You are on page 1of 6

ጠመኔ ያዥ

አንተ ለኔ ተስፋ አንተ ለኔ ብርሃን ውጋገን ፈንጣቂ


ለነገ ኑሮዬ ጉዞን ያመቻቸህ ህይወቴን አድማቂ
አንተ ጠመኔ ያዥ ቁጥር ያስደመርቀኝ የፉደል አባቴ
እውቀትን የዘራህ ምርትን የሰበሰብክ ገብተህ በውስጤ
ዛሬ ያገኘኸን እኔ ያንተ አዝመራ እኔ ያንተ ፍሬ
ድንቁርናን ጣልቁት ታግዬ አሸነፍኩት አንብቤ ደምሬ
አሁን አንብቡልኝ ድምሩልኝ የለም እኔው አነበብኩት
ቁጥር ከቁጥር ጋር ደመርኩት ቀነስኩት ደግሞ አበዛሁት
አንተ ድንቁርና
ትናንትና ነበርክ የኔን ማንነቴን ውስጤን ተቆጣጥረህ
ብዙ እንዳልራመድ እጅ እግሬን ጠፈረህ አምሮ ገዝተህ
አምርሬ ጠላሁህ ብዙ በደልከኝ ደግሜ ረገምኩህ
የጥላቻን በትር መምህሩ አስጨበጠኝ
ገድዬ እንድቀብርህ ጉድጓድ አሳይቶኝ
ድንገት ከተነሳህ እንደማትምረኝ
እዛው ጨለማ ውስጥ ዳግም እንደምትከተኝ
የነን ጥበበኛ ሊቁን ሰው የፈራ መምህሩ ነገረኝ
አሁንም ጠላሁህ አንተ ድንቁርና አንቅሬ ተፋሁህ
ነገም እማራለሁ በያዝኩት ዕውቀት ሌላ እጨምራለሁ
አንተ ጠመኔ ያዥ
አንተ ጠመኔ ያዥ ትናንት የፈረሰው ህይወትን ታደገ መብራት ፈጠረ
ተሽከርክሮ ፈጥኖ ድካምን ቀነሰ መንገድን ቀያስ ኒኩለርን ቀመረ
ፈላስፋው መጠቀህዋለህ አደራ ደረሰው ፃፈና ለሀገር ተዘመረ
የነዚህ መነሻ መፍለቂያቸው አንተ ጠመኔ ያዥ ነህ
ትናንት አከበርኩህ ደግሞም ዛሬ ምስጋና ይድረስህ
መንኩራኩር ሰርቶ ወደላይ ቢያቀር ምሁር ቢመረመር
መድሃኒት ቢሰራ መጥፊያና መዳኛ ሁሉም ቢቀምር
ፍጡራን ደቆ መልሶ ቢሰፋ ህይወትን ቢታደግ
እንደእንቁራሪቶች እንደአሳ ነባሪ ውቅያኖስ ቢመሸግ
ታምር የተባለ ግኝትን ቢፈጥር ለአለም ቢያበረክት
እሱስ የማን ሆኖ እሱስ የማን ግኝት
የአንተ አይደለም እንዴ የመምህርነት የዕውቀት መሰረት
ታድያ መምህሬ እስኪ ደጋግሜ አሁንም ላክብርህ
ገብተህ በአዕምሮ ብርሃን ይፈጥርሃል ምስጋና ይድረስህ
፶/አ ጌቱ ለታ
ከአውቶ መካኒክ B

የጊዜም ጀግና አለው


የጊዜም ጀግና አለው
ክፉና ምቀኝነትን ከስር ላስወገደው
ከጅቦች አምልጠው
ኢትዮጵያን ያዳነው
እኛም ለዚህ በቃን
አንድ ቀን ሰንቀን
ያን ሁሉ መከራ በውስጣችን ይዘን
ይሆናል አይሆንም በቁማችን ነቅዘን
በሽታችን ጣፍ በሃኪም ተይዘን
የጊዜም ጀግና አለው
የመከራን ቀንበር ክፉን ላስወገደው
እኛን ይበል ስማቸው እውነት ጉልበት አለው
ምሰሶችን ፈርሶ ታሪክ ተሰርዞ
ጎተኝነት ነግሶ እውነት ተመርዞ
ሀገርን ሊያጠፋ ውሸት ተጠርዞ
ዘመን ሳይጠባበቅ ሀቅ ተቀዝቅዞ
ደርሶልን እውነት በሌሊት ተጉዞ
በየቦታው ጬኸት በየቦታው ለቅሶ
ወጣት ተመርዞ በክፉ ተቀምሶ
ሰው ሰውን ሲገድል ድግስ ተደግሶ
እንባችን ታብሶ ይሄው ጊዜ ደርሶ
ሻለቃ ባሻ አንዳርጌ ዳኘው
ከአውቶ መካኒክ B
መከራ ይምከረው
በዘር በፖለቲካ በጠባብ አዕምሮ
ሕሊናውን ሽጦ በጥቅም ታውሮ
በታሪክ መሰረት የተገነባ አቅሟን
በቃለ እግዚኣብሔር የተፃፈ ስሟን
የኢትዮጵያ ክብር በሔራዊ ነፃነት
ክህደት በተሞላው ያልተገራ አንደበት
በሰው ሃገር ሆኖ ያውም በኪራይቤት
ከጁንታው ቡድን ጋር ከጠላት ወግኖ
ዳውን ዳውን አላት ባህር ማዶ ሆኖ
ለእሱ ይበለኝ እንጂ ሀገሩን ለከዳው
ታሪክ አልባ ሆኖ ክብሩን ላዋረደው
አንድ ነች ኢትዮጵያ አትቆራረስም
እንደጅምር ግንብ ለጩኸት አትፈርስም
በጀግኖች ልጆቿ አኩሪ ታሪክ ስራ
ምንጊዜም ኢትዮጵያ ትኖራለች ታፍራና ተከብራ
ታሪኳ ተፅፎ በአረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ በደማቁ ቀለም
ነገም ከፍ ብላ ትኖራለች በዓለም
ይህን ከሀዲ ጡቷን የነከሰው
አቦ ሟርተኛውን እራሱን ያፍርሰው
፶/አ አለባቸው ተረፈ
ከአውቶ መካኒክ B
ወታደር ነኝ እኔ
የሰላም ተምሳሌት ታማኝ ለወገኔ
ቃሌን የማላጥፍ ወታደር ነኝ እኔ
ለክብሯ የቆምኩኝ ምሰሶና ማገር
ግንባሬን የምሰጥ ለሀገሬ ድንበር
የህዝባችን ሰላም ደስታን የምፈጥር
በቀበሮ ጉድጓድ ጫቃ ላይ የማድር
ዋልታ ነኝ መከታ የታሪክ ምስክር
መሬቱ እንደ ፍርናሽ ድንጋዩም ትራሴ
ቅጠሉም ከለላ ሃረግ ሆነች ነፍሴ
አፈር እስኪጫነኝ እስክትውጣ ነፍሴ
ቃል አለኝ በሰማይ እያለሁ በምድር
ውዷን ባንዲራዬን ሃገሬን ላስከብር
በደሜ ጠብታ በአፅሜ የተማገርሽ
ብሄሬም ሆነ ዘሬ ሃይማኖቴ አንቺ ነሽ
እናቴ ኢትዮጵያ ቃል አለኝ ላልከዳሽ
ቁሜአለሁኝ እኔ የለም የሚደፍርሽ
ደስታሽ ደስታዬ ስትስቅ እስቃለሁ
ሲርብሽ ይራበኝ እኔም እጠማለሁ
ሲከፋሽ ያመኛል የልቤን አውቃለሁ
በክብርሽ ለመጣ ሞቴን እመርጣለሁ
የሰላም ተምሳሌት ታማኝ ለወገኔ
ቃሌን የማላጥፍ ወታደር ነኝ እኔ
፶/አ ሞላ መዝገቡ
ከ GMF
እኔ ነኝ ወታደር
ያትንኩኝ ባይ አሻራ ያበው ጥቁር ሰውልጅ
ጀግንነት እንደምንጭ የሚቀዳው ከደጅ
ለጠላቴ እረመጥ ለወገኔ ወዳጅ
ድልን ሰርቻለሁ በተሠጠኝ ግዳጅ
አረሮና ሲንባ ሠገዴ ከዳሮ
በአካል ብቃት ስልቱ ሰውነቴ ዳብሮ
ጋራው ሸንተረሩ መረቀኝ መስክሮ
ከዛ በኋላማ ታጠኩለት ለጉድ
ቦገገው አፋፍ ላይ ወነድነት ሲዋሃድ
ሠናፌን ጠቅጥቄ ጠላቴን ሳሳድድ
ያንን እፁብ ስራ ያየሁት በምዕናብ
እኔ ነኝ ወታደር እያደርኩ የማብብ
እንደ ቋያ እሳት ቢንቀላቀል ነድድ ጋሬጣ ቢበዛ መንገድ ባይመቸኝ
እኔ ምን ደንታ አለኝ ጀግንነት ውርሴ ነው ከጥንት የተሰጠኝ
ጠላቴን መትቼ እንዲያስብ ያደረኩኝ እኔ የሚያቃጥል የምፋጅ እሳት ነኝ
፶/አ ኤርሚያስ መኮንን
ከ Communication
ወይ ወያኔ ወይ ውርደት
ኢትዮጵያና ህዝቧ በአንድ ተቧደኑ
ብቻውን ታጠቀ ወያኔ ምስኪኑ
አንዳንዴ ተገዶ ለሽንፈት ሲፈጠር
በጥቅሻ ይወድቃል እንኳንስ በጠጠር




እሪታን ለብሰው አራግበው አራግበው
ግሳት የለኮሰው እሳትን አንግበው
ያነደዱት እቶን
ተንቀልቃዩ ፍመት ደርሶ ቢፈጃቸው
በል ብረድ እንብረድ ሆነ ዝማሬያቸው
፶/አ ዳኛቸው ፈንታሁን
ከአውቶ መካኒክ B
እርሳው ብሔርህን
የቱ ነው ያንተ ጎጥ
የቱ ነው ያንተ ብሄር
ስንሞት አንድ ነን ከአፈር በታች አፅም ነን
እንደ ብሔር ሳይሆን እንደ ሃገር
አስተሳሰባችን አነድ ነው
ሃገር በልማት መጥታ ማየት ህልማችን ነው
ባለ አላማ ልዩ ነን
ባለ ተስፋ ኩሩ ነን
ለመማር በተግባር ዘመናዊነትን ያነፅን
የአንዲት ኢትዮጵያ ትውልዶች
ኩሩ ነን የሃገር ኩራት
ውበታችን የአንድነት የአብሮነታችን መፍለቂያ
ብሄር ብሔረሰቦች ነን
የኢትዮጵያዊነት ኩራት መገለጫ
ከአንተ በፊት እኔነቴን
ከአበው ታሪክ የወረስን
እራሳችን አስቀድመን ፍቅርን ኩራት ያደረግን
ብሄር ቀለም ያለያየን አንድ ነን
በአንድነት የቆምን
ወታደሮች ነን እኛ ለዓላማ ዘብ የቆምን
ወታደሮች ነን እኛ ለዓላማ ዘብ የቆምን
፶/አ ዳኛቸው ፈንታሁን
ከአውቶ መካኒክ B

ከድቶሻል
ከድቶሻል ሃገሬ አድምጪልኝ ልንገርሽ
ከአፍሽ ያጎረሽው ያ ያመንሽው ልጅሽ
ሲበላ የኖረው ከማጀት ከጓዳሽ
ዛሬ ቆሞ ሲሄድ ሁሉን ነገር ሲያውቀው
ምነው እንዲህ ሆነ ማንስ አስተማረው
ማን ሲገል አይቶ ማንን ተከተለ
መቼ ተመርዞ መችሽ ደም ለመደ
ንገሪኝ ሃገሬ መች ነው ያመለጠሸ
ከጉያሽ ፈልቅቆ መች ነው የሮጠብሽ
መሬትሽ ሲታረስ ሲዘራበት ያኔ
ዘር ማለት ይሄ ነው የሰው ዘር የለውም አላልሽውም እንዴ
እናልሽ ሃገሬ
የልጅሽ ለውጡን ግዜውን ባናውቅም
የሆነው ሆነና ዛሬ አንቺን አያውቅም
ሰው መሆን እረስቶ አውሬ ሆኖልሻል
ሰው በላ አራዊት ቤተሰብ አፍርቷል
ልንገርሽ እምዬ ልጅሽ እረስቶሻል
ከአንድ ሆድ የወጣን ወንድሙን ይደፋል
እናም ባንቺ መሬት የደም ጎርፍ ይወርዳል
እናት ማቅ ለብሳለች ልጇቿም ታርደዋል
ልጅም እናት የለው እንባው ደርቆልሻል
በይ ስሚኝ ሃገሬ አድምጪኝ ልንገርሽ
ከድቶሻል ያልጅሽ
አንቺ እንደው ሃገሬ ክፉ ነው አትይም
የእናት ሆድሽ ችሎ ገፍተሸ አጥይውም
ግና እናት አለሜ ልጅሽ ማለት ይህ ነው
እውነታው ይሄ ነው የእናት ጡት ነካሽ ነው
፶/አ ዳኛቸው ፈንታሁን
ከአውቶ መካኒክ B

ዳግም ቃል ገብተናል
ይለፍ ይረግጥ ዳንኪራ
ኢትዮጵያዊ ሁሉ ይደሰት ይኩራራ
ለአንድነት ቃል ገብተናል በህብረት ልንሰራ
አብረን እንገስግስ ከዘመኑ ጋራ
ገበሬው ከማሳው ሁሉም በየሙያው
ወዛደሩ ሳይቀር ላፍታ ከፋብሪካው
ቀን ከሌሊት መስራት ነው የድህነት መፍቻው
በእጥረት ብቻነው ሀገር የምትለማው
የሀገር መከታ ዙሪያውን ጠባቂ
አኩሪ ጀግኖች አለን ጠላት አስጨናቂ
በየመሸገበት አንገቱን አናቂ
ሠላም የሰነቀ እድገትን ናፋቂ
እምየ ምድርሽን ጠላቶች ቢራቡ
ከሰሜን ከደቡብ ከምስራቅ ከምዕራቡ
አይሆንላቸውም ከንቱ ነው ሃሳቡ
የጀግኖች ዳር ድንበር ይፋጃል ወሰኑ
በእብሪት ተውጠው ጀግናን የደፈሩ
ትዕግስት ባይገባቸው እነሱ አፈሩ
ጥቃት የማይወደው ከትውልድ ከዘሩ
ድንበር ላይ ስላለ የጦር ሜዳ ሃገሩ
ሠላምሽን ገፎ ውድቀትሽን የሚሻ
የጀግናው ሞት አለ የትቤት ማርከሻ
በየአጋጣሚው ተመስክሮለታል
ድንቁን ብቃታችን ህዝቡ አውቆለታል
ይበልጥ ልንሰራም ዳግም ቃል ገብተናል
፶/አ ዳኛቸው ፈንታሁን
ከአውቶ መካኒክ B

You might also like