Professional Documents
Culture Documents
“ስለ ጽድቅኽም ፍርድ ሰባት ጊዜ በቀን አመሰግንኻው።” መዝ. ፻፲፰÷፻፷፬ በማለት በቀን ሰባት ጊዜ
ይጸልይ እንደነበር ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ተናግሯል። በኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ቤተክርስትያን ስርዓት መሰረት በአንድ ቀን ውስጥ የተመደቡ የጸሎት ጊዜያት ሲኖሩ እነርሱም ሰባት
(፯) ናቸው። አንድ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታይ የሆነ ሰው ቢችል በአንድ ቀን ዉስጥ
ሰባቱንም ጸሎታት ማድረስ ይኖርበታል፣ በስራ ወይም በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ሳይመቸው ቢቀር
ቢያንስ በጸሎቱ ሠዓታት ሚታሰቡትን ነገሮች አስቦ ማሳለፍ ይኖርበታል። ነገር ግን እናመሰግነው
ዘንድ ለፈጠረን አምላክ በስራስ ቦታ ቢሆን የሁለት እና የሦስት ደቂቃ ጊዜ እነዴት እናጣለታለን? እና
ከቻልን አቡነ ዘበሰማያት (አባታችን ሆይ) የምትለዋን አጭር ጸሎት ብናደርስ ይመረጣል። ያንንም
እናደርግ ዘንድ እግዚአብሄር ይርዳን!
ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ስለ ጽድቅኽ ፍርድ በቀን ሰባት (፯) ጊዜ አመሰግንኻለኑ ብሎ
አምላኩን በቀን ሰባት(፯) ጊዜ እንዳመሰገነ እና እንደጸለየ ሁሉ እኛም አባቶች በጉባኤ በደነገጉት እና
ባፀኑት ሕግ መሠረት የአባቶቻችንን መንገድ ተከትለን በቀን ውስጥ ሰባት (፯) ጊዜ እራሳችንን
ለእግዚአብሔር በማስገዛት ለጸሎት እንተጋለን። ሰባቱ የጸሎት ጊዜያት ከዚህ በታች በዝርዝር
ተቀምጠው እናገኛለን። እነሱም ነግኅ፣ ሠለስት፣ ቀትር፣ ተሰዓት፣ ሠርክ፣ ንዋም እና መንፈቀ-ሌሊት
ናቸው።
፯. መንፈቀ ሌሊት
ይህ ሰዓት ታላቅ ሰዓት ነው። አምላካችን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደበት፣
ሙታን መካከል ተለይቶ የተነሣበት፣ ዳግመኛም በህያዋን እና በሙታን ለመፍረድ የሚመጣባት ሠዓት
ስለሆነች ይህን ሁሉ በማሰብ እና እግዚአብሔር ለእኛ ሲል ያደረገዉን ነገር ሁሉ በማሰብ
የሚጸለይበት ሠዓት ነው። (ሉቃ. ፪÷፯-፰፣ ዮሐ. ፳÷፩፣ ማቴ. ፳፭÷፮፣ ማር. ፲፫÷፴፭) በዚህም
ምክንያት አምላካችን ለእኛ የሆነውን እና ያደረገውን ሁሉ በማስተዋል እንጸልያለን። አንድም፤
ቅዱስ ጳውሎስ እና ደቀመዝሙሩ ሲላሰ በእሥር ቤት ውስጥ እያሉ በዜማ አሸናፊ ልዑል
እግዚአብሔር ያመሰገኑበት ሰዓት ነው። (የሐዋ. ፲፮÷ ፳፭)
በነዚህ የጸሎት ሰዓቶች ውስጥ እግዚአብሔር በረዳን መጠን በጸሎት ልንተጋ ይገባል። እነዚህን
የጸሎት ሰዓቶች በተለያየ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነን መተግበር ቢያቅተን እንኳን ጠዋት
ከመኝታችን ስንነሳና ማታ ወደ መኝታችን ስናመራ መጸለይ ይገባናል ከዚህ ውጭ በገዳም ተወስነው
ዳዋ ጥሰው ጤዛ ልሰው ቁርበት ለብሰው ድንጋይ ተንተርሰው ድምፀ-አራዊቱን ግርማ ሌሊቱን ፀብና
አጋንንቱን ታግሰው የሚኖሩ ገዳማውያን መነኮሳት አባቶቻችን እና እናቶቻችን እነዚህ ከላይ
በዝርዝር ያየናቸውን ሰባቱን የጸሎት ሰዓታት ለአይን ጥቅሻ እንኳ ለምታክል ጊዜ እንኳ ሳያስታጉሉ
እስካሁን ፀንተው ኖረዋል፤ ወደፊትም ይኖራሉ።
አማርኛ ግዕዝ
፫. አባታችን ሆይ በሰማያት የምትኖር ስምህ ይቀደስ አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ፤ ትምጻእ
መንግሥትህ ትምጣ ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች መንግሥትከ ወይኩን ፈቃድከ፤ በከመ በሰማይ
እንዲሁም በምድር ትሁን፤ የዕለት እንጀራችንን ከማሁ በምድር ሲሳየነ፤ ዘለለ ዕለትነ ሀበነ ዮም፤
ስጠን ዛሬ በደላችንንም ይቅር በለን እኛ ኅድግ ለነ አበሳነ ወጌጋየነ ከመ ንሕነኒ ንኅድግ
የበደሉንን ይቅር እንደምንል፤ አቤቱ ወደ ለዘአበሰ ለነ፤ ኢትኣብአነ እግዚኦ ውስተ መንሱት
ፈተናምም አታግባን ከክፉ ሁሉ አድነን እንጂ፤ ኣላ አድኅነነ፤ ወባልሐነ እምኵሉ እኩይ፤ እስመ
መንግሥት ያንተ ናትና ኃይል እና ስብሃሃት ዚአከ ይእቲ መንግሥት ኃይል ወስብሐት ለዓለመ
ለዘለዓለሙ፤ አሜን። ዓለም፤ አሜን።
፬. እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ በመልአኩ በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል መልአክ ኦ እግዝእትየ
በቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ ሰላም እልሻለሁ ማርያም ሰላም ለኪ፤ ድንግል በኅሊናኪ
በሃሳብሽ ድንግል ነሽ በሥጋሽም ድንግል ነሽ። ወድንግል በሥጋኪ፤ እመ እግዚአብሔር ጸባዖት
የአሸናፈ የእግዚአብሔር እናት ሆይ ሰላምታ ሰላም ለኪ፤ ቡርክት አንቲ እምአንስት ወቡሩክ
ላንቺ ይገባል። ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ አንቺ ፍሬ ከርሥኪ፤ ተፈሥሒ ፍሥሕት ኦ ምልእተ
የተባረክሽ ነሽ የማኀፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው። ጸጋ እግዚአብሔር ምስሌኪ፤ ሰአሊ ወጸልዪ ኀበ
ጸጋን የተሞላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ እግዚአብሔር ፍቁር ወልድኪ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ይሥረይ
ከአንቺ ጋር ነውና ከተወደደው ልጅሽ ከጌታችን ለነ ኃጣዊኢነ።
ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርከቶስ ዘንድ
ይቅርታን ለምኝልን ኃጥያታችንን ያስተሠርይልን
ዘንድ ለዘለዓለሙ፤ አሜን።
፮. አሸናፊ እግዚአብሔር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚብሔር ጸባዖት ፍጹም
ተብለህ ትመሰገናለህ። ምስጋናህም በሰማይና ምሉዕ ሰማያት ወምድረ ቅድሳተ ስብሐቲከ።
በምድር የሞላሞላ ነው። ክርስቶስ ላንተ ንስግድ ለከ ክርስቶስ ምስለ አቡከ ኄር ሰማያዊ
እንሰግድልሃለን፤ ከሰማያዊው ከቸር አባትህ ጋር፤ ወመንፈስከ ቅዱስ ማኅየዊ እስመ መጻእከ
አዳኝ ከሆነው ከመንፈስ ቅዱስም ጋር ወአድኃንከነ።
እንሰግድልሃለን፤ ወደዚህ ዓለም መጥተህ
አድነኸናልና።
፯. ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት
ለመንፈስ ቅዱስ (፫ ጊዜ በል)። አምላክን ለመንፈስ ቅዱስ (፫ ጊዜያተ በል)። ስብሐት
ለወለደች ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
ምስጋና ይገባል። ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስብሐት ለመስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ
መስቀልም ምስጋና ይገባል። ክርስቶስ በምህረቱ በምሕረቱ ይዘከረነ። አመ ዳግም ምጽአቱ
ያስበን፤ ዳግመኛም በመጣምም ጊዜ አያሳፍረን፤ ኢያስተኀፍረነ። ለሰብሖተ ስሙ ያንቅሀነ፤
ስሙን ለማመስገን ያንቃን፤ በእርሱ አምልኮትም ወበአምልኮቱ ያጽንአነ። እግዝእትነ ማርያም
ያጽናን። እመቤታችን ጸሎታችንን አሳርጊልን፣ አዕርጊ ጸሎተነ ወአስተሥርዪ ኃጢአተነ ቅድመ
ኃጢአታችንንም አስተሥርይልን፤ በጌታችን መንበሩ ለእግዚእነ ለዘአብልዐነ ዘንተ ኅብስተ
መንበር ፊት ጸሎታችንን አሳርጊልን። ይህንን ወለዘአስተየነ ዘንተ ጽዋዓ ወለዘሠርዐ ለነ ሲሳየነ
ኀብስት ላበላን ይህንንም ጽዋ ላጠጣን፤ ወአራዘነ ወለዘተዐገሠ ኵሉ ኃጢአተነ
ምግባችንንና ልብሳችንን ላዘጋጀልን፤ ወለዘወሀበነ ሥጋሁ ቅዱስ ወደሞ ክቡረ
ኃጢአታችንንም ሁሉ ለታገሠልን፤ ክቡር ደሙን ወለዘአብጽሐነ እስከ ዛቲ ሰዓት።
ቅዱስ ሥጋውን ለሰጠን፤ እስከዚችም ሰዓት
ላደረሰን።
፰ ለልዑል እግዚኣብሔር ፍፁም ምስጋና ይገባል፤ ነሀብ ሎቱ ስብሐተ ወአኰቴተ ለእግዚአብሔር
. ለድንግል እናቱ እና ክቡር መስቀሉም ምስጋና ልዑል ወለወላዲቱ ድንግል። ወለመስቀሉ ክቡር
ይገባል። የእግዚአብሔር ስሙ ፈጽሞ ይመስገን ይትአኰት ወይሰባሕ ስሙ ለእግዚአብሔር
ዘወትር በየጊዜያቱና በየሰዓቱ። ወትረ በኲሉ ጊዜ ወበኲሉ ሰዓት።
፱. ሰላም ላንቺ ይሁን እያልን እንሰግድልሻለን ሰላም ለኪ እንዘ ንሰግድ ንብለኪ ማርያም እምነ
እናታችን ማርያም ሆይ እንማልድሻለን ከአዳኝ ናስተበቊዐኪ። እምአርዌ ነዓዊ ተማኅፀነ ብኪ።
አውሬ ታድኝን ዘንድ ተማጽነንብሻል ስለ እናትሽ በእንተ ሐና እምኪ ወኢያቄም አቡኪ ማኅበረነ
ስለ ሐና ብለሽ ስለ አባትሽ ስለ ኢያቄም ብለሽ ዮም ድንግል ባርኪ።
ድንግል ማኀበራችንን ዛሬ ባርኪልን።
፲. ማርያም አለችች፦ ነፍሴ እግዚአብሔርን ታላቅ ወትቤ ማርያም፦ ተዐብዮ ነፍስየ ለእግዚአብሔር
ታደርገዋለች። መንፈሴም በመድኃኒቴ ወትትሐሠይ መንፈስየ በአምላክየ እስመ ርእየ
በእግዚአብሔር ደስ ይላታል። የባሪያይቱን ሕማማ ለአመቱ። ናሁ እምይእዜሰ
መዋረድ አይቷልና፤ እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ያስተበፅፅዑኒ ኲሉ ትውልድ እስመ ገብረ ሊተ
ሁሉ ብርክት ይሉኛል፤ እርሱ ብርቱ የሚሆን ኃይለ ዐቢያተ ወቅዱስ ስሙ፤ ወሣህሉኒ
ታላቅ ሥራን ለእኔ አድርጓልና፤ ስሙም ቅዱስ ለትውልደ ትውልድ ለእለ ይፈርህዎ ወገብረ
ነው። ለሚፈሩትም ምሕረቱ ለልጅ ልጅ ነው። ኃይለ በመዝራዕቱ። ወዘረዎሙ ለእለ ያዐብዩ
ኃይልን በክንዱ አሳይቷል፤ በልባቸው አሳብ ኅሊና ልቦሙ ወነሠቶሙ ለኃያላንያላን
የሚኮሩ ትዕቢተኞችን በታተናቸው፤ እመናብርቲሆሙ ኣዕበዮሙ ለትሑታን
ብርቱዎችንም ከዙፋናቸው አዋረዳቸው ወአጽገቦሙ እምበረከቱ ለርኁባን። ወፈነዎሙ
የተዋረዱትንም ከፍ ከፍ አደረጋቸው፤ ዕራቆሙ ለለብዑላን ወተወክፎ ለእስራኤል
የተራቡትንም በቸርነቱ አጠገባቸው፤ ቍልዔሁ ወተዘከረ ሣህሎ ዘይቤሎሙ ለአቢዊነ
ባለጠጎችንም ባዶ እጃቸውን ሰደዳቸው፤ ለአብርሃም ወለዘርዑ እስከ ለዓለም።
ምሕረቱን እንዲያስብ እስራኤል ባሪያውን
ተቀበለ። ለአባቶቻችን ለአብርሃምና ለዘሩም
እስከዘለዓለሙ ድረስ እንደተናገረው።
የመቁጠሪያ ጸሎት
፯. ኦ አምላክ፦ ፵፩ ጊዜ
፰. ኦ ክርስቶስ፦ ፵፩ ጊዜ
፱. ኤሎሄ (አምላኬ)፦ ፵፩ ጊዜ