You are on page 1of 55

አዕማደ ምሥጢር

( ምሥጢረ ሥላሴ ወሥጋዌ )

1
ማውጫ
አርእስት ገጽ
1. መግቢያ........................................................................................................ 2
2. ሃይማኖት .................................................................................................... 3
2.1 ሃይማኖት እንዴት ተገኘ....................................................................... 4
2.2 ክርስትና ሃይማኖት.............................................................................. 4
2.3 ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና ሃይማኖት............................................... 5
2.4 እምነት.................................................................................................... 6
3. አዕማደ ምስጢር.......................................................................................... 7
3.1 አዕማደ ምሥጢር ለምን አዕማድ ለምንስ ምሥጢር ተባሉ? .......... 7
4. ምስጢረ ሥላሴ ............................................................................................ 8
4.1 የሥላሴ አንድነት.................................................................................... 9
4.2 የሥላሴ ሦስትነት.................................................................................... 9
4.2.1 የስም ሦስትነት........................................................................... 9
4.2.2 የአካል ሦስትነት ....................................................................... 10
4.2.3 የግብር ሦስትነት ........................................................................ 12
4.3 ምሥጢረ ሥላሴ በመጽሐፍ ቅዱስ....................................................... 13
4.4 የሥላሴ ምሳሌዎች................................................................................ 14
5. ምስጢረ ሥጋዌ ........................................................................................... 14
5.1 ምስጢረ-ተዋሕዶ.................................................................................. 16
5.1.1 የአካል ተዋህዶ.............................................................................. 16
5.1.2 የባህርይ ተዋህዶ........................................................................... 17
5.1.3 የግብር ተዋህዶ............................................................................ 17
5.1.4 የተዋህዶ ምሳሌዎች..................................................................... 18
5.2 ምሥጢረ- ቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ....................................................... 19
5.2.1 በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከበረ..................................................... 19
5.2.2 ቅብዓት............................................................................................ 19
5.2.3 ቀባ/ቀብዓ/...................................................................................... 20
5.2.4 አብ ቀባዒ(ቀቢ) ፣ ወልድ ተቀባዒ(ተቀቢ) ፣
መንፈስ ቅዱስ ቅብዕ(ቅብ).......................................................... 21
5.2.4.1 መሲህ............................................................................... 22
5.2.5 መቀባቱ ምን ጊዜ ነው ?................................................................ 27
5.2.5.1 ክርስቶስ.......................................................................... 28
5.2.5.2 ኢየሱስ.................................................................................. 29
5.2.6 መንፈስ ቅዱስ ለምን ቅብዕ ተባለ ?........................................... 33
5.2.7 የመንፈስ ቅዱስ ግብር.................................................................. 33
5.2.7.1 ማንፃት............................................................................... 34
5.2.7.2 መክፈል.............................................................................. 34
5.2.7.3 ማዋሐድ............................................................................. 34
5.2.7.4 መፍጠር................................................................................ 34
5.2.7.5 ቅብዕ መሆን........................................................................ 35
5.2.8 ምስጢረ ቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ በመጽሐፍ ቅዱስ..................... 36
5.2.9 ወልደ አብ....................................................................................... 38
5.2.9.1 ወልደ አብ በመጽሐፍ ቅዱስ............................................ 40
5.2.10 በተዋሕዶ ከበረ................................................................................ 41
6. ልደተ ክርስቶስ ታሕሳስ 29 ወይስ 28 ?....................................................... 43
6.1 ፈለገ ጥበብ መጽሔት 1993 ዓ/ም መግረሬ ፀር..................................... 44
6.2 ልደት ረቡዕና ዓርብ ቢውልስ መብላት ይቻላልን?..................................... 47
6.3 ታህሳስ 28 ለማክበር የሚጠቅሷቸው ምክንያቶች እና መልሶቻቸው....... 47
7. ጾመ ነቢያት የሚገባው ህዳር 19 ፣15 ወይስ 16 ? ....................................... 48
8. ጾመ ሐዋርያት ................................................................................................. 48
9. አንዲት ጥምቀት.............................................................................................. 50
10.የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ታሪክ
(አንዲት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
ቅባት ፣ ፀጋ እና ካራ ተብላ መከፋፈል ).......................................................... 51

የመጀመሪያ እትም ሰኔ 12 ቀን 2009 ዓ.ም


መግቢያ
የክርስትና ሃይማኖት ኦርቶዶክስ (ርትዕት ሃይማኖት) የሚል ስያሜ የተሰጠው በኒቅያ ጉባኤ በ318ቱ ሊቃውንት
በ325 ዓ/ም ሲሆን በ431 ዓ/ም ደግሞ ንስጥሮስ ሁለት አካል በማለቱ 200 ሊቃውንት በኤፌሶን ጉባኤ ንስጥሮስን
አውግዘው ተዋሕዶ የሚለውን ምሥጢር አንድ እንደሆነ ማለትም ሥጋ ከቃል ጋር ሲዋሐድ ሁለትነትን አጥፍቶ ያለመቀላቀል
በተዓቅቦ ፍፁም አንድ አካል፣አንድ ባሕርይ፣አንድ ግብር እንደሆነ ተንትነው አስቀምጠዋል፡፡ የንስጥሮስ ክህደት የተዋሐዶን
ምሥጢር የሚያጎድፍ በመሆኑ እንጅ የቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ምሥጢርንስ ያጎደፉ በኋላ የተነሱ ምሥጢሩ ያለገባቸው ሰዎች
ናቸው፡፡

በምስጢረ ሥጋዌ ላይ ያሉ ነሥአ (ወሰደ፣ተቀበለ)፣ እና ተወክፈ(ተሰጠ) እያልን ለሥግዉ ቃል የምንናገርለት


ምስጢር አለ፡፡ይህም ምስጢር እነሆ ለዘመናት ሊቃዉንተ ቤተክርስትያን ሲጨቃጨቁበትና ሲነታረኩበት እየተስተዋለ ነዉ፡፡
በዚሁ ጉዳይ መጻህፍትና ቅዱሳን አበዉ ተስማምተዉ እዉነቱን እዉነት ሀሰቱን ደግሞ ሀሰት ሲሉ ፤የዘመኑ አባቶች የተባሉ
ሰዎች ደግሞ መጻህፍትን በማጣመምና በመቆራረጥ፣ግሥን አለ ዘየዉ አለአገባቡ እየተረጎሙ የተለየ እንግዳ ትምህርትን
እያስተማሩ ቤተክርስትያንን እየበረዟት ነዉ፡፡በተለይ ደግሞ ከ1878 ዓ.ም ወዲህ በቤተክርስትያን ላይ ስር የሰደደ የነልዮን
እና ንስጥሮስ አስተምህሮ(ወልድ ቅብዕ በተዋሕዶ ከበረ የሚል አስተምህሮ) መጥቷል ፡፡

ስለሆነም ይህ አነስተኛ ጽሑፍ በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከበረ እና በተዋሕዶ ከበረ ያላቸውን ልዩነት እና መጽሐፍትን
መሰረት ያደረገው አስተምህሮ ምን እንደሆነ ይገልጻል ፤ ከምሥጢረ ሥጋዌ በተጨማሪም ስለበዓላት እና ሥርዓት አከባበር
ያለውን ልዩነት እና እውነታው ምን እንደሆነ ያብራራል ፤ ማለትም ልደተ ክርስቶስ ከአራት ዓመት አንዴ በዘመነ ዮሐንስ
በታህሳስ 28 ይከበራል ወይስ ምንጊዜም ታህሳስ 29 ? ፤ ጾመ ነቢያት መግቢያው ህዳር 16 ወይስ ህዳር 19 ? ፤ የጾመ
ሐዋርያት መግቢያው ከጰራቅሊጦስ ማግስት ነው ወይስ ጰራቅሊጦስ በዋለ ከአንድ ሳምንት በኋላ ? ፤ ዳግመኛ መጠመቅ
ያስፈልጋል ወይስ አያስፈልግም ? ለሚሉት ጥያቄዎች መልስ ይሰጣል ።

ለዚህም የመፅሐፍትን ማስረጃ ጥቅስ የግእዝ ቃል በዚህ ምልክት ተጠቅሶ ይገኛል ።

የአማርኛ ትርጉም ደግሞ በዚህኛው ምልክት ተጠቅሷል ።

ሃይማኖተ አበውን በብዛት ለማስረጃነት ተጠቅመናል ። ለምሳሌ ሃ. አበው ዘቄርሎስ 80 ፥ 1 ማለት ሃይማኖተ አበው
ዘቄርሎስ ምእራፍ 80 ቁጥር 1 ማለት ነው ። አንባብያን ሆይ ሃይማኖተ አበውን ስታነቡ ግእዝ ከአማርኛ እያመሳከራችሁ
ቢሆን ይመረጣል ። ምክንያቱም አንዳንድ ቃላትን አለዘየው አለአገባቡ ስለተረጎሟቸው ነው ። ለምሳሌ ተቀብዓ = ተቀባ ፣
ከበረ .... ተብሎ ሊተረጎም ሲገባ ተቀብዓ = ተዋሐደ ፣ በተዋሕዶ ከበረ እያሉ አለንባቡ አለስልቱ ይተረጉሙታልና ።
የዚህ አነስተኛ ጽሑፍ መዘጋጀት ዋና ዓላማ “ በእኔም የማይሰናከለው ሁሉ ብፁዕ ነው ” (ሉቃ 7 ፥ 23 ) እንዳለ ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙዎች የሚስቱትና የሚሰናከሉት ምሥጢረ ሥጋዌን ካለመረዳት የተነሳ በመሆኑ ከመሰናከልና ከመሳት
ለመዳን እንችል ዘንድ ሥለ ምሥጢረ ሥጋዌ የተወሰነ ፍንጭ ይኖረን ዘንድ ከማሰብ ነው ። ርዕሱም አዕማደ
ምሥጢር(ምሥጢረ ሥላሴ ወሥጋዌ ) የተባለበት ምክንያት ምሥጢረ ሥጋዌን ለመረዳት በመጀመሪያ ምሥጢረ ሥላሴን
መማር ፣ ማወቅ ያስፈልጋልና የጽሑፉም አትኩሮት ምሥጢረ ሥላሴ እና ምሥጢረ ሥጋዌ ላይ በመሆኑ እንዲሁም እነዚህ
ምሥጢራት የአዕማደ ምሥጢር ክፍል ስለሆኑ ነው ።

ከሙሉዓለም ጋሻው(ገብረ ማርያም)/ኦሪት/

2
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

አዕማደ ምሥጢር( ምሥጢረ ሥላሴ ወሥጋዌ )

¦Y¥ñT
¦Y¥ñT ›ም’ = አመነ ŸT>K¨< ¾Ó°´ Óe ¾}Ñ– c=J” ƒ`ÕT@¨<U TS” S¬S”
TKƒ ’¨<:: TS” c=vM u¯Ã’ YÒ ›Ã„ u°´’ YÒ (Ða) cU„' uMw ›ex'
ueT@ƒ QªdƒU ›ÉUÙ K=S[U\ƒ ¾TÉK¨<” u`kƒ (\p uSJ”) “ u`kƒ
(u[mp’ƒ) ÁK¨<”' ÃJ“M' ÃÅ[ÒM wKA SkuM ’¨<:: S¬S” TKƒ ÅÓV
ÃJ“M ÃÅ[ÒM wKA u°U’ƒ ¾}kuK<ƒ” X”Ç=J” X”Ç=Å[Ó X”Ç=ðçU }Óv^© ULi
SeÖƒ TKƒ ’¨<::eK²=I HÃT•ƒ ማለት TS”“ S¬S” ፤ የሚታመንበት ተስፋ
የሚደረግበት ፤ መከታና አለኝታ የሚሆንበት ማለት ነው :: ይች የተባረከች የተቀደሰች ሃይማኖት
የመጀመሪያም የመጨረሻም የሆነች ፈጣሪ የመሠረታት ተቀዳሚም ተከታይም የሌላት አንዲት
ለሁሉ የተሰጠች የጸናች ናት፡፡

ሀ. አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት ኤፌ 4÷5

ለ. ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።.
ይሁዳ 1÷3
ስለዚህም ሃይማኖት

h. y¸qbl#T nWÝ ×/ 1Ý12 (ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር


ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤
l. btSÍ y¸rÇT nWÝ :B 11Ý1 tSÍ SlMÂdRgW ngR y¸ÃrUG_ nW
/. bFQR y¸gl_ nWÝ kFQr XGz!xB/@RÂ kFQr sB: bmn= lsW b¯
b¥DrG y¸gl_ nW
m. b|‰ y¸tr¯M nWÝ KRST b¥mN BÒ y¸ÃöM ngR xYdlMÝ
Ãmn#TN b|‰ bmGl_ bsÑT ”L mñR mÒL nWÝÝ
\. XGz!xB/@RN dS yMÂs"bT nWÝ :B 11Ý6 Ãl XMnT XGz!xB/@RN dS
¥sßT xYÒLM

3
ሃይማኖት እንዴት ተገኘ?
btlÆ zmÂT Bz# sãC ¦Y¥ñT sW \‰> yçn nገR mçn#N l¥SrÄT Bz# _rêLÝÝ
kFR¦T DNU-@ ymÈ nW l¥lT YäK‰l#ÝÝ Xነz!H sãC ¦Y¥ñT sW \‰> nW s!l#
XGz!xB/@R ylM ¥l¬cW nWÝÝ lz!HM ¥Sr© s!-Qs# yqDä sãC ynb‰cW :WqT
WSN SlnbR knRs# b§Y yçnWN ngR h#l# lxND ¦YL Xys-# ñ„ XNJ fȶ ylM Y§l#ÝÝ
Yh#N XNJ y¦Y¥ñT MNŒÂ mg¾W yXGz!xB/@R mñR nWÝÝ ¦Y¥ñT h#l#N yf-r
lRs# xSg" yl@lW kzmÂT bðT ynbr h#l#N xúLæ y¸ñR yF_rT h#l# mUb! -ÆqE
XGz!xB/@R xl k¥lT YjM‰LÝÝ Slz!HM ¦Y¥ñT ytgßW wYM yñrW yh#l# fȶ
XGz!xB/@R bmñ„ nWÝÝ

ysW LJ kl@§W F_rT LöÂ kBé bL;#l Æ?RY bXGz!xB/@R xRxÃÂ xMúL
ytf-r bWS-# z§l¥êET yçnC y¥TfRS y¥TbsBS nFS ÃlCW bmçn# fȶWN
ymrÄT xµÆb!WN y¥wQ ymG²T y¥StÄdR [U yts-W F-#R nWÝÝ bz!H xµÆb!WN
y¥wQ ymG²T [U MKNÃT bMD‰êE ngéC §Y BÒ t-Mì XNÄYqR fȶWN
y¸ÃWQbT yh#l#N ngR MN+ b¥wQ XNÄ!ñR bm-n# bxGÆb# bm-qM z§l¥êET
yçnC nFs#N XNÄÃÈ kfȶW y¸gÂ"bT mNgD ts-WÝ YHM ¦Y¥ñT nWÝÝ Slz!H
s!ÂgR Yh#Ä bmL:Kt$ §Y 'lQÇúN xND g!z@ f{ä Slts- ¦Y¥ñT XNDTUdl#
XymkRk#êCh# X{F§Ch# zND GD çnB" ' ይሁዳ 1÷3 b¥lT ¦Y¥ñT kXGz!xB/@R yts-
mçn#N YgLÈLÝÝ

ክርስትና ሃይማኖት
¦Y¥ñT ytjmrW k|n F_rT UR nWÝÝ ¦Y¥ñT çcW F-#‰NM sW m§XKT
ÂcWÝÝ Yh#N XNJ ¦Y¥ñT bzmn xbW bzmn å¶T bzmn KRST ytlÃy mLK
xlWÝÝ zmn xbW b{/#F yts- ?G úYñR bLb#Â ?G BÒ bmm‰T xM§KN ÃmLk#
ynbrbT zmN nWÝÝ Slz!HM yzmn xbW ¦Y¥ñT fȶ mñ„N ¥mN lRs# mg²T BÒ
nbRÝÝ XGz!xB/@RM l¸ÃMn#T sãC b?LM b‰:Y bmgl_ mSê:¬cWN bmqbLÂ
”L k!ÄN bmS-T ¦Lãt$N YgL_ nbRÝÝ bzmn å¶T dGä YH ¦Y¥ñT ybl- ¯§ BlÖ
b{/#F bts- ?G tgl-ÝÝ XGz!xB/@RM bs! t‰‰ lXS‰x@L bXúT bdm bqNd
mlkT bn¯DÙD DM{ tgLõ ‰s#N xSrÄÝÝ Slz!HM bzmn å¶T ynbrW ¦Y¥ñT
yxML÷ |R›TN bm=mR yÃz nbRÝÝ

4
kz!H h#l# bh#ê§ GN yKRST ¦Y¥ñT b‰s# bL;#L XGz!xB/@R |UN lBî mgl_
ytm\rt ytgß çnÝÝ mZ 83(84)Ý7½ l#” 2Ý15 ¿ 1¾ -!ä 3Ý 16 Slz!HM yKRSTÂ
¦Y¥ñT

h bKRSèS x!ys#S çñ bFQR y¸\‰ XMnT nWÝ ( YHM ¥lT yKRST ¦Y¥ñT sWN
l¥ÄN b|U ytgl-WN xM§K yMÂmLKbT XRs# bz!H ›lM b|U btgl- g!z@
ÃúyNN ÃSt¥rNN b¯ MGÆR bFQR yMNgL_bT ¦Y¥ñT nW ¥lT nWÝ bKRSTÂ
¦Y¥ñT kfȶÃCN UR ÃlNM GNß#nT b”§T BÒ ytdgf bhúB BÒ Ãl úYçN bFQR
ytm\rt b”L k!ÄN y[Â nWÝÝ 'XNµCh# Bl# YH |Uü nW¿ ... lBz#ãC y¦-!xT
YQR¬ y¸fS yxÄ!S |Uü d» YH nWÝ' '|UüN y¸b§ d»N y¸-È bXn@ Yñ‰L
Xn@M bRs# Xñ‰lh#Ý' XNÄlÝÝ

l. bsW FLSFÂ wYM b|UÂ bdM ÃLçn bxM§K y¸gl_ nWÝ g@¬CN QÇúN
/êRÃTN bðl!ÕS qEúRÃ sãC ysWN LJ ¥N Yl#¬L BlÖ l-yqW _Ãq& QÇS ’@_éS
s!mLS 'xNt y?ÃW XGz!xB/@R LJ nH' BlÖ ymlsWN mLS g@¬CN YHNN |UÂ dM
xLgl-LHM ys¥† xÆt& XNJ BlÖ¬LÝÝ yQÇS ’@_éSNM NGGR ›lT BlÖ -Rè¬LÝÝ
Slz!HM yKRST ¦Y¥ñT x!ys#S KRSèSN bTKKL b¥wQ b¥mN §Y ytm\rt nWÝÝ

YHNN y¸gL-W bTKKL XNDNrÄW XNDÂMnW y¸ÃdRgW dGä ‰s# xM§K nWÝÝ

ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና ሃይማኖት


k§Y yKRST ¦Y¥ñT ymgl_ ¦Y¥ñT mçn#N xYtN ytgl-WM yF_r¬T h#l# g@¬
L;#l Æ?RY ‰s# XGz!xB/@R mçn#N tÂGrÂLÝÝ YHNN mgl_ bTKKL lmrÄTM ‰s#
XGz!xB/@R xU™ µLçn bqR b|UêE MRMር mrÄTÂ ¥wQ y¸ÒlW ylMÝÝ lz!HM nW
g@¬cN kxB bqR wLDN y¸ÃWQ ylM kwLDM bqR wLDM l!gL_lT k¸wD bqR
xBN y¸ÃWQ ylMÝ b¥lT yngrNÝÝ

bKRST ¦Y¥ñT WS_ ytgl-WN xM§K ¥NnT mrÄT tSñêcW Sltgl-W xM§K
ys-#TN yy‰úcWNM |UêE húB wd¯N bmtW bTKKl¾WÂ b:Wnt¾W mgl_ xMÂ
ÃlC b@tKRSTÃN åRèìKስ têHì b@tKRSTÃN TƧlCÝÝ

ስለዚህ በመጀመሪያ በአንፆኪያ የክርስቶስ ተከታዮች ክርስቲያን ሲባሉ ኖሩ ። ይህችን ሃይማኖት በ 325 ዓ.ም በኒቂያ
ጉባኤ አርዮስን ለማውገዝ 318 ሊቃውንት ተሰብስበው ከሁለት ሀገር ማለትም ከግሪክና ከግብፅ ቃሎች
በመጠቀም «ኦርቶ» እና « ዶክስ» የሚለውን «ኦርቶዶክስ » በማለት መጠሪያ ሰጥተዋታል ። ኦርቶ ማለት
ቀጥተኛ ፣TKKl¾ ፣Rt$: ሲሆን ዶክስ ማለት ደግሞ እምነት ማለት ነው ። የኢትዮጵያ ሊቃውንት በራሳቸው
ቋንቋ ርትዕት ሃይማኖት ብለዋታል ። ትርጓሜውም ቀጥተኛ ሃይማኖት ማለት ነው ፡በአጠቃላይ ምንም እኳን ቃሉ

5
የተለያየ ቢሆንም «ኦርቶዶክስ» = «ርቱዓነ ሃይማኖት» (ቀጥተኛ ሃይማኖት) የሚለው ትርጓሜ አንድ መሆኑን መገንዘብ
አለብን ፡፡

በኋላም በ 431 ዓ.ም በጉባኤ ኤፌሶን 200 ሊቃውንት ተሰብስበው የንስጥሮስን ባህል ኅድረት ማለትን ነቅፈው ፤
ንስጥሮስን አውግዘው ፤ተዋህዶ የሚለውን ምስጢር አንድነት እንደሆነ ማለትም ቃል ከሥጋ ጋር ሲዋሐድ ሁለትነት ጠፍቶ
ያለመቀላቀል ፍፁም አንድ አካል ፣አንድ ባህርይ ፣አንድ ግብር እንደሆነ በማስረዳት ኦርቶዶክስ በሚለው ላይ እንደ ድህረ ግንድ
ቅጥያ ጨምረው ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብለዋታል ። ስለዚህ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ማለት ቀጥተኛ የአንድነት እምነት ማለት ነው ከዚህ
በኋላ ሌላ የሃይማኖት ስም ጉባኤ ተሰርቶ አልተሰጠም ።

እምነት
XMnT lMN XNÁT BlW úYmrM„ mqbL ¥lT nWÝÝ XMnT xND sW bxND ngR
§Y wYM SlxND g#ÄY YçNL¾L YdrGL¾L b¥lT y¸ñrW tSÍ ¥lT nWÝÝ YHM
?l!ÂWN y¸ÃúRFbT RĬ g#LbT xgኝb¬lh# BlÖ y¸¬mNbT ngR h#l# nWÝÝ Slz!HM
XMnT Bz# xYnT nWÝÝ sW bBz# ngR l!ÃMN YC§LÝÝ bÈåT l!ÃMN YC§L¿ búYNS
l!ÃMN YC§L wztÝÝ lMúl@ QÇS ÔWlÖS bxt&Â bnbrbT g!z@ yxt&Â sãC
s!ÃmLk#êcW knb„T ngéC mµkL y¥Y¬wQ xM§K y¸L XNdnbrbT QÇS l#”S
{æLÂLÝÝ /ê 17Ý22(23ÝÝ kh#l# b§Y yçnW GN bxND XGz!xB/@R §Y Ãl XMnT nWÝÝ
YHM ¦Y¥ñT nWÝÝ lMúl@ b¥t& 15Ý28 §Y g@¬CN 'LË çY XMnT> ¬§Q nW
XNdwdD> YdrGL>' çT s@T LJê ¬¥ÆT úl g@¬CNM y\‰WN t›M‰T sM¬Â
xÄ"nt$N trD¬ wdRs# ÿË BlMnW LËN ÃDNL¾L B§ q$R_ tSÍ nb‰TÝÝ Bz#
tÈR¬Â lM xLs¥ s!§T ¿yWëCN MGB lb#ClÖC l!s-# xYgÆM s!§T h#l# ¬Gú
möyT yÒlCW ÃDNL¾L B§ knb‰T q$R_ tSÍ nWÝ ÃM XMnTê nWÝÝ Slz!H XMnT
xND sW L;#L XGz!xB/@R ÃdRGL¾L Yf{ML¾L Ys-¾L BlÖ tSÍ b¥DrG bBz#
WÈ WrDÂ CGR y¥YçN b¸mSl# ngéC WS_M b!çN XNk#êN bLb#Â {ÂT XNÄ!öY
y¸ÃdRgW ¦YL nWÝÝ

XNÄ!H ÃlW XMnT mqbL nW SNL sW lDµÑ MKNÃT úYš y‰s#N F_r¬êE WSNnT
bmrÄT b¥wQ WSNnT g#DlT yl@lbT yh#l# fȶ yçn XGz!xB/@RN |‰ãc$N
y¸qbLbT nWÝÝ Slz!HM XMnT

h. kS»T b§Y nWÝ bS»T ?êúèÒCN LNrÄW y¥NClWN XGz!xB/@RN yMNrÄbTÂ


yMÂg"bT mNgD nWÝÝ

l. kXWqT b§Y nWÝ XWqT yxXMé nWÝÝ xXMé dGä l!ÃWqW y¸ClW ngR WSN
nWÝÝ XMnT GN kz!H yxXMé WSNnT b§Y ÿì y¥YwsnWN ngR bmNfS QÇS m¶nT
YmrM‰LÝÝ

6
አዕማደ ምሥጢር
አዕማደ ምስጢር አዕማድ እና ምሥጢር ከሚሉት ሁለት ቃላት የተገኘ ሲሆን የቃላቱ ትርጉም ፦

1 አዕማድ ፦አምድ= ምሰሶ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ የእርባታ(የብዙ ቁጥር) ቃል ሲሆን ትርጉሙም ምሰሶዎች ማለት
ነው ።

2 ምስጢር ፦ድብቅ፣ ሽሽግ ፣ስውር ፣ለልብ ወዳጅ ካልሆነ በስተቀር የማይነገር ፣በአንድ ወይም በተወሰኑ ግለሰቦች
ማህበረሰቦች ብቻ የሚታወቅ ለባዕድ ለጠላት የማይነገር ማለት ነው።

አዕማደ ምሥጢር ለምን አዕማድ ለምንስ ምሥጢር ተባሉ?


1 አዕማድ የተባሉበት ምክንያት

 አምድ ምሰሶ ፣ገደፋ ነው ። በምሰሶ የተሰራ ቤት አይዛባም አይፈርስም ይፀናል ። እንደዚህም ሁሉ አምስቱን
አዕማደ ምሥጢር ጠንቅቆ ያወቀ ሃይማኖቱን አይክድም ፤ ለጣኦት አይሰግድም ፤ እምነቱን አይሸረሽርም ማለት
ነው ።ገላ 2÷9
እስመ እሙንቱ አዕማደ ህግ እንዳለ ሳዊሮስ በ ሃይማኖተ አበው
 አምድ ወይም ምሰሶ ተፈልጦ ፣ተጠርቦ ቤትን ያፀናል ። ሐዋርያት ሰማዕታትም በመጋዝ ተሰንጥቀው ፤ በሰይፍ
ተቆርጠው እና ሌሎችንም መከራዎች አሳልፍው አዕማድ ምሥጢርን አስተምረዋል ፤ ሃይማኖትን አፅንተዋል
ማለት ነው ።
 አንድም አዕማደ ምሥጢር ለክርስትና እምነት መሰረት በመሆናቸው ነው ።
2 ምሥጢር የተባሉበት ምክንያት

 አምስቱን ምሥጢራት በዐይኔ ካላሳያችሁኝ ፤ በእጀ ካልዳሰስኩኝ ብሎ መጠራጠር አይገባም ። በቃል ተምሮ
በልቦና ተመራምሮ አሜን ብሎ መቀበል ይገባል ለማለት ምሥጢር ብሏቸዋል ።
 ምሥጢር ለሌላ ወገን ለባዕድ እንደማይነገር ሁሉ አዕማደ ምሥጢርም ላላመኑ ፣ ላልተጠመቁ ለአህዛብ አይነገርም
አይገባቸውምና ።
 አንድም በሰው ልጅ ጠባብ አዕምሮ በስጋዊ ዕውቀት መርምረን ስለማንደርስባቸው ምሥጢር ይላቸዋል
 በሚታይ ፣ በሚዳሰስ እና በሚሰማ አገልግሎት የማይታይ ፣ የማይሰማና የማይዳሰስ ሰማያዊ ፀጋ ስለሚሰጥ ነው ።
አዕማደ ምሥጢር አምስት ናቸው እነርሱም

1 ምሥጢረ ሥላሴ ማቴ 28 ÷19

2 ምሥጢረ ሥጋዌ ዮሐ 1 ÷ 1 – 14

3 ምሥጢረ ጥምቀት ማር 16 ÷ 16 ,ዮሐ 3 ÷3

4 ምሥጢረ ቁርባን ዮሐ 6 ÷ 54

5 ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን ዮሐ 11 ÷ 25

7
ምሥጢረ ሥላሴ!
ሥላሴ ሠለሠ = ሦስት አደረገ ከሚለዉ የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን፣ መሠለስ ሥለሳ፣ሦስትነት ሦስት መሆን ማለት ነዉ፡፡
በቁሙ የሦስቱ አካላት ሥም ሆኖ ልዩ ሦስትነት ይባላል ፡፡ ልዩ ሦስትነት የተባለበት ምክንያት ሥላሴ አንድ ሲሆኑ ሦስት፣
ሦስት ሲሆኑ አንድ ናቸውና ። ምሥጢረ ሥላሴ አለምን ከነግሱ ምድርን ከነልብሱ የፈጠረ የሦስቱ አካላት የአንድ መለኮት
ሁናቴ ነዉ፡፡ሥላሴ አንድም ሦስትም ናቸው፡፡

 መቅድመ ኩሉ ንእመን በ፩ዱ አምላክ ዘቦቱ ፫ቱ አካላት አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ሥሉስ ዕሩይ እንዘ አሐዱ
ሠለስቱ ወእንዘ ሠለስቱ አሐዱ።(ሃ. አበው ባስልዮስ ዘቂሳርያ ፴ ፬ ÷ ፪)
 ከስራው ሁሉ አስቀድሞ ሦስት አካላት ባሉት በአንድ መለኮት እንመን በባህርይ አንድ በአካል ሦስት የሚሆኑ አብ
ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ሲሆኑ ሦስት ናቸው ፣ ሦስት ሲሆኑ አንድ ናቸው።(ሃ. አበው ባስልዮስ ዘቂሳርያ
34÷2)
 ይሤለሱ በአካላት ወይትወሐዱ በመለኮት(በአካል ሦስት ሲሆኑ በመለኮት አንድ ናቸው) ። (ሰለስቱ ምዕት በፀሎተ
ሃይማኖት)

8
የሥላሴ አንድነት
ሥላሴበባሕርይ፣በእግዚአብሔርነት፣በአምላክነት፣በፈጣሪነት፣በሥልጣን፣በፈቃድ፣በክብር፣በመሰገድ፣በሥምረት፣
በትዕዛዝ፣በህልዉና፣ በአነዋወር፣ በምልዓት፣ በርቀት፣በመለኮት፣ይህንን ዓለም በመፍጠር፣ በኋላም ይህንን ዓለም
በማሳለፍ….ይህንን በመሳሰሉት ከዚህም በሚበዛዉ ነገር ሁሉ አንድ ናቸዉ፡፡

 “አንዲት አገዛዝ፣አንዲት ፈቃድ አንዲት ኃይል አንዲት መንግስት አንዲት ስግደት አንዲት ምስጋና አንዲት ግብር
አንድ ጽንዕ ለሥላሴ ይገባል፤አንዲት ምክር አንዲት ስልጣን፣አንድ ክብር አንዲት ጽንዕ አንድ አኗኗር አንድ ፈቃድ
ለሥሉስ ቅዱስ ይገባል” (ሃ.አበዉ ዘአግናጥዮስ 11 ፥ 6) ዘዳ 6 ፥ 4 ፡ ኤፌ 4 ፥ 5
 “አንድ፡ሲሆኑ፡ሦስት ናቸዉ፤ሦስት ሲሆኑ፡በባሕርይ፤በመለኮት፤በክብር፤በመመስገን፤በሥልጣን፤ፍጡራንንም ሁሉ
በመፍጠር፤በፈቃድ፤ኃጢአትን ይቅር በማለት፤በማትለወጥ እዉቀት፤በረከትን በመስጠት አንድ ናቸዉ፡፡”
ሃ.አበዉ ዘአትናቴዎስ 28 ፥ 11
 “የሦስቱ አካላት መለኮት ፍጹም አንድነትን ልናዉቅ ይገባናል፤የእነርሱ የሚሆን አንድ መለኮትን አንድ በማድረግ
እናዋሕድ” (ሃ.አበዉ ባስልዮስ ዘቂሳርያ 32 ፥ 5)
 “ሥላሴ ክቡር ምስጉን ነዉ፤በአካላት ሦስት ናቸዉ፤መለኮት አንድ ነዉ ስልጣን አንድ ነዉ ፈቃድ አንድ ነዉ
የመለኮት ገንዘብ የሚሆን ባሕርይ አንድ ነዉ” (ሃ. አበዉ ዘአባ ገብርኤል 94 ፥ 2)

የሥላሴ ሦስትነት
ሥላሴ በስም ፣በአካል ፣በግብር ሦስት ናቸው ፡፡

፩ የስም ሦስትነት

የሥላሴ ሥማቸው አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ነው ። አብ አብ ቢባል እንጅ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አይባልም ፤
ወልድም ወልድ ቢባል እንጅ አብ መንፈስ ቅዱስ አይባልም ፤ መንፈስ ቅዱስም መንፈስ ቅዱስ ይባላል እንጅ አብ ወልድ
አይባልም ፡፡የአንዱ ሥም ለአንዱ አይሰጥም ።

 እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ


እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ
ከእናንተ ጋር ነኝ።(ማቴ 28፥19-20)
 “በከበርንባቸዉ በእሊህ ስሞች በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ እንመን ሰዉ የሆነ ቃል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
እንደ አዘዘን” (ሃ.አበዉ ባስልዮስ ዘቂሳርያ 32 ፥ 10)
 “ዳግመኛም በባሕርይ አንድ እንደሆኑ በሦስቱ እናምናለን፤እሊህም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ናቸዉ፤አብ የሚያድን
ነዉ፤ወልድም የሚያድን ነዉ፤መንፈስም የሚያድ ነዉ” (ሃ. አበዉ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ 28 ፥ 10)
 “በስም ሦስት ናቸዉ እንላለን አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ባሕርይ አንድ ሥልጣን፡በመለኮት አንድ በባሕርይ
አንድነት የጸኑ ሦስት አካላት ሲሆኑ ከሦስቱ አንዱ የሚበልጥ አንዱ የሚያንስ አይደለም በማይመረመር በአንድ ክብር
የተካከሉ ናቸዉ እንጅ፡፡” (ሃ.አበዉ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ 60 ፥ 7)
 “ከአካላትም አንዱም አንዱ ከባሕርያቸዉ አይለወጡም አብ ወልድን መንፈስ ቅዱስን ለመሆን አይለወጥም፡
ወልድም አብን መንፈስ ቅዱስን ለመሆን አይለወጥም፡መንፈስ ቅዱስም አብን ወልድን ለመሆን አይለወጥም”
(ሃ.አበዉ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ 60 ፥ 9)
 “አብም አብ ነዉ እንጅ ወልድን መንፈስ ቅዱስን አይደለም፡ወልድም ወልድ ነዉ እንጅ አብን መንፈስ ቅዱስን
አይደለም፡መንፈስ ቅዱስም መንፈስ ቅዱስን እንጅ አብን ወልድን አይደለም” “አብ ወልድን መንፈስ ቅዱስን

9
ወደመሆን አይለወጥም፤ወልድም አብን መንፈስ ቅዱስን ወደ መሆን አይለወጥም፡መንፈስ ቅዱስም አብን ወልድን
ወደ መሆን አይለወጥም፡፡እሊህ ሥስቱ አካላት በጌትነት በክብር ፍጹማን ናቸዉ፤በአንድ መለኮት አንድነትም አንድ
ናቸዉ”(ሃ.አበዉ ዘአግናጥዮስ 11 ፥ 7- 8)ዘፍ 18 ፥ 1 – 10 ፡ ዘዳ 32 ፥ 6 ፡ ምሳ 30 ፥ 4 ፡ ዳን 3 ፥ 25 ፡
ዮሐ 5 ፥ 37 ፡ ሐዋ 7 ፥ 55

፪ የአካል ሦስትነት

አብ የራሱ ሆነ ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ ፍጹም አካል አለዉ፤ወልድም የራሱ የሆነ ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ ፍጹም
አካል አለዉ፤መንፈስ ቅዱስም የራሱ የሆነ ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ ፍጹም አካል አለዉ፡፡ፍፁም የተባለበት ምክንያት
የሥላሴ አካል መልክ እና ገፅ እንደ ሰው ልጅ በእድሜ የሚለወጥ የሚታደስ ሳይሆን ለዘላለም አንድ አይነት ሆኖ የሚኖር
ስለሆነ ነው።የሰው ልጅ ግን በህፃንነት ፣ በወጣትነት ፣ በአረጋዊነት የተለያየ መልክ አለው።

 “አብ በአካሉ በገጹ በመልኩ ያለ ነዉና፤ወልድም እንዲሁ በአካሉ በገጹ በመልኩ ያለ ነዉና፤መንፈስ ቅዱስም
እንዲሁ በአካሉ በገጹ በመልኩ ያለ ነዉና ፤ እንደሰዉም አይወሰኑም፤አምላክነት ያላቸዉ አካላት ናቸዉና”
(ሃ.አበዉ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ 26 ፥ 3)
 “ይህ ሦስትነት በገጽ፤በአካል፤በመልክ ቀዳማዊ ነዉ አብን እናዉቀዋለን፤አብ በገጹ በአካሉ በመልኩ ያለ ፍጹም
የባሕርይ አምላክ እንደሆነ ነገር ግን አይመረመርም መጸሕፍት እንደመሰከሩ፡ወልድን እናዉቀዋለን ወልድ በገጹ
በአካሉ በመልኩ ያለ ፍጹም የባሕርይ አምላክ እንደሆነ፤ከአብ ባሕርይ የተገኘ ነዉ ስለአብ የተናገርነዉ ሁሉ ገንዘቡ
ነዉ፤ያለርሱ ሌላ አባትን አያዉቅም፤ከሦስቱ አካል አንዱ አካል በአካሉ በመልኩ በሁሉ ፍጹም ነዉ፡፡መንፈስ
ቅዱስን እናዉቀዋለን መንፈስ ቅዱስ እንደ አብ እንደ ወልድ እንደ ባሕርያቸዉ ገናንነት በገጹ በአካሉ በመልኩ ያለ
ፍጹም የባሕርይ አምላክ እንደሆነ” (ሃ.አበዉ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ 28 ፥ 12-14)
 “ከሐዲዎች የሰባልዮስ ወገኖች እንደሚናገሩት አንድ አካል አይደለም፤አንድ መለኮት ሦስት አካላት ያሉት ነዉ እንጅ
አብ አብ ነዉና፡ወልድም ወልድ ነዉና መንፈስ ቅዱስም መንፈስ ቅዱስ ነዉና፡፡አብ ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ
ተለይቶ አንዲት ሰዓት እንደ ዓይን ጥቅሻ ያህል ስንኳ አልነበረም፡ሁልጊዜ ከእነርሱ ጋር የነበረ የሚኖር ነዉ እንጅ፡፡”
(ሃ.አበዉ ባስልዮስ ዘቂሳርያ 34 ፥ 3 – 4)
 “እኛስ ሦስቱ በሦስትነት እንዳሉ እናምናለን ። ሦስትነታቸዉም በባሕርይ ፣ በመለኮት አይደለም በተለዩ አካላት ነዉ
እንጅ፤ክህደቱ የጸና ስሙ የከፋ አርዮስ እንደሚታመናቸዉ አረማዉያን እንደሚያመልኳቸዉ ብዙ አማልክት አሉ
ከማለት ፈጽመን እንራቅ ዳግመኛም ጽኑዓን አካላት በየራሳቸዉ እንዳሉ እናምናለን”
(ሃ. አበዉ ቴወዶስዮስ ዘአንፆኪያ 92 ፥ 4)
 “የፈጣሪያችን የእግዚአብሔርን የባሕርዩን አንድነት በፍጹም ገጽ በፍጹም መልክ የአካሉን ሦስትነት እንዲህ
እንመን” (ሃ.አበዉ ባስልዮስ ዘቂሳርያ 32 ፥ 7)
 “ዳግመኛም በየስማቸዉ በየገጻቸዉ ሦስቱን አካላት እንወቅ፡ከመለኮት ባሕርይ የተለየ አካል የለም፡በአካላትም
በማይመረመር ክብር መለያየት የለም፤የሦስቱ ሥልጣን፡የሦስቱ ፈቃድ አንድ ነዉ እንጅ”
(ሃ.አበዉ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ 60 ፥ 5)
 “በአካላት ሦስት ህላዌ፤በመለኮት አንድ ህላዌ ናቸዉ ሃማኖታችን ይህ ነዉ ሐዋርያት በሰበሰቧት በቅድስት
ቤተክርስትን ያገኘነዉ ድኅነታችን ይህ ነዉ” (ሃ.አበዉ ዘባስልዮስ 34 ፥ 22)

10
11
፫ የግብር ሦስትነት
የአብ ግብሩ መውለድና ማሥረጽ ነዉ ። የወልድ ግብሩ መወለድ ነዉ ፤የሚወለደውም ከአብ ነው ። የመንፈስ ቅዱስ
ግብሩ መሥረጽ(መዉጣት) እስትንፋስ፣ሕይወት መሆን ነዉ ፤ የሚሰርጸውም ከአብ ነው ፡፡ ስለሆነም አብ ቢወልድና
ቢያሠርጽ እንጅ እንደ ወልድ አይወለድም ፤ እንደመንፈስ ቅዱስም አይሠርጽም ። ወልድም ቢወለድ እንጅ እንደ አብ
አይወልድም አያሰርፅም ፤ እንደመንፈስ ቅዱስ አይሠርጽም ።መንፈስ ቅዱስም ቢሠርጽ ፣ እስትንፋስ ፣ ሕይወት ቢሆን እንጅ
እንደ አብ አይወልድም ፤ እንደ ወልድም አይወለድም፡፡አብ ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስ ልባቸዉ ነዉ፤ወልድ ለአብና ለመንፈስ
ቅዱስ ቃላቸዉ ነዉ፤መንፈስ ቅዱስ ለአብና ለወልድ እስትንፋሳቸዉ የባሕርይ ሕይወታቸዉ ነዉ፡፡ስለሆነም ቅድስት ሥላሴ
በአብ ልብነት ያስባሉ በወልድ ቃልነት ይናገራሉ በመንፈስ ቅዱስ ሕይወትነት ሕያዋን ሆነዉ ይኖራሉ፡፡

 “ለአብ የአብነት ስም የአባትነት ክብር አለዉ፤ለወልድም በባሕርይ ክብሩ ከአብ ሳያንስ የልጅነት ስም የልጅነት ክብር
አለዉ፤መንፈስ ቅዱስም እንዲህ በክብር አይለይም ፤ ነገር ግን ተለዉጦ አብ ወልድ አይባልም፤በዚህ ጊዜ ተገኘ
አይባልም፤በመለኮት እንደ አብ እንደ ወልድ ነዉ አንጅ ፤ እስትንፋሳቸዉ ነዉና ፡ሥስቱም ትክክል ናቸዉና”
(ሃ.አበዉ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ 60 ፥ 3)
 “ጽኑዓን አካላት በየራሳቸዉ እንዳሉ እናምናለን፤የአብ አካል ወላዲ የወልድ አካል ተወላዲ መንፈስ ቅዱስ አካል
ሠራፂ ነዉና” (ሃ.አበዉ ዘቴዎዶስዮስ ዘአንፆኪያ 92 ፥ 4)
 “በአብ ወላዲነት አሥራፂነት መለኮት አንድ እንዲሆን፡ሃይማኖትን እንመን፤ወልድ ከአብ ተወልዶአልና መንፈስ
ቅዱስም ከአብ ተገኝቷልና፡አብ ከወልድ ወልድም ከመንፈስ ቅዱስ ሳይቀድም ወልድ ከአብ በመወለዱ፡መንፈስ
ቅዱስም ከአብ በመሥረጹ የፈጣሪያችን የሦስትነቱ መለኮት አንድ ነዉ” (ሃ.አበዉ ባስልዮስ ዘቂሳርያ 32 ፥ 6)
 “ዳግመኛም መንፈስ ቅዱስ ከእግዚአብሔር አብ ተላከልን፡ያልተወለደ አብን ከአብ የተወለደ ወልድ ነዉ ሊሉት
አይገባም፤የተወለደ ወልድና ያልተወለደ የአብ ግብሩ አንድ አይደለምና፤በአወላለድ ስራ አንዱ ከአንዱ ልዩ ነዉ
እንጅ፡፡ጽኑ ከሀሊ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለዉ ወልድ ከአንድ እግዚአብሔር አብ ተወልዶአልና እርሱም በመለኮት
ከአብ ጋር አንድነዉና፡መለኮት የማይከፈል አንድ ሲሆን ሥላሴ በሦስት አካላት ፍጹም ነዉ”
(ሃ.አበዉ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ 25 ፥ 11-12)

 (ሃ. አበዉ ዘዲዮናስዮስ 99 ፥ 2)

12
 (ሃ.አበዉ ዘዲናስዮስ 99 ፥ 6 – 8)

ምሥጢረ ሥላሴ በመጽሐፍ ቅዱስ፦

 ዘፍ 1፥26 እግዚአብሔርም አለ፦ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ
ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ።
 ዘፍ 3፥22 እግዚአብሔር አምላክም አለ፦ እነሆ አዳም መልካምንና ክፉን ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ፤
አሁንም እጁን እንዳይዘረጋ፥ ደግሞም ከሕይወት ዛፍ ወስዶ እንዳይበላ፥ ለዘላለምም ሕያው ሆኖ እንዳይኖር፤
 ዘፍ 11፥ 7 ኑ፥ እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው።
 ዘፍ 18 ፥2 – 22
 ዘፀ 3፥ 6 ደግሞም፦ እኔ የአባትህ አምላክ፥ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ
አለው። ሙሴም ወደ እግዚአብሔር ያይ ዘንድ ፈርቶአልና ፊቱን ሸፈነ።
 መዝ 32፥ 6 በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ፥ ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ

13
 ኢሳ 6፥3 አንዱም ለአንዱ፦ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ ምድር ሁሉ ከክብሩ
ተሞልታለች እያለ ይጮኽ ነበር።
 ማቴ 3፥17 እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።
 ማቴ 28፥ 19 እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥
ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም
ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።
 2 ቆሮ 13፥ 14 የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር
ይሁን። አሜን።
 1 ዮሐ 5፥7 መንፈስም እውነት ነውና የሚመሰክረው መንፈስ ነው።
 1 ጴጥ 1፥1 ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ጴጥሮስ፥ እግዚአብሔር አብ አስቀድሞ እንዳወቃቸው በመንፈስም
እንደሚቀደሱ፥ ይታዘዙና በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ይረጩ ዘንድ ለተመረጡት በጳንጦስና በገላትያ በቀጰዶቅያም
በእስያም በቢታንያም ለተበተኑ መጻተኞች፤ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።

የሥላሴ ምሳሌዎች ፦
1. እሳት ፦እሳት ፍህም ፣ ብርሃን ፣ ነበልባል አለው ። ፍህም የአብ ፣ ብርሃን የወልድ ፣ ነበልባል የመንፈስ ቅዱስ
ምሳሌ ነው ። ብርሃን እና ነበልባል ከፍህም እንደሚወጡ ሁሉ ወልድ ከአብ ተወልዷል መንፈስ ቅዱስ ከአብ
ወጥቷል ። እሳት ፍህም ፣ ብርሃን ፣ ነበልባል የተባሉ ሦስት ነገሮች ስላሉት ሦስት እሳት አይባልም አንድ እሳት
ይባላል እንጅ ። እንደዚህም ሁሉ ሥላሴ በስም፣በአካል ፣ በግብር ሦስት ቢሆኑ አንድ አምላክ ይባላል እንጅ ሦስት
አማልእክት አይባሉም ።
2. ፀሀይ ፦ ፀሀይ ክበብ ፣ ብርሃን ፣ ሙቀት አላት ። ክበብ የአብ ፣ ብርሃን የወልድ ፣ ሙቀት የመንፈስ ቅዱስ
ምሳሌ ነው ። ፀሀይ ክበብ ፣ ብርሃን ፣ ሙቀት ቢኖራትም አንድ ፀሀይ ትባላለች እንጅ ሦስት ፀሀይ አትባልም ።
እንደዚህም ሁሉ ሥላሴ በስም፣በአካል ፣ በግብር ሦስት ቢሆኑ አንድ አምላክ ይባላል እንጅ ሦስት አማልእክት
አይባሉም ።

ምሥጢረ ሥጋዌ!
ሥጋዌ ሥጋነት ሥግና ሥጋ መኾን፡ ማለት ሲሆን ቀዳማዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ እጸበለስን በልቶ ከገነት ወጥቶ
ምድረ ፋይድ ገብቶ የነበረ አዳምን ያድነዉ ዘንድ አምስት ቀን ተኩል (5500ዘመን) ሲፈጸም ከልጅ ልጅህ ተወልጀ አድንሃለሁ
ብሎ ቃል ገብቶለት ነበርና ያንን ቃል ኪዳን የፈጸመበት ረቂቅ ምስጢር ነዉ፡፡ስለሆነም ይህ ከሶስቱ አካላት አንዱ አካል ወልድ
በተለየ አካሉ ሰዉ እንደሆነ፣ከእግዝእትነ ማርያም እንደተወለደ፣ ከመህጻናት(እንደ ህጻናት) በየጥቂቱ እንዳደገ፣30 ዘመን
ሲሆነዉ በማሕጸነ ዮርዳኖስ(በዮርዳኖስ ወንዝ) በእደ ዮሐንስ(በዮሐንስ እጅ) እንደተጠመቀ፣ ወደገዳመ ቆሮንቶስ ሄዶ 40
መዓልት 40 ሌሊት እንደጾመ እንደ ጸለየ፤ሶስት አመት ከሶስት ወር ወንጌልን እንዳስተማረ፣ሰዉን ያድን ዘንድ በሰዉ
እንደተሰቀለ፣እንደሞተ፣እንደተነሳ፣ ከተነሳም በ40ኛዉ ቀኑ እንዳረገ እንዲሁም በዳግም ምጽዓት ዓለምን ያሳልፍና
ለእያንዳንዱ ዋጋዉን ይከፍል ዘንድ እንደሚመጣ የሚያስተምረን ምስጢር ነዉ ምሥጢረ ሥጋዌ፡፡

ስለምን ምስጢር አለዉ ቢሉ እነሆ ረቂቅ መለኮት ርቀቱን ሳይለቅ ግዙፍ ከሆነ ሥጋ ጋር ቢዋሐድ፤ሰማይና ምድር
የማይወስኑት የማይችሉትን አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያም በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ብትወስነዉ፤በአምላክነቱ
ሳይሰቀል በሥጋዉ ሲሰቀል፣በአምላክነቱ መከራን ሳይቀበል በሥጋዉ መከራን ሲቀበል፤በሥጋዉ መከራን ሲቀበል ከመለኮቱ
ፍጹም ሳይለይ እንደነበረ፣በአምላክነቱ ሳይሞት በሰዉነቱ ሞተ ብለን የምንናገርለት ይህ እንዴት ሆነ? እንዴትስ ሊሆን
ይችላል?በአይኔ ካላሳችሁኝ፣በእጄ ካላስዳሰሳችሁኝ ብለን በዘመኑ የሳይንስ ዉጤት በሆነዉ በቤተ ሙከራ የምናረጋግጠዉ
ሳይሆን በእምነት የምንቀበለዉና የምንኖርበት እዉነት ስለሆነ ምስጢር አለዉ፡፡
14
አመጣጡስ (ሰዉ አኳኋኑስ) እንዴት ነዉ ቢሉ በስድስተኛዉ ወር መልአኩ ገብርኤል የገሊላ ክፍል እፃ ወደምትሆን
ናዝሬት ወደ ምትባል አገር ከእግዚአብሔር ዘንድ ታዝዞ ሄደ። ከዳዊት ወገን ለተወለደ ዮሴፍ ለሚባል ሰዉ ወደታጨች
ድንግል፡፡(ሐተታ)ብዙ ገሊላ አለና ከዚያ ሲለይ ናዝሬት ወደ ምትባል ፡ብዙ ደናግል አሉና ከዚያ ሲለይ ዮሴፍ ለሚባል ሰዉ
ወደታጨች ፡ብዙ ዮሴፍ አለና ከዚያ ሲለየዉ ከዳዊት ወገን አለ፡፡ ይህችም ድንግል ብላቴና ስሟ ማርያም ትባላለች፡፡
መልአኩ እርሷ ወዳለችበት ቤት ገባ ። የቦታ፤ አንድም ባሕርዩን መሰለላት መስሎ ታያት፡፡ እግዚአብሔር ከሥጋሽ ሥጋ
ከነፍስሽ ነፍስ ነሥቶ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ይሆናልና ፡፡በትንቢተ ነቢያት በመላእክት ተልእኮ ደሽ ያለሽ ምልዕተ ክብር
ሆይ ደስ ይበልሽ አላት ። ከሴቶች ተለይተሸ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለብሽ ነሽ ፡፡

ማርያምም መልዓኩን አይታ ደነገጠች፡፡አንድም ሰምታ ደነገጠች ። እንዴት እንዲህ ያለ ሰላምታ እንደምን ይቀበላሉ
ብላ አስባ ተናገረች፡፡(ሐተታ) እናቴን ሔዋንን ያሳተ ሰይጣን ሊያስተኝ መጥቷል ብላ፡፡መልአኩም ማርያም ሆይ አትፍሪ
አላት፡፡(ሐተታ) ለመልአክ ፍርኃት አርቆ መናገር ልማድ ነዉና፡፡ኢትፍራህ ብእሴ ፍትወት ዳንኤል ኢትፍራህ ዘካርስ እንዲል፡
፡በእግዚአብሔር ዘንድ ባለሟልነትን አግኝተሻልና፡፡እነሆ ትጸንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ ፡፡
…(ኢሳ7፡14፤ሉቃ 2፡21) እርሱም አቢይ እግዚአብሔር ነዉ ፡፡የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል ፡፡

እግዚአብሔር አብ የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል ፡፡(ሐተታ) ይህማ የተነገረ ለሰሎሞን አይደል እንዴ ቢሉ
ለጊዜዉ(በወቅቱ፣በዛን ሰዓት) ለሰሎሞን ነዉ ለፍጻሜዉ ግን ለጌታ ነወና፡፡አንድም ሰሎሞን በግዘፍ በነገሰባቸዉ ጌታ በርቀት
ይነግስባቸዋልና፡፡አንድም የጌታ መንግስቱ መንበርከ እግዚኦ ለዓለመ ዓለም ብሎ በተናገረለት ሥልጣን ነዉና፡፡አንድም ስምዒ
ወለትየ ወአጽምዒ ብሎ መንበር አድርጎ በተናገረለት በምዕመናን ላይ ነዉና፡፡አንድም ነግሠ መባሉ ቅሉ በሥጋ ዳዊት ነዉና
ዲበ መንበረ ዳዊት ትፀንዕ መንግስቱ እንዲል፡፡ በያዕቆብ ወገን ለዘለዓለም ሠልጥኖ ይኖራል፡፡ለጌትነቱ ፍጻሜ የለዉም ፡፡

ወንድ ሳላዉቅ መጽነስ መውለድ እንደምን ይሆንልኛል፤ምድር ያለዘር ታፈራ ዘንድ ሴት ያለወንድ ትፀንስ ዘንድ እንዲህ
ያለ የምስራች ከማን አገኘኸዉ አለችዉ፡፡እንዲህ ማለቷ ነገሩን ሽታዉ ፈልጋዉ አይደለም፤ጥንቱን እንደምን ይኾንልኛል ነገሩን
አላደርገዉም ስትል እንጅ፡፡መልአኩም መለሰ፡፡ያንችማ ጽንስ መቼ እንደ ሌሎች ሴቶች ፅንስ ነዋ መንፈስ ቅዱስ ያድርብሻል፡፡
ኃይለ ልዑል ወልድ ሥጋሽን ይለብሳል፡አንድም መንፈስ ቅዱስ ያድርብሻል ኃይለ ልዑል ወልድ ከሦስቱ ግብራት
ይከለክልሻል። ካንች የሚወለደዉ ቅዱስ ፣ ቅዱስ ፣ ቅዱስ ተብለዉ ከሚመሰገኑ ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ ነዉ፡፡የልዑል
እግዚአብሔር ልጅ ይባላል፡፡

ከዘመዶችሽ ወገን የምትሆን ኤልሳቤጥ ስንኳ በፍጹም እርጅናዋ ልጅ አግኝታ ጸንሳለች፡፡(ሐተታ) ኤልሳቤጥ ስንኳ
ማለቱ ስለምን ነዉ ቢሉ እመቤታችን ምንም በድንግልና ቢሆን ሙቀት ልምላሜ አልተለያትም፡፡ኤልሳቤጥ ግን ምንም በዘር
በሩካቤ ቢሆን ሙቀት ልምላሜ(ልማደ አንእስት) ተለይቷት ነበርና፡፡ይህማ ሙቀት ልምላሜ ሳለ በድንግልና እንዲወልዱ፡
ሙቀት ልምላሜ ከተለየ በኋላ በዘር በሩካቤ እንዲወልዱ የሚያደርግ እርሱ አይደለምን?ብሎ መጽሐፍ ያለበትን ማጽናት
ልማድ ነዉና እንዲህ አለ፡፡አንድም ከዘመዶችሽ ወገን የምትሆን ኤልሳቤጥ በል፡፡ መካን ለሚሏት ለኤልሳቤጥ ከጸነሰች እነሆ
ይህ ስድስተኛ ወር ነዉ፡፡ሙቀት ልምላሜ ሳለ እንበለ ዘርእ(ያለ ዘር) እንዲወልዱ ቢያደርግ እግዚአብሔር የሚሳነዉ ነገር
የለምና መንፈስ ቅዱስ በአንች ላይ ይመጣል ላለዉ፡፡አንድም ሙቀት ልምላሜ ከተለየ በኋላ በዘር በሩካቤ እንዲወልዱ
ቢያደርግ የሚሳነዉ ነገር የለምና እነሆ ኤልሳቤጥ ላለዉ ነዉ፡፡እንዲህ ባላት ጊዜ እመቤታችን ለመልአኩ የእግዚአብሔር
ገረዱ እነሆ አለሁ እንዳልክ ይሁንልኝ አለችዉ፡፡በዚህ ጊዜ ቃሏን ምክንያት አድርጎ አካላዊ ቃል በማኅፀኗ አደረ፡፡”
ሉቃስ 1 ፥ 26-38 (አንድምታ ትርጓሜ)

 “በኋላ ዘመንም ከሦስቱ አካላት አንዱ ጥንት የሌለዉ የእግዚአብሔር አብ ቃል ማንም ግድ ሳይለዉ በራሱ በአብ
በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ሰዉ ሆነ፤በአርያም ካሉ መላእክት ማንም ሰዉ መሆኑን አላወቀም፤ከአባትና ከእናት
(ከኢያቄም ከሐና) በተወለደች በቅድስት ድንግል ማርያም ማሕጸን አደረ” ሃ.አበዉ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ 60 ፥ 11
 “ከእናቱ በድንግልና ተወልዶ ወደዚህ ዓለም ገባ በመወለዱም ድንግልናዋ አልተለወጠም፤የወሰነችዉ የድንግል
ማሕጸን አልተለወጠም እንደ ቀደመዉ አጸናት እንጅ” (ሃ.አበዉ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ 61 ፥ 6)

15
 “ይህ እግዚአብሔርን በመልክ የሚመስለዉ በባሕርይ የሚተካከለዉ ሲሆን ቃል ስለእኛ በሥጋ የታየዉ መታየት
ነዉ” (ሃ.አበዉ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ 35 ፥ 11)
 “እግዚአብሔር አብን በመልክ የሚመስለዉ በባሕርይ የሚተካከለዉ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰዉ የሆነበትን ሥራ
በልቡናችሁ ዕወቁ ሽቶ ፣ ቀምቶ ከእግዚአብሔር ጋር የተካከለ አይደለም፤ራሱን አዋርዶ ሰዉ ኾኖ የሰዉ ባሕርይን
ተዋሕዶ ነዉ እንጅ” (ሃ.አበዉ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ 35 ፥ 30)ፊልጵ 2 ፥ 5 - 8
 “የማይለወጥ ንጹህ ቃል የሚለወጥ የሰዉን ባሕርይ ተዋሐደ የሰዉንም ሥራ ገንዘብ አደረገ፡ነፍሱን ከሥጋዉ
እስከመለየት ደርሶ ትሕትናን አብዝቶ ሠራ፡፡በነፍስ በሥጋ የሚፈርድ እርሱን ይሙት በቃ ወደሚፈረድበት አደባባይ
አወጡት ሊቃነ መላእክትን ሁሉ ፈጥሮ የሚገዛ እርሱ በኃጥአን እጅ ተያዘ ሕይወት እርሱ ሞተ”
(ሃ.አበዉ ዘጎርጎርዮስ ዘኑሲስ 35 ፥ 33-34)መዝ 11(12) ፥ 6 ፡ፊልጵ 2 ፥ 8 ፡ማቴ 17 ፥ 22 ፡ ዕብ 2 ፥ 5 - 10

ይች የተቀደሰች የቀናች ሃይማኖት የሁለት ምስጢር ባለቤት በመሆን « ቃል ሥጋ ኮነ ወኀደረ ላዕሌነ፡ ዮሐ 1፥14»
የሚለውን መሠረት አድርጋ የኖረች አምድ ናት፡፡በምስጢረ ሥጋዌ ላይ ሁለት የማይነጣጠሉ የማይለያዩ ምስጢራት አሉ
እነርሱም፡-ምስጢረ ተዋሕዶ እና ምስጢረ ቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ናቸዉ፡፡እነዚህንም ምሥጢራት ኦርቶደክስ ከምን አግኝታ
ታስምራለች ቢሉ!

 ሲቀባም ሲዋሐድም አንድ ጊዜ ነዉ ፡፡ከመ ቅጽበተ ዓይን እለሰ የአምኑ ርቱዓ ይሜህሩ ከመ ተቀብዓ ቃል በሥጋሁ
ወእምአመ ኮነ ቃል ሥጋ አሜሃ አስተርአየ በመንፈስ ቅዱስ እንዲል፡፡” ማቴ1፡16 (አንድምታ)፡፡
 “መንክረ ገብረ ወልደ እግዚአብሔር ዉስተ ከርሰ እሙ እስመ ፈጸመ ሥርዓተ ተዋሕዶ ወቅብዓት ምዕረ ከመ
ቅጽበተ ዓይን” ድርሳን ዘቅዱስ አውሳብዮስ፡፡
 የእግዚአብሔር ልጅ በእናቱ ማሕጸን ድንቅ ነገርን አደረገ የተዋሕዶን (የአንድነትን) እና የቅብዓትን ነገር እንደ ዓይን
ቅጽበት አንድ ጊዜ ፈጽሟልና ። ድርሳን ዘቅዱስ አውሳብዮስ

፩.ምስጢረ-ተዋሕዶ
ተዋሕዶ ማለት ተወሐደ = አንድ ሆነ ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ከሁለት ነገር ወደ አንድ ነገር
ያለመጠቅለል አንድ መሆን ማለት ነው፡፡ በምሥጢረ ተዋሕዶ ግን ከሁለት አካል አንድ አካል፤ከሁለት ባሕርይ አንድ
ባሕርይ፤ከሁለት ግብር አንድ ግብር፤አንዱ አንዱን ሳያጠፋው ሳይለውጠው ያለመደመር ፣ ያለመቀነስ፣ ያለመጨመር ፣
ያለመበላለጥ፣ ያለመተናነስ ፣ያለመቀላቀል ፣ ያለመደራረብ በተዓቅቦ(በመጠባበቅ) አንድ መሆን ማለት ነው፡፡ ይኸውም
የመለኮትና የሥጋ ውሕደት ነው፡፡ ይህም ሲባል መለኮት ወደ ሥጋነት ተለወጠ ወይም ሥጋ ወደ መለኮትነት ተለወጠ ማለት
ሳይሆን ሁለትነትን አጥፍቶ ፍፁም አንድ አካል፣አንድ ባሕርይ አንድ ግብር ሆነ ማለት ነው፡፡እግዚአብሔር ወልድ ከሰማየ
ሰማያት ወርዶ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ያንን የነሳውን ሥጋ ተዋህዶ
ተወለደ ።

መለኮት ከሥጋ ፤ ሥጋ ከመለኮት በሦስት ነገር ተዋህዷል። እነርሱም ፦

1) በአካል
2) በባህርይ
3) በግብር ናቸው

1) የአካል ተዋህዶ
የመለኮት አካል ረቂቅ ፣ ምሉዕ(የማይወሰን፣ ሁሉም ቦታ ያለ ፣ ሁሉን ቻይ) ፣ ስፉህ(ሰፊ) ነው ። የሥጋ አካል ግዙፍ ፣
ውሱን ፣ጸቢብ(ጠባብ) ነው ። ስለዚህ ከተዋህዶ በፊት አካለ ሥጋና አካለ መለኮት ሁለት አካላት ነበሩ ። መለኮት ከሥጋ

16
ቢወሐድ ምላቱን ፣ ርቀቱን ፣ ስፋቱን ሳይለቅ ግዙፍ ፣ ውሱን ፣ ጸቢብ ሆነ ።ሥጋም ከመለኮት ቢወሐድ ግዘፉን ፣
ውሱንነቱን ፣ ጸቢብነቱን ሳይለቅ ረቂቅ ፣ምሉዕ ፣ ስፉህ ሆነ ። መለኮት ከሥጋ ፣ ሥጋ ከመለኮት በተወሐደ ጊዜ ከሁለት
አካል አንድ አካል ሆነ ማለት ነው።

2) የባህርይ ተዋህዶ
የመለኮት ባህርይ ይህ ነው ተብሎ አይታወቅም አይመረመርም ። የሥጋ ባህርይ ደግሞ ውሃ ፣ እሳት ፣ ነፋስ ፣
መሬት ነው ተብሎ ይነገራል ፤ይታወቃል ፤ ይመረመራል ። ስለዚህ መለኮትና ሥጋ ከተዋህዶ በፊት ሁለት ባህርይ
ነበራቸው ። መለኮት ከሥጋ ጋር ሲወሐድ የመለኮት ባህርዩ ሳይመረመር በሥጋ ርስት ባህርዩ ውሃ ፣ እሳት ፣ ነፋስ ፣
መሬት ነው ተብሎ ታወቀ ፣ተነገረ ፣ ተመረመረ ። ሥጋም ከመለኮት ጋር ሲወሐድ ውሃ ፣ እሳት ፣ ነፋስ ፣ መሬት የሆነውን
ባህሪውን ሳይለቅ በመለኮት ርስት ባህርዩ የማይታወቅ ሆነ ። መለኮት ከሥጋ ፣ ሥጋ ከመለኮት በተወሐደ ጊዜ ከሁለት
ባህርይ አንድ ባህርይ ሆነ ማለት ነው።

3) የግብር ተዋህዶ
የመለኮት ግብሩ(ሥራው) መፍጠር ፣ መመለክ ፣ መስጠት ፣ ማወቅ ነው ። የሥጋ ግብሩ መፈጠር ፣ ማምለክ ፣
መቀበል ፣ አለማወቅ ነው ። ስለዚህ መለኮትና ሥጋ ከተዋህዶ በፊት ሁለት ግብር ነበራቸው ። ይህ ፍጡርነት ፣
ተወካፊነት(ተቀባይነት ) ርስቱ የሆነ ሥጋ ፈጣሪነት ፣ ወሃቢነት(መስጠት) ርስቱ ከሆነ መለኮት ጋር ሲወሐድ በመለኮት
ርስት ፈጣሪ ፣ ወሃቢ ፣አዋቂ አምላክ ሆነ ። ፈጣሪነት ፣ እውቀት ግብሩ የሆነ ቃል ፍጡርነት ፣ ተወካፊነት ርስቱ ከሆነ ሥጋ
ጋር ቢወሐድ ፈጣሪነቱን ፣ እውቀቱን ፣ ወሃቢነቱን ሳይለቅ በሥጋ ርስት ፍጡር ደኃራዊ ተወካፊ ሲሆን ጊዜ ሳይሻ
(ወዲያውኑ ፣ ከመ ቅጽበተ ዐይን) ህይወቱን መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ከአብ ቢወለድ በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ፈጣሪ ፣
ወሃቢ ፣ አዋቂ ፣ አምላክ ሆነ ።

 አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው እንዲሁ ደግሞ ለወልድ በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታልና። የሰው ልጅም
ስለ ሆነ ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን ሰጠው።ዮሐ 5፥ 26 ፟

ሥላሴ በባህርይ አንድ ናቸው ብንልም ሥጋን የተወሐደ ግን ወልድ ብቻ ነው ። አብ እና መንፈስ ቅዱስ ሥጋን
አልተወሐዱም ፤ ሰው አልሆኑም ። ለዚህም ምሳሌ ያስረዳል

1) የሰው ባህርይ አንድ ነው(፬ቱ ባህርያተ ሥጋ እና ፫ቱ ባህርያተ ነፍስ) አንድ ሰው ቢታመም ባህርዬ አንድ ነውና
ብሎ ሌላው አይታመምም ። እንደዚህም ሁሉ ወልድ ሰው ሲሆን ሥጋን ሲወሐድ ባህርዬ አንድ ነውና ብለው
አብና መንፈስ ቅዱስ ሰው አልሆኑም ።
2) የውሃ ባህርይ አንድ ነው ። ከአንድ ቦታ ያለን ውሃ በጻህል አድርጎ ቢያፈሉት ባህርዬ አንድ ነዉና ብሎ ሌላ ቦታ
ያለ ውሃ አብሮ አይፈላም ። እንደዚህም ሁሉ ወልድ ሰው ሲሆን ሥጋን ሲወሐድ ባህርዬ አንድ ነውና ብለው
አብና መንፈስ ቅዱስ ሰው አልሆኑም ።
3) የእሳት ባህርይ አንድ ነው ። አንድ ቦታ ያለን እሳት ከብረት ጋር አዋህዶ አንጠረኛ ሲቀጠቅጠው ባህርዬ አንድ
ነውና ብሎ ሌላው እሳት አብሮ አይቀጠቀጥም ። እንደዚህም ሁሉ ወልድ ሰው ሲሆን ሥጋን ሲወሐድ ባህርዬ
አንድ ነውና ብለው አብና መንፈስ ቅዱስ ሰው አልሆኑም ።

ተዋህዶ የመለኮት እና የሥጋ የሁለቱም ነው ። ይህም ማለት መለኮት ሰው ሆኖ ሰው አምላክ ሳይሆን አልቀረም ለማለት
ነው ። ሥጋ በቃል ርስት የማይራብ ፣የማይጠማ ፣የማይታመም ፣ የማይሞት ሲሆን ቃል በስጋነቱ ታመመ ፣ሞተ ፣ተቀበረ
ተባለ ።

በመለኮት እና በሥጋ ተዋህዶ ተጋውሮ(ጎረቤት መሆን) ፣ ውላጤ (መለወጥ፡ የቃና ዘገሊላ ውሃ ወደ ወይን፣የግብጽ
ውሃ ወደ ደም እንደተለወጠ ) ፣ ሚጠት(መመላለስ ፡እንደ በትረ ሙሴ ፣እንደ ሙሴ እጅ ) ፣ ቱሳሄ(መደባለቅ ፡እንደ
ማኪያቶ፣ እንደ ስፕሪስ) ፣ እና የመሳሰሉት የለበትም ።

17
 “የእግዚአብሔር ቃል ከባሕርይ መለኮቱ ሳይለወጥ እርሱን ተዋህዶ ሰው ሆነ የተዋሐደውን ያንን ሥጋም ከሰውነቱ
ባህርይ ሳይለወጥ አንድ አካል አንድ ባህርይ በመሆን ከእርሱ ጋር አንድ አደረገው፡፡” ሃ.አበው ዘአትናቴዎስ 30፥7
 “ሥጋ የሌለው ቃልና ሥጋ አንድ አካል አንድ ባሕርይ አንድ ግብር በመሆን እንደ ተዋሕዱ ተናገረ፡፡ ሰው የሆነ
አምላክ እሱ ብቻ ነው፡፡ፈፅሞ መለወጥ የሌለበት እርሱ ብቻ ነው፡፡”(ሃ. አበው ዘአትናቴዎስ 26፥9)
 “እግዚአብሔር ቃል ከሥጋ ጋር ተዋሕዷልና ከሥጋ ሁሉ ይልቅ ፈፅሞ የከበረ ሥጋን ገንዘቡ ባደረገ ጊዜ ፈፅሞ
መለወጥ የሌለበት አደረገው፡፡” (ሃ.አበው ዘአትናቴዎስ 31፥29)
 “እግዚአብሔር ቃል አንድ አካል ፤አንድ ባሕርይ ነው ብለን አስቀድመን እንደተናገርን እርሱስ ከሥጋ ጋር አንድ ነው
፡፡ እርሱ በእውነት የሁሉ ገዥ የሁሉ አምላክ ነው፡፡ ሥጋ ለቃል ተገዥ አይደለም ፡፡ ቃልም የሥጋ ገዥ አይደለም፡፡
ቃል ገዥ ሥጋ ተገዥ እንደሆነ ታምኖ ትናገሩ ዘንድ ይህ ፈፅሞ ክህደት ነው፡፡ ቃል ሥጋ ኮነ (ቃል ሥጋ ሆነ ዮሐ 1፥
14) ያለውንም መዘንጋት ነው፡፡” (ሃ. አበው ዘቄርሎስ 73፥39)
 “አብን በልብነት ፣ መንፈስ ቅዱስን በእስትንፋስነት(በሕይወትነት) የሚታወቁት መታወቅ መለየት የሌለበት አንድ
እንደሆነ መጠን ወልድም ቃልነት የሚታወቀው መታወቅ መለየት የሌለበት አንድ ነውና አብን በልብነት መንፈስ
ቅዱስን በእስትንፋስነት ገንዘብ ለማድረግ ሥጋ ቃልን ተዋሐደ፡፡” (ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 2 ገፅ 53)

 (ሃ.አበው ባስልዮስ ዘአንጾኪያ 96 ፥ 17)

በአጠቃላይ ምሥጢረ ተዋሕዶ ቃል መለኮታዊ ባሕርይ ሳይለቅ (ሳይቀይር) ከአዳም ሥጋ ጋር ሲዋሐድ የሥጋን
ባሕርይ ሳይለቅ ሁለትነትን አጥፍቶ አንዴት አንድ እንደሆነ የሚያስረዳ ረቂቅ ምሥጢር ነው፡፡ መለኮት ከሥጋ ሥጋ
ከመለኮት ጋር ሲዋሐድ ሁለትነት ጠፋ አንድነት ፀና ፡፡ ክርስቶስ በሥጋው ታመመ ሞተ የሚባለው በፈቃዱ እንጅ እንደሰው
ልጅ ሁሉ የግድ መራብ ፣ የግድ መጠማት ፣ የግድ መታመም ፣ የግድ መሞት የለበትም ። በሰውነቱ በመንፈስቅዱስ
የማይታመም የማይሞት ሆኗል ።

የተዋህዶ ምሳሌዎች ፦
1) የሰው ነፍስ እና ሥጋ ተዋህዶ ፦ የሰው ልጅ አካል ይህ ሥጋ ነው ይህ ነፍስ ነው ተብሎ መለየት
መከፋፈል እንደማይቻል ሁሉ የመለኮት እና የሥጋ ተዋህዶም ይህ ሥጋ ነው ይህ መለኮት ነው ብሎ
መክፈል አይቻልም ። ነፍስ ረቂቅ ስትሆን ከግዙፍ ሥጋ ጋር እንደተዋሐደች ሁሉ ረቂቅ መለኮትም
ከግዙፍ ሥጋ ጋር ተዋሕዷል ።

18
2) የእሳት እና ብረት ተዋህዶ ፦ ብረት ከእሳት ባስገቡት ጊዜ ብረትነቱን ሳይለቅ በብረቱ ቅርፅ መጠን
እሳት ይሆናል ። ሥጋም ባህሪውን ሳይለቅ ከእሳታዊ መለኮት ጋር ተዋሕዶ የባህርይ አምላክ ሆኖአል ።
ሃ.አበው ዘብንያሚ 89 ፥ 6 ፡ 89 ፥ 27

፪. ምሥጢረ- ቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ


ምሥጢረ-ቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ማለት ቃል ከሥጋ ጋር ሲዋሐድ ሁለትነትን አጥፍቶ ሥጋም የስጋን ባሕርይ ሳይለቅ
መለኮትም የማይመረመረውን የመለኮት ባሕርይ ሳይለቅ ሁለቱ በአንድ በሚዋሐዱበት ጊዜ የአዳምን ስጋ መንፈስ ቅዱስ
እንዴት እንዳነጻው፣ እንደከፈለው፣እንዳከበረው፣ እንደቀደሰው የሚያስረዳ ረቂቅ ምሥጢር ነው፡፡ ስለዚህ ምሥጢረ ቅብአት
መለኮት ከስጋ ስጋ ከመለኮት ጋር በተዋሐደ ጊዜ ወልድ በሰውነቱ በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከበረ የባሕርይ አምላክ የባሕርይ
ልጅ ሆነ ብሎ የሚያስረዳ በምሥጢረ ሥጋዌ ሥር ያለ ምሥጢር ነው ፡፡

በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከበረ ማለት ወልድ ሥጋን በተዋሐደ ጊዜ በሰውነቱ የባህርይ ህይወቱ
መንፈስ ቅዱስን በመላ ተቀብሎ ከአብ የባህርይ ልደት ተወለደ ማለት ነው ።

 “ዘአንገሦ ለሥጋ አዳም በመንፈስ ቅዱስ ወረስዮ ቅዱስ ወማህየዌ፡፡” (ሃ.አበው ዘእልመስጦአግአያ ፪ ፥ ፭)
 “በመንፋስ ቅዱስ ሕይወትነት የአዳምን ባህርይ ያከበረዉ የባሕርይ አምላክ ያደረገዉ እርሱ ነዉ፡፡”
(ሃ.አበው ዘአልመስጦአግአያ 2 ፥ 5)
 በእንተ ወልዱ ዘተወልደ ወወጽአ እምዘርአ ዳዊት በሥጋ ሰብ ወአርአየ ከመ ወልደ እግዚአብሔር ውእቱ በኃይሉ
ወበመንፈሱ ቅዱስ፡፡ (ሮሜ ፩ ፥ ፬)
 ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል
የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። (ሮሜ 1፥4)
 ተሠርዓ ወልደ እግዚአብሔር በኃይል ዝ ውእቱ ቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ፡፡(ተረፈ ቄርሎስ ምቅዋም ፰ ገፅ ፳ ፪ )
 ወቄርሎስኒ ይቤ በመጽሐፈ ድርሳኑ በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ተሰምየ ወልደ እግዚአብሔር ።(ድርሳነ ቄርሎስ )

በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆነ ማለት በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ሆነ ማለት ነው ። ምክንያቱም ኃይል


የተባለ መንፈስ ቅዱስ ነውና ።

 ወናሁ አነ እፌኑ ተስፋሁ ለአቡየ ላእሌክሙ ወአንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም እስከ ትለብሱ ኃይል እምአርያም
(ሉቃ ፳ ፬ ፥ ፵ ፱)
 እነሆም፥ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም
ከተማ ቆዩ። (ሉቃ 24 ፥ 49)

ሐዋርያት የጰራቅሊጦስ ዕለት የተቀበሉት መንፈስ ቅዱስ ሆኖ ሳለ ኃይል ያለው ኃይል የተባለ መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ
ነው ።

ቅብዓት ማለት ምሥጢራዊ ትርጉሙ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው


 “እምቅድመ ቅብዓትሰ ነበሩ መላዕክት ከመ ህፃናት በዝንጋዔ ወሶበ ተቀብዑ መልዓ ላዕሌሆሙ አእምሮ፣ ወኂሩት፣
ፍቅር ወትዕግሥት ትህትና ወየዋሃት፡፡(መጽሐፈ አክሲማሮስ ዘእሑድ ክፍል ፬ ፥ ፩)
 ይህም ቅብዓት ምንድን ነው ቢሉ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡የቅብዓት ጣዕሙ ምሥጢሩ ምንድን ነው ቢሉ መላእክት
ሳይቀቡ አእምሮ፣እውቀት እንደሌላቸው ህፃናት ነበሩ፤ከተቀበሉ በኋላ ግን አእምሮ፣ፍቅር ትህትና፣የዋህት፣ትዕግሥት

19
አደረባቸው ምስጋና እንደምንጭ እየፈሰሰ እንደጎርፍ እየጎረፈ ከአፋቸው የማይለይ ሆነ፡፡”መፅሐፈ አክሲማሮስ
ዘእሑድ ክፍል 4 ፥ 1
 ወእምዝ ተቀብዓ ቅብዓ ትፍስሕት ዘክርስቶስ ዘቦቱ ይነሥዑ ቅብዓ መንፈስ ቅዱስ ኩሎሙ አሕዛብ፡፡ (መፅሐፈ
አክሲማሮስ ዘሰሉስ ክፍል ፪ ፥ ፲ ፰)
 ይህስ ቅብዓት ምንድን ነው ቢሉ ቀድሞ ጌታችን ከባህርይ አባቱ በባህርይ ልጅነት ተወልዶ የባህርይ ልጅነት ያገኘበት
መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ዛሬ ህዝቡ አሕዛቡ ከሥላሴ የፀጋ ልጅነትን የሚወለዱበት ቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ይህ ነው፡፡
(መፅሐፈ አክሲማሮስ ዘማክሰኞ ክፍል 2 ፥ 18)
 ዘኢተወልደ እማይ ወእመንፈስ ቅዱስ ኢይክል በዊአ ውስተ- መንግሥተ እግዚአብሔር እስመ ዘተወልደ እምሥጋ
ሥጋ ውእቱ ወዘተወልደ እመንፈስ ቅዱስ ውእቱ፡፡ (መፅሐፈ አክሲማሮስ ዘሰሉስ ክፍል-2) ፡ ዮሐ3÷3-6
 ይህም ቅብዓት መንፈስ ቅዱስ ነው፤ለሁሉ ፀጋ ክብር መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ሲያጠይቅ ጌታችን ከረቂቅ የተወለደ
ረቂቅ ነው፤ከግዙፍ የተወለደ ግዙፍ ነው ሲል ከውሃ እናትነት፣ከመንፈስ ቅዱስ አባትነት ልጅነት ነስተው አህዛብ
አረማውያን ረቂቅ መንግስተ ሰማያትን እዲወረሱ ተፃፈ ፣ተነገረ ። (መፅሐፈ አክሲማሮስ ዘሰሉስ ክፍል-2)
ዮሐ3÷3-6
 ወአንትሙሰ ቅብዓት ብክሙ እምነ መንፈስ ቅዱስ ወተአምሩ ኩሎ ። (፩ ዮሐ ፪ ፥ ፳)
 እናንተም ከቅዱሱ ቅባት ተቀብላችኋል፥ ሁሉንም ታውቃላችሁ ። (1 ዮሐ 2 ፥20)
 ወአንትሙሰ ቅብዓት ብክሙ እንተ ነሣእክሙ እምኀቤሁ ወትነብር ኀቤክሙ ወኢትፈቅዱ መኑሂ ይምሃርክሙ አላ
መንፈሰ ዚአሁ ይሜህረክሙ በእንተ ኩሉ ወእሙን ውእቱ ወኢኮነ ሐሰተ ወበከመ ትምህርትክሙ ንበሩ ባቲ
(፩ ዮሐ ፪ ፥ ፳ ፯)
 እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን
የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥ እናንተንም
እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ።(1 ዮሐ 2 ፥27)

 ቀባ - መቀባት በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ 3 ዓይነት ነገር ያገለግላል …….:: ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ ተቀብቷል
(በመንፈስ ቅዱስ ተሞላ ሐዋ 10፥38):: ምዕመናን በመንፈስ ቅዱስ ይቀባሉ 2ኛቆሮ 1፥21-22፤ 1ኛዮሐ 2፥
22-27 ::<<መሲሕ>>በአረብ<<ክርስቶስ>>>በግሪክ ቋንቋዎች የተቀባ ማለትነው:: .........ቅብዓት/ቅባት/:-
ከልዩ ልዩ እንጨቶች ተቀምሞና ተነጥሮ የሚወጣ ፈሳሽ አይነት ገፅ 30፥22-32፣ የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌነው
1ኛዮሐ 2፥20- 27” (የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገፅ 90 1992 ዓ.ም እትም)

 ቀባ/ቀብዓ/ ለከከ፣ለቀለቀ፣ደለሰ ቅቤን:: የህፃንን ሕዋሳት ሜሮን አስነካ፣በራስ ላይ ዘይት አፈሰሰ፣


አከበረ፣ሾመ፣ ስልጣን፣ሀብት፣መብት፣ችሎት አሳደረ አደለ ሰጠ፤ ካህን ነቢይ ንጉስ አደረገ:: (አዲስ የአማርኛ
መዝገበ ቃላት ከደስታ ተክለ ወልድ ገጽ 1022” 1962 ዓ.ም እትም ፣ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ
ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሀዲስ ገፅ 780)
 ተቀብዓን ተዋሐደ እያሉ አለቋንቋው፣አለንባቡ፣አለስልቱ፣አላገባቡ ይፈቱታል፤ቀብዓና ተወሐደን ተመልከት ” አለቃ
ኪ/ወ/ክ/መዝ/ቃላት ገፅ 550::

ሐዋርያት በጽርአ ፅዮን የተቀበሉት ፣ እኛም በልጅነት ጥምቀት የምንቀበለው የፀጋ መንፈስ ቅዱስ ሆኖ ሳለ ዮሐንስ
በመልእክቱ (1 ዮሐ 2 ፥27 ) ቅባት ብሎ የተናገረው ቅባት ማለት መንፈስ ቅዱስ ማለት ስለሆነ ነው ።

በሌላ በኩል ቅብዓት ማለት ክብር ማለት ነው፡፡ክብርነቱም ለመለኮት አይደለም ለሥጋ ነው እንጅ፡፡

20
 “ወዘሂ ተብህለ ከመ ውእቱ ተሰብሐ እምአብ በአይ አምሳል ተሰብሐ እምአብ እንዘ ውእቱ እግዚአ ስብሐት
ወግብሩሂ ጥዩቅ ከመ ዝንቱ ነገር ይመስል ከመ ዘይብል ፍጡር ውእቱ ወኢተብህለ ዝንቱ ዘእንበለ ዳእሙ በእንተ
ሥርአተ ትስብእት ለሊሁ ይነሥእ ስብሐተ እምአብ በትስብእቱ እንዘ ለሊሁ እግዚእ ስቡህ በመለኮቱ ወለብዕለ
ህላዌ መለኮት ንህነ ንሬእዮ በልእልና ስብሐቲሁ ዘውቱ ላእለ ኩሎሙ ፍጡራን ወበአምጣነ ንዴተ ትስብእት
ዘነሥአ ይትበሐል ከመ ዉእቱ ተሰብሐ እም አብ ወዝንቱ ዓዲ ይትመሰል ዘተብህለ ከመ ውእቱ ነሥአ ስብሐተ
ወመንግስተ ወስልጣነ ላዕለ ኩሉ ነሢእሰ ይትበሃል በእንተ አቅመ ትስብእቱ………………….”
(ሃ.አበዉ ዘቄርሎስ ፸ ፱ ፥ ፸ ፬ - ፸ ፭)
 “ከአብ በክብር እንደተገለጠ የተነገረውም የክብር ባለቤት ሲሆን በምን ነገር ከአብ ተገለጠ ይባላል፤ ይህ ነገር ፍጡር
እንደሚመስል ነገሩ ግልፅ ነው ይህም ሰው ስለመሆኑ እንጅ ለሌላ አልተነገረም እርሱ የባህርይ አምላክ ሲሆን ሰው
በመሆኑ ከአብ ክብርን ገንዘብ ያደርጋል::የባህርየ መለኮትን ክብር ከፍጡራን ሁሉ በራቀ በልዑል ጌትነቱ እንዳለ እኛ
እናውቃለን የተዋህደው ስጋ ክብርን የሚሻ በመሆኑ መጠን ከአብ ክብርን ገንዘብ አደረገ ይባላል፤ ይህም ጌትነትን
መንግስትን በሁሉ ላይ ስልጣንን እርሱ ገንዘብ እንደ አደረገ የተነገረውን ይመስላል፤ ክብርን ገንዘብ አደረገ መባሉ ሰው
ስለመሆኑ ይነገራል፤ በመለኮቱ የክብር ባለቤት እንደሆነ ከአብ ጋርም እኩል ትክክል እንደሆነ ከአባቱ ልዑል ጌትነት በባህርየ
መለኮቱም አንድ ከሚሆንበት ግብሩም በምንም በምን ሕጸጽ እንደሌለበት እናውቃለን፤ አምነን አንድ የምንሆንበት ትምህርት
ይህ ነው:: ” ሃ.አበዉ ዘቄርሎስ 79 ፥-74-75

አብ ቀባዒ(ቀቢ) ፣ ወልድ ተቀባዒ(ተቀቢ) ፣ መንፈስ ቅዱስ ቅብዕ(ቅብ) ይባላሉ ።

 እስመ ብሂለ ክርስቶስ ይመርህ ኀበ አብ ቀባዒ ወኀበ ወልድ ተቀባዒ ወኀበ መንፈስ ቅዱስ ቅብዕ ።(ዮሐንስ
አፈወርቅ በድርሳኑ)
 እስመ ዝክረ ክርስቶስ ይመርህ ኀበ ፫ቱ አካላት ዝውእቱ አብ ቀባዒ ወወልድ ተቀባዒ ወመንፈስ ቅዱስ ቅብዕ
በእንተ ዘተቀብዓ ሥጋ ወልድ ። (ድርሳነ ቄርሎስ ገፅ 406 የብራና ፣ ኪርያኮስ)
 ወልድ በሥጋው ስለከበረ ክርስቶስ ሲጠራ ወደ ሦስቱ አካላት ይኧውም አብ ቀባዒ ወልድ ተቀባዒ መንፈስ ቅዱስ
ቅብዕ ይመራናልና ።(ድርሳነ ቄርሎስ ገፅ 406 የብራና ፣ ኪርያኮስ)
 አብ ቀባዒ ወወልድ ተቀባዒ ወመንፈስ ቅዱስ ቅብዕ(መጽሐፈ ዝክሪ ወጳውሊየብራና ገጽ 78/የትርጓሜ ሊቅ/)

21
አብ በልብ፣ወልድ በቃል፣መንፈስ ቅዱስ በእስትንፋስ ይመሰላሉ ብለናል ፡፡ ቅድመ ተዋሕዶ ወልድ (ቃል) በአብ
ልብነት ያስባል በመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስነት(ሕይወትነት) ሕያው ይሆናል፡፡ ቃል የተወሐደው ሥጋ ከአብ ልብን፣
ከመንፈስ ቅዱስ የባሕርይ ሕይወቱን ገንዘብ ቢያደርግ (በመንፈስ ቅዱስ ቢከብር) ተቀባ ተባለ፡፡ አብ ለወልድ በሥጋው
መንፈሱን ሊሰጠው ፈቃዱ ቢሆን ቀባው ተባለ፤ ቃል በሥጋው መንፈስ ቅዱስን ከአብ ቢቀበል ተቀባ ተባለ፤ መንፈስ
ቅዱስም ለቃል በሥጋ ርስት የባሕርይ ሕይወት ሊሆነው በመሰጠቱ ቅብዕ ተባለ (ዮሐንስ 5÷26፤መዝ 44÷7፣ ሐዋ
10÷38፣ድርሳነ ዘዮሐንስ አፈወርቅ፣ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሀዲስ ገፅ 780)
፡፡

ቀባዒው የባሕርይ አባቱ አብ ነው ፡፡

 ለምንት አንገለጉ አሕዛብ ወለሕዝብኒ ነበቡ ከንቶ ወተንሥኡ ነገስተ ምድር ወመላእክትኒ ተጋብኡ ምስሌሆሙ
ኅቡረ ላዕለ እግዚአብሔር ወላዕለ መሲሑ አማን አንገለጉ በዛቲ ሃገር ላዕለ ቅዱስ ወልድከ ኢየሱስ ዘቀባዕካሁ
ሄሮድስ ወጲላጦስ ጰንጤናዊ ምስለ ሕዝቢሆሙ ወሕዝበ እስራኤል ከመ ይግበሩ በከመ ሥርዓተ እዴከ ወምክርከ
ከመ ይኩን ።(ሐዋ ፬ ፥ ፳ ፭ - ፳ ፰)
 አሕዛብ ለምን አጕረመረሙ? ሕዝቡስ ከንቱን ነገር ለምን አሰቡ?የምድር ነገሥታት ተነሡ አለቆችም በጌታና
በተቀባው ላይ አብረው ተከማቹ ብለህ የተናገርህ አምላክ ነህ።በቀባኸው በቅዱሱ ብላቴናህ በኢየሱስ ላይ
ሄሮድስና ጴንጤናዊው ጲላጦስ ከአሕዛብና ከእስራኤል ሕዝብ ጋር፥ እጅህና አሳብህ እንዲሆን አስቀድመው
የወሰኑትን ሁሉ ሊፈጽሙ፥ በዚች ከተማ በእውነት ተሰበሰቡ።(ሐዋ 4 ፥ 25 – 28)
 በኢየሱስ ዘእምናዝሬት ዘቀብዖ እግዚአብሔር መንፈሰ ቅዱሰ ወኀይለ ወውእቱ መጽአ ወረድኦሙ ለእለ
ይትዔገሎሙ ሰይጣን እስመ እግዚአብሔር ምስሌሁ (ሐዋ ፲ ፥ ፴ ፰)
 እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባዉ” (ሐዋ10 ፥ 38)
 “አስመ እንከ ተቀብዐ ቅብዐ ትስብእት ዘእመንፈስ ቅዱስ በኀበ አግዚአብሔር አብ፡፡ (ተረፈ-ቄርሎስ ምቅዋም 8 ገጽ 49 ብራና
መጽሐፍ)”፡፡
 “በእግዚአብሔር አብ የደስታ ዘይት መንፈስ ቅዱስን እግዲህ ተቀብቷልና”(ተረፈ-ቄርሎስ ምቅዋም 8 ገጽ 49 ብራና
መጽሐፍ)”፡፡
አብ ቀባ ማለት ሰጠ ማለት ሲሆን ትርጉሙም ለወልድ በሰውነቱ የባህርይ ህይወቱ መንፈስ ቅዱስን ሊሰጠው ለአብ
ፈቃዱ ሆነ ማለት ነው ።

 “ወበከመ ለአብ ቦቱ ሕይወት ኀቤሁ ከማሁ ለወልድኒ ወሀቦ ህይወተ ከመ ይኩን ሕይወት ኀቤሁ ።ወወሀቦ ሥልጣነ
ከመ ይግበር ፍትሐ ወኩነኔ እስመ ወልደ እግዚአብሔር ወልደ እጓለ እመሕያው ውእቱ(ዮሐ ፭ ፥ ፳ ፮)
 አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው እንዲሁ ደግሞ ለወልድ በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታልና።የሰው ልጅም ስለ
ሆነ ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን ሰጠው። (ዮሐ 5 ፥ 26)

ተቀባዒው ሰው የሆነው ሥጋ የለበሰው ወልድ ነው ፡፡

 ላዕለ እግዚአብሔር ወላዕለ መሢሑ (መዝ ፪ ፥ ፪)


 የምድር ነገሥታት ተነሡ፥ አለቆችም በእግዚአብሔርና በመሢሑ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ። (መዝ 2፥2)

መሲህ ማለት ቅቡዕ (የተቀባ ) ማለት ነው ።


 ማስያስ በዕብራይስጥ፤ክርስቶስ በጽር (በግሪክ) ፤መሲሕ በአረብ፤ቅቡዕ በግዕዝ፤የተቀባ በአማረኛ ።(ዮሐ 1÷41
አንድምታ ትርጓሜ)

22
 “.......ለእግዚአብሔር የተለየ የተቀባ የሆነ የስሙ ትርጉም መሲህ የሆነ ክርስቶስ እስከ ተወለደ ድረስ በገሊላ
ነገስታት ዘንድ መሲህ ተብሎ መጠራት አልነበረም።ክርስቶስም መሲህም ናዝራዊም በማለት በአንድነት የተቀባ
ተባለ ። መሲህ የተቀባ ማለት ነው። ክርስቶስ የተባለ ኢየሱስ ተወለደ የተቀባ መባል በእርሱ ተፈፀመ። እነሆ
ናዝራዊ ኢየሱስ ቅባትን ተቀብቶ የመቀባትን መንግስት ተቀበለ አምላክ ሲሆን ስለሰውነቱም የመለኮትን ቅብዓት
ተቀብቶ ሰው ሆነ እግዚአብሔር ሰው ለመሆን ወረደ ሰውም እግዚአብሔር ለመሆን ከፍ ከፍ አለ ጳውሎስ
እግዚአብሔር ዓለምን ተወዳጀ እንዳለ ዳግመኛም የኃጢያትን ስጋ ለበሰ ያችንም ኃጢያት በስጋው ገዛት በ 2ኛቆሮ
5፥19 ። (መጽሐፈ ምስጢር 20 ፥ 40 – 41)
 መሲህ በዕብራይስጥ የተቀባ ማለት ነው ።ክርስቶስ ከሚለው የግሪኩ ቃል ጋር አንድ ነው ። …… ጊዜው ሲደርስም
እውነተኛውን መሲህ ጌታ ኢየሱስን ላከ ። (የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገፅ 32 ፣ 1992 ዓ.ም እትም)
 “ወአዉሥአ ወይቤሎሙ አንትሙ መኑ ትብሉኒ፡፡ወተሰጠዎ ጴጥሮስ አንተ ውእቱ መሢሑ ለእግዚአብሔር”
(ሉቃ 9 ፥ 20)
 እናንተ ማን ትሉኛላችሁ. ጴጥሮስ መለሰ አንተ ከእግዚአብሔር የተቀባሕ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ አለዉ (ሉቃ 9
፥ 20) (መሲህ ማለት የተቀባ መሆኑን ይገልፃል )

 መሲህ መሰሐ-ቀባ ከሚለው የግዕዝ ግስ የተገኘ/የወጣ/ ሲሆን መሲህ ማለት የተቀባ ፣ቅቡዕ የተሾመ ወይም የነገሰ
ማለት ነው።መሲህም የተባለ ክርስቶስ ነው።ቅድመ አለም ንጉስ ቢሆንም በሰውነቱ ተቀባ ፣ከበረ፣ተሾመ ፣ነገሰ
ይባላል። (ከመምህር ሰቡሕ አዳምጤ የሰዋሰው ብርሃን ቅ/ጳውሎስ መ/ኮሌጅ የሐዲሳት ትርጓሜ መምህር )።

ወልድ በሰውነቱ ተቀባ ማለት ተቀበለ ማለት ነው ። ትርጉሙም ወልድ በሰውነቱ የባህርይ ህይወቱ መንፈስቅዱስን
ከባህርይ አባቱ ከአብ ተቀብሎ ህይወት ሊሆነው ገንዘብ አደረገ ማለት ነው ።

 ወካዕበ ነጽሩ ከመ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሶበ ነስአ መንፈሰ ቅዱሰ በትስብእቱ እንዘ ውእቱ ፍጹም ኀበ አቡሁ
በመለኮቱ ። (ሃ.አበው ዘቄርሎስ ምዕ ፹ ፥ ፩)
 “ዳግመኛም ጌታችን ኢየሱስ ክረስቶስ እንደ ባሕርይ አባቱ በመለኮቱ ፍፁም ሲሆን ሰው በመሆኑ መንፈስ ቅዱስን
ገንዘብ አደረገ፡፡”(ሃ.አበው ዘቄርሎስ ምዕ 80፥1)
 ወበእንተ ዝንቱ ይደሉ ይትበሃል ከመ ውእቱ ነሥአ መንፈሰ ዚአሁ ዘተነግረ በኢሳይያስ ነቢይ እንዘ ይብል መንፈሰ
እግዚአብሔር ላዕሌዬ በእንተ ዝንቱ ቀብዓኒ በእንተዝ ሰበከ እንዘ ይብል እስመ መንፈስ ዘዚአዬ ዘህላዌዬ ለሊሁ
ኀደረ ላዕሌዬ በእንተ ዝንቱ ወለምንትኑ ተሰመይኩ መሲሐ ዘእንበለ ዳእሙ ሶበ ኮንኩ ሰብዓ። ዝንቱ ውእቱ
መድኀኒትነ ዝንቱ ውእቱ ፈውስነ ዝንቱ ውእቱ ሐዋጺነ ወበእንተዝ ይቤ እምድኅረዝ በእንተዝ ፈነወኒ እዜንዎሙ
ለነዳያን ወአስተፍሥሆሙ ለትኩዛነ ልብ ወእስብክ ግእዛነ ለፂውዋን ወይርአዩ ዕውራን ወዘሰ ኃደረ ላእሌሁ
መንፈስ ቅዱስ በእንተ ሥርዓተ ትስብእት ዉእቱ ወእመ አኮሰ መንፈስ ቅዱስ ዘዚአሁ ዉእቱ በህላዌ መለኮት ዘከመ
እግዚአብሔር በእግዚአብሔር በከመ ይቤ እስመ አብ በወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፍፁም ”
(ሃ.አበዉ ዘሳዊሮስ ፹ ፯ ፥ ፲ ፮- ፲ ፰)
 ስለዚህም የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ህልው ነው ። ስለዚህ ነገር ቀባኝ ሲል በኢሳይያስ የተነገረለትን የባህርይ
ህይወቱ መንፈስ ቅዱስን እርሱ ገንዘብ እንዳደረገ ሊነገር ይገባል ። ስለዚህ በባህርዬ ገንዘቤ የሚሆን መንፈስ ቅዱስ
በህልውናዬ ፀና ብሎ አስተማረ ሰው ብሆን ነው እንጅ ያለዚያ ለምን ክርስቶስ ተባልኩ? የምንድንበት ይህ ነው
የሚፈውሰን ይህ ነው የጎበኘን ይህ ነው ። ስለዚህም ከዚህ በኋላ ለድሆች የምስራች እነግራቸው ዘንድ ያዘኑትን
አረጋጋቸው ዘንድ ለተማረኩት ነጻነትን እሰብክላቸው ዘንድ እውሮች ያዩ ዘንድ ስለዚህ ላከኝ አለ ። መንፈስ ቅዱስ
ገንዘቡ ሆነ መባሉ ቃል ሰው ስለሆነ ነው፤ሰውማ ባይሆን ኑሮ እግዚአብሔር በእግዚአብሔር ህልው እንደሆነ
መንፈስ ቅዱስም በባሕርይ መለኮት ገንዘቡ ነውና እንደምን ገንዘቡ ሆነ ይባላል?አብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ
ህልው መሆኑ እንደተነገረ” (ሃ.አበው ዘሳዊሮስ 87፥ 16 – 18) ፤ኢሳ 61 ፥ 1፣ ሉቃ 4፥18-19

23
 እስመ ወልድ ይትወከፍ ህይወተ ወይሬስዮ ቦቱ ወበአይ አምሳል ዝንቱ በእንተ ስጋ ዘነሥአ ወኮነ አሐደ ምስለ ቃል
ህያወ ወረሰዮ ሎቱ ዘዚአሁ ወበእንተዝ ተብህለ በእንቲአሁ ፈድፋደ ከመ ውእቱ ተወክፈ ህይወተ ወባህቱ ዘዚአሁ
ውእቱ ህይወት በህላዌሁ። (ሃ. አበው ቄርሎስ ፹ ፥ ፳ – ፳ ፩)
 ዳግመኛም ወልድ ህይወትን ገንዘብ አድርጎ ይሰራበታል ይህ በምን ነገር ነው?ስለነሳው ከህያው ቃል ጋር አንድ
ስለሆነ ገንዘቡም ስለደረገው ስለ ሥጋ ነው ።ስለዚህም ፈፅሞ ህይወትን ገንዘብ እንደአደረገ ስለ እርሱ ተነገረ ።
ነገር ግን በባህርዩ ህይወት ገንዘቡ ነው ። (ሃ. አበው ቄርሎስ 80 ፥ 20 – 21)
 ወቦቱ ዓዲ መንፈስ ቅዱስ ዘዚአሁ በህላዌ መለኮታዊ ወእም አመ ኀደረ ቃል ውስተ ከርሠ እሙ ድንግል አስተርአየ
ሥጋ በመንፈስ ቅዱስ ወኮነ ፩ደ ምስሌሁ በኩሉ ዘዘርከነ ወተዐውቀ በሥርዓት ከመ ኢፍሉጥ ውእቱ ።
(ሃ.አበው ዘሳዊሮስ ፹ ፯ ፥ ፲ ፬)
 “በባህርየ መለኮት ገንዘቡ የሚሆን መንፈስ ቅዱስም አሁንም የባህርይ ህይወቱ ነው፡፡ቃል በእናቱ በድንግል ማህጸን
ካደረ ጀምሮ ሥጋ በመንፈስ ቅዱስ ተገለፀ፡፡ በተናገረው ሁሉ ከቃል ጋር አንድ ሆነ፤በተዋሕዶም ልዩ እንዳይደል
ታወቀ፡፡” (ሃ.አበው ዘሳዊሮስ 87 ፥ 14)
 ወበእንተ ዝንቱ ቦአ ውስተ ሥጋየ ከመ እትወከፍ አነ ቃሉ ነሥአ ሥጋየ ሎቱ ።ወወኀበኒ መንፈሶ ወወሀብኩ
ወነሣእኩ ወዘገብኩ ሊተ ረባሐ ህይወት ለሊሁ ነሥአ ሥጋየ ሎቱ ከመ ያንጽሖ ወወሀበኒ መንፈሶ ዘያድኀነኒ ።
(ሃ.አበው ዘዮሐንስ አፈወርቅ ፷ ፮ ፥ ፲ ፱ ) ፡ ዕብ ፪ ፥ ፲ ፬ - ፲ ፰ ፡ ዮሐ ፩ ፥ ፲ ፩ - ፲ ፰
 “ስለዚህ ሥጋዬን ተዋሕደ ወንጌልን ሲያስተምር እሰማው ዘንድ ሥጋዬን በተዋሕዶ ገንዘብ አደረገ ፤መንፈስ
ቅዱስን ሰጠኝ ሰጠሁ፤ተቀበልኩ ለእኔም ፍፁም ህይወትን ገንዘብ አደረግሁ፤እርሱ ያከብረው ዘንድ ስጋየን
ተዋሕደው ፤የሚያድን መንፈስ ቅዱስን ሰጠኝ፡፡”
(ሃ.አበው ዘዮሐንስ አፈወርቅ 66 ፥ 19) ፡ ዕብ 2 ፥ 14-18 ፡ ዮሐ 1 ፥ 11 - 18
 ወይእዜኒ አንተ አባ ሰብሐኒ በስብሐትየ ዘሀሎ ኀቤከ እምቅድመ ይትፈጠር ዓለም ።(ዮሐ ፲ ፯ ፥ ፭ )
 “አሁንም አባት ሆይ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ”
(ዮሐ 17 ፥ 5)
ወልድ በሰውነቱ መንፈስ ቅዱስን የተቀበለው ከሰው ልጅ በተለየ ያለመጠን ያለ መስፈርት በባሕርይ ነው ። የሰው ልጅ
ግን በመጠን በመስፈርት የሚገባውን የጸጋ መንፈስ ቅዱስ ይቀበላል ።

 “እስመ አኮ በመሰፈርት ዘይሁብ እግዚአብሔር መንፈሶ አብሰ ያፈቅር ወልዶ ወኩሎ ኩነኔሁ አወፈዮ ለወልዱ
ውስተ እዴሁ ” (ዮሐ ፫ ፥ ፴ ፬)
 እግዚአብሔር መንፈሱን ሰፍሮ አይሰጥምና።አባት ልጁን ይወዳል ሁሉንም በእጁ ሰጥቶታል። ዮሐ 3 ፥34
 እስመ አኮ በመስፈርት ዘወሀቦ እግዚአብሔር መንፈሰ ። (ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን ፲ ፭ ቁ ፺ ፪ ገጽ
፪ ፻ ፹ ፰)
 እግዚአብሔር አብ ህይወቱ መንፈስ ቅዱስን በልክ በመጠን የሰጠው አይደለምና የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ሁሉ
ገንዘቡ ነው ፡፡ (ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 15 ቁ 92 ገጽ 288)
 እስመ ለእግዚእ ክርስቶስ አኮ በመስፈርት ዘተውህቦ መንፈስ (ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን ፫ ቁ ፹ ፯ገጽ፸ ፭)
 መንፈስ ቅዱስ ለክርስቶስ በልክ በመጠን የተሰጠው አይደለምና ቅብዓ ትፍሥህት እምእለ ከማከ አለ፤ ዘይኄይስ
ያለበት ነው ። (ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 3 ቁ 87 ገጽ 75)

ወልድ በሰውነቱ ተቀባዒ ቢሆንም በአምላክነቱ ግን ቀባዒ ነው ። ምክንያቱም ሥጋ ከቃል ጋር ተዋሕዶ አምላክ ሲሆን
የሰውነቱን ግብር እንዳልለቀቀ ሁሉ ቃልም ከሥጋ ጋር ተዋሕዶ ፍፁም ሰው ሲሆን የአምላክነትን ሥራ አልለቀቀምና ከአብ
ጋር በአንድነት ይቀባል ።

24
 ወበእንቲአሆሙ አነ እቄድስ ርዕስየ ። (ዮሐ ፲ ፯ ፥ ፲ ፱)
 እኔ ራሴን ስለ እነርሱ እቀድሳለሁ። (ዮሐ 17 ፥ 19)
 ወከመዝ ነአምሮ ከመ ለሊሁ ተቀብዓ ከመ ሥርዓተ ትስብዕት ወዳዕሙ ውእቱ ዘይቀብዕ ርእሶ በመንፈሱ ባሕቲቱ።
(ሃ.አበው ስምዐት ዘቄርሎስ ፻ ፳ ፬ ፥ ፲ ፬)
 “ሰው በመሆኑ እርሱ እንደከበረ እናውቀዋልን፤ ነገር ግን ሕይወቱ በሆነ በመንፈስ ቅዱስ ራሱን የሚያከብር እሱ
ነው ፡፡” (ሃ.አበው ስምዐት ዘቄርሎስ 124 ፥ 14 የአስመራ ዕትም ሃይማኖተ አበው )
 ወለእመ ኮነ ውእቱ ዝንቱ ፩ዱ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ይነስእ መንፈስቅዱስ ወዓዲመ ውእቱ ይሁብ ኪያሁ
ወግብሩሂ ክሱት ከመ ዝንቱ ፩ዱ ኢየሱስ ክርስቶስ ይነስእ መንፈስ ቅዱስ ዘከመ ሥርዓተ ትስጉቱ ወከማሁ ዓዲ
ይሁብ ኪያሁ እስመ እግዚአብሔር ውእቱ በህላዌሁ ዘበአማን ። (ሃ.አበው ዘቄርሎስ ፸ ፱ ፥ ፷ ፪)
 “ይህ አንዱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መንፈስ ቅዱስን በእስትንፋስነት ገንዘቡ የሚያደርግ፤ ወዲህም የሚሰጥ ከሆነ
ይህ አንዱ የኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ለመሆኑ የሚገባ ሥርዓት እንደመሆኑ መንፈስ ቅዱስን ገንዘብ የሚያደርግ
ወዲህም የባሕርይ አምላክ ነውና መንፈስ ቅዱስን እንዲሰጥ ነገሩ የተገለጠ ነው፡፡”
(ሃ.አበው ዘቄርሎስ 79 ፥ 62)
“እኔ ራሴን ስለ እነርሱ እቀድሳለሁ” የሚለውን ጥቅስ በማንሳት የካራ እምነት ተከታዮች በተዋሕዶ ከበረ፣በተለየ ክብሬ
እራሴን አከብራለው ማለት ነው አክባሪው ቃል ተከባሪው ሥጋ ነው ይላሉ ። ትርጉሙ ግን መለኮት ከሥጋ ጋር ተዋሕዶ
ፍፁም ሰው ሲሆን ቃል በሥጋ ርስት መንፈስ ቅዱስን ሲቀበል ሥጋ በቃል ርስት ከአብ ጋር እኩል ነውና ራሱን በመንፈስ
ቅዱስ አከበረ ማለት ነው ።

 እንከ ክርስቶስ ወልድ ወእግዚእ ይቄድስ በመለኮቱ ወይትቄደስኒ ምስሌነ በሥጋሁ እም ወንጌለ ዮሐንስ ይቤ ወእመ
ርእሶ ይቄድስ ክርስቶስ አሐዱ ውእቱ ወልድ ወእግዚእ ተቀደሰ ከዊኖ ሰብእ ወይቄድስ እንከ በመለኮቱ በዘዚአሁ
መንፈስ ቤተ ዚአሁ ። ተረፈ ቄርሎስ ገፅ 122 የብራና

በተለየ ክብሩ እራሱን ያከብራል ፤ አክባሪው ቃል ተከባሪው ሥጋ ነው ማለት ክህደት ነው ። ምክንያቱም ቃል አክባሪ
ሥጋ ተከባሪ ከሆነ ግብር መለየት ነው ። ቃልን አክባሪ አድርጎ አባት ፤ ሥጋን ተከባሪ አድርጎ ልጅ ፤ በማለት ግብር
ይለያል። ግብር ከተለየ ደግሞ አካል እና ባህርይ አይቀርም እና ሥላሴን በአካል በባህርይ በግብር መለየት ይሆናል ።
አንድም ቃል ሥጋን ካከበረው ይህ ክብር አካላዊ ክብር ነውና ቃል ከራሱ አካል ጋር ሌላ አካላዊ ክብር አለው ፤ ለአብ እና
ለመንፈስ ቅዱስም እንዲሁ የየራሳቸው አካላዊ ክብር አላቸው ያሰኛል ። ይህም ሥላሴን ስድስት አካላት ሦስት አማልእክት
ማድረግ ነው ።

 እስመ አዔረዮ ለወልድ ምስለ አቡሁ ፤ወንእዶ ከመ ከማሁ ፤ወአስተላጸቆ ምስሌሁ ፡፡


(ዮሐንስ አፈወርቅ ድረሳን ፫ ቁ ፺ ፱ - ፻ ፩ ገጽ ፸ ፯ )
 ወልድን ከአብ ጋር አስተካክሎታልና ፤ እንደ እሱ አካል ባለ አካል አክብሮታልና፤ ከእሱ ጋር በባህሪ አንድ
አድርጎታልና ።(ዮሐንስ አፈወርቅ ድረሳን 3 ቁ 99 – 101 ገጽ 77 )

“ እንደ እሱ አካል ባለ አካል አክብሮታልና ” ሲል አክባሪው አብ ሲሆን “ እንደሱ ባለ አካል ” የተባለው የመንፈስ ቅዱስ
አካል ነው ። ምንም እንኳ ሥላሴ በአካል ሦስት ቢሆኑም የአብ አካል ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ አካል ጋር ተመሳሳይ ነውና።

ቅብዕ የሆነው የባሕርይ ሕይወቱ መንፈስ ቅዱስ ነው ፡፡ ምክንያቱም ቅብዕነት፣ ሕይወትነት ፣መሰጠት(ተሰጭነት)
የመንፈስ ቅዱስ ግብር ነውና፡፡

25
 አፍቀርከ ጽድቀ ወአመፃ ጸላዕከ በእንተዝ ቀብዓከ እግዚዚአብሔር አምላክከ ቅብዓ ትፍሥሕት እምአለ ከማከ ።
(መዝ ፵፬፥፯ ፡ ዕብ ፩ ፥ ፱)
 ጽድቅን ወደድህ ዓመፃንም ጠላህ፤ ስለዚህ ከባልንጀሮችህ ይልቅ እግዚአብሔር አምላክ የደስታ ዘይትን ቀባህ።
(መዝ 44፥ 7 ፡ ዕብ 1 ፥ 9)
 “ወእምዝ አትለወ ይቤ በእንተ ሥጋዌሁ ፡አፍቀርከ ርትዐ ወአመጻ ጸላእከ ፡በእንተዝ ቀብዓከ እግዚአብሔር
አምላክከ፣ቅብዓ ትፍስሕት አምለከማከ፡፡አንድም መንበርከ እግዚኦ ለዓለመ አለም፤አንድም በትረ መንግስትከ ካለ
በኋላ ስለሰዉነቱ በእንተዝ ቀብዓከ እግዚአብሔር አምላክከ አለ ። ”
(ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 3 ፥ 67 ገጽ 73)
ቅብዓ ትፍሥሕት ማለት መንፈስ ቅዱስ ማለት ነውና፡፡መንፈስ ቅዱስ ቅብዕ ሆነ ማለት ተሰጠ ማለት ነው ።
ትርጉሙም ጥንተ ህይወቱ መንፈስ ቅዱስ ለወልድ በሰውነቱ የባህርይ ህይወት ሆነው ማለት ነው ።

ዕብራውያን 1፥9 አንድምታ ትርጉም “አፍቀርከ ጽድቀ ወጸላዕከ አመፃ- ጽድቅን ወደድህ ሐሰትን ጠላህ ማለት ሰው
መሆንን ወደድክ ሰው አለመሆንን ጠላህ አንድም ዘመንን፣ ቀጠሮን፣ አሥሩ ቃላትን፣ ሕማማተ መስቀልን ትንቢተ ነብያትን፣
መፈጸምን ወደድክ፣ አለመፈጸምን ጠላህ:: ወበእንተዝ ቀብዓከ እግዚአብሔር አምላክከ ቅብዓ ትስፍሕት ዘይኄይስ እምለ
ከማከ/መዝ44፥7 ኢሳ 61፥1 ግብ ሐዋ 10፥ 38/ ስለዚህ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን በእርግብ አምሳል በራስህ ላይ አኑሮ
ወልድየ ፍቅሩየ ዘኃረይኩ ወቦቱ ሠመርኩ ብሎ እንዳንተ ካሉ ሰዎች መረጠህ ለየህ:: ዘይኄይስ በነብዩ የለም:: ሐዋርያው
ተናግሮታል:: ሐዋርያው ዘይኄይስ ያለውን ቄርሎስ ቅብዓ ነከራ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ዘአልቦ መስፈርት ብለው ወስደውታል::
እምእለ ከማከ ያለውንም ዮሐንስ አፈ ወርቅ መኑ እሙንቱ እለ ከማሁ አኮኑ ውሉደ ሰብእ፣ ቄርሎስም ዘውእቶሙ ንሕነ
ብለው ወስደውታል:: ”

መንፈስ ቅዱስንም ቅብዕ ነው ስላሉ ቅብዕ ብቻ አይደለም ቀባዒም ነው ፡፡ መንፈስ ቅዱስ በተለየ አካሉ ቅብዕ ሲሆን
በስልጣን ስራ ከአብ ከወልድ ጋር አይለይምና በአንድነት ይቀባል፡፡

 የጌታ የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች የምሥራችን እሰብክ ዘንድ እግዚአብሔር ቀብቶኛልና፤
ልባቸው የተሰበረውን እጠግን ዘንድ፥ ለተማረኩትም ነጻነትን ለታሰሩትም መፈታትን እናገር ዘንድ ልኮኛል።
(ኢሳ 61 ፥ 1)
 ለሊሁ ዘይሁብ ወለሊሁ ዘይትወሀብ ። (አረጋዊ መንፈሳዊ ድርሳን ፲ ፩ ገፅ ፶ ፮)
 ፀጋውን የሚሰጥ እርሱ ነው ፀጋም ሆኖ የሚሰጥ እርሱ ነው ። (አረጋዊ መንፈሳዊ ድርሳን 11 ገፅ 56)
ሰጭነቱ በስልጣን ከአብ ከወልድ ጋር አብሮ ማክበሩ ነው ተሰጭነቱ ደግሞ በተለየ አካሉ ለፍጥረታት እንደየ
ስጦታው የተሰጠ ፀጋ በረከት ስለሆነ ነው ፡፡

ቃል ከሥጋ ሳይወሐድ ቅብዓትን(መንፈስ ቅዱስ መቀበልን) አይፈልግም ።ቃል በሥጋ ርሰት ተቀባ እንጂ በመለኮቱማ እከብር
አይል ክቡር፣እቀደስ አይል ቅዱስ ስለምን ተቀባ ይባላል ።

 ከመ መለኮት ኢይትቀባዕ ዘእንበለ ዳዕሙ ትስብእተ ሥጋሁ


(ድርሳን ዘ ዮሐንስ አፈወረቅ ድርሳን ፫ ቁ ፹ ፫ ገጽ ፸ ፭)
 በሰውነቱ እንጂ በአምላክነቱ ተቀባ (ከበረ) እንደማይባል አስረዳቸው
(ድርሳን ዘዮሐንስ አፈወረቅ ድር 3 ቁ 83 ገፅ 75 )
 ኢይጽሕቅ ቅብዓተ በሕላዌ መለኮቱ አላ ተሰጊዎ ነስዓ ቅብዓተ እምአብ በትስብእቱ ። ድርሳነ ቄርሎስ ድርሳን ፳ ፱
 በህላዌ መለኮቱ መንፈስ ቅዱስን የሚቀበል አይደለም በለበሰው ሥጋ ከአብ ተቀበለ እንጅ ። (ድርሳነ ቄርሎስ
ድርሳን 29 )

26
 “ወለመንክንሂ፡አግሀደ ሎቱ ከመ መለኮት ኢይትቀባዕ ዘእንበለ ዳዕሙ ትስብእተ ሥጋሁ…..ምትሐት የሚሉ እለ
መንክዮንን በሰዉነቱ እንጅ በአምላክነቱ ከበረ እንዳባል አስረዳቸዉ (ሐተታ) ምትሐት ይላሉ እንጅ በባሕርዩ ከበረ
ይላሉን ቢሉ መጽሐፍ ቃልን በስጋ ተቀባ ይለዋል፡፡በሥጋ እንዳሉ ምትሐት ይላሉ፡፡ምትሐት ካሉ በአምላክነቱ ከበረ
ያሰኛልና፡፡አንድም ተቀብቶ ተዋሐደ ይላሉና፡በመለኮቱ ከበረ እንዳይባል አስረዳ በእንተዝ በማለቱ ነዉ”
(ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 3 ፥ 83 ገጽ 75 )

መቀባቱ ምን ጊዜ ነው ?
ሲወሐድ ሲቀባ አንድ ጊዜ ነው ። ይህም ማለት ወልድ ከእግዝእትነ ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ
ይህንን የሰው ልጅ ሥጋ ሲወሐድ እና ቃል በሥጋነቱ የባህርይ ህይወቱ መንፈስ ቅዱስን ሲቀበል አንድ ጊዜ ነው ። ሲወሐድ
ሲቀባ መቀዳደም የለበትም ።ሳይወሐድ ተቀባ ከተዋሐደ በኋላ ተቀባ ማለት አይገባም ።

 ሲቀባም ሲዋሐድም አንድ ጊዜ ነዉ ፡፡ከመ ቅጽበተ ዓይን እለሰ የአምኑ ርቱዓ ይሜህሩ ከመ ተቀብዓ ቃል በሥጋሁ
ወእምአመ ኮነ ቃል ሥጋ አሜሃ አስተርአየ በመንፈስ ቅዱስ - በእውነት የሚያምኑ ቃል በሥጋው እንደ ከበረ እንደ
ተቀባ ያስተምሩ ፣ቃል ስጋ ሲሆን በመንፈስቅዱስ ታወቀ፤ ተገለጠ፤ ከበረ።
(ማቴ 1፥ 16 (አንድምታ) ፡፡ የ1997 ዓ.ም ዕትም::)
ይህ ከሆነ ተቀባ ማለት ተዋሐደ ማለት አይደለም ። ምክንያቱም ሲዋሐድ ሲዋሐድ አንድ ጊዜ ነው የሚል ትርጉም
የሌለው ድግግሞሽ ስለሚሆን ነው ።ተቀብዓ ተዋሐደ ከሆነ ቄርሎስና ዮሐንስም “መለኮቱሰ ኢተቀብዓ” ይላሉና
መለኮቱስ አልተዋሐደም ያሰኝብናል::

 “መንክረ ገብረ ወልደ እግዚአብሔር ዉስተ ከርሰ እሙ እስመ ፈጸመ ሥርዓተ ተዋሕዶ ወቅብዓት ምዕረ ከመ
ቅጽበተ ዓይን” (ድርሳን ዘቅዱስ አውሳብዮስ፡፡)
 የእግዚአብሔር ልጅ በእናቱ ማሕጸን ድንቅ ነገርን አደረገ የተዋሕዶን (የአንድነትን) እና የቅብዓትን ነገር እንደ ዓይን
ቅጽበት አንድ ጊዜ ፈጽሟልና ።(ድርሳን ዘቅዱስ አውሳብዮስ፡፡)
 “ወከመ አኮ ቀዲሙ ዘወረደ ወእምዝ ተሠይመ››››››ቀድሞ ሰዉ እንዳልሆነ ኋላ እንዳልተሾመ መጠን አንድ ጊዜ
ሰዉ ለመሆን እንደመጣ አስረዳ፣አንድም ቀድሞ ሰዉ እንዳልሆነ ኋላ እንዳልተሾመ አስረዳ፣ሰዉ ሁኖ ኑሮ ኑሮ ተቀባ
የሚሉ አሉና እንዲህ አለ፡አንድም በተዋሕደ ጊዜ ተቀባ አለ ተቀብቶ ኖሮ ኖሮ ተዋሐደ አላለም ”
(ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 15 ቁ 105 ገጽ 288)
 እንዘ ይትወሐድ ወይትቀባዕ ኢገብረ ንስቲተ ጊዜ እስመ ዝንቱሰ ለድኩም ብእሲ ወአልቦ ጊዜ ማዕከለ ተዋሕዶ
ወቅብዓት ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ??????

እኛም ለአንደበታችን መናገር ባይቻለን በትምህርትም በጽህፈትም ተወሐደን አስቀድመን ተቀብዓን እናስከትላለን ።ይህንንም
ምሳሌ ያስረዳል ።

1) እነሆ በሥላሴ ሦስትነት መቀዳደም መከታተል የለባቸውም ። ምንም መቀዳደም መከታተል ባይኖርባቸው ለወልድ
መወለድ ፣ ለመንፈስቅዱስ መስረፅ ምክንያታቸው አብ ነውና አብ ወልድ መንፈስቅዱስ እንላለን እንጅ ወልድ አብ
መንፈስቅዱስ ፤ መንፈስቅዱስ ወልድ አብ ሌላም አንልም ። እንደዚህም ሁሉ በተውሕዶ እና በቅብዓት ምንም
መቀዳደም መከታተል ባይኖርባቸው የቅብዓት ምክንያት ተዋሕዶ ነውና ተዋሐደ ተቀባ እንላለን ።
2) ዐይን ሳይገለጥ አያይም ተገልጦም ሳያይ አይቆይም ። ሲገለጥ ሲያይ አንድ ጊዜ ነው ። እንደዚህም ሁሉ መለኮት
ከሥጋ ሳይወሐድ አልተቀባም ተዋሕዶም ሳይቀባ አልቆየም ሲወሐድ ሲቀባ አንድ ጊዜ ነው ። ይህንንም ምሳሌ
ብናጣ ትናገርነው እንጅ ሲወሐድ ሲቀባ ከአይን መገለጥ እና ማየት እልፍ አእላፍ ጊዜ ይቀድማል ።

27
ማቴ 1 ፥ 16 ሲቀባም ሲዋሐድም አንድ ጊዜ ነዉ የሚለው ክርስቶስ የሚለውን ሥም በተረጎሙበት አንቀፅ ነው ።

ክርስቶስ ማለት የስሙ ትርጉም ቅቡዕ(የተቀባ) ማለት ነው ። ክርስቶስ የተቀብዖ (ሉቃ 9÷20 ፤ ዮሐ 1÷42)
ስሙ ሲሆን አማኑኤል የተዋሕዶ ስሙ ነው (ማቴ ትርጓሜ 1÷16)፤ነገርግን አማኑኤል ተብሎ ክርስቶስ ያልተባለበት ክርስቶስ
ተብሎ አማኑኤል ያልተባለበት አንዳችም ቅጽበት የለም ሁለቱም በአንድ ጊዜ ተፍጽመዋል እንጂ ፡፡

 ናሁ ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ ወትሰምይዮ ስሞ አማኑኤል ዘበትርጓሜሁ እግዚአብሔር ምስሌነ ።


(ኢሳ ፯ ፥ ፲ ፬)
 እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች ።
ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው ። (ኢሳ 7 ፥ 14)
 ወተሰምየ ክርስቶስሃ በእንተ ዘተቀብዓ ምስሌነ ከመ ሰብእ በከመ ቃል ዳዊት በእንተ ክርስቶስ ዘይቤ አፍቀርከ
ጽድቀ ወአመፃ ጸላዕከ በእንተዝ ቀብዓከ እግዚዚአብሔር አምላክ በዘይተ ፍሥሐ እምኩሎሙ እሊአከ እለ
እሙንቱ ሱቱፋኒከ ወለሊሁ ውእቱ ዘይፌኑ መንፈሰ ቅዱሰ ወይሁብ ለእለ ይደልዎሙ በአቅም ለሊሁሰ ፍጹም
ውእቱ ወንኅነኒ ኩልነ ነሣእነ እምፍጻሜሁ በከመ ጽሑፍ ንህነሰ ንብል በለብኦ ውእቱሰ ተቀብዓ በከመ ሥርዓት
ወረደ ላዕሌሁ መንፈስ ቅዱስ ከመ ይኩን ውስቴትነ ለነሂ ዓዲ ።
(ሃ.አበው ቃለ ግዘት ዘቄርሎስ ፻ ፳ ፩ ፥ ፳ ፱)
 እንደሰው ከእኛ ጋር ስለተቀባ ክርስቶስ ተባለ ሰው መሆንን ወደድህ አለመሆንን ጠላህ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር
አምላክ በነፍስ በሥጋ ከመሰሉህ ምእመናን በተለየ ደስ በሚያሰኝ በመንፈስ ቅዱስ ቀባህ ብሎ ስለ ክርስቶስ ዳዊት
እንደተናገረ ለሚገባቸው ሰዎች ሃብተ መንፈስ ቅዱስን መጥኖ መጥኖ የሚሰጥ እርሱ ነው እርሱ ክብር የማይሻ
ፍጹም ነው እኛ ሁላችንም እንደተጻፈ ከምላቱ ከፍጹም ጌትነቱ ክብርን ተቀብለናል እኛስ በማስተዋል እሱ ተቀባ
እንላለን እኛም የባሕርይ ሕይወቱን በጸጋ እንቀበል ዘንድ መንፈስ ቅዱስ በእሱ ላይ ወረደ እንላለን ።
(ሃ.አበው ቃለግዘት ዘቄርሎስ 121 ፥ 29)
 “ወሶበሂ ተሰምየ ሐዋርያ አው ተብህለ በእንቲአሁ ከመ ቅቡዕ ውእቱ ወተሰምየ ወልደ አምላክ ኢነኀፍር ንኅነ
እምሥርአተ መድኅን ወንብል በእንቲአሁ ከመ አምላክ ቃል ለሊሁ ውእቱ ዘመጽአ እምኀበ አብ ወሶበ ኮነ ሰብአ
ከማነ ተሰምየ ሐዋርያ ወተቀብዓ ምስሌነ ከመ ስርአተ ትስብእት።”
(ሃ.አበው ቃለ ግዘት ዘቄርሎስ ፻ ፳ ፩ ፥ ፲ ፪)
 ሐዋርያ ቢባል ወይም ክርስቶስ እንደሆነ ቢነገር የአምላክ ልጅም ቢባል መድኅን ክርስቶስ በፈፀመው ሥርዓት እኛ
አናፍርም ከአብ ተወልዶ ሰው የሆነ እርሱ አምላክ ቃል እንደሆነ እንናገራለን እንደኛ ያለ ሰውም ቢሆን ሐዋርያ
ተባለ ለሰውነትም እንደሚገባ እንደኛ መሲህ ተባለ ። (ሃ.አበው ቃለ ግዘት ዘቄርሎስ 121 ፥ 12)
 “ወወረደ ባሕቲቱ ወልድ ዋሕድ ቃለ እግዚአብሔር ኀደረ ኀበ ማርያም ድንግል ወሶበ ተሰገወ ተሰምየ ክርስቶስሃ
ዘዉእቱ ቅቡዕ ብሂል” (ሃ.አበዉ ቃለ ግዘት ዘቄርሎስ ፻ ፳ ፩ ፥ ፴)
 በተለየ አካሉ ወልድ ዋሕድ የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኛ ወረደ በድንግል ማህፀን አደረ ቃል ሥጋን ነስቶ ሰው
በሆነ ጊዜ ክርስቶስ ተባለ ይኧውም የተቀባ ማለት ነው ። (ሃ.አበዉ ቃለ ግዘት ዘቄርሎስ 121፥ 30)
 “እስመ ሶበ ቃል ሥጋ ኮነ አሜሃ ንብል ተሰምየ ክርስቶስ እስመ እንከ ተቀብዓ ቅብዓ ትፍስሕት እመንፈስ ቅዱስ
በኀበ እግዚአብሔር አብ በእንተዝ ተሰምየ ክርስቶስ” (ድርሳነ ቄርሎስ ድርሳን 20)

28
 ጰላድዮስ ቅዱስ ቄርሎስን የጠየቀውን ጥያቄ
ጰላድዮስ ይቤ እዎኬ ይብሉ ይደልዎ ለዘእምብሲት ባሕቲቱ ዘእምዘራ ዳዊት ክርስቶስ ይሰመይ በእንተ ቅብዐት
ዘተቀብዐ በመንፈስ ቅዱስ እስመ ክርስቶስ ብሂል ቅቡዕ ብሂል ወዘሰ እግዚአብሔር ቃል ኢይጽሕቅ በህላዌ ዚያሁ
ቅብዐተ፤ እስመ በህላዌሁ ቅዱስ ወእቱ፤ ወክርስቶስ ሰሚይ ቅብዐተ ዘውእቱ መሲህ፡፡
 ጰላድዮስ ከዳዊት ዘር ከድንግል የተወለደውን ስለ ቅብዐት በመንፈስ ቅዱስ የከበረ ነው ይሉ ዘንድ ይገባዋልን?
ክርስቶስ ማለትም የተቀባ ማለት ነውና፤ኾኖም ግን እግዚአብሔር ቃል በባሕርይው መክበርን መቀባትን አይሻም
አለ፡፡
 ቄርሎስኒ ይቤ ነበብከ ርቱዓ ከመ በእንተ ቅብዓት ክርስቶስ ይሰመይ ዘውእቱ መሲህ ፤ በከመ ሐዋርያ በእንተ
ሐዊሮቱ ይሰመይ ፤ ወመልአክኒ ይሰመይ በተልእኮቱ ፤ወለከመዝ አስማት አማን በአማን በእንተ ሲመቱ ፤ ወግብሩ
ይሰመይ አኮ ዘህላዌ አው ዘገጽ ውእቱ በዝንቱ አስማት ተሰምዩ ነቢያት ቅቡዓን ዘውእቶሙ መሲሐዊያን በከመ
ሀሎ በመዝሙር ኢትግስሱ መሲሐንየ ወካእበ ይቤ ዕንባቆም መጻእከ ለአድኅኖ ህዝብከ ከመ ታድኅኖ ለመሲህከ
(ጰላድዮስ ተረፈ ቄርሎስ ገፅ 122 የብራና)
 ቄርሎስም በሥርዓተ ቅብዓት ክርስቶስ እንዲባል እውነትን ተናገርክ ። ይኧውም የከበረ ፣ የተቀባ ማለት ነው አለ።
ዞሮ በማስተማሩ ሐዋርያ ይባላል ፤ በመላኩም መላክ ይባላል ፤ በእኒህ ስሞች ሁሉ እውነት በእውነት ስለሹመቱ
ስለሰውነቱ ይጠራል ፤ እንዲህም ሲሆን ሁለት አካል ሁለት ባህርይ አይደለም ፤ በእኒህ ስሞችም ነቢያት ቅቡዓን
ይኧውም መሲሐዊያን ተባሉ በመዝሙር የቀባኋቸውን አትዳሱ ተብሎ እንደተጻፈ ።
(ጰላድዮስ ተረፈ ቄርሎስ ገፅ 122 የብራና)
 ይቤ ኢየሱስ ክርስቶስ ፃድቅ ወምእመን በኀበ ዘገብሮ ይብል እስመ ንህነ ነአምር ከመ ውእቱ ይቀውም ሰናየ
ለህዝቡ ወኢየኀድጎሙ ይማስኑ ወዘሰ ይብል ኀበ ዘገብሮ ይብል ዘንተ ከመ ውእቱ ገብሮ ሐዋርያ ወሊቀካህናት
ወኢተናገረ በዝየ በእንተ ህላዌ መለኮት አላ ተናገረ በእንተ ሥርአተ ትስብእቱ እስመ ትስብእቱ ግቡር ውእቱ ።
(ሃ. አበው ዘዮሐንስ አፈወርቅ ፷ ፫ ፥ ፳ ፯ – ፳ ፰)
 ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ሊቀ ካህናት በአደረገው በአብ ዘንድ የታመነ እውነተኛ ነው አለ ለወገኖቹ በጎ ማገልገልን
እንዲያገለግል ይጎዱም ዘንድ ቸል እንደማይላቸው እኛ እንድናውቅ መናገሩ ነው ። ገብሮ ያለውንም ሐዋርያ
ሊቀካህናት አድርጎ እንደሾመው መናገሩ ነው በዚህ አንቀጽ ስለ ባህርየ መለኮት አልተናገረም አምላክ ሰው
ስለመሆኑ ሥርዓት ተናገረ እንጅ ሥጋ ፍጡር ነውና ። (ሃ. አበው ዘዮሐንስ አፈወርቅ 63 ፥ 27 – 28)

 ኢየሱስ ከዕብራይስጥ የተወረሰ የግሪክ ቃል ነው ።ትርጉሙም አዳኝ ማለት ነው ማቴ 1 ፥ 21 ።


የኢየሱስ ስሞች ፦ ክርስቶስ በግሪክ ቋንቋ የተቀባ ማለት ነው ። መሲህ የሚለውን የዕብራይስጥ ቃል
ይተረጉማል ። (የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገፅ 164 ፣ 1992 ዓ.ም እትም)

29
 (ኪዳነወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ ገጽ 549-550)

30
31
ኢየሱስ ክርስቶስ እኔማን ነኝ ብሎ ለሐዋርያት በጠየቃቸው ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ የመለሰዉን መልስ ወንጌላዊው ማርቆስ
አንተ ክርስቶስ ነህ ብሎ መለሰለት ብሎ ሲጽፍ ወንጌላዊው ሉቃስ ደግሞ ከእግዚአብሔር የተቀባህ ነህ አለ ብሎ ጽፏል
ምክንያቱም ክርስቶስ ማለት የተቀባ ማለት ስለሆነ ነው ። “ እናንተስ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? ብሎ ጠየቃቸው።
ጴጥሮስም፦ አንተ ክርስቶስ ነህ ብሎ መለሰለት። ” (ማር 8 ፥ 29) “ እናንተስ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው።
ጴጥሮስም መልሶ፦ ከእግዚአብሔር የተቀባህ ነህ አለ። ” (ሉቃ 9 ፥ 20)

ክርስቶስ ማለት የተቀባ ማለት ከሆነ መጽሐፍ “ክርስቶስ ወረደ እምሰማያት”(ክርስቶስ ከሰማያት ወረደ) ሲል ከተዋሕዶ
በፊት ተቀብቶ ወረደ ማለት ሳይሆን ከተዋሕዶ በኋላ መለኮትና ሥጋን መለያየት የለምና መለኮትን በሥጋ ስም ጠርቶ
መለኮት ወረደ እምሰማያት ማለት ነው ።

አንዳንድ ሰዎች ቅዱስ ቄርሎስ ከዚህ በታች የተናገረውን ቃል በመያዝ በመንፈስ ቅዱስ ከበረ የሚል ቢኖር የተወገዘ ነው
ይላሉ ። ትርጉሙ ግን እንዲህ አይደለም
 “እመቦ ዘይብሎ ለ፩ዱ እግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሴባሕ እምኀበ መንፈስ ከመ ይግበር ኀይለ ነኪረ በረድኤቱ
ወይነሥእ ኃይለ ወምግባረ እምኔሁ በአውጽኦ መናፍስት ርኩሳት ወይፌጽም መንክራተ መለኮት ዘእጓለ እመሕያው
ወኢይብል ከመ ዚያሁ ወእቱ መንፈስ ወለሊሁ ይገብር ኃይለ ዘመለኮት ወጉዘ ለይኩን፡፡
(ሃ.አበው ዘቄርሎስ ፸ ፫ ፥ ፵ ፱)
 “ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ በእርሱ አጋዥነት ድንቅ ታምራትን ያደርግ ዘንድ በመንፈስ ቅዱስ ከበረ የሚለው ርኩሳን
አጋንትን በማውጣት ጊዜም ኃይልን ታምራትን ከመንፈስ ቅዱስ ይቀበላል ፤ በሰውም የአምላክነትን ሥራ ይሰራል ፤
የሚለው መንፈስ ቅዱስ የባህርዩ ነው፤የአምላክነትንም ሥራ እርሱ ራሱ ይሰራል የማይል ቢኖር ውግዝ (የተለየ)
ይሁን፡፡” (ሃ.አበው ዘቄርሎስ 73 ፥ 49)

ቅዱስ ቄርሎስ ያወገዘው ክርስቶስ እንደ ቅዱሳን መንፈስ ቅዱስን በጸጋ ተቀብሎ ታምር ያደርጋል፣መንፈስ ቅዱስ
የባህሪው አይደለም የሚሉትን ነው እንጅ በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከበረ የሚሉትን አያወግዝም ። እንዲያውም ይህንን
ጥቅስ ቅዱስ ቄርሎስ ለማን እንደጠቀሰው እንደገና በቃለ ግዝቱ አስቀምጦታል ::

 እመቦ ዘይብል በእንተ ፩ዱ እግዚአብሔር እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ለሊሁ ከብረ በመንፈስ ቅዱስ ወተሰብሐ
ዘከመ ኃይል ነኪር ውእቱ ይገብር ውስቴቱ ወይነሥእ ኃይለ ገቢር ላዕለ መናፍስት ርኩሳን ወይፌጽም ላዕለ ሰብእ
ተአምራተ አምላካዊተ ወኢኮነ ውእቱ እመንፈስ ዘሎቱ ለሊሁ ይገብር ውስቴቱ ተአምራተ አምላካዊተ ዉጉዘ
ለይኩን ።(ሃ.አበው ቃለ ግዘት ዘቄርሎስ ፻ ፳ ፩ ፥ ፴ ፫)
 “ስለ አንዱ አምላክ ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ ልዩ ሥልጣን በእርሱ አድሮ እንደሚሰራ አድርጎ በመንፈስ
ቅዱስ ከበረ፤አጋንንትን የሚያወጣበትን ተአምራትን የሚያደርግበትን ስልጣን ተቀብሎ የአምላክነትን ስራ በሰው ላይ
ይሰራል፤እርሱ ገንዘቡ በሚሆን ሥልጣን የአምላክነትን ስራ አይሰራም የሚል ሰው ቢኖር ውግዝ ይሁን፡፡”
(ሃ.አበው ቃለ ግዘት ዘቄርሎስ 121 ፥ 33)

ኃይለ ቃሉ በድርብ ሠረዝ የተያያዙ ሦስት ተመሣሣይ አረፍተ ነገሮች አሉት፤ እነሱም፡-

1) ስለአንዱ አምላክ ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ ልዩ ሥልጣን በእርሱ አድሮ እንደሚሠራ አድረጎ በመንፈስ
ቅዱስ ከበረ፤
2) አጋንንት የሚያወጣበትን ታምራት የሚያደርግበትን ሥልጣን ተቀብሎ የአምላክነትን ሥራ በሰው ላይ ይሠራል፤
3) እሱ ገንዘቡ በሚሆን ሥልጣን የአምላክነትን ሥራ አይሠራም የሚል ሰው ቢኖር ውጉዝ ይሁን ፤ ናቸው፡፡

1ኛውና 2ኛው ዐ. ነገሮች ምዕመናን ሁሉ ያምኑ ዘንድ ስለክርስቶስ ተነገሩ፤ በመንፈስ ቅዱስ እንደከበረ፣ በሰውም ዘንድ
ያምላክነት ሥራ እንሚሠራ በእኒህ በሁለቱ አረፍተ ነገሮች ተነገረ፤ እኛም ክርስቲያኖች በእነዚህ እንገዛለን፡፡3ኛዋ ዐ. ነ. ግን
“ክርስቶስ በራሱ ሥልጣን ያምላክነትን ሥራ አይሠራም የሚለውን ሰው እንደምታወግዝ ይናገራል እንጂ “በመንፈስ ቅዱስ

32
ከበረ” የሚለውን አታወግዝም፡፡
“ʻበመንፈስ ቅዱስ ከበረʼ የሚል ሰው ከተወገዘ እነግዲያውስ ʻያምላክነትን ሥራ በሰው ላይ ይሠራልʼ ከሚለው ሰው ጋር
ባንድነት ይወገዙ ማለት ነውን ? ውግዘቱ ለ3ኛዋ ዐ፣ነ ብቻ ʻክርስቶስን አምላክ አይደለም፤ ሥልጣኑም ከእርሱ አይደለም፤ʼ
ለሚል ሰው ነው እንጂ ʻበመንፈስ ቅዱስ ከበረʼ ለሚል ሰው አይደለም፡፡

ይህ ኃይለ ቃል ከቄርሎስ ከ12 ግዝት ውስጥ አንዱ ሲሆን የማቴወስን ወንጌል (ማቴ 12፣ 24-28) የተረጎመበት
ክፍል ነው፡፡ ወንጌሉን ይመልከቱ፡፡
ቅዱስ ቄርሎስ ከዚህ በላይ የተጠቀስውን ከተናገረ በኋላ ከቅዱሳን እንደ አንዱ፣ እንደ ፍጡር ከበረ እንዳይሉት ፈርቶ
በዚችው ቃለ ግዝት

 “ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ ኃይልን ሥልጣንን ከሚቀበሉ ከቅዱሳን እንደአንዱ አድርጎት
ከአባቱ ስልጣንም ልዩ አድርጎት ሰው እንደመሆኑ እንደ እኛ ከበረ፤ ወደሰማይም ይወጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ
ያደለውን ይቀበላል እንጂ የአምላክነትን ሥራ አይሠራም የሚል ሰው ቢኖር የዚች ግዝት ሥልጣን በእሱ አድራ
ትለየዋለች፡፡”(ሃ.አበው ቃለ ግዘት ዘቄርሎስ 121 ፥ 34)

ሲል በጽኑ ሥልጣን በማይፈታ ግዝት አውግዟል፡፡ መጻሕፍት ሰው እንደ መሆኑ “በመንፈስ ቅዱስ ከበረ” ቢሉ
ክርስቶስ በሰውነቱ በስግውነቱ መንፈስ ቅዱስ የባሕርይ ሕይወቱ ሆነው ሲል ነው እንጂ እንደ ቅዱሳን በጸጋው ያከበረው
አይደለም፡፡ ይኸንም (ሃ.አ. 73፣49) “በመንፈስ ቅዱስ ከበረ” የሚለው መንፈስ ቅዱስ የባሕርይው እንደሆነ ይገልጻል፡፡
ዮሐንስ አፈ ወርቅም በ3ኛው ድርሳን “አኮ ካልዕ ክብሩ እምአብ፤ ---- የወልድ ክብሩ ከአብ ልዩ አይደለም፤
ወንዕዶ ከመ ከማሁ ------- እንደ እርሱ ባለ አካል አከበረው እንጂ” እያለ ክብሩ የባሕርዩ እንደሆነ ተናግሯል፡፡

መንፈስ ቅዱስ ለምን ቅብዕ ተባለ ?


መንፈስቅዱስ ቅብዕ የተባለ ክብር ይግባውና ቅቤ ወይም ሽቶ ሆኖ ሳይሆን ምሳሌውን ለመፈፀም ነው ።

1) ቅቤ ቢበሉት አካለ ሥጋ ያለመልማል ፤ ቢቀቡት ፊት ያበራል ፀጉር ያለመልማል ። እንደዚህም ሁሉ መንፈስ


ቅዱስን ምግባር ሰርቶ ንስሐ ገብቶ ቢቀበሉት አካለ ነፍስ ያለመልማል ገፀ ነፍስ ያበራልና ።
2) ብረት በዛገ ጊዜ ቅቤ ቀብቶ ፀሀይ አሙቆ በጨርቅ ቢጠርጉት ወደቀደመ ጥራቱ ይመለሳል ። ነፍስም በኀጢአት
በክህደት በጎሰቆለች ጊዜ ሃይማኖት ይዞ ምግባር ሰርቶ ንስኀ ገብቶ መንፈስ ቅዱስን ቢቀበሉት ነፍስ ወደ ቀደመ
ንፅህናዋ ትመለሳለች ። ሥጋዬም ቅቤ በማጣት ከሳ እንዳለ ቅዱስ ዳዊት መዝ 108 ፥ 24
3) በዘመነ ኦሪት በነበረው ምሳሌ ጠርቶ ቅብዕ ይባላል ።በዘመነ ኦሪት የነበሩ ካህናት አበሞ ፣ ቀናንሞ ፣ ዘይት ፣
ቀፂመታት የተባሉ ሽቶዎችን በአንድ አድርገው ሊቀ ካህኑ ሲጸልይበት መንፈስ ቅዱስ ያድርበታል ። ከዚህ ሽቶ
እየተቀቡ ንጉሥ ፣ ሊቀካህን ይሆኑ ነበር ። ወልድም በሰውነቱ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ንጉሠ ነገሥት ፣
ሊቀካህናት ሆኗልና በምሳሌው ጠርቶ መንፈስቅዱስን ቅብዕ አለው ።

የመንፈስ ቅዱስ ግብር


በማህፀነ ድንግል ማርያም የመንፈስ ቅዱስ ግብራት አምስት ናቸው ።

1) ማንፃት
2) መክፈል
3) ማወሐድ
4) መፍጠር
5) ቅብዕ መሆን

33
1) ማንፃት
መንፈስ ቅዱስ ያነፃት እግዝእትነ ማርያምን ነው ። እመቤታችን ንፅህት በድንግልና ፣ ክብርት በልዕልና ፣ ንፅህተ ሥጋ
ወነፍስ ብትሆንም እንኳ የአምላክ እናት ለመሆን አትበቃም ነበርና የአምላክ እናት ለመሆን አበቃት ፣ እሳተ መለኮትን
በማህፀን መሸከም አስቻላት ፣ ከመቃጠል አዳናት ለማለት ነው እንጅ የእመቤታችን ንፅህናስ እንኳንስ ከሰው ከመላእክተ
ብርሃን ንፅህና ይበልጣል ።

አንድም አነፃት ማለት ልማደ አንስትን(የሴቶችን ልማድ) አጠፋላት ማለት ነው ። ሴቶች በዘር ፣ በሩካቤ ፣ በሰስሎተ
ድንግልና ይወልዳሉ ። እመቤታችን ግን ያለዘር ፣ ያለሩካቤ ፣ ያለሰስሎተ ድንግልና አምላክን እንድትፀንስ ፣ እንድትወልድ
ስለአደረጋት አነፃት አለ እንጅ ቀድሞ ኀጢአት ኖሮባት ኋላ አነፃት ማለት አይደለም ።

 መንፈስ ቅዱስ ቀደሰ ወአንጽሐ ሥጋሃ ለማርያም ወረሰያ ድሉተ ለተወክፎ ቃለአብ ።
(ሃ.አበው ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ፴ ፮ ፥ ፲ ፱ )
 መንፈስ ቅዱስ የማርያምን ሥጋ አነፃ ቀደሰ የአብ አካላዊ ቃልንም ለመጸነስ የበቃች አደረጋት ።
(ሃ.አበው ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ 36 ፥ 19 )

2)መክፈል
ለልማዱ በሩካቤ ነፍስ ሥጋ የሚሆን ዘር ከአባት ይከፈላል ። ነፍስ ሥጋ የሚሆን ደም ከእናት ይከፈላል ። ተከፈለ
የሚባለውም ባህርየ ሥጋ( መሬት፣ እሳት ፣ ውሃ ፣ነፋስ ) እና ግብረ ነፍስ(ለባዊነት ፣ ነባቢነት ፣ ሕያዊነት ) ናችው ። ረቂቅ
ነፍስ ከግዙፍ እናትና አባት ትከፈላለች ሰውም ይፈጠራል ። የሚከፈለውም ደመ ሩካቤ ነው ።

እንደዚህም ሁሉ መንፈስ ቅዱስ ከእግዝእትነ ማርያም ደመ ድንግልናን ከፈለ ። የተከፈለው ግን በዘር በሩካቤ ሳይሆን
በመንፈስ ቅዱስ ግብር ስለሆነ ደመ ድንግልና ይባላል ።

 ወገብረ ሎቱ ሥጋ እምደመ ድንግልና ሥጋሃ እመንፈስ ቅዱስ ። ዲዮናስዮስ ዘአንጾኪያ


 የከፈለ ፣ ያዋሐደ ፣ የፈጠረ መንፈስቅዱስ ነውና ። (ውዳሴ ማርያም ዘእሁድ ትርጓሜ ገፅ 163 (ማእጠንት
የሚለውን ክፍል በተረጎመበት አንቀጽ ))

3) ማዋሐድ
ከአባት ዘር ከእናት ደም ተከፍሎ እንዲወሐድ መንፈስቅዱስም ከእመቤታችን ደመ ድንግልናዋን ከፍሎ ከአካለ
ወልድ ጋር አዋሐደ ። ሳይከፈል አልተወሐደም ተከፍሎም ሳይወሐድ አልቆየም ። ሲወሐድ ሲከፈል አንድ ጊዜ ነው ።

4) መፍጠር
መፍጠር ማለት ነፍስ የሚሆነውን ባህርየ ነፍስ ማድረግ ፤ ሥጋ የሚሆነውን ባህርየ ሥጋ ማድረግ ነው ። ሲወሐድ
ሲፈጠር አንድ ጊዜ ነው ።

 ወእምደመ ድንግልናሃ በመንፈስ ቅዱስ ፈጠረ ሎቱ ሥጋ ዕጓለእምሕያው ዘከመ አርአየነ ዘቦቱ ነፍስ ነባቢት
ወለባዊት ። (ሃ.አበው ዘ አባ ገብርኤል ፺ ፬ ፥ ፲ ፩)
 በድንግልና ከፀና ባህርይዋ የምታውቅ የምትናገር ነፍስ ያለችው የእኛን የሚመስል የአዳምን ሥጋ በግብረ መንፈስ
ቅዱስ ሊወሐደው እንደፈጠረ አምናለሁ ። (ሃ.አበው ዘ አባ ገብርኤል 94 ፥ 11)

34
ውስተ ትርጓሜ ወንጌል ዘማቴዎስ በእንተ ዘይቤሎ መልአክ ኢትፍራህ ኦ ዮሴፍ ከመ ትንሥአ ለማርያም ፍኅርትከ
እስመ ዘይትወለድ እምኔሃ እመንፈስ ቅዱስ ውእቱ እስመ መንፈስ ቅዱስ ውእቱ ዘፈጠረ ሥጋ ውስተ ከርሰ ድንግል
ሥጋሁ ለቃል ውእቱ እምግብረ ሥምረቱ ለመንፈስ ቅዱስ ።
(ሃ.አበው ዘዮሐንስ አፈወርቅ ፷ ፮ ፥ ፮ ) ማቴ ፩ ፥ ፳ - ፳ ፭
 “ከእርሷ የሚወለደው በግብረ መንፈስ ቅዱስ ነውና ዮሴፍ ሆይ የታጨችልህን ማርያምን መቀበልን አትፍራ ብሎ
መልአክ ለዮሴፍ ስለተናገረው ቃል የማቴዎስን ወንጌል በተረጎመበት አንቀጽ በድንግል ማህፀን ሥጋን የፈጠረ
መንፈስ ቀዱስ ነውና የቃል ሰው መሆን የመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ከተፈፀመው ግብር የተነሳ ነው፡፡”
(ሃ.አበው ዘዮሐንስ አፈወርቅ 66 ፥ 6) ማቴ 1፥ 20-25
 የከፈለ ፣ ያዋሐደ ፣ የፈጠረ መንፈስቅዱስ ነውና ። ውዳሴ ማርያም ዘእሁድ ትርጓሜ ገፅ 163 (ማእጠንት
የሚለውን ክፍል በተረጎመበት አንቀጽ )

መፍጠር የመንፈስ ቅዱስ ግብር ነው ስላሉ የአብም የወልድም ግብር ነው እንጅ የመንፈስ ቅዱስ ግብር ብቻ አይደለም ።

አብ እንደፈጠረ ዮሐንስ አፈወርቅ ተናግሯል ።

 እስመ እግዚአብሔር ፈጠረ ሎቱ ሕያወ መቅደሰ በመንፈስ ቅዱስ ወቦቱ አድኀነ ዓለም ። (ሃ. አበው ዘዮሐንስ
አፈወርቅ ፷ ፰ ፥ ፵ ፫ )
 እግዚአብሔር ሕያው አምላክ የሆነ ሥጋን በመንፈስ ቅዱስ ፈጠረ ዓለምንም በእርሱ አዳነ ። (ሃ. አበው ዘዮሐንስ
አፈወርቅ 68 ፥ 43)
ወልድ እንደፈጠረ ደግሞ አዮክንድዮስ ተናግሯል ።

 ወለሊሁ ሐነፀ ሥጋሁ ዉስተ ከርሰ ድንግል ወኢተሳተፎ መኑሂ በፈጢረ ሥጋሁ አላ ለሊሁ ባህቲቱ ፈጠሮ ።
(ሃ.አበው ዘአዮክንድዮስ ፵ ፬ ፥ ፫)
 እርሱም ሥጋውን በድንግል ማህፀን ፈጠረ ሥጋውንም በመፍጠር ማንም ማን አጋዥ አልሆነውም እርሱ ራሱ
ፈጠረው እንጅ ። (ሃ.አበው ዘአዮክንድዮስ 44 ፥ 3)

ስለዚህ ሦስቱም አነጹ ፣ ከፈሉ ፣ አዋሐዱ ፣ ፈጠሩ ማለት ነው ። ሲዋሐድ ሲፈጠር አንድ ጊዜ ነው በተዋሕዶ እና
በመፍጠር መካከል ጊዜ አለ ከተዋሐደ በኋላ ተፈጠረ ካሉ እንደ አርዮስ ወልድን ፍጡር ማለት ይሆናልና ክህደት ነው ።
መፍጠር የሚባል ነገር በማህፀነ ማርያም የለም ማለት ደግሞ ወልድ የፍጡር ሥጋ አልተዋሐደም ማለት ስለሆነ ይህም
ክህደት ነው ። ስለዚህ ሲዋሐድ ፣ ሲቀባ ፣ ሲከፈል ፣ አንድ ጊዜ ነው ።ወልድ በሰውነቱ ፍጡር ይባለል እንጅ በመለኮትነቱ
ፍጡር ካሉት እንደ አርዮስ ወልድ ፍጡር ማለት ስለሆነ ክህደት ነው ።

5)ቅብዕ መሆን
ቅብዕ የሆነ በተለየ አካሉ በተለየ ግብሩ መንፈስ ቅዱስ ብቻ ነው ። አብ ቀባዒ ወልድ ተቀባዒ መንፈስ ቅዱስ ቅብዕ
እንደተባለ ።

ማንፃት ፣ መክፈል ፣ ማዋሐድ ፣ መፍጠር የመንፈስ ቅዱስ ስራ ነው ስላሉ የሦስቱ የአንድነት ስራቸው ነው እንጅ
የመንፈስቅዱስ ብቻ አይደለም ።ሥላሴ በመንፈስቅዱስ ህያዋን ሆነው በመስራታቸው ለመንፈስ ቅዱስ ተነገረ ።

35
ምስጢረ ቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ በመጽሐፍ ቅዱስ
 ወተንስኡ ነገስተ ምድር ወመላእክትኒ ተጋብኡ ምስሌሆሙ ህቡረ ላዕለ እግዚአብሔር ወላዕለ መሲሑ ።
(መዝ ፪ ፥ ፪)
 የምድር ነገሥታት ተነሡ፥ አለቆችም በእግዚአብሔርና በመሢሑ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ።(መዝ 2፥ 2)
 አፍቀርከ ጽድቀ ወአመፃ ጸላዕከ በእንተዝ ቀብዓከ እግዚዚአብሔር አምላክከ ቅብዓ ትፍሥሕት እምአለ ከማከ ።
(መዝ ፵ ፬ ፥ ፯ )
 ጽድቅን ወደድህ ዓመፃንም ጠላህ፤ ስለዚህ ከባልንጀሮችህ ይልቅ እግዚአብሔር አምላክ የደስታ ዘይትን ቀባህ።
(መዝ 44፥ 7 )
 ናሁ ቁልዔየ ዘአኀዝክዎ ወእስራኤልኒ ኅሩይየ ዘተወክፈቶ ነፍስየ ወወኀብኩ መንፈስየ ድቤሁ ወናሁ ያመፅእ ፍትሐ
ለአሕዛብ ።(ኢሳ ፵ ፪ ፥ ፩)
 እነሆ ደግፌ የያዝሁት ባሪያዬ፤ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ምርጤ፤ በእርሱ ላይ መንፈሴን አድርጌአለሁ፥ እርሱም
ለአሕዛብ ፍርድን ያወጣል።(ኢሳ 42 ፥ 1 )
 መንፈሰ እግዚአብሔር ላዕሌየ ዘቀብዓኒ ዘበእንቲአሁ አሥተፍሥሖሙ ለነዳያን ፈነወኒ ወእፈውሶሙ ለቁሱላነ ልብ
ወእስብክ ሎሙ ግዕዛነ ለፂውዋን ወይርአዩ እውራን ። (ኢሳ ፷ ፩ ፥ ፩)
 የጌታ የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች የምሥራችን እሰብክ ዘንድ እግዚአብሔር ቀብቶኛልና፤
ልባቸው የተሰበረውን እጠግን ዘንድ፥ ለተማረኩትም ነጻነትን ለታሰሩትም መፈታትን እናገር ዘንድ ልኮኛል።
(ኢሳ 61 ፥ 1 )
 ሰንበታተ አድሞሙ ለሕዝብከ ወለሃገርከ ቅድስት ከመ ትሰለጥ ኃጢአት ወትትሐተም ጌጋይ ወይደመሰስ አበሳ
ወትሠረይ አመፃ ወትመጽእ ጽድቅ እንተ ለዓለም ወይትዓተብ ራእየ ነቢያት ወይትቀባዕ ቅዱሰ ቅዱሳን ። አእምር
ወለቡ እምፀዓተ ቃሉ ዘታወሥእ ወትትሐነጽ ኢየሩሳሌም እስከ ክርስቶስ ንጉስ ሰብአተ ሰንበታተ ስሳ ወክልኤተ
ሰንበታተ ይትመየጥ ወይትሐነፅ መርኅባ ወዓረፍታ ወይትከዓው መዋዕል ።(ዳን ፱ ፥ ፳ ፬ - ፳ ፭ )
 ዓመፃን ይጨርስ፥ ኃጢአትንም ይፈጽም፥ በደልንም ያስተሰርይ፥ የዘላለምን ጽድቅ ያገባ፥ ራእይንና ትንቢትን
ያትም፥ ቅዱሰ ቅዱሳኑንም ይቀባ ዘንድ በሕዝብህና በቅድስት ከተማህ ላይ ሰባ ሱባዔ ተቀጥሮአል።ስለዚህ እወቅ
አስተውልም፤ ኢየሩሳሌምን መጠገንና መሥራት ትእዛዙ ከሚወጣበት ጀምሮ እስከ አለቃው እስከ መሢሕ ድረስ
ሰባት ሱባዔና ስድሳ ሁለት ሱባዔ ይሆናል፤ እርስዋም በጭንቀት ዘመን ከጎዳናና ከቅጥር ጋር ትሠራለች።
(ዳን 9 ፥ 24 – 25)
 ወይቤሎሙ አንትሙኬ መነ ትብሉኒ ወተሰጥዎ ጴጥሮስ ወይቤሎ አንተ ውእቱ ክርስቶስ (ማር ፰ ፥ ፳ ፱)
 እናንተስ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? ብሎ ጠየቃቸው። ጴጥሮስም፦ አንተ ክርስቶስ ነህ ብሎ መለሰለት።
(ማር 8 ፥ 29)
 ወአውሥአ ወይቤሎ አንትሙ መነ ትብሉኒ ወተሰጥዎ ጴጥሮስ ወይቤሎ አንተ ውእቱ መሲሑ ለእዚአብሔር ።
(ሉቃ ፱ ፥ ፳)
 እናንተስ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው። ጴጥሮስም መልሶ፦ ከእግዚአብሔር የተቀባህ ነህ አለ።
(ሉቃ 9 ፥ 20)
 ወናሁ አነ እፌኑ ተስፋሁ ለአቡየ ላእሌክሙ ወአንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም እስከ ትለብሱ ኃይል እምአርያም
(ሉቃ ፳ ፬ ፥ ፵ ፱)
 እነሆም፥ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም
ከተማ ቆዩ። (ሉቃ 24 ፥ 49)
 “ወበከመ ለአብ ቦቱ ሕይወት ኀቤሁ ከማሁ ለወልድኒ ወሀቦ ህይወተ ከመ ይኩን ሕይወት ኀቤሁ ።ወወሀቦ
ሥልጣነ ከመ ይግበር ፍትሐ ወኩነኔ እስመ ወልደ እግዚአብሔር ወልደ እጓለ እመሕያው ውእቱ ።

36
(ዮሐ ፭ ፥ ፳ ፮)
 አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው እንዲሁ ደግሞ ለወልድ በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታልና።የሰው ልጅም ስለ
ሆነ ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን ሰጠው። (ዮሐ 5 ፥ 26)
 “ወዘእግዚአብሔር ፈነዎ ቃለ እግዚአብሔር ይነግር እስመ አኮ በመሰፈርት ዘይሁብ እግዚአብሔር መንፈሶ አብሰ
ያፈቅር ወልዶ ወኩሎ ኩነኔሁ አወፈዮ ለወልዱ ውስተ እዴሁ ” (ዮሐ ፫ ፥ ፴ ፬ - ፴ ፭)
 እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራልና፤ እግዚአብሔር መንፈሱን ሰፍሮ አይሰጥምና።አባት
ልጁን ይወዳል ሁሉንም በእጁ ሰጥቶታል።(ዮሐ 3 ፥ 34 – 35 )
 ለምንት አንገለጉ አሕዛብ ወለሕዝብኒ ነበቡ ከንቶ ወተንሥኡ ነገስተ ምድር ወመላእክትኒ ተጋብኡ ምስሌሆሙ
ኅቡረ ላዕለ እግዚአብሔር ወላዕለ መሲሑ አማን አንገለጉ በዛቲ ሃገር ላዕለ ቅዱስ ወልድከ ኢየሱስ ዘቀባዕካሁ
ሄሮድስ ወጲላጦስ ጰንጤናዊ ምስለ ሕዝቢሆሙ ወሕዝበ እስራኤል ከመ ይግበሩ በከመ ሥርዓተ እዴከ ወምክርከ
ከመ ይኩን ።(ሐዋ ፬ ፥ ፳ ፭ - ፳ ፰)
 አሕዛብ ለምን አጕረመረሙ? ሕዝቡስ ከንቱን ነገር ለምን አሰቡ?የምድር ነገሥታት ተነሡ አለቆችም በጌታና
በተቀባው ላይ አብረው ተከማቹ ብለህ የተናገርህ አምላክ ነህ።በቀባኸው በቅዱሱ ብላቴናህ በኢየሱስ ላይ
ሄሮድስና ጴንጤናዊው ጲላጦስ ከአሕዛብና ከእስራኤል ሕዝብ ጋር፥ እጅህና አሳብህ እንዲሆን አስቀድመው
የወሰኑትን ሁሉ ሊፈጽሙ፥ በዚች ከተማ በእውነት ተሰበሰቡ።(ሐዋ 4 ፥ 25 – 28)
 በኢየሱስ ዘእምናዝሬት ዘቀብዖ እግዚአብሔር መንፈሰ ቅዱሰ ወኀይለ ወውእቱ መጽአ ወረድኦሙ ለእለ
ይትዔገሎሙ ሰይጣን እስመ እግዚአብሔር ምስሌሁ (ሐዋ ፲ ፥ ፴ ፰)
 እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም
የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤(ሐዋ10 ፥ 38)
 በእንተ ወልዱ ዘተወልደ ወወጽአ እምዘርአ ዳዊት በሥጋ ሰብ ወአርአየ ከመ ወልደ እግዚአብሔር ውእቱ በኃይሉ
ወበመንፈሱ ቅዱስ፡፡ (ሮሜ ፩ ፥ ፬)
 ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል
የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። (ሮሜ 1፥4)
 አፍቀርከ ጽድቀ ወጸላዕከ አመፃ ወበእንተዝ ቀብዓከ እግዚዚአብሔር አምላክከ ቅብዓ ትፍሥሕት ዘይኄይስ እምአለ
ከማከ ። (ዕብ ፩ ፥ ፱ )
 ጽድቅን ወደድህ ዓመፅንም ጠላህ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ ከጓደኞችህ ይልቅ በደስታ ዘይት ቀባህ ይላል
(ዕብ 1፥9)
 ወአንትሙሰ ቅብዓት ብክሙ እምነ መንፈስ ቅዱስ ወተአምሩ ኩሎ ። (፩ ዮሐ ፪ ፥ ፳)
 እናንተም ከቅዱሱ ቅባት ተቀብላችኋል፥ ሁሉንም ታውቃላችሁ ። (1 ዮሐ 2 ፥20)
 ወአንትሙሰ ቅብዓት ብክሙ እንተ ነሣእክሙ እምኀቤሁ ወትነብር ኀቤክሙ ወኢትፈቅዱ መኑሂ ይምሃርክሙ አላ
መንፈሰ ዚአሁ ይሜህረክሙ በእንተ ኩሉ ወእሙን ውእቱ ወኢኮነ ሐሰተ ወበከመ ትምህርትክሙ ንበሩ ባቲ
(፩ ዮሐ ፪ ፥ ፳ ፯)
 እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን
የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥ እናንተንም
እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ።(1 ዮሐ 2 ፥27)
 ወመኑ ውእቱ ሐሳዊ ዘእንበለ ዘይክሕድ ወይብል እስመ ኢየሱስ ኢኮነ መሲሐ ወዝንቱ ውእቱ ሐሳዌ መሲሕ
ዘይክህድ በአብ ወበወልድ (፩ ዮሐ ፪ ፥ ፳ ፪)
 ክርስቶስ አይደለም ብሎ ኢየሱስን ከሚክድ በቀር ውሸተኛው ማን ነው? አብንና ወልድን የሚክድ ይህ የክርስቶስ
ተቃዋሚ ነው።(1 ዮሐ 2 ፥ 22)

37
ወልደ አብ
ወልደ አብ የቃሉ ትርጉም የአብ ልጅ ማለት ነው ። የወልድ ልደቱ ሁለት ነው ።

፩. እምቅድመ ዓለም ከአብ ያለእናት ተወልዷል (ወልደ አብ )

፪. እምድኅረ ዓለም ከእመቤታችን ያለአባት ተወልዷል (ወልደ ማርያም )

 ወይደልወነ ንእመን ከመዝ በእግዚአብሔር ቃል ከመ ቦቱ ፪ቱ ልደት ። ፩ዱ እምአብ እምቀዲሙ እንበለ ሱታፌ


ምስካበ አንስት ልደት ዘኢይትረከብ ወካልእ በደኃሪ መዋእል እምቅድስት ድንግል ማርያም እንበለ ሩካቤ ተባእት
ልደት ዘኢይትነገር ወኢይትረከብ ። (ሃ. አበው ሳዊሮስ ዘአንፆኪያ ፹ ፬ ፥ ፰)
 ሁለት ልደት እንዳለው በእግዚአብሔር ቃል እንዲሁ ልናምን ይገባናል። አንዱ ቅድመ ዓለም ከአብ ያለእናት
የተወለደው የማይመረመር ልደት ነው ። ሁለተኛውም በኋላ ዘመን ከንፅህት ድንግል ማርያም ያለአባት
የተወለደው የማይመረመር የማይነገር ልደት ነው ። (ሃ. አበው ዘሳዊሮስ ዘአንፆኪያ 84 ፥ 8)

በማህፀነ ድንግል ማርያም ወልድ በተለየ አካሉ የተዋሐደውን ሥጋ መንፈስ ቅዱስ በተለየ አካሉ በህይወትነት ግብሩ
የባህርይ ሕይወት ሆኖታል ። አብም በተለየ አካሉ በወላዲነት ግብሩ የባህርይ ልደት ወልዶታል ። ወልድ እምቅድመ ዓለም
በመለኮቱ አካሉ ከአብ አካል ሳይከፈል በራሱ አካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ አካል ዘእምአካል ከአብ በተወለደበት ልደት
ዛሬም መለኮት ሰው ቢሆን በማህፀነ ድንግል ማርያም በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ አካሉ ከአብ አካል ሳይከፈል በራሱ አካል
ባሕርይ ዘእምባሕርይ አካል ዘእምአካል ከአብ በሥጋው ተወልዷል ።

ወልድን እምቅድመ ዓለም በመለኮቱ ተወለደ ባሉ ጊዜ በመለኮትነቱ መቀበል የለበትምና መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ
ተወለደ አይባልም ። በእመቤታችን ማሕፀን ግን ወልድ የተዋሐደው የፍጡር ሥጋ ስለሆነ ይህ የፍጡር ሥጋ ፈጣሪ ይሆን
ዘንድ ወልድ በሥጋ ርስት መንፈስቅዱስን በመላ ተቀብሎ ከአብ የባህርይ ልደት ተወለደ ።

 እግዚአብሔር ይቤለኒ ወልድየ አንተ ወአነ ዮም ወለድኩከ ። (መዝ ፪ ፥ ፯ ፡ ዕብ ፩ ፥ ፭)


 እግዚአብሔር አለኝ፦ አንተ ልጄ ነህ፥ እኔ ዛሬ ወለድሁህ። (መዝ 2 ፥ 7 ፡ ዕብ 1 ፥ 5)
 “ይቤ ዳዕሙ ለሊሁ አክበሮ ዘይቤሎ ወልድየ አንተ ወአነ ዮም ወለድኩከ ፡፡”
(ድርሳነ ሐንስ አፈወርቅ ድርሳን ፰ ፥ ፷ ፱ ገጽ ፻ ፸ ፰)
 ዳግመኛም እንዲህ አለዉ አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወለድኩህ ይህንን ማለቱ እራሱ ስላከበረዉና ስለ ሾመዉ ነዉ ።
(ድርሳነ ሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 8 ፥ 69 ገጽ 178)

ትርጉሙም ”እግዚአብሔር“ የተባለ አብ ነው ። ”አንተ ልጄ ነህ“ ማለቱ እምቅድመ ዓለም የባሕርይ ልጁ መሆኑን
ሲያጠይቅ ነው። እኔ ዛሬ ወለድሁህ ማለቱ ዛሬም በሰውነቱ የባህርይ ልደት እንደወለው ሲያጠይቅ ነው ። ቅዱስ ዳዊትም
ለእርሱ አስመስሎ ለወልድ በትንቢት ተናግሮታል ። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መዝ 2 ፥ 7ን ሲተረጉም እንዲህ ብሏል ፦

 “ይቤ ዳዕሙ ለሊሁ አክበሮ ዘይቤሎ ወልድየ አንተ ወአነ ዮም ወለድኩከ ፡፡እንዲህ አለ።እመቦ ዘይብል ዝኑ
ይትበሃል በእንተ ወልድ ወልድየ አንተ ያለውን አይሻውም ወአነ ዮም ወለድኩከ ያለው ለሹመቱ ይነገራልን?

የሚል ሰው ቢኖር ንብሎ እወ ይትበሃል አወ ለሹመቱ ይነገራል ብለን እንመልስለታለን ። (ሐተታ)ወአነ ዮም

ወለድኩከ ያለው መወለዱን ያስረዳል እንጅ መሾሙን ያስረዳልን የልጅነቱን ለሹመቱ ስለምን ምስክር አደረገው?

38
ቢሉ ቢወልደው እንጅ ሾመው እስመ ዝንቱ ይጸንዕ ወይረትዕ በእንቲአሁ ወአነ ዮም ወለድኩከ ያለው ስለሹመቱ
ይነገር ዘንድ ይገባልና ። እስመ ዝንቱ ሥዩም ወፍንው እምኀበ እግዚአብሔር ከእግዚአብሔር ስለተሾመ በከመ
ይቤ በውስተ ካልዕ ገጸ መካን አንተ ካህኑ ለዓለም በከመ ሢመቱ ለመልከ ጼዴቅ በሌላ አንቀጽ አንተ ካህኑ
ለዓለም በከመ ሢመቱ ለመልከ ጼዴቅ እንዳለ ስለተሾመ ። (አንድም )ከእግዚአብሔር ተሹሟልና በሌላ
አንቀጽ ቀደሶ ወአክበሮ እንዳለ ወአነ ዮም ወለድኩከ ያለው ስለሹመቱ ይነገር ዘንድ ይገባልና አንተ ካህኑ ለዓለም
ይቤ የቀረው ንባብ ። (አንድም )ነቢይ ከተናገረው ነገር አምጥቶ አንተ ካህኑ ለዓለም ብሎ ያርኢ ያስረዳል ።
ስለዚህ ይደረግ ዘንድ ያለውን ነቢይ የተናገረውን አንተ ካህኑ ለዓለም ብሎ ተናገረ ። ይቤ ሲል አጠገቡ ቢያገኘው
አነበበው ። እመቦ ሲል ካነበበው ዘንድ እግረ መንገዱን ተረጎመው ወአነ ዮም ወለድኩከን አይሻውም ወልድየ
አንተ ያለውን ስለባህርይ ልጅነቱ ይነገራልን?የሚል ሰው ቢኖር አወን ስለባህርይ ልጅነቱ ይነገራል ብለን

እንመልስለታለን ።( አንድም) ወአነ ዮም ወለድኩከን ይሻል፣ የባሕርይ ልጁን እንደገና በሥጋ የባሕርይ ልጅ
አድርጎታልና ወልድየ አንተ ያለዉ ስለ ባሕርይ ልጅነቱ ይነገር ዘንድ ይገባልና ። …………..እንዲህ ከሆነ አንተ ካህኑ
ለዓለም ያለው ክብር ምስጋና ይግባውና ለክርስቶስ ብቻ ይገባል እንጅ አንተ ካህኑ ተብሎ የተነገረለት ማንም ማን
የለ ብዬ እመልስልሃለሁ ። ”
(ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 8 ፥ 69 -81 ገፅ 178 - 179)

አብ ወልድን በመንፈስ ቅዱስ በማህፀነ ማሪያም እዳከበረው እንደወለደው የአገራችን ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንዲህ
ብሏል ፦

 አብኒ ወለደ ዘኢዚአሁ ሥጋ በዘዚአሁ መለኮት ምስለ ዘዚአሁ ኃይል ዘህልውና አምላክ ።
(መጽሐፈ ምስጢር ፫ ፥ ፵ ፮)
 ድንግል ለእርሷ በተገባ ሥጋዌ የእሷ በሆነ ስጋ የእሷ ያልሆነውን መለኮት ወለደችው አብም የባህሪይ ያልሆነውን ስጋ
የባህሪው በሆነ የህልውና አምላክ ኃይል ጋር በሆነ መለኮት ወለደው ። (መጽሐፈ ምስጢር 3 ፥ 46)

እምቅድመ ዓለም በመለኮቱ ወልድ ከአብ ተወለደ ብለናል ። ኋላም በማህፀነ ማርያም በሰውነቱ ከአብ ተወለደ
እንላለን ። ዳግመኛም ከእመቤታችን በሥጋ በከብት በረት ተወለደ እንላለን ። ይህ ሦስት ልደት አይሆንምን ? ቢሉ
እምቅድመ ዓለም በመለኮቱ የተወለደው ልደት እና በማህፀነ ማርያም በሥጋው በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ የተወለደው ልደት
አንድ ልደት ይባላል እንጅ ሁለት ልደት አይባልም ። ምክንያቱም እምቅድመ ዓለም እና ኋላም በሰውነቱ የወለደው አብ
ነው። ተወላዲውም ራሱ ወልድ በሥጋው ነው ። የጥንት የባህርይ ሕይወቱ መንፈስ ቅዱስም ስላልተለወጠ አንድ ልደት
ነው። ልዩነቱ መንፈስ ቅዱስን ሳይቀበል እና ተቀብሎ መወለዱ ብቻ ነው ።

 ወኢየአምሩ ወኢበአሐዱ ፍና ዘክርስቶስ ምሥጢረ ከመ እግዚአብሔር አብ ወለዶ ለወልድ እምህላዌሁ በአሐቲ


ልደት ። ቄርሎስ ሥጣ ፳ ፬
 በእንተ ወልዱ ዘተወልደ ወወጽአ እምዘርአ ዳዊት በሥጋ ሰብ ወአርአየ ከመ ወልደ እግዚአብሔር ውእቱ በኃይሉ
ወበመንፈሱ ቅዱስ፡፡ሮሜ ፩ ፥ ፬
 ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል
የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። (ሮሜ 1፥4)

“ ወአርአየ ከመ ወልደ እግዚአብሔር ውእቱ በኃይሉ ወመንፈሱ(በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ


ነው) ” ማለቱ መለኮት ሰው ቢሆን በማኅጸነ እግዝትነ ማርያም በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከአብ የተወለደውን ልደት ሲናገር
ነው:: “ ወመጽአ እምዘርአ ዳዊት በሥጋ ሰብእ (በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ) ” ማለቱ ከእግዝትነ ማርያም በሥጋ

39
መወለዱን ሲናገር ነው:: 1ቆሮ 11፥3 “ ወርእሱ ለክርስቶስ እግዚአብሔር አብ(የክርስቶስም ራስ እግዚአብሔር) ” ያለውን
ቄርሎስ ሲተረጉመው እስመ እምኔሁ ውእቱ በህላዌ ወተወልደ ቃል እምእግዚአብሔር አብ ዓዲ በሥጋ:: እስመ እምኔሁ
ውእቱ በህላዌ ማለቱ እምቅድመ አለም በመለኮቱ ከአብ የተወለደውን ልደት ሲናገር ነው:: ወተወልደ ቃል እምእግዚአብሔር
አብ ዓዲ በሥጋ ማለቱ መለኮት ሰው ቢሆን ከአብ በባህርይ የተወለደውን ልደት ሲናገር ነው:: ሳዊሮስም እመንዎኬ ከመ
ውእቱ ወልደ እግዚአብሔር በመለኮቱ እምቅድመ መዋዕል ወአዝማን ወበትስብእቱ አመ ዕድሜ መዋዕል ካዕበ እመንዎ ከመ
ውእቱ ወልደ ማርያም መለኮት በትስብእቱ ብሏል:: እምቅድመ አለም በመለኮቱ የተወለደው ልደትና ዛሬ በማኅጸነ እግዝትነ
ማርያም በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከአብ የተወለደው ልደት ምንም ጊዜ ቢለየው በግብር በምስጢር አንድ እንደሆነ ሲያጠይቅ
እመንዎኬ ለክርስቶስ ከመ ውእቱ ወልደ እግዚአብሔር በመለኮቱ እምቅድመ መዋዕል ወአዝማን ወበትስብእቱ አመ ዕድሜ
መዋዕል ብሎ ተናገረ ከእመቤታችን በሥጋ የተወለደው ልደት ሁለተኛ እንደሆነ ሲያጠይቅ ካዕበ እመንዎ ከመ ውእቱ ወልደ
ማርያም መለኮት በትስብእቱ ብሎ ተናገረ:: ይህን ጊዜ ሦስት ልደት ቢሆን ኖሮማ ሥልሰ እመንዎ ባለው ነበር እንጅ ካዕበ
እመንዎ ባላለው ነበር::

ስለዚህ ሁለት ልደት የተባሉት 1 ወልደ አብ

2 ወልደ ማርያም ናቸው ።

ወልድ እምቅድመ ዓለም በመለኮቱ እምድኅረ ዓለም በሰውነቱ ለአብ አንድ የባሕርይ ልጁ ነው ።

 አጠየቀነ በመለኮቱ ወበትስብእቱ ከመ ወልድ ዋህድ ለአቡሁ ። ሳዊሮስ ዘእስሙናይን ????

ይህ ወልድ የተዋሐደው ሥጋ ቅድመ ተዋሕዶ ከሥላሴ እንኳንስ የባሕርይ ልጅነት ይኖረው የጸጋ ልጅነት የሌለው ባዕድ
ነበረና አምላክ ይሆን ዘንድ አብ ወለደው መንፈስ ቅዱስ ሕይወት ሆነው ። ስለዚህ ከቅድመ ዓለም ልደቱ ጋር አንድ
ለማድረግ በሰውነቱ የባሕርይ ሕይወቱ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ከአብ ተወለደ ።

 አንተ ልጄ ነህ፥ እኔ ዛሬ ወልጄሃለሁ፥ ደግሞም፦ እኔ አባት እሆነዋለሁ እርሱም ልጅ ይሆነኛል ያለው ከቶ ለማን
ነው? ዕብ 1፥ 5

ወልድ በሥጋ ርስት የባሕርይ ህይወቱ መንፈስ ቅዱስን ከአካሉ ጋር በመላ ተቀብሎ እርሱ ከአብ የባህርይ ልደት ተወልዶ
እኛን የፀጋ ልደት ይወልደናል ።

 እግዚአብሔር አብ ወእቱ አቡሁ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ በህላዌ መለኮቱ ወአኮ በፀጋ ወውእቱ አቡሆሙ ለአርዳኢሁ
በጸጋሁ እግዚአብሔር አብ አምላኩ ለወልድ ወእቱ በእንተ ትስብእቱ ወአቡሁ በእንተ መለኮቱ ቀዳማዊ፡፡
 እግዚአብሔር አብ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በባሕርየ መለኮቱ አባቱ ነው ለሐዋርያት ግን በሰጣቸው ጸጋ አባታቸው ነው
ሰው ስለሆነ እግዚአብሔር አብ ለወልድ አምላኩ ነው፤ ስለቀዳማዊ ባሕርዩም አባቱ ነው፡፡ ሃ.አ.ክ.1 ቁ 1. ? (መልሕቅ ሃ.አ
54፤ 7-9)????

አብ ወልድን በሥጋ ርስት የወለደው በዘመነ ዮሐንስ መጋቢት 29 ቀን ዕለተ እሁድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል
ማርያም የቅዱስ ገብርኤልን ቃል በተቀበለች ጊዜ ሲሆን እመቤታችን ድንግል ማርያም ወልድን በሥጋው የወለደችው
በዘመነ ማቴዎስ ታህሳስ 29 ቀን ዕለተ ሠሉስ ነው:: ።

ወልደ አብ በመጽሐፍ ቅዱስ


 እግዚአብሔር ይቤለኒ ወልድየ አንተ ወአነ ዮም ወለድኩከ ። (መዝ ፪ ፥ ፯ )
 እግዚአብሔር አለኝ፦ አንተ ልጄ ነህ፥ እኔ ዛሬ ወለድሁህ። (መዝ 2 ፥ 7 )

40
 ለመኑ እመላእክቲሁ ይቤሎ እም አመ ኮነ ወልድየ አንተ ወአነ ዮም ወለድኩከ ።ወካእበ ይቤ አነ እከውኖ አባሁ
ወውእቱ ይከውነኒ ወልድየ ።( ዕብ ፩ ፥ ፭)
 ከመላእክትስ፦ አንተ ልጄ ነህ፥ እኔ ዛሬ ወልጄሃለሁ፥ ደግሞም፦ እኔ አባት እሆነዋለሁ እርሱም ልጅ ይሆነኛል
ያለው ከቶ ለማን ነው?( ዕብ 1 ፥ 5)
 በእንተ ወልዱ ዘተወልደ ወወጽአ እምዘርአ ዳዊት በሥጋ ሰብ ወአርአየ ከመ ወልደ እግዚአብሔር ውእቱ በኃይሉ
ወበመንፈሱ ቅዱስ፡፡ሮሜ ፩ ፥ ፬
 ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል
የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። (ሮሜ 1፥4)
 ወእንዘ ይትናገሩ መጽአ ደመና ብሩህ ወጸለሎሙ ወናሁ መጽአ ቃል እም ውስተ ደመና ዘይብል ዝንቱ ውእቱ
ወልድየ ዘአፈቅር ዘቦቱ ሠመርኩ ።(ማቴ ፲ ፯ ፥ ፭)
 እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው
ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።(ማቴ 17 ፥ 5)

በተዋሕዶ ከበረ
በተዋህዶ ከበረ ማለት መለኮታዊ ቃል ከሥጋ ጋር በተዋህደ ጊዜ ቃል ስጋን አከበረው አካለ መለኮት እና አካለ ስጋ
ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባህርይ አንድ ባህርይ በሆኑ ሰዓት በመለኮት ርስት ስጋ ከበረ ። የመንፈስ ቅዱስ ህይወት
አያስፈልገውም እራሱን በራሱ ያከብራል ማለት ነው ፡፡

ወልድ ዋሕድ በተዋሕዶ ከበረ ከተባለ አክባሪው፣ ከባሪው፣ ክብሩ ማነው? “አክባሪና ክብር ቃል፣ ከባሪ ሥጋ ነው፤ ቃል
ሥጋን አከበረው ማለት ስለሆነ ፡፡” አክባሪ አንድ ከባሪ አንድ “ወልድ ዋሕድ” ወዴት ይሆናል ? ቃል ሥጋን ታከበረ፤
አክባሪ ቃል፣ ከባሪ ሥጋ ተብሎ በአካል፣ በግብር ይለያል “አክባሪ የቃል /የመለኮት/ አካል ሲሆን ከባሪ የሥጋ አካል፤
ማክበር የመለኮት ግብር፣ መክበርም የፍጡር ግብር ስለሆነና መለኮት የመለኮትን ሥራ ይሠራል፤ ትስብእትም የሥጋን ሥራ
ይሠራል የሚል ስለሚሆን ነው፡፡ “እንቲያሁ ለቃል ኮነ ለሥጋ ወእንቲያሁ ለሥጋ ኮነ ለቃል ዘእንበለ ኃጢኣት ባሕቲታ”
“እንቲያሁ ለቃል ወእንቲያሁ ለሥጋ” የሚለው በቃል አካልና በሥጋ አካል ያለውን ሁነት ብቻ የምታሳይ እንጂ በአብና
በመንፈስ ቅዱስ አካል ያለውን የምትነግር አይደለችም ፡፡

በተዋህዶ ከበረ ስለምን ክህደት ሆነ?

1.ማኅበረ ቅዱሳን በሁለቱ ኪዳናት በተባለው መጽሐፍ ላይ ተቀባ ማለት ከበረ ማለት ሲሆን አክባሪውም ከባሪውም ራሱ
ነው ይላሉ ፡፡

አካለ ቃል አክባሪ አካለ ሥጋ ከባሪ ካልን ተዋሕዶ ኅድረት ይሆንብናል፤ክርስቶስ መባልንም ለሥጋ ብቻ እንድንሰጥ
ያስገድደናል (ቅዱስ ዳዊት በመዝ 44፣7 ጽድቅን ወደድክ አመጻንም ጠላህ ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክ ከባለንጀሮችህ
ይልቅ የደስታ ዘይትን ቀባህ ። አምላክህ ቀባህ ያለው ሥግው ቃልን እንጂ ሥጋን ብቻ አይደለምና)፡፡ክርስቶስ ክርስቶስን
ቀባው ቢሉ ተዋሕዶ ይጎድላል፡፡ መጽሐፉ ተቀባ-ተዋሐደ ነው የሚሉትን (የመዝሙረ ዳዊት አንድምታንና የኢትዮጵያ
ኦ.ተ.ቤ/ክ ታሪክ-አቡነ ጎርጎርዮስን) ነቅፏል፡፡ተቀብዐ ከበረ ማለታቸው ደግ ነው ሐዋ 10÷38 እግዚአብሔር የናዝሬቱን
ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው ይላልና ቀባውን አከበረው ካሉት እውነቱን ተቀበሉ ማለት ነው፡፡

2. ሁለት አካል-ሁለት ባሕርይን ያስከትላል፡- ተዋሕዶ ያገናዝባል (እንቲአሁ ለቃል ኮነ ለሥጋ ወእንቲአሁ ለሥጋ ኮነ ለቃል
እንዳለ ቅዱስ ቄርሎስ)፤ነገር ግን እነርሱ አካለ ሥጋን በርስቱ አካለ ቃል በርስቱ አከበረ ይላሉ (ማገናዘብን ትተው)፡፡አክባሪና
ከባሪ ከሆኑ እንደ ልዮን ግብር መለየት ነው፡፡ግብር ከተለየ አካልና ባሕርይ አይቀርምና ሁለት አካል ማድረግ ነው፡፡

41
በተለየ ክብሩ እራሱን ያከብራል ፤ አክባሪው ቃል ተከባሪው ሥጋ ነው ማለት ክህደት ነው ። ምክንያቱም ቃል አክባሪ
ሥጋ ተከባሪ ከሆነ ግብር መለየት ነው ። ቃልን አክባሪ አድርጎ አባት ፤ ሥጋን ተከባሪ አድርጎ ልጅ ፤ በማለት ግብር
ይለያል። ግብር ከተለየ ደግሞ አካል እና ባህርይ አይቀርም እና ሥላሴን በአካል በባህርይ በግብር መለየት ይሆናል ።

አንድም ቃል ሥጋን ካከበረው ይህ ክብር አካላዊ ክብር ነውና ቃል ከራሱ አካል ጋር ሌላ አካላዊ ክብር አለው ፤ ለአብ
እና ለመንፈስ ቅዱስም እንዲሁ የየራሳቸው አካላዊ ክብር አላቸው ያሰኛል ። ይህም ሥላሴን ስድስት አካላት ሦስት
አማልእክት ማድረግ ነው ።

 እስመ አዔረዮ ለወልድ ምስለ አቡሁ ፤ወንእዶ ከመ ከማሁ ፤ወአስተላጸቆ ምስሌሁ ፡፡


(ዮሐንስ አፈወርቅ ድረሳን ፫ ቁ ፺ ፱ - ፻ ፩ ገጽ ፸ ፯ )
 ወልድን ከአብ ጋር አስተካክሎታልና ፤ እንደ እሱ አካል ባለ አካል አክብሮታልና፤ ከእሱ ጋር በባህሪ አንድ
አድርጎታልና ።(ዮሐንስ አፈወርቅ ድረሳን 3 ቁ 99 – 101 ገጽ 77 )

“ እንደ እሱ አካል ባለ አካል አክብሮታልና ” ሲል አክባሪው አብ ሲሆን “ እንደሱ ባለ አካል ” የተባለው የመንፈስ ቅዱስ
አካል ነው ። ምንም እንኳ ሥላሴ በአካል ሦስት ቢሆኑም የአብ አካል ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ አካል ጋር ተመሳሳይ ነውና።

3. ውላጤን (መለወጥን) ያመጣል፡- ሥጋ በርስቱ ከበረ፤ፈጣሪ ሆነ ከተባለ ተዋሕዶ አገናዛቢ ነውና ቃልንም በባሕርይው
በርስቱ ፍጡር ማለት ይሆናል፡፡በተዋሕዶ ሥጋ በርስቱ ወልደ አብ ከሆነ ቃልም በርስቱ ወልደ ማርያም ይሆናል፡፡እንደዚህ
አንልም ካሉ ተዋሕዶ ኅድረት (ቃል በሥጋ አዳሪ-አልተዋሐደም) ማለት ይሆናል፡፡በኅድረት ደግሞ የሥጋ ሁሉ ለቃል
አይተላለፍምና ተዋሕዶ ግን አገናዛቢ ነውና በመንፈስ ቅዱስ ካልተሞላ ከላይ ከጠቀስናቸው ኑፋቄያት አያድንም ፡፡አንድም
ሥጋን በርስቱ አካለ ቃል አከበረው ማለት አካለ ቃልን አክባሪ እና አባት ፡ አካለ ሥጋን የልጅ ልጅ አብን አያት ማድረግ ነው፡፡
ይህም በሥላሴ በግብራቸው፣በባሕሪያቸው ውላጤ አለባቸው ያሰኛል፡፡ማለትም ወልድ ተወላዲነቱን ትቶ እንደ አብ ወላዲ
(አሥራፂ) እንደ መንፈስ ቅዱስ ሕይወት ማድረግ ነው፡፡

4.ተድኅሮን ያመጣል ፡- ሥጋን በርስቱ በተዋሕዶ ከበረ ካሉ በቃል ርስት እምቅድመ ዓለም (ከዓለም በፊት) አልነበረም፤
ዓመተ ምሕረትን እንጂ ዓመተ ዓለምን አልገዛም ያሰኛል፡፡

5.ሥጋን ዜገኛ (ጥገኛ) ያደርጋል፡- ሥጋን በርስቱ በተዋሕዶ ከበረ ካሉ ድሃ ከባለጸጋ ጥቂት ተቀብሎ እንዲኖር አካለ ሥጋም
ከአካለ ቃል ጥቂት ክብር ተቀብሎ ከበረ ያሰኛል፡፡ይህም ሥጋን ለቃል ዜገኛ (ተገዥ) ማድረግ ነው፡፡ ይህ ሥጋ ከቃል
ሲወሐድ ልብን ከአብ ሕይወትን ከመንፈስቅዱስ ገንዘብ አላደረገም ማለት ሥላሴን ፱ አካላት ፫ መለኮት ማድረግ ይሆናል፤

6. ተዋሕዶ ያገናዝባል ብለው “ለሊሁ ቀበዒ፣ወለሊሁ ተቀባዒ፣ወለሊሁ ቅብዕ…ራሱ አክባሪ ራሱ ከባሪ ራሱ ክብር”
ይላሉ፡፡

በሌላ አባባል ክርስቶስ ቀባዒ፣ክርስቶስ ተቀባዒ፣ክርስቶስ ቅብዕ ማለት ነው ፡፡ ዘይት ዘይትን ቀባ እንደማይባል ሁሉ
ተዋሕዶ አገናዛቢ ነውና ሥጋን በቃል ርስት ቀባዒ (ቀቢ) ቃልን በሥጋ ርስት ተቀባዒ (ተቀቢ) ማለት ግድ ነውና ማንን ይቀባ
(አጥብቅ) ራሱን ሥጋን በቃል ርስት ወሀቢ (ሰጭ) አደርገን ቃል በርስቱ ወሀቢነቱን ሳይለቅ በሥጋ ርስት ተወካፊነትን
(ተቀባይነትን) ገንዘብ ሲያደርግ ማንን ይቀበል (ገንዘቡ ያድርግ) ዳግመኛም ለሊሁ ቅብዕ ከተባለ ክርስቶስ በሥጋው ቅብዓትን
ይሻልና ክርስቶስ ክርስቶስን ተቀበለ (ተቀባ) ማለት ዓይን የጨፈነ ክህደት ነው፤ምስጢረ ተዋሕዶንም ያጎድላል፡፡ እንደዚህ
አንልም ቢሉ ባይሉም ምሥጢሩ የግድ አይሰድምና ስሕተት ነው፡፡

42
አንድም ቅብዕ እና ቅቡዕ ፣ ኀዳሪና ማኅደር፣ ጥሬና ቅጽል፣መንፈስና ቃል ስለሆኑ በስምና በግብር የተለዩ ሁለት ዓይነት
ቃሎች፣ሁለት ልዩ አካሎች ናቸውና እንኳን በግዕዝ በማንም ቋንቋ አንድ ሊባሉ በአንድ ስም ሊጠሩ አይችሉም፡፡ምሥጢረ
ሥላሴንም ያፋልሳል፡፡

ልደተ ክርስቶስ ታሕሳስ 29 ወይስ 28 ?


ልደተ ክርስቶስ መከበር ያለበት በየአመቱ ታህሳስ 29 ቀን ነው :: ከታህሳስ 29 ቀን ከፍ ወይም ዝቅ እንደማይል መጽሐፍት
ያስረዳሉ።

1. ከ81 መጽሐፍ ቅዱስ ከሚካተተው የሐዋርያት የትዕዛዝ መጽሐፍ (ድድስቅሊያ) አዘዘነ ሲኖዶስ ዘጸሐፈ ቀለሜንጦስ
ካለው ትዕዛዝ (ስምንት) ላይ በአንቀፅ 29 ልደት ሁልጊዜ 29 እንዲከበር ያዝዛል።
 ኦ ፍቁራኒሁ ለእግዚአብሔር ዕቀቡ እንከ እለተ በዓላት ቀዳሜ በአል ዘውእቱ ዕለተ ልደቱ ለክርስቶስ አመ ፳ወ፭
ለታስዕ ወርኅ በኊልቈ ሐሳበ ዕብራውያን ወበኊልቈ ሐሳበ ግብፃውያን አመ ፳ወ፱ ለታህሳስ ዘውእቱ ራብዓይ
ወርኅ ። (ዲድስቅልያ አንቀጽ ፳ ፱ ቁ ፩ - ፪ ገጽ ፪ ፻ ፳ ፱)
 እግዚአብሔርን የምትወዱ ወንድሞቼ ሆይ የበዓላትን ቀን ጠብቁ ። መጀመሪያው በዓል ይኸውም ክርስቶስ
የተወለደበት ቀን በዕብራውያን አቆጣጠር በዘጠንኛው ወር በ25ኛው ቀን ነው በግብፃውያን አቆጣጠር
በአራተኛው ወር በታህሳስ በ29 ቀን ነው ።(ዲድስቅልያ አንቀጽ 29 ቁ 1 - 2 ገጽ 229 )
2. ፍትሐ ነገስት በአንቀፅ 19 ሁልጊዜ በ29 እንድናከብር ያዝዛል።ይኸውም በድድስቅልያ አንቀፅ 29 በዓለ ልደትን
በግብፃዊያን በ4ኛው ወር በ29ኛው ቀን አክብሩ በማለት የሚገኘው ነው።
 ድስቅ ፳ወ፱ቱ ኦ አኃውየ ተዐቀቡ በዕለተ በዓላት ዘውእቱ በዓለ ልደቱ ለእግዚእነ ወግበሩ አመ ፳ወ፭ሱ ለታስዕ
ወርኅ ዘዕብራውያን ዘውእቱ አመ ፳ወ፱ዑ ለራብዕ ወርኅ ዘግብፃውያን ።
(ፍርሐ ነገስት አንቀጽ ፲ ፱ ቁ ፯ ፻ ፳ ፮ ገጽ ፻ ፹ ፫ )
 ድስቅ 29 ወንድሞቼ ሆይ በበዓላት ቀን ተጠበቁ ይኸውም የጌታችን በዓለ ልደት ነው ። በዕብራውያን በዘጠንኛው
ወር በ25ኛው ቀን አድርጉ ይኸውም በግብፃውያን በአራተኛው ወር በ29ኛው ቀን ነው ።
(ፍርሐ ነገስት አንቀጽ 19 ቁ 726 ገጽ 183 )
 “ወይግበሩ በዓለ ልደቱ ለእግዚእነ በዕለተ ተወልደ በበዓመት አመ ፳ወ፱ ለወርኀ ታህሳስ እስመ ውእቱ ርእሰ
በዓላት ” (አዘዘነ ሲኖዶስ ዘመጽሐፈ ቀለሜንጦስ ካለው ትዕዛዝ ስምንት ላይ)
 “የጌታችን በዓለ ልደት በተወለደበት ዕለት በየአመቱ ታህሳስ 29 ቀን አድርጉ(አክብሩ) እሱ የበዓላት ርእስ ነውና”
(አዘዘነ ሲኖዶስ ዘመጽሐፈ ቀለሜንጦስ ካለው ትዕዛዝ ስምንት ላይ)
አስተውሉ የግብፃዊያን እና የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ተመሳሳይ ነው፤ ይኸውም መስከረም አንድ ቀን ነው ።
ከመስከረም ጀምሮ ቆጥሮ በግብፃውያን በአራተኛው ወር ታህሳስ 29 አለ ። ዕብራውያን የተባሉ እስራኤላውያን ናቸው ።
የእነርሱም የዘመን መለወጫ መጋቢት 5 ቀን ነው ።(ከግብፅ ባርነት ነፃ የወጡበትን የቂጣ በዓል(ፋሲካ) ምክንያት
በማድረግ የዘመን መለወጫ ስለሚያከብሩ ነው)። ከመጋቢት 5 ጀምሮ ቆጥሮ በ 9ኛው ወር ታህሳስ 25 አለ ።
3. ሊቁ የኔታ ገ/ስላሴ አወቀ በፈለገ ጥበብ መፅሔት መግረሬ ፀር በሚል አምድ ስር ልደት በ28 እንዲከበር ያደረጉ መናፍቃን
ሚናስና እንድራኦስ ናቸው ብለዋል።

43
ፈለገ ጥበብ መጽሔት 1993 ዓ/ም መግረሬ ፀር
“የመድኃኒያለም ክርስቶስን በዓለ ልደት አከባበር አስመልክቶ የተጻፉ ብዙ መጽሐፍት አሉ፥ ልደተ ክርስቶስ የሚከበረው
ታህሳሥ 29 ቀን ብቻ ነው:: ታህሳሥ 29 መከበር የሚገባ ስለመሆኑ ብዙ መረጃዎችን መጥቀስ ይቻላል፥ ሐዋርያት
በዲድስቅሊያ ጽፈዋል፥ ሰለስቱ ምእት ወስነዋል፥ በሃይማኖተ አበው ሊቃውንት ወስነዋል፥ በ28 በዓለ ልደት ፋሲካ ይሁን
የሚል አንድም መጽሐፍ የለም:: ልደተ ክርስቶስ በ29 እንዲከበር ከ29 እንደማይወጣና እንደማይወርድ የሚደነግጉ
መጽሐፍት ብዙ ናቸው:: አለቃ ኪዳነ ወልድም ተንትነው አስቀምጠውታል::

ልደት በዘመነ ዮሐንስ ታህሳሥ 28 ቀን መከበር አለበት የሚል ሐሳብ ያመጡ ሐሳዊ ሚናስና እንድራኦስ የሚባሉ
መናፍቃን ናቸው:: እነዚህ መናፍቃን ጳጉሜ ስድስት ስትሆን በዓለ ታፋልሳለች አሉ፥ አረ እንዴት አድርጋ ታፋልሳለች?፥
ጳጉሜ ስድስተኛይቱ ቀን ደግሞ የአራቱ ወንጌላዊያን ሦስት ሰዓት ሌሊት ሦስት ሰዓት መዓልት ከዮሐንስ 6 ሰዓት፣ ከማቴዎስ
6 ሰዓት፣ ከማርቆስ 6 ሰዓት፣ ከሉቃስ 6 ሰዓት በድምሩ 24 ሰዓት 1 ቀን ሆኖ በሉቃስ ትፈጸማለች:: ስድስተኛዋ ቀን ጳጉሜን
በዮሐንስ በዓላትን ታፋልሳለች ካላችሁ ግዝረት መቼ ይሁን? ጥምቀት መቼ ይሁን? ትንሳኤስ ቅዳሜን ትቶ እሁድ ይሁን?
ቢሏቸው መልስ አጡ:: መናፍቃኑ እነ ሐሳዊ ሚናስ መስሎአቸው ስለተሳሳቱ ነው እንጅ የልደት በዓል በ29 ነው:: ለዘላለሙ
አይናወጥም::

አዘዘነ ሲኖዶስ ዘመጽሐፈ ቀለሜንጦስ ካለው ትዕዛዝ ስምንት ላይ “ወይግበሩ በዓለ ልደቱ ለእግዚእነ በዕለተ ተወልደ
በበዓመት አመ ፳ወ፱ ለወርኀ ታህሳስ እስመ ውእቱ ርእሰ በዓላት ”ማለትም ቀለሜንጦስ ከጻፈው ሲኖዶስ ላይ “የጌታችን
በዓለ ልደት በተወለደበት ዕለት በየአመቱ ታህሳስ 29 ቀን አድርጉ(አክብሩ) እሱ የበዓላት ርእስ ነውና” ብሏል:: በአራቱ
አመት በአራቱ ወንጌላዊያን በ29 ቀን እንዲከበር አዝዟል:: ዳግመኛም ሐዋርያት በዲድስቅልያ በአንቀጽ 29 ሰለስቱ ምዕት
በፍትሐ ነገስት አንቀጽ 19 “አኀዊነ ተዐቀቡ በዕለተ በዓላት ዘውእቱ በዓለ ልደቱ ለእግዚእነ ወግበሩ አመ ፪ወ፭ ለታስዕ ወርኅ
ዘዕብራዊያን ዘውእቱ አመ፪ወ፱ ለራብዕ ወርኅ ለግብፃዊያን” “ወንድሞቻችን ሆይ በበዓላት ጊዜ ተጠንቀቁ እሱም የጌታችን
በዓለ ልደቱ በዕብራዊያን በዘጠነኛው ወር በ25ኛው ቀን እርሱም በግብፃዊያን በ4ኛው ወር በ29ኛው ቀን ነው” ብሏል::
የዕብራዊያን ቀን መለወጫ በሚያዚያ ነውና ከሚያዚያ ወር ጀምሮ እስከ ታህሳስ ዘጠኝ ወር አለ፥ ወሩንም የሚያብቱ
በአምስት/የአቦ/ ዕለት ነው:: እኛ ግን ከመባቻው ጀምረን ቆጥረን ነው 29 ቀን የምንለው:: እነሱ ከአቦ /ከአምስት ቀን/
ጀምረው ቆጥረው 25ኛውን አሉ:: ይህን አስተውል የኢትዮጵያዊያንና የግብፃዊያን ዘመን መለወጫ መስከረም ነውና
ከመስከረም ጀምሮ እስከ ታህሳስ አራተኛው ወር ቆጥሮ በ29ኛው አለ:: የዲድስቅሊያና የፍትሐ ነገስቱ ቃሉ ያው ነው::
(አንድ ነው) የተለያየ አይምሰልህ::

ሃያ ስምንትስ ፍትሐ ነገስት በ15 አንቀጽ “ድራረ ፆም ልደት” የልደት ዋዜማ አድርጉ “ጹሙ” አለ እንጅ በዓሉን አክብሩ
አላለም:: ይህን ፋሲካ ማድረግ ድፍረት፣አመጽ ነው:: የወንጌላዊው ማርቆስ፣ ገድለ ጊዮርጊስ ወልደ አሚድ፣ መጽሐፈ ሐዊ
እነዚህ ሁሉ በ29 አክብሩ አሉ እንጅ በ28 ቀን አክብሩ አላሉም::ሃይማኖተ አበው ዘቴዎዶጦስንም ተመልከት:: ጌታችን
ከተወለደ ጀምሮ እስኪሰቀል ወንጌላዊው ዮሐንስ ስምንት/8/ ጊዜ ውሏል በዚህ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በ29
ቀን እየወጣች ታከብር ነበር:: ሐዋርያትም በ29 ቀን ያከብሩ ነበርና ልደትን በ29 ቀን አክብሩ ብሏል:: ስድስተኛይቱ ጳጉሜን
የተረፈው ስድስት ሰዓት ስድስት ሰዓት ተሰብስቦ 24 ሰዓት ይሆናል:: ይህም በሉቃስ ይፈጸማል እንጅ ወደ ዮሐንስ
አይሻገርም:: በዮሐንስ ዕለት እንደ አዲስ አንድ ተብሎ ነው የሚቆጠረው:: ምክንያቱም 24 ሰዓቱ በዮሐንስ ብቻ የተገኘ
አይደለምና::

ጳጉሜ ስድስት በሆነችበት ዘመን በ28 ቀን አክብሩ ያለ መናፍቅ አንስጣስዮስ ንጉስ ነበርና በዚህ የተነሳ 300
(ሦስት መቶ) የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በሰማዕትነት ሞተዋል:: በደገኛይቱ ዘመን ከግራኝ በፊት
በተጻፈ ስንክሳር በ28 ቀን አክብሩ የሚል የለም:: ይህም ይታወቅ ዘንድ የደብረ ብርሃን ስላሴ ጎንደር ስንክሳር፣ ጋይንት
አንስታ ቁላ እስቴ ከሚባል ሀገር ከአንድ ቦታ ያለ ስንክሳር፣ በዘጌ መሐል ዘጌ ጊዮርጊስ ያለ ስንክሳር በ28 ቀን አክብሩ
አላሉም:: እንደዚህ የመሰሉ መጽሐፍት በየሀገሩ ቢፈለጉ አልፎ አልፎ አይታጡም:: ቅዱስ ያሬድም ተርታ በዓል ሁሉ
“ለእመ ኮነ” እያለ ሲጽፍ ትልቁ የጌታችን የልደት በዓል ግን ጳጉሜን ስድስት ሲሆን በ28 ቀን “ዮም ፍስሓ ኮነ” በል ሳይል
በ29 ቀን “ዮም ፍስሓ ኮነ” ብሎ አምልቶ አስተምሯል::

44
ጳጉሜ ስድስት ሲሆን በዓለ ልደት ወደ 28 ቀን የሚወርድ ከሆነ ግዝረትስ፣ጥምቀትስ፣ በዓለ ስምኦንም፣ የግንቦት
ልደታም ካለበት አንድ ቀን ወደ ኋላ መውረድ አለባቸው ማለት ነው:: ጥምቀት ጥር 11 ቀርቶ ወደ ጥር 10፣ ትንሳኤ እሁድን
ትቶ ቅዳሜ መከበር ነበረበት ማለት ነው:: በዓላት ሁሉ ወደ ዋዜማ በወረዱ ነበር ማለት ነው:: ለዚህ ቅዱስ ጳውሎስ
“ወባሕቱ አንትሙ አሠረዚአነ ትልው አንትሙሰ መልአክ እምሰማይ ለእመ መሀረክሙ ካልአ እምዘ መሀርናክሙ ውጉዝ
ለይኩን” “እናንተ ግን የእኛን ፍለጋ ተከተሉ፣ እናንተ ስ መልአክ ስንኳ ከሰማይ ወርዶ እኛ ካስተማርናችሁ ትምህርት ሌላ
ቢያስተምራችሁ ውጉዝ/የተለየ/ ይሁን” ብሏል:: ገላ 1፥8 የእነዚህን መጽሐፍት ቃል መጣስ ድፍረትና ክህደት ነውና በጥንቱ
ትምህርትና ስርዓት ጸንቶ መኖር ነው::“ሰላመ እግዚአብሔር የሃሉ ምስሌክሙ ወያብርህ አዕይንተ አልባቢክሙ”
“የእግዚአብሔር ሰላም ከእናንተ ጋር ይሁን ዓይነ ልቦናችሁንም ያብራ::አሜን::”” ይላል::

4. ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሁለተኛ እጨጌ የነበሩት አቡነ ፊልጶስ ስለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አከባበር
በዘመኑ ከነበረው ንጉሥ ከዓፄ አምደ ጽዮን ሰይፈ አርእድ ጋር የተጋደሉበትን የገድላቸው ዜና

ሰይጣን ንጉሡን ብዙ ሴቶችን እንዲያገባ፣ በጌና እለትም አርብና ረቡዕን ጠዋት እንዲበላ አሳሳተው፡፡ ጳጳሱ አባ ያዕቆብም
ይህን እንዳያደርግ ባወገዘው ጊዜ ወደ ሐገሩ ወደ ምድረ ግብፅ ያሳድደው ዘንድ መከረበት፡፡ ጳጳሱ አባ ያዕቆብም ሁሎችንም
ማህበረ ካህናት እና ከአባታቸው ከአቡነ ፊልጶስ ጋር አሥራ አንዱን መምሕራን ሰብስቦ “የጌና በዓልን ምክንያት በማድረግ
አርብና ረቡዕ ጠዋት በነግህ እንብላ ከሚሉአችሁ ዓላውያን ጋር አንድ አትሁኑ” አላቸው፡፡ ሰባት የጧፍ መብራቶችም
እንዲበሩ ተደረገ፡፡ አቡነ ያዕቆብም “መብራቱን እያበራ እያጠፋ ቃሌንና የወዳጄን የአባ ፊልጶስን ቃል ብትተላለፉ እንደነዚህ
መብራት እግዚአብሔር ያጥፋችሁ፡፡” እያለ ቃል አሳደረባቸው፡፡ ሁሎችም ማሕበረ ካህናት ከመናፍቃንና ከዓላውያን
እንደማይተባበሩ ሰባቱን የጧፍ መብራቶች ሰባት ጊዜ እያበሩ ሰባት ጊዜ እያጠፉ በጳጳሱ ቃል ታመኑ፡፡

ሁለተኛም ንጉሡ እጨጌ ፊልጶስን “በጌና እለት አርብና ረቡዕ ጠዋት መስዋዕት ሠርተህ ቅዳሴ ቀድሰህ ሥጋ ወደሙ
አድርግ” አለው፡፡ አባታችን ፊልጶሰስም “ስለምን? በምንስ ሕግ ይህን እሠራለሁ?” አለው፡፡ ንጉሡም “የጌታችን የኢየሱስ
ክርስቶስ ልደት ዛሬ ነው” አለው፡፡ አቡነ ፊልጶስም መለሰ፤ “ጌታችን ሁለት ቀን ነው የተወለደን? እኛ ግን ያለአንዲት እለት
ሁለት ቀን ተወለደ አንልም፤ ይችውም እለት በምእመናን ሁሉ የታወቀች ታህሳሥ 29 ቀን ናት፤ በየዓመቱም የልደትን በዓል
ስናከብር በየአመቱ ይወለዳል እያልን አይደለም፤ ለአዳምና ለዘሩ መድኃኒት ይሆን ዘንድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሁለት
ወገን ድንግል ከምትሆን ከቅድስት እመቤታችን በሥጋ የተወለደበት የልደት በዓል መታሰቢያ እንዳይረሳ ነው እንጂ፡፡ “ንጉሥ
ሆይ የልደት ገሐድ በሆነበት ይኸውም ጌና መሥዋዕት ሠርታችሁ በነግህ ጠዋት ቀድሳችሁ የልደትን በዓል አድርጉ፤ ሥጋንም
በመብላት ደስ ይበላችሁ፡፡” አልክን? የሐዋርያት ሕግስ በዛሬይቱ በጌና እለት እና በጥምቀት ዋዜማ የገሐድ እለት ስለሆኑ
እንደ ጾመ ኢየሱስ እንደ “አርባው ጾም” እንዲጾሙ፤ ሥጋን ከመብላት፣ ወይንንም ከመጠጣት፣ ቁርባንንም በነግህ ከማድረግ
መታቀብ እንደሚገባ ታዝዛለች፤ እኔ ይችን የሐዋርያትን ትእዛዝ ትቼ ያንተን ትእዛዝ በፍጹም አላደርግም፡፡” አለው

ሦስተኛም ንጉሡ ምሉዓ ሞገስ አቡነ ፊልጶስን “አንተ ሁልጊዜ የንጉሡን ትእዛዝ ታቃልላለህ፤ ሁሎችም የቤተ ክርስቲያን
አለቃዎችና ሹሞች ከእኔ ጋር አንድ ሁነዋል፤ አንተ ብቻ ግን እምቢ አልክ፡፡” አለው፡፡ ተወዳጅ እጨጌ አቡነ ፊልጶስም
“በእለተ ጌና ጠዋት እንብላ፣ ሥጋና ወይን እንመገብ ብዬ በዚህ ከአንተ ጋር አንድ አልሆንም፡፡ ስለሃይማኖት ስደትን
እመርጣለሁ፡፡ የወደድከውንም በእኔ ላይ አድርግ፡፡” አለው፡፡

አራተኛም ንጉሡ አቡነ ፊልጶስን “ዛሬ ቃሌን አትሰማምን? ስለጌና በዓል አከባበርም ከእኔ ጋር አንድ አትሆንምን”
አለው፡፡ አባታችን ፊልጶስም ንጉሡን “መጽሐፍ ʽዛሬ እንብላ እንጠጣ፤ ነገ እንሞታለን፤ʼ ከሚሉ አሕዛብ ጋር አንድ አትሁኑ፤
ክፉ ነገር በጎውን ዋጋ ያጠፋልና ለእውነት ትጉ፤ ነገር ግን አትሳቱ፡፡ያለውን አልሰማህምን”? አለው፡፡ ዳግመኛም አባታችን
እጬጌ ፊልጶስ እንዲህ አለ፤ “በዓላትን ምክንያት በማድረግ ጾምን እነዳትሽሩ እንግዲህ ትጉ፤ ለመነኮሳት ነፍሳቸው
ከሥጋቸው ሳትወጣ በዓል የላቸውምና፡፡”

45
አምስተኛ ጳጳሱ አባ ያዕቆብ ከሄደ በኋላ ሌላ አባ ሰላማ የተባለ ጳጳስ መጣ፡፡ በንጉሡና በአቡነ ፊልጶስ መካከል ሰላም
እንዲፈጠር አሰበ፡፡ አቡነ ፊልጶስም “የጌናን በአል ምክንያት በማድረግ አርብና ረቡዕን ሻሩ ስላለን በዚህ ተለያይተናል፡፡”
አለ፡፡ አባ ሠላማም “ይህንስ እኔም አልቀበል፤ የተወገዘ ነውና፡፡” አለ፡፡

ስድስተኛ ያን ጊዜ ካህናተ ደብተራ ባንድነት ተነስተው ጳጳሱን “አባታችን ሆይ የልደት በዓል የሚከበረው እንደ
ዕብራውያን እና እንደ ጽርህአውያን አቆጣጠር ታህሳሥ 25 እንደ ግብጻውያንና እንደ እንደ አግዐዝያን /ኢትዮጵያውያን/
አቆጣጠር ታህሣሥ 29 እንደሆነ አታውቅምን? ስለዚህ የልደትን በዓል በእለተ ጌና አናከብርም ብለናል አሉት፡፡ አቡነ
ፊልጶስም “የእኛ አና የግብጻውያን አቆጣጠር አንድ ነው፡፡ እናንተ ለእኛ በዓለ ልደት ታህሣሥ 29 እንደሆነ ምስክሮች
ናችሁ፡፡ እብራውያንና ጽርህአውያን በታህሣሥ 25 ልደትን ያከበብራሉ ያላችሁት በዓሉን አክብረው ካለፉ በኋላ ያለ
አንዲት ቀን ተመልሶ ዓመቱ ሳይደርስ በ29 ሁለተኛ ቀን አያከብሩም፡፡ ያለአንዲትም ቀን ሁለት ቀን አያከብሩም፡፡ እኛም
በ29 ብቻ እናከብራለን እንጂ በአንድ አመት ሁለኛ ቀን በ28 አናከብርም፡፡”ብለው ቅዱሱ አባታችን አቡነ ፊልጶስ
አብራርተው ተናግረውታል፡፡ ይህ ቃል ከአርብና ከቅዳሜ ገድለ ፊልጶስ ላይ ይገኛል፡፡ አቡነ ፊልጶስም ስለዚሁ ምክንያት
የጣሉት ንጉስ አምደ ጽዮን ሰይፈ አርእድ ይባላል፡፡(ገድለ ፊሊጶስ የአርብና የቅዳሜ)

5. በቆዝሞስ ዘመነ መዋዕል ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ጳጳስ ሹሞ ሰዶ በነበረበት ጊዜ ከግያኖሳውያን ወገን የሚሆኑ ህዝባዋያን
መለኮሳት የሀሰት ወረቀት ይዘው ወደ ኢትዮጵያ መጡ። አንዱም የተላከውን ኤጲስ ቆጶስ አልተሾመም የተሾመው ይህ ነው
ብሎ አንደኛው ወረቀቱን ለንጉሱ ሰጠው።ንጉሱም ተቆጥቶ የተሾመውን ጳጳስ አጋዘው። አሰተኞች ግያኖሳውያን እንደ
አባታቸው ሳይሾሙ ቅስና ዲቁና ይሾሙ ጀመር። ቆዝሞስ ይህን ሰምቶ የግዛት ወረቀት ፅፎ ለንጉሱ ላከ።ንጉስም የክታቡን
ቃል ተመልክቶ በቁጣ ተነስቶ ሁለቱን በሰይፍ ቀጣቸው። የፊተኛውን ጳጳስ ከተጋዘበት ሞቶ ተገኘ። በዚህም ምክንያት
ከቆዝሎሞስ እስከ ፊላታዎስ ኢትዮጵያ ያለ ጳጳስ ኖረች።ሆኖም በሸዋ መንግስት ዘመን ከግያኖሳውያን ተምረው በኢትዮጵያ
የተለያዩ ምንፍቅና በመፅሃፍ ላይ መቀየጥ ጀመሩ። ይህም
1) ወልድ ቅብዕን በግብረ ህማማት ላይ
2) ልደት በ28 እና በ29 በስንክሳር ላይ
3) ክርስቶስ በስጋ በመንፈስ ቅዱስ ከበረ የሚለው ውጉዝ ይሁን የሚለውን በሃይማኖተ አበው
ይህን ሁሉ ምንፍቅና ለንጉሱ አፄ አምደ ፅዮን አስተማሩ። ንጉሱም ልደትን በ28 አክብሩ ብሎ አዋጅ ነገረ።ቀድሞውኑ
የአባቱን ምስት አግብቶ አኖሪዎስ ቢያወግዘው ሰብኣ ደብረ ሊባኖሶችን አሳዷቸው ስለነበር እጨጌ ፊልጶስ እኛ በ28 ልደትን
አናከብርም፣ አርብ ወይም እሮቡ በሚውልበት ጧት አንቀድስም፣ የእኛ ስርኣት አይደለም የፅርእ ስርኣት እንጂ አናደርገውም
አለ። በዚህም ሰበብ አሳደደው። ልጁም ሰይፈ አርእድ ሁለተኛ በልደት ሰበብ አሰደዳቸው።

6. አቡሻኽር ወልደ አቤል ሄሬም በአንቀፅ 38 በእፎኬ ይደሉ ከመናብዕል ወንብላዕ በዕለተ ዘኢወለደት ቦቱ
ድንግል(ድንግል ባልወለደችበት ዕለት ለምን እንበላለን ብሎ በ28 ቀን እንዳይበላ ደንግጓል።)

7. መ/ር ልዑል ቃል እሸቱ የእምነት አደራ በሚለው መጽሐፋቸው በ28 ማክበር ያስጀመሩ መናፍቃን ሚናስና እንድራኦስ
የተባሉ ሶሪያዊያን ናቸው ብለዋል።

8. አቡነ ጎርጎርዮስ በ28 መከበር የተጀመረው በ1298 ዓ/ም ነው ብለው ያንኑ 29ኙን መያዙ ይሻላል ብለዋል(የኢትዮጵያ
ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ቁ.2)::
 እስከ 1298 ዓ/ም ድረስ ልደት ሁልጊዜ ታህሳስ 29 ቀን ከነበረ አባቶቻችን ሐዋርያት ተሳስተዋል ልትሉ
ነውን?

46
9. ሃይማኖተ አበው ዘቴዎዶጦስም ጌታችንም ከተወለደ ጀምሮ እስኪሰቀል ወንጌላዊው ዮሐንስ 8 ጊዜ ውሏል በዚህም
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በ29 እየወጣች ታከብር ነበር ይላል።

 ይቤ ቅዱስ ቴዎዶጦስ ኤጲስ ቆጶስ ዘእንቁራ ውስተ ድርሳኑ ዘደረሰ በእንተ ልደቱ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ አመ
፳ወ፱ ለወርኀ ታህሳስ (ሃ. አበው ዘቴዎዶጦስ ፶ ፫ ፥ ፩)
 ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በታህሳስ 29 ቀን ስለመወለዱ በተናገረበት አንቀጽ የእንቁራ ኤጲስ ቆጶስ ቴዎዶጦስ
እንዲህ አለ ።(ሃ. አበው ዘቴዎዶጦስ 53 ፥ 1)

ልደት ረቡዕና ዓርብ ቢውልስ መብላት ይቻላልን?


አቡነ ጎርጎርዮስ ዘሸዋ ስለ በዓላትና አፅዋማት ላይ ስለ ገሀድ ፆም በጻፉት አምድ ላይ ገሀድ ያለው ለጥምቀት ብቻ ነው
ብለዋል:: ፍትሀ ነገስት ደግሞ እንዲህ ይላል:-
1. ረሥጣ 28 ልደት በፆም ቀኖች ረቡዕና ዓርብ ቢውል ይጸልዩ፤ ስጋውና ደሙን ይቀበሉ፣እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ
ይጹሙ ብለው አይፍረዱ :: (ፍትሐ ነገስት አንቀፅ 15 ቁ 587)

2.ዳግመኛም በየሳምንቱ ሁሉ ዓርብና ረቡዕን መፆም ነው በዓለ ሃምሳ የልደትና የጥምቀት በዓል የተባበሩባቸው ጊዜ ካልሆነ
በቀር እንደተፃፈው እስከ 9 ሰዓት ድረስ ይጹሙባቸው:: (ፍትሐ ነገስት አንቀፅ 15 ቁ 566)

3. “....የልደትና የጥምቀት ዋዜማ ፆም(ገሀድ)”:: (ፍትሐ ነገስት አንቀፅ 15 ቁ 567)

4. የአርብንና የረቡዕን ጾም ግን ከልደት ፣ ከጥምቀት ፣ ከበዓለ ሃምሳ በቀር ዘወትር ይጹሙ ።

(ፍትሐ ነገስት አንቀፅ 15 ቁ 603)

ስለዚህ ታህሳስ 29 ቀን የልደት በዓል እና ጥር 11 ቀን የጥምቀት በዓል በዕለተ ዓርብና ረቡዕ ቢውሉ ይበላል::የዋዜማው
ግን ገሀድ አላቸው::

ታህሳስ 28 ለማክበር የሚጠቅሷቸው ምክንያቶች እና መልሶቻቸው


ሀ. ግዕዘ ህፃናት እንዳይፋለስ ይላሉ:-

ግዝረቱስ ለምን ከጥር 6 ወደ 5 አልወረደም ፤ ጥምቀትስ ለምን ከጥር 11 ወደ ጥር 10 አይወርድም እዲሁም ሌሎች
በዓላትና አፅዋማትስ ለምን ወደ ዋዜማ አይወርዱም? እርሱ ግዕዘ ህፃናትን አያፋልስምን ፤ ክርስቶስ ሲወለድ ይኖራልን? ፤
የኢየሱስ ክርስቶስ ልደታት ደግሞ ሁለት ናቸው:: እነርሱም:- ቅድመ አለም ከአብ ያለ እናት እና ድህረ አለም ከቅድስት
ድንግል ማርያም ያለ አባት ይህም በዘመነ ማቴዎስ ታህሳስ 29 ቀን ዕለተ ሠሉስ ነው:: ልደትን የምናከብረው የጌታችን
የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት ቀን ስለሆነ እንደ መታሰቢያነት እናከብረዋለን እንጂ በየአመቱ ይወለዳል ብለን
አይደለም ::

ለ. በዘመነ ዮሐንስ ጳጉሜ 6 ስለምትሆን:-

6ኛዋ ጳጉሜ የአንዱ ወንጌላዊ ብቻ ሳትሆን ከ 4ቱ ወንጌላዊያን የ6 ሰዓት አስተዋፀኦ የተውጣጣች 24 ሰዓት(1 ቀን) ስትሆን
በሉቃስ ትፈፀማለች እንጅ ወደ ዮሐንስ አትሻገርም፤ የወንጌላዊው ቀመር (ዐውደ ዕለት፣ዐውደ ዓመት፣ጥንተ ዖን፣ዐውደ
ወርኅ) መሰረት የሚያደርገው መስከረም አንድን(1) ብቻ እንጅ ጳጉሜ 6 ን አይደለም።

47
ከሆነችስ ለልደት ብቻ ተፈጠረችን? ሌሎች ድሜጥሮስ በፀሎት እንዳይፋለሱ ያደረጋቸው በዓላትን (ዕርገት፣ትንሳኤ፣
ጰራቅሊጦስ የመሳሰሉትን) አያፋልስምን ወይስ እስከ 13ኛው ክ/ዘመንስ ጳጉሜ አልነበረችምን? ምሁራንስ አልነበሩምን?
ወይስ እስከ 13ኛው መቶ ክ/ዘመን ጳጉሜን የሚያገኛት ጠፍቶ ነውን ?

ሌላው ከየወንጌላዊው የምትተርፍ ትንሽ የጊዜ ልኬት (ካልዒት) አለች፤ ይቺ ተጠራቅማ ከ600 አመታት በኋላ አንድ ቀን
ትሆናለች፤ ያኔም ጳጉሜ 7 ትሆናለች ፤እንግዲህ ያኔ ልደትን ታህሳስ 27 ቀን ልታከብሩ ነውን ?

ሐ. በዕለተ ምርያ ምክንያት:-

ምርያ ማለት ትክክል ማለት ነው ስለሆነም ሁሌ ጳጉሜ በጨረሰበት ቀን ልደት ይውላልና አንድም በሶስቱ ወንጌላዊያን
ነሀሴ በዋለበት ቀን መስከረም ይውላልና (ነሀሴ 1 እሑድ ቢውል መስከረም 1 እሑድ ይውላልና)። በዘመነ ዮሐንስ ግን አንድ
ቀን ስለሚሻገር ሰግር ይባላል(ነሀሴ 1 እሑድ ቢውል መስከረም 1 ሰኞ ይውላል)።

የሰግር ጉዳት ነሐሴ የዋለበትን ዕለት መስከረም እንዳይውልበት ማድረግ ነው። ስለዚህ ምርያ ማጭበርበሪያ እንጅ
ምስጢርነት የላትም። ምርያስ ከ13ኛው ክ/ዘ በፊት አልነበረችምን?

ጾመ ነቢያት የሚገባው ህዳር 19 ፣15 ወይስ 16 ?


ይህ ፆም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ይወርዳል፤ይወለዳል ብለው ነቢያት የፆሙት ፆም ሲሆን ነብያት በሙሉ ከ40 ቀን በላይ
አልፆመምና ፆሙ 40 ቀን 40 ሌሊት ነው፤ ጾመ ሙሴ ፵ መዓልተ ወ፵ ሌሊተ እንዳለ። 40 ቀን የሚሆነውም ፆሙን ህዳር
19 ስንጀምር ነው ። ከነቢያት በኋላ የነበሩት ቅዱሳን አባቶቻችንም እስከ 980 ዓ.ም ድረስ የፆሙት 40 ቀን ነው:: ነገር ግን
በ980 ዓ.ም አካባቢ የነበረው አብርሃም ሶሪያዊው ሦስት ቀን በመፆም ተራራውን አንቀሳቅሦ ከመናፍቃን ህዝቡን ያዳነባት
ፆም ስለሆነ ከ 40 ው ፆም ጋር የአብርሃም ሶሪያዊው ሦስት ቀን ፆም ተጨምራ እንድትፆም ራሱ አብርሃም አዝዟል እንጅ
ቅ/ሲኖዶስ አልወሰነም ።

እኛም ይህን መሰረት በማድረግ የነቢያትን ፆም ከህዳር 19 እስከ ታህሣሥ 29 በመፆም 40 ቀን ነው እንላለን:: ነገር ግን
በፆም ምክንያት ጠብ ክርክር ቢሆን መጾም ይገባል ከመብላት በጣም ይሻላል (ፍትሐ ነገስት አንቀጽ 15 ቁ 584) ብሏልና
ይህችን የአብርሃምን ፆም(3 ቷን ) ቀን በመጨመር ከኅዳር 16 ጀምረን እስከ ታኅሣሥ 29 ቀን ድረስ (40 ውን ፆም 43/44
አድርገን እየፆምን እንገኛለን )እንፆማለን:: ያልፆሙትን ግን መናፍቃን እያሉ መሳደብ ተገቢ አይደለም። ምክንያቱም በሲኖዶስ
አልተደነገገችም በአንድ ጳጳስ ትዕዛዝ ነው እንጅ።

መቼ ይጀመር በሚለው ግን ስምምነት የለም፤አንዱ ወገን በ15 ሲል ሌላው በ16 ይላል፤በዮሐንስ በ14 ይጀመራል የሚሉም
አሉ ምናልባት እርሷም ግዕዘ ህፃናትን ታፋልሳለች ተብሎ ይሆን፥አንዳንዶች ፍትሐ ነገስት አንቀፅ 15 ቁ 568 መንፈቁ ለኅዳር
ስለሚል በ16 መጀመር አለበት ይላሉ፤ለመሆኑ ፍትሐ ነገስት የተፃፈው መቼ ነው ጾሟን ጳጳሱ ካዘዘ በኋላ አይደለምን?

ጾመ ሐዋርያት
ጾመ ሐዋርያት ሐዋርያት በበዓለ ጰራቅሊጦስ መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላ የፆሙት ፆም ነው ። ይህን ፆም በተዋህዶ
ከበረ የሚሉ ወገኖች ከጰራቅሊጦስ ማግስት ይጀምራሉ ። በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከበረ የሚሉት ደግሞ ከጰራቅሊጦስ
በኋላ 7 ቀን ዘግይተው ይጀምራሉ ። በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከበረ የሚሉት ምን ይዘው ዘግይተው ጀመሩ ?

48
1. ስንክሳር ዘግንቦት 18 ሐዋርያት 40 ቀን ፆሙ ይላል፤
 በአዲስ ቋንቋም ተናገሩ ለጌትነቱ እጅ መንሻ ሊሆን አርባ ቀን ጾሙ ።(ስንክሳር ዘግንቦት 18 ቁ 7 ገጽ 297)

ጥንተ ትንሳኤ መጋቢት 29 ቀን ነውና ጥንተ ጰራቅሊጦስ ግንቦት 18 ቀን ይሆናል፤ሐዋርያት ከግንቦት 19(ከጰራቅሊጦስ
ማግስት) ጀምሮ ፆሙ ብንል 47 ቀን ፆሙ ያሰኝብናል፤ይህም የስንክሳሩን ቃል (40 ቀን ፆሙ) የሚለውን ያፈርስብናል። እኛ
ግን ሌላ 7 ቀን በዓል አደርጉ ስለሚል ጾሙን ግንቦት 26 ጀምረን ሐምሌ 5 ሲጨርሱ 40 ቀን ይሞላል፤40 ቀንስ አይሞላም
ቢሉ መዐልት ይስሕቦ ለሌሊት ወሌሊት ይስሕቦ ለመዐልት ነውና 40 ቀን ሞላ ይባላል አንድም ቅዳሴው ውሎ መሆን አለበት
ይላሉ፡፡ አሁን ግን በድሜጥሮስ ቀመር ሲሰላ ከ40 ቀን ከፍ ወይም ዝቅ ሊል ይችላል፤ሆኖም ቀመሩ የ7ቷን ቀን ርዝማኔ
ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ስለማይችል ልዩነቱ ለውጥ አያመጣም። በኋላ የመጡና የፍትሐ ነገስት ቃል ያልተመቻቸው ሰዎች
ግን ለፍትሐ ነገስቱ በስርዋፅ መልክ ማስተካካያ እየሰጡ ይገኛሉ። ሠረፀ-ገባ ፣ ሥርወጽ -አዲስ የገባ ማለት ነው። ጥንተ
ስቅለት(ጌታ የተሰቀለበት ቀን) መጋቢት 27 ቀን ፣ጥንተ ትንሳኤ መጋቢት 29 ቀን፣ ጥንተ ዕርገት ግንቦት 8 ቀን፣ ጥንተ
ጰራቅሊጦስ ግንቦት 18 ቀን ስለሆነ ነው።

2. ፍትሐ ነገስት አንቀጽ 15 በዓለ ሃምሳን ከፈፀማችሁ በኋላ ሁለተኛም ሌላ 7 ቀን በዓል አድርጉ ከዚያም ከአረፋችሁ
በኋላ ጹሙ ። ይህ ሲባል ግን ጾመ ድኅነት(ዓርብ እና ረቡዕ ) አይጀምርም ማለት አይደለም ። በዚሁ አንቀጽ ላይ በዚህ
ሳምንት እንዲጀመር ያዝዛልና ። በሌላ አንቀጽም ግብረ ሕማሙን ያልጾሙ ይችን 7 ቀን እንደ ቀኖና ይጹሟት ይላል ።

 በዓለ ሃምሳን ከጨረሳችሁ በኋላ ዳግመኛ ሰባት (7) ቀን ሌላ በዓል አድርጉ ከዚህም ቀጥሎ ከአረፋችሁ በኋላ
ጹሙ ።(ፍትሐ ነገስት አንቀጽ 15 ቁ 580)
 ከዚህም ቀጥሎ ከበዓለ ሃምሳ ቀጥሎ ያለ የሐዋርያት ጾም ነው ፋሲካውም በጴጥሮስና በጳውሎስ በዓል ሐምሌ
አምስት ቀን ነው ።(ፍትሐ ነገስት አንቀጽ 15 ቁ 569)
 ዳግመኛም የሰሙነ ሕማማትን ሥራ ሳይሰራ ላለፈበት ከበዓለ ሃምሳ በኋላ ስለእርሷ መጾም መስገድ ይገባ ዘንድ
ታዘዘ ። ከበዓለ ሃምሳ በኋላ የሚውለው ሳምንት ይህ ቢሆን ኖሮ ከ ሃምሳ ቀኖች በኋላ ይበሉበት ዘንድ የሚገባ
ቢሆን እንደገና ብሉበት በተባለ ነበር ። በዓል አድርጉ ማለቱ ግን በዓል ዓድርጉ ከማለት በስተቀር ብሉበት
አላለምና ።ሥርዋጽ ይህስ በውስጡ ያሉትን የአርብንና የረቡዕን ጾም ያስረዳል ።እነርሱንም ይፈጽሟቸው ዘንድ
አያስረዳም እነሆ ባስልዮስና አፈወርቅ እንዲህ አሉ ። በዓል ማክበር በመብል አይደለምና ። ዳግመኛም በጾም
በዓል ማክበር እንዲገባ የታወቀ ነው ። ይኧውም ለበአሉ የሚስማማው እንዲነበብ ነው እንጅ ሊበሉበት
አይደለም።(ፍትሐ ነገስት አንቀጽ 15 ቁ 582 – 583 ፡ ቁ 588)

3. የጾመ ሐዋርያት ተውሳኩ ስንት ነው? ለምን? እንዴት?


የጾመ ሐዋርያት ተውሳኩ 6 ነው ። ምክንያቱም ከጾመ ነነዌ እስከ ጾመ ሐዋርያት ድረስ ያለው የቀን ርዝማኔ(የቀን ልዩነት)
126 ቀን ነው ። 126 ን ለ 30(በአንድ ወር ብዛት ) ስናካፍለው 4 ቀሪ 6 ይሆናል ። ቀሪው ተውሳክ ተብሎ ይወሰዳል ።
ተውሳክ ማለት ወሰከ = ደመረ ፣ ጨመረ ከሚለው የግእዝ ግስ የተወሰደ ሲሆን መደመሪያ መጨመሪያ ማለት ነው ። ነነዌ
ከዋለበት ቀን ላይ እየተደመረ በዓላትን ለማውጣት ይጠቅማልና ። ለምሳሌ ነነዌ ጥር 29 ቀን ቢውል ጾመ ሐዋርያት
የሚውልበትን ስናሰላ 29 + 6 = 35 ፡ 35 ፥ 30 = 1 ቀሪ 5 ይሆናል ። ቀሪዋን እንወስድና ጾመ ሐዋርያት ሰኔ 5 ይሆናል ።

በተዋሕዶ ከበረ የሚሉ ወገኖች ግን ጾሙን የጰራቅሊጦስ ማግስት ለማስገባት ከጾመ ነነዌ እስከ ጾመ ሐዋርያት ድረስ ያለው
የቀን ርዝማኔ(የቀን ልዩነት) 119 ቀን ነው ይላሉ ። ተውሳኩንም 119፥30 =3 ቀሪ 29 ብለው 29 ያደርጉታል ።ይህም ስህተት
ነው ምክንያቱም ጾመ ሐዋርያት የጰራቅሊጦስ ማግስት እንደማይገባ ከላይ ስላየን ነው ።በ 119 እና በ 126 የ 7 ቀን ልዩነት
መኖሩን አስተውሉ ። ለበለጠ ባህረ ሐሳብን ያንብቡ።

49
አንዲት ጥምቀት
ጥምቀት ከማይደገሙት ምሥጢራተ ቤተ-ክርስቲያን አንዷ ናት፡፡ ስለዚህ ወንድ ልጅ በተወለደ
በ40 ቀኑ ሴት ልጅ በተወለደች በ80 (ማለትም አዳም እና ሄዋን ገነት በገቡበት ምሳሌ) የልጅነት ጥምቀትን ከተጠመቁ በኋላ
ሁለተኛ ጥምቀት የለም ፡፡ለዚህም፡-

 አሐዱ እግዚአብሔር ወአሐቲ ሃይማኖት ወአሐቲ ጥምቀት ።(ኤፌ ፬ ፥ ፭)


 አንድ ጌታ ፣ አንድ ሃይማኖት ፡ አንዲት ጥምቀት (ኤፌ 4÷5)
 ወካዕበ ይቤ ወተቀበርነ ምስሌሁ በጥምቀተ ሞቱ (ከእርሱ ጋር በጥምቀት ተቀበርን) ዳግመኛም እንዲህ አለ ወከመ
ኢይትከሀል ዳግመ ይስቅልዎ ለክርስቶስ ወኢትካሀሎ ለሞት ይሰልጥ ላህሌሁ ( ክርስቶስን ዳገምኛ ይሰቅሉት ዘንድ
እንዳይቻል ዳግመኛም ሞት ይሰለጥንበት ዘንድ አይቻለውም……..) እስመ ዘይጠመቅ ዳግመ ይፈቅድ ይስቅልዎ
ዳግመ በእንቲአሁ (ዳግም እጠመቃለሁ የሚል ሰው ምሳሌው ስለሆነ ጌታን ዳገመኛ ይሰቅሉት ዘንድ ይወዳሉና)፡፡
ወእመሰ ከመዝ ወእቱ ኢይትካሀል ይሙት ዳግመ (ጥምቀት ስቅለት ከሆነ ሁለተኛ ይጠመቁ ዘንድ አይገባም)፡፡
ወሶበ የረትዕ ዝንቱ ከመ ይጠመቁ ዳግመ ይደሉኬ ከመ ይጠመቁ ሥልሰ ወርባዐ(ሁለተኛ ጥምቀት የሚገባ ከሆነ
ሦስተኛ ሊጠመቁ ይገባል፡፡ሦስተኛ ጥምቀት የሚገባ ከሆነ አራተኛ ሊጠመቁ ይገባል)፡፡ እስመ ለቀዳማዊ ይነስቶ
ደኀራዊ(የመጀመሪያውን ጥምቀት የሁለተኛው ጥምቀት ያፈርሰዋልና፡፡)ሥልሰ ላለው ወለደኀራዊ ይነስቶ
ካልዑ(የሁለተኛንም ጥምቀት የሶስተኛንም ጥምቀት ያፈርሰዋልና።) ርብዐ ላለው፡፡ ወለዘከመዝሰ አልቦ
ፍፃሜ(ለእንደዚህ ያለው ጥምቀት ፍፃሜ የለውም፡፡እንደ ቱቻ ሲነከሩ መኖር ነው እንጂ ። )
(ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 9 ቁ 197 – 247 ገፅ 211 – 214)
 አሐቲ ሃይማኖት ወአሐቲ ጥምቀት እንበለ ርስሐት ከመዝ እስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ዱ መለኮት
እንበለ ፍልጠት ።(ሃ.አበው ዘሳዊሮስ ፹ ፬ ፥ ፳ ፪)
 ሃይማኖት አንዲት ናት ኃጢአትን የምታስተሰርይ ጥምቀትም እንዲህ አንዲት ናት ፡፡ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ
ያለመለያየት በመለኮት አንድ ናቸው፡፡(ሃ.አበው ዘሳዊሮስ 84 ፥ 22)
 ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኃጢአት ።(ጸሎተ ሃይማኖት /መሠረተ ሃይማኖት/ )
 ኃጢአትን በምታስተሠርይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን ። (ጸሎተ ሃይማኖት /መሠረተ ሃይማኖት/ )
 ወዘንተ ባህቱ አእምሩ ኩልክሙ ከመ እለ ተጠመቅነ በእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ውስተ ሞቱ ተጠመቅነ ወተቀበርነ
ምስሌሁ ውስተ ጥምቀት በሞቱ ከመ በከመ ውእቱ ክርስቶስ ተንስአ እም ሙታን በስብሐተ አቡሁ ከማሁ ንህነኒ
ናንሶሱ ውስተ ሓዳስ ሕይወት ።(ሮሜ ፮ ÷ ፫ - ፬)
 ወይስ ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ የተጠመቅን ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደ
ተጠመቅን አታውቁምን? እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት
እንድንመላለስ፥ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን።(ሮሜ 6 ÷ 3 - 4)

አንድ ጊዜ መጠመቃችን ምሳሌ አለው ፡፡ ይኸውም አንድ ጊዜ በውሃ መጠመቃችን በክርስቶስ ሞት አንድ መሆናችን
ነው፡፡ ከውሃውም መውጣታችን ሁለተኛ ከእርሱ ጋር የመነሳታችን ምሳሌ ነው፡፡

ከዚህም የተነሳ የልጅነት ጥምቀት እንደማይደገምና ከዚህም አልፎ አንድ ሰው ከተጠመቀ በኋላ ወደ አረማዊነት ገብቶ
ቢመለስ እንኳ የሚያስፈልገው የንስሐ ጥምቀት (ቄደር) ነው ብለው አባቶች ደንግገዋል፡፡ እስመ ዘይጠመቅ ዳግመ ውእቱኬ
ዘረስኣ ሀብተ ጸጋ ዘቀዲሙ (ሁለተኛ እጠመቃለሁ የሚል ሰው በመጀመሪያው ያገኘውን ፀጋ ክብር የነቀፈ አንድም የዘነጋ
ስለሆነ ነው)ወአበሰ አበሳ ምኑነ (የተናቀ በደል የበደለ ስለሆነ ነው፤ጌታን ሁለተኛ ይሰቀልልኝ የሚል ስለሆነ ነው፡፡) ወዘይገብር
ከመዝ ይከውን ከመዘያምን በካልእ ጥምቀት (እንዲህ የሚያደርግ ሰው በሌላ ጥምቅት እንደሚያምን ሰው ነው)፡፡

50
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ታሪክ (አንዲት ኦርቶዶክስ
ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅባት ፣ ፀጋ እና ካራ ተብላ መከፋፈል )
1.የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያደረገችው ተፅዕኖ፤ —ዓፄ
ቴዎድሮስና ጳጳሱ አቡነ ሰላማ በኢትዮጵያ ባሉት የካቶሊክ ሚሲዮን መሪዎች ላይ የደረጉት ተቃውሞ — በኢትዮጵያ
የጸጋዎች ውድቀት የካራዎች መንሰራራት፡፡

………በአምስተኛው መቶ ምዕት በኬልቄዶኑ ጉባኤ ከክርስቶስ በሁለትና በአንድ ባህርይ ልዩነት የተነሳ የሮማ የካቶሊክ
ቤተክርስቲያን እና የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን በጠብ ከተለያዩ ወዲህ የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የኢትዮጵያን
ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከእስክንድርያ ገንጥላ ወደ ራሷ ለማድረግ በየዘመኑ ያልተቆጠበ ጥረት አድርጋለች።

በ16ኛው ምዕተ ዓመት ላይ በቱርኮችና በአረቦች የተደገፈው የአህመድ ኢቭን ኢብራሂም ህልቂት በፈጸመበት ዘመን ንጉሱ
ልብነ ድንግል የፖርቱጋል ንጉሥን የጠየቁት እርዳታ በልጃቸው በአፄ ገላውዲዎስ ደርሶ የግራኝ አህመድ ወረራ በፖርቹጋሎች
ትብብር ከተደመሰሰ በኋላ የሮማ ቤተ ክርስቲያን ባለስልጣኖች የፖርቱጋል መንግስትን ተገን ይዘው ይህም መንግስት
ላደረገው ውለታ ዋጋ በመፈለግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ወደ ካቶሊክነት እንድትለወጥ እርዳታውን
በመጣው በዣብ ቤርሙዴዝ አማካኝነት አጥብቀው ያዙ፡፡

ወጣቱ ገላውዴዎስም ምንም እንኳ የፖርቹጋል መንግስት ያደረገውን ወታደራዊ እርዳታ ከፍተኛ ግምት ቢሰጡትም በዚህ
እርዳታ ምክንያት የሐይማኖት ለውጥ ቢያደርጉ በግራኝ ዘመን የነበረው ሁከት እንደሚመለስ በማመን የቤርሙዴዝ ሀሳብ
ሣይቀበሉ ቀሩ፡፡ በዚሁ ጠብና ክርክር ተፈጥሮ እርሱም በንዴት ወደ ሀገሩ በ1559 ዓ.ም ከተመለሰ በኋላ በ1575 ዓ.ም
ሞተ፡፡

ቀጥሎም በሮማ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ዮልዮስ ሦስተኛ እና የፖርቹጋል ንጉሥ ዮሐንስ ሦስተኛ ተመካክረው የቤርሙዴዝን
ሀሳብ ወደ ፍጻሜ ለማድረስ ከርሱ በትምህርት የጠለቀና በዘዴኝነት የታወቀውን ሮድሪጎ ጎንዛሊስ ከእርሱም ቀጥሎ
ከኢየሱሳውያን ማህበር (Jesuits) እና አንድርያ ኦቪዮዶ ተመርጠው መጡ፡፡እነዚህም በ1567 ዓ.ም መጥተው መልካም
መስተግዶ ከተቀበሉ በኋላ ኢትዮጵያ ወደ ካቶሊክነት እንድትለወጥ ባቀረቡት ልዩ ልዩ ጥያቄ እና ክርክር ንጉሡም
ሊቃውንቱም የሚገባ መልስ እየሰጡ ሳይቀበሏቸው ቀሩ፡፡ ዓፄ ገላውዴዎስ በአንድ ወገን በምጥዋ በኩል ቱርኮች ስለተነሱና
በሌላ ወገን እነዚህ ሚስዮናውያን በሚያቀርቡት ክርክር መካከል ተቸግረው እንደነበረ ታሪከ ነገስት በደንብ ዘግቦት ይገኛል።

ነገር ግን እነዚሁ የኢየሱሳውያን ማህበር አባሎች በአንድ ጊዜ የኢትዮጵያን ቤተ ክርስትያን ለሮማ ቤተ ክርስትያን ተገዥ
የማድረጉ ነገር ቢስትም ባለፈው የፖርቹጋል ንጉሥ ባደረገው ውለታ ምክንያት በኢትዮጵያ ተቀምጠው እንዲያስተምሩ
ስለተፈቀደላቸው፥ እነርሱም በኢትዮጵያ ተቀምጠው እያደር በዘዴም፥ በስብከትም ሃይማኖታቸውን ሲያስፋፉ ቆዩ ።
አሳባቸውም በመጨረሻ በአፄ ሱስንዮስ ዘመን(1599-1624 ዓ.ም) ግቡን ለመምታት ቀረበ፡፡

“አልፎንሱ ሜንዴንዝ ”የሚባለው የኢየሱሳውያኑ ሹም የዓፄ ሱስንዮስን ባለሟልነት እያደር በማግኘት ኤትዮጵያም
ካቶሊክ ብትሆን የምታገኘውን አውሮፓዊ እርዳታ እያመለከተ በመጨረሻ ንጉሱ ራሳቸው የካቶሊክን ሃይማኖት
መቀበላቸውን አስታውቀው ሕዝቡም የእርሳቸውን አርአያ እንዲከተል አወጁ ።ቅጣት የፈራው ፣ ሹመትና ባለሟልነት
የፈለገው ሲቀበል የቀረው መኳንንትና ካህናት ከለሕዝቡ እምቢ ስላለ ባገር ውስጥ ከፍ ያለ ጦርነትና ሁከት ተነሳ ፡፡ የገዛ
እንደራሴያቸውና አማቻቸው ራስዮልዮስ(የልጃቸው የወይዘሮ መለኮታዊት ባል ) ከአቡኑ ከአባ ስምዖን ጋር በጦርነቱ ላይ
ሞተ ፡፡ ከእነዚህም ጋር ብዙ ሕዝብ ለንጉሱ ታዛዥ በሆነው ወታደር እየተመታ አለቀ ።

በመጨረሻም የሕዝብን አነሳስ በጦር ሃይል መደምሰስ አስቸጋሪ ስለሆነ እርሳቸውም ከዚህ የሃይማኖት ለውጥ የተነሳ
ሁከቱም ዉጣ ውረዱም ስላደከማቸው ሕዝቡን አሸንፈው የባዕዱን ሃይማኖት በማስገባት ፈንታ ራሳቸው ተሸንፈው
“ፋሲል ይንገስ ሃይማኖት ይመለስ” የሚል ቃል ወርውረው ብዙም ጊዜ ሳይቆዩ በ1625 ዓ.ም በታህሳስ ወር አርፈው

51
ልጃቸው ፋሲል ስመ መንግስታቸው ዓለም ሰገድ ተብሎ ነገሡ ፡፡ በዚህም ጊዜ በዓፄ ፋሲል ዘመነ መንግስት ደግሞ አጥቂና
ተጠቂ ሥፍራ ለሥፍራ ተለዋውጠው በያለበት የተደበቁት የካቶሊክ ሚስዮናዊያን እየተያዙ በስቅላትና አንገት በመቆረጥ
ተቀጡ ።

በዚህም ዘመን ከአበሾቹ እነ አባ ያእቆብ በቤጌምድርና ከፈረጆቹ ደግሞ ምንሴፔርዶ ቼኮቢስ ዋና ዋናዎቹ የካቶሊክ
ሰባኪዎች ነበሩ፡፡በኋላ ደግም የውጭ ሀገር ተወላጆች በግድ እንዲወጡ ሲገደዱ እነ አባ ገብረ-ሜካኤል ተወላጆቹ በእሥራት
እንዳሉ ሞቱ፡፡ በዚህም መካከል የአንድ የቤተ ክህነት አባባሎች “ቅብዓት፣ ጸጋ፣ ካራ” በመባል ለሦስት ተከፍለዋል፡፡
ቅብዓቶች ክርስቶስ በመቀባት ማለትም በሰውነቱ የባሕርይ አምላክ ሆነ ይላሉ፡፡ እነርሱም በጎጃም ክፍለ ሀገር አብዛኛዎቹ
በደብረ ወርቅ ደብር ነው የሚገኙበት፡፡ ጸጋዎች ደግሞ ሦስት ልደት ክርስቶስን የጸጋ ልጅ ሆነ ይላሉ፡፡ የዚህ ክፍል አማኞች
በንጉሥ ሣህለ ሥላሴ ከተማ በአንኮበርና በሌሎችም ቦታዎች ይገኛሉ፡፡ ካራዎች ክርስቶስ በሰውነቱ የባህርይ አምላክ ነው
የሚሉት በተዋሕዶ ብቻ ከበረ በእነሱ ግእዘኛ አባባል “ወልደአብ ወልደ ማርያም በተዋሕዶ ከበረ” ይላሉ፡፡ እነዚህም
የተሠራሩበት በአፄ ቴዎድሮስና በአባ ሰላማ ጊዜ ነው፡፡ አባ ሰላማና ቴዎድሮስ በአንድ የካራዎች መስመር ለማስጓዝ ያላደረጉት
ጥረት የለም ነበር፡፡( ምንጭ ፦ ተክለ ፃዲቅ መኩሪያ አፄ ቴዎድሮስ የኢትዮጵያ አንድነት ገፅ 149- 156)

2. በቦሮ ሜዳ ላይ በተደረገው ክርክር ጸጎችና ካሮች ተከራክረው ማለትም ጸጎች ሦስት ልደት ፣ ካሮች ደግሞ ሁለት ልደት
በማለታቸው ከመጽሐፍ ጠቅሰው (ወነአምን ፪ተ ልደታተ) ሃ.አበው ረተዋቸዋል፡፡ በዚህ ቅብዓቶች እንደሌሉ ያስረዳል፡፡
(ምንጭ ፦ተክለ ፃዲቅ መኩሪያ፥አፄ ዮሐንስ የኢትዮጵያ አንድነት ገፅ 197)፡፡

3. በንግድ ምክንያት አንድ ሰው እስክንድሪያዊ(ግብፃዊ) መስሎ በኢትዮጵያ ይኖር ነበር፡፡ ይህ ሰው እንዲህ ሲል ተናገረ፤
እናንተ ኢትዮጵያውያን ቃል ስጋን በለበሰ ጊዜ በማህፀነ-ማርያም መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ የባህርይ
ልጅ የባህርይ አምላክ ሆነ ትላላችሁ፡፡ በማህፀን መንፈስ ቅዱስን ሲቀበል ያየው ሰው የለም፤ ሮማውያን እስከ 30 ዓመት
በሰብአዊ ግብር ኖሮ በዮርዳኖስ ወንዝ ላይ በተጠመቀ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ሰው ሁሉ እያየው በርግብ አምሳል በራሱ ላይ
ስላረፈበት የጸጋ አምላክ ሆኖ የአምላክነት ስራ ከአባቱ ከአብ ጋር ተካከለ ይላሉ፡፡ ስለዚህ ከእስክንድርያ ሃይማኖት የሮማ
ሃይማኖት ትሻላለች አለ ይባላል፡፡ (ምንጭ፦ መድሎተ አሚን ከመልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ መቅድም ገጽ 15 )

ልብበሉ፡- ኢትዮጵያ ቀደም የምታምነው ወልድ በሰውነቱ በመንፈስ ቅዱስ ከበረ ብላ እንደሆነ ይህ ኢ-አማኒ(ሮማዊ)
መስክሯል፡፡ ይህም እነቅዱስ ቄርሎስ በሃ.አበው ምዕ 73፥49 ከተናገሩት ጋር አንድ ነው፡፡

4. ፋሲልም መዓልም ጴጥሮስ የተባለውን የካቶሊክ ሰባኪ በንግድ እንደመጣ በምፅዋ በር በኩል ሸኝታ ሰጥተው ሰደዱት
ምፅዋ አካባቢ ሲደርስ እነዚህ ደንቆሮ ሊቃውንቶች “ነሳአ፣ ተወክፈ”(ያዘ፣ ተቀበለ) ይላል፡፡ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ምን
አደረገው ቢሏቸው አያውቁትም አላቸው፡፡ ሸኝታዎችም ተመልሰው ያላቸውን ለአፄ ፋሲል ነገራቸው፡፡ አፄ ፋሲልም ነሳአ፣
ተወክፈ ይላል መጽሐፍ በብዙ አንቀጽ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ምን አደረገው ትላላችሁ? አሏቸው፡፡ ገሚሶቹ መንፈስ
ቅዱስን ተቀብሎ የፀጋ ልጅ ሆነ አሉ፤ እነዚህ ጸጎች ተባሉ፡፡ ገሚሶቹ ደግሞ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ በማህፀነ ማርያም
በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ የባሕርይ አምላክ የባሕርይ ልጅ ሆነ አሉ፤ እነዚህም ቅብዓቶች ተባሉ፡፡ ገሚሶቹ ደግሞ እንደ
ጥምቀቱ እንደ ሞቱ ተቀበለው እንጅ አልጠቀመውም አሉ፤እነዚህ ካሮች ተባሉ፡፡ መንፈስ ቅዱስን ከወልድ የለዩ ካሮች
(በተዋሕዶ ከበረ የሚሉት) ናቸው፡፡(ምንጭ፦ መድሎተ አሚን ገጽ 292 ) ከገጽ 277 ጀምረው ያንብቡ ።

5. ከብላቴን ጌታ ኅሩይ ዋዜማ በተባለው መጽሐፍ በዘመነ መሳፍንት የመጣው ቄርሎስ የተባለው ጳጳስ የጎንደር ሊቃውንት
በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ የባሕርይ ልጅ የጸጋ ልጅ በመበበል ሲከራከሩ ቢያገኛቸው ወልድ ቅብዕ ለሊሁ ቀባዒ ወለለሁ
ተቀባዒ ብሎ ለጎንደር ሊቃውንት የማይስማማ ትምህርት አስተማረ ብለዋል፡፡ (ምንጭ፦ መድሎተ አሚን)

6. ወልድ ቅብዕ (ካራ) በተዋሕዶ ከበረ የሚል አስተምሮ የትም የሌለ የፈጠራ ስራ ነው፡፡ይህም ጊዜ ሰጥቶት በአፄ
ቴወድሮስና በሣልስ ሰላማ እንደተስፋፋ ብዙ የታሪክ መጽሐፍት ይናገራሉ፡፡ (ምንጭ አቡነ ጎርጎርዮስ -የኢትዮጵያ ቤተ

52
ክርስቲያን ታሪክ፣ተክለ ፃዲቅ መኩሪያ፣ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣መድሎተ አሚን፤የመንግስት ሃይማኖት እንደሆነ በህገ መንግስት
ድጋፍ ያገኝ እንደ ነበር ያስረዳል፡፡)

7. ከአቡነ ዮሳብ ቀጥሎ ጳጳስ ቄርሎስ(መናፍቁ) መጣ፣ በዘመኑ ራስ ወልደ ስላሴ የትግራይ ገዢ፣ ራስ ጉግሳ የቤጌምድር ገዢ፣
ዕጨጌ መምህር ወልደዮና ነበሩ፡፡ጎንደር እንደ ደረሰ ቅብዓትና ጸጋን አወገዛቸው መንፈስ ቅዱስ ቅብዕ አይደለም ክርስቶስ ራሱ
ቀቢ ራሱ ተቀቢ ራሱ ቅብዕ ነው ሲልም ተናገረ፡፡በዚህ ምክንያት ካህናት ሁሉ በንጉሥ ኢዮአስ ፊት ለመከራከር ወሰኑ፡፡ ንጉሱ
ኢዮአስ የጳጳሱን አባባል በመደገፍ ላይ ነበር፡፡ (ምንጭ ፦ገብረ ዮሐንስ ገ/ማርያም-የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ታሪክ ክፍል ፪)

8. ከላይ ከተራ ቁጥር ፫፣፭ እና ፯ የሚያመለክተው ወልድ ቅብዕ ከመባሉ በፊት ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ታምን የነበረው መንፈስ
ቅዱስ ቅብዕ በማለት እንደሆነ ነው፡፡

9. After death of the ABUN KARIIOS about 1828 Ethiopia remained without a bishop until the
appointment of ABUN SLAMA (3rd) in 1841 the new bishop was a young energetic who had
attended protestant collage in CAYRO. (ምንጭ ፦ ከሣልስ ሰላማ ታሪክ የተወሰደ)

ወልድ ቅብዕ (በተዋሕዶ ከበረ-ካራ) የተስፋፋው በአጼ ቴዎድሮስና ሣልስ ሰላማ ዘመን በመሆኑ በዚህ ዘመንም በዙ
ሊቃውንት ሃይማኖቴን አለቅም በማለት እነ አባ አሥራተ ማርያም ዘደብረ ማርቆስ፣እነ አባ ወልደ ሚካኤል ዘመርጡ
ለማርያም እና ሌሎችም ብዙ ሊቃውንት ከበአታቸው(ከጸሎት ቤታቸው) እየወጡ እንዲገረፉ ተደርጓል፡፡

10. “Yohannis never applied the flexibility and liberalism he showed in the
field of politics over religious. In religion he sought complete unity as the
guiding principle. He thus ended the century – old religious divisions within
the Orthodox Church at the council of Borumeda in may 1878. Yohannis
gave state support to the upholders of the karrra haymanot (Two Births)
camp.”( ምንጭ፦ከ 12ኛ ክፍልየታሪክ መጽሐፍ ገፅ 62 የተወሰደ)

ዛቲ ሐይማኖት መሢሐዊት ዘትትአመን በአሐቲ ቤተክርስትያን ቅድስት


ስብሐት ለሥሉስ ቅዱስ
ወለእሙ ቅድስት
ወለመስቀሉ ክቡር
ይቆየን አሜን

ከሙሉዓለም ጋሻው(ገ/ማርያም) /ኦሪት/


ሰኔ 12 ቀን ፣ 2009 ዓ.ም

53

You might also like