Professional Documents
Culture Documents
᎘ ሂደት ፡- ሂደት ማለት እንደ ሜዳ፣ እንደ መንገድ፣ እንደ ቦይ ውሃ ሰተት ብሎ እንደሚሄድ ተጓዥ አንተም
ሳታቆም ወይም ሳታቋርጥ ምንም ነገር ሳይዝህ ሰተት ብለህ ሂድ ወይም አዚም ማለት ነው፡፡
᎕ ቅናት ፡- ቅናት በቅርጽነቱ ደጋን የመሰለና ከቀኝ ወደግራ የተሰመረ ወልጋዳ መስመር ይመስላል፡፡ ቅናት ማለት
በዜማው ቃል መጨረሻ ያለውን ቃል አንዱን ፊደል ይዘህ አንገትህን ወደላይ በማቅናትና ድምፅህን እንቅ
በማድረግ አዚም ማለት ነው፡፡
ይዘት፡- ይዘት ማለት በፍጥነት ከዜማው ዘር አንዱን የፊደል ሆሄ ያዝ በማድረግ አዚም ማለት ሲሆን ምንም ተጨማሪ
የሌለውን አንድ ብቻ የሆነን ነገር የሚያመለክት ነው፡፡
᎙ ቁርጥ፡- ቁርጥ ማለት ዜማውን በምታዜምበት ጊዜ ድምፅን በመጠኑ በመቀነስ ትንፋሽን ወደታች
በማመቅ እንደገናም ድምፅን በማጋነን አገጭን ወደፊት በማድረግ አዚም ማለት ነው፡፡
᎖ ጭረት ፡- ጭረት ማለት በዜማው መካከል ያለውን ንባብ አንዱን ፊደል ጎተት ወይም ሳብ አድርገህ
አንገትህን ወደላይ አቅንተህ አዚም ማለት ነው፡፡
፡ ርክርክ ፡- ርክርክ በቅርጹ ሲታይ የሚንጠባጠቡ ነገሮችን ያመለክታል ርክርክ ማለት ረጅም የሆነውን
᎑ ደረት፡- ደረት ማለት ደረትን ከፍ በማድረግ ፊት ለፊት ቀጥ ብሎ በጉልህ ድምፅ በጉሮሮ የሚዜም
ማለት ሲሆን ቅርጹ አንድ ተኝቶ የነበረ ሰው አፈፍ ብሎ ሲነሣ የሚያሳይ ይመስላል፡፡
ስ ድርስ ፡- ድርስ ማለት የቃሉ መጨረሻ የሆነውን አንዱን የፊደል ሆሄ ያዝ በማድረግና ድምፅን ወደ ኋላ በመሳብ
ር አንብር፡- አንብር ማለት አስቀምጥ አሳርፍ ማለት ሲሆን የአንዱን ዘር የመጨረሻ ሆሄ ያለምንም ተጨማሪ
ድምጽና ርክርክ በማስቀመጥ ወይም በማቆም አዚም ማለት ነው፡፡
᎔ ድፋት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት ከልዕልናው ወርዶ ወደዚህ ዓለም መምጣቱንና ከቅድስት ድንግል ማርያም ሰው መሆኑን ይገልጻል፡፡
᎘ ሂደት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ በዚህ ዓለም ከቦታ ቦታ እየተዘዋወረ በባሕር በየብስ እየተመላለሰ ማስተማሩን እንዲሁም አይሁድ አንድ ጊዜ ከሐና ወደ ቀያፋ፣ ከቀያፋ
ወደ ጲላጦስ፣ ከጲላጦስ ወደ ሄሮድስ፣ እየወሰዱ እንዲንገላታ ማድረጋቸውን የሚያስረዳ ነው፡፡
᎕ ቅናት፡- ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአምላክነቱ በሽተኞችን መፈወሱ ለምጻሞችን በማንጻቱ፣ ዕውራንን ማብራቱ፣ ሙታንን ማስነሣቱና ጎባጣ የሆኑትን ማቅናቱ ያስቀናቸው ካህናተ
አይሁድ ጠማማ በሆነ አእምሯቸው ቀንተው፣ ተመቅኝተው እንዲሰቀል ማድረጋቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
ይዘት ምሳሌነቱም ከጽድቅ በቀር ሌላ ኀጢአትና በደል ወይም ጥፋት የሌለበት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አይሁድ በትምህርቱና በተአምራቱ ቀንተው ከሳሽ መስካሪ ሆነው
በሐሰት ማስያዝያቸውንና ዓለምን በእጁ (በመዳፉ) የያዘ አምላክ መሆኑን ያስተምረናል፡፡
᎙ ቁርጥ ሲሆን ምሳሌነቱም አይሁድ በሐሰት መስክረው ጌታችንን ቢያስይዙትም መከራ ቢያደርሱበትም በሲዖል ተግዞ የነበረውን አዳምና ልጆቹን ለማዳን ቆርጦ መነሣቱንና በፈቃዱ
ራሱን ለመከራ አሳልፎ በመስጠት ነፍሱን ከሥጋው ለመለየት ቁርጥ ውሳኔ ማድረጉን ያመለክታል፡፡
᎖ ጭረት ፡- ምሳሌነቱም ራሰ ጠማማ ራሰ ጎባጣ በሆነ በትር /ዘንግ/ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መመታቱን ያመለክታል፡፡
᎑ ደረት፡- ፡ ምሳሌነቱም ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቅሎ ከሞተና ከተቀበረ በኋላ ሞትን ድል አድርጎ በራሱ ክብርና ሥልጣን ከመቃብር አፈፍ ብሎ በመነሣት ሁሉን
ከፈጸመ በኋላ በክብር በውዳሴ፣ በቅዳሴ በቅዱሳን መላእክት ታጅቦ ወደ ሰማይ ማረጉን ያስተምራል፡፡
ስ ድርስ ፡- ነቢያት ጌታ ይወርዳል፤ ይወለዳል፤ ይሞታል፣ ይነሣል፣ ወደ ሰማይ ያርጋል፣ ሲሉ የተናገሩት ትንቢትና የተቆጠረው ሱባዔ መድረሱን
ር አንብር፡- ጌታ የማዳን ሥራውን ሁሉ ጨርሶ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ በአብ ቀኝ መቀመጡን የሚያስረዳ ነው፡፡
የቅዱስ ያሬድ ለሀገራችን ያደረገው አስተዋጽኦ የጠለቀ ግንዛቤ አለመኖሩ ሥራዎቹ ፣
ከሀገርም አልፎ ለዓለም እንዳይተርፍ አድርጎታል፡፡