Professional Documents
Culture Documents
1
1
ምዕራፍ አንድ
ትርጉም ፡ የወንጌል መግቢያ የነገረ ድኅነት መጀመሪያ ማለት ነውና እግረ መንገዳችንንም
የሰው ልጆችን የመዳን ታሪክ የምናይበት ትምህርት ነዉ፡፡
በትርጉም እና
በትርጓሜ
ትርጉም ፡-ማለት ቃሉ ማርያም የሚለው ከምንም ነገር ጋር ሳይያያዝ ቀጥተኛ ትርጉሙ ማለት
ነው፡፡
ትርጓሜ፡- ማለት ደግሞ ዝርዝር ጉዳይ የያዘ ነው ከተሠጣት ቃልኪዳን ክብር ከመሳሰሉት ጋር
ተገናዝቦ የሚተረጎም ነው፡፡
ነቅዐ ጥበብ የሚለው ስም በትርጉም ደረጃ ሲታይ የእውቀት ምንጭ ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት ስሙ
ከምንም ጋር ሳይያያዝ ማለት ነው፡፡ ቀጥተኛ ትርጉሙ ማለት ነው፡፡ ይህ የሚሆነው ነቅዓ ጥበብ ማለት
ምን ማለት ነው ለሚለው ጥያቄ ነው፡፡
በዚህ መሠረት ማርያም የሚለውን በትርጉም ደረጃ የምናየው ከሆነ ቃሉ በእብራይስጥ ማርያም
ተብሎ ይጠራል፡፡
ማር የሚል እና ያም የሚል ሁለት ቃላት ተገጣጥመው የሚነበብ ነው፡፡
ማር ማለት መራራ ፣ጎምዛዛ፣ሀሞት፣ እሬት ማለት ይሆናል፡፡
ያም ማለት ዮም ከሚል ግእዝ ቃል የተገነ ሲሆን
ትርጉሙ ዘመን ፣እለት፣መዋእል ማለት ይሆናል፡፡
ሁለቱ በአንድነት ሲጠሩ
ዘመነ መራራ
ዘመነ እሬት
ዘመነ ቆምጣጣ
ዘመነ መራራ የሆነባት ሴት ማለት ይሆናል፡፡ ይህም መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ ያለው ነው፡፡
- በመጀመርያ ማርያም ተብላ በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠራችው የሙሴ እህት ማርያም ናት ፡፡
- ታድያ ለምን ማርያም ብለው ጠሯት ሲባል
- በእርሷ ዘመን እስራኤል በመከራ ስደት ይኖሩ ነበርና እንዲሁ በእርሷ ዘመን የእስራኤል
ወንዶች እየታገቱ ይገደሉ ነበርና በዚህ የተነሳ ዘመንሽ መራራ ጎምዛዛ ነው ሲሉ ስሟን ማርያም
ጠርተዋታል፡፡
- ብሉይት ማርያም ለአዲስ ኪዳኗ ማርያም ምሣሌ መርገፍ ሆና የተጠቀሰች ናት ፡፡
- በአዲስ ኪዳንም ማርያም ጊዜ ልጇን ይዛ ተሰዳለችና በእርሷም ጊዜ ሔሮድስ ወንድ ህጻናትን
አስፈጅቷልና ስሟን ዘመንሽ መራራ፣ ቆምጣጣ፣ ጎምዛዛ ነው ሲሉ ማርያም ብለው
ጠርተዋታል፡፡
ማርያም ማለት ኮከብ ባህር ማለት ነው፡፡
እግዚአብሔር ለእስራኤል ባህር በከፈለ ጊዜ ጠላቶቻቸውን በገደለ ጊዜ የሙሴ እህት ማርያም ከበሮዋን
ነጥቃ በባህር ወስጥ አንደኮከብ ቦግ ቦግ እያለች ንሴብሆ እያለች አመስግናለችና ፡፡
ሌላው ራእይ ዮሐንስ 8፣10 ላይ ታላቅ ኮከብ ከሰማይ ወደቀ በውሃም ምንጮች ሢሶ ላይ ወደቀ የኮከቡም
ስም ዕጉስታር (ሬቶ) ይባላል፡፡
ይህ ሲተረጎም
በማዕፀን ውስጥ ንጉስ ሆኖ የተወለደ እርሷ ከወለደችው ክርስቶስ በስተቀር ማንም የለም፡፡
ሀ) መንግስት ስማያት ክርስቶስ ነውና አምላክ ሰው የሆነባት ሰውም አምላክ የሆነበት እርሷ
ስለሆነች ነው፡፡
- በኦሪቱ ከ22ቱ አርስተ አበው 7ኛው ትውልድ የነበረው ሄኖክ ተስፋ ትንሳኤን እንዳሳየን ሁሉ
በሐዲስ ኪዳን በወንጌል አንደተገለፀው ጌታ እኔ ትንሳኤ እና ህይወት ነኝ ማለቱ ይታወቃል
ይህን ትንሳኤና ሕይወት የሆነ ጌታንም የወለደች እመቤታችን በ7ኛውትውልድ የተገኘች ነች፡፡
የእመቤታችን ምሳሌዎች
o ፅርሃ አርያም
o መንበረ ስብሐት
o ሠማይ ውዱድ
ከላይ የተጠቀሱት መቅደሶች ፍጡራን የማይገቡባቸው
የእግዚአብሔር ብቻ ከተሞች ናቸው፡፡
አስር ከተማ ያለው የብዙ ሠሪዊት መኖርያ እና ሦስት ክፍል ያለው ዓለም ነው፡፡
ምድር ብለን የመሠልናት እንደ አምላክነቱ ባርያው መሆኗን ለመግለጥ ነው ሠማይ ስንል ግን
ባለሟልነቷን ለመግለፅ ነው፡፡
ዕለተ እሁድ ይህ ዓለም አዲስ ሆኖ የተጀመረባት ዕለት በኃላም አዲሱ ዓለም መንግሰተ ሠማይ
የሚከፍትባት ዕለት ናት፡፡ እመቤታችንም የፍጥረት ሁሉ መጀመርያ አዳም የታደሰባት በኩር
ሆኖ የተጠራባት ክርስቶስም የተገኘባት ስለሆነች ነው በዕለተ እሁድ የምንመስላት፡፡
የዚህ ዓላም መፈፀምያው እሁድ ስለሆነ የእመቤታችንም ውዳሴዋ በዕለተ እሁድ ያልቃል፡፡
እንደ ወዝ ከንባይ አድርጎ በላይዋ ላይ ከደነባት እስከዚህ ዕለት ምድር ክዳን አልነበራትም
በዐለተ ሠኑይ ምድር የነበረባትን ሸክም ሁሉ ያራገፈችበት ዕለት ዕለት ነበር፡፡ በዚህ ዕለትም
አንድ ግዜ ሸክሟ ረግፎላት ተገኘ፡፡
ምድር የተባለ የሰው ልጅም የዕዳ፰ ደብዳቤው ተነስቶለት የሃጢያት ሸክሙ ቀሎለት
በእግዚአብሔር ፊት መታየት የጀመረው እመቤታችን ጌታን ካስገኘች በኃላ ነው፡፡
በዘርና
በግብር
ዕለተ ረቡዕ ከኋላውም ላሉት ከፊትም ላሉት ሦስት ሦሰት ቀናት የብርሃን ምንጭ ሆኗል፡፡
መጀመርያ የተፈጠረላቸው ብርሃንና ጨለማ ሲፈራረቅባቸው በዕለተ ረቡዕ በተሰጠው ብርሃን
መጠቀም ጀምረዋል፡፡ በዛኛው ብርሃን አይጠቀሙም ነበር
እመቤታችንም ከእርሷ በፊት ለነበረው ለብሉይ ኪዳን ሕዝብና ከእርሷ በኋላ ለሚነሳው የሐዲስ
ኪዳን ሕዝብ ብርሃን ክርስቶስን ይዛ ስለተገኘች ነው የተመሰለችው፡፡
ከፊትም ከኋላም ያሉት ቀናት ዕድሜያቸው የሚሰላው በዕለተ ረቡዕ በተፈጠሩት በፀሐይ
፣ጨረቃ እና ከዋክብት ነው፡፡
በዕለተ ሐሙስ የተፈጠሩ ፍጥረታት በልብ የሚሳቡ በእግር የሚሽከረከሩና በክንፍ የሚበሩ
ናቸው፡፡ምሣሌዎቻቸውም በቅደም ተከተሉ መሠረት የሃጥያን ፣የፃድቃንና ፣የመላእክት ነው፡፡
በገነት ወስጥ ያሉ ጻድቃን በአንቺ የደሰታሉ በደይን( በመከራ) ያሉ አንቺን ተስፋ ያደርጋሉ
(አባ ጽጌ ድንግል)
ለ/ በስምንተኛው ቀን ከጎኑ ሔዋንን አስገኝቷል ይህም ስምንቱ ብሔረ ኦሪት ሲፈፀሙ ከባህሪው
እመቤታችን ለመገኘቷ ምሳሌ ነበር፡፡
ቀድሞዋ ሄዋን ትውልድ እንዲበዛ የተፈጠረች ነበረች የአሁኗ አማናዊቷ ሔዋን ድንግል
ማርያም ግን ትውልድ እንዲባረክ የተፈጠረች ነች፡፡
ምክንያቱም ሔዋን ማለት የህያዋን እናት ማለት ሲሆን እሷ ግን የቃኤል እናት ስለሆነች
በዚያም ላይ ሞትን የተማርነው ከእርሷ ቃል የተነሣ ስለሆነ ነው፡፡
ሃ/አበው ዘ ቅ/ዮሐንስ አፈወርቅ የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 27ን በተረጎመበት አንቀፁ እንዲህ
ብሏል፡፡
የሔዋን ዕዳ ከፋይ
የሔዋን ዕዳ ምን ነበር?
ወንዱ ያለሴት ሴትን አስገኝቶ ነበርና ሴቲቱ ያለ ወንድ ወንድን ሳታስገኝ 5500 ዘመን ቆይታ
ነበርና እመቤታችን ያለ ወንድ ወንድን በማስገኘት ዕዳዋን ከፈለችላት፡፡
በቀደመው ዘመን ወንዶች በሴቶች ላይ ከእኛ ነው የተገኛችሁት እያሉ ይመኩ ነበር፡፡ በሐዲስ
ኪዳን ግን እመቤታችንም ያለ ወንድ ዘር ወንድን በመውለዷ የደናግል መመኪያ ተሰኝታለች፡፡
ቀዳማዊት ሔዋን ድንግልናዋን አጥታ ሞትን ስታስገኝ ዳግሚት ሔዋን ድንግል ማርያም ግን
ድንግልናዋን በመጠበቅ ሕይወትን ለዓለሙ ሁሉ አስገኝታለች፡፡
ድንግልና የሚጀምው ከህሊና ነው፡፡ ከዚያም በነፍስና በሥጋ ድንግል መሆን ይመጣል ማለት
ነው፡፡
በዚህም ምክንያት እመቤታችን ድንግል ማርያም የቀዳሚት ሔዋን ዕዳ ከፋይ ሆናለች፡፡ በዚህም
የተነሳ ሴት ተብላ ተጠርታለች፡፡
እመቤታችን ለምን ሴት ተባለች?
ሴቲቱ ተብላ የተጠራችው እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት፡፡ ምክንያቱም በዘሯና በርሷ
መካከል ከዲያብሎስ ጋር ጠላትነት የተደረገ ስለሆነ ነው፡፡
ራዕይ 12፡1-6 ‹‹ ከዘሯ የቀሩትን ሊዋጋ ሄደ፡፡›› ይህ ጠላትነት የተደረገው በእመቤታችን ዘመን
ነው እንጂ በሔዋን ዘመን አልነበረም፡፡
ለ) የክርስቶስ የባሕሪ አምላክነት ከአይሁድ ጀምሮ እስከ አህዛብ ድረስ ሕዝቡ ያልተቀበለበት
ጊዜ ስለነበር ነው።
ይህ እንዴት ሆነ ቢሉ?
ገነት የተጠበቀችው ለምን ነው? ቢሉ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከገነት መውጣቱ ይታወቃል።
ይህ ሳይሆን ቀርቶ አዳም በገነት ቆይቶ ቢሆን ኖሮ ዕፀ ሕይወትን በልቶ ባልሞተና ከክብሩ
ባልተለየ ነበር። ነገርግን አዳም በድሏልና ቅጣትም እንዲገባው እግዚአብሔር ብሏልና ።
ወደገነት ተመልሶ ዕፀ ሕይወትን እንዳይበላ ገነት በምትገለባበጥ ሰይፍ መታጠርና መጠበቅ
ለዚህ ነው ይላል።
ዕፀ ሕይወት ምንድነው ?
ሐ) ዕፀ ሕይወት:- አዲስን ሕይወት የምታሰጥ አዳም ሳይበድል በገነት ቆይቶ ቢሆን ኖሮ 1000
(አንድ ሺ) ያህል ዓመት ከቆየ በኋላ ዕፀ ሕይወትን በልቶ ዳግመኛ ልጅ ሆኖ የኖረበት የነበረ
ምግብ ነው።
"ወደዚህ አትቅረብ አንተ የቆምህባት ሥፍራ የተቀደሰች መሬት ናት።" (ኦ.ዘፀ 3፥5)
ለሙሴ የተገለጠችው ይህች ምድር (መሬት) የእመቤታችን ምሣሌ ናት ይህች ምድርም
በእግዚአብሔር ዘንድ የተመረጠች ምድር ናት።
ከተረገመች ምድር መሀከል ሙሴ ጫማህን ከእግርህ አውልቅ የተባለላት ቅድስት ቦታ
(ምድር) መገኘት ከቻለች። ዕፀ በለስን በልታ ሞትንና ኃጢያትን ለማስተዋወቅ
ከተረገመችው ሔዋንም (ቀዳሚት ሔዋን) የተቀደሰችዋና የሔዋን ርግማን ወይም ጥንተ
አብሶ የማያውቃት ንጽህት ዘር እመቤታችን (ዳግሚት ሔዋን) መገኘቷ ለተቀደሰችው
ምድር ምሣሌ ናት።
ይህች ቅድስትና ንጽህት ምድር እመቤታችንም የልቦናችንን የኃጥያት ጫማ አውልቀን
ወደ እርሷ ብንቀርብና አማልጂን ልንላት የምትገባ እናት ሆና በቀራንዮ በእግረ መስቀሉ
ሥር በፀጋ የተሰጠችን እመቤት ናት።
ቅዱስ ቄርሎስ:- ሐመልማሉ ከነበልባሉ ሳይለወጥ ...
ሐመልማሉና ነበልባሉ :- የመለኮትና የሰው ምሣሌ ነው።
ቅድስት ምድር:- ደግሞ የእመቤታችን ምሣሌ ናት ፣ አማናዊ ሙሴ እየሱስ ክርስቶስም
የነገረ ድህነት አገልግሎቱን የጀመረው ገና በማዕዘነ ማርያም ሣለ ነው።
3. እግዚአብሔር በመልዓኩ አድሮ ባናገራት ቃል
አብርሃም እንኳ "እባርክሃለሁ" አለው እንጂ አንተ የተባረክህ ነህ አላለውም። ነገርግን የመባረክ
ተስፋ ግን አሳይቶታል። አልፎ ተርፎም "በዘርህ አህዛብ ሁሉ ይባረካሉ" በብሎታል።
እመቤታችንን ግን ከፍጥረት ሁሉ ለይቶ እንደመረጣት የምንረዳው "አንቺ የተባረክሽ ነሽ" ነው
ያላት። አብርሃምን ስለመባረኩ ኦ.ዘ.ፍ 12፥2 እመቤታችን ብሩክ ስለመሆኗ ሉቃ 1፥26-40
መንፈስ ቅዱስ ገና ወደ እመቤታችን ሳይመጣ እርሷ የተባረከች ናት።
…..ይቆየን….