You are on page 1of 6

ዜጎችን ከከፋ ጥፋት ለማዳን “ለውጡን ለውጡት

ተጻፈ ከፋንታሁን ዋቄ
ጳጉሜን ፭ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም.
ለኢትዮጵያ የፖለቲካ ልሂቃን

የአገራችን የፖለቲካ ልሂቃን ሆይ! አንደ አንድ የጨነቀው ምሰኪን ዜጋ ምክረ-ሀሳብ ነውና
ለመስማት ሞክሩ፤ በለውጥ ስም የከፈታችሁትን የሲዖል በር ለመዝጋት ፈቃደኛ ከሆናችሁ ይህን ድምጽ
ስምታችሁ ለእናንተም መሪዎች እና ለእኛም ለተመሪዎች ከጥፋት እንድንተርፍ ” ለውጡን ለውጡት”።

ለ50 ዓመታት የተጠራቀመውንና የተወሳሰበውን የዚህን ተውልድ የፖለቲካ ብልሽትና የትውልድ ግራ


መጋባት፣ የእናንተ የፖለቲካ ልሂቃንም ከዚህ ግራ ከተጋባ ትውልድ መገኘት ለመልካም እንለውጣለን ያላችሁት
ሁሉ በተቃራኒው ለጥፋት ሆኗል። መልካም ንግግሮቻችሁ አንፃርእየደረሰብን ካለው የመከራ ሕይወት
እንደምንረዳው ተግባራችሁ እጅግ ተቃርኖ ሆኗል። ለውጥን የጀመራችሁት ከአምላክ የለሹ እና ደም አፍሳሽ
ማርክሲስት ሥርዓት በወያኔ መሪነት ወደ ብሔረሰብ ዘረኝነት ጣዖት ያሽቆለቆለውን ብልሹ ፖለቲካ ወደ ሰውነት
ፖለቲካ ክፍ የማድረግ መልካም ለውጥ ጠብቀን ነበር። ነገር ግን አሁን ከደረስንደበት የውድቀት ደረጃ ሚዛን
ለውጡ መንገዱን ስቷል ብቻ ሳይሆን ወደከፋ አዘቅት ወድቋል። ዘረኝነትና ቡድን ሰውነትን ተክቷል። ሰብአዊነት፣
ፍትሐዊነት፣ አገራዊነት፣ እውነተኝነት በፍጹም ኢሰብአዊ ጭካኔና ተራ ቁማርተኝነት ተተክቷል። የመልካም
ትርጉሙ እስካልተቀየረ ድረስ አሁን የምንገኝበት መከራ “ለውጥ” ለጥፋት ሆኗል። ይህን ተጨባጭሁኔታ
በመገንዘብ እባካችሁ “ልውጡን ለውጡት” ።

ከዚህ ጽሑፍ የበለጠ ጮኾ የሚናገረው እየፈሰሰ ያለው የንጹሐን ደም፣ በቁማቸው በመከራ ውስጥ
እንዲገቡ የተደረጉ ዜጎች ዕንባ፣ አገር ውስጥ ተፈብርኮ እንዳይጠናቀቅ ተደርጎ የሚካሄደው የአገር ውስጥ ጦርነት
“ለውጡን ለውጡ” እያላችሁ ነው! ጽሑፉ ምናልባት ጩኸቱን በመየጠኑ ለማጉላት ይጠቅም ይሆናል።

በእኔ አረዳድ አገራችን አሁን የምትገኝበት አውድ፡- መንግሥት በሕዝቡ ዘንድ ሙሉ በሙሉ እንደ
መንግሥት ተአማኒነት አጥቷል። መንግሥት የጥቂት ልሂቃን ጠባብ ቡድን እንጂ የዜጎች አይደለም የሚል ዜጋ
አብላጫ ቁጥር አለው። መንግሥት በተወሰነ የብሔር ንዑስ ማንነት መሣሪያነት የሚያገለግል ብቻ ሳይሆን
በብሔረሰብ ሽፋን ጥቂት ልሂቃንና በሠልጣን ዙሪያ የተኮለኮለው ሙሰኛና የቁሳዊነት ሰቀቀን ሕሊናውን
የጋረዳቸው ቡድኖች አገልጋይ ሆኗል። በብሔር ፖለቲካ ሥር ራሳቸውን የሰወሩ በተለያዩ ቁሳዊና እምነታዊ ቡድን
የተደራጁ አካላት መንግሥትን እጅ አድርገው ብዙኃኑን ለመከራና ለስቃይ ዳርገዋል። አገሪቱ እነዚህ ቡድኖች
እንወክለዋልን በሚሉአቸው ክፍለ-ሕዝቦች እየማሉ በተቃራኒው ግን ከሕዝቡ ባህል፣ እምነት፣ እሴትና ዘለቄታዊ
የትውልድ ፍላጎት ውጭ ራሳቸውን ባደራጁ ጥቂት ራስወዳድ ልሂቃን ምናብ የተፀነሰችን ልዩ አገር ወይንም አካባቢ
ለመፍጠር በሚሠሩ ልሂቃን የተወጠረች አገር ሆናለች። የፖለቲካ ተቋማት ጠቃሚ ሀሳብ ከማመንጨት ያረጡ
የመከራ ምንጮች በመሆን የሚመሩትን ሕዝብ በቡድን መንጋነት አሥረው ወደባርነት የሚያግዙ መሣሪያዎች
አድርገዋዋል።

መንግሥት የተባለውን ተቋም የመመሥረቱ ቀዳሚ ዋና ዓለማ የእያንዳንዱን ዜጋ የመኖር ዋስትና ማረጋገጥ
ነበር፤ አሁን ያለው መንግሥት ግን በብሔር ንዑስ ማንነት መሠረት ላይ የቆመ መሆኑ ሰውን በሰውነቱ ለመቀበል
ፈተና ገጥሞታል። ትኩረቱ ለሥልጣን ዘለቄታዊነት አንዲያገለግለው ልዩነትን በቦታ፣ በቋንቋ፣ በባህል፣

ከ6ቱ ጠቅላላ ገጾች 1ኛው


በትርክት፣ በመልክዐ ምድራዊ አሠፋፈር ማጠናከር ሕዝብን የማጋጨት ፕሮጄክት ነዳፊና ፈጻሚ መስሏል።
ለውጡ መለወጥ እንደሚገባው ከሚጣሩ የመንግሥት እና የፖለቲካ ልሒቃን አሉታዊ መገለጫዎች መካከል፡-

1. ሐሰተኝነት፣ ቁማርተኝነትና ክፋት በዜጎች መካከል መለያየትና አለመተማመንን አንሰራፍቷል፤


2. በዜጎች አገራዊ የመናበብና የመግባባት እሴት እና የሽምግልና ባህል ገድሏል፤
3. ሙሰኞችን፣ ጨካኞችንና ሌቦችን ወደ ታላላቅ የመንግሥት ሥልጣን አምጥቷል፤
4. በአንድ አገር ውስጥ አገር የሚፈጠር ድንበርና ክፍለ-ሕዝብ ለመፍጠር ሲባል ሕዝብ ለሕዝብ እያዋጋና
እያጠፋፋ ነው፤
5. የአገርን ወደ ፍጹም ጥገኝነት በማስገባት ለሁለገብ የውጭ ጠላቶች ጣልቃገብነት ማመቻቸት
መቀጣላቸው አፍ አውጥቶ ይናገራል።

ይህን አሳዘኝ የመከራ አውድየፈጠረው ርእዮት፣ አሠራርና መዋቅር በፍጥነትና በቁርጠኝነት ካልተቀየር
መንግሥትንም አገርንም ያጠፋዋል የሚል ጠንካራ እምነት አለኝ። በአንድ አገር ሕዝብ መካከል ወገን የሆነ እና
ጠላት የሆነ በማለት ትርክትን የሚያራግበው ቡድንን እንጂ ሰውን የማያውቀው የለውጥ አቅጣጫ ቀጥሏል።
እኛም ተራው ዜጎች ኃጢአታችን በዝቶና በንስሐ ከመመለስ እጅግ ዘግይተን በመኖራችን ውጤቱ ከደርግ ወደ
ወያኔ ከዚያም ወደ ብልጽግና ዘረኛ የባሰ የእብደትና ውጥንቅጥ አጥፊ ፖለቲካ መሻጋገር ሆነብን። አሁንም
እንደሚገባ ንስሓ ገብትንና እርስበርሳችን ተፈቃቅረን ከሰውነት አስወጥተው በዘረኛ የቡድን ፖለቲካቸው
እየከፋፈላችሁ የምታጠፋፉንን ስላላስቆናችሁ መከራችን ቀጥሏል። ወደፊትም ከዚህ ፖለቲካ ካልወጣን ይቀጥላል።
የዚህ ጽሑፍ ዋና ዓለማ እኛ እንደ ሕዝብ ንስሐ እንድንገባ እናንተ ለሂቃን እንደ ፖለቲካ ነዳፊዎችና መሪዎች
ከክፋታችሁ እንድትመለሱ፣ ሁላችንም አብረን ራሳችንን በራሳችን ከማጥፋት እንድንድን ማሳሰብ ነው።

እናንተ መሪዎች ሰማችሁም አልሰማችሁ እኛ ተመሪዎች አሁን ያለን አማራጭ እናንተንም መምከር እኛም
አንደ ሕዝብ ወደ ልቦናችን ተመለሰን ከቡድን እብደት ወደ ሰውነት ለመመለስ መመካከርና በተግባር መለወጥ
ነው። በሁለተኛ ደረጃ በሥልጣን ላይ የምትገኙና በፖለቲካ ተፎካካተሪነት ያላችሁ የወደፊት የአገር መሪዎች ምን
ያህል ተፈጥሮአዊ ያልሆነ፣ ከውጭም ያልመጣብን ችግር ፈጥራችሁ እንደምታሰቃዩን መለስ ብላችሁ
እንድትመለከቱ፤ በሶስተኛ ደረጃ ምን ብታደርጉ ከዚህ አጣብቂኝ ይዛችሁን ልትወጡ እንደምትችሉ የዜግነት
እይታን በማጋራት ከሕሊና ጫና እረፍት ለማግኘት ነው።

ለመልካም ለውጥ መጣን ብላችሁ ነበር፤ ነገር ግን ከእናንተ አስቀድሞ የነበሩ የፖለቲካ ሥርዓታት በጣሉብን
ክፋት ላይ ጨምራችሁ፣ ክፋትን እንደ ልሕቀትና አዋቂነት በምትሠሩት ማስተዋል የጎደለው የቁማር ፖለቲካ
ለሕዝቡ ያፈራው ነገር፡- ጥርጣሬ፣ ስደት፣ መፈናቀል፣ ሞት፣ ሕገወጥነት እና ተስፋቢሰነት ነው። አሁን በኢኮኖሚ
ሥርዓት፣ በፍትሕ ሥርዓት፣ በማኅበራዊ መስተጋብር፣ በሕዝብ አሠፋፈር፣ በመንግሥት መዋቅር አድሎአዊነት
ወዘተ በምታደርጉት ተግባር ለውጡ ከአዎንታዊነት ወደ ባሰ ጥፋት የሚወስድ መሆኑን አስመስክራችኃል። ያንኑ
የቀደመ ሥረዓት ጥፉ ርእዮት አባብሳችሁና አክፍታችሁ ቀጠላችሁበታል። ይህን የሲኦል መንገድና በሩን
መልሳችሁ ለመዝጋት እድል የምታገኙበትን እና የንስሐ እድል አግኝታችሁ መከራ ውስጥ ከከተታችሁት ሕዝብ
ጋር በአንድነት እንድትድኑ በገባኝ መጠን መውጫውን ልጠቁማችሁ።

ለሀገር ሰላምና አንድነት ሊያመጣ የሚችለው ይህን መንገድ መጠጋገንና ማሽሞንሞን ሳይሆን ሙሉ በሙሉ
መቀልበስ ብቻ ነው። ጥቆማው ተቀባይነት አግኝቶ እንደገመትኩት እናንተም እኛም ከተረፍን ደስተኞች እንሆናል።

ከ6ቱ ጠቅላላ ገጾች 2ኛው


ይህ ምክረ ሀሳብ የመነጨው መጭዉን ጊዜ ከመፍራቴ የተነሳ ለራሴ፣ ለአገሬና ለሰው ልጆች ሁሉ ስል የማደርገው
ድፍረት ነውና ለድፍረቴ ይቅርታ አድርጉለት።

የመፍትሔ ሀሳብ ጥቆማ


አሁን አገራችንና እናንተ መሪዎች የምትገኙበትን ውጭአዊና የተጠራቀመ የውስጥ ውስብስብና ሁለገብ
አገራዊ ኪሣራንም ታሳቢ ያደረገ ነው። ከወያኔ የተረከባችሁትን አገር ወደተሻለ ለመለለውጥ የመረጣችሁት
አቅጣጫውና ግቡ እስከነ ሂደቱ ፍጹም አጥፊ ነው። ለለውጡ ስኬታማነት የምተጠቀሙት መሥፈርትም
ሙሉ በሙሉ ሰብእናን ወይንም የሰውን ነፃ ተፍጥሮ የዘነጋ በቡድንና በቁስ ላይ የተንጠለጠለ በመሆኑ ብቻውን
ዋጋ-ቢስ ነው። የዚህ መንስዔው የምትከተሉት ሥሑት ፖለቲካዊ ርእዮት ሲሆን ለነባር አገራዊ የሕዝብ እሴትና
ማንነት አሉታዊ እይታ አላችሁ። ስለዚህ ለውጥ ብላችሁ የጀመራችሁት ሁሉ የሚያተኩረው ነባር ነገርን
በመንቀልና በማጥፋት በምትኩ በጭፍን ይትገለብጡትና ዘለቁታዊነት የሌለው አዲስ የሚመስል እርባና ቢስ ነገር
ነው። በዚያውም ላይ የምትሞክሩትን አዲሱን የለውጥ መንገድ አንደ ሰማያዊ ሃይማኖት ወይንም “አማራጭ
የሌለው” እንደሚለው ማርክሳዊ ሌኒናዊ አብዮት ስለተቸከላችሁበት አማራጭ ሁሉ የጠላት መስሎ
ስለሚታያችኑ ያሰባችሁትን ለማሳካት ወደ ጉልበትና ሸፍጥ ታዘነብላላችሁ። እናንተም ወያኔ ከማርክሲዝም
ርእዮት የውድቀት ትቢያ ላይ ያነሳውን ዘረኝነት በብሔርሰብና ጎሣ ፖለቲካ ሸፋፍናችሁ ሁለንተናዊውን ሙስናና
የአገር ጥፋት ቀጠላችሁበት።

ለውጥ ብላችሁ ስትነሱ መሪ ያደረጋችሁት ጥፋቱን ባስከተለው የማንነት ፖለቲካ ልሂቅነት አንቱ የተባሉ
ዘረኞችን ወደ ሥልጣን በማምጣትና አገራዊያን አዋቂዎችንና እሴቶቻቸውን፣ ሃይማኖታቸውንና እውቀቶቻቸውን
ሁሉ በጠላትነት በመፈረጅ ነበር። ስለዚህ ለእናንተ ለልሂቃኑ ከጀመራችሁት መንግድ የተለየ ሌላ የለውጥ
ምክር-ሀሳብ ማቅረብ የዋሕነት ሊመስላችሁ አንደሚችል እገምታለሁ። ቢሆንም በዝምታ ከማለፍ
ተናግሮ በደባባይ ምላሻችሁን መጠበቅ ይሻላል በሚል ይህችን አጭር መልዕክተ ልኬላችኋለሁ። ሀሳቤብ
ዋጋ ትሰጡት ይሆናል ብዬ እንዳስብ የሚደርገኝ አሁን የያዛችሁት መንገድ ሞት፣ ስደት፣ ጥርጣሬ፣ ጥላቻ፣
ሌብነት፣ ክፋት፣ ሐሰተኝነት፣ ጦርነት ብቻ በመሆኑ የምታጎርፉት የፕሮፓጋንዳ ወንዝ፣ በየጊዜው የምትሞክሩት
ብልጣብልጥ የልማትና የእምርታ ምስል ሊሸፍነው አለመቻሉ ፈጥጦ እንደወጣ መገንዘብ የጀመራችሁ
ስለሚመስለኝ ነው። በእኔ አምነት ከበለጠ ጥፋት ለመትረፍ ያለችንና የቀረችዋ አንዲት አማራጭ
“ለውጣችሁን መለወጥ” ብቻ ነው። ጭፍን አልኸኝነት፣ አማራጭ ሀሳብን በመቃወም ወደ ኃይልና ማሳደድ
መግፋት፣ ሀሳብን ከማሻሻል ይለቅ የብልጽግና መንገዱ “እነርሱ” የተባሉ ክፍሎችን ማሸነፍ፣ ማጥፋትና የበላይ
መሆን፤ በሐሰተኝነትና በእውነት መካከል ያለውን ድንብር ማደበዝዝና ማጥፋት፤ የቁማርተኝነት እንደማያወጣ
እየተካሄደ ያለው ጦርነት፣ የሰው መፈናቀልና እልቂት፣ በሁሉም ቦታ የሚካሄደው ሰቆቃ የሚጠቁማችሁ
ይመስለኛል።

ለውጥን የመለወጥ ምክረ ሀሳብ


በመንግሥት ቁርጠኝትና ጫንቃ፣ በአመራራራችሁንና ሰብእናችሁን በመለወጥ ሊተገበር የሚችል
የመፍትሔ ምክረ ሀሳብ

1. መንግሥት ከሁሉ አስቀድሞ በዘውግ ፖለቲካና በፕሮፓጋንዳ ያልተበከሉትን የባህልና የእምነት መሪዎች፣
የአገር በቀል እውቀት ባለቤቶች፤ ከዘርኝነት፣ ባሳለፍናቸው የ50 ዓመታት ተከታታይ ፈተናዎች ሁሉ
ከሙስናና ከጽንፈኝነት ነፃ መሆናቸው የሚመሰከርላቸው፣ ከሙስና የጸዱ ኃይለ-ግብራት አማካሪዎችን

ከ6ቱ ጠቅላላ ገጾች 3ኛው


ከሁሉም ባህሎችና እምነቶች ማሰባሰብ። የማሰባሰቡን ሂደት የሚጠብቅ ተአማኒኒ መመሪያ ማዘጋጀት
ያስፈልጋል።
2. ለዘረኝነትና ለመለያየት መሠረት የጣለውን ውጭ-ገብ የፖለቲካ ርእዮት ላይ የተመሠረቱ ሕጎችን፣ ሕገ
መንግሥቱን ጨምሮ በአዋጅ ማገድ
3. የብሔር የፀጥታ መዋቅርን በማፍረስ በአንድ አገራዊ እዝ ሥር ማስገባት
4. የብሔርና የጎሣና የሃይማኖት የኢኮኖሚ መዋቅራትንና ኢምፓየሮችን በሕግ ማገድና መዋሐድ
5. በምንም መልክና ደረጃ ቢሆን ሙስና ከባድ ቅጣት የሚያስከትል ሕጎችን መደንገግ
6. የአገር በቀል የባህልና የእምነቶች የፍትሕና የአስተዳደር ሥርዓቶችን መመዝገብና በየአከካባቢው ሥራ
እንዲጀምሩ ማድረግ፣ በዜጎች መካከል ምንም አይነት አድልዎ እነዳይፈፀም ማዕከላዊ ቁጥጥር ሥርዓት
መዘርጋት
7. ዳኞች፣ ፖሊሶች፣ ዐቃቢያነ ሕግ በጎሣና በአካባቢ እንዳይመለመልና እንዳይመደብ በሕግ ማገድ
8. የአፈር ማዳበሪያ፣ የሰብልና የእንሳት ዘርያና ልማት በውጭ-ገብ ግብአት ላይ ጥገኟ የማይሆንበትን ፈጣን
የምርምር፣ የባህላዊና በጊዜአዊነት ገብተው አገራዊ የሚሆኑ መንገዶችን መቀየስ
9. ዓለም አቀፍ የአፍሪካ ቀንድ ተዋኒያንን ፍላጎት በማጫወት ለኢትዮጵያ እደገትና ራስን መቻል፣ የሁሉን
ጥቅም የምታቻችል ገለልተኛ ታማኝ አገር መሆኗን የምታሳይበት አዲስ የዲፕሎማሲ ሥልት መቀየስ
10. የአረብ፣ የቻይና፣ የሩሲያ፣ የአውሮፓ፣ የአሜሪካ እና የአፍሪካ ጎረቤቶቻችንን ዘለቄታዊ ጥቅሞች ሳይጋጩና
በውድድር መንፈስ ሳይጠራጠሩ በትብብር የተሻለ ጥቅም የሚገኝበት አሰላለፍን በማስተዋወቅ ለዓለም
አዲስ የትብብር ምክኒያት ሆኖ ለመውጣት አዲስ ኢትዮጵያዊ/አፍሪካዊ አቅም መፍጠር በሚቻልበት ላይ
መሥራት፣ ሐሳቡን የሚደግፉ አዐለምአቀፍ አገራትን ማሰባሰብ፣
11. በአገር ውስጥ ከአገራዊ አጀንዳ በተለየ ሁኔታ በሃይማኖት፣ በፖለቲካና በባህል ስም ከፋፋይ ሚና ያላቸው
ስብስቦችን፣ ከውጭ አካላት ጋር የሚወዳጁትን ጥብቅ ክትትል በማደርግ በአገር ክህደት ደረጃ ፈርጆ
ያማያደግም ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ
12. በዘርና፣ በሃይማኖትና በሌላ መስፍርት ዜጎችን የሚከፋፍል መልዕክት ያላቸው መጽሐፍ፣ ትምህርት፣
ሚዲያ፣ የኪነ ጥበብ ውጤት፣ አገራዊና አካቢያዊ ሕግ፣ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ መዋቅር በህግ እንዲታገድና
ነባሩ ዜጋ በሰውነቱ ብቻ የሚገናኝበት ሥርዓት በሕግ መዝረጋት
13. በእፍሪካ አንድነት ውስጥ ልዩ መዋቅር በመፍጠር ለቀጠናና አህጉራዊ መዋሐድ ፍጥነት የሚሰጥ
አገልግሎት መጀመር
14. ከሶማሊያ፣ ሱዳን፣ ግብጽ፣ ኬኒያና ዩጋንዳ ጋር መተማመንን የሚፈጥር ግኑኝነት፣ የጋራ ትላልቅ
ፕሮጄክቶች፣ የጋር ቀጠናዊ ራእይና የጋራ አስፈጻሚ ተቋም በማዕከላዊ ድንበሮቻችን ላይ ነፃ ክልሎችን
በበከለል ማቋቋም፤ የጋራ የፀጥታ ኃይሎችን መመሥረት
15. የጋራ የሆነ ከአውሮፓ፣ ከኤሲያ፣ ከአረብ አገራት፣ ከአሜሪካና ሌሎችም ጋር ግኑኝንት የሚደረግበት
የአፍሪካ አንድ ዲፕሎማሲያዊ ማእከል መፍጠር፣ ለንግድና ለፀጥታ የሚደረጉ ስምምነቶች በአንድ
አፍሪካዊ በርና ውሳኔ ብቻ እንዲካሄዱ የመሪነቱን ሥራ ወስዶ መሥራት

ከ6ቱ ጠቅላላ ገጾች 4ኛው


16. የአፍሪካ የአስተሳሰብ ልሕቀት ማዕከል በመመሥረት በጭፍን ተውሶ በሚመጡ ርእዮቶች፣ የኢኮኖሚ
ሥርዓቶች ምክኒያት አፍሪካን ወደ ጥገኝነት፣ የእርስበርስ ግጭት፣ አሉታዊ አፍራሽ ውድድር የሚመራ
አሠራርን ላመስቆም የሚሠራ ተቋም መፍጠር
17. በንዑስ ፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ሕሊናቸው ያልተዛቡ ብሔራዊያን ሊቃውንትን ከሁሉም አምነቶችና ባህሎች
በማሰባሰብ አንድ የአገራዊ እውቀትና ክሂሎት ማእከል መመሥረት፡- ማዕከሉ ለአስተዳደር፣ ለፍትህ፣
ለመድኃኒትና ምግብ፣ ለአገራዊ የግጭትና ያለመግባባት መፍትሔ መሪ እንዲሆኑ በሕግ መደንገግ
18. ዜጎችን ሁሉ በእኩልነት ተስፋ የሚሰጥ አገራዊ ርእይና ግብ፣ ግቡን ለማሳካት የሚኬድበት ከንዑስ ማንነትና
ክፉ ትርክት ነፃ የሆነ ፍኖተ-ካርታ መንደፍ፤ ለፍኖተ ካርታው እንቅፋት የሚሆኑ ውች-ገብ፣ አገር ነቀል
አስተሳሰቦችንና ርእዮቶችን ብሔራዊያን ሊቃውንትና በአአገራዊ እሴት መተካት፣ በህግ መጠበቅ
19. ላለፉት 50 ዓመታት በተውሶ ርእዮት ማኅቀፍነት የተናኙ የጥፋት አስተምህሮዎች፣ የተመሠረቱ ፓርቲዎች፣
የተጻፉ መጽሐፍት፣ የተዘመሩ መዝሙሮችና የዘፈኑ ዘፈኖች፣ የተቀረጹ ፊልሞችን የተተወኑ ድራማዎች
ተሰብስበውና ተመርምረው በህግ አንዲታገዱ ማድረግ።
20. በውጭ አገራት እርዳታ፣ በውጭ አገራት ተቀምጠው ወይንመምበአገር እየኖሩ ከውጭ ተወዳጅተው
አገራቸውን የሚያፈርሱ ትርክቶችን የመመርቱ ልሒቃንን በሕግ ማገድ፤ አንዚህ ሰዎች የሚረዱ የውጭ
አካላትን በዲፕሎማሳዊ መንግድ ማሳረፍ የሚስችል ሕግ መደንገግና መተግበር።
21. የፖለቲካ ልሂቃን ቀማሪነት፣ በሐሰት ትርክት ፕሮፓጋንዳና ምናባዊ ተስፋ የተናኘው የትግራዋይነት፣
የሲዳማነት፣ የአማራነት፣ የአሮሞነት (-“ኡማ”)፣ ወዘተ የንዑስ ማንነቶች በተለያየ አቅታጫ የተሠመረ
ርእይና ግብ ወደ አንድ የሚመልስ ብሔራዊያን ሊቃውንት የሚመሩት አንድ ወጥ አገራዊ የአገር መልሶ
ግንባታና አንድ ወት የጋራ ልማት ፍኖተ-ካርታ ማዘጋጀት፡ ይህን ፍኖተ-ካርታ አዉን አንዳሆን እንቅፋት
የሚሆን የፖለቲካና የማኅበራዊ ንቅናቄን በህግ መገደብ።
22. እስከአሁን የተፈጸሙ ግፎች (ስም ማጥፋት፣ ማፈናቅል፣ መግደልና ማግለል ወዘተ) ፍትሕ በባህላዊና
ሃይማኖታዊ ተቋማት መሪነት፣ በዘመናዊ የህግ ሥርኣት ተባባሪነት እንዲያገኙ ማድረግ፣ ቁስለችን
አንዲሽሩ፣ መጠራጠር ተወግዶ መተማመን እንዲጎለብት አሠፋፈርን ወደቀደመ (የዛሬ 32 ዓመትን ታሳቢ
አድርጎ) መልሶ ማቋቋም።
23. በሁሉም ቦታና ስፍረራየሚነገርና የሥራ ቋንቋ የሚሆን አንድ ቋንቋ በፖለቲካ ሳሆን በሳይነሳዊ ምክኒቶች
መደንገግ
24. ቡድንን ሳይሆን ሰብአዊነትን፣ ፍትሕን፣ እውነትን፣ አገራዊ አምነትና ባህልን ማዕከል ያደረገ ፖለቲካ፣
ሚዲያ፣ ትምህርት መቀየስና ብሔራዊያን ሊቃውንትን መሪ ማደርግ።
25. የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ከክልልና ከቋንቋ ዘውግ ወደ አገራዊ ማዕከላዊ አስተዳደር በሕግ
እንዲዞሩ በማድረግ (1) እስከአሁን አዲስ ትርክት ለመፍጠር የተደረገውን ስሕተት/ሐሰት ሁሉ በዝርዝር
ለሕዝቡ ማሳወቅ፣ (2) የሕዝብ አንድነት፣ እርቅ፣ ንስሐን የሚሰብኩ የሚዲያ ፍኖተ-ካርታን መተግበር፣
(3) ባሳለፍናቸው አብዮተኛና ባእድ አምላኪ ትውልድ የሠራኛቸው ስህተቶች፣ የስህተቶች መሠረት የሆኑ
የአስተሳሰብ መዛባት፣ የፍልስፍና መምታታትና የፖለቲካ ርእዮቶች ስህተትን ተንትኖ ለተማረው ሁሉ
ማድረስ ትውልዱ ራሱን እንዲገመግም መቀስቀስ፣ ከጭፍን ገልባጭነትና ከእውር የመንጋ ተከታይነት ነፃ
መውጣት ለአገርና ለትውልድ ያለውን ፋይዳ ማስረዳት

ከ6ቱ ጠቅላላ ገጾች 5ኛው


ለውጥን የመለወጥ አተገባበር
1. ይህን አዲሱን የመንግሥት መንገድ በመደገፍበና የውጭ ጥቃትና ጣልቃገብንት ለመቀነስ ፈቃደኛ የሆኑ
አገራትን ፈልጎ በምሥጢር ስምምነት ማድረግ
2. ልሂቃኑንና ወጣቱን በአዲስ መንገድ ማሰብ እንዲጀምር የሰማውን ብቻ መልሶ ከሚናገር የፖለቲካ ካድሬ
በራቀ መንገድ በሚየስቡና ለሕሊናቸው በሚገዙ ሊቃውንት የሚመሩ አውደ ጥናቶ በማዘጋጀት ገለፃዎችን
በመገናኛ ብዙኃን ማሠራጨት
3. አፍራሽ ርእዮቶችን መነሻና መገለጫዎች በግልጽ ቋንቋ ለሕዝቡ መንገር
4. አግባብነት ያላቸው አዋጆችና የአስቸኳ ጊዜ ድንጋጌዎችና ማንበር
5. አፍራሽ ሚና ያላቸውን አካላት በስማችው ሳይሆን ሕዝቡ በንግግራቸውና በድርጊቶቻቸው እንደሊያቸው
መለያ የሆኑ ግልጽ ማሳየዎችን በሚዲያና በመድረክ መግለጽ
6. ይህንን ምክረ ሀሳብ በሰፊ የሚዲያ መድረክ ምግለጫ መስጠትና በግልጽ ደብዳቤ መልክ በተለያዩ
ቋንቋዎች ለፌደራልና ለክልል መንግሥታት፣ ለፖለቲካ ድርጅቶች መላክ
7. የተመረጡ ሚዲያዎች ቋሚ አምድ ከፍተው እንዲሠሩበት ማግባባት
8. መተማማን እጅግ ስለሳሳ ብልጠት፣ ሐሰት፣ የስነ ልቦና ጨዋታዎችን መቀነስና በዚህ መንግድ የሚሄድን
ባላሠልታንና ቡድን መቅጣት
9. እስከ አሁን በመንግሥት የተመሠረቱ የድንበር፣ የምክክር ወይንም ማንኛውም ለሕዝብ የተነገሩ የሰላም
መንግዶች ምን ላይ እንዳሉ፣ ምን ተግዳሮቶች እንዳገጠሟቸው፣ ደካማ ጠንካራ ጎኖቻቸው፣ በአዲስ
መልክ መልሶ ተአማኒነትን በሚፈጥር መንገድ ማስተዋወቅ፣ ሂደቱን በሚመሩ ሰዎች የእሴት ገለልተኝነት
ላይ መተማመኛ ማስጠት

እግዚአብሔር በደላችንን ይቅር ብሎን ዘመነ ሉቃስ (2015 ዓ.ም.) የመደማመጥ፣ የእውነተኝነት፣
የፍትሐዊነት፣ የሰላም፣ የአንድነት ይሁንልን። ይህ እንዲሆን እኛም ተመሪዎች ተለውጠን፣ እናንተም መሪዎች
“ለውጣችሁን ለውጣችሁ” በቡድን ያይደለ በሰውነት ደረጃ ለመኖር ያብቃን!

ከ6ቱ ጠቅላላ ገጾች 6ኛው

You might also like