Professional Documents
Culture Documents
አክሲዮን ማህበር ምስረታ
አክሲዮን ማህበር ምስረታ
hihoney3@gmail.com
መንደርደሪያ
ሰሞኑን የቤት አከራዮቼ ከወትሮው በተለየ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው እሰጣ አገባ ውስጥ ገብተው ሲነታረኩ እሰማለሁ እኔም የፀቡ መነሻ ምን
እንደሆነ እና በተቻለኝ ለመገላገል ወደ መኖሪያ ቤታቸው ጎራ ብዬ ስለተፈጠረው ነገር ስጠይቅ ባል ቀደም በማለት “እንደምታውቀው በከተማ
ግብርና ተሰማርተን ውጤታማ ሆነናል ሆኖም ግን ባለቤቴ እንደዚህ ለፍተን ባንክ ያስቀመጥነውን ገንዘብ አውጥተን ጦማር አግሮ ኢንዱስትሪ
አክስዮን ማሕበር በግብርና የንግድ ዘርፍ በታወቁ ሙሁራን በምስረታ ላይ ስለሆነ የአክሲዮን ድርሻ እንግዛ እያለች መውጫ መግቢያ አሳጣችኝ፡፡
እኔ ግን ማህበሩ ወደፊት ቢከስር እና እዳ ከሶስተኛ ወገን ቢኖርበት ያፈራሁትን ንብረት ለእዳ መክፈያ አድርጌ ልጆቼን ሜዳ ላይ አልጥልም ነው
የምለው፡፡” እንግዲህ እኔም የህግ ባለሙያ እንደመሆኔ ይህ አይነት ክርክር በሌሎች ሰዎች ዘንድ በሰፊው ይኖራል የሚል ግምት በመያዝ
የአክሲዮን ማህበር አጠቃላይ ይዘት ጥልቅ እና ውስብስብ ቢሆንም ለግንዛቤ ይረዳን ዘንድ መሰረታዊ ጉዳዮችን በ 1952 ዓ/ም ስራ ላይ ከዋለው
የሀገራችን የንግድ ህግ አንጻር እንመለከታለን፡፡
የንግድ ህጋችን አንዱ ዓላማ ለንግዱ ማህበረሰብ አማራጭ የንግድ አደረጃጀትን ማቅረብ ሲሆን ግቡም የንግድ ማህበረሰቡ ወዶ እና ፈቅዶ እንደ
ልዩ ፍላጎቱ፣እንደ ካፒታል አቅሙ፣የሽሪኮቹን አቀራረብና የሃላፊነት ወሰኑን መሰረት በማድረግ በመደራጀት የንግድ ስራ እንዲከውኑ ለማድረግ
ነው ይህንንም ለማድረግ ይቻል ዘንድ የንግድ ህጉ 6 የተለያዩ የንግድ ማህበራት አይነቶችን አስቀምጧል ከነዚህም ማሀከል የአክሲዮን ካምፓኒ
(ማህበር) አንዱ ነው፡፡ (የንግድ ህግ አንቀጽ 212 ይመለከቷል፡፡)
በተጨማሪም ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች እየተመረቁ የሚወጡ ወጣት ሙሁራኖች የእነዚህ ግዙፍ አክሲዮን ማህበራት መመስረት ሰፊ የስራ እድል
ይፈጥርላቸዋል፡፡ በአጠቃላይ አክሲዮን ማህበር በለሀብቱን (capitalist) ከስራ ፈጣሪ (entrepreneur) ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ ጠቀሜታው
የጎላ ነው ፡፡
ትርጉም
አክሲዮን ማህበር ማለት ቢያንስ በአምስት ሰዎች መካከል የሚቋቋም፣የህግ ሰውነት ያለው፣ካፒታሉ አስቀድሞ ተወስኖ በአክሲዮኖች የተከፋፈለ
እና የአባላቱ ኃላፊነት ለኩባንያው ካፒታል ባዋጡት ወይም በሚያዋጡት መጠን የተወሰነ የንግድ ማህበር ማለት ነው፡፡ (የንግድ ህግ አንቀጽ
210(2), 304, 307(1) ይመለከቷል)፡፡ ከዚህ ትርጉም ውስጥ አክሲዮን ማህበር 4 መሠረታዊ ባህሪያት እንዳሉት መረዳት ይቻላል፡፡ እነዚህንም
በቅደም ተከተል እናያለን፡፡
4. የህግ ሰውነት
በንግድ ህጋችን ውስጥ ከአሽሙር ሽርክና ማኅበር በሥተቀር የንግድ ማህበራት የህግ ሰውነት እንደሚኖራቸው በአንቀጽ 210(2) በግልፅ
ተደንግጓል፡፡ የህግ ሰውነት ዋና አላማ አንድ ግዑዝነት የሌለው ተቋም ከአባላቱ በተለየ የራሱ ህልውና(ሕይወት) እንዳለው በመቁጠር የራሱ
መብት፣ንብረት፣ግዴታ ወዘተ ባለቤት በማድረግ ብዙ ሰዎች አባላት የሆኑበት ማህበር በአንድ ስያሜና በአንድ ውክልና እንዲሠራ ማስቻል ነው፡፡
ስለ ህግ ሰውነት ዓላማ ይሄን ያክል ካልን አንድ አክሲዮን ማህበር መቼ እና የት የህግ ሰውነት እንደሚያገኝ ቀጥለን እናያለን፡፡
አንድ አክሲዮን ማህበር እንደማንኛውም ድርጅት ጥንስሱ የሚጀምረው በአንድ ሰው አዕምሮ ነው፡፡ ይህ ሰው ሃሳቡን ለሌሎቹ አካፍሎ
የሚተባበሩትን ካገኘ በኋላ ለአክሲዮን ማህበሩ አስፈላጊ የሆኑ የህግ ቅድመ ሁኔታዎች ለማሟላት አብረው ይሰራሉ፡፡ ከቅድመ ሁኔታዎቹ ውስጥ
የካፒታሉን መጠን ስንት መሆን እንዳለበት፣ የአንድ አክሲዮን አቻ ዋጋ እና ካፒታሉ በስንት አክሲዮን እንደሚከፋፈል ይወስናሉ ይህ ከተደረገ
በኋላ በአባላቱ መካከል አክስዮኖቹ ይከፋፈላሉ፡፡ በመስራች አባለቱ ከተወሰነው ካፒታል ላይ ቢያንስ እሩቡ ወይም ሃያ አምስት በመቶ ከተከፈለ፣
በዝግ ሂሳብ ከተቀመጠ ለማህበሩ ምስረታ በቂ እንደሆነ እና ምዝገባውም በአንድ አመት ውስጥ ካልተፈፀመ በዝግ ሂሳቡ ውስጥ የተቀመጠው
ገንዘብ ለአዋጡት ተመላሽ እንደሚደረግ በአንቀፅ 312 በግልፅ ተደንግጓል፡፡ አክሲዮን ማህበሩ እነዚህን ቅደመ ሁኔታዎች ካሟላ የት ነው
የሚመዘገበው የሚለውን ጥያቄ ደግሞ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 686/2002 አንቀፅ 9 እና 5(2) መልስ ይሰጠናል ይህም አክሲዮን
ማህበሩ ከተመሰረተ በኋላ በንግድ ሚኒስቴር በሚተዳደር አገር አቀፍ የንግድ መዝገብ ውስጥ መመዝገብ እንዳለበት ይገልፃል፡፡ በንግድ መዝገብ
ውስጥ ከመመዝገብ በተጨማሪ ማህበሩ የህግ ሰውነት ለማግኘት ሌላኛው አስፈላጊ ጉዳይ የመተዳደሪያ ደንቡ እና መመሥረቻ ፅሁፉ በሰነዶች
ማረጋገጫና ምዝገባ ጽ/ቤት ካልተረጋገጡና ካልተመዘገቡ ህጋዊ ውጤት እንደማይኖራቸው የሰነዶች ማረጋገጥና ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 334/1995
አንቀጽ 5 ንዑስ አንቀፅ 1(ሐ) ይደነግጋል፡፡ ይህ ማረጋገጥና ምዝገባ ግን በንግድ ሚኒስቴር ከሚደረገው ምዝገባ በአላማም በይዘትም የተለየ
ነው፡፡ የንግድ ሚኒስቴር ምዝገባ ዓላማ ለመንግስት ቁጥጥርና ለሦስተኛ ወገኖች መረጃን አደራጅቶ ማስቀመጥ ነው፡፡ ሦስተኛ ወገኖች ሲባል
ከንግድ ድርጅቱ ጋር የንግድ ሥራን የሚሰሩ ተገበያዮች፣ አክሲዮን ገዢዎች እና ተመራማሪዎች ድርጅቱ በትክክል የተቋቋመ፣ በቂ ካፒታል ያለው
መሆኑን፣ የሃብት መጠኑ(net worth)፣ታሪኩን የቀድሞ የውጤታማነት ደረጃውን፣ የወደፊት ተስፋውን፣እዳዎቹን ወ.ዘ.ተረፈ የሚያሳይ መዝገብ
ነው፡፡ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽ/ቤት በኩል የአክሲዮን ማህበሩ መመሥረቻ ፅሁፍ እና መተዳደሪያ ደንቡ የማረጋገጡና የማስመዝገቡ
አላማ ደግሞ የሰነዶቹ ይዘት ህግንና መልካም ጠባይን የማይቃረኑ መሆንን ማረጋገጥ ሲሆን ይህ መዝገብ ለሦስተኛ ወገኖች ክፍት እንደማይደረግ
በአዋጅ ቁጥር 334/1995 በእንቀፅ 9(2) ላይ ተደንግጓል፡፡
በአጠቃላይ አንድ አክሲዮን ማህበር የህግ ሰውነት የሚያገኘው በንግድ ሚኒስቴር በሚተዳደር አገር አቀፍ የንግድ መዝገብ ውስጥ ከተመዘገበ እና
መተዳደሪያ ደንቡና መመስረቻ ፅሁፉ በሰነዶች ማረጋጫና ምዝገባ ጽ/ቤት ህግን እና መልካም ጠባይን የማይቃረኑ መሆኑ ተረጋግጦ ከተመዘገበ
ቡኋላ ነው፡፡
እንግዲህ የአክሲዮን ማህበራትን ፋይዳ፣ ባህርያት እና መቋቋም በአጭሩ ከተመለከትን የአክሲዮን አይነቶችን እና አክሲዮን የገዛ ሰው የገዛውን
አክሲዮን በተመለከተ ምን መብት አለው የሚለውን ቀጥለን እናያለን፡፡
የአክሲዮን አይነቶች
በንግድ ህጋችን አንቀፅ 328(1) እና 715 መሰረት አክሲዮን የማይከፋፈል እና ግዑዝነት የሌለው የሚተላለፍ ሰነድ ነው፡፡ አክሲዮኖች ከአንድ
ባለቤት ወደ ሌላ ከሚተላለፉበት መንገድ በመነሳት ለአምጪው የሆነ አክሲዮን “(to bearer) እና በባለቤቱ ስም የተመዘገበ አክሲዮን በማለት
በሁለት ዓይነት መልክ እንደሚከፈሉ ከንግድ ህጋችን አንቀጽ 325 መረዳት እንችላለን፡፡
ከላይ የጠቀስናቸው የአክሲዮን አይነቶች መሠረት ያደረጉት ከአንድ ባለቤት ወደ ሌላ ከሚተላለፉበት መንገድ በመነሳት ሲሆን አሁን ደግሞ
ማህበሩ በመመሥረቻ ፅሁፉ ወይም ይህንኑ የሚለውጠው የጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ መሰረት ልዩ ልዩ መብቶችና ጥቅሞች የሚያስገኙ የአክሲዮን
አይነቶች ማውጣት እንደሚቻል ከንግድ ህጉ አንቀፅ 335፣336፣337 እና 345 መረዳት እንችላለን በዚህም መሠረት አክሲዮኖቹን መደበኛ
አክሲዮን(ordinary share)፣ ቅድሚያ መብት የሚያስገኙ አክሲዮን(preference share) እና ትርፍ ብቻ የሚያስገኙ አክሲዮኖች (dividend
share) በማለት መክፈል ይቻላል፡፡
መደበኛ አክሲዮን
በንግድ ህጋችን አንቀጽ 345፣406 እና 417 መሠረት መደበኛ ወይም ተራ አክሲዮን የገዛ ሰው በአመቱ መጨረሻ ከተጣራ ትርፍ
የመካፈል፣ማህበሩ ሲፈርስ ዕዳው ተከፍሎ ከሚቀረው ገንዘብ የመካፈል፣በጠቅላላ ጉባኤ ድምፅ የመስጠት ፣በያዙት የአክሲዮን ቁጥር አዳዲስ
አክሲዮኖች ሲወጡ ለመግዛት የቀደምትነት መብት እና የማህበሩን የትርፍና ኪሳራ የሂሳብ ሰነዶች እና አስተዳዳሪዎቹንና ተቆጣጣሪዎቹ ለጠቅላላ
ጉባኤው ያቀረቡዋቸውን ሪፖርቶችን የማዎቅ ወይም ቅጂዎችን የመውሰድ መብት ያስገኛሉ፡፡
አሁን ደግሞ በአንድ አክሲዮን ማህበር ውስጥ አክሲዮን የገዛ ሰው አክሲዮኖቹ ምን መብት ያስገኙለታል የሚለውን እናያለን፡፡ ከላይ የአክሲዮን
አይነቶቸን ከሚያስገኙት ልዩ ልዮ ጥቅሞች ወይም መብቶች በመነሳት በመደብ በንግድ ህጉ የተከፋፈሉ ሲሆን እነዚህን አክሲዮኖች የገዛ ሰው
በአመቱ መጨረሻ ከተጣራ ትርፍ የመካፈል፣ማህበሩ ሲፈርስ ዕዳው ተከፍሎ ከሚቀረው ገንዘብ የመካፈል፣በጠቅላላ ጉባእ ድምፅ የመስጠት
፣በያዙት የአክሲዮን ቁጥር አዳዲስ አክሲዮኖች ሲወጡ ለመግዛት የቀደምትነት መብት እና የማህበሩን ሰነዶች ለማወቅ የመቻል ወ.ዘ.ተረፈ መብት
እንዳለው ያየን ሲሆን አክሲዮኖቹን በማዘዋወር ረገድ ባለአክሲዮኑ አክሲዮኑን የማስተላፍ ወይም የመሸጥ፣ በመያዣ የመስጠት እና በአላባ ጥቅም
ለሌላ ሰው የመስጠት መብቶች አሉት ( 329 እና 333 ይመለከቷል) እነዚህንም በቅደም ተከተል እናያለን፡፡
ተቃራኒ ስምምነት ከሌለ በቀር በጉባኤዎች ድምፅ የመስጠት መብት (አንቀፅ 329(1))
ከአክሲዮኑ የሚገኘውን ትርፍ የመቀብል መብት ያለው ሆኖ ባለመያዣው ከአክሲዮኑ የሚገኘውን ትርፍ የሚወስደው
እንዲያው በነፃ ሳይሆን ደረጃ በደረጃ ከባለአክሲዮኑ የሚጠይቀውን እዳ ለማወራረድ ነው ይህንንም ሲያደርግ መጀመሪያ
የዕዳውን ወጪ፣ ቀጥሎ ወለዱን እና በመጨረሻም ዋና እዳውን ያወራርድበታል፡፡(የፍትሐብሄር ህግ አንቀፅ 2868(1-2)
ይመለከቷል)
ማጠቃለያ
አክሲዮን ማህበራት በሃገራችን አንቨስትምንትን እና ሰፊ የስራ እድል ከመፍጠራቸው በተጨማሪ ዜጎች እንደ አቅማቸው የተለያየ መደብ
ያለቸውን አክሲዮኖች በመግዛት ማህበሩ በዓመት ከሚያስገኘው ትርፍ በመቀበል የተለያየ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን እንዲፈቱ
ያስችላቸዋል፡፡
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !!!
ምንጭ፡-
በ 1966 ዓ/ም በስራ ላይ የዋለው የኢትዮጵያ የንግድ ህግ
የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 686/2002
የሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጥ አዋጅ ቁጥር 334/1195
1952 ዓ/ም የወጣው የፍትሐብሄር ህግ
በፍታዱ ጴጥሮስ ገ/መስቀል ፡የኢትዮጵያ የኩባንያ ህግ ፡ የካቲት 2004 ዓ/ም, በፋር ኢስት ትሬዲንግ ኃላ.የተ.የግ.ማህበር
የታተም
Getahun Seifu, Revising company law with the advent of Ethiopian commodity exchange:an
overview, 2003 http://www.ajol.info/index.php/mlr/article/download/57150/45538
Endalew Lijalem Enyew, The doctirine of piercing the corporate veil: its legal and judicial
recognition in Ethiopia፡http://www.ajol.info/index.php/mlr/article/download/81650/71801