Professional Documents
Culture Documents
አንሱ፣
ምጡን እርሱ።
%
ወልደው ሳያበቁ
በሰው ልጅ አይስቁ።
%
ሥራን ሲፈልጉ፣
ጉልበትን አያባልጉ።
%
አህያን ሥጋ ጭነህ፣
ጅብን ንዳ ብለህ።
%
አንዱ ባንዱ ሲስቅ፣
ጀንበር ጥልቅ፤
%
የአፍ ዘመድ፣
ከገበያም አይገድ።
%
የጉም ሌባ!
ጉሙ ሲለቅ የት ትገባ?
%
ባለጌና የቆቅ አውራ፣
ያለበትን ያወራ።
%
የበደለ ይካስ፣
የቀማ ይመልስ።
%
የተደረገላትን ረድኤት ትታ፣
የተሠራላትን ውለታ ዘንግታ፣
%
ወደሽ ከተደፋሽ
ቢረግጡሽ አይክፋሽ።
%
የኃጥኡ ዳፋ፣
ጻድቁን ያዳፋ።
%
ሀሰተኛ ሲናገር ይታወቃል፣
ስስታም ሲበላ ይታነቃል።
%
ጊዜ አለው ለሰው፣
ዕድሜ ካላነሰው።
%
በምክራቸው ተጎዱበት፣
በሰይፋቸው ተመቱበት።
%
ባፍ ይጠፉ፣
በለፈለፉ።
%
ብናስር እናጠብቃለን፣
ብንመታም እናደቃለን።
%
ውሸት ዓለምን ዞሮ፣ በመጨረሻ ወደ ዋሾው ይመለሳል።
-- የአባቶች ምሣሌ
%
ሥነ ጹሁፍ ሁለት ጊዜ የሚነበብ ኪነጥበብ ሲሆን ጋዜጣ ግን አንድ ጊዜ ብቻ ታይቶ የሚታለፍ ነው።
-- ሳይረል ኮኖሊይ
%
ታሪክ የሌሊት ቅዥት ስለሆነ በእርሱ ቀስቃሽነት እነቃለሁ።
-- ጄምስ ጆይስ
%
ታማኝነት እንደትሮይ የምስጢር መሣሪያ ነው።
-- ሎርድ ኪኒዮር
%
ማየቱን ታያለህ፣ ግን አትገነዘብም
-- ሰር አርተር ዶየል
%
በተሰጥኦ የምንጠቀመው ከመቶው በአንዱ ብቻ ነው።
በብርቱ ጥረት ግን ዘጠና ዘጠኝ ከመቶውን መሸፈን እንችላለን።
%
እንኳንስ እናቴ ሞታ፣ እንዲሁም ለቅሶ ለቅሶ ይለኛል።
%
ጆሮ ለባለቤቱ ባዕድ ነው።
%
ድል አድራጊነት የሚገኘው ገምቶ ከመነሳት ከፍላጐትና እነዚህን በተግባር
ለማሣየት ከሚደረገው የአሠራር ስልት ነው።
-- ዊልያም ፔን
%
ዘለሰኛ፦
ጐበዝና ፈሪ፣ ሁለት መልክ ይዘሽ፤
ጥርስሽ ሰው ገደለ ከንፈርሽ ሲሸሽ።
%
ዘለሰኛ፦
ያባቴ ነው ብሎ፣ ይፋጃል በርበሬ፤
%
ዘለሰኛ፦
ለኔ የት ታወቀኝ፣ ወዳጄስ ጠላቴ፤
እንዲያው ኡኡ፣ ሲባል ሁሉም መጡ ደጄ።
%
መዲና፦
የማናውቀውን ሌብነት፣
ልንሠርቅ ገብተን ከሰው ቤት፣
ይቅርብህ ጓዴ እንውጣ፣
የሚጠብቀን መጣ።
%
መዲና፦
ጠላ ጠምቄ ለሰንበት፣
አንስቼው ነበር በቡይት፣
ዞሬ ባየው አጣሁት፣
-- ከመልካም መዓዛ
%
ሠይጣን ሠለጠነ
%
ግዛኝ ግዛኝ ብለው ሊሸጠኝ አሰበ።
%
በሬ ካራጁ ይውላል።
%
አትረፍ ያለው መነኩሴ መቁጠሪያውን ሸጦ ፍየል ይገዛል።
%
ጊዜ መስታዎት ነው
%
ጐበዝ ይሙት ፈሪ ይኑር ቢሻው፣
አተላ መሸከም ይችላል ትከሻው።
%
ከቶ ለምን ይሆን ፈሪ ማጦንጦኑ፣
ቅጠል አይበጠስ ካልደረሰ ቀኑ።
%
ቢያዝኑለት ያለቅስ፣
ቢስሙት ይነክስ።
%
በወሰኑት ፍልሚያ ተረቱ፣
በቆረጡት አርጩሜ ተመቱ።
%
በቅሎ እንዳሰገሩት፣
ሎሌ እንደነገሩት።
%
በተለሙ ያርሷል፣
በጀመሩ ይጨርሷል።
%
ባጭር ታጥቆ፣
ጋሻ ነጥቆ፣
ዘገር ነቅንቆ፣
ይዋጓል አጥብቆ።
%
ግፈኛማ ባሪያ፣ ምን ነፅነት አለው፤
የሰው ልጅ ነፃነት እልቡ ውስጥ ነው።
ዋና አውቃለሁ ብዬ እንዲያ ስፎክር፣
ሀገሬ ምን ይለኝ ጠልቄ ብቀር?
%
ሁሉ በሽተኛ ሁሉ ራሴን ባይ?
በቤታችን ደህና መጥፋቱ ነው ወይ?
-- ከብላቴን ጌታ ማህተመ ሥላሴ አማርኛ ቅኔ የተወሰደ
%
እሾህ አጣሪውን፣
ነገር ፈጣሪውን።
%
ማሩን አመረረ፣
ወተቱን አጠቆረ።
%
ግፍ ሲናኝ
ኩበት ሰጥሞ ድንጋይ ይዋኝ።
%
ከመጠን በላይ በመሥራቱ የሞተ ሰው መኖሩን አላውቅም። ነገር ግን ከጭንቀት ብዛት ብዙ ሰዎች ሞተዋል።
-- ዶ/ር ቻርለስ ማዩ
%
ከምንም ነገር የበለጠ ደስታ የሚሰጠን የምንመቀኛቸው ሰዎች ችግር ላይ ወድቀው ማየት ነው።
-- የጀርመኖች ምሣሌ።
%
የነፃነቶች እናት የሆነው የፕሬስ ነፃነት ቁጥጥርና እግድ የሚደረግበት በፈላጭ ቆራጭ መንግሥት ብቻ ነው።
-- ጆርጅ ማስን
%
ያደግሁባት መሬት፣
ማነው ሜዳ ናት ያላት፣
ልናገር እኔ የማውቃት፣
አገሬ ጋራ ናት።
%
ተፈረደብህ ብዙ ዓመት
በራስሕ ጥፋት እሥራት፣
የኔ ወንጀል ቢቀልም፣
በወሬ አልፈታም።
%
ንጉሥ የሰጡኝ ታላቅ ዕቃ፣
ላገር ለምድር የሚበቃ፣
አድጦኝ ወድቆ እስኪሰበር፣
%
አፍ ቀለም ሲነዳ፣
ልብ ዕቃ ያሰናዳ።
%
ካልቀመሰ፣
የደገመው ባሰ።
%
የአፍ ዘመድ
ከገበያም አይገድ።
%
የኑሮህን ዕቅድ አስቀድመህ ንደፍ።
እንግዲህ በዚያ መሠረት ላይ ነው ሕይወትህን የምትመራ።
-- ማርክ ትዌይን
%
በአጋጣሚ ወም በእድል ካልሆነ በስተቀር በምድር ላይ የተሟላ ሰላም የለም።
%
ማዕረገ ቢስ፣
እራቱ ገሚስ።
%
በአፍ ይጠፉ፣
በለፈለፉ።
%
በሬ ያርሣል፣
አህያ ምርቱን ያፍሣል።
%
አስቀድሞ የተናገረን ሰው ይጠላዋል፣
አስቀድሞ ያሸተን ወፍ ይበላዋል።
%
ሥራን ሲፈልጉ፣
ጉልበትን አያባልጉ።
%
ከሰዎች መጥፎና መልካም ነገር መቀሰም ይቻላል። የተሻለውን መርጦ መያዝ ግን የኔ ፋንታ ነው።
%
ምንም ሣይኖራቸው ሁሉንም አለን ብለው ከሚኮሩና ባዶ ሆነው እራሳቸውን ምሉዕ አድርገው ከሚገምቱ ሰዎች ጋር
መኖር ሰለቸኝ።
አልበርት ኦሸዋይዘር
%
የፍትሕ ማስተባበር ተግባር የመንግሥት ጠንካራ ዋልታ ነው
-- ጆርጅ ዋሽንግተን
%
እግዚአብሔር ትክክለኛ መሆኑን ሳሰላስል ለአገሬ በጣም እሰጋለሁ
-- ቶማስ ጃፈርሰን
%
ረሀብተኛ ውሻን አንስተህ ሀብታም ካደረግኸው አይነክስህም። በሰውና በውሻ መካከል ያለው ልዩነት ይኸው ነው።
-- ማርክ ትዌይን
%
እምነትና ክብርን በማዋረድ፣ ዕውነትንም በመጣል የሚገኘው ከፍተኛ ማዕረግ ለባሹን የማያሞቅ ነጠላ ነገር ነው።
-- ጆን ቴይለር
%
ጋዜጠኛ ሊከለልበት የሚገባው ብቸኛ ጥግ ቢኖር አንድ ብቻ ነው። እርሱም «የዕውነት ጥግ»
-- ሪዚያ ባቲ (የፓኪስታን ጋዜጠኛ)
%
እንደሰው ያለ አህያ ባላውቅም፤ እንደ አህያ የሚያስቡ ሰዎች ግን አጋጥመውኛል።
-- ሄንሪክ ሄደን
%
መለመን የለመደ ምላስ፣
በሕልሙ አቆማዳ ይዋስ።
%
ከተመቱ ማንጠርጠር፣
ጅብ ከሄደ አጥር ማጠር።
%
ቂል አይሙት፣
እንዲያጫውት።
%
ቅቤና ቅልጥም
ወዴት ግጥምጥም።
%
ሣይናገር ብልሀቱ፣
ሣይታረድ ስባቱ።
%
የኃጥኡ ዳፋ፣
ጻድቁን ያዳፋ።
%
አገር ያለ ምክር፣
ቤት ያለማገር።
%
እራትና መብራት፣
አማትና ምራት።
%
የሰው እምቢተኛነት
እሣትና ነፋስ መሬትና ሰማይ፣
አየርና ውሃ በቀልትና ድንጋይ፣
እነዚህ ፍጥረቶች እግዜር የሠራቸው፣
ሳያወላውሉ ሁሉም በባሕርያቸው፣
ጠባይ እንለውጥ ታከተን ሣይሉ፣
የተሰጣቸውን ሥራ ይሠራሉ።
ደግሞ ስናስተውል በመካከላቸው፣
መዋጋት፣ መጋደል፣ ጠብም የለባቸው።
እሣት ያቃጥላል፣ ነፋስም ይነፍሳ፣
በቀልት ይመግባል ውሃውም ያርሣል፣
መሬት ስትሸከም ጠፈር ይጋርዳል፣
እግዜር ያዘዘውን ቃሉን ሲፈፅሙ፣
ለማ፣ ጠፋ፣ ብለው እያጉረመረሙ።
ተሰብረው ቢወድቁ ተቃጥለው ቢነዱ፣
ልፋታቸው በዝቶ ቢደክሙ ቢጎዱ፣
ታዝዘው ይኖራሉ ጥንት እንደተሠሩ፣
ከፈጣሪ ጋራ ሣይከራከሩ።
ሕጉን በመከተል አምኖ እንዳይታዘዝ፣ይይጎትቶ ሊያመጣ በራሱ ላይ መዘዝ፣
ይህ የሰው ልጅ ብቻ አርፎ እንዳይገዛ፣
%
አንዲቱን ቀዘባ
እንደ ሐምሌ ወራት ፊቷ ጭፍና ለብሶ፣
እንደ መኸር ድርቆሽ ልብሷ ተልከስክሶ፣
አየኋት ለየኋት እንዲቱን ቀዘባ፣
ዘንጠፍ ዘና ብላ እንደ መስክ አበባ።
ፊቷ ጭፍና ቢለብስ፣
ልብሷ ቢልከሰከስ፣
ግና ሥግው ሆኖ ውበት ተደብቆ፣
ታየኝ ተገለጠ ድንገት አሸብርቆ።
ልብሷ የባላገር አየረዋ ገጠር፣
ኩለንታዊ ውበት ይዛ የምትኖር፣
አየኋት ከመስኩ ወደ ገጠር ሄጄ፣
ተፈጥሮን ስፈልግ ተፈጥሮን ወድጄ፣
ነባይ አባይ ማለት በተፈጥሮ ቤት፣
አንዲቱ ቀዘባ አክሊል የውበት፣
ያልተዳደፈችው በሰው ሠራሽ ፈሊጥ ከንቱ ፈንደለላ፣
አየኋት ለየኋት የገጠረዋን ስንድቅ የገጠረዋን አፍላ።
-- «እስኪ ተጠየቁ»
ከሚለው ከዮሐንስ አድማሱ ግጥሞች የተወሰደ
«በውሸት» አስለቅሳችሁ።
ደካማውን አጎልብታችሁ፣
ጀግናውን ፈሪ አርጋችሁ፣
የውሸት ጨዋታ መጫወታችሁ፣
ሁላችሁም ዋሾዎች ናችሁ።
ቀለም ተመቸን ብላችሁ፣
ዓይንን በውበት አታልላችሁ፣
ቋንቋ እናውቃለን ብላችሁ፣
በቃላት ተጨዋውታችሁ።
ተደራሲን በምናብ አማልላችሁ፣
የሌለ ዓለም በመፍጠራችሁ፣
ሁላችሁም ዋሾዎች ናችሁ።
የታለ ታዲያ በእውን ያ ውብ ዓላማችሁ፣
ነፃነት ለተጠሙት፣
አርነት መች አለበሳችሁ፣
ለተጨቆነውስ ክፍል፣
ደህና ቀን መች አወጣችሁ?
የመድረኩ ላይ ጀግንነት፣
የብራና ላይ ዕውቀት፣
የሸራው የወረቀት ውበት፣
%
አትቁም ያሉት ለማኝ ከሰጡት አንድ ነው።
%
የቤቴ መቃጠል ለትኋኑ በጀኝ።
%
ሆድን በጐመን ቢደልሉት ጉልበት በዳገት ይለግማል።
%
ሲሮጥ የመጣን አህያ አህያ አጥብቀህ ጫነው።
%
ሻማ እራሱ እየተቃጠለ ለሌሎች ብርሃን ይሰጣል።
%
አንበሣና አንዲት ጥጃ ጐን ለጐን ሊያርፉ ይችላሉ። ነገር ግን ጥጃዋን ጥሩ እንቅልፍ ሊወስዳት አይችልም።
-- ውዲ አለን
%
አደባባይ ቆሞ አበጀሁ ቢላችሁ፣
ይህን ባለ ጊዜ ምን ትሉታላችሁ?
%
አይጣል፣ አይጣል እያልን ስንለምነው፣
%
ሃሣቡና ነገሩ፣
ጠባዬና ግብሩ።
%
ጥበብና ዕውቀትን፣
ማስተዋልና ዕውነትን፣
%
አጥር ጥሶ፣
ግድግዳ ምሶ።
%
መማለጃ እየበሉ፣
ወንድማቸውን እየበደሉ።
%
ደኃ አደግ
እሥር ቤት ነው የኛ ጽንሰት፣ የኛ ትውልድ ባጠቃላይ፣
የኛ ሕይወት የኛኑሮ፣ አስተዳደግ ከታች ከላይ፣
ሽብር እንጂ ሰላም አናውቅ፣ ጨለማ እንጂ ብርሃን አናይ፣
እስር ቤት ነው የኛ ደስታ፣ የኛ ፍቅር የኛ ሠናይ።
ልዩ ልዩ ድግሪ ድፋ፣ ዶክተር ተባል የምሁር ሠፈር፣
እስር ቤት ነው ያንተም እጣ፣ ያንተም ሕይወት፣ በኛ መንደር።
እረስ አምርት፣ ነግድ፣ ፍጠር፣ ሀብታም ተባል ባለፀጋ፣
እሥር ቤት ነው ያንተም ዕድል ሲቀየር አልጋ ባልጋ።
የትንናቱ ጅል ጦርነት በዘር ተቀየረ፣
ሶሻሊሽም ለኛ አልሆነም ዲሞክራሲም አልሠመረ።
ዛሬም የኛ መኖርያችን ዓለም በቃኝ ሆኖ ቀረ።
እናታችን ጀግና ፈሪ፣ ወላድ መሐን ናት ሾተላይ፣
አባታችን አንዱ ሆዳም፣ አንዱ ኮብላይ አንዱ አታላይ፣
እኛም ሕዝቦች ነን ሁሉን ቻይ፣ ነገር አድርባይ፣ ነገ ወላዋይ፣
የማርያም ልጅ እርዳን አንተ፤ አንዴ ውረድና ወይ ላክና ከላይ።
-- ከአያልነህ ሙላት
%
ሐኪሙ-ሐኪም አጣ
ያ-ዕውቀት መዘክር የትምህርት አባት፣
ችሎታውን ሁሉ በአይምሮው ይዞት፣
ዓለም አለቀሰ፣ በአስራት አሟሟት።
-- ከአለነ አሰፋ