Professional Documents
Culture Documents
የመንገድ ፈንድ ጽ/ቤት በአዋጅ ቁጥር 66/1989 የተቋቋመ' ከመንግስት' ከክልሎችና ከመንገድ ተጠቃሚዎች የሚወከሉ
አባላት ባሉት ቦርድ የበላይነት የሚተዳደር እና ተጠሪነቱ ለትራንስፖርት ሚኒስቴር የሆነ ተቋም ነው፡፡ ጽ/ቤቱ በአዋጁ
የተሰጡት ሥልጣንና ኃላፊነቶች በዚህ ሠነድ (ቻርተር) የወደፊት ገጾች በዝርዝር የሚመላከት ሲሆን በጥቅሉ ሲታይ ግን
ጽ/ቤቱ በአዋጅ በተደነገጉት እና በመንግስት ውሳኔ የፈንዱ የገቢ ምንጮች እንዲሆኑ ከተወሰኑት የገቢ ዓይነቶች (በፈንዱ
ማቋቋሚያ አዋጅ ከተዘረዘሩት ማለትም በመንግስት ከሚመደብ በጀት' ለመንገድ ጥገና ከተጣለ የነዳጅ ታሪፍ' በክብደት
ላይ ከተመሰረተ ዓመታዊ የተሸከርካሪ ፈቃድ ማደሻ ክፍያ' ከተፈቀደው ክብደት በላይ በመጫን ከሚጣል ቅጣት'
እንደአስፈላጊነቱ ከሚጣል ከማናቸውም ሌላ የመንገድ ታሪፍ) ገቢ መሰብሰብ' በየበጀት ዓመቱ ለፈንዱ ተጠቃሚዎች
በጀት መደልደልና በተደለደለ በጀት መሰረትም ገንዘብ በማስተላለፍ የተላለፈው ገንዘብ ለታለመለት ዓላማ በአግባቡ
ሥራ ላይ መዋሉን የማረጋገጥ ኃላፊነት የተጣለበት ተቋም ነው፡፡
የፈንዱ ተጠቃሚዎች የፌዴራል መንገዶችን የሚያስተዳድረው የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን' 9 የክልል መንገድ
ባለሥልጣኖች' ይህ የዜጎች ቻርተር በተዘጋጀበት ወቅት የፈንዱ ተጠቃሚ የሆኑ 60 የከተማ አስተዳደሮች እና የብሄራዊ
የመንገድ ደህንነት ካውንስል ጽ/ቤት ሲሆኑ በድምሩ 71 ተቋማት ናቸው፡፡ ጽ/ቤቱ ለእነዚህ ተቋማት የሚመድበው በጀት
የሚውለው ግንባታቸው ተጠናቆ አገልግሎት ለሚሰጡ የመንገድ መስመሮች እና ድልድዮች ጥገና እና ለመንገድ ደህንነት
ሥራዎች ነው፡፡
የፈንድ ጽ/ቤቱ የተቋቋመበትን ዓላማ ለማስፈፀም የሚያስችለው አደረጃጀት ያለው ሲሆን በዚህም መሰረት በሶስት
ዓላማ አስፈፃሚ ቡድኖች ማለትም ፕላን ዝግጅት' ክትትልና ግምገማ& ፋይናንስ እና ኦዲት ቡድኖች እንዲሁም በድጋፍ
ሠጪ እና በህዝብ ግንኙነት የሥራ ዘርፎች ተደራጅቷል፡፡ ጽ/ቤቱ ለደንበኞቹ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እና
ውጤታማ ሥራዎችን ለማከናወን ይቻለው ዘንድ የመሰረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ጥናት (BPR) በማድረግ እና
የውጤት ተኮር ሥርዓትን (BSC) በመዘርጋት በተግባር ላይ ያዋለ ሲሆን የሚሰጣቸው አገልግሎቶች ጥራት ያላቸው'
የደንበኞችን እርካታ የሚያስገኙ' ግልፅነትንና ተጠያቂነትን የተላበሱ እንዲሆኑ ለማስቻል ዜጎች ከጽ/ቤቱ ማግኘት
የሚፈልጓቸውን አገልግሎቶች ለማግኘት ማሟላት የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች' የአገልግሎት አሠጣጥ
ስታንዳርዶች እና መብቶቻቸውን እንዲሁም በአገልግሎት አሠጣጡ ቅሬታ ያላቸው የሚስተናገዱበትን ሥርዓት በዚህ
ቻርተር ውስጥ በማካተት ለአገልግሎቱ መሻሻል የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ለማስቻል ይህ የዜጎች ቻርተር
የተዘጋጀ ሲሆን በሠነዱም የተቋሙ ራዕይ' ተልዕኮ' ዕሴቶች እና በአዋጅ የተሰጡት ሥልጣንና ኃላፊነቶች እንዲካተቱ
ተደርጓል፡፡
2. የቻርተሩ ዓላማ፡-
በጽ/ቤቱ እና በዜጎች (ደንበኞች' ባለድርሻ አካላት' ተባባሪ አካላት' ወዘተ…) መካከል የተጠናከረ
ግንኙነት እንዲኖር ማስቻል'
3. የተቋሙ ራዕይ
4. የተቋሙ ተልዕኮ
“የመንገድ ፈንድ አስተዳደር ሥርዓትን በማሟላት የታቀዱ የመንገድ ጥገናና የመንገድ ደህንነት ሥራዎችን ለማከናወን
የሚያስችል ፈንድ በማፈላለግ' በመሰብሰብና ለመንገድ ኤጀንሲዎች በማከፋፈል ከመንገድ ተጠቃሚው የመክፈል
አቅምና ፍላጎት ጋር የተመጣጠነ የመንገድ ጥገና ሥራ ጥራቱን ጠብቆ እንዲከናወን በማድረግ አፈፃፀሙን በመከታተልና
በመገምገም መንገድ ተጠቃሚው ህብረተሰብ ምቹና ደህንነቱ የተጠበቀ መንገድ ማግኘቱን ማረጋገጥ”
5. ዕሴቶች
የላቀ የመንገድ ፈንድ ማመንጨትና ማስተዳደር (በፈንድ ጽ/ቤቱ ማቋቋሚያ አዋጅ የገቢ ምንጮች
እንዲሆኑ ከተወሰኑት የገቢ ዓይነቶች ገቢ ለማሰባሰብ እና ተጨማሪ ፈንድ ሊገኝ የሚችልበትን ሁኔታ
ለማመቻቸት የሚያስችሉ ደንቦችን እና መመሪያዎችን በማዘጋጀት ለመንግስት የውሳኔ ሀሳብ
ማቅረብን ያካተተ ነው)፡፡
8.1. ደንበኞች
ለዜጎች (ደንበኞች' ባለድርሻ አካላት' ተባባሪ አካላት' ወዘተ…) ጥያቄዎችና አስተያየቶች ፈጣን
ምላሽ መስጠት&
የፈንድ ጽ/ቤቱ የሚሠጣቸውን አገልግሎቶች በተመለከተ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱት ጉዳዮች ታሳቢ ያደረጉት
የጽ/ቤቱን ደንበኞች' ባለድርሻ አካላት እና ተባባሪዎችን ሲሆን ዋና ዋና የትኩረት ነጥቦችን የዳሰሱ እንዲሆኑ
ተደርጓል፡፡
ከአማካሪ ድርጅቶች የሚቀርቡ የመንገድ ጥገና ሪፖርቶችን በመገምገም ግብረ መልስ መስጠት&
የፈንዱን ማዕከላዊና የመንገድ ኤጀንሲዎችን ሂሣብ በየበጀት ዓመቱ በውጭ ኦዲት ማስመርመር'
በጽ/ቤቱ በተለዩት የትኩረት መስኮች የስራ ክንውን ዙሪያ ዶክመንተሪ ፊልም እንዲዘጋጅ
ማድረግ'
1.2.5. የድጋፍ ሠጪ
1 ለፈንዱ ተጠቃሚዎች የበጀት ድልድል በማድረግ ማሳወቅ ከግንቦት 1 - ሰኔ 30 ዓመታዊ የፊዚካልና ፋይናንሻል ዕቅድ
3 ከፈንዱ ተጠቃሚ የሚቀርብ የፊዚካልና ፋይናንሻል ዕቅድ ገምግሞ ግብረ መልስ መስጠት ከ 1 እስከ 3 ቀን ዓመታዊ የፊዚካልና ፋይናንሻል ዕቅድ
ከፈንዱ ተጠቃሚ የሚቀርብ የፊዚካልና ፋይናንሻ ዕቅድ ክንውን ሪፖርት ገምግሞ ግብረ
4 3 ቀን ዓመታዊ የፊዚካልና ፋይናንሻ ዕቅድ ክንውን ሪፖርት
መልስ መስጠት
7 ለሚቀርቡ የበጀት ዝውውር ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት እስከ 1 ሳምንት የበጀት ዝውውር ጥያቄ
9 ለደንበኞችና ባለድርሻ አካላት መረጃዎችን መስጠት እስከ 1 ሳምንት አግባብነት ያለው የመረጃ ጥያቄ
ዜጎች ያላቸውን አስተያየት' ቅሬታ' ጥቆማ እንዲሁም ጥያቄዎችን በጽ/ቤቱ ዌብሳይት' በሀሳብ መስጫ ሳጥን'
በሀሳብ መስጫ መዝገብ' በስልክ' በፋክስ' በኢ-ሜይል ወይም በጽ/ቤቱ በአካል በመገኘት በቃል' በፅሁፍ ወይም
በሁለቱም ማቅረብ ይችላሉ፡፡
በቻርተሩ በተቀመጠው መሰረት አገልግሎት ያላገኘ ዜጋ ቅሬታ የማቅረብ መብት አለው፡፡ በዚህም መሰረት
ከላይ በተራ ቁጥር 15 ላይ በተገለፁት ዘዴዎች፡-
በፈፃሚዎች ምላሽ ያልረካ ቅሬታ አቅራቢ ቅሬታውን ለሥራ ክፍሉ ያቀርባል የሥራ ክፍሉም
ተገቢውን ምላሽ የመስጠት ኃላፊነት ያለበት ሲሆን ቅሬታ በቀረበለት በ 1 (አንድ) ቀን ውስጥ ለቅሬታ
አቅራቢው ምላሽ መስጠት ይኖርበታል'
በሥራ ክፍሉ ምላሽ ያልረካ ከሆነ መስሪያ ቤቱ ለሰየመው ቅሬታ አጣሪ አካል ቅሬታውን ያቀርባል&
ቅሬታ አጣሪው አካል ቅሬታ በቀረበለት በ 2 (ሁለት) ቀን ውስጥ ለቅሬታ አቅራቢው ምላሽ መስጠት
ይኖርበታል'
ቅሬታ ያቀረበ ዜጋ በቅሬታ አጣሪው አካል ምላሽ ያልረካ ከሆነ ለመስሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ያቀርባል፤
የመስሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊም በዜጋው የቀረበውን ጥያቄ እንዲጣራ በማድረግ ከሶስት ቀን ባልበለጠ
ጊዜ ውስጥ ለቅሬታ አቅራቢው የመጨረሻ መልስ ይሰጣል፡፡
ጽ/ቤቱ በቻርተሩ መሰረት ዜጎች አገልግሎት እያገኙ መሆኑን የሚያረጋግጥበት የክትትልና ድጋፍ
ሥርዓት ይኖረዋል፡፡
011-470-2932
1 ጽ/ቤት አቶ ራሺድ መሐመድ ዋና ዳይሬክተር 0911-20-08-24 011-553-44-07
011-470-2662
7 የሥነ ምግባር ክትትል ክፍል አቶ ደረጀ ኪሮስ የስነ ምግባር መኮንን 0912115817