ተግባራት ከዚህ በታች ቀርበዋል፡፡
የኤጀንሲዉ ማኔጅመንት አካል በተግባር ምእራፍ ወቅት በእቅድ የተያዙ ተግባራት ወሳኝ
47
በእቅድ አፈጻጸም ወቅት የነበሩ ጠንካራ አፈጻጸሞችን ፣ ደካማ አፈጻጸሞችን እና በአፈጻጸም
አቅጣጫ ያስቀምጣሉ፡፡
ያደርጋል፡፡
48
ቡድኖች በእቅድ የተያዙ ተግባራት አፈጻጸም የሚያሳይ ወቅታዊ ሪፖርት ከ 1 ለ 5 አደረጃጀቶች
ስራ የሚሰራ ይሆናል፡፡
በክልል፣ በማኔጅመንት ፣ በስራ ሂደት እና በቡድን ሊከናወኑ የሚገባቸዉ ተግባራት ከዚህ በታች
ቀርበዋል፡፡
ያስቀምጣል፡፡
ዝርዝር ግብረ መልስ የግምገማ መድረኮቹ በተጠናቀቁ በሶስት ቀናት ዉስጥ በማዘጋጀት
ያስቀምጣል፡፡
ዝርዝር ግብረ መልስ የግምገማ መድረኮቹ በተጠናቀቁ በሁለት ቀናት ዉስጥ በማዘጋጀት ለለዉጥ
50
ቡድኖች የእቅድ አፈጻጸማቸዉን የ 1 ለ 5 አደረጃጀቶች በሚያቀርቡት ሪፖርት ላይ በመመስረት
ያስቀምጣሉ፡፡
ስራ የሚሰራ ይሆናል፡፡
ከተቋሙ ተልእኮ ጋር ተያያ™ነት ያለዉ ባለሙያ በገበያ ላይ አለመኖር እና የተሻለ ልምድ ያላቸው
ኤጀንሲዉ ተልእኮዉን በብቃት እንዲወጣ ከማድረግ አንጻር የግብዓት አቅርቦት ማነቆ በተሟላ
ሁኔታ አለመፈታት፣
6.2 መፍትሄዎች
የለዉጥ ስራዎችን ተግባራዊ ለማድረግ በአመለካከት ለውጥ ለማምጣት በዕቅድና ግምገማ ሪፖርት
51
በእቅድ የተያዙ ተግባራትን እና በተለያየ ጊዜ ከእቅድ ዉጭ የሚመጡ ተግባራትን ከዋናዉ እቅድ ጋር
በተቋሙ ያሉ ክፍት የስራ መደቦችን በሰዉ ሃይል እንዲሟሉ ለማድረግ የሚታዩ ክፍተቶችን
በተቋም ደረጃ ያለዉ የሰዉ ሃይል ለረ™ም ጊዜ እንዲያገለግል የስራ አካባቢዉ ምቹ እና ሳቢ እንዲሆን
በቀጣይ ዓመት የግብዓት ችግር ለመፍታት በዋና ዋና የግብዓት ችግሮች መነሻ ጥናት በማድረግ
በኤጀንሲ ደረጃ የታቀደው የዉጤት ተኮር እቅድ በሚፈለገው መልኩ ተፈፃሚ እንዲሆን ለማስቻል በየደረጃዉ
የሚገኘዉ አመራር እና ፈጻሚ አካል ግልጽ የአፈፃፀም አቅጣጫ በማስቀመጥ በተቀመጠለት አቅጣጫ መሰረት
እንዲመራ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በዚህ መሰረት የ 2010 በጀት አመት የኤጀንሲው የውጤት ተኮር እቅድ
ኤጀንሲው በ 2010 በጀት አመት በእቅድ የተያዙ ግቦችን እና ተግባራትን ዉጤታማ በሆነ ሁኔታ ለመፈጸም
እንዲቻል እቅዱን በየደረጃዉ ለሚገኙ ፈጸሚ አካላት በማዉረድ ተግባራዊ እንዲያደርጓቸዉ የጋራ መግባባት
መፍጠር፣
በኤጀንሲ ደረጃ በእቅድ የተያዙ ተግባራትን ዉጤታማ ለማድረግ በእቅድ የታዘዉ የውጤት ተኮር እቅድ
በተቀመጠው የአፈፃፀም ደረጃ ተግባራዊ እንዲደረግ በየደረጃዉ የሚገኘዉ አመራር ስራዎችን በየወቅቱ
እየገመገመ እና የአፈፃፀም አቅጣጫ እያስቀመጠ የውጤት ተኮር እቅዱ ተግባራዊ እንዲሆን ማድረግ ½
በተቋም ደረጃ በእቅድ የተያዙ ግቦችን እና ተግባራትን ዉጤታማነት ለማረጋገጥ ተቋሙ ለእያንዳንዱ የስራ
ሂደት ፣ የስራ ሂደቶች ለቡድኖች ፣ ቡድኖች ለፈፃሚዎች ተከታታይነት ያለው እና በእቅድ አፈጻጸም ላይ
ተቋማዊ የውጤት ተኮር እቅዱ ተግባራዊ ሲደረግ ከእቅድ ጀምሮ እስከ ምዝና ባለዉ ሂደት አጠቃላይ
ክፍተትን የለየ ½ ቀጣይነት ያለዉና ችግር ፈቺ የሆነ የድጋፍ አግባብን ተከትሎ ተግባራዊ እንዲሆን
ማድረግ ½
52
በተቋም በስራ ሂደት እና በቡድን ደረጃ የተቀረጸዉ የውጤት ተኮር እቅድ በየደረጃዉ የሚገኘዉን ፈጻሚ
ተቋማዊ እቅዱን በመፈጸም ረገድ በተቋም ½ በሂደትና በፈጻሚ ደረጃ የሚታዩ የአፈጻጸም ጉድለቶችንና
በአፈጻጸም ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል የተቀናጀ እና የተናበበ የአሰራር መርህን
ተግባራዊ ማድረግ፣
በተቋም ½ በስራ ሂደት ½ በቡድን እና በፈጻሚ ደረጃ በእቅድ የተያዙ ተግባራትን ዉጤታማነት ለማረጋገጥ
በውጤት ተኮር እቅድ መሰረት የእርስ በእርስ አቅም መገንቢያ ስልቶችን በላቀ የቡድንና የባለቤትነት መንፈስ
ተቋማዊ የዉጤት ተኮር እቅዱን ስኬታማ ለማድረግ ከሁሉም ባለድርሻ እና አጋር አካላት ጠንካራ ትስስር
በመፍጠር ለውጤት ተኮር እቅዱ አስተዋጽኦ ስኬት የበኩላቸዉን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ማስቻል ½
53